Telegram Web Link
ብፁዕ አቡነ እስጢፋኖስ በጂማ ከተማ በፀጥታ አካላት ተወስደዋል።

በነገው ዕለት አዲስ ሕንጻ ቤተ ክርስቲያን በጂማ ከተማ ለማስመረቅ የተለያዩ ሊቃነ ጳጳሳት እና የመምሪያ ኃላፊዎች ጋራ ዛሬ ጠዋት ለመሄድ አዲስ አበባ አየር መንገድ ተገኝተው ነበር።

ከእነዚህም መካከል ብፁዕ ዶ/ር አቡነ ጴጥሮስ፣ ብፁዕ አቡነ ኤልያስ፣ብፁዕ አቡነ ናትናኤል፣ ብፁዕ አቡነ ኤርምያስ ሲገኙ ሌሎች እንግዶች ሊቀ ትጉሃን ቀሲስ ታጋይ ታደለ፣ ንቡረ ዕድ ኤልያስ፣ ሊቀ አእላፍ ቀሲስ በላይ መኮንን፣ሊቀ ማእምራን ፋንታሁን ሙጬ፣ ሊቀ ትጉሃን እስክንድር ገ/ክርስቶስ ይገኙበታል።
አየር መንገድ ሲደርሱም የሀገረ ስብከቱ አባት ይበቃሉ በማለት ቀሲስ ታጋይ አብረው እንዲሄዱ በመፍቀድ ሌሎች አባቶችና እንግዶችን ከጉዞ መልሰዋቸዋል።

ጂማ ከተማ አየር ማረፊያ ሲደርሱ በፀጥታ አካላት የተያዙ ሲሆን የያዟቸው አካላትም ከክልል የደረሰን አቅጣጫ ነው ማለታቸው ተሰምቷል።

በተመሳሳይ ዜና ሕገ ወጡን ሹመት ትተው ይቅርታ ጠይቀው የተመለሱት መጋቤ ብሉይ ወሐዲስ አባ ጸጋ ዘአብ አዱኛ ታፍነው መወሰዳቸው ተገልጿል።

ዝርዝሩን እንደደረሰን እናቀርባለን።

ማኅበረ ቅዱሳን

ሌሎች መረጃዎች እንደደረሱን እናቀርባለን።
👍26
ኦርቶዶክስ ተዋህዶ - ‌🇴‌🇷‌🇹‌🇭‌🇴‌🇩‌🇴‌🇽 ‌🇹‌🇪‌🇼‌🇦‌🇭‌🇩‌🇴
Photo
ብፁዕ አቡነ እስጢፋኖስ በጅማ መቆየት አይችሉም ተብለው ወደ አዲስ አበባ እንዲመለሱ ተደርጓል።

© ማኅበረ ቅዱሳን
👍6
╔​✞═┉✽🌹🌹✽┉═✞╗
❀ . "#ዕረፍተ_ሶልያና" ❀
╚✞═┉✽🌹🌹✽┉═✞╝

የቤተክርስቲያናችን ዐይን ሊቁ ቅዱስ ያሬድ ለአምልኮ መቅረዝ ለምስጋና ማኅቶት በሆነው የድጓ ድርሰቱ የእመቤታችንን የከበረ ዕረፍት ከዘመነ አስተርእዮ ምስጢር ጋር እያዛመደ እንዲህ አስፍሮታል።

∽†∽ "ጊዜ ዕረፍታ ለሶልያና፣ ወረደ ወልድ እም ዲበ ልዕልና፣ ጠሊሳነ ንግሥ ሶቤሃ ከደና " ∽†∽

#ድጓ:
⇆⇄
☞ መነሻው "ድግ" ካለው ግስ ነው የሚሉቱ "ድጋ ለቤተክርስቲያን" ብለው ድርሰቱ የተዋህዶ መደገፊያ መሆኑን ይነግሩናል።

☞ ምንጩን " ደግደገ" ካለው የሚያነሱትም ድግዱግ በሚለው ድግዱገ ጽሕፈት፣ ጥፈቱ የከሳ የቀጠነ ደቂቅ ረቂቅ የኾነ አሸዋ እብቅ ማለትም ነው ይላሉ ፤ እንደ ሊቃውንቱ ይኽ ሀተታ ከጽሕፈቱ ረቂቅነት ከምልክቱ ብዛት የተነሣ የተሰጠው መጠሪያ ነው።

☞ በሌላ አገባብም በዘይቤ የዓመቱ መዝሙራት ተወጣጥተው ተሰብስበው ይገኙበታልና ድጓ እስትጉቡእ ወይም ስብስብ ማለትም ይሆናል።

☞ ድጕዓ ከሚለው ዘር ሲነሳ ቍዘማ ፣ የልቅሶ ዜማ፣ ሙሾ ግጥም የሚለውን ይይዛል።

☞ በምሥጢራዊ የዘይቤ ትርጉም ደግሞ በፊደል ቍጥር ሲፈታ ፦ ድጓ ⇝ የ "ድ" አናቱ «ደ» ⇨ ፬
«ገ» ደግሞ ፫ ይሆንና አንድነት ድጓ ፯ ይኾናል፤ እስመ ኁልቈ ሳብዕ ፍጹም ውእቱ ይላልና ሳዊሮስ ዘአንጾክያ ፯ ፍጹም ቍጥር ነው በዚህ መነሻ ፍጹም ድርሰት መሥዋዕተ ስብሐት ይሉታል ድጓን፡፡

ሊቁ በዚህ የድጓ ድርሰቱ ፦ የነቢያቱን የትንቢት ማረፊያ፣ የሐዋርያቱን የስብከት መነሻ፣ የነገረ ድኅነት ጥልቅ ማብራሪያ፣ የሆነውን ነገረ ማርያምን በልዩ መንገድ ያስረዳናል። በተለይም የሥላሴ ማደሪያ የቤተክርስቲያን አንደበት ለሥጋ ለባሽ ሁሉ ትምክኅት የሆነች እመቤታችን በዘመነ አስተርእዮ በጥር ፳፩ ቀን የተከናወነው የከበረ "ዕረፍተ ሶልያና" በምን ክስተት እንዳለፈ እንዳንዘነጋው ሁሉን ከሚያስብ ከማይዘነጋ ልጇ እንድታማልደን እየተማጸነ ጭምር አብራርቶ ይዘግባል።

የዕረፍቷን ታሪክ ለማተት እጅግ ጥቂት መነሻ ታሪክ እናስቀድም፤

በነቢያቱ የተስፋ ትንቢትና በአበው ኅብረ ምሳሌ ስትጠበቅ የኖረች እመቤታችን የብጽአት (የስእለት) ልጅ ሆና ከአብራከ ኢያቄም ተመርጣ፣ ከማኅጸነ ሃና ተገኝታ ፣ ከአንስተ ዓለም ተለይታ፣ ከሁሉ ልቃ፤ ወደምድራችን ስትገለጥ በወላጆችዋ ቤት ለ፫ ዓመታት ቆይታ ለቤተ መቅደስ የስእለት ሥጦታ ሆና ለ፲፪ ዓመታት ብርሃናውያን የሚሆኑ የሰማይ ሠራዊት ቅዱሳን መላእክት ዘወትር እያረጋጓት በአገልግሎት ትጋት በተቀደሰው ሥፍራ ቅድስቲቱ በክብር ኖራለች። እንዲጠብቃት ለፃድቅ ገሊላዊ ዘመዷ ዮሴፍ ታጭታ ሳለች በብሥራተ መልአክ አምላክን ልጇ ክርስቶስን በግብረ መንፈስ ቅዱስ ጸንሳ በመውለድ ለ፴፫ ዓመት ከቤተልሔም ዋሻ ልደቱ እስከ ቀራንዮ ኮረብታ ስቅለቱ ሳትለየው አብራው ተገኘች። የዓለም መድኅን እናቱን በጎልጎታ ለወዳጁ ወንጌላዊ ዮሐንስ በእናትነት ሰጠው እርሱም ለ፲፭ ዓመታት እጠብቃት ብሎ ወስዶ ተጠበቀባት። ለአረጋዊው ፃድቅ በ፲፭ ዓመቷ በእጣ የመታጨቷን እና ለወጣቱ ሐዋርያ በ፵፭ ዓመቷ በእናትነት የመሰጠቷን በእርሱ ቤትም ፲፭ ዓመት የመኖርዋን ነኪር ኩነት የቁስጠንጥንያው ሊቅ አፈወርቅ ዮሐንስ እንዲህ አራቅቆታል።

በከመ ሰመያ እግዚእነ ለእሙ እመ ዮሐንስ በብሂሎቱ "ነያ እምከ" እንዘ ኢተወልዶ፤ ወመልአክኒ ከመዝ ሰመያ ለእግዝእትነ ማርያም (ፍኅርትከ) እንዘ ኢየአምራ (እመቤታችን ዮሐንስን ሳትወልደው ጌታችን እናቱ ማርያምን እነኋት እናትህ ብሎ የዮሐንስ እናት እነደሆነች እንደገለጣት ሁሉ መልአኩም ኅትምት ድንግልን ዮሴፍ 'ሳያውቃት' እጮኛው ብሎ ጠራት)

በታማኝ ልጇ በቅዱስ ዮሐንስ በኩል የሚታመኑ ልጆችዋን ስትጠብቅ የኖረች እናት ፷፬ ዓመት ሲሆናት በፍጥረት ሁሉ የደረሰ የሥጋን ዕረፍት እንዲያገኛት በእጅጉ የሚያስደንቀው ዕለተ ሞቷ ጥር ፳፩ ቀን በ፵፱ ዓ·ም ተፈፀመ።

ደራሲ "ሞትሰ ለመዋቲ ይደሉ: ሞታ ለማርያም የአጽብ ለኩሉ" እንዳለው የሕይወት መሠረት፣ የመድኃኒት እናት፣ የፈውስ ቤት፣ ቤዛዊተ ዓለም፣ አዲሲቷ እምቦሳ፣ የደስታ መፍሰሻዪቱ፣ የነባቢው በግ እናት ያን የሥጋ ሞት እንድትቀምሰው ልጇ ከመላእክቱ ጋር ተገለጠላትና ቅን ፍርዱን ገለጠላት፤ ለእኛም ይጥቀማችሁ ሲለን ታላቁን ክብሯን ገለጠልን።

⊙ ይኼንን ይዞ አፈ ሊቃውንት ቅዱስ ያሬድ "ጊዜ ዕረፍታ ለሶልያና፣ ወረደ ወልድ እም ዲበ ልዕልና፣ ጠሊሳነ ንግሥ ሶቤሃ ከደና" አለ። ⇨ ሶልያና ባረፈች ጊዜ ክብር፣ የክብርም ክብር የተገባው ወልድ ልጇ ክርስቶስ ከልዕልናው በልዕልና ወረደ እናቱን በጠሊሳነ ንግሥ በዚያን ጊዜ ሸፈናት። ጠሊሳነ ንግሥ ያለው የክብሯን መንዲል የንግሥናዋን መጎናፀፊያ ነው።

ሶልያና ማናት? (#ሶልያና)
–⇝↻†↺⇜–

ለሶልያና ስመ ተጸውኦ መነሻ ግንዱ "ሴሊኒ" የሚለው ልሳነ ጽር (የግሪክ ቃል) ነው ይላሉ የሀገራችን የሰዋስው ሊቃውንት፤ በትርጉም ሶልያና ያለውን የቅዱስ ያሬድን ስያሜ ከሴሌኒ ጋር በአቻ ፍካሬ "ጨረቃ" የሚል ትርጉም ሰጥተውት እናገኛለን።

ለአገናዛቢነቱም በዓለማችን ያሉ በስም ዙርያ መነሻ ግንዱን ታሪካዊ ይዘቱን እና አገባባዊ ትክክለኛ አጠቃቀም በሳይንሳዊ መንገድ የሚያትቱ ባለሙያዎች " መፈክራነ አስማት " (Onomatologists or Onomasticians) ይባላሉ።

ፍካሬ አስማት፣ የስም ትርጉም ጥናትም ( Onomastics or Onomatology) በሥሩ ሁለት ዓበይት ዘርፎች ያቅፋል፤ ይኸውም
① አስማተ መካን (Toponymy or toponomastics) የቦታ ስያሜዎችን የሚመረምር ሲሆን
② አስማተ ሰብእ (Anthroponomastics) በሰዎች ስም ዙሪያ የሚያተኩር ሀተታ የሚሰጥበት በየጊዜው ለሚወጡና ለሚሰሙ መጠሪያ ስሞች በአስረጅ አስደግፎ ማብራሪያ የሚያስቀምጥ ዘርፍ ነው።

ታዲያ እነዚህ 'ሊቃናትም' ቢሆን ምንጭ አልባ ፈሳሽ፣ ሥር አልባ ግንድ እንዳይኖር ተረድተው ሶልያናን "Σελήνη" ካለው ከግሪክ ምንጩ ቀድተው "Celena" ወይም "Selene" ያለውን መነሻ ግንድ አንቅተው ለአንስት የተገባ ትርጉሙም "ጨረቃ" (The Moon) ማለት ነው አሉን። የምንጩን ምንጭ የበለጠ ለማተት ከሚያስችል ማደሪያ ሲያደርሱን ደግሞ selas (σέλας) ከሚለው ማመሳከሪያ ጋር ያጣምሩልናል ትርጉሙም ብርሃን (light) ማለት ነው።

ጨረቃ እንደ ፀሐይና ከዋክብቱ ማኅደረ ብርሃንም አይደል!

እስኪ ደግሞ በእኛው ቅዱሳን ሊቃውንት እና ቅዱሳን መጻሕፍት ሀተታ የምሥጢር ባህር የትርጓሜ ማዕበል እጅግ ጥቂት እንመላለስ።

. ጨረቃና እመቤታችንን ምን ያገናኛቸዋል? የሚል ቢኖር
┈↺†↻┈┈◦◎✧◎◦ ┈┈↺†↻┈

☞ አቡቀለምሲስ ዮሐንስ "ብእሲተ ሰማይ ለባሲተ ፀሐይ" እያለ በራእይ ምዕራፍ ፲፪ ላይ የተገለጠለትን ዓቢይ ትእምርት ሲገልጥልን "ጨረቃን ተጫምታለች ከዋክብትን ተቀዳጅታለች" እያለ የብርሃን ድንኳን (ደብተራ ብርሃን) መሆኗን ያትታል።

የድጓው ባለቤትም ከድርሰቱ የአንዱን ክፍል መጠሪያ "አንቀጸ ብርሃን" በሚል ስያሜ ለሕይወት መሰላል፣ ለመለኮት ማደሪያ፣ እመ ብርሃን ምስጋናን ማዘጋጀቱ ቅሉ ለዚህ ነው! የፀሐይ መውጫ ምሥራቁ፣ ለብርሃነ ጽድቅ ደጃፉ እርሷ ናትና።
👍6
ዳግመኛም አማናዊቷን ጽዮን ወላዲተ አምላክን ጸወን ያደረገ የ "ሕዝበ ጽዮን" እና "እምነ ጽዮን" ልጅ የጋስጫው ሊቅ አባ ጊዮርጊስ በሰዓታት ምስጋናው "ኮከበ ብርሃን ጽብሐዊ፣ ፀሐየ ጽድቅ አርያማዊ" የሚሆን የፍጥረት ሁሉ ገዥ ብርሃን ክርስቶስን የወለደች እናትም አገልጋይም ሆና የተገኘች ድንግል ማርያም የተጫማችው ጨረቃ የለበሰችው ፀሐይ የብርሃን መኖርያ የንጽሕና ማደሪያ መሆኑን ገላጭ እንደሆነ ሲያስረዳ

"ለአሣዕንኪ ወርኅ ወለቶታንኪ ጎህ ልብስኪ ንጽሕ" በማለት ተቀኝቶላታል።

☞ በነገረ ማርያም የምናገኘው ሌላው የጨረቃ ምሥጢር ደግሞ ከእመቤታችን ፯ኛ ቀዳሚ አያቶች ከጴጥርቃና ከቴክታ የተገኙ ፷፯ ወንዶች መካከል ነገር ያላቸውን ትንቢት የተነገረላቸውንና ሱባኤ የተቆጠረላቸውን ሲነግረን ከጨረቃውም ትርጉም ሲያደርሰን ቴክታ ያየችውን ለከበረ ጴጥርቃ የነገረችውን ሕልም እንዲህ ብሎ ያሳትታል " በህልሜ ነጭ ጥጃ ከማህጸኔ ስትወጣ ያችም ነጭ ጥጃ ሌላ ነጭ ጥጃ ስትወልድ እንዲሁ እስከ ፯ት ትውልድ ሲዋለድ ሰባተኛይቱ ጨረቃን ስትወልድ ጨረቃዋም ፀሐይን ስትወልድ አየሁ"

ይኽውም በመፈክረ ሕልም "እግዚአብሔር በምሕረቱ አይቷችኋል በሳህሉ መግቧችኋልና ፯ አንስት ጥጆች መውለዳችሁ ፯ ሴቶች ልጆች እና የልጅ ልጆች ትወልዳላችሁ ከቤታችሁ ሰባተኛይቱ ጨረቃ መውለዷም ከሰው በእጅጉ የበለጠች ከመላእክትም የከበረች ደግ ፍጥረት ትወልዳላችሁ የፀሐይ ነገር ግን አልታወቀኝም" ተብሎ ተነግሯቸው ነበርና ይኸውም ሊደርስ በፈቃደ እግዚአብሔር ሄሜን የተባለች ልጅ ወልደዋል።በዚህም የዘር ሐረግ ሰንሰለትም ሄሜን → ደርዲ → ቶና → ሲካር → ሴትና → ሄርሜላ → ቅድስት ሀና (እማ ለእማምላክ ፯ተኛይቱ ጣዕዋ) ተገኝታለች።

ሰባተኛይቱ "ጥጃ" ሀናንም በእርግናዋ ወራት አምላክ አስቧት ጨረቃ የተባለች "አዲሲቷን እምቦሳ" የፀሐይን እናት ድንግል ማርያምን ብትጸንስ ሞቶ የነበረ የአጎቷ ልጅ "ሳሚና" በተአምር ተነስቶ ከመፈክረ ሕልም የቀረውን ፈ'ቶ እንዲህ ሲል መስክሯል "ስብሃት ለኪ ማርያም እሙ ለፀሐየ ጽድቅ ለአብ መርዓቱ ለወልድ ወላዲቱ ለመንፈስቅዱስ ጽርሃ ቤቱ ተፈስሒ"

ይኽ ምሥጢር በሳሚና የተገለጠ ብቻ አልነበረም መላእክቱ በመንጦላእተ ብርሃን ውስጥ ሆነው የሚያመሰግኗት 'እንዲያ' እያሉ ነው "በሐኪ ማርያም ሐዳስዩ ጣዕዋ … አዲሲቷ እምቦሳ ላንቺ ምስጋና ይገባሻል"

◆ ሶልያና አዲስ እምቦሳ ከጥጆች የተገኘችና ፀሐይን ያስገኘች ጨረቃ ድንግል ማርያም ናት።

☞ የበለጠ ይኽን ለማመሳጠር የጋሥጫው ሊቅ በአርጋኖነ ውዳሴ ቀዳሚ ክፍል «ወህየንተ ወርኅ ተርእየት ቅድስት ድንግል ማርያም» የሚለውን ለማምጣት እንዲህ በማለት ስቦ ይመራናል ፦

"ሥርዐተ ሰማይ ተሠርዓ በዲበ ምድር ⇒ የሰማይ ሥርዓት በምድር ላይ ተሠራ፤ ቤተ ልሔም ሰማይን መሰለች
🔯 ስለ #ፀሐይም በቅዱሳን ላይ የሚያበራ ለዘወትርም ጨለማ የማይቃወመው ኅልፈት ጥፋትም የሌለበት ዕውነተኛ ፀሐይ በውስጧ ተገኘ፡፡
🔯 የብርሃኑም ክበብ መምላትና መጉደልን ስለሚያፈራርቅ #በጨረቃ ፈንታ በዕብራይስጥ ማሪሃም የተባለች የድንግልናዋም ምስጋና በሁሉ የመላ ነው፡፡ ለዘወትርም የማይጐድል እመቤታችን የተመረጠች ድንግል ማርያም ተገኘች
🔯 ስለ ከዋክብትም መላእክተ ብርሃን ታዩ፡፡"

ሊቃውንቶቻችን መች በዚህ ብቻ ይብቃን ይላሉ፤ የሊቁን ስያሜ ሲያራቅቁ በዘይቤ ረቂቁ አካላዊ ቃል ወልድ የተነበበባትን ሶልያና ትርጉም የፊደል ገበታ ማለት ነው ይሉናል "መዝገቡ ለቃል" ትባላለችና::

መልሰውም የስሟን ዝርዝር በፊደል "በአኅጽሮተ ቃል" የተዋቀረ የእመቤታችንን ክብር የሚገልጽ መጠሪያ ስምም ያደርጉታል። እንዲህ እያሉ

ሶ ✧ ሶበሰ ኪዳንኪ ምክንያተ ድኂን ኢሀሎ (ኪዳንሽ ባይኖር ምክንያተ ድኂን የለም)

ል ✧ ልሳንየ ላእላእ ይሴብሀኪ (ዲዳው ትብ አንደበቴ ያመሰግንሻል)

ያ ✧ ያንቅአዱ ሀቤኪ ኩሉ ፍጥረት(ፍጥረታት ሁሉ ወደአንቺ ያንጋጥጣሉ)

ና ✧ ናሁ ተግህደ ልዕልናሃ ለድንግል፥ (እነሆ የድንግል ታላቅነቷ ተገለጠ)

. ዘመነ አስተርእዮ እና ዕረፍተ ሶልያና
┈↺†↻┈┈◦◎✧◎◦ ┈┈↺†↻┈

ዘመነ አስተርእዮ የበጎ ነገር ሁሉ ወዳጅ ክርስቶስ የጸላዔ ሰናያት የዲያቢሎስን ክፉ ሥራ ለማፍረስ መገለጡ የሚታሰብበበት ነው። (፩ዮሐ ፫፥፱) ከልደቱ እስከ ጥምቀቱ "አንሶሰወ ከመሰብእ እንደ ሰው ተመላለሰ" በሕግ ጠባይዓዊ፣ በሕግ መጽሐፋዊ ግብር ታየ በመባል ሲነገርለት የነበረ የእዳ ጽሕፈታችንን እንደሰውነቱ ረግጦ እንደ አምላክነቱ አቅልጦ ከፈለገ ዮርዳኖስ ሲደመስስ ለቤዛነት መምጣቱን በግልጥ ያስመሰክር ጀመር። ከገዳም የ፵ ቀን ቆይታ መልስ በቃና ዘገሊላም ቀዳሚ ተአምር ውኃን ወደ ወይን በእናቱ ምልጃ በመቀየር አሳይቷል። ተያይዞም አስተርእዮቱን የሚያትቱ በዓላት በምሥጢር እየተገናኙ በዚህ ዘመን ይታወሳሉ (፭ቱን ኅብስተ ሠገም ፪ቱን ዓሣት ያበረከተበት ጥር አማኑኤልን ጨምሮ)

ሊቁ "ጊዜ ዕረፍታ ለሶልያና፣ ወረደ ወልድ እም ዲበ ልዕልና" ማለቱ በዘመነ አስተርእዮ ምሥጢር ውስጥ የማናጣት "ለቃል ርደት ዙፋን ለሥጋ ዕርገት መሰላል" የሆነችው እናቱ በዕለተ ዕረፍቷ የበለጠ አስተርእዮቱ መገለጡን ለማሳሰብ በታላቅ ልዕልናው ከልዕልናው ወደ ምድር ዳግመኛ የመጣውን የአምላካችንን አስተርእዮ ለማተትም ጭምር ነው።

ውበቷን የወደደው የሠማይ ንጉሥ ቀድሞ ለኑሮ ያደገችበትን 'ቤት' ፤ ኋላ ለነፍስ ያደረችበትን 'ሥጋዋን' ትታ እንድትከተለው ሲጠራት "ልጄ ሆይ፥ ስሚ እዪ ጆሮሽንም አዘንብዪ፤ ወገንሽን ያባትሽንም ቤት እርሺ፤ ንጉሥ ውበትሽን ወድዶአልና፥ እርሱ ጌታሽ ነውና።" (መዝ ፵፬ ፥፲) ይላታል። ወስዶም በዐረፍተ ዘመን የማይተዋት በቅድስት ትንሳኤና በከበረ ዕርገት እንደሚጎበኛት ሲያስረዳ "ወዳጄ ሆይ! ተነሺ:: ውበቴ ሆይ! ነዪ::"+ (መኃ. ፪፥፲፫) ሲል ትንቢቱን አናግሯል።

የጥር ፳፩ዱን "ዕረፍተ ሶልያና" አስተርእዮ ማርያም ያሰኘው በሥጋ መለየቷ በዘመነ አስተርእዮ መፈጸሙ ብቻ ሳይሆን ጌታ እልፍ አዕላፋት መላእክቱን አስከትሎ በዕረፍቷ ዕለት ተገልጦበታልናም ነው።

. የዘመነ አስተርእዮ ሰርግ (ዘመነ መርዓዊ) እና ዕረፍተ ሶልያና
┈↺†↻┈┈◦◎✧◎◦ ┈┈↺†↻┈

ዘመነ መርዓዊ ከቃና ዘገሊላው ተአምር ተያይዞ በዘመነ አስተርእዮ ማገባደጃ የሚታሰብ ወቅት ነው።

በስንክሳሩ አርኬ የተቀመጠው ሰላምታ ዕረፍቷን ከሰርግ ጋር እያዛመደ እንዲህ ያስተምረናል።

ሰላም ለጸአት ነፍስኪ በመዓዛ ክርስቶስ ዘተነቅበ
ወመሰንቆ ማኅሌት ሐዋዝ እንዘ ያመዓርር አልባበ
ሐራ ሰማይ ብዙኃን እለ አልቦሙ ሐሳበ
እንዘ ይዜምሩ ቅድሜኪ ወመንገለ ድኅሬኪ ካዕበ
ማርያም ሞትኪ ይመስል ከብካበ፡፡

በክርስቶስ መዓዛ ለሰቀቀው (ከዚኽ ዓለም ለተለየው) እና ልብን በእጅጉ ደስ በሚያሰኘው በመሰንቆ ጣዕመ ማኅሌት ለተከናወነው የነፍስሽ መውጣት ሰላምታ ይገባል፤ ብዙ የሚሆኑ ቁጥር የማይገድባቸው ልክ የማይወሰንላቸው የሰማይ ሠራዊት በፊትሽ እየቀደሙ ዳግመኛም ከኋላሽም እየተከተሉ ሲዘምሩ ታይተዋልና ማርያም ሆይ ሞትሽስ ሰርግ ይመስላል።
👍5
በምድር እየተሰረጉ በሰማይ የከበረውን እንዲህ ያለ ሰርግ ለማሰብ የታደሉ እንደምን የተመሰገኑ ናቸው!
በንጽሕና የኖረ ወልደ ነጎድጓድ ዮሐንስ በታላቅ ክብር ወደተመለከታት፣ ድምጹን አሰምቶ ወደተናገረላት፣ የነቢያት ሁሉ ደስታቸው ፈጣሬ ዓለማት ክርስቶስ ወደ አደረባት፣ አዲሲቷ ጽዮን፣ የአምላካችን ሀገሩ፣ የመለኮት ማኅደሩ፣ በእንግዳ ሥርዓት ዕረፍቷ ሰርግ ወደተባለላት ንስቲት መርዓት (ታናሽ ሙሽራ) እንድናይ የማለዳው ምስጋናችን ሁላችንንም እንዲህ ሲል ይጠራናል

"ሃሌ ሉያ ንዑ ትነጽሩ ኅበ ዛቲ መርዓት ዘሥርጉት እመ በግዕ ወዑጽፍት በዝንቱ ስብሐት ዓቢይ በከመ ይቤ ወልደነጐድጓድ። ዮሐንስ ድንግል ወንጹሕ ይጸርሕ እንዘ ይብል እስመ አብርሀ(ት) (ለ)ዛቲ ይእቲ። ጽዮን ሐዳስ። ሀገረ አምላክነ። ዘኃደረ ላዕሌሃ ፍሥሓ ኵሎሙ ነቢያት ቅዱሳን።"

ደገኛ መጽሐፍ በጀመረበት መጨረስ ልማዱ እንደሆነ በማሰብ እኛንም ከርቱዕ ሕሊና ከርቱዕ ሕሊና እንዳያርቀን እየተማፀንን ከሊቁ በረከት እንዲያሳትፈን ደጅ እየጠናን፤ መልሰን ፈልፈለ ማኅሌት ቅዱስ ያሬድን ከድጓው እንጥራው እና የሰርግ ቀን በተባለ የዕረፍቷ ዕለት ሰማያዊውን ሰርግ በዓይነ ሕሊናችን አቅርበን የሶልያናን ዕረፍት ሀተታ እንዲህ እንቋጨው፤

ዮም ይባቤ የበቡ
ኃጢዓተ እለ ዘገቡ
በኪዳነ ድንግል ካህን ሥርየተ እለ ረከቡ
ከመ ይባኡ ለወልድኪ ውስተ ከብካቡ

የሊቁ ፍቅር ምንኛ ይደንቃል! የድንግሊቱ የአምላክ እናት "ቃልኪዳኗ" ኃጢአት ሲሰሩ ለኖሩ ሥርየት የሚያሰጥ "ካህን" ነው ይላል። የታመኑባት ኃጥአን በዕለተ ምጽዓት በደስታ እየዘመሩ ወደ ሰርጉ አዳራሽ የሚሻገሩባት አግዓዚት፣ ተጨንቀው ለሚጠሯት ሰማዒት ፣ ወደ ማኅደረ ነፍስ የሚደርሱባት ማዕዶት እርሷው ናትና።

በዕረፍቷ በድካመ ሥጋ በገቢረ ኃጢአት ከመባከን በንሰሀ መልሳ የዕረፍት ውኃ የለመለመ መስክ በተሰኘ "ሥጋሁ ለአማኑኤል ዘነሥአ እምእግዝእተ ኩልነ" ብለን በምንቀበለው ቅዱስ ምሥጢር እንድናርፍ ምልጃዋ አይለየን።

በቴዎድሮስ በለጠ εαδïтεδ αทδ Яερ๑รтεδ ƒя๑๓ ℓαรт γεαя 🕒🕕 ጥር ፳፩ ቀን ፳፻፲፩ ዓ·ም· 🕘🕛
👍7
አባ ጸጋ ዘአብ ተለቀዋል።
ብዙ ሥራ የምንጠብቅባችሁ ቢሆንም ይህን ያደረጋችሁ አካላት እናመሰግናለን።
ከቀሲስ ታጋይ ታደለ የተላለፈ
"አሁን ማምሻውን በሰላም አዲስ አበባ ገብተናል። ተጨነቃችሁ ለጻፋችሁ ምን ተፈጠረ ብላችሁ ላሰባችሁ እግዚአብሔር ያክብርልኝ። ብጹዕ አባታችን አቡነ እስጢፋኖስ በሰላም ወደ አዲስ አበባ ማረፊያቸው ገብተዋል። ጅማ ያላችሁ ምዕመናንን ፍጹም መረጋጋት አለባችሁ ። መልእክቴ ነው።" ....ብለዋል።
ኦርቶዶክስ ተዋህዶ - ‌🇴‌🇷‌🇹‌🇭‌🇴‌🇩‌🇴‌🇽 ‌🇹‌🇪‌🇼‌🇦‌🇭‌🇩‌🇴
Photo
ጊዜ ዕረፍታ ለቅድስት ድንግል

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ፤ አሜን፡፡

ሊቀ መላእክት ቅዱስ ገብርኤል ብሥራት ይዞ ለሁለተኛ ጊዜ ወደ እመቤታችን ከእግዚአብሔር ዘንድ ተልኮ የሔደው የዕረፍቷ ጊዜ መድረሱን ለማብሠር ነበር፡፡ የድል ምልክት የሆነውን ፍሬው የተንዠረገገ የቴምር ፍሬ የሚያፈራውን ዘንባባ ይዞ ለሁለተኛ ጊዜ እርሷ ወዳለችበት ይዞ ገብቶ ደስ ይበልሽ ሲላት አሁንም እየሰገዳና እጅ እየነሣ ነበር፡፡ ጌታችን እንዳዘዘውም "ልጅሽና ጌታሽ እናቴ ወደ እኔ ትመጣ ዘንድ ጊዜው ደርሷል ብሏል፡፡ ከሴቶች ተለይተሸ የተባረክሽ ቅድስት ሆይ ስለዚህም ለሁለተኛ ጊዜ ይህን መልካም የምሥራች እነግረሽ ዘንድ ላከኝ፡፡ ብፅዕት ሆይ በምድር የሚኖሩትን ሁሉ በደስታ እንደሞላሻቸው አሁን ደግሞ በዕረፍትሽና በዕርገትሽ ምክንያት የሰማይ ኃይላት በደስታ ይሞሉ ዘንድ በሰማይ ያሉ ነፍሳትም ሁሉ ከመቼውም ጊዜ በላይ በክብር ያበሩ ዘንድ ምክንያት ትሆኛለሽ፡፡ ደስተኛይቱ ፍስሕት የሚል ማዕረግ ለዘላለም ተስጥቶሻልና ስታዝኝና ስታለቅሽ በኖርሽው መጠን ደስ ይበልሽ፡፡ ጸሎቶችሽና አስተብቁዖቶችሽ በሙሉ በልጅሽ ፊት ወደ ሰማይ ዐርገዋል፤ ስለዚህም ይህን ዓለም ትተሽው ወደ ሰማይ ትሔጅና ፍጻሜ በሌለው የዘላለም ሕይወት ከልጅሽ ጋር ትኖሪ ዘንድ አዝዟል" ብሎ ዘንባባውንም በእጇ ሰጣት፡፡ የነበረውን ትውፊት ሁሉ አሰባስቦና አጠናቅሮ በሰባተኛው ክፍለ ዘመን በግሪክ ቋንቋ ሕይወቷንና ተጋድሎዋን በተሻለ ሁኔታ የጻፈው መክሲሞስ ዘኢየሩሳሌም እንደመዘገበው እመቤታችን የመልአኩን ብሥራት በሰማች ጊዜ እጅግ ተደስታ እንደ ቀድሞው ሁሉ በፍጹም ትሕትና "እነሆ የእግዚአብሔር አገልጋዩ፤ አሁንም እንደቀድሞው እንደቃልህ ይደረግልኝ አለችው" ይላል፡፡ ከዚህ በኋላ አሁን በዚህ ጽሑፍ የማልገልጻቸው እጂግ ብዙ ገቢረ ተአምራት ተፈጽመዋል፡፡ እመቤታችን መልአኩ ቅዱስ ገብርኤል የሰጣትን ዘንባባ ይዛ በደብረ ዘይት ተራራ ሔዳ ከጸለየች በኋላ ቀድማ ትነግረው ዘንድ ትፈልገው የነበረውን ወንጌላዊና ነቢየ ሐዲስ ንጹሕ ድንግል ዮሐንስን በደመና አምጥቶላታል፡፡ ከዚያም ልዩ የእግዚአብሔር መቅደስ ወዳደረገቻት ቤቷ ከተመለሰች በኋላ ሐዋርያትና ብዙ ተላውያነ ሐዋርያት ድንገት አንድ ጊዜ በደመና ደረሱ፡፡ ቅዱስ ዮሐንስ ከደመናው ከተቀበላቸው በኋላ ወደ እርሷ ይዟቸው ገባ፡፡ ሁሉም አንድ በአንድ እየሆኑ በፊቷ እያለፉ ተሳለሟት፤ እርሷም አነጋገረቻቸው፡፡ ከአርድእት አንዱ የሆነው ተላዌ ቅዱስ ጳውሎስ የሆነውና ከፍልስፍና የተመለሰው የአቴናው ዲዮናስዮስ ከተገኙት አርድእት መካከል እርሱ ቅዱስ ጤሞቴዎስና ቅዱስ ሔሮቴዎስ እንደነበሩና ቅዱስ ጴጥሮስን፤ ቅዱስ ጳውሎስንና ሌሎቹን ሐዋርያት ስታናግራቸው በዓይኑ እንዳየና ራሱም በፊቷ አልፈው እማሔ ካደረጉት መካከል መሆኑን ለጢሞቴዎስ በላካት መልእክት ላይ መዝግቦታል፡፡ ከዚያም በኋላ መንፈስ ቅዱስ ወርዶባቸው ሁሉም ሐዋርያትና አርድእት መንፈስ ቅዱስ እንደሰጣቸው መጠን ተሰምቶ የማያውቅ ልዩ ምስጋና ማቅረባቸውን መዝግቧል፡፡ ከዚህም በኋላ የተደረጉት ተአምራት ብዙዎች ስለሆኑ በሌላ ጽሑፍ እስክምለስ ድረስ አሁንም እነርሱን ከመዘርዘር እቆጠባለሁ። በመጨረሻም ጌታችን በሚያስፈራና በልዩ ግርማ ከቅዱሳኑ ሁሉ ጋር መውረዱንና እነሙሴ እነዳዊት በአንድነት ከአእላፋት መላእክት ጋር ሲዘምሩና የሰማይ ሠራዊት በደስታ ሲጥለቀለቁ ጽዮንም ስትናወጥ ማየታቸውን በእኛ የጥር ወር በልዩ ከብር ማርፏን የነበሩት ሐዋርያትና አርድእት ሁሉ መስክረዋል፡፡

የአካላዊ ቃልን ወደዚህ ዓለም መምጣት ማብሠር እንደተሰጠህ የድንግሊቱንም ወደዚያኛው ዓለም መሔድ ማብሠር ድጋሜ የተሠጠህ የታመንህና የከበርክ ቅዱስ ገብርኤል ሆይ እባክህ መልካም ነገር እያለ የራቀውን የእኛን ትውልድም ከመልካሙ ነገር አገናኝልን፤ መልካሙን አሰማን፡፡ ከድንግሊቱና ከደስተኛይቱ እናታችን በረከትም አድርስልን፡፡ ክብሯን ግለጥ ፤ እኛንም ፈጽመህ አማልደን።

እንግዲያውስ ቅዱሳኑን ተከትለን እኛም እየዘመርንና እያመሰገንን የሰው ዘር መመኪያ የሆነችውን የእናታችንና የእመቤታችን የንጽሕተ ንጹሐን የቅድስተ ቅዱሳን የድንግል ማርያምን በዓለ ዕረፍት በተከበረው ትውፊታችን መሠረት እናክብር፡፡

ኢትዮጵያዊው ሊቅ ቅዱስ አባ ጊዮርጊስና ሶርያዊ ማር ኤፍሬም የመሥዋዕቱን በግ ያስገኘሽልን፤ እረኛችን የወልድሽልን ንጽሕት በግ ሆይ የሚሉሽ ፍጽምትና የታመንሽ አማላጅ ሆይ በፍጹም ምልጃሽ ሁላችን አስምሪ ።

እንኳን ለበዓለ ዕረፍታ ለንጽሕት ቅድስት ድንግል ማርያም አደረሳችሁ፡፡
ዲ.ን ብርሀኑ አድማስ
👍2710
"በሀገራችን ሁሉ ነገር ተበጣጥሶ አልቋል። አሁን ሁላችንም የሚያያይዘንና የሚያስተሳስረን ኃይማኖታችን ነበር የቀረው። እርሱንም ዛሬ እየበጣጠሱት ነው። ኃይማኖታችን የደም ሥራችናትና ልንጠብቃት ይገባል።"
ዛሬ ቅዱስነታቸው በቤተ ክህነቱ ስብሰባ ከተናገሩት።
41👍8👏2
ኦርቶዶክስ ተዋህዶ - ‌🇴‌🇷‌🇹‌🇭‌🇴‌🇩‌🇴‌🇽 ‌🇹‌🇪‌🇼‌🇦‌🇭‌🇩‌🇴
Photo
ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) ለሚኒስትሮችና ለካቢኒ አባላት በሰጡት የወቅታዊ ጉዳይ ማብራሪያ አስመልክቶ ከቅዱስ ሲኖዶስ የተሰጠ መግለጫ።
ጥር 24 ቀን 2015 ዓ.ም.
+++++++++++++++++++++++++++++++++++++
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!
ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ የተሰጠ
መግለጫ።
በመንፈስ ቅዱስ የሚመራው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ ጥር 18 ቀን 2015 ዓ.ም ባደረገው ምልዓተ ጉባኤ ጥር 14 ቀን 2015 ዓ.ም በደቡብ ምዕራብ ሸዋ ሀገረ ስብከት በሶዶ ደሙ ወረዳ ሀሮ በዓለወልድ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ የተፈጸመውን ኢ-ሲኖዶሳዊ የሆነ የሃይማኖት፣ የቀኖናና የአስተዳደር ጥሰት አስመልክቶ በሰፊው ተወያይቶ ከቤተ ክርስቲያኒቱ የሃይማኖት ልዩ ልዩ ሕግጋት ውጭ ጳጳስ ሾመናል ባሉ አካላት እና ተሹመናል በሚሉት አካላት ላይ የቤተ ክርስቲያኒቱ ሕግጋት በሚፈቅድለት መሠረት የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ አውግዞ ከቤተ ክርስቲያን የተሰጣቸው ከዲቁና ጀምሮ ያለው ሙሉ ሥልጣነ ክህነት በመሻር አውግዞ የለያቸው ሲሆን፣ በዕለቱ ይኸው ውግዘት በመላው ዓለም ለሚገኙ የዕምነቱ ተከታዮች ማኅበረ ካህናትና ማኅበረ ምዕመናን ውግዘቱን እንዲያውቁት መንግሥትም በዚህ ጉዳይ የሚፈጠር ችግር እንዳይኖር ሰላም እንዲያስከብር ዓለም በዚህ ጉዳይ ላይ ግልጽ መረጃ ኖሮት ቤተ ክርስቲያን ለወሰነችውም ውሳኔ ግንዛቤ እንዲወስድ በመግለጫ ማሳወቃችን ይታወሳል፡፡
በዚህ የቅዱስ ሲኖዶስ ውሳኔ የቤተ ክርስቲያኒቱ ተከታይ የሆኑ አገልጋይ ካህናት እና ምዕመናን በመላው ዓለም የሚገኙት ደስታቸውን በመግለጥ የቅዱስ ሲኖዶስን ውሳኔ ሳይሸራረፍ እንደሚያስፈጽመ በልዩ ልዩ መንገድ እየገለጹ ይገኛል፡፡
ከዚህም በተጨማሪ በሀገር ውስጥና ከሀገር ውጭ የሚገኙ የልዩ ልዩ ሃይማኖት ተቋማትና ሲቪክ ማኅበራት የተፈጸመውን ድርጊት በመቃወም እና ቤተ ክርስቲያኒቱ የወሰነችውን ውሳኔ በመደገፍ ከጎናችን እንደሆነ እና አብረውን እንደሚሰሩ በልዩ ልዩ መንገድ እየገለጹልን ይገኛል፡፡ በዚህ ቤተ ክርስቲያናችን ከጎናችን ለቆሙትና ድጋፋቸውን ለገለፁልን ዓለም አቀፍና ሀገር አቀፍ የሃይማኖት እና የሲቪክ ተቋማት ምስጋናዋን አቅርባለች።
እነዚህ በሕገ ወጥ መንገድ ተሹመናል የሚሉት አካላትም በአንዳንድ ቦታዎች ላይ ከማዕከላዊ መዋቅር ውጭ ተወግዘው ተለይተው እያለ በሌላቸው ሥልጣን ወዳልተፈቀደላቸው የአገልግሎት በታዎች በመግባት በሚያደርጉት ግብ ግብ በዕምነቱ ተከታዮች፣ በማህበረ ካህናትና ምዕመናን ላይ ሁከት እየተፈጠረ መሆኑን ለመረዳት ችለናል።
በዚህ ጉዳይ ላይ ቤተ ክርስቲያናችን ለመንግሥት ያቀረበችው ሕግን የማስከበር እና የዜጎችን ሰላም የማስፈን ሥራ ጥሪ ተቀብሎ በሕገወጦች ላይ የወሰደው ምንም ዓይነት እርምጃ እየታየ አለመሆኑም ታውቋል፡፡
ይህ ሁሉ ድርጊት ሲፈፀም መንግሥት ሰምቶ እንዳልሰማ በዝምታያለፈውን ጉዳይ በጥር 23 ቀን 2015 ዓ.ም ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ የኢፌዲሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ለሚኒስትሮችና ለካቢኔዎቻቸው በሰጡት የወቅታዊ ጉዳይ ማብራሪያ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ የተከሰተውን ወቅታዊ ችግር በማንሳት ልዩ ልዩ አስተያየቶችን ሰጥተዋል፡፡
ይኸውም ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትሩ በቅዱስ ሲኖዶሱ እና ውጭ ባሉ አባቶች መካከል ሲካሄድ የነበረውን የዕርቅ ሒደት እልባት እንዲያገኝ ማድረጋቸው፤ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ይዞታዎችና ሕንጻዎች መካከል 4ኪሎ የሚገኙትን ሁለቱን ቀደምት ሕንጻዎች ለቤተ ክርስቲያን መመለሳቸው፣ በተባበሩት አረብ ኤሚሬቶች ሀገረ ስብከት ለሚገኘው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሕንጻ መሥሪያ ቦታ ማድረጋቸው! የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሀገር መሆኗን መግለጻቸው፣ የቤተ ክርስቲያኗ መዳከም ጉዳቱ ለቤተ ክርስቲያኗ ብቻ ሳይሆን ለሀገረ መንግሥቱም ጭምር መሆኑን መግለጻቸው፣ አግባብነት ያለውና ለዚህም : አድራጎታቸው ቤተ ክርስቲያናችን በወቅቱ በእውቅና ሽልማት አጅባ አመሰግናለች፡፡
ሆኖም ግን ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትሩ ጥር 23 ቀን 2015 ዓ.ም በተለያዩ የመንግሥት ሚዲያዎች በተላለፈው 36 ደቂቃ በሚፈጀው በሰላምና ሃይማኖታዊ ጉዳዮች ዙሪያ ለሚኒስትሮች ካቢኔ አባላት የሰጡትን ማብራሪያ ቤተ ክርስቲያናችን በአጽንዖት ተመልክታዋለች፡፡
በመሆኑም በቀረበው ማብራሪያ ላይ ቤተ ክርስቲያናችን ያላትን አቋም እንደሚከተለው
በዝርዝር እንገልጻለን፡፡
፩. መንግስት በቤተ ክርስተያናችን የተፈጠረውን ሃይማኖታዊ እና ቀኖናው ጥሰትን በተመለከተ ቤተ ክርስቲያን የሰጠችውን ሲኖዶሳዊ ውሳኔ ሊያመጣ የሚችለውን ውጤት አቅልለው በአሁኑ ወቅት በኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን የተፈጠረው ጉዳይ በጣም ቀላል ነው” በማለት ያዩበት መንገድ፤ ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትሩ በሰጡት ማብራሪያ ጉዳዩ ቀላል እና በንግግር የሚፈታ እንደሆነ ገልጸዋል፡፡ ይህ አገላለጽ በቤተ ክርስቲያናችን አስተምህሮ ውስጥ ጣልቃ እንደመግባት እና ቤተ ክርስቲያን የምታስተላልፋቸውን ሃይማኖታዊና ቀኖናዊ ውሳኔዎች ያላቸውን ውጤት ወደ ጎን የተወ መሆኑን ቤተ ክርስቲያን ታምናለች፡፡ ከዚህም አልፎ ሁለቱም ወገን ውስጥ እውነት አለ፣ ሁለቱም አባቶቻችን ናቸው፣ ለማንም አንወግንም፤ ማንም የካቢኔ አባል እዚህ ውስጥ እጁን እንዳያስገባ፣ የሚሉት አገላለጾች በሕግ እውቅና የተሰጣትን ቤተ ክርስቲያን እና በሕጋዊቷ ቤተ ክርስቲያን ላይ በሕገ ወጥ መንገድ የተነሱትን ሕገ ወጥ ቡድኖች በአቻ እይታ ተመልክተው ሊወያዩ ይገባል በማለት የስጡት ማብራሪያ ሕገ ወጥነትን የሚያበረታታ፣ ለሕጋዊ ተቋማት መንግሥት ያለበትን የመጠበቅና ዋስትና የመስጠት ኃላፊነቱን ወደ ጎን ያደረገ፣ ሕጋዊ ሰውነት ያላቸው ተቋማት በሕገ ወጥ ቡድኖች እንዲታመሱና እንዲተራመሱ ይሁንታ የሚሰጥ፣ ሕግንና የቤተ ክርስቲያኒቱን ጥንታዊ ታሪክና የሀገር ባለውለታነትዋን ያላገናዘበ፣ ማብራሪያ በመሆኑ ሊታረም የሚገባ መሆኑን ቅዱስ ሲኖዶስ በጽኑ ያሳስባል።
ከዚህም በተጨማሪ ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትሩ የትኛውም ካቢኔ በዚህ ጉዳይ እጁን እንዳያስገባ በማለት የሰጡት የሥራ መመሪያ የቅዱስ ሲኖዶሱን ውሳኔ እና የቤተ ክርስቲያኒቱን ሕጋዊ ሰውነት አክብረው እና የሕዝብን ሰላምና ደህንነት ለማስከበር ከፍተኛ ጥረት እያደረጉ ያሉትን በየደረጃው ያሉ የመንግሥት አስፈጻሚ አካላትን ኃላፊነታቸውን እንዳይወጡ የሚያደርግና በሕገመንግሥቱ ለአስፈጻሚው አካል የተሰጠውን ሥልጣን የሚሽር፤ ሥርዓተ አልበኝነትን የሚያበረታታ፤ የሕግ የበላይነትን ጥያቄ ውስጥ የሚጥል አድራጎት በመሆኑ ይህ አድራጎት እንዲታረምና መንግሥት በሕገ መንግሥቱ የተጣለበትን የሕግ የበላይነትና የተቋማትን ደህንነት የማረጋገጥ ሕገ መንግሥታዊ ኃላፊነቱን እንዲወጣ ቅዱስ ሲኖዶስ በጽኑ ያሳስባል፡፡
በሕገ መንግሥቱ መንግሥትና ሃይማኖት የተለያዩ መሆናቸው በግልጽ የተደነገገ እንደመሆኑ መጠን መንግሥት በቤተ ክርስቲያን ሃይማኖታዊና ቀኖናዊ ላይ እጁን ማስገባት እንደሌለበት የምናምንበት ሐቅ ሲሆን ከዚህ ሕገ መንግሥታዊ ድንጋጌ ውጭ በሆነ መንገድ በቤተ ክርስቲያኒቱ ላይ የተፈጸመውን ሃይማኖታዊ፣ ቀኖናዊ እና አስተዳደራዊ ጥሰትን እንደተራ ግጭት እና የግለሰቦች አለመግባባት በመቁጠር ትንታኔ ለመስጠት የተሄደበት ርቀት ሲታይ በአሁኑ ሰዓት ሕጋውያን የሆኑትን ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት ሐዋርያዊ ተልዕኳቸውን ከኤርፖርት ታግተውና
👍10🙏1
ኦርቶዶክስ ተዋህዶ - ‌🇴‌🇷‌🇹‌🇭‌🇴‌🇩‌🇴‌🇽 ‌🇹‌🇪‌🇼‌🇦‌🇭‌🇩‌🇴
Photo
ለሃይማኖታዊ አምልኮ የተሰበሰበውን ሕዝበ ክርስቲያን አዝኖ እንዲበተን በማድረግ ለአንድ አንጋፋና የሀገር ባለውለታ ሊቀጳጳስ የማይመጥን እንግልትና ማዋከብ መደረጉ ሳያንስ ይባስ ብሎ ለሕገወጡ የቡድን አባላት ለአብነትም ያህል በምዕራብ ወለጋ፤ በምሥራቅ ወለጋ፣ በቄለም ወለጋና ሆሮጉድሩ ዞኖች በኦሮምያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት የልዩ ኃይል አባላት ልዩ የፓትሮል እጀባና እንክብካቤ የቤተ ክርስቲያኒቱን ሕጋዊ ተቋማት በሕገወጥ መንገድ ተደፍረው እንዲገቡ፣ የቤተ ክርስቲያኒቱ የአምልኮና የአስተዳደር ተቋማት ተሰብረው በሕገወጥ ቡድኖች እንዲወረሩ መደረጋቸው፤ ይህን ሕገወጥ አድራጎት የተቃወሙትን የቤተ ክርስቲያኒቱን የሃይማኖት አባቶችና የአስተዳደር ሠራተኞች ለእስር እንዲዳረጉ መደረጉ፣ ሕጋዊ የቤተ ክርስቲያኒቱ የአገልግሎት ተሽከርካሪ መኪኖች ለማንኛውም
አገልግሎት እንዳይንቀሳቀሱ፣ በክልሉ መንግሥት አመራር ተሰጥቷል በሚል እገታ መከናወኑ ሲታይ መንግሥታችን ሕገመንግሥታዊ ጥስት በመፈጸም በሃይማኖታዊ ጉዳይ ጣልቃ መግባቱንና በእርሱም ይሁንታ መፈንቀለ ሲኖዶስ እየተከናወነ እንዳለ እምነት የሚያሳድር በመሆኑ ይህ አድራጎት እንዲታረምና መንግሥት ኃላፊነቱን በመወጣት የቤተ ክርስቲያኒቱን ተቋማዊ ልዕልናና መብት እንዲያስከብር ንብረቶቿ በሕገወጥ ቡድኖች ከመወረር እንዲጠብቅ፣ በሕጋዊው ቅዱስ ሲኖዶስ መዋቅራዊ አደረጃጀት መሠረት የቤተ ክርስቲያኒቱ ብፁዓን ሊቃነጳጳሳትና የሥራ ኃላፊዎች ያለምንም እንግልትና የደህንነት ስጋት ተመድበው ሲሠሩባቸው በቆዩበት አህጉረ ስብከት ኃላፊነታቸውን እንዲወጡ መንግሥት አስፈላጊውን ጥበቃና የሕይወት ዋስትና እንዲያረጋግጥ ቅዱስ ሲኖዶስ በጥብቅ ያሳስባል፡፡
፪. ክቡር ጠቅላይ ሚኒስቴሩ ቀደምት ሥርዓተ መንግሥታትን በዋቢነት አሁናዊው የብልጽግና መንግሥት በውጭ የነበረውን የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ ቅዱስ ሲኖዶስ በእርቅ አንድ ማድረጋቸውን ሲገልጹ በሀገር ውስጥ ሁለት መንበርና ሁለት የፕትርክና መሪነት እንደነበረ የሰጡትን ማብራሪያ በተመለከተ፡- በቤተ ክርስቲያናችን አስተዳደራዊ መዋቅር በወቅቱ በነበረው ፖለቲካዊ ሁኔታ የተከሰተውን ልዩነትና የሲኖዶስ መከፈል በእርቀ ሰላም ማለቁ የማይካድ ሐቅ ቢሆንም በተፈጸመው የእርቅ ስምምነት ውሳኔ መሠረት በግልጽ እንደሰፈረው ሁለት ፓትርያርክ በአንድ መንበር ላይ የነበረ ሳይሆን ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ መርቆሬዎስ ፓትርያርክ ክብራቸው ተጠብቆ በጸሎትና ቡራኬ ቅድስት ቤተ ክርስቲያንን በአባትነት እንዲያገለግሉ እንዲሁም ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት ደግሞ የቤተ ክርስቲያኒቱን አስተዳደራዊ የመሪነት ሥራን በአባትነት እንዲመሩ በግልጽ በቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ ተወስኖ በውሳኔው መሠረት ተግባራዊ የሆነና በሁሉም የቤተ ክርስቲያኒቱ መዋቅር የሚታወቀውን እውነታ በሚንድ መልኩ ቤተ ክርስቲያኒቱ በአንድ መንበር ሁለት ፓትርያርክ ሲመራ ቆይቷል ተብሎ የተገለጸበት አካሄድ በእውነታ ላይ የተመሠረተ ሳይሆን
በአሁኑ ሰዓት የቤተ ክርስቲያኒቱን ሃይማኖታዊ፣ ቀኖናዊና አስተዳደራዊ አሠራር በመጣስ በሕገ-ወጥ መንገድ የተፈጸመውን "ሢመተ ጵጵስናና መፈንቅለ ሲኖዶስ ሕጋዊ ሽፋን ለመስጠት የተደረገ ከመሆኑም በተጨማሪ በቅዱስ ሲኖዶስ ውሳኔ ተወግከው የተለዩት ግለሰቦች ቀድሞውንም ሹመቱን ፈጽመን በዕርቅ እና በድርድር አንድ እንሆናለን : በሚል ሲገልጹት የነበረውን ሀሳብ የሚያረጋግጥና አሁንም በድርድር ሃይማኖታዊ መመሪያችሁን ጥሳችሁ ቀኖናዊ ሥርዓታችሁን አፍርሳችሁ፤ አስተዳደራዊ መዋቅራችሁን ንዳችሁ ተቀብሏቸው እንደማለት የሚያስቆጥር ማብራሪያ አዘል መመሪያ እርምት እንዲሰጥበት ቅዱስ ሲኖዶስ ያሳስባል፡፡
፫ ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትሩ በተፈጸመው የእርቀ ሰላም ሂደት ወቅት በውጭ ሀገር የነበሩት አባቶች ሹመታቸው ተቀባይነት አግኝቶ ወደ ሀገር ሊገቡ የቻሉት በየደረጃው አገልግሎት ሲሰጡ በመቆየታቸው ነው በማለት የሰጡትን በተመለከተ፡- በውጭ የነበሩ ብፁዓን ሊቃነጳጳሳት በእርቀ ሰላሙ ወደሀገር ተመልሰው የቅዱስ ሲኖዶስ አባላት ሊሆኑ የቻሉትና ተቀባይነት ያገኙት ሹመታቸው የተከናወነው በቀኖና ጥሰት ሳይኖን በሕጋዊ ፓትርያርክ የተፈጸመ ሲመት ከመሆኑም በላይ በስደት ሊቆዩም የቻሉት በወቅቱ በተፈጠረው የፖለቲካ ጫና እየታወቀና ከአሁኑ ሕገወጥ፣ ሃይማኖታዊ፣ ቀኖናዊና አስተዳደራዊ መሠረት የሌለው ሹመት ጋር ግንኙነት የሌለው ሆኖ እያለ ሕጋዊውን ከሕገወጡ ጋር በማቀላቀልና በማነጻጸር የተሰጠው ማብራሪያ እርምት እንዲሰጥበት ቅዱስ ሲኖዶስ በጽኑ ያሳስባል።
0 ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማብራሪያቸው በቋንቋ የመገልገል መብትን መንግሥት ማፈን አይችልም በማለት የተሰጠው ማብራሪያ በተመለከተ፡- እናት ቤተ ክርስቲያን ዘመን ተሻጋሪ ታሪኳ እንደሚያረጋግጠው የቋንቋ አገልግሎትን በሕጎቿ እውቅና የሰጠች፣ ከዚህም አልፎ በተለይም ግለሰቦች በተደጋጋሚ በሚጠቅሱት በኦሮምያ ክልላዊ መንግሥት ለሚኖሩ የቤተ ክርስቲያኒቱ የእምነት ተከታዮች የቋንቋ አገልግሎት ስትሰጥ የቆየች በመሆኑ በላይ የቤተ ክርስቲያኒቱን
የአምልኮና የሥርዓት መጻሕፍቶች በኦሮምኛ ቋንቋ በማስተርጎም ለአገልግሎት ያበረከተች፣ ሕገወጥ ሹመቱን ከፈጸሙት ሦስቱ የተሻሩት ሊቃነጳጳሳት ጨምሮ በርካታ የቋንቋው ተናጋሪ ብፁዓን ሊቃነጳጳሳትን በክልሉ ባሉ አህጉረ ስብከት መድባ አገልግሎት እየሰጠች የክልሉን ተወላጆች በቋንቋቸው የቤተ ክርስቲያኒቱን እውቀት ቀስመው ለአገልግሎት ብቁ እንዲሆነ መንፈሳዊ ኮሌጆችን በመክፈት፤ በሁሉም አህጉረ ስብከት የካህናት ማሠልጠኛ ተቋማትን አደራጅታ በብዙ ሺዎች የሚቆጠሩ አገልጋይ ካህናት፣ ዲያቆናት፣ እና _ ሰባክያነ ወንጌል አስተምራ ለአገልግሎት አሰማርታ እያለች የቋንቋ አገልግሎትን እንደተቃወመችና ለአገልግሎቱም በሯን እንደዘጋች በሚያስቆጥር ሁኔታ የተሰጠው ማብራሪያ ከእውነታቸው የራቀና የሕገወጥ ሥልጣን ፈላጊዎችን ሕገወጥ አካሄድና መግለጫ እውቅና የሚሰጥ አድራጎት በመሆኑ እርምት እንዲሰጥበት ቅዱስ ሲኖዶስ በጽኑ ያሳስባል።
፭. ለቤተ ክርስቲያን ተሰጠ ስለተባለው ይዞታና ስለ ደብረ ሮሃ ቅዱስ ላሊበላ ውቅር አብያተ ክርስቲያን የተሰጠውን ማብራሪያ በተመለከተ፣ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማብራሪያቸው ከአምልኮ ሥፍራ የመሬት ይዞታ አሰጣጥ ጋር በተያያዘ ለኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ባለፉት አራት ዓመታት ከሌሎች ቤተ እምነቶች በተሻለ መልኩ ከአንድ አንድ ሚሊዬን አርባ አምስት ሺህ ካሜ ይዞታ በላይ እንደተሰጣትና ይህም የይዞታ ስፋት ለሌሎች ቤተ እምነቶች በድምሩ ከተሰጠው በሦስት እጥፍ እንደሚበልጥ እና አዲስ ይዞታ እንደተሰጠ ተደርጎ በማስመሰል የተሰጠው ማብራሪያ ፍጹም ስህተት እና ሕዝብን የሚያሳስት በመሆኑ ሊታረም ይገባል፡፡ ይኼውም ለቤተ ክርስቲያን ተሰጠ የተባለው ይዞታ ቤተ ክርስቲያን ቀድሞውን በእጂ አድርጋ ለዘመናት ስትጠቀምበት የነበረውን ሕጋዊ ይዞታዋ እና ይሄው በካርታ ተረጋግጦ እንዲሰጥ ስትጠይቅ የቆየች ንብረቷ እንጂ እንደ አዲስ በሊዝ አዋጁ መሠረት በምደባ ያገኘችው አይደለም፡፡
👍8👏2
ኦርቶዶክስ ተዋህዶ - ‌🇴‌🇷‌🇹‌🇭‌🇴‌🇩‌🇴‌🇽 ‌🇹‌🇪‌🇼‌🇦‌🇭‌🇩‌🇴
Photo
ምንም እንኳን በተገለጸው ልክ አልተሰጣትም እንጂ ቢሰጣት እንኳን ከአዲስ አበባ ከተማ ነዋሪ ሕዝብ ውስጥ ከ75% በላይ የሚሆነውን የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ እምነት ተከታይ እንደመሆኑ መጠን ከሌሎች ቤተ እምነቶች በተሻለ የሰፋ ይዞታ ማግኘቷ እንደልዩ ጥቅም የሚያስቆጥር አይደለም፡፡
የደብረ ሮሃ ቅዱስ ላሊበላ ውቅር አብያተ ክርስቲያን ከኢትዮጵያ አልፎ የዓለም ቅርስ መሆኑ እየታወቀ፣ የውጪ መንግሥታት በዕርዳታ ለመሥራት ፈቃዳቸውን መስጠታቸው በራሳቸው በክቡር ጠቅላይ ሚኒስትሩም እንደበት የተገለጸ ሆኖ እያለ፣ መንግሥት ቋሚ የገቢ ምንጭ የሚያገኝበት የቱሪስት መዳረሻ መሆኑ እየታወቀ የቤተ ክርስቲያን ሀብት ብቻ ተደርጎ ከፈረንሣይ መንግሥት የተገኘውን ድጋፍ ለቤተ ክርስቲያን እንደተሰጠ ልዩ ጥቅም በማድረግ ማቅረብ አግባብነት የለውም፡፡
፮ ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትሩ በክልል ትግራይ የተከሰተውን ጦርነት ተከትሎ በክልሉ ለሚኖሩ የቤተ ክርስቲያኒቱ አባቶች በወቅቱ ሰጥተውን የነበረውን መግለጫ አንድም ተቃውሞ ሳይቀርብበት አሁን በኦሮምያ ለተከሰተው ይህን ያህል ተቃውሞ አግባብ አይደለም በማለት የሰጡትን ማብራሪያ በተመለከተ፡- በመጀመሪያ ደረጃ በክልል ትግራይ የሚኖሩ የቤተ ክርስቲያኒቱ አባቶች ከሰጡት መግለጫ መረዳት እንደሚቻለው እና መላው ሕዝበ ክርስቲያን እንደሚያውቀው የቤተ ክርስቲያኒቷን ሕጎችና ቀኖናዎች ጥሰው ሕገወጥ ሲኖዶስ አልመሠረቱም፤ ጳጳሳትንም አልሾሙም፣ እውነታው ይህ ሆኖ እያለ አሁን የተፈጸመውን ሕገወጥ ሹመትና መፈንቅለ ሲኖዶስ ሕጋዊ ሽፋን እንዲኖረው ለማድረግ በሚያስመስል ሁኔታ ሁለቱ የማይገናኙ ድርጊቶችን በንጽጽር የተሰጠው ማብራሪያ እርምት እንዲሰጥበት ቅዱስ ሲኖዶስ በጥብቅ ያሳስባል፡፡
በመጨረሻም መንግሥታችን በሕገ መንግሥቱ የተጣለበትን ኃላፊነት በመወጣት የቤተ ክርስቲያኒቱን ተቋማዊ ልዕልና፣ በሕግ የተሰጣትን መብትና ጥቅም በማስከበር ሕገወጡን ድርጊት ተገቢውን እርምት በመስጠት ኃላፊነቱን እንዲወጣ ቅዱስ ሲኖዶስ በጥብቅ እያሳሰበ ይህ የማይሆን ከሆነ ግን ከቅዱስ ፓትርያርኩ ጀምሮ ብፁዓን አበው ሊቃነጳጳሳት፣ የቤተ ክርስቲያኒቱ አገልጋይ ካህናትና ምእመናን ጭምር የሚሳተፉበት ሀገር አቀፍና ዓለም አቀፍ ሰላማዊ ሰልፍ በማካሄድ በደላችንን ለዓለም ሕዝብ ችግሩ ተፈቶ የቤተ ክርስቲያኒቱ መብት እስኪረጋገጥ ድረስ ያለማቋረጥ እስከ ሕይወት መስዋዕትን ድረስ በመክፈል የምናሳውቅ መሆኑን ቅዱስ ሲኖዶሱ ይገልጻል፡፡
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ
ጥር 24 ቀን 2015 ዓ.ም.
አዲስ አበባ
ኢትዮጵያ
👍29👏2
"ጳጳሳት ከአንድ አካባቢ የሆኑ ናቸው የሚሾሙት"
የሚለውን ውንጀላ አስመልክቶ ሲጠየቁ አቡነ ኤርምያስ እንደሚከተለው ብለዋል ...

"ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከመረጣቸው 12 ሐዋርያት መካከል ሁሉም ሐዋርያት ደግሞ ዕብራውያን ናቸው:: ከእነዚህ ሐዋርያት መካከል 9ኙ ከአንድ አውራጃ የተገኙ ናቸው:: ከእነዚህ ደግሞ ጴጥሮስና እንድርያስ ወንድማማቾች ፥ ዮሐንስና ያዕቆብ ወንድማማቾች ናቸው:: እነዚህ ሁሉም ሐዋርያት ከኢየሩሳሌም ተነስተው ወንጌለ ክርስቶስን ለዓለም ሁሉ አስተምረዋል:: ሁሉም ሐዋርያት ዕብራውያን ስለሆናችሁ አንቀበላችሁም ያላቸው የለም:: አሁንም በመንፈሳዊ ዐይን ካየነው በቤተ ክርስቲያናችን የጵጵስና ሹመት መስፈርቱ ሃይማኖት እና ምግባር እንጅ የትውልድ ቦታ አይደለም:: የሆነው ሆኖ ግን ሊቃነ ጳጳሳቱ የአንድ አካባቢ ተወላጅ ሳይሆኑ ከልዩ ልዩ የሀገራችን ክፍል የተገኙ ናቸው::"
👍324
ኦርቶዶክስ ተዋህዶ - ‌🇴‌🇷‌🇹‌🇭‌🇴‌🇩‌🇴‌🇽 ‌🇹‌🇪‌🇼‌🇦‌🇭‌🇩‌🇴
Photo
መረጃ !
---------
"በኢትዮዽያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤ/ክርስትያን ጉዳይ የአምስቱ እህት አብያተ ክርስትያናት ቅዱሳን ፓትርያርኮች በግብጽ ካይሮ ከተማ ሊሰባሰቡ ነው !

የኤርትራ ቅዱስ ሲኖዶስን ጨምሮ የአምስቱ እህት አብያተ ክርስትያናት ቅዱሳን ፓትርያርኮች በኢትዮዽያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስትያን ስም በቅርቡ የተመሰረተውን ህገወጥ ሲኖዶስ እና በቅድስት ቤተክርስትያኗ ላይ የተከሰተውን ፈተና በተመለከተ ምክክር ለማድረግና ውሳኔ ለማሳለፍ በግብጽ ካይሮ ሊሰባሰቡ ነው።

የሚሰባሰቡት ቅዱሳን አባቶችም:-

• የኤርትራ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስትያን ቅዱስ ሲኖዶስ
ዋና ፀሓፊ አቡነ እንደርያስ

• ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ታዋድሮስ ዳግማዊ - 118ኛው
የእስክንድርያ ፓትርያርክ

• ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ካርኪን ዳግማዊ - 132ኛው የመላው
አርማንያ ፓትርያርክ

• ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ባስልዮስ ማርቶማ ማቴዎስ ሳልሳይ -
22ኛው የህንድ ፓትርያርክ

• ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ አግናጤዎስ ኤፍሬም- 122 ኛው
የአንፆኪያና የመላው ሶርያ ፓትርያርክ

አምስቱም ቅዱሳን አብያተ ክርስትያናት በኢትዮዽያ ቅድስት ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስትያን ውስጥ የተፈጠረውን መከፋፈል አውግዘው ከነባሩና ከህጋዊው ቅዱስ ሲኖዶስ ጎን እንደሚቆሙ በመግለጽ ቅድስት ቤተክርስትያኗ የደረሰባትን ክፉ ፈተና በሰላም እንድትሻገር እግዚአብሄርን በፀሎት እንደሚጠይቁም ጭምር ገልፀው ለኢትዮዽያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስትያን ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ማትያስ፣ ለህጋዊው ቅዱስ ሲኖዶስ አባላትና ለመላው ኢትዮዽያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ምዕመናን መልእክት መላካቸው ይታወሳል።

አሁን ደግሞ የአምስቱ እህት አብያተ ክርስትያናት መሪዎች በካይሮው ስብሰባ ተገኝተው በዘርና በቋንቋ የተዋቀረውን በእነ አቶ አካለወልድ (በቀድሞ ስሙ ሳዊሮስ) በተባለው ግለሰብ የሚመራውን ህገወጡን ሲኖዶስ ከማውገዝ ጀምሮ ከእነርሱ ጋር ህብረት ያለው፣ በገንዘብ፣ በምክር እና በሌላ መንገድ ድጋፍ የሚያደርጉ ግለሰቦችን ድርጅቶችን እና ተቋማትን አውግዘው እስከመለየት ድረስ ውሳኔ ያሳልፋሉ ተብሎ ይጠበቃል። "
👍312👏1
2025/07/13 12:00:41
Back to Top
HTML Embed Code: