Telegram Web Link
እግዚአብሔርን የሚያምንና የሚወድ ቢኖር፥ እርሱ በዚህ አንፀባራቂና የደስታ በዓል ደስ ይበለው፡፡ ብልህ አገልጋይ ቢኖር፥ እርሱ ወደ ጌታው ሐሴት ገብቶ ዕልል ይበል፡፡

በጾም የደከመ ቢኖር፥ አሁን ደመወዙን ይቀበል፡፡ በመጀመሪያው ሰዓት ወደ አምላኩ የቀረበ ቢኖር፥ ዛሬ ሽልማቱን ይውሰድ፡፡
በሦስተኛው ሰዓት የመጣ ቢኖር፥ እርሱ በዓሉን በምስጋና ያክብር፡፡  በስድስተኛው ሰዓት የደረሰ ቢኖር፥ አይጎድልበትምና አይጠራጠር፡፡ እስከ ዘጠነኛ ሰዓት የዘገየ ቢኖር፥ ሳይጠራጠር ይቅረብ፡፡ እስከ ዐሥራ አንደኛዋ ሰዓት የዘገየ ቢኖር፥ ስለ መዘግየቱ አይደንግጥ፡፡ ጌታ ቸር ነውና፤ በመጨረሻ የመጣውንም እንደ መጀመሪያው አድርጐ ይቀበሏልና፡፡ በዐሥራ አንደኛው ሰዓት ለመጣው ከመጀመሪያው ሰዓት አንሥቶ ሲደክም ከነበረው ጋራ እኩል ይሰጧልና፡፡
መጨረሻ ለመጣው ጌታ ምሕረቱን ይለግሰዋል፤ መጀመሪያ ለመጣውም ያስብለታል፡፡ ለአንደኛው ይሰጠዋል፤ ለሌላኛውም ጸጋውን ያድለዋል፡፡ ለአንደኛው መልካም ምግባሩን ይቀበልለታል፡፡ ለሌላኛውም መልካም ፍቃዱን ይቀበልለታል፡፡ ለአንዱ ምግባሩን ያከብርለታል፤ ለሌላኛውም በቅን ልቡና የሚያደርገውን ጥረት ያደንቅለታል፡፡ ስለዚህ ኹላችሁም ወደ ጌታችሁ ደስታ ግቡ፡፡

ፊተኞች ኋለኞችም ሆይ! እኩል ደመወዛችሁን ተቀበሉ፡፡ ባለጸጐች ድኾችም ሆይ! በአንድነት ዘምሩ፡፡ እናንተ ብርቱዎች ደካሞችም ሆይ! በዓሉን አክብሩት፡፡ እናንተ የጾማችሁ መጾም ያልቻላችሁም ሆይ! ዛሬ ላይ ደስ ይበላችሁ፡፡
መሠዊያው ሙሉ ነውና ኹሉም በማዕዱ ደስ ይበለው፡፡ ፍሪዳው የሰባ ነውና አንድ ሰው ስንኳ እንደ ተራበ እንዳይሔድ፡፡ ኹላችንም የእምነት በዓሉን እንካፈል፤ ከቸርነቱና ከፍቅሩ ሀብትም እንቋደስ፡፡

ማንም ስለ ድኽነቱ አይዘን፥ ኵላዊቷ መንግሥት ተገልጣለችና፡፡ ማንም በኃጢአቱ አያንባ፥ ከመቃብሩ የይቅርታ ብርሃን ተንቦግቧልና፡፡ ማንም ሞትን አይፍራ፥ የመድኃኒታችን ሞት ከዚህ ነጻ አውጥቶናልና፡፡ ለእርስዋ  በመታዘዝም ጌታ አጥፍቷታልና፡፡
በሞቱ ሞትን ገደለው፡፡ ወደ ሲዖል በመውረድ ሲዖልን በዘበዘው፡፡

ኢሳይያስም አሰምቶ እንደ ተናገረ ሲዖል ከጌታችን ጋር ፊት ለፊት ተገናኘች፤ መረራትም! ከንቱ አድርጓታልና መረራት! ሸንግሏታልና መረራት! ሽሯታልና መረራት!
ነፍሳትን ይዛ እንዳታስቀር አስሯታልና መረራት!
[መቃብር የዕሩቅ ብእሲ] ሥጋ አገኘሁ ብላ ዋጠችው፤  ስትውጠው ግን እግዚአብሔር ኾኖ አገኘችው - መረራትም!

ሞት ሆይ! መውጊያህ ወዴት አለ? ሲዖል፥ መቃብርም ሆይ! ድል መንሣትህ ይዞም ማስቀረትህ ወዴት አለ?
ክርስቶስ ተነሣ፤ ሞት ሆይ፥ አንተም ጠፋህ!
ክርስቶስ ተነሣ፣ አጋንንትም አዘኑ!
ክርስቶስ ተነሣ፤ መላእክትም ሐሴት አደረጉ!
ክርስቶስ ተነሣ፤ የሰው ሕይወትም ነጻ ወጣች!
ክርስቶስ ተነሣ፤ መቃብርም ባዶ ኾነች!
ክርስቶስ ከሙታን ተለይቶ ተነሥቶ ለአንቀላፉት ኹሉ በኵር ኾኖላቸዋልና፡፡

ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ


╭══•:|★✧♡💝♡✧★|: ══╮
  @orthodox1 @orthodox1
  @orthodox1 @orthodox1
  @orthodox1 @orthodox1
╰══•:|★✧♡💝♡✧★|:  ══╯
ምሕዛል ወቃለ ባሕ ዘትንሣኤ [Paschal troparion & Greeting] #የፋሲካ_አመላለስና_ሠላምታ
᳀͟͞ ͟͞ ̸͟͞ ͟͞ ͟͞ ͞ ͟͞ ̸ ͟͞ ͟͞᯼᳀᯼͟͞ ͟͞ ͟͞ ̸͟͞ ͟͞ ✙ ͟͞ ͟͞ ̸͞͝ ͟͞᯼᳀᯼͟͞ ͟͞ ͟͞ ̸͟͞ ͟͞ ͟͞ ͟͞ ̸͞͝ ͟͞᳀

(ለትንሣኤ የተቆነጠረ ሐሳብ)

ሀገርኛው የዘውትር ሰላምታችን ሰላም ላንተ ይኹን👋 ጠላትኽን ያውድቅ ቢሰኛኽን ያርቅ! 🙏 በሚል መነሻ ስብሐተ እግዚአብሔር የሚታከልበት ምኞት መግለጫና ምስጋና ማቅረቢያ ነው!

የሰላምታው መንገድ ደግሞ በሦስት ሂደት (በቃል በእጅና በአንገት) የሚከወን ነው።

🤝
መጨባበጥ (ተራክቦተ እድ ፣ ፅብጠት፣ ተጻብሖ) ☞ በእጅ የሚፈጸም ፦  በመጨባበጥ [handshake] በመተቃቀፍ [hugging] አልያም በጉንጭ በመሳሳም [cheek kissing] ይፈጸም የነበረውን በቀደሙቱ ዘንድ “አምኃ ቅድሳት” [holy kiss & kiss of peace ⇨ ἐν ἁγίω φιλήματι, και φιλί της ειρήνης ] እየተባለ የሚጠራው መንገድ ነው!

በዚኽ አጋጣሚ በወቅቱ ጉዳይ መጨባበጥ መተቃቀፍና መሳሳም ለወረርሽቹ በፍጥነት መዛመት ምክንያት መሆናቸውን አውቀን #አካላዊ_ፈቀቅታ|ን በመጠበቅ በበሽታው የምናልፍ ሳንሆን በሽታውን የምናሳልፍ ነገንም የምናይ እንድንሆን በተከታዮቹ መንገዶች ሰላምታ የምንለዋወጥ ይሁን!

🙇 
"እጅ መነሳሳት" (እማኄ) ☞ ባንገት፣ በወገብና በጕልበት የሚፈጸም ነው።

🙋
የሰላምታ ቃል መለዋወጥ (በቃለ ተአምኆ) ሰላምታ በንግግር በመለዋወጥ የሚፈጸም ዋናዎቹ ናቸው!

ወደተቆነጠረው ሐሳብ እንለፍ ተዝካረ ትንሣኤው በሚታሰብበት ዐባይ ፋሲካ ፶ ዕለት በቤተክርስቲያናችን የሚፈጸም የተለየ ሰላምታና የዜማ ድጋም አመላለስ አለ።

የጌታችን ተዝካረ ትንሣኤ በቤተክርስቲያናችን ሰፊ ቦታና ትርጉም ያለው በመሆኑ የዓመት ሢሦው (⅓) ነገረ ፋሲካን የሚያስታውስ ነው (የፋሲካ ጾም ⁵⁵ እና ዘመነ ትንሣኤ⁵⁰)

በቅዳሴው መግቢያ መስዋእቱ ከቤተልሔም ወደ ቤተ መቅደስ ሲመጣ ከትንሳኤው እስከ በዓለ ፶ ጊዜው የተለየ መሆኑን ለማሳወቅ "እመቦ ብእሲ… " በሚለው መግቢያ ፈንታ "ሃሌ ሉያ ዮሴፍ ወኒቆዲሞስ ገነዝዎ ለኢየሱስ በሰንዱናት ለዘተንሥአ እሙታን በመንክር ኪነ ⇨ ሃሌ ሉያ ዮሴፍና ኒቆዲሞስ ድንቅ በሚሆን ጥበብ ከሙታን ተለይቶ የተነሣ ኢየሱስን በበፍታ ገነዙት፡፡" የሚል መልእክት በዜማ ይደርሳል!

ከዚኽ ውጪ ምሕዛል ዘትንሣኤ ወይም «የፋሲካ አመላለስ» ያልነው [Paschal troparion] እና ቃለ ባሕ ዘትንሣኤ «የፋሲካ ሰላምታ» ያልነው [Paschal Greeting] ከወትሮው በተለየ መንገድ ይፈጸማል። ሁለቱም በልሳነ ጽር (ግሪክ)   #ክሪስቶስ_አኔስቲ / Χριστὸς ἀνέστη እየተባለ ይጠራል።

#ምሕዛል_ዘትንሣኤ [Paschal troparion] የፋሲካ አመላለስ

በእርግጥ ምሕዛል አልያም ምስትሕዛል የሚባለው በድጓው ሊቃውንቱ የሚያስተዛዝሉት ዜማ ድጋም ሲሆን መነሻውን ድጓ ያደረገው በቅዳሴው ክፍል የምናገኘው ይኽ የተዝካረ ትንሣኤ ምስትሕዛል
«ህየንተ ዝውእቱ ጊዜ ባርኮት እምትንሣኤ እስከ በዓለ ፶ » በሚል የገባ ሦስት ጊዜ ደጋግመን በመቀባበል የምናደርሰው " ክርስቶስ ተንሥአ እሙታን ሞተ ወኬዶ ለሞት ለእለ ውስተ መቃብር ወሀበ ሕይወተ ዘለዓለም ዕረፍተ ⇝ ክርስቶስ ከሙታን ተለይቶ ተነሣ ሞቶ ሞትን አጠፋው በመቃብር ላሉ የዘላለም ዕረፍት የሚሆን ሕይወትን ሰጠ "

በሌሎች ምሥራቃውያን (Eastern ) እና ጽባሓውያን (Orientals) ዘንድም በእጅጉ የተለመደ ነው!

በግሪክ ፓስካል ትሮፓርዮን አልያም [χριστος ανεστη] የሚባል በዜማ የሚደርስና የዘመነ ሐዋርያት ጭምር ጥንታዊ መገለጫ አለው ተብሎ የሚታመን ነው።

Χριστὸς ἀνέστη ἐκ νεκρῶν,

θανάτῳ θάνατον πατήσας,

καὶ τοῖς ἐν τοῖς μνήμασι,

ζωὴν χαρισάμενος!

የንባባዊ ፍቺው አማርኛ ትየባ (transliteration) ደግሞ ይኽን ይመስላል!

ክርስቶስ አኔስቲ ኤክ ኔክሮኒ ፣ ታናቶ ታናቶን ፓቲሳስ፣ ኬቲስ ኤን ቲስ ሚ’መሲ፣ ዞይን ካሪዛሜኖስ

በትርጉሙም የእኛው " ክርስቶስ ተንሥአ እሙታን ሞተ ወኬዶ ለሞት ለእለ ውስተ መቃብር ወሀበ ሕይወተ ዘለዓለም ዕረፍተ ⇝ ክርስቶስ ከሙታን ተለይቶ ተነሣ ሞቶ ሞትን አጠፋው በመቃብር ላሉ የዘላለም ዕረፍት የሚሆን ሕይወትን ሰጠ " ካለው ጋር አቻ ፍቺ አለው።

Christ is risen from the dead, Trampling down death by death, And upon those in the tombs, Bestowing life!

#ቃለ_ባሕ_ዘትንሣኤ [Paschal Greeting] «የፋሲካ ሰላምታ»

በሓ ወይም ባሕ የሚባለው የሰላምታ የቡራኬ ቃል ፍሥሓ ሰላም የሚለውን የሚገልጥ ነው!

በቤተክርስቲያናችን አበው መምህራንም ቅድመ ቃለ እግዚአብሔር ፣ ድኅረ ቃለ ቡራኬ ለ፶ው ዕለት ከምእመናን ጋር የሚለዋወጡት ሰላምታ ነው! ከዚያም አልፎ ምእመናንም ከምእመናን ጋር የትንሳኤውን የምሥራች ለማብሰርና መልካም ምኞት ለመግለጥ ያውሉታል።

አቀራረቡ በአመላለስ አገባብ የሚከወን ሲሆን ሰላምታ ሰጪና ሰላምታ ተቀባይ ይኽን ይለዋወጣሉ፤

በኢትዮጵያዊቷ የተዋህዶ ቅድስት ቤተክርስቲያናችም ከ6ኛው ምዕተ ዓመት አንስቶ አገልግሎት ላይ መዋሉን መረጃዎች ይገልጣሉ።  በቅዱስ ያሬድ ምዕራፍ (ዘመወድስ) ውስጥ በፍታሕ ሊተ ሥር በመሪና ተመሪ የሚቀርብ ዛሬ ለፋሲካ ሰላምታ የምንገለገልበት የትንሣኤው ምስክርነት ቃል አለ። እንዲህ ይላል ፦

☞ ክርስቶስ ተንሥአ እሙታን በዓቢይ ኃይል ወሥልጣን አሠሮ ለሰይጣን አግዓዞ ለአዳም ሰላም እምይእዜሰ ይኩን ሰላም!

በመቀባበል እንዲህ ተጽፏል

☞ Christ is risen from the dead!
☜ By the highest power and authority!
☞ He chained Satan!
☜ Freed Adam!
☞ Peace!
☜ Henceforth!
☞ Is!
☜ Joy and Peace!

☞ክርስቶስ ተንሥአ እሙታን!
☜ በዐቢይ ኃይል ወሥልጣን!
☞ አሰሮ ለሰይጣን!
☜ አግዐዞ ለአዳም!
☞ ሰላም!
☜እምይእዜሰ!
☞ ኮነ!
☜ ፍስሐ ወሰላም!

ክርስቶስ በታላቅ ኃይልና ሥልጣን ከሙታን ተለይቶ ተነሣ ዲያብሎስን አሰረው አዳምን ነጻ አወጣው፤ሠላም ከዛሬ ጀምሮ ሰላም ሆነ!

በውጪው ግን ሰጥቶ መቀበል እንጂ አመላለስ የሌለው ባለ አጭር ይዘት ሆኖ በተለያየ ስያሜ የሚጠራ ነው The Paschal Greeting / the Easter Acclamation / The Paschal troparion / Christos anesti…
የበዙቱ የቀደመ መነሻውን ከግሪኩ ተውሰው ሰላምታውንም በሰጣዊ ተሰጣዊ (ሰጪና ተቀባይ) ቃል ልውውጥ ይከውኑታል እንዲህ ሲሉ

#ሰጣዊ ☞ ክሪስቶስ አኔስቲ Χριστός ἀνέστη! Christ is Risen! ✧ ክርስቶስ ተንሥአ እሙታን

#ተሰጣዊ ☜ አሊቶስ አኔስቲ "Ἀληθῶς ἀνέστη! " - "Truly He is Risen!" or "He Has Risen Indeed!" ✧ (አሜን) በአማን ተንሥአ

በአረማይኩ ግን ጥቂት የተሰጣዊ ምላሽ ልዩነት ያለው ሆኖ ይነገራል

☞ ክሪስቶስ ሃሪያቭ ኢ ሜሬሎዝ Քրիստոս հարյա՜վ ի մեռելոց: Christ is risen! ክርስቶስ ተንስሥኣ እሙታን

☜  ኦርኺያል ኤ ኻሮውቲዮን ክሪስቶስ Օրհնյա՜լ է Հարությունը Քրիստոսի: Blessed is the resurrection of Christ!" ቡሩክ ትንሣኤሁ ለክርስቶስ

በሀገርኛ ልሣናት አገባቡ እንዲህ ሊገለጥ ይችላል

⇝ በአማርኛ (☞ ክርስቶስ ተነስቷል ፣ ☜ በእርግጥ ተነስቷል!)

⇝ ኦሮሚፋ /Oromiffa (☞ Kiristoos du'aa ka'eera ፣ ☜ Dhugumaan ka'eera)

⇝ በትግሪኛ (☞ ክርስቶስ ተንሢኡ፣ ☜ በኻቂ ተንሲኡ)

⇝ በጉራጊኛ (☞ ክርስቶስ ተረሳም ፣ ☜ በውረም ተረሳም)
.
.
.
⇨ (በሌሎችም ሀገርኛ ልሳናት የቻላችሁትን ጨምሩበት)



(ከቴዎድሮስ በለጠ ☞ በማዕዶት ፳፻፲፪ ዓ.ም. ተጽፎ በማሻሻያ ለዛሬ በድጋሚ የተለጠፈ )
+++ ጣዖት ምንድን ነው? +++
[እግር ኳስ ጣዖት ነው ወይስ አይደለም?]

«ጣዖት» ለአንድ ነው። ለብዙ ሲሆን «ጣዖታት» ይሆናል። በዕብራውያን ቋንቋ «ጣዑት» ይሉታል። «ጣዖት» ማለት ስሕተት የሆነ ሥራ፣ በቊሙ ግልፎ፥ ስብኮ፣ የጥጃ፥ የእንቦሳ፥ የሰው፥ የእንስሳ ምስል፣ ስሑታን ሰዎች የሚያመልኩት ተብሎ ይተረጒማል። (ኪዳነ ወልድ ክፍሌ መዝገበ ቃላት ሐዲስ)

የመጽሐፍ ቅዱስ መዝገበ ቃላትም «ጣዖት ማለት ከዕንጨትና ከቀለጡ ማዕድናት የተሠራ፣ የማምለኪያ ምስል...» እያለ ይተረጒምና ምእመናን ከጣዖት መራቅ እንዳለባቸው ገልጦ «እግዚአብሔር ከሰጠን ውጭ ሌላ ነገር እንዲኖረን መመኘት ጣዖት ነው» በማለት ደምድሞ አስቀምጦታል።

ይህች ዓለም ጣዖትን ያመለኩ በርካታ ነጋሽ እና አንጋሾችን አፍርታለች። በመጽሐፍ ቅዱስ ታሪክም ይሁን በገድላትና በድርሳናት እንደምናነበው «ሃይማኖታችሁን ካዱ፥ ለጣዖት ስገዱ» በማለት እግዚአብሔርን የሚያመልኩ ደጋግ አባቶችን ሲያሳርዱ የነበሩ ክፉ ጣዖታሞች ነበሩ። አሉ። ለወደፊቱም ይኖራሉ።

እነዚህ ልበ ደንዳኖች ምስል ቀርጸው፣ ጣዖት አቊመው፣ ዕጣን አጢሰው፣ ለምስሉ ሲሰግዱና ሲያሰግዱ በመኖራቸው እንደ ክፋታቸው መጠን በየጊዜው ዋጋቸውን አግኝተዋል። ለወደፊት እነሣለሁ የሚሉም ዋጋቸውን ያገኛሉ።

ጣዖት የምንለው የተቀረጸ ምስል ብቻ አይደለም። እግዚአብሔር የማይከብርበት ከንቱ ሥራ ሁሉ ጣዖት ነው። አንዲት ሴት መልክና ደም ግባቷን በመስታውት እያዬች ዘወትር የምትኮፈስ ከሆነ መልኳ ደምግባቷ ለእሷ ጣዖት ሆኖባታል። አንድ ሰው የዝሙት ልምድ ካለውና ያንን ክፉ ሥራ መልቀቅ ካልሻተ ዝሙቱ ጣዖት ነው። «ወዘመዉ በጣዖቶሙ» እንዲል (መዝ ፻፮፥፴፰)

ወዳጄ በየቤቱ ብዙ ጣዖት ያቆመ አለ። ከሥርዓተ ቤተ ክርስቲያን የሚበልጥበት ራሱ ያቋቋመው ቀኖና ጣዖት ሆኖበት የሚያስቸግረው ስንቱ ነው? ጫቱ፣ ሲጋራው፣ መጠጡ ጣዖት የሆነበት ስንቱ ነው? ዝሙቱ፣ መዳራቱ፣ ውንብድናው፣ ፍቅረ ነዋዩ፣ ጣዖት የሆነበት ስንቱ ነው?

ለዚህ አይደል ሐዋርያው «የጌታን ጽዋና የአጋንንትን ጽዋ ልትጠጡ አትችሉም፤ ከጌታ ማዕድና ከአጋንንት ማዕድ ልትካፈሉ አትችሉም።» (፩ኛ ቆሮ ፲፥፳፩) ብሎ የዘጋው። ቅዱስ ጳውሎስ አድበስብሶ አላለፈም። ይልቊንም «ወዳጆቼ ሆይ፥ ጣዖትን ከማምለክ ሽሹ።» (፩ኛ ቆሮ ፲፥፲፬) ሲል ቊርጥ ያለ ቃል አስቀምጧል። ወልደ ነጐድጓድ ዮሐንስም በመልእክቱ «ልጆች ሆይ፥ ከጣዖታት ራሳችሁን ጠብቁ።» ሲል ያስጠነቅቃል። (፩ኛ ዮሐ ፭፥፳፩)

ከዚህ አንጻር እግር ኳስ ጣዖት ነው አይደለም ብሎ የሚጠይቅ ሰው ካለ ምን ያሕል ሞኝ መሆኑን እንመን። ወዳጄ አንተነትህን ለማያውቅህ ለአውሮጳ ኳስ ተጫዋች ጨርቅህን ጥለህ ስታብድለት እየዋልህ ጣዖትነቱን እንዴት ዘነጋኸው? በቴሌቪዥን ስክሪን አፍጥጠህ ስታይ እያመሸህና አጋንንት እንደተቆጣጠረው ድውይ ልብህ እስኪወልቅ ስትጮህ እያደርህ ጣዖት መሆኑ እንዴት ተረሳህ?

ልብ በል እንጅ! «እግዚአብሔር ከሰጠን ውጭ ሌላ [ባዕድ] ነገር እንዲኖረን መመኘት ጣዖት ነው» ተባልህ'ኮ። ደግሞስ የኳስ ጥቅሙ ምንድን ነው? የሚረባህንና የሚጠቅምህን ሳትይዝ ስለ አውሮጳ እግር ኳስ ልብህ እስኪወልቅ መደገፍ ምን ይሉታል?

አንተ ከድጋፍ (በሌላው ከመደ'ገፍ) ሳትወጣ የአውርጳን ኳስ ትደግፋለህ አይደል? አንተ ከሰው ጫንቃ ሳትወር የሌላው ደጋፊ መሆንህ አይገርምም? እስኪ ወደራሳችን እንመለስ? ሀገር እንዲህ በሰላም እጦት ተወጥራ ከኳስ ጋር ልናብድ ይገባል? መንፈሳውያን ነን የሚሉ ሰዎች ብሰው ሳይ አዝናለሁ።

«ሁሉ ተፈቅዶልኛል፥ ሁሉ ግን የሚጠቅም አይደለም፤ ሁሉ ተፈቅዶልኛል፥ ነገር ግን ሁሉ የሚያንጽ አይደለም።» (፩ኛ ቆሮ ፲፥፳፫)

© ቀሲስ ጌትነት ዐይተነው (ክንፈ ገብርኤል)
ሚያዝያ 18/2015 ዓ.ም
🎍🎍🎍

++ በሰንበት መፍረስ ++

የኢያሪኮ ሰዎች የሠራዊት ጌታ የእግዚአብሔርን ኃይል በመናቃቸው ምንኛ ተጎዱ?!  እርሱ ዓለምን የፈጠረ መሆኑን ስላላመኑ እንዳልተፈጠሩ የሆኑት የኢያሪኮ ሰዎች መጨረሻ እጅግ አሳዛኝ ነበር፡፡

ቅጥራቸው ከመፍረሱ በፊት እስራኤል የእግዚአብሔርን ታቦት ይዘው ለስድስት ቀናት ያህል በዝምታ ኢያሪኮን ዞሯት፡፡ ዓለምን በስድስት ቀናት የፈጠረውን ጌታ እንዲያስተውሉ ስድስት የዝምታ ቀናት ተሠጧቸው፡፡ በሰባተኛው ቀን ግን ጮኹ የኢያሪኮም ቅጥር ፈረሰ፡፡

ሰባተኛ ቀን የዕረፍት ቀን ነው፡፡ ለኢያሪኮ ግን የመፍረስ ቀን ሆነባት፡፡ ሰባተኛ ቀን ፈጣሪን ለሚያምኑ የተቀደሰ ቀን ነበር ፤ ለኢያሪኮ ኝ የመረገም ቀን ሆነባት፡፡
እግዚአብሔር የፈጠረው ሁሉ መልካም እንደሆነ ባየበት ሰባተኛ ቀን ኢያሪኮ ግን ከፉ እንደሆነች ታየባት፡፡

እግዚአብሔር የሌለበት ሕይወት እንዲህ ነው፡፡ ወዳጄ እግዚአብሔር በሕይወትህ ውስጥ ከሌለ የሰንበት ቀን የነፍስህ ዕረፍት ቀን መሆኑ ይቀርና እንደ ኢያሪኮ የመፍረስ ቀን ይሆናል፡፡ በዚያ ቅዱስ ቀን ቅጥርህን በመጠጥ ፣ ብስካር ብዝሙት ስታፈርስ ትውልና ታድራለህ፡፡ ራስህን አንድደህ ትሞቃለህ ፤ እያራገብህ ትቃጠላለህ፡፡ ታቦት ይዘው ቢዞሩህም የኃጢአት ግንብን አጥረሃልና አትሰማም፡፡ በላይህ ላይ ቢቀደስብህም እንደ ኢያሪኮ ሰዎች ካህናቱን እያየህ ‘ዝም ብሎ መዞር ምንድር ነው?’ እያልክ ትስቃለህ፡፡ የካህናቱ የቅዳሴ ዜማ ለአንተ የሚያፈርስ ጩኸት ይሆንብሃል፡፡ የኢያሪኮ ሰው ከመሆን ፣ በሰንበት ፈራሽ ከመሆን ያድንህ!

ቅዳሴያችን መካከል ካህኑ ዕጣን እያጠኑ ዞረው ሲመለሱ የዚህች አጭር ጽሑፍ መነሻ ሃሳብ የሆነውን ይህንን ጸሎት ይጸልያሉ፦  አምላካችን እግዚአብሔር ሆይ አስቀድመህ በባሪያህ በነዌ ልጅ በኢያሱ እጅ የኢያሪኮን ግንብ እንዳፈረስከው የእኔንና የሕዝብህን የኃጢአታችንን ግንብ አፍርሰው፡፡

ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ

https://www.tg-me.com/joinchat-AAAAAEILHwyFiBuqHNVyRw
#መፆር_እምዕፀወ_ሊባኖስ (የሊባኖስ እንጨቶች ዙፋን ) ቅድስት ድንግል ማርያም!

በወንጌል "ዕፅ ሰናይ ፍሬ ሰናየ ይፈሪ" (ማቴ ፯፥፲፯) እንዳለው ከመልካም ዛፍ ቤተሰብ የተኘች ምግባረ መልካም ደምግባተ ቀና፣ የሊባኖሷ ብላቴና አማናዊት መፆር (ዙፋን) እግዝእትነ ማርያም ናት! እርሷ ፆረቶ በከርሳ ፣ፆረቶ ዲበ ዘባና ፆረቶ ዘኢይፀወር እያሉ ሊቃውንቱ የሚያወድሷት ለአምጻኤ ዓለማት መፆሩ ፣ ለመጋቤ ዓለማት አገሩ ፣ ለአኅላፌ ዓለማት መንበሩ ናት!

♧ በሰቆቃ ወድንግል "አብርሂ አብርሂ ናዝሬት ሀገሩ ንጉሥኪ በጽሐ ዘምስለ ማርያም መፆሩ። … ናዝሬት ሀገሩ አብሪ አብሪ ከዙፋኑ ማርያም ጋር ንጉስሽ ወዳንቺ ደርሷልና" ተብላለች፤

♧ በሰአታቱ ገነይነ ለኪ እና ኵሎሙ ዘእግዝእትነ ምስጋናው አፈ ሊቃውንት አባ ጊዮርጊስ
♢ "ሐዳስ መቅደስ መፆረ ንጉሥ። ወላዲቱ ለኢየሱስ።… አዲሲቷ መቅደስ የንጉስ ዙፋኑ ለኢየሱስ ወላዲቱ " ብሏታል፤
♢ "አንቲ ውእቱ ለንጉሠ ነገሥት መፆሩ ለአዳም ተድላ መንበሩ ብኪ ተመይጠ ኅበ ዘቀዳሚ ማኅደሩ።… ለነገሥታቱ ንጉሥ ዙፋኑ ፣ ለአዳም ወደቀደመ ማደሪያው መመለሻ የደስታው ማረፊያ አንቺ ነሽ" ሲል ይገልጣታል፤

♧ የተአምረ ማርያማችን መቅድም "አልቦ ዘፆረ እሳተ ወአልቦ ዘኢገብረ ኅጢአተ እንበለ እግዝእትነ ማርያም። … ከእመቤታችን በቀር ኀጢአትን ያልሠራ ለእሳት ዙፋን የሆነ የለም " ይለናል

♧ ውዳሴ ማርያም ከአንቀጸ ብርሃንና ከቅዳሴው ጋር በምስጢር እየተሳሰረ "ማዕጠንት ዘወርቅ እንተ ፆርኪ ፍሕመ እሳት … የእሳተ መለኮት ዙፋን የወርቅ ማዕጠንት" ይላታል።

♧ የመልክአ ቁርባን ምስጋናም "ናዛዝትነ እምኃዘን ወኃይለ ውርዙትነ እምርስዓን በማኅፀንኪ ተፀውረ ብሉየ መዋዕል ሕፃን።… ከሃዘን የምታረጋጋ መጽናኛችነን፣ ከድካም የምታበረታን የወጣትነት ኃይላችን ፣ ዘመኑ ጥንት የሆነው ሕፃን ማኅፀንሽን ዙፋን አድርጎ አደረ" እንላታለን።

#መፆረ_ገብረ_ለርእሱ (ለራሱ ዙፋን ሰራ)

ይህንን በመሰለው ምሥጢር ውስጥ የተገለጡ ሁለት ፍሬ ነገሮችን እንመርምር

፩ ለራሱ ዙፋኑን የሠራት ራሱ ነው!

ይችን ወላዲተ ቃል መሠረተ ንጽሕ ድንግል
በዚህም በአባት ዘር ከሚመጣ ቁራኝነት በእናት ደም ከሚያርፍ የመርገም ጽነት ለይቶ እኩያት ፍትወታት ኀጣውእ ሳይደርሱባት ራሱ ሠራት ቅዱስ ያሬድ "ማርያምሰ ተሐቱ ውስተ ከርሱ ለአዳም ከመ ባሕርይ ፀዓዳ … ማርያምስ በአዳም ገላ ውስጥ እንደ ነጭ እንቁ ታበራ ነበር " እንዳላት
ቅድስናዋ የመመረጥ አንድም እንድትመረጥ ሆና በተገባ ለመገኘት ጽናት ያለበት ነውና! ሊቁ "አቀባ መንፈስ ቅዱስ እምከርሰ እማ" ያለውን እንዲህ አብራርቶታል "የበጎ ዕድል ፈንታ ጽዋ ተርታ የሚሆን እግዚአብሔር ብዙ ስጦታ ከብዞች መናፍስት የሚቀዳ አይደለም ካንድ መንፈስ ነው እንጂ የክፉ ዕድል ፈንታ ግን የሚገኝ ከሰይጣን ነው፡ እንዳትበድል ድንግልን ከናቷ ሆድ ጀምሮ የጠበቃት መንፈስ ቅዱስ እንዳትረክስም ያነጻት ለወልድ ዋህድም ማደሪያ ያደረጋት እርሱ ነው፡፡ አብ ወደዳት ወልድ ከርሷ ሥጋ ለበሰ መንፈስ ቅዱስ ጋረዳት፡፡ "

፪ ራሱ የሠራት ለራሱ ዙፋንነት ነው!

ይኽችን የንጉሥ ዙፋን የአብ ሙሽራ (መርዓቱ) ፣ የወልድ እናት (ወላዲቱ)፣ የመንፈስ ቅዱስ እልፍኝ (ጽርሐ ቤቱ) ከሰማይ ከወረደ ቃል በቀር ሌላ አድሮባል እንዳያሰኝ "ወትረ ድንግል ማርያም" ብለን እንድናምን እና ድንግሊቱ "ብቻ መውለድን ቀምሶ አቀመሰኝ" እንዳለች ከእርሱ ውጪ ሌላ ልጅ እንደሌላት "እምድኅረ ወለደት ኪያሁ ነበረት በድንግልና" ብለን እንድንመሰክር ዙፋኑን ለራሱ ሠራ ይላል።

ሁለቱ የሊባኖስ እፀው ቅድስት ሀናና ቅዱስ ኢያቄም መሰላቸውን ሳይተኩ በመቆየታቸው ያዘኑት ሐዘን ማንም የማይተካትን የዓለም ሁሉ መክበሪያ አስገኘ! ይህስ ሐዘን የፍጥረት ሁሉ ሐዘን ነበር ዳግሚት ሰማይ ዳግሚት ምድር በመውለድ ደስታቸውን ወደ መካፈል አሳደጉን ከዚቁ ይህን ብለን የዛሬውን በዛሬ እንቋጭ፦

" አዕሩግ አመ በከዩ ብካየ
ረከቡ ወለተ ዘታሥተሰሪ ጌጋየ
ለወንጌላውያን ኩልነ ዘኮነተነ ምጉያየ
ኢያቄም ወሀና ወለዱ ሰማየ
ሰማዮሙኒ አሥረቀት ፀሐየ
ምስራቀ ምስራቃት ሙፃዕ ፀሐይ
እግዝእትየ ዘመና ሙዳይ
ተወልደት ዮም ዳግሚት ሰማይ "
አረጋውያኑ ― በእጅጉ ቢያለቅሱ፣
በደል በምታርቅ ― በሴት ልጅ ተካሱ፤
ለወንጌልም ልጆች ― መሸሻቸው ካለም ፣
ሰማይን ወለዱ ― ሃናና ኢያቄም ፣
ሰማይዋም (ሰማዯም) ፀሐይን ― አውጥታለች ለዓለም፤
የምሥራቃት ምሥራቅ ― መውጫዋ ለፀሐይ ፣
የፍጥረት እመቤት ― የመናዋ ሙዳይ ፣
ዛሬ ተወለደች ― ዳግማዊቷ ሰማይ ።

⊙✧⇥ ይቆየን !

ከቴዎድሮስ በለጠ ( ክፍለሥላሴ)
Яερ๑รтεδ ƒя๑๓፦ ግንቦት ፩ ቀን ፳፻፲ ዓ·ም ከደብረ እንቊ ልደታ ለማርያም
«ተውኔተ ጵጵስና ☞ የጵጵስና ጨዋታ»
✥ °°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°° ✥

የኩላዊት ቤተክርስቲያናችንን ትውፊት [παραδοσις] ትምህርት [διδασκαλια] እና እምነት [πιστις] ከመነሻው ስንመለከት በክርስቶስ የተሠጠ በሐዋርያት የተሰበከና በአበው የተጠበቀ መንገድ ነው። በዚህም ቤተክርስቲያን ተመሠረተች!【ቅዱስ አትናቴዎስ ሐዋርያዊ】

በቀደመው ዘመንማ የገሃዱ ሢመት ቀርቶ የሕጻናቱ ተውኔት እንኳ ደርዝ ነበረው!

በክርስትና ማኅተም ያልከበርክ
እንዴት ለጵጵስና ተመረጥክ? 【አባ ጊዮርጊስ】

ዛሬ ግንቦት ፯ ቀን በሃይማኖት የተዋቀረ ፦ የማይናወጥ መሠረት፣ የማይፈርስ ግድግዳ ፣ የማያዘነብል ምሰሶ የተባለ ቅዱስ አትናቴዎስ ሐዋርያዊ ፳ኛው የኢትዮጵያና የግብፅ ፓትርያርክ በ፬፻፸፬ ዓ.ም. ከሥጋ ድካም ያረፈበትን ቀን ቤተክርስቲያናችን ትዘክራለች። ይህ የምሥጢር ምንጭ የጉባኤ ኒቅያ አፈ ጉባኤ ደገኛው መምህር ቅዱስ አትናቴዎስ ሐዋርያዊ ለ፵፯ ዓመት በፕትርክና ሲቆይ ሢሦውን 【፲፭ ዓመት】በስደት ነበር ያሳለፈው።

ለኢትዮጵያ ቤተክርስቲያን የመጀመሪያውን ጳጳስ ቅዱስ ፍሬምናጦስን【አባ ሰላማ ከሣቴ ብርሃንን】የሾመልን ባለውለታችንና በመንበረ ማርቆስ የተቀመጠ ፳ኛው ፓትርያርካችን ነው። («ወማርቆስ ወንጌላዊ ‘ወኮነ ሰባኬ ወመጥምቀ ወሠያሜ ካህናት’ በእስክንድርያ ወግብፅ ወኖባ ወምድረ ኢትዮጵያ እስከ ጽንፋ» እንዲል መጽሐፈ ግጽው ምዕራፍ ፩ ቁጥር ፲፩ )

ቅዱስ አትናቴዎስ ወደ ክርስትናው የመጣበትና ለጵጵስና የበቃበት መንገድ እጅጉን የሚደንቅና አስተማሪ ነው። ስንክሳራችን በቀደመ ሕይወቱ ከአረማውያን ቤተሰብ የተገኘ አረማዊ እንደነበርና ለመጠራቱ ምክንያት ስለሆነች «የጵጵስና ጨዋታ» እንዲህ እያለ ይነግረናል

ውእቱ ይነብር ምስለ ሕፃናት እለ ይትሜህሩ ኀበ መምህር ርእዮሙ ለእሙንቱ ውሉደ ክርስቲያን እንዘ ይገብሩ ሥርዓተ ቤተ ክርስቲያን ወይትዋነዩ በበይናቲሆሙ ወይረስዩ እምኔሆሙ ዲያቆናተ ወኤጲስ ቆጶሳተ አደሞ ተላህዮቶሙ። ሰአሎሙ ዝንቱ አብ ለውሉደ ክርስቲያን ከመ ይሳተፍ ምስሌሆሙ በተላህዮቶሙ። ወከልእዎ ወይቤልዎ እስመ አንተ አረማዊ ኢንዴመር ምስሌከ ወይቤሎሙ ውእቱ አነ እከውን ክርስቲያናዌ ወተፈሥሑ ቦቱ።

【 እርሱም ከመምህር ከሚማሩ ሕፃናት ጋራ እያለ እርስ በርሳቸው በመጫወት ሥርዓተ ቤተ ክርስቲያን እየሠሩ ከእነርሱ ውስጥ ዲያቆናትን ኤጲስ ቆጶሳትንም ሲያደርጉ እሊያን የክርስቲ ያንን ልጆች አይቶ ጨዋታቸው ደስ ስለአለው ከእሳቸው ጋራ በጨዋታቸው አንድ ይሆን ዘንድ የክርስቲያንን ልጆች ለመናቸው። እነርሱም አንተ አረማዊ ነህና ከእኛ ጋራ አትደመርም ብለው ከለከሉት እርሱም ክርስቲያን እሆናለሁ አላቸው እነርሱም ደስ ተሰኙበት።】

ወነሥእዎ አሜሃ ወረሰይዎ አምሳለ ሊቀ ጳጳሳት ወመትሕቲሁ አምሳለ መንበር። ወእኀዙ ይስግዱ ሎቱ ወበውእቱ ጊዜ ኀለፈ አባ እለእስክንድሮስ ሊቀ ጳጳሳት። ወሶበ ርእዮሙ ለውሉደ ክርስቲያን እንዘ ይትዋነዩ ይቤሎሙ ለእለ ሀለዉ ምስሌሁ ወለዎ ለዝንቱ ሕፃን ይሠየም ሢመተ ክብርተ ወልዕልተ።
【ያን ጊዜም ወስደው በሊቀ ጳጳሳት አምሳል አደረጉት ከበታቹም ወንበር አድርገው ይሰግዱለት ጀመር። በዚያን ጊዜም ሊቀ ጳጳሳት አባ እለእስክንድሮስ በዚያ አለፈ የክርስቲያን ልጆች ሲጫወቱ በአያቸው ጊዜ አብረውት ላሉ ይህ ሕፃን ከፍ ከፍ ያለችና የከበረች ሹመትን ይሾም ዘንድ አለው አላቸው።】

ወንድማለም እንግዲህ ስማ መሾም ስለምትፈልግ ብቻ አትሾምም! እንኳን ሢመቱ ጭውውቱም ቢሆን ሥርዓት አለው። እንዳየኸው ጥንቱን የገሃዱ ሢመት ቀርቶ የሕጻናቱ ተውኔት እንኳ ደርዝ ነበረው! መጽሐፉም ቢሆን እንኳን ራስህን በቦታው ልታስቀምጥ በቦታው ተቀመጥ እንኳ ቢሉህ እምቢኝ በል ነው የሚል።
【"ኢመፍትው ለመኑሂ እምሰብእ ይምሥጥ ሢመተ ክህነት ለርእሱ አላ ለእመ ተውህበ እምእግዚአብሔር ☞ #የክህነትን_ሹመት ከእግዚአብሔር ካልተሠጠው በቀር ከሰው ወገን ማንም ለራሱ ይገባኛል ብሎ ቀምቶ እጅ አያድርጋት" መጽሐፈ ኪዳን ካልዕ ፩፥፷፩】

ዛሬ የሕጻናቱን ያኽል ድፍረት አጥተን መሰል እምነት የሌለው ኢጥሙቅ ልብሰ ጵጵስና ለብሶ ሲተውን አይተን ዝም ከማለት አለፍንና በበር ያልገቡ «መስኮተኞች» አይደለም ጵጵስናው ፕትርክናውም ሳይቀር ይገባናል ሲሉ እየሰማን «ሃይ–ባይ» አለመገኘቱ በእጅጉ ያሳዝናል። «ኧረ ተዉ» የሚል መገስጽ ብቅ ሲል ተቆጪውን መቆጣት ከመንገድ ማጥፋት ሥራችን ሆኖ አረፍነው።

ኧረ ጉድ የዚያ ዘመን የእስክንድርያ ሕጻናት እንዴት አድርገው እንደሚበልጡን እዩልኝማ

«ሰአሎሙ ዝንቱ አብ ለውሉደ ክርስቲያን ከመ ይሳተፍ ምስሌሆሙ በተላህዮቶሙ። ወከልእዎ ወይቤልዎ እስመ አንተ አረማዊ ኢንዴመር ምስሌከ ☞ #እሊያን_የክርስቲያን ልጆች አይቶ ጨዋታቸው ደስ ስለአለው ከእነርሱ ጋራ በጨዋታቸው አንድ ይሆን ዘንድ የክርስቲያንን ልጆች ለመናቸው። እነርሱም አንተ አረማዊ ነህና ከእኛ ጋራ አትደመርም ብለው ከለከሉት »

እንዲህ ያለውን ጨዋታ ወዳጅ ፡ አልፎ ሂያጅ «ና ግባና ጰጵስ» ለሚሉ ድንበር አፍራሾች እንዲህ ባለው የሌባ መንገድ እንዳልመጣ የምናውቀው ራሱ ቅዱስ አትናቴዎስ በድርሳኑ "ንሕነሰ ኢንኌልቆ ምስለ ክርስቲያን አላ ምስለ አረሚ ወዐላውያን ☞ እኛ ግን እንዲህ ያለውን ከማያምኑና ከሚያምጹት እንጂ ከክርስቲያን ወገን እንኳ አንቆጥረውም!” እያለ ይዘልፋል 【ሃይ አበው ፳፱፥፲፭】

አባ ጊዮርጊስ የመንፈስ ቅዱስ ሥጦታና የእግዚአብሔር ምርጫ የሆነውን ሹመት በራሱ ጳጳስ ነኝ ይገባኛል ለሚል ንሥጥሮሳዊ በላከው ተግሳጽ ይህን ይላል ፦

እፎ ተኀረይከ ለጵጵስና ?
ዘኢተቀደስከ በማኅተመ ክርስትና
እፎ ተኀረይከ ለተክህኖ ?
ዘኢተሠርጎከ በተአምኖ
【በክርስትና ማኅተም ያልከበርህ ለጵጵስና እንዴት ተመረጥህ፡ በመታመን ያልተሸለምህ ሆይ እንደ ምን ለክህነት አገልግሎት ተመረጥህ ?】
【መጽሐፈ ምሥጢር ምዕራፍ ፬ ቁጥር ፲፮】

«ወአንተሰ ተመሰልከ ተክለ ዘእንበለ ፍሬ: ወዖመ ዘእንበለ ቈጽል: ፈለገ ዘእንበለ ውሒዝ : ወዐዘቅተ ዘእንበለ ማይ፡ ንጉሠ ዘእንበለ ጌራ መንግሥት : ሐራዌ ዘእንበለ ንዋየ ሐቅል : ደመና ዘእንበለ ዝናም : ወሰዊተ ዘእንበለ መስበልት : አበ ዘእንበለ ሀብተ ሲሳይ : ወእመ ዘእንበለ አጥባት : ንድቀ ዘእንበለ ተድባብ : ወኆኅተ ዘእንበለ ማዕፆ : መርዓዌ ዘእንበለ አክሊል : ወመርዓተ ዘእንበለ ባዝግና : ካህነ ዘእንበለ ኤፉድ : ምሥዋዐ ዘእንበለ ቊርባን : ኖትያዌ ዘእንበለ ሥርዐተ ሐመር : ወምሥያጣዌ ዘእንበለ ንዋይ : ሠረገላዌ ዘእንበለ ድርዐ ሐጺን : ወፈረሳዌ ዘእንበለ ኲያንው! እፎ ተኀረይከ ለጵጵስና ? ዘኢተቀደስከ በማኅተመ ክርስትና ፣ እፎ ተኀረይከ ለተክህኖ ? ዘኢተሠርጎከ በተአምኖ »
☞ አንተ ግን ፍሬ በሌለው ተክል ፣ ቅጠል በሌለውም ዛፍ ፣ ፈሳሽ በሌለው ወንዝ ፣ ውኃ በሌለው ጉድጓድ ፣ የመንግሥት ዘውድ በሌለው ንጉሥ ፣ የጦር መሣሪያ በሌለው ወታደር ፣ ዝናም በሌለው ደመና ፣ ፍሬ በሌለው እሸት ፣ ለምግብ የሚሆን ሀብት በሌለው አባት ፣ ጡቶች በሌላት እናት ፣ ጣሪያ በሌለው ሕንፃ፡ መዝጊያ በሌለው ደጃፍ፡ አክሊል ባልደፋ ሙሽራ ፣ ጌጥ በሌላት ሙሽሪት፣ ልብሰ ተክህኖ በሌለው ካህን ፣ ቁርባን በሌለው መሠዊያ ፣ የመርከብ ሥርዓት በማያውቅ ዋናተኛ ፣ ገንዘብ በሌለው ገበያተኛ ፣ የብረት ጥሩር በሌለው ባለሠረገላ፣ ጦሮች በሌሉት ፈረሰኛ ትመሰላለህ ! በክርስትና ማኅተም ያልከበርህ ለጵጵስና እንዴት ተመረጥህ? በመታመን ያልተሸለምህ ሆይ እንደ ምን ለክህነት አገልግሎት ተመረጥህ?

Let us look from the beginning at that very tradition, teaching, and faith of the «Orthodox Church» which the Lord gave (εδωκεν), the apostles preached (εκηρυςαν) and the Fathers preserved (εφυλαςαν). Upon this the Church is founded. 【Athanasius of Alexandria (First Letter to Serapion, 28)】

በቃን ማለት አልቻልንበትምና ሥሉስ ቅዱስ ራሱ በቃችሁ ይበለን!

ከቴዎድሮስ በለጠ ☞ ግንቦት ፯ ቀን ፳፻፲፭ ዓ ም 📍ከሀረር መካነ ሥላሴ ካቴድራል
መምህራችን ክቡር ቀሲስ ኅብረት የሺጥላ (Hibret Yeshitila Hibret) ከዛሬ 10 ዓመት በፊት ያጋሩን ጽሑፍ ነው! በየዓመቱ እንደ አዲስ የሚነበብና ባለብዙኅ ምሥጢር ትምህርት በመሆኑ ተደጋግሞ እንዲነበብ አጋርቻለሁ!
በጎ ጾም መልካም ንባብ ያድርግልን!

✮༒✮ #ጾመ_ሐዋርያት ✮༒✮

(በቀሲስ ኅብረት የሺጥላ)

በየዓመቱ በዕለተ ሰኑይ ብቻ (ሰኞ ቀን ብቻ) የሚጀምሩ ሦስት አጽዋማት አሉ፡፡ እነርሱም ዓቢይ ጾም፣ ጾመ ነነዌ እና ጾመ ሐዋርያት ናቸው፡፡
እነዚህ አጽዋማት ምን ጊዜም ቅበላቸውእሁድ ሲሆን የሚገቡት ደግሞሰኞ ቀን ነው፡፡

በየትኛውም ዓመት ይህን ዕለት አይለቁም፡፡ ስለዚህ የ2004 ጾም ሐዋርያት ግንቦት 27 ሰኞ ዛሬ ተጅምሯል ፡፡ (ጽሑፉ የተለጠፈበትን ዓመት ያመለክታል ለዘንድሮው ሰኔ 1 ዛሬ ሰኞ) ቤተ ክርስቲያናችን ያለችበትን ነባራዊ ሁኔታ ከግምት ውስጥ በማስገባት፣ በየግላችንም ያጋጠሙንን መንፈሳዊና ሥጋዊ ውጊያዎች በማሰብ ድል የምናደርግበትን ኃይል ፈጣሪያችን ይሰጠን ጾሙን ከወትሮው በበለጠ ጥንቃቄ ልንጾመው ይገባናል፡፡

የጾሙን ታላቅነት ተረድተን እንድንጾመው የትመጣውን፣ ትንቢቱን፣ ምሳሌውንና ምሥጢሩን መረዳት አጋዥ ስለሚሆነን አስቀድመን ስለጾሙ እንማር ዘንድ በአጭሩ አቅርቤዋለሁ! የምችለውን ያህል እጽፍ ዘንድብርታቱንና ጥበቡን የሰጠኝ አምላከ ቅዱሳን ሐዋርያት ክብር ምስጋና ይድረሰው! አሜን!

ጾመ ሐዋርያት በራሳቸው በሐዋርያት የተጀመረ ጾም እንደመሆኑ መጠን በአንደኛው መቶ ክፍለ ዘመን ማለትም ከዛሬ አንድ ሺህ ዘጠኝ መቶ ዓመታት በፊት ጀምሮ ሲጾም የኖረ ጾም ነው፡፡ ለዚህም የመጽሐፍ ቅዱስ፣ የአዋልድ መጻሕፍትና የታሪክ በርካታ ምስክሮች አሉ ስለዚህ ጾሙን እንደ እንግዳ ነገር መቁጠርና ዘመን አመጣሽ አድርጎ ማየት የራስን አላዋቂነት ያሳያል፡፡ ይህን ማለት ያስፈለገው ጥቂቶች ጾሙን ድሮ ያልነበረና ዘመን አመጣሽአድርገው ስለሚናገሩ ነው፡፡
ጾመ ሐዋርያት ቤተ ክርስቲያን ዕድሜያቸው ለጾም የደረሱ ምእመናን በሙሉ እንዲጾሙአቸው ካወጀቻቸው ሰባት የአዋጅ አጽዋማት መካከል አንዱ ነው፡፡ ከዚህም በተጨማሪ በጌታችንና በአምላካችን በኢየሱስ ክርስቶስ አንደበት ቀን የተቀጠረለት፣ ትንቢት የተነገረለትና ምሳሌ የተመሰለለት ጾም መሆኑ ከአጽዋማት ሁሉ ለየት ያደርገዋል፡፡

ጌታችን ስለዚህ ጾም ትንቢተ በመናገር፣ ምሳሌ በመመሰል ሰፊትምህርት የሰጠው ፈሪሳውያን ወደ እርሱ ቀርበው ‹‹ደቀ መዛሙርትህ የማይጦሙት ስለ ምንድር ነው?›› ብለው በጠየቁት ጊዜ ነው፡፡ እርሱም ሲመልስ እንዲህ አላቸው፡- ‹‹ሚዜዎች ሙሽራው ከእነርሱ ጋር ሳለ ሊያዝኑ ይችላሉን? ነገር ግንሙሽራው ከእነርሱ የሚወሰድበት ወራት ይመጣል፤ በዚያ ጊዜም ይጦማሉ፡፡ በአረጀ ልብስ አዲስ እራፊ የሚያኖር የለም፤ መጣፊያው ልብሱን ይቦጭቀዋልና፤ መቀደዱም የባሰ ይሆናል፡፡ በአረጀ አቁማዳ አዲስ የወይን ጠጅ የሚያኖር የለም፤ ቢደረግ ግን አቁማዳው ይፈነዳል፤ የወይን ጠጁም ይፈሳል፡፡ አቁማዳውም ይጠፋል፡፡ ነገር ግን አዲሱን የወይን ጠጅ በአዲስ አቁማዳ ያኖረዋል ሁለቱም ይጠባበቃሉ፡፡›› (ማቴ9.14-17)

በመቀጠል እስከ መጨረሻ የምንመለከተው ከላይ የሰፈረውን የማቴዎስ ወንጌል አጭር ገጸ ንባብ ሐሳብ በመሆኑ መለስ እያሉ
ታሪኩን ማንበብ ወይም በልብ ከመዘገቡ በኋላ ቀጣዩን ክፍል ማንበብ ምሥጢሩን ለመረዳት ያግዛል፡፡
በዚህ የጌታችን መልስ ውስጥ ‹‹ነገር ግን ሙሽራው ከእነርሱ የሚወሰድበት ወራት ይመጣል በዚያ ጊዜም ይጦማሉ፡፡›› የሚል ስለጾመ ሐዋርያት የተነገረ የትንቢት ቃል እናገኛለን፡፡ ይህ አምላካዊ ቃል ጾሙ ስለሚጀመርበት ወራት ቀጠሮ ይሰጣል፡፡ ያም ጊዜ ሙሽራው ከእነርሱ ከተወሰደ በኋላ ያለው ጊዜ ነው፡፡ ‹‹ሙሽራው ከተወሰደ›› በኋላ ማለት ኢየሱስ ክርስቶስ ወደ ሰማይ ካረገ በኋላ ማለት ሲሆን በቤተ ክርስቲያን ጾመ ሐዋርያት ከዕርገት በኋላ የሚጀምረው በዚህ ቃል ምክንያት ነው፡፡ ይህም ቤተ ክርስቲያን ምን ያህል መጽሐፍ ቅዱሳዊ መሠረት ያላት መሆኗን ያሳያል፡፡
ጾመ ሐዋርያት ከዕርገት በኋላ ለዐሥር ቀናት ያህል ዘግይቶ እንጂወዲያው አይጀምርም ምክንያቱም የሐዋርያት ሰውነት በአዲስ ሁኔታ ጌታችን ላዘጋጀው የአዲስ ኪዳን ጾም ተመቻችቶ ያልተገኘ በመሆኑ ነው፡፡ ስለዚህ በመጀመሪያ የሐዋርያት ሰውነት ለጾሙ መዘጋጀት ነበረበት፡፡ ከዚያ በኋላ ሐዋርያት መጾም ጀምረዋል ይህም በጌታችንን የመልስ ቃል ውስጥ የተካተተ እንጂ የፈጠራ ድርሰት አይደለም፡፡ ‹‹በአረጀ ልብስ ላይ››እና ‹‹በአረጀ አቁማዳ›› የሚሉት ሁለት ተከታታይ ምሳሌያዊ ማብራሪያዎች ሐዋርያት ሰውነታቸው በመንፈስ ቅዱስ ከመታደሱ በፊት ጾም መጾም እንደማይጀምሩ ወይም እንደሌለባቸው የሚያስረዱ ምሳሌዎች ነበሩ፡፡ ስለዚህ ሐዋርያት የተዘጋጀላቸውን ጾም መጾም የጀመሩት ከኢየሱስክርስቶስ ዕርገት በኋላ በዐሥረኛው ቀን በወረደ ጸጋ መንፈስቅዱስ የሕይወት ሕድሳት አግኝተው ነው፡፡

ከላይ በተጠቀሰው የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ትምህርት ውስጥ ስለጾመ ሐዋርያት የቀረቡ ሦስት ዓይነት ምሳሌዎችን እናገኛለን፡፡ ምሳሌዎቹ በምሥጢር የተሞሉ በርካታ መንፈሳዊ መልእክቶችን ያዘሉ ናቸውና ተራ በተራ እንመለከታቸዋለን፡፡

①ኛ...‹‹ሚዜዎች ሙሽራው ከእነርሱ ጋር ሳለ ሊያዝኑ ይችላሉን?›› የሚለው ዐረፍተ ነገር በገጸ ንባቡ ውስጥ ስለ ሐዋርያት ጾም የተመሰለው የመጀመሪያው ምሳሌ ነው፡፡ ሚዜዎች የተባሉት እንደ መጥምቁ ዮሐንስ መንገድ የሚጠርጉ፣ የሚያስተምሩና ምእመናንን ወደ ኢየሱስ ክርስቶስ የሚያቀረቡ ሁሉ ናቸው፡፡ ሙሽሪትን ወደ ሙሽራው መውሰድ የሚዜዎች ሥራ መሆኑ በአይሁድና በኢትዮጵያውያን ባህል ሲሠራበት የኖረ ነው፡፡ ስለዚህ ዋነኞቹ ሚዜዎች ሐዋርያት ናቸው ማለት ነው፡፡ ኢየሱስ ክርስቶስ ሙሽራ ሲሆን ቤተክርስቲያን (ምእመናን) ደግሞመርዓት (ሴት ሙሽራ) ትባላለች፡፡ (2ቆሮ11.2፤ዮሐ3.29)
‹‹ሚዜዎች ሙሽራው ከእነርሱ ጋር ሳለ ሊያዝኑ ይችላሉን?›› ሲልሚዜዎች ሙሽራውን ለማስደሰት ሲሉ ምንም የሚያሳዝን ነገር ቢያጋጥማቸውም እንኳን ጨክነው በመቻል ያሳልፉታል እንጂ በሙሽራው ፊት እንደማያዝኑ፤ እንደዚሁም መጾም ተገቢ ነገር ቢሆንም ሐዋርያትኢየሱስ ክርስቶስ ከእነርሱ ጋር ሳለ መጾም እንደማይገባቸው ነገር ግን ከእነርሱ ተለይቶ ሲያርግ መጾም እንደሚጀምሩ ያስረዳል፡፡

በዚህ ምሳሌያዊ ንባብ ውስጥ ጾም በኀዘን ተመስሏል፡፡ መጾም ተድላነቱ ለነፍስ እንጂ ለሥጋ አይደለምና፡፡ ሥጋ ጾምን እስኪለምድ ድረስ ቅጣት ይሆንበታል፡፡ ስለዚህ በጾም ነፍስ ስትደሰት ሥጋ ግን ያዝናል፡፡ በዚህ ምክንያት ጾም በኀዘን ተመስሏል፡፡ በዚህም ምክንያት ጾም በብዙ የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍል ከኀዘን፣ ከዕንባ፣ከጸጸትና ከንስሐ ጋር ተያይዞ ቀርቧል፡፡ (ኢዩ2.12)

②ኛ...‹‹በአረጀ ልብስ አዲስ እራፊ የሚያኖር የለም፤ መጣፊያው ልብሱን ይቦጭቀዋልና፤ መቀደዱም የባሰ ይሆናል፡፡›› ይህ ዐረፍተ ነገር ደግሞ ሁለተኛው ምሳሌ ነው፡፡ እራፊ ማለት ቅዳጅ ወይም መጣፊያ ጨርቅ ማለት ነው፡፡ የስፌት ባለሙያ ባረጀ ልብስ ላይ አዲስ ጨርቅ አይጥፍም (አይሰፋም) ወይም አይለጥፍም፡፡ ይህም አንደኛ ግንጥል ጌጥ እንዳይሆን፤ ሁለተኛ ላሮጌ ልብስ ሲባል አዲሱን ማበላሸት እንዳይመጣና አዲሱ ካሮጌው ስለሚበረታ የባሰ እንዳይቦጭቀው በማሰብ ነው፡፡
በምሳሌው መሠረት በጣፊ ወይም በልብስ ሰፊ የተመሰለው ኢየሱስክርስቶስ ነው፡፡ በአዲስ እራፊ ጨርቅ ምሳሌነት የተወከለው ደግሞ ኢየሱስ ክርስቶስ በአዲስ ኪዳን እንድንጾመው የሠራልን ጾም ነው፡፡ የተቀደደውና መጣፊያ የሚያስፈልገው ልብስ ደግሞ የሐዋርያት ሕይወት ምሳሌ ነው፡፡
እንደ ምሳሌው ሁሉ ሰዎች የክርስቶስ ልብሶች ይባላሉ፡፡

‹‹አልባሲሁሰ ለክርስቶስ መሃይምናን እሙንቱ›› እንዲል፡፡ ይህም ‹‹የክርስቶስ ልብሶቹ ምእመናን ናቸው፡፡›› ማለት ነው፡፡ክርስቶስም ለሰዎች ልብሳቸው ነው፡፡ሐዋርያው ‹‹እናንተ የተጠመቃችሁ ክርስቶስን ለብሳችኋል›› ብሏልና፡፡(ገላ3.27) ምእመናን የክርስቶስ ልብሶች ናቸው ማለት የክብሩ መገለጫዎች ናቸው ማለት ነው፡፡ ልብስ የክብር መገለጫ ይሆናልና፡፡ እርሱ ደግሞ ለምእመናን ልብስ ነው ማለት ጌጣቸው፣ ነውራቸውንየሚሸፍንላቸውና ክብራቸውም እርሱ ነው ማለት ነው፡፡

ጾም ‹‹እራፊ›› መባሏ ምሥጢር አለው፡፡ ይኸውም እራፊ የተለያየውን እንደሚያቀራርብና አንድ እንደሚያደርግ ጾምም የተለያዩ ፈቃዳት ያሏቸውን ነፍስና ሥጋ አንድ ታደርጋለች፡፡ ከዚህም በላይ ከእግዚአብሔር የተለየውን ሰውም አስታርቃ አንድታደርገዋለች፤ ከመንጋውም እንዲቀላቀል ትረዳዋለች፡፡

‹‹በአረጀ ልብስ አዲስ እራፊ የሚያኖር የለም፤ መጣፊያው ልብሱን ይቦጭቀዋልና፤ መቀደዱም የባሰ ይሆናል፡፡›› ማለት አንድ የስፌት ባለሙያ ባረጀ ልብስ ላይ አዲስ እራፊ እንደማይጥፍ ሁሉ ኢየሱስ ክርስቶስም የሐዋርያት ሰውነት በኃጢአት ያረጀ ሆኖ ሳለ በመንፈስ ቅዱስ ሳያድስላቸው አዲስ የሠራውን የአዲስ ኪዳን ጾም ጹሙ ብሎ ሐዋርያትን አያዛቸውም ማለት ነው፡፡

ሰውነታቸው ሲታደስ ያን ጊዜ ግን ይጾማሉ፡፡
ይህ አገላለጥ እግዚአብሔር መንጋዎቹን ያለ አቅማቸው እንዲሸከሙ የማያደርግ አዛኝ ጌታ መሆኑን ያሳያል፡፡
እንዴት ቢባል ሐዋርያትን ሊፈጽሙት በማይችሉበት ሁኔታ ውስጥ እያሉ እንዲጾሙ አላዘዛቸውምና፡፡ ፈጣሪ ለሕዝቡ መቼ ሕግ መስጠት እንዳለበት በሚገባ ያውቃል፡፡ ለእስራኤላውያን በባርነት ሳሉ ዐሥርቱ ትእዛዛትን ያልሰጣቸው ስለዚህነው፡፡ ቢሰጣቸውም ሊጠብቁት አይችሉም ነበርና፡፡ በባርነት ያለ ሰው የራሱ ነጻነት እስከሌለው ድረስ የፈቀደውን ማድረግአይችልም፡፡

በታላላቅ ተአምራት ከባርነት ካወጣቸው በኋላ ግን ሕጉን ሰጣቸው፡፡ ስለዚህ ከክርስቲያን ወገን ማንም ቢሆን ከአቅሙ በላይ የሆነ ነገርፈጣሪ እንዳዘዘው አያስብ፡፡ የታዘዝነው ሁሉ በዐቅማችን ልክ እንደሆነ እንመን፡፡

③ኛ... ‹‹በአረጀ አቁማዳ አዲስ የወይን ጠጅ የሚያኖር የለም፤ ቢደረግ ግንአቁማዳው ይፈነዳል: የወይን ጠጁም ይፈሳል፡፡ አቁማዳውም ይጠፋል፡፡›› ይህ ስለ ጾመ ሐዋርያት የተመሰለው ሦስተኛውና የመጨረሻው ምሳሌ ነው፡፡
በአረጀ አቁማዳ የተመሰለው ሐዋርያት በጸጋ መንፈስ ቅዱስ ሳይታደሱ በፊት የነበራቸው ሕይወት ሲሆን፤ በአዲስ ወይን የተመሰለው ደግሞ ጌታችን በወንጌል የመሠረተልን ጾም ነው፡፡ የጾም ሕግን የሰጠን ኢየሱስ ክርስቶስ ራሱ ደግሞ በጠጅ ጣዩ (በጠማቂው) ተመስሎ ቀርቧል፡፡ አዲስ ጠጅ ባረጀ አቁማዳ እንደማይጣል አምላካችንም ባልታደሰ ሕይወታቸው ሐዋርያትን እንዲጾሙ አላዘዛቸውም፡፡

ቀደም ሲል ጾም ሥጋን ለጊዜው ደስ ባለማሰኘቱ በኀዘን እንደሚመሰል ተመልክተን ነበር፡፡ አሁን ደግሞ በዚህ ምሳሌ ጾም ነፍስን ደስ የሚያሰኝ በመሆኑ በወይንተመስሎ አገኘነው፡፡ ‹‹ወይን የሰውን ልብ ደስ ያሰኛል›› እንዲል፡፡ (መዝ103.15) ጠጅ ጣዮች ሲጥሉ (ሲጠምቁ) ተመልክታችሁ ታውቃላችሁ? አስቀድመው ቦታ ያዘጋጁለታል፡፡ እግር እንዳይበዛበትም ጥላ እንዳይወድቅበትም ይጠነቀቃሉ፡፡ እንዳይነፍስበትም ቀን ከሌሊት ይተጉለታል፡፡ በመጨረሻ ሥራው አልቆ ሳለ ጠጁ ከደረቀ (ከጠነከረ) ይላላ ብለውማር ያልሱታል (ይበርዙታል)፡፡ ከላላ ደግሞ ይድረቅ ብለው ጊዜ ይሰጡታል፡፡

በጠጅ ለተመሰለ ለጾምም በዓይነቱ ተመሳሳይ ከጥቅሙ አኳያ ደግሞ የበለጠ ጥንቃቄ ሊደረግለት ያስፈልጋል፡፡ ለጠጅ ቦታ እንደሚዘጋጅለት ለጾምም ሰውነትን ማዘጋጀትና ጊዜና ዕለት ወስኖ መመደብ በአጠቃላይ ጾምን ማወጅ ይገባል፡፡ ስንዱ እመቤት ቤተክርስቲያናችን የአጽዋማት ዐዋጅ ስላላት እኛ የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ልጆች የዚህ ችግር የለብንም፡፡ ለጠጅ እግር እንዳይበዛበትና ጥላ እንዳይድቅበት እንደሚጠነቀቁለት ጾማችንም በከንቱ ውዳሴ አጋንንት እንዳይገቡበትና ያለ መልካም ሥራ በጾም ብቻ ቀርተን ዋጋው እንዳያንስብን እየተጠነቀቅን መጾም ይገባናል፡፡ ጠጅ ደረቀ ይላላ፤ ላላ ይድረቅ እንደሚባል ጾማችን በሕግ ከተሠራልን በላይ ሠዓቱ እንዳይበዛና ከዓቅማችን በላይ አልፎ ሰውነታችን እንዳይጎዳ፤ እንደዚሁም የአጽዋማትን ሰዓት ሳንጠብቅ ቀርተንም መንፈሳዊ ሕይወታችን እንዳይላላ ማዕከላዊውን ስፍራ ይዘን በሕገ ቤተክርስቲያን መሠረት በጥንቃቄ መጾም እንደሚገባን ይህ ሦስተኛው ምሳሌ ያስረዳናል፡፡

ይህን ትምህርት ጌታችን መድኃኒታች ኢየሱስ ክርስቶስ የሚቋጨው ‹‹አዲሱን የወይን ጠጅ በአዲስ አቁማዳ ያኖረዋል ሁለቱም ይጠባበቃሉ፡፡›› በሚለው ኃይለ ቃል ነው፡፡ ዐረፍተ ነገሩ አዲስ የወይን ጠጅ መጣል ያለበት በአዲስ አቁማዳ መሆኑን ይናገራል፡፡ ስለዚህ ሐዋርያት ሕይወታቸው በጸጋ መንፈስ ቅዱስ ከታደሰ በኋላ በአዲሱ አቁማዳቸው አዲሱን ወይን ጣሉ፡፡ ማለትም በአዲስ ሕይወት የአዲስ ኪዳንን ጾም (ጾመ ሐዋርያትን) መጾም ጀመሩ፡፡

አዲስ የወይን ጠጅ በአሮጌ አቁማዳ ሲጣል ያፈነዳዋል፡፡ በአዲስ አቁማዳ ሲጣል ግን ያለፋዋል እንጂ ሊያፈነዳው አይችልም፡፡ ስለዚህ ወይኑም አቁማዳውም አዲስ የሆኑ እንደሆነ አቁማዳው ወይኑን ያፈላዋል፡፡ ወይኑ ደግሞ አቁማዳውን ያለፋዋል፡፡ በዚህ ጊዜ‹‹ሁለቱም ይጠባበቃሉ›› የሚለው ቃል ይፈጸማል፡፡ ጾምና ሰውነት እንደ ወይንና አቁማዳ ናቸው፡፡ ወይንና አቁማዳ እንደሚጠባበቁ (እንደሚጠቃቀሙ) ጾምና ሰውነትም እንዲሁ ናቸው፡፡ ሰው የጾም ሕግን ቢጠብቅ ሕግም እርሱን ትጠብቀዋለች፡፡ ‹‹ይጠባበቃሉ›› የተባለው ለዚህ ነው፡፡ ይህን የሚያስረዳ ‹‹አኮ ንሕነ ዘነዓቅቦሙ ለሕገጋት አላ እማንቱ ሕገጋት የዓቅቡነ ለዓቂብ ወለተፀውኖ›› የሚል ቃል ይገኛል፡፡ ይህም ‹‹ሕጎችን እኛ አንጠብቃቸውም፡፡ እነርሱ መጠበቅን ይጠብቁናል፤ መጠጊያም ይሆኑናል እንጂ፡፡›› እንደማለት ነው፡፡
ወይኑ ቆዳውን ማልፋቱ መልካም ነገር ነው፡፡ የለፋ ቆዳ ብዙ አገልግሎት ስላለው ይፈለጋልና፡፡ ለቀበቶ፣ ለቦርሳ፣ ለጫማና ለልብስ የሚሆነው የለፋ ቆዳ ነው፡፡ የጾምም ጥቅም እዚህ ላይ ነው፡፡ ለልዩ ልዩ አገልግሎትና ጥቅም የሚውል መንፈሳዊ ሕይወት እንዲኖረን ከፈለግን በጾም የለፋ (የደከመ) ሰውነት ያስፈልገናል፡፡ ቆዳን ማልፋት ማዘጋጀት እንጂ ከጥቅም ውጭ ማድረግ አይደለም፡፡ ሰውነትን በጾም ማድከምም ለመንፈሳዊ ሥራ ማዘጋጀት እንጂእንዳይሠራ ማድረግ እንዳልሆነ መረዳት ያስፈልጋል፡፡ የታረሰ መሬት ለዘር እንደሚመች በጾም የደከመ ሰውነትም ለመንፈሳዊጉዞ ይመቻል፡፡ ቅዱስ ዳዊት ‹‹ጉልበቶቼ በጾም ደከሙ›› ያለው ለዚህ ነው፡፡ (መዝ108.24)

ይህን የመሰለ ምሥጢር ያለውን ጾም ‹‹የሽማግሌዎች ጾም፣ ከጥንት ያልነበረ›› እያሉ በመጽሐፍ እና በቀኖና የሌላ ስም በመስጠት ምእመናን እንዳይጾሙት ማድረግ የዲያብሎስ ትጥቅ የማስፈታት ዘዴ እንጂ ሌላምን ሊሆን ይችላል?
ላለመጾም ምክንያት ከመፍጠር ምክንያት ፈጥሮ መጾም በእጅጉ ይጠቅማል፡፡ ደሀው ድኅነት ራሱ ጾም ነው ካለ፤ ሌላው ኢትዮጵያ ውስጥ መኖር ራሱጾም ነው ካለ ለመጾም ክርስቲያን መሆን ሳይሆን ሀገር ወይም ዜግነትመቀየር ሊያስፈልግ ነው ማለት ነው? ምእመናን ‹‹ይህ የሽማግሌዎች ጾም ነው›› ካሉ ስለ ጾም ማስተማርና ጾመው ማሳየት የሚጠበቅባቸው ‹‹ሰባክያን›› ደግሞ ‹‹ቃለ እግዚአብሔር ይመትር ነደ እሳት›› እያሉ ጾምን ሽሮ ለመብላት ጥቅስ ከጠቀሱ ጾምን በጽሑፍ እንጂ በሥራ ላናውቃትነው ማለት ነው፡፡

ሐዋርያት እንደታዘዙት ዓለምን ሁሉ ለማስተማር ከመሰማራታቸው በፊት መጀመሪያ ያደረጉት ጾምን ነው፡፡ ሐዋርያት አልጾሙም ማለት ከላይ የተብራራው የኢየሱስ ክርስቶስ ትንቢትና ምሳሌ ሐሰት ሆነ ማለት ነው፡፡ ሎቱ ስብሐት! ቃሉም ተፈጽሟል ሐዋርያትም ጾመዋል፡፡ እኛም ጾሙን ጾመን የምናስበውና የምንሠራው በጎ ሥራ ሁሉ ይከናወንልን ዘንድፈጣሪ በረድኤት አይለየን!

ይቆየን! ወስብሐት ለእግዚአብሔር!

www.tg-me.com/An_Apocalypse
እግዚአብሔር በወዴት ይገኛል ቢሉ፡-

በደዌ ደኛ በአልጋ ቁራኛ ተይዘዉ በሚማቅቁ፣ አስታማሚና ጠያቂ አጥተዉ ዕለተ ሞታቸዉን በሚናፍቁ ምስኪን ህሙማን መካከል እግዚአብሔር ይገኛል፡፡

በባዶዉ አስፋልት ላይ ካርቶን አንጥፈዉ በሚተኙ ዝናቡ፣ ቁሩ፣ ዋዕዩ በሚፈራረቅባቸዉ፣ ቆሻሻ ገንዳ ላይ ተንጠላጥለዉ የበሰበሰ ፍራፍሬን ቀለባቸዉ ባደረጉ፣ ችጋር ጠንቶባቸዉ መማሪያ ክፍል ዉስጥ እንዳሉ በረሀብ በሚያሸልቡ የድሃ ድሃ ልጆች መካከል እግዚአብሔር ይገኛል፡፡

በግፈኞች ፍትህ ተንጋዶባቸዉ ባልዋሉበት እንደዋሉ፣ ባልሰሩት እንደሰሩ ተደርገዉ በጨለማ እስር ቤት በተወረወሩ፣ብረት በተቆለፈባቸዉ የህሊና ታሳሪዎችና የህዝብ ጠበቆች መካከል እግዚአብሔር ይገኛል፡፡

በእኩይ ባሎቻቸዉ አካላዊም ሆነ ስነ ልቦናዊም ጥቃት በደረሰባቸዉ፣ እጅግ የከበደዉን መከራ መቋቋም ተስኗቸዉ ቀኑ በጨለመባቸዉ እንዲሁም ቢጮሁ ቢጮሁ ሰሚ አጥተዉ ሌት ተቀን በሰቆቃ በሚባዝኑ አንስቶች መካከል እግዚአብሔር ይገኛል፡፡

ለዚህች ሀገር የሚችሉትን ሁሉ አበርክተዉ አቅማቸዉ ሲደክም ጉልበታቸዉ ሲከዳ ጧሪ ቀባሪ ጧሪ ቀባሪ በማጣት ቤታቸዉ በፈረሰባቸዉ እንዲሁም ለልመና እጅ በሰጡ አዛዉንት አባቶችና አሮጊት እናቶች መካከል እግዚአብሔር ይገኛል፡፡

ታዲያ እነዚህን አካላት ሲራቡ በማብላት፣ ሲጠሙ በማጠጣት፣ ሲታሰሩ በመጠየቅ፣ ሲታረዙ በማልበስ፣ ሲያዝኑ በማጽናናት ሲታመሙ በመንከባከብ በመርዳት ከጎናቸዉ ሆነን ችግራቸዉን ከተካፈልን ከእግዚአብሔር ጋር እንገናኛለን ምክንያቱም የእርሱ ቦታዉ እዚህ ነዉና ሁሌም በፍቅሩ ይጎበኘናል እኛ አናየው ይሆናል እንጂ እርሱ ሁሌም በፍቅር ይመለከተናል መሻታችንን ሁሉ ይፈጽምልናል የሚበልጠዉንም ያደርግልናል፡፡


https://www.tg-me.com/joinchat-AAAAAEILHwyFiBuqHNVyRw
ምንት አሥሐቃ ለሳራ ?
   ሣራ ለምን ሳቀች ?
    【ዘፍ. ፲፰፥፲፱】
▦▦ 〣𓆩⪩♱⪨𓆪〣 ▦▦
        የሰው ልጅ ከሌላው ፍጥረት በተለየ በፊት ገጽታው ፣ በአካላዊ ኹኔታው ፣ በቁመናው ፣ በዓይን እንቅስቃሴው ከዚያም ባሻገር በመንካትና በአካል ርሕቀት ጭምር የሚገልጣቸው ሐሳቦች አሉት፤  ታዲያ እኒህ መንገዶች አንዳንዴ ከቃል ንግግር ባልተናነሰ ሳይሆን በተሻለ መንገድ እውነተኛ ስሜትን የመግለጥ ጉልበት ይኖራቸዋል።  የነገረ ሰብእ አጥኚዎች (anthropologist)  ይኽን በአካላዊ እንቅስቃሴና በፊት ገጽታ መልእክት የማስተላለፍ መንገድ ኪኔሲክስ [Kinesics] ብለውታል።

      አንድ መረጃ  ቀጥታ በቃል ሳይነገር  በተዘዋዋሪ መንገድ የስሜት ተረፈ ምርት (emotion residue) በሆነ አካላዊና የገጽታ ኩነት ሲገለጽ  ሐሳቡ እንዴት መተርጎም እንዳለበት ልማዳዊ የጋራ ስምምነቶች ከቦታ ቦታ የሚለያዩ ቢሆንም  በዲበ ተግባቦት (Meta-communication)  ግን የጋራ ትርጉም እንዲሠጣቸው ታሶቦ «እንዲህ የሚኮነው በዚህ ምክንያት ነው» የሚል አስማሚ ትርጉም ይቀመጥላቸዋል።

      ሳቅ ከእነዚህ ውሥጥ አንዱ ነው። በሥሉስ ቅዱስ በኩል ሐይመተ አብርሃም ውሥጥ ለሳራ የቀረበ ጥያቄ አለ ፦  «ምንት አሥሐቃ ለሳራ ☞ ሣራ ለምን ሳቀች?»  በእርግጥ ጥያቄው ሳራ የሳቀችው በምን ምክንያት እንደሆነ ለማወቅ ተፈልጎ የተነገረ ሳይሆን «እንዲህ ተደንቃ የምትስቀው ፣ እጅጉን ተገርማ የምትፈገው ስለምነው? »   ለማለት እንጂ ። “እግዚአብሔርም አብርሃምን አለው፦ ካረጀሁ በኋላ በውኑ እወልዳለሁን? ስትል ሣራ ለምን ሳቀች?”  እርሷ ግን ቅሉ ከሐሳብ አስቀድሞ ሁሉን የሚመረምረውን ፣ ከሕሊና አስቀድሞ ሁሉን የሚያውቀውን ልብአውቃ የሆነ ማእምረ ኵሉ  አምላክን ፈርታ ብትክደውም  “ሣራም ስለ ፈራች፦ አልሳቅሁም ስትል ካደች። እርሱም፦ አይደለም፥ ሳቅሽ እንጂ አላት።” (ቁ፲፭)

      ከዚህ ምዕራፍ ቀድሞ በተገለጠው የዘፍጥረት ታሪክ ውሥጥ ራሱን «ኤልሻዳይ» ብሎ ለአብርሃም የገለጠ ልዑል እግዚአብሔር ለይስሐቅ ይስቃል በሚል መጠሪያ መሰየም መነሻው ከነሚስቱ ሸምግሎ በእርግና ሳለ ትወልዳለህ ሲባል የአብርሃም ተገርሞ መሳቅ እንደነበር እናያለን፦
“አብርሃምም በግምባሩ ወደቀ፥ ሳቀም፥ …  እግዚአብሔርም አለ፦ በእውነት ሚስትህ ሣራ ወንድ ልጅን ትወልድልሃለች፥ ስሙንም ይስሐቅ ብለህ ትጠራዋለህ ”  【ዘፍ ፲፯፥፲፯(፲፱)】

         አብርሃምና ሳራን ምን አሳቃቸው?  ደስታ ነዋ! 
⊚⃝⊚ ሰው ሲደሰት ይስቃል (ከውሥጥ ወደ ውጪ)
☞ ያዘነ ሰው ፊቱ ጠቁሮ የተደሰተ ሰው ፊቱ በርቶ መታየቱ ለዚያ ነው  «እምከመ ይቴክዝ ልብ ይዴምን ገጽ እምከመ ይትፌሣሕ ልብ ይበርህ ገጽ» እንዲል
⊚⃝⊚  በሌላ መንገድ ሰው ሲስቅም ይደሰታል (ከውጭ ወደ ውሥጥ)
☞ የተከዙ ሰዎች ወደሳቅ የሚቀርቡት ያዘኑ ሰዎች መዝናናት የሚመርጡት ለዚያ ነው   "ሳቅ የደስታ ምንጭ ነው" እንዲል

ኢያሱ ወልደ አልዓዛር (ወልደ ሲራክ) በመጽሐፉ "እስመ እምራእዩ ይትዐወቅ ሰብእ፣ ወእምገጹ ይትዐወቅ ጠቢብ ⇨ ሰው በመልኩ ይታወቃልና ፣ ጠቢብም በገጹ ይታወቃል"

የተረጋጋ፣ ተስፋ የቆረጠ፣  የታመመ፣ የደከመ ሰው ከቸኮለ(ከሚጣደፍ) ፣ ከበረታ ፣ ከሚጓጓ…  ሰው  የሚለየው በአካሐዱ ነው ፤   
           ያዘነ ከሚደሰት ፣ ወደመኝታ የሚሔድ ወደሥራ ከሚሔ ፣ ወደቤተክርስቲያን የሚሔድ ከማይሔድ…  በአለባበሱ እንደሚታወቅ። ሳቅም ከአካሔድና ከለባበስ በበለጠ የአንድን ሰው አሁናዊ ሁኔታ በተሻለ መልክ ያስረዳል፤ በ‘ኢሞጂ’ ውሥጥ የፈገግታ ገጽ / የሳቅ ፊት (smiley face) አንዱ የደስታ ስሜን ወኪል ሥዕላዊ ምልክት (ideogram)  ተቀምጧል።  

«ወእምልብሰቱ ለሰብእ ወእምሑረቱ ወእምሠሐቁ ይትዐወቅ ግዕዙ  ⇨ ካለባበሱና ካካሄዱ ከአሳሣቁም የተነሣ የሰው ጠባዩ ይታወቃል» 【ሲራ ፲፱፥፳፯(፴)】

እንዲያውም  አንዳንዴ ሳቅ ከቁጥጥር ውጪ ‘እየገነፈለ’ የደስታን ስሜት የውሥጥን ሐሴት በሌላው ፊት ያሳብቃል፤ እንደ ሳራ! ታዲያ  ፎቶ አንሺ ፣ ቪዲዮ ቀራጭ ፣ ሠዓሊ… መታወሻ  ምስልን ለማስቀረት ሲሻ "እስኪ ፈገግ በሉ" ማለቱ ቅሉ ለዚህ ነው "ፍሡሓ ገጽ" ሆኖ መታየት የደስተኝነት መገለጫ ነውና።

          አቡነ ኤርምያስንስ ምን አሳቃቸው?
አቡነ ኤርምያስን በሐዘን ፊት ፣ በተቋጠረ ገጽ ፣ በዝቶ በሚፈሰው እንባ ፣ በተከዘ ልብ የማያውቃቸው የለም! «ጦርነት» በተባለው እርስበእርስ ፍጅት ከህዝበ ክርስቲያኑ ጋር የመከራውን ጽዋዕ ቀምሰዋል እንደቀደመው ኤርምያስ
ቅዱስ ቀሌምንጦስ ዘሮም  " ካህኑ ኤርምያስ ከሕዝበ እሥራኤል ጋር አብሮ የተሠደደው እስራኤሎችን ቃለእግዚአብሔር እንዲያስታውሳቸው ነው።" ብሏል! 

         እና ዛሬ ምን ተገኝቶ እንዲህ ይስቃሉ? 
“የእግዚአብሔርም ደስታ ኃይላችሁ ነውና አትዘኑ” 【ነህ ፰፥፲】
እንደሳራ ትውልዱ ላይ ተስፋ ፈንጥቆ የበረከት ዘር ሲተካላቸው  በመካን ማሕጸን ፍሬ ቢታያቸው ገጻቸው በርቶ ፊታቸው ፈክቶ ታይቷል!  በሀገሬ ቲቪ የቀረበው የዶንኪ ቲዩብ ድንቅ ልጆች መሰናዶ በዚህ ሳምንት በደስታ የሚስቁ በሐሤት የሚፍለቀለቁ አቡነ ኤርምያስን ደጋግሞ አሳይቶናል። ዐይናቸው ውሥጥ አንድ ሕፃን ሶልያና ተፈራ ብቻ ሳትሆን  የብዙ ተተኪ አዳጊ ዜጎች ተስፋ ይታያል!  [https://youtu.be/jnt9FJgcj2w]

     ፈለገ አእምሮ መንፈሳዊ ትምህርት ቤት በአቡነ ኤርምያስ ራእይ የታነጸው    “ታላላቅ ካቴድራሎችን ገንብተን በውስጡ አገልጋይ ከሚጠፋ አብነት ት/ቤቶችን ገንብተን እንደጥንቱ በድንኳን ብንገለገል ይሻለናል” በሚል ኃይለ ቃል እንዲህ ያለውን ፍሬ ለማየት ነበር።  ዛሬ ግን የባሰ ሌላ ችግር በሀገረ ስብከቱ ተጋርጧል፤

     ብፁዕ አቡነ ኤርምያስ (ዶ/ር ) የሰሜን ወሎ ሀገረ ስብከት ሊቀጳጳስና የላሊበላ ውቅር አብያተ ክርስቲያናት የበላይ ጠባቂ በሀገራችን «በወንድማማቾች መኻል ተከስቶ በነበረው እርስ በእርስ ግጭት» የደረሰውን ውድመት ተከትሎ እሑድ ሰኔ 25 ቀን 2015 ዓ.ም. በሚሌኒየም አደራሽ ከቀኑ 6፡oo ጀምሮ የወደቀችዋን ድንኳን ለማንሳት ፣ የተናደውን ቅጥር ለመጠገን ፣ የፈረሰውን ለማደስና እንደቀድሞው ዘመን ለመሥራት ማንም የማይቀርበት ታላቅ መንፈሳዊ ጥሪ እንዲህ ሲሉ ለቤተክርስቲያን ልጆች አስተላልፈዋል፦
‹‹የክርስትናው ሀዲድ ተሰብሮ የእግዚአብሔር የማዳን ሥራ እንዳይቋረጥ ሃይማኖታዊ ግዴታችሁን ትወጡ ዘንድ በቅድስት ቤተ ክርስቲያን ስም አሳስባለሁ፡፡››

«ንሕነኒ ውስተ ሐይላ ንደይ ልበነ ንዴግና ወንበላ በሐ  ወትረ ንሳለማ ለቅድስት ቤተክርስቲያን ☞ እኛም በቤተክርስቲያን  ኃይል ልቡናችንን እንጨምር እንከተላት ሰላምም እንበላት» 【መጽሐፈ ቀሌምንጦስ ፲፩፥፶】

✞ ቴዎድሮስ በለጠ ✞ ሰኔ ፳፫ ቀን ፳፻፲፭ ዓ.ም. ከፍራንክፈርት
2025/07/05 03:11:44
Back to Top
HTML Embed Code: