Telegram Web Link
ላለመጾም ምክንያት ከመፍጠር ምክንያት ፈጥሮ መጾም በእጅጉ ይጠቅማል፡፡ ደሀው ድኅነት ራሱ ጾም ነው ካለ፤ ሌላው ኢትዮጵያ ውስጥ መኖር ራሱጾም ነው ካለ ለመጾም ክርስቲያን መሆን ሳይሆን ሀገር ወይም ዜግነትመቀየር ሊያስፈልግ ነው ማለት ነው? ምእመናን ‹‹ይህ የሽማግሌዎች ጾም ነው›› ካሉ ስለ ጾም ማስተማርና ጾመው ማሳየት የሚጠበቅባቸው ‹‹ሰባክያን›› ደግሞ ‹‹ቃለ እግዚአብሔር ይመትር ነደ እሳት›› እያሉ ጾምን ሽሮ ለመብላት ጥቅስ ከጠቀሱ ጾምን በጽሑፍ እንጂ በሥራ ላናውቃትነው ማለት ነው፡፡

ሐዋርያት እንደታዘዙት ዓለምን ሁሉ ለማስተማር ከመሰማራታቸው በፊት መጀመሪያ ያደረጉት ጾምን ነው፡፡ ሐዋርያት አልጾሙም ማለት ከላይ የተብራራው የኢየሱስ ክርስቶስ ትንቢትና ምሳሌ ሐሰት ሆነ ማለት ነው፡፡ ሎቱ ስብሐት! ቃሉም ተፈጽሟል ሐዋርያትም ጾመዋል፡፡ እኛም ጾሙን ጾመን የምናስበውና የምንሠራው በጎ ሥራ ሁሉ ይከናወንልን ዘንድፈጣሪ በረድኤት አይለየን!

ይቆየን! ወስብሐት ለእግዚአብሔር!

www.tg-me.com/An_Apocalypse
እግዚአብሔር በወዴት ይገኛል ቢሉ፡-

በደዌ ደኛ በአልጋ ቁራኛ ተይዘዉ በሚማቅቁ፣ አስታማሚና ጠያቂ አጥተዉ ዕለተ ሞታቸዉን በሚናፍቁ ምስኪን ህሙማን መካከል እግዚአብሔር ይገኛል፡፡

በባዶዉ አስፋልት ላይ ካርቶን አንጥፈዉ በሚተኙ ዝናቡ፣ ቁሩ፣ ዋዕዩ በሚፈራረቅባቸዉ፣ ቆሻሻ ገንዳ ላይ ተንጠላጥለዉ የበሰበሰ ፍራፍሬን ቀለባቸዉ ባደረጉ፣ ችጋር ጠንቶባቸዉ መማሪያ ክፍል ዉስጥ እንዳሉ በረሀብ በሚያሸልቡ የድሃ ድሃ ልጆች መካከል እግዚአብሔር ይገኛል፡፡

በግፈኞች ፍትህ ተንጋዶባቸዉ ባልዋሉበት እንደዋሉ፣ ባልሰሩት እንደሰሩ ተደርገዉ በጨለማ እስር ቤት በተወረወሩ፣ብረት በተቆለፈባቸዉ የህሊና ታሳሪዎችና የህዝብ ጠበቆች መካከል እግዚአብሔር ይገኛል፡፡

በእኩይ ባሎቻቸዉ አካላዊም ሆነ ስነ ልቦናዊም ጥቃት በደረሰባቸዉ፣ እጅግ የከበደዉን መከራ መቋቋም ተስኗቸዉ ቀኑ በጨለመባቸዉ እንዲሁም ቢጮሁ ቢጮሁ ሰሚ አጥተዉ ሌት ተቀን በሰቆቃ በሚባዝኑ አንስቶች መካከል እግዚአብሔር ይገኛል፡፡

ለዚህች ሀገር የሚችሉትን ሁሉ አበርክተዉ አቅማቸዉ ሲደክም ጉልበታቸዉ ሲከዳ ጧሪ ቀባሪ ጧሪ ቀባሪ በማጣት ቤታቸዉ በፈረሰባቸዉ እንዲሁም ለልመና እጅ በሰጡ አዛዉንት አባቶችና አሮጊት እናቶች መካከል እግዚአብሔር ይገኛል፡፡

ታዲያ እነዚህን አካላት ሲራቡ በማብላት፣ ሲጠሙ በማጠጣት፣ ሲታሰሩ በመጠየቅ፣ ሲታረዙ በማልበስ፣ ሲያዝኑ በማጽናናት ሲታመሙ በመንከባከብ በመርዳት ከጎናቸዉ ሆነን ችግራቸዉን ከተካፈልን ከእግዚአብሔር ጋር እንገናኛለን ምክንያቱም የእርሱ ቦታዉ እዚህ ነዉና ሁሌም በፍቅሩ ይጎበኘናል እኛ አናየው ይሆናል እንጂ እርሱ ሁሌም በፍቅር ይመለከተናል መሻታችንን ሁሉ ይፈጽምልናል የሚበልጠዉንም ያደርግልናል፡፡


https://www.tg-me.com/joinchat-AAAAAEILHwyFiBuqHNVyRw
ምንት አሥሐቃ ለሳራ ?
   ሣራ ለምን ሳቀች ?
    【ዘፍ. ፲፰፥፲፱】
▦▦ 〣𓆩⪩♱⪨𓆪〣 ▦▦
        የሰው ልጅ ከሌላው ፍጥረት በተለየ በፊት ገጽታው ፣ በአካላዊ ኹኔታው ፣ በቁመናው ፣ በዓይን እንቅስቃሴው ከዚያም ባሻገር በመንካትና በአካል ርሕቀት ጭምር የሚገልጣቸው ሐሳቦች አሉት፤  ታዲያ እኒህ መንገዶች አንዳንዴ ከቃል ንግግር ባልተናነሰ ሳይሆን በተሻለ መንገድ እውነተኛ ስሜትን የመግለጥ ጉልበት ይኖራቸዋል።  የነገረ ሰብእ አጥኚዎች (anthropologist)  ይኽን በአካላዊ እንቅስቃሴና በፊት ገጽታ መልእክት የማስተላለፍ መንገድ ኪኔሲክስ [Kinesics] ብለውታል።

      አንድ መረጃ  ቀጥታ በቃል ሳይነገር  በተዘዋዋሪ መንገድ የስሜት ተረፈ ምርት (emotion residue) በሆነ አካላዊና የገጽታ ኩነት ሲገለጽ  ሐሳቡ እንዴት መተርጎም እንዳለበት ልማዳዊ የጋራ ስምምነቶች ከቦታ ቦታ የሚለያዩ ቢሆንም  በዲበ ተግባቦት (Meta-communication)  ግን የጋራ ትርጉም እንዲሠጣቸው ታሶቦ «እንዲህ የሚኮነው በዚህ ምክንያት ነው» የሚል አስማሚ ትርጉም ይቀመጥላቸዋል።

      ሳቅ ከእነዚህ ውሥጥ አንዱ ነው። በሥሉስ ቅዱስ በኩል ሐይመተ አብርሃም ውሥጥ ለሳራ የቀረበ ጥያቄ አለ ፦  «ምንት አሥሐቃ ለሳራ ☞ ሣራ ለምን ሳቀች?»  በእርግጥ ጥያቄው ሳራ የሳቀችው በምን ምክንያት እንደሆነ ለማወቅ ተፈልጎ የተነገረ ሳይሆን «እንዲህ ተደንቃ የምትስቀው ፣ እጅጉን ተገርማ የምትፈገው ስለምነው? »   ለማለት እንጂ ። “እግዚአብሔርም አብርሃምን አለው፦ ካረጀሁ በኋላ በውኑ እወልዳለሁን? ስትል ሣራ ለምን ሳቀች?”  እርሷ ግን ቅሉ ከሐሳብ አስቀድሞ ሁሉን የሚመረምረውን ፣ ከሕሊና አስቀድሞ ሁሉን የሚያውቀውን ልብአውቃ የሆነ ማእምረ ኵሉ  አምላክን ፈርታ ብትክደውም  “ሣራም ስለ ፈራች፦ አልሳቅሁም ስትል ካደች። እርሱም፦ አይደለም፥ ሳቅሽ እንጂ አላት።” (ቁ፲፭)

      ከዚህ ምዕራፍ ቀድሞ በተገለጠው የዘፍጥረት ታሪክ ውሥጥ ራሱን «ኤልሻዳይ» ብሎ ለአብርሃም የገለጠ ልዑል እግዚአብሔር ለይስሐቅ ይስቃል በሚል መጠሪያ መሰየም መነሻው ከነሚስቱ ሸምግሎ በእርግና ሳለ ትወልዳለህ ሲባል የአብርሃም ተገርሞ መሳቅ እንደነበር እናያለን፦
“አብርሃምም በግምባሩ ወደቀ፥ ሳቀም፥ …  እግዚአብሔርም አለ፦ በእውነት ሚስትህ ሣራ ወንድ ልጅን ትወልድልሃለች፥ ስሙንም ይስሐቅ ብለህ ትጠራዋለህ ”  【ዘፍ ፲፯፥፲፯(፲፱)】

         አብርሃምና ሳራን ምን አሳቃቸው?  ደስታ ነዋ! 
⊚⃝⊚ ሰው ሲደሰት ይስቃል (ከውሥጥ ወደ ውጪ)
☞ ያዘነ ሰው ፊቱ ጠቁሮ የተደሰተ ሰው ፊቱ በርቶ መታየቱ ለዚያ ነው  «እምከመ ይቴክዝ ልብ ይዴምን ገጽ እምከመ ይትፌሣሕ ልብ ይበርህ ገጽ» እንዲል
⊚⃝⊚  በሌላ መንገድ ሰው ሲስቅም ይደሰታል (ከውጭ ወደ ውሥጥ)
☞ የተከዙ ሰዎች ወደሳቅ የሚቀርቡት ያዘኑ ሰዎች መዝናናት የሚመርጡት ለዚያ ነው   "ሳቅ የደስታ ምንጭ ነው" እንዲል

ኢያሱ ወልደ አልዓዛር (ወልደ ሲራክ) በመጽሐፉ "እስመ እምራእዩ ይትዐወቅ ሰብእ፣ ወእምገጹ ይትዐወቅ ጠቢብ ⇨ ሰው በመልኩ ይታወቃልና ፣ ጠቢብም በገጹ ይታወቃል"

የተረጋጋ፣ ተስፋ የቆረጠ፣  የታመመ፣ የደከመ ሰው ከቸኮለ(ከሚጣደፍ) ፣ ከበረታ ፣ ከሚጓጓ…  ሰው  የሚለየው በአካሐዱ ነው ፤   
           ያዘነ ከሚደሰት ፣ ወደመኝታ የሚሔድ ወደሥራ ከሚሔ ፣ ወደቤተክርስቲያን የሚሔድ ከማይሔድ…  በአለባበሱ እንደሚታወቅ። ሳቅም ከአካሔድና ከለባበስ በበለጠ የአንድን ሰው አሁናዊ ሁኔታ በተሻለ መልክ ያስረዳል፤ በ‘ኢሞጂ’ ውሥጥ የፈገግታ ገጽ / የሳቅ ፊት (smiley face) አንዱ የደስታ ስሜን ወኪል ሥዕላዊ ምልክት (ideogram)  ተቀምጧል።  

«ወእምልብሰቱ ለሰብእ ወእምሑረቱ ወእምሠሐቁ ይትዐወቅ ግዕዙ  ⇨ ካለባበሱና ካካሄዱ ከአሳሣቁም የተነሣ የሰው ጠባዩ ይታወቃል» 【ሲራ ፲፱፥፳፯(፴)】

እንዲያውም  አንዳንዴ ሳቅ ከቁጥጥር ውጪ ‘እየገነፈለ’ የደስታን ስሜት የውሥጥን ሐሴት በሌላው ፊት ያሳብቃል፤ እንደ ሳራ! ታዲያ  ፎቶ አንሺ ፣ ቪዲዮ ቀራጭ ፣ ሠዓሊ… መታወሻ  ምስልን ለማስቀረት ሲሻ "እስኪ ፈገግ በሉ" ማለቱ ቅሉ ለዚህ ነው "ፍሡሓ ገጽ" ሆኖ መታየት የደስተኝነት መገለጫ ነውና።

          አቡነ ኤርምያስንስ ምን አሳቃቸው?
አቡነ ኤርምያስን በሐዘን ፊት ፣ በተቋጠረ ገጽ ፣ በዝቶ በሚፈሰው እንባ ፣ በተከዘ ልብ የማያውቃቸው የለም! «ጦርነት» በተባለው እርስበእርስ ፍጅት ከህዝበ ክርስቲያኑ ጋር የመከራውን ጽዋዕ ቀምሰዋል እንደቀደመው ኤርምያስ
ቅዱስ ቀሌምንጦስ ዘሮም  " ካህኑ ኤርምያስ ከሕዝበ እሥራኤል ጋር አብሮ የተሠደደው እስራኤሎችን ቃለእግዚአብሔር እንዲያስታውሳቸው ነው።" ብሏል! 

         እና ዛሬ ምን ተገኝቶ እንዲህ ይስቃሉ? 
“የእግዚአብሔርም ደስታ ኃይላችሁ ነውና አትዘኑ” 【ነህ ፰፥፲】
እንደሳራ ትውልዱ ላይ ተስፋ ፈንጥቆ የበረከት ዘር ሲተካላቸው  በመካን ማሕጸን ፍሬ ቢታያቸው ገጻቸው በርቶ ፊታቸው ፈክቶ ታይቷል!  በሀገሬ ቲቪ የቀረበው የዶንኪ ቲዩብ ድንቅ ልጆች መሰናዶ በዚህ ሳምንት በደስታ የሚስቁ በሐሤት የሚፍለቀለቁ አቡነ ኤርምያስን ደጋግሞ አሳይቶናል። ዐይናቸው ውሥጥ አንድ ሕፃን ሶልያና ተፈራ ብቻ ሳትሆን  የብዙ ተተኪ አዳጊ ዜጎች ተስፋ ይታያል!  [https://youtu.be/jnt9FJgcj2w]

     ፈለገ አእምሮ መንፈሳዊ ትምህርት ቤት በአቡነ ኤርምያስ ራእይ የታነጸው    “ታላላቅ ካቴድራሎችን ገንብተን በውስጡ አገልጋይ ከሚጠፋ አብነት ት/ቤቶችን ገንብተን እንደጥንቱ በድንኳን ብንገለገል ይሻለናል” በሚል ኃይለ ቃል እንዲህ ያለውን ፍሬ ለማየት ነበር።  ዛሬ ግን የባሰ ሌላ ችግር በሀገረ ስብከቱ ተጋርጧል፤

     ብፁዕ አቡነ ኤርምያስ (ዶ/ር ) የሰሜን ወሎ ሀገረ ስብከት ሊቀጳጳስና የላሊበላ ውቅር አብያተ ክርስቲያናት የበላይ ጠባቂ በሀገራችን «በወንድማማቾች መኻል ተከስቶ በነበረው እርስ በእርስ ግጭት» የደረሰውን ውድመት ተከትሎ እሑድ ሰኔ 25 ቀን 2015 ዓ.ም. በሚሌኒየም አደራሽ ከቀኑ 6፡oo ጀምሮ የወደቀችዋን ድንኳን ለማንሳት ፣ የተናደውን ቅጥር ለመጠገን ፣ የፈረሰውን ለማደስና እንደቀድሞው ዘመን ለመሥራት ማንም የማይቀርበት ታላቅ መንፈሳዊ ጥሪ እንዲህ ሲሉ ለቤተክርስቲያን ልጆች አስተላልፈዋል፦
‹‹የክርስትናው ሀዲድ ተሰብሮ የእግዚአብሔር የማዳን ሥራ እንዳይቋረጥ ሃይማኖታዊ ግዴታችሁን ትወጡ ዘንድ በቅድስት ቤተ ክርስቲያን ስም አሳስባለሁ፡፡››

«ንሕነኒ ውስተ ሐይላ ንደይ ልበነ ንዴግና ወንበላ በሐ  ወትረ ንሳለማ ለቅድስት ቤተክርስቲያን ☞ እኛም በቤተክርስቲያን  ኃይል ልቡናችንን እንጨምር እንከተላት ሰላምም እንበላት» 【መጽሐፈ ቀሌምንጦስ ፲፩፥፶】

✞ ቴዎድሮስ በለጠ ✞ ሰኔ ፳፫ ቀን ፳፻፲፭ ዓ.ም. ከፍራንክፈርት
❀ ተጣሉብኝ ❀
༺♱༻
"ደቂቀ እምየ ተበአሱ በእንቲአየ ⇨ የእናቴ ልጆች ስለእኔ እርስበእርሳቸው ተጣሉብኝ" (መኃ ፩፥፮)

በዛሬው ዕለት የምናገናቸው የከበሩ የቤተክርስቲያን መብራቶች ቅዱሳን ሰማዕታት ቅዱስ ጳውሎስና ቅዱስ ጴጥሮስ በአንድ ወቅት ስለ እናት ቤተክርስቲያን ክብር ተጣልተው እንደነበር! አንድነቷን ለመጠበቅ «ጽና ፣ አትዛል ፣ ፣ ከጥፋት ተመለስ…» ለመባባል በዛ መንድ ሳይሆን በዚህ መንገድ ጥቀማት እያሉ ተጣሉ!

ዛሬስ ለቤተክርስቲያን ሳይሆን በቤተክርስቲያን ላይ የተነሱ አንድነቷን ለማጽናት ሳይሆን ለመክፈል እንቅልፍ የሚያጡ “በዚህ መንገድ ቢሆን ነው ልክ” በሚል ቅንነት ያለው መበላለጥ ሳይሆን «ትክክል አንተ ነህ እኔ አጥፍቻለሁ» የሚል እንኳ ሲገኝ ይቅርታን በማይቀበል ጥመት ጨፍነው «ዘላቂ ጥቅም እንጂ ቋሚ ጠላት የለኝም» የሚለው ፖለቲከኛው እንኳን የሚበልጣቸው «ሃይማኖተኛ» መሳዮች!

ሆድ ለባሰው ማጭድ አታውሰው ሆኖ እየታመምን እናስታምማለን እንጂ ቁስላችን ሲያመረቅዙና ሕመማችን ሲያብሱማ ተዉ እንላለን! መንጋውን ለመጠበቅ ያልበቁ በመንጋው መጠበቅ የሚገባቸው ስማቸው እረኛ ከሚለው ወርዶ ተረኛ፣ ዘረኛ … በሚል እየተተካካ ቤተክርስቲያንን የሚያቆስሏት የሚያሳምሟት ከማያምን ይልቅ የከፉ እንዲህ ያሉ ገባርያነ እኪት ጸላዕያነ ሠናያት ለጥፋት ሲሮጡ ሔደው ሲለምኗቸው እምቢኝ ካሉ ተለይተው አለመወገዛቸው ፣ ተጠርተው አለመከልከላቸው ነገ የበለጠ ዋጋ ያስከፍለናል!

“ነገር ግን ለእርሱ ስለ ሆኑት ይልቁንም ስለ ቤተ ሰዎቹ የማያስብ ማንም ቢሆን፥ ሃይማኖትን የካደ ከማያምንም ሰው ይልቅ የሚከፋ ነው።” 【1ኛ ጢሞቴዎስ 5፥8】

☞ የቀደሙቱ ጳውሎስና ጴጥሮስ ፣ አፈወርቅና ኤጲፋንዮስ ፣ ተክለሃይማኖትና ኤዎስጣቴዎስ… ስለእኔ እርስ በእርሳቸው ተጣሉብኝ ብላ የምታዝንላቸው ቤተክርስቲያን ነበረችን። ዛሬ ግን ስለእርሷ ሳይሆን በእርሷ ላይ ነውና ታዝንብናለች!

በሁሉ መንገድ ሴራው ቢበቃ፣ ሸፍጥ ቢቆም፣ «እበልጥ አልበለጥ» መባባሉ ብናስቀር ፣ መበሻሸቁን ብናርቅ … «በእነ እገሌ ምክንያት ይኽ ሆነ» ባዮች ወጣ ገባውን አይተን ለአንድነት እንቁም መለያየቱን እናስቁም፤ እድሉ ስላለን «በእኛ ምክንያት ነው ይህ ሁሉ የመጣው» ብለን የምንችለውን ብናደርግ። ባትሹት ግን ሁሉን የሚያስችለው እርሱ ሁሉን ይችላል!

ጌታችን ቅዱስ ዮሐንስ ፍቁረ እግዚእን ከሊቀ ሐዋርያቱ ቅዱስ ጴጥሮስ ጋር ወደ አንጾክያ እንዲያስተምሩ ቢልካቸው በዚያ አሕዛብ መከራ አጸኑባቸው ኋላ ቅዱስ ጳውሎስ ይህን ከቅዱስ ዮሐንስ ቢሰማ በአካሔድ መሳታቸውን ፣ ዘይቤ ማጣታቸውን አይቶ ተለያቸው … የአሕዛብን ልብስ ለብሶ ወደሸንጓቸው ገብቶ በፈሊጥ መከረና ከቅዱስ ጴጥሮስ ደርሶ በፊታቸው በጥፊ መታው ፦ ቅዱስ ጴጥሮስ " ተመይጠኑ ጳውሊ ሃበ ቀዳሚ ግብሩ" ብሎ ደነገጠ "እስኪ ሙት ካስነሳ እንመንበት?" ብሎ መክሮ ከሞተ ፫ ወር (መንፈቅ) ያለፈው የንጉሥ ልጅ እንዲያስነሳ ጠየቀላቸው! ሊቀ ሐዋርያት ሲጸልይ ቅዱስ ጳውሎስ ከውጭ፦ በእነርሱ ልብስ፣ ከውስጥ፦ በንጹሕ መንፈስ "ላንተ ብሎ እንጂ እሾም እሸለምበት ብሎ አይደለምና እባክህ ስማው አስነሳለት" እያለ በጥፊ ለመታው ወንድሙ ለመነ ያም ሙት ተነስቶ ያስነሳኝስ ያ ነው ብሎ ቅዱስ ጳውሎስን ጠቁሞላቸዋል በዚህ ነው "የእናቴ ልጆች ስለእኔ እርስበእርሳቸው ተጣሉብኝ" ያለው የተገለጠው!

የዛሬው የጠሉ የተጠሉና የተጣሉ ጥለኞች ለቤተክርስቲያን ምን እንደሚጠቅሟት እንጃ!

በእግራቸው ገስግሰው በእጃቸው ደም አፍሰው የተመለሱትን አጨብጭቦ ይቅር አልኩ ፣ ረሳሁ ፣ ታረቅሁ… ሲለን ያየነው አካል የገዛ አባቶቹን "ይቅርታቸውን አንቀበልም" ብሎ ልብንም በርንም ዘግቶ መጥፋትቱ የይቅርታን ትርጉም በምን እንደተረዳው እንጃ በራሱ መበቀል እግዚአብሔርን መጣል ነውና የበለጠ ቁጣ ይጠራል!

በዜና አበው እንዲህ የሚል ታሪክ አለ፦

አንድ ወንድም ወደ አባ ስልዋኖስ ሄደና "በጣም ክፉ ነገር እያደረሰብኝ ያለና ሊያጣፋኝ የሚፈልገኝ ጠላት አለብኝ:: እንዲገድሉኝም ለመሰርያን(ክፉ አድራጊዋች) ነግሯቸዋልና እንዲያሳርፍልኝና እንዲገስጸው ልነግር ወደ ባለስልጣኑ መሄድ እሻለሁ" አለው ::እርሱም "እ...የመሰለህን አድርግ አለው...." :: ያም ወንድም "እንግዲያውስ ጸልይልኝ" አለውና አብረው ጸሎት ሲያደርሱ "በደላችንን ይቅር በለን እኛም የበደሉንን ይቅር እንደምንል" ከሚለው ስፍራ ላይ ሳሉ አባ ስልዋኖስ "በደላችንን ይቅር አትበለን:: እኛም የበደሉንን ይቅር ስለማንል::" አለ:: ያም ወንድም "አባ... ተው እንጂ እንዲህማ አትበል!" ቢለው "ይበቀልልህ ዘንድ ወደ መኮንኑ የምትሄድ ከሆነ ስልዋኖስ ከዚህ ሌላ አይጸልይም" አለው:: ያም እኁ(ወንድም) ይህን ሰምቶ ወደልቡ ቢመለስ ከእግሩ ሥር ተደፍቶ የበደለውን ይቅር አለ::

❀ ሮሜ. 12:19 "ተወዳጆች ሆይ፥ ራሳችሁ አትበቀሉ፥ ለቍጣው ፈንታ ስጡ እንጂ፤ በቀል የእኔ ነው፥ እኔ ብድራቱን እመልሳለሁ ይላል ጌታ ተብሎ ተጽፎአልና።"

❀❀ ማቴ. 5:44-45 "እኔ ግን እላችኋለሁ፥ በሰማያት ላለ አባታችሁ ልጆች ትሆኑ ዘንድ ጠላቶቻችሁን ውደዱ፥ የሚረግሙአችሁንም መርቁ፥ ለሚጠሉአችሁም መልካም አድርጉ፥ ስለሚያሳድዱአችሁም ጸልዩ፤ እርሱ በክፎዎችና በበጎዎች ላይ ፀሐይን ያወጣልና፥ በጻድቃንና በኃጢአተኞችም ላይ ዝናቡን ያዘንባልና።"

❀❀❀ ማቴ.6:15 "ለሰዎች ግን ኃጢአታቸውን ይቅር ባትሉ፥ አባታችሁም ኃጢአታችሁን ይቅር አይላችሁም።ለሰዎች ኃጢአታቸውን ይቅር ብትሉ፥ የሰማዩ አባታችሁ እናንተን ደግሞ ይቅር ይላችኋልና"

በዚህ አያያዝ ክርስትናችን ምኑ ላይ ነው? እንግዲህ እኛም እንደዚህ እያልን ልንጸልይ ነው "በደላችንን ይቅር አትበለን:: እኛም የበደሉንን ይቅር ስለማንል::"
አቤቱ ማረን ፈሪሃ ኃጢዓትን ፣
ፍቅረ መለኮትን ፣
ተዘክሮ ሞትን … ከእኛ አታርቅብን 🙏

☞ ሐምሌ አቦ ፳፻፲፭ ዓ.ም. በቴዎድሮስ በለጠ የተጻፈ።
ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ የተሰጠ መግለጫ

በመንፈስ ቅዱስ የሚመራው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ በፍትሕ መንፈሳዊ አንቀጽ አምስትና በሕገ ቤተክርስቲያን አንቀጽ 19 ቁጥር 3 አስቸኳይ ጉዳይ ሲያጋጥም ምልዓተ ጉባኤ እንደሚያደርግ በተደነገገው መሠረት ሐምሌ 26ቀን 2015 ዓ.ም. ባካሄደው አስቸኳይ ምልዓተ ጉባኤ በቤተ ክርስቲያናችን ላይ በተፈጠረው ወቅታዊ የዶግማ፣ የቀኖናና የአስተዳደራዊ ጥሰቶችን አስመልክቶ ውሳኔዎች አሳልፏል፡፡

ጥንታዊት፣ ሐዋርያዊትና ዓለም አቀፋዊት የሆነች ቅድስት ቤተክርስቲያን ሕዝብና አሕዛብን፣ ሰውና መላእክትን፣ ፍጡራን እና ፈጣሪን አንድ አድርጋ የሰው ልጆች ሁሉ በቋንቋ፣ በቀለምና በጐሣ ሳይከፋፈሉ ሀብተ ወልድና ስመ ክርስትና አግኝተው ከአብራከ መንፈስ ቅዱስ ከማህፀነ ዮርዳኖስ የተወለዱ በማየ ገቦ ተጠምቀው የቤተ ክርስቲያን ልጆች በመሆን ልዩነት የሌለባትን ዘለዓለማዊት መንግሥተ እግዚአብሔር እንዲወርሱ በደመ ክርስቶስ የተመሠረተች ስትሆን በየዘመናቱ የተነሣባትን ፈተና ሁሉ አልፋ ከእኛ ዘመን ደርሳለች፤

ምንም እንኳ ከኦርቶዶክስ ትምህርተ ሃይማኖት ፈጽሞ በተለየ ሁኔታ ቤተ ክርስቲያንን በጐሣና በቋንቋ የመለየት ሂደት በዓለም አቀፍ ደረጃ እንግዳ ክስተት ቢሆንም ቤተ ክርስቲያን ከሃይማኖታዊና መንፈሳዊ ጠባይዋ በተለየ፣ ታሪኳንና ሥርዓቷን በማይመጥን፣ ከሕግ መንፈሳዊ፣ ከሕግ ጠባይአዊ እና ከሕገ አእምሮ በወጣ መልኩ የደረሰባት የዶግማ፣ የቀኖናና የአስተዳደር ጥሰት ቅዱስ ሲኖዶስን እጅግ አሳዝኖታል፤

ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ለሀገር አንድነት፣ ለፍትሕ፣ ለጥበብ፣ ለሕዝብ ትስስር፣ ለማኅበራዊ ዕድገት፣ ለጤና፣ ለሥነ-ምግባር መሠረትና ዐምድ፤ ሆና በዓለም አቀፍ ደረጃ የተፈራች፣ የተከበረችና የተወደደች፤ ዕሴቷ እና ዕምቅ የዕውቀት ሀብቷ በምሁራን የታወቀ፣ በትምህርተ ዓለም ሳይቀር የተቀረጸ፤ በእውነተኛ ሊቃውንት የተመሠከረ፣ ቅርሶቿ የተመዘገቡላት ስትሆን፤ ከፍተኛውን ሐዋርያዊ ተልእኮ እንዲወጡ አደራ በተሰጣቸው ሊቃነ ጳጳሳት በማኅበረሰብ ዕድገትና አስተዳደር ውስጥ ከሕዝብ ጋር በቆመች፣ ከፖለቲካ በጸዳች ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ላይ መንፈሳዊና ሕዝባዊት ተቋምነቷን በመካድ ከፍተኛ የሆነ ሕገ ወጥ ድርጊትና ተቋምን የመናድ እንደሁም መዋቅሯን የማፍረስ ተግባር ተከናውኗል፡-

በዚሁ መሠረት፡-
ሐምሌ 16 እና 23 ቀን 2015 ዓ/ም በክልል ትግራይ በማእከላዊ ዞን አክሱም ሀገረ ስብከት በርእሰ አድባራት ወገዳማት አክሱም ጽዮን ማርያም ገዳም ውስጥ የተፈጸመውን ሕገወጥ የሆነ አስነዋሪ፤ የቀኖና ቤተ ክርስቲያን ጥሰት አስመልከቶ ቅዱስ ሲኖዶስ ሐምሌ 26 ቀን 2015 ዓ/ም አስቸኳይ ምልዐተ ጉባዔ አድርጓል፤

ቅድስት ቤተ ክርስቲያን በደመ ክርስቶስ ከተመሠረተችበት ጊዜ ጀምሮ ያለፈተና የኖረችበት ጊዜ እንደሌለ ቅዱሳት መጻሕፍትና የታሪክ መዛግብት ሲመሰክሩ በዘመነ ሐዋርያት ቢጽ ሐሳውያን፣ በዘመነ ሊቃውንት የተለያዩ መናፍቃን፣… በየጊዜው እየተነሡ ሲፈታተኗት ኑረዋል፡፡ አሁንም በግልጽ እንደሚታየው ከውጭም ከውስጥም በተደራጁ ምንደኞች በመፈተን ላይ ትገኛለች፡፡ ይህንኑ በመረዳትም ቅዱስ ሲኖዶስ የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት አስተዳደር ጉባዔ፣ የሊቃውንት ጉባኤ፤ የሕግ አገልግሎት መምሪያና የህግ ባለሙያዎች አቢይ ኮሚቴ፤ የውጪ ግንኙነት መምሪያ፣ ካቀረቡት ዶግማዊ፣ ቀኖናዊ፣ ታሪካዊና ትውፊታዊ ሰነዶች በመነሣት የቤተ ክርስቲያንን ልዕልና ለማስከበር ያስችል ዘንድ ጥልቅ ውይይት አድርጓል፡፡

በዚህም መሠረት ሐምሌ 16 እና 23 ቀን 2015 ዓ.ም. በክልል ትግራይ በርእሰ አድባራት ወገዳማት አክሱም ጽዮን ገዳም ውስጥ በትግራይ ክልል በሚገኙ ሊቃነ ጳጳሳት፡-
1. አባ ኢሳይያስ
2 አባ መቃርዮስ
3. አባ መርሐ ክርስቶስ
4 አባ ጴጥሮስ መሪነት እጅግ አሳዛኝ ኢ-ሲኖዶሳዊ የሆነ አስነዋሪ፣ ሕገ-ወጥ፣ የቀኖና ቤተ ክርስቲያን ጥሰት በመፈጸም 10 መነኮሳትን በእጩነት በመምረጥና ለዘጠኙ ህገወጥ ሲመት በመፈጸም፣ ሥርወ ትውፊት ዘሐዋርያት የሆነውን የኢትዮጽያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ሐዋርያዊ መንበር በመካድ "መንበረ ሰላማ" የሚባል ህገወጥ መንበር በመሠየምና በህገወጥ መንገድ የሾሟቸውን ግለሰቦች ሊቃነ ጳጳሳት በሚመሯቸው በሀገር ውስጥና በውጪ በሚገኙ አህጉረ ስብከት በሕገ ወጥ መንገድ በመመደብ ከቀኖና ቤተ ክርስቲያን ጥሰት አልፎ አንዲት ኩላዊትና ዓለም አቀፋዊት የሆነችውን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያንን የሚከፋፍል፤ የሀገር አንድነትን የሚሸረሽር እና የሚያፈርስ፣ ምእመናንን ከምእመናን፣ ካህናትን ከካህናት፣ ሊቃውንትን ከሊቃውንት ወጣትን ከወጣት የሚያጋጭ ሰላም የሚያናጋ መሆኑን ቅዱስ ሲኖዶስ ተገንዝቧል። በመሆኑም፤

- የቤተ ክርስቲያን መንበር ሐዋርያዊ ነው፡፡ ሐዋርያዊ መንበር ጌታችን አስተምሮ ከሾማቸው ከዐሥራ ሁለቱ ከሐዋርያት የወጣ አይደለም፤ ሥልጣነ ክህነት የሚተላለፍበት፣ የኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ትምህርተ ሃይማኖት እና ቀኖና ምንጩ ወይም ሥሩ የሚነገርበት፣ የሐዲስ ኪዳን ቤተ ክርስቲያን አማናዊና ሐዋርያዊ ታሪክ፣ ሃይማኖታዊና ቀኖናዊ ትውፊት የሚጀመርበት መነሻ ነው፡፡

- ቤተ ክርስቲያን የምትመራው በሐዋርያት ሥልጣነ ክህነት ነው፤ ይኽንን ሥልጣን ማንም እንደፈለገው ሊከፋፍለው አይችልም፤ በየትም ቦታ ያሉ ጳጳሳት ከቅዱስ ሲኖዶስ እና ከቅዱስ ፓትርያርክ ዕውቅና ውጭ እንደፈለጉ በቡድኑ እየሆኑ መንበር አቋቁመናል ሊሉ አይችሉም፤ ይህ ከቤተ ክርስቲያን ትውፊትና ታሪካዊ ቅብብል ውጭ የሆነ መናፍቅነት ነው፡፡ ከቅዱስ ሲኖዶስ ሕግ እና ሥርዓት ውጭ መውጣት ሕገ ወጥነት፣ ቀኖናን መሻር፣ ኃይማኖትን ማፍረስ ነው፡፡ የገቡትን ቃል መጣስ ነው፤ ከጥንት ጀምሮ መንበር ያለ ፓትርያርክና ከሀገሪቱ ርእሰ ከተማ ውጭ የማይሰየም መሆኑ እየታወቀ መንበር አቋቁመናል ማለት የፓትርያርክን እና የሲኖዶስን ሥልጣን መቃወም፤ ከሃይማኖትም፣ ከቀኖናዊ ትውፊትም፣ ከአስተዳደራዊ መዋቅርም መውጣትና ራሳቸውን ከቤተ ክርስቲያን መንበር የለዩ በመሆኑ ቅዱስ ሲኖዶስ ድርጊቱን አውግዟል፡፡

ይህን ህገወጥ ተግባር ለመፈጸም በሀገራችን ተከስቶ የነበረው ጦርነት እንደ ምክንያት የተጠቀሰ ቢሆንም ቤተክርስቲያን ከጦርነቱ በፊት ጦርነት እንዳይከሰት ያደረገችውን ጥረት በጦርነቱ ወቅት ለተደረጉ ድጋፎችና ከጦርነቱ በኋላ ለተደረጉ የእንወያይ ጥረቶች እንዲሁም በቤተክርስቲያን በኩል የተዘረጋውን የሰላምና የእርቅ በር ይልቁንም ለሰላም ሲባል በቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባዔ የተጠየቀውን ይፋዊ ይቅርታ በመግፋት የተደረገ ኢ-ክርስቲያናዊ ተግባር ነው።

በመሆኑም
• በሕገ ቤተ ክርስቲያን አንቀጽ 16 ንዑስ ቁጥር 30 የአጲስ ቀጶሳት መሾም አስፈላጊ ሆኖ ሲገኝ፣ በቤተ ክርስቲያን ቀኖና መሠረት እንዲመረጡና እንዲሾሙ የመወሰን ሥልጣን የቅዱስ ሲኖዶስ መሆን የሚደነግገውን ክፍል በግልጽ የጣሰ በመሆኑ
• በሕገ ቤተክርስቲያን አንቀጽ 31 ንዑስ ቁ 1 እና 3 የቅዱስ ፓትርያርኩን የመዓርግ ስምና መንበር በተመለከተ የተደነገገውን ድንጋጌ የሚያፋልስ ህገወጥ ተግባር የተፈጸመ በመሆኑ
• በሕገ ቤተ ክርስቲያን አንቀጽ 37 ንዑስ ቁ.1 የኤጲስ ቆጶሳት ምርጫ የሚፈጸመው ኤጲስ ቆጶሳት እንዲሾሙ አስፈላጊ መሆኑ በቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ ሲታመንበትና ሲወሰን ብቻ እንደሚፈጸምና መደንገጉ፤
• በሕገ ቤተ ክርስቲያን አንቀጽ 18 ንዑስ ቁጥር 5 የቤተ ክርስቲያንን ሃይማኖታዊ ሕግጋትንና ቀኖናን የሚያፋልስ ሊቀ ጳጳስ /ኤጲስ ቆጶስ/ ከአባልነት እንደሚሰረዝ በመደንገጉ፤
• በአጠቃላይ የተፈጸመው ሕገ ወጥ ተግባር በሕገ ሰብእም ሆነ በሕገ እግዚአብሔር ሚዛን የተወገዘ ከመሠረተ እምነት የተለየ፣ በአበው ቀኖና፣ በሕገ ቤተ ክርስቲያን እና በቤተ ክርስቲያን አስተዳደር ተቀባይት የሌለው ነው፡፡ ስለዚህ

1ኛ. በፍትሕ መንፈሳዊ አንቀጽ 5 ንኡስ አንቀጽ 138 መሠረት ሐምሌ 16 እና ሐምሌ 23 ቀን 2015 ዓ.ም በክልል ትግራይ በማዕከላዊ ዞን አክሱም ሀገረ ስብከት በርእሰ አድባራት ወገዳማት አክሱም ጽዮን ቤተክርስቲያን ውስጥ
1. ብፁዕ አቡነ ኢሳይያስ የመቀሌ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ የእንቅስቃሴው ሰብሳቢ
2. ብፁዕ አቡነ መቃርዮስ በክልል ትግራይ የማዕከላዊ ዞን አክሱም ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ
3. ብፁዕ አቡነ መርሐ ክርስቶስ የአዲግራት ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ
4. ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ የሽሬ እንዳሥላሴ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ

የቤተ ክርስቲያንን ቀኖና በመጣስ ባልተሰጣቸው ስልጣን 9 ኤጴስ ቆጰሳትን ሾመናል፤ ሲኖዶስ አቋቁመናል በማለት በተለያዩ ሚዲያዎች በሰጡት መግለጫና በክልሉ መንግሥት ሚዲያ በተላለፈው የቀጥታ ስርጭት የተረጋገጠ በመሆኑ በዚሁ ድርጊታቸው በሀገር ውስጥም ሆነ በውጭው ዓለም የሚኖረውን ሕዝበ ክርስቲያንን በማታለል የክህደት እና የኑፋቄ ተግባር በመፈጸማቸው በመንፈስ ቅዱስ የሚመራው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ አውግዞ፤ ከቤተ ክርስቲያን የተሰጣቸውን ከዲቁና ጀምሮ ያለው ሙሉ ሥልጣነ ክህነት በመሻር አውግዞ ለይቷቸዋል፡፡

በመሆኑም፡-
ሀ. ሥልጣነ ክህነታቸውና የማዕረግ ስማቸው በቅዱስ ሲኖዶስ ምልዐተ ጉባኤ ውሳኔ የተነሣ ስለሆነ ከዛሬ ሐምሌ 26 ቀን 2015 ዓ.ም ጀምሮ በቀድሞ ዓለማዊ ስማቸው እንዲጠሩ፤
ለ. በቤተ ክርስቲያናችን መንፈሳዊ አገልግሎት ዙርያም በሕይወትም ሆነ በሞት ማናቸውንም መንፈሳዊ አገልግሎት እንዳያገኙ ቅዱስ ሲኖዶስ አውግዞ ከቤተ ክርስቲያን ለይቷቸዋል፡፡
• ይሁን እንጅ ከላይ በስም ተጠቅሰው የተወገዙት ግለሰቦች በሠሩት የቀኖና ጥሰት ተጸጽው ይቅርታን ቢጠይቁ የቅድስት ቤተ ክርስቲያን የምህረት ደጆች ሁል ጊዜ ክፈት መሆናቸውና በቀኖና ቤተ ክርስቲያን መሠረት የምንቀበላቸው መሆኑን ቅዱስ ሲኖዶስ ያሳውቃል፤
2ኛ. የቅዱስ ሲኖዶሱንና የቤተ ክርስቲያኒቱን ልዕልና በመዳፈር እና ቀኖና ቤተ ክርስቲያንን በመጣስ በተነሳሱ ግለሰቦች አማካኝነት የኤጲስ ቆጶስነት ሹመት አግኝተናል፤ ተሹመናል እያሉ የሚገኙ 9 መነኮሳት

፩. አባ ዘሥላሴ ማርቆስ
፪. አባ ኃይለ ሚካኤል አረጋይ
፫. አባ እስጢፋኖስ ገብረ ጊዮርጊስ
፬. አባ መሓሪ ሀብቶ
፭. አባ ኤልያስ ታደሰ ገብረ ኪዳን
፮. አባ ጽጌ ገነት ኪዳነ ወልድ
፯. አባ ዘርአ ዳዊት ብርሃነ
፰. አባ ዮሐንስ ከበደ
፱. አባ የማነ ብርሃን ወልደ ሳሙኤል

በሕገ ወጥ መንገድ ቀኖና ቤተ ክርስቲያንንን ጥሰው የተገኙ በመሆኑ አስቀድሞ ከቤተ ክርስቲያን የተሰጣቸው ከዲቁና ጀምሮ ያለው ሙሉ ሥልጣነ ክህነት ተሽሮ ከዛሬ ሐምሌ 26 ቀን 2015 ዓ.ም ጀምሮ በቤተ ክርስቲያናችን መንፈሳዊ አገልግሎት ዙርያ በሕይወትም ሆነ በሞት ማናቸውንም መንፈሳዊ አገልግሎት እንዳያገኙ ቅዱስ ሲኖዶስ አውግዞ ከቤተ ክርስቲያን ለይቷቸዋል፡፡

3ኛ. ይህ ህገወጥ ሢመት እንዲፈጸም ከመጀመሪያው ጽንሰ ሀሳብ ጀምሮ መሪ ተዋናይና ቀስቃሽ በመሆን ኢትዮጵያን ኤልዛቤል በማለትና ስሟን የሚጠራ የተረገመ ይሁን በማለት እንዲሁም ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ጋር የዶግማ ልዩነት አለን በማለት የኑፋቄ ትምህርት በተለያዩ መገናኛ ብዙኃን የተናገሩትና በህገወጥ ሢመቱ ላይም በእጩነት ተመርጠው በሂደት ላይ ያሉት አባ ሠረቀ ብርሃን ወልደ ሳሙኤልና ሂደቱን በዋና አስፈጻሚነት በመምራትና መግለጫ በመስጠት ላይ ያሉት መ/ር ተስፋዬ ሐደራ ከዛሬ ሐምሌ 26 ቀን 2015 ዓ/ም ጀምሮ በቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ ተወግዘው ከቤተክርስቲያን ተለይተዋል።

ከላይ በስም ተጠቅሰው የተወገዙት ግለሰቦች በሠሩት የቀኖና ጥሰት ተጸጽው ይቅርታን ቢጠይቁ የቅድስት ቤተ ክርስቲያን የምህረት ደጆች ሁል ጊዜ ክፈት መሆናቸውና በቀኖና ቤተ ክርስቲያን መሠረት የምንቀበላቸው መሆኑን ቅዱስ ሲኖዶስ ያሳውቃል።

4ኛ. “መንበረ ሰላማ” የሚለው ሕገወጥ ሥያሜን በተመለከተ በቅድስት ኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ትውፊትም ሆነ በቀደምት አብያተ ክርስቲያናት ትውፊት የማይታወቅ፣ ሃይማኖታዊ መሠረት የሌለው፣ ከቀኖና የወጣ፣ አስተዳደራዊ መዋቅርን የሚያዛባ በመሆኑ የኢትዮጵያ ኦርቶዶከስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን አትቀበለውም፤ በተጨማሪም ከአንዲት፣ ቅድስት፣ ሐዋርያዊትና ዓለም አቀፋዊትየሆነች የኢትዮጵያ ኦርቶዶከስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሐዋርያዊ መንበር መሠረተ እምነት፣ ታሪክና ቀኖና፣ ከአስተዳደር እና ሕግ ባፈነገጠ ሁኔታ ትውፊትን በመዳፈር ጎሣን መሠረት አድርጎ የተፈጠረ ሕገ ወጥ አደረጃጀት በመሆኑ የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ አውግዞታል፡፡ ይሕንንም የክርስትናን ትውፊት እና ሐዋርያዊ መሠረት የሚዛባና ቅድስት ቤተ ክርስቲያንን የማይወክል መሆኑ ታውቆ በመላው ዓለም ለሚመለከተው ሁሉ በደብዳቤ እንዲገለጽ እንዲደረግ፤

6. በየደረጃው የሚገኙ የቤተ ክርስቲያኒቱ የሥራ ኃላፊዎች፤ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን፤ መነኮሳት፤ አገልጋይ ካህናት፤ የሰንበት ትምህርት ቤት ወጣቶች፤ ልዩ ልዩ የቤተ ክርስቲያኒቱ መንፈሳዊ ማህበራት እና ምእመናን እና ምእመናት ይህን ሕገ ወጥ አድራጎት ከመከላከል እና የቤተ ክርስቲያናችሁን ደህንነት ከመጠበቅ በተጨማሪ ለዚህ ሕገ ወጥ አድራጎት ልዩ ልዩ ድጋፍ የሚያደረግ ተቋማት እና ግለሰቦችን አስፈላጊውን ክትትል እና ቁጥጥር በማድረግ የመከላከል ሥራችሁን እንድትወጡ ዘንድ ቅዱስ ሲኖዶስ ወስኗል፡፡

8. የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ስምን ከፊትም ሆነ ከኃላ በመጨመር እና በመቀነስ በከፊልም ሆነ በሙሉ መጠቀም፤ ዓርማዋን፤ አድራሻዋን፤የአምልኮ እና የሥርዓት መፈጸሚያ የሆኑ ንዋያ ቅዱሳትንና አልባሳት እንዲሁም መጻሕፍት መገልገል የማይችሉ መሆኑ ታውቆ ይህንን ጉዳይ በየደረጃው ያሉ መንግሥታዊ አካላት እና የቤተ ክርስቲያኒቱ የሥራ ኃላፊዎች ተከታትለው እንዲያስፈጽሙ ቅዱስ ሲኖዶስ የወሰነ ሲሆን በተጨማሪም ይህን ውሳኔ ተላልፈው በሚገኙ ማናቸውም ግለሰቦች እና ተቋማት ላይ ተገቢውን ሕግ አግባብ ተከትሎ በሀገር ውስጥም ሆነ በውጭ ዓለማት የሚያስፈጽም ዓለም አቀፍ እና ሀገር አቀፍ የሕግ ባለሙያዎች በመመደብ ተገቢውን ሁሉ በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽ/ቤት በኩል እንዲፈጸም ቅዱስ ሲኖዶስ ወስኗል፡፡
9. በሀገር ውስጥም ሆነ ከሀገር ውጭ የሚገኙ መንግስታዊም ሆነ መነግስታዊ ያልሆነ ተቋማት፤ አኃት አቢያተ ክርስቲያናት፤ የምሥራቅ ኦርቶዶክስ አብያተ ክርስቲያናት፤ የሮም ካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን እና ሌሎች አብያተ ክርስቲያናት፤ የዓለም አቢያተ ክርስቲያናት ምክር ቤት፤ የመላው አፍሪካ አብያት ክርስቲያናት ጉባዔ እና ሌሎች የአብያተ ክርስቲያናት እና የሃይማኖት ጉባኤዎች በሙሉ እነዚህ የተወገዙት ግለሰቦች የኢትዮጵያ ኦርቶደክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንን የማይወክሉ እና ምንም አይነት የሥራ ግንኙነት የሌላቸው መሆኑ ታውቆ ማናቸውም ግንኙነት በቤተ ክርስቲያኑቱ ስም እንዳያደርጉ በጽሑፍ አንዲገለጽ ቅዱስ ሲኖዶስ ወስኗል፡፡

11. እነዚህ ግለሰቦች የፈጸሙት ተግባር ሃይማኖቱን የሚወድ፣ አባቶቹን የሚያከብር እና አስተዋይ የሆነውን የትግራይ ሕዝብ የማይወክል፣ የራሳቸውን የሥልጣን ጥማት ለማርካት ያደረጉት ሕገወጥ የቀኖና ጥሰት መሆኑ እንዲታወቅ፤ በተጨማሪም ለሚያሠራጩት የሐሰት አሉባልታ ወደፊት ተገቢው መልስ እንዲሰጥበት ቅዱስ ሲኖዶስ ወስኗል።

12. ይኽ ሕገወጥ አደረጃጀት ከረጅም ጊዜ ጀምሮ የታሰበበት፤ በየጊዜው የነበሩ የፖለቲካ እና የመንግሥት ኃላፊዎች በመታገዝ ሥር የሰደደ ድብቅ አጀንዳ በሚያስፈጽሙ ግለሰቦች የተቀናበረ መሆኑን ቅዱስ ሲኖዶስ ተገንዝቦ ቅዱስ ሲኖዶስ አውግዞታል፡፡ በመሆኑም ሕገ ወጥ አደረጃጀትን ማምከን እና ቤተ ክርሰቲያንን ነፃ ማድረግ የሚቻለው ጠንካራ ውስጣዊ አደረጃጀት እና ዓለም አቀፍ እንቅስቃሴ ሲደረግ በመሆኑ ከቅዱስ ሲኖዶስ አባላት ጀምሮ ሊቃውንት፣ መላው ውሉደ ክህነት፣ ወጣቶች ሰንበት ትምሀርት ቤት አባላት፣ መንፈሳውያን ማኅበራት፣ ምእመናን እና የቤተ ክርስቲያን ወዳጆች በሙሉ በመጾም፣ በመጸለይ፣ የቤተ ክርስቲያንን ተልእኮና መዋቅር በጠበቀ መልኩ በመደራጀት አፍራሽ እና የጥፋት መረጃዎችን፣ በመሰብሰብ፣ በመተንተን፣ ለውሳኔ በማቅረብ የቤተ ክርስቲያን ሁለንተናዊ ደኅንነት እስኪረጋገጥ ድረስ ያለማቋረጥ በመንፈሳዊ ተጋድሎ መበርታትና የመጣብንን ፈተና በጽናት መታገል እንደሚገባ፣ ቅዱስ ሲኖዶስ ያሳስባል፡፡

13. በአሁኑ ወቅት በሀገራችን በተለያዩ ክፍሎች እየተከሠተ ያለውን የሰላም መደፍረስ እና የእርስ በርስ ግጭት ምክንያት የሰው ሕይወትና የንብረት ውድመት የተፈጠረ አለመግባባት ካለፈው ስህተታችን በመማር ችግሩን ተቀራርቦ በውይይትና በእርቅ እንዲፈታ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ለሁሉም አካላት የሰላም ጥሪዋን ታስተላልፋለች፡፡

14. እንደ ሀገር የገጠመንን የሰላም መደፍረስ በተመለከተ ዘላቂ መፍትሔ በማፈላለግ እንደ ቤተ ክርስቲያን ስለ ሰላም ጉዳይ የሚሠሩ ከብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት፣ ከሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን፣ ከሀገር ሽማግሌዎች እና ምሁራን ያካተተ ዐቢይ ኮሚቴ በቋሚ ሲኖዶስ በኩል ተቋቁሞ ሥራው እንዲሠራ ወስኗል፡፡

በመጨረሻም እስከ አሁን ድረስ በተፈጠረው ችግር ምክንያት ከቅድስት ቤተ ክርስቲያን ጎን በመሆን አጋርነታችሁን ያሳያችሁ፣ ለቤተ ክርስቲያን አንድነት እና ሉዐላዊነት መከበር የበኩላችሁን በመወጣት መግለጫ የሰጣችሁ ሁሉ በልዑል እግዚአብሔር ስም እያመሰገንን ለወደፊቱም በጸሎታችሁ እና በመልካም አጋርነታችሁ ከጎናችን እንድትሆኑ ቅዱስ ሲኖዶስ ጥሪውን ያስተላልፋል፡፡
እግዚአብሔር ኢትዮጵያን ይባርክ
ሐምሌ 26 ቀን 2015 ዓ.ም.
አዲስ አበባ ኢትዮጵያ
#የጽዮን_መቀነት
🌈✿ ✥ ✦━

መጪው ጾመ ፍልሰታ ሰሙነ ሱባኤ ነው። በዚህ ወቅት መቸውንም የማይዘነጋውን የቅዱሳን ሐዋርያትን ሐዘን ሐዋርያዊቷ ቤተክርስቲያን በላቀ ትኩረት ታስባለች !

ከክርስቶስ መከራ መስቀል በታች የፍጥረት ሁሉ ጸወን (ምሽግ) የሆነች ጽዮን ማርያምን ማጣት ፣ የሕይወት መሠረት የምትሆን ወላዲተ አምላክን በሞት መነጠቅ እና የትንሣኤ እናት አዛኝቷ ድንግልን ቀብሮ መመለስ… ይኽን የመሰለ ሐዘን በሐዋርያቱ ዘንድ ደርሶ ያውቅ ይሆን? እንጃ!

ይህን ጥልቅ ሐዘን ያስወገደው ሞትን ያሸነፈ ሕይወት ፡ መቃብርን የረታ ትንሳኤ ፡ ርደትን ድል የነሳ ዕርገት በጽዮን መቀነት በሰበነ ማርያም ለሐዋርያቱ የተበሠረው የምሥራች ነው። አብሣሪው ሐዋርያ ቅዱስ ቶማስ ዘሕንደኬ ነው።

ሐተታው እንዲህ ይተረካል

«ጌታችን ሦስት መዓልት ሦስት ሌሊት በከርሰ መቃብር ቆይቶ ሙስና መቃብር (የመቃብር ጥፋት) ሳያገኘው፣ መግነዝ ፍቱልኝ መቃብር ክፈቱልኝ ሳይል በሥልጣኑ እሑድ በመንፈቀ ሌሊት እንደተነሣ ሁሉ እርሷም በተቀበረች በሦስተኛው ቀን ማኅደረ መለኮት ናትና ሙስና መቃብር ሳያገኛት መግነዝ ፍቱልኝ፣ መቃብር ክፈቱልኝ ሳትል የልጅዋ ሥልጣን ኃይል ሆኗት በመነሣቷ ትንሣኤዋ “ከመ ትንሣኤ ወልዳ፤ እንደ ልጅዋ ትንሣኤ” ነው ተብሎ ይመሰከራል! »

የድንግል መካነ ዕረፍት በጌቴሴማኒ ነው፤ ሥርዓተ ቀብሯ በተፈጸመ ጊዜ ከአሥራ ሁለቱ አንዱ ቶማስ ዘሕንደኬ አልነበረምና ከሀገረ ስብከቱ በደመና ተጭኖ ወደ ኢየሩሳሌም ሲመጣ እመቤታችን በተቀበረች በ«ሦስተኛው» ቀን እንደ ልጅዋ ትንሣኤ ተነሥታ ስታርግ ያገኛታል፡፡ ትንሣኤዋን ሌሎቹ ሐዋርያት አይተው ለእርሱ የቀረበት መስሎት ተበሳጭቶ “በመጀመሪያ የልጅሽን ትንሣኤ አሁን ደግሞ የአንቺን ትንሣኤ ሳላይ ቀረሁ” ብሎ ከማዘኑ የተነሣ ከደመናው ተወርውሮ ሊወድቅ ቃጣው፡፡ እመቤታችንም ከእርሱ በቀር ሌሎቹ ሐዋርያት ትንሳኤዋን እንዳላዩ ነግራው አጽናንታዋለች፤ የተጽናናው ቅዱስ ቶማስ ያዘኑትን ወንድሞቹን እንዲያጽናና የሆነውን ሁሉ እንዲነግራቸው አዝዛው #ምልክት_ይሆነው_ዘንድ_ሰበኗን_ሰጠችው በዚያ ገንዘዋት ነበርና።

ቅዱስ ቶማስም ኢየሩሳሌም በደረሰ ጊዜ ሐዋርያት በሐዘን እመቤታችንን‘ኮ ቀበርናት ብለው ነገሩት እርሱም የበለጠ ይደነቁ ብሎ “ሞት በጥር በነሐሴ መቃብር እንዴት ይሆናል?” አላቸው፡፡ “አንተ እንጂ ቀድሞ የጌታን ትንሣኤ ተጠራጠርክ አሁንም አታምንምን?” ብለው በቅዱስ ጴጥሮስ መሪነት ወደ እመቤታችን መካነ መቃብር ይዘውት ሔዱ በዚያም መቃብሯን ቢከፍቱ እንኳን ለእርሱ የሚያሳዩት ለራሳቸውም ያዩት ነገር አልነበረም፤ ሥጋዋን በማጣታቸው ደግመው በሐዘን ተዋጡ እጅጉንም ደነገጡ። ያኔ ሐዋርያው ቶማስ “አታምኑኝም ብዬ እንጂ እመቤታችን ተነሥታ ዐርጋለች” ብሎ የሆነውን ሁሉ ነገራቸው፡፡ የምሥራቹ ብሥራት ማረጋገጫ ምልክት እንዲሆን ጽዮን ድንግል ማርያም የሰጠችውን ሰበኗን አሳያቸው፡፡

☞ ይኽ ሰበኗ መቀነቷ ነው ፣ መታጠቂያዋ ነው ፣ መግነዟም ነው! በገዛ እጇ ከግመል ጠጉር ያሰናዳችው ስለመሆኑ የትውፊት ምስክርነት አለ።

ያንን መቀነት ለበረከት ቆራርጠው ከተከፋፈሉ በኋላ ብዙኅ ገቢረ ተአምራት ፡ ታላላቅ ኅብረ መንክራት እያደረጉበት ወደ የአህጉረ ስብከታቸው በደስታ ሄደዋል፡፡ ምስክርነቱን ለማጽናት ዛሬም ሠራዒ ዲያቆኑ በቅዳሴ ጊዜ በሚይዘው መስቀል ላይ የሚደረገው ጨርቅ የእመቤችን ሰበን ምሳሌ ሆኖ ሐዘናችን በተስፋ ሊታበስበት ይታያል።

ለእኛም የትኛው ቶማስ ይሆን የማርያምን መቀነት አምጥቶ ከሐዘን የሚያረጋጋን?

ለዛሬው ይህን ምሥጢራዊ ሰበን ከሁለት ወቅታዊ ፈተናዎች ጋር አያይዘን ብንመካከርበትስ አልኩ!
አንዱ እሳተ ሰዶምን ያዘነበ ግብረ ገሞራ (እሳተ ገሞራን ያዘነበ ግብረ ሰዶም ቢል አንድ ነው ቃለ ጸሐፊ ነው… )
ሁለተኛው በመንበር ሰበብ ያየነው መከፋፈል

የማርያም ሰበን እና ግብረ ሰዶማዊነት
✥ °°°🌈°°°°°°°🌈°°°°°°°° ✥

ኪዳነ ምሕረትን ትእምርተ ኪዳኑ ለኖኅ ይሏታል። በዚህ መነሻ የማርያም መቀነት የኖኅ ቃልኪዳን ምልክት የሆነው የቀስተ ደመና ሌላ ስሙ ሆኖ ሲጠራበት እንሰማለን። ያንን በኖኅ በኩል ፍጥረቱን ከጥፋት ለማዳን ለምሕረቱ ማሳያ በምልክትነት ከሰማይ ቀስተ ደመናውን እያሳየ ምልክት እንደሠጠ ፡ ይኽን በቶማስ በኩል የሐዋርያት ሐዘን እንዲርቅ ሰበኗን ለምልክት ሠጥታቸዋለች። ዛሬም ለእኛ ከጥፋት ማምለጫ ከሞት መውጫ እንዲሆን የተገባላትን ቃልኪዳን በቀስተ ደመና ቀስተደመናውን በማርያም ሰበን ወክለን «የጽዮን መቀነት ያድነን ከጥፋት» እያልን ወደላይ አንጋጠን ደጅ እንጠናበታለን። በዓለምም ላይ የበጎ ትግል መገለጫ አድርገው አንዳንዶች ተጠቅመውበታል፤ ለምሳሌ በ1994 ዴዝሞን ቱቱና ኔልሰን ማንዴላ የድኅረ አፓርታይድ ዴሞክራሲያዊ ሀገር ዜጎች መጠርያ ይሁን ብለው ነበር። በዚህም የቀስተደመና ሕዝብ በሚል መጠሪያ ዜጎች ታውቀዋል። በሀገሪቱ ሰንደቅ ያለውን የ6 ቀለማት ውክልና እንደሥጦታ አይተው ቀስተደመናዊ [Rainbowism] እንቅስቃሴ የጸረ ዘረኝነትን መገለጫ ሆኗቸው ለነጻነት እንደውክልና አገልግሏል።

ይሁንና አንዳንዶች መቀጣጫ ቀስቱ የተመለሰ ባለኅብር ደጋን [multicoloured circular arc] የመሰለውን ምልክት ዛሬ ላይ በማይገባ መንገድ ለማይገባ ዓላማ መገለጫችን ነው እያሉ ከዓላማው በተጻረረ መንገድ ፡ ቅዱስ ዳዊት "ወረሰዩ ትእምርቶሙ ትእምርተ ዘኢያእመሩ ⇨ የማያውቁትንም ምልክት ምልክታቸው አደረጉ” እንዳለው ቀስተደመናን ያላወቁት ባላወቁት መንገድ እንጠቀምበት ብለው ይኽን የሚያረጋጋውን ምልክት ሁከት የሚፈጥር ፤ ይኽን ሰላም ሠጪውን ዐርማ መንፈስ የሚያስጨንቅ … እናድርገውታል【መዝ ፸፫፥፬】

እንደጊዜአዊ አቋም ስለእነዚህ "ስም አይጠሬ” ነውረኞች አብዝቶ ማውራት፣ ትኩረት መስጠት መረጃ ማዛመትና ዓላማቸውን ማሳካት እንደሆነ ስለማምን ለግንዛቤ ጥቂት ካልን በተከታዩ የቅዱስ መጽሐፍ ቃለ ተማጽኖ እንለፈው።
☞ “ምልክትንም ለመልካም ከእኛ ጋር አድርግ”【መዝ ፷፮ ፥ ፲፯】

የማርያም ሰበን እና የመንበር መከፈል!
✥ °°°🌈°°°°°°°🌈°°°°°°°° ✥

በአንዲቷ ኅብረ ክርስትና የጸኑ ሐዋርያት ሰበኗን ተከፋፈሉና ዓለምን ዞረው አስተማሩ እንጂ እርስ በእርስ ተከፋፈሉ የሚል ከምንም አናገኝም። ከሰሙኑ የታቦተ ጽዮን ማደርያ የቅዱሳኑ ገዳማት መኖርያ የሰሜን ክፍል መንበረ ሰላማ ይባል የሚል የቤት-ሥራ ሰጥተው የሚከፋፍሉን ጥርስ ያወጡ ጉዶች እያየን ነው። በተመሳሳይ ፈተና የወደቀችውን የሕንድ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን ለዚህ ጉዳት ክብደት ማሳያ አድርገን በምሳሌነት እናንሳ።

ጥንቱን አንድ የነበረችው የሕንድ ኦርቶዶክሳዊት ቤተክርስቲያን ዛሬ ለሦስት ተከፋፍላለች
① ማርቶማ (በተሐድሶ ኑፋቄ የተከፈለ)
② የጃኮባይት ኦርቶዶክስ ሲሪያን ቤተ ክርስቲያን (አስተዳደርን መነሻ አድርጎ በመንበር ሰበብ የተከፈለ)
③ የማላንካራ ቤተክርስቲያን በሐዋርያዊ እምነቷ ጸንታ የቀረች
ቀደም ብሎ በቅኝ ግዛትና በእርዳታ ሰበብ ወደ ቅዱስ ቶማስ ልጆች ያቀኑ ሚሲዮናውያን በይበልጥ ካቶሊካውያንና ፕሮቴስታንቱ እንዲሁም በ፲፱ኛው መ/ክ/ዘ በውሥጥ ተሰግስገው ቤተክርስቲያኒቷን በተሐድሶ ከፈልናት ያሉ ማርቶማዎች እየተፈራረቁ ዘምተው በሀገረ ሕንድ ካሉና ቅዱስ ቶማስ ከሠራቸው ሰባት ተኩል አብያተ ክርስቲናት ውሥጥ (ስምንተኛውን ሳይጨርስ በሰማዕትነት በማረፉ) ከሦስቱ በቀር ሌሎቹን አብያተ መቅደሶችና ከርትዕት ቤተክርስቲያን ልጆች አያሌዎቹን አስክደው ነጥቀዋል።

ይህ ሳይበቃ ሁለተኛው ወገን ጥያቄው የመንበር በማስመሰል አስተዳደርን ወደ ወደ ቀደመው የሶርያ መንበር እንመልስ የሚል ጥያቄ በማንሳትና የእርስ በእርስ መከፋፈል መርዝ በመትከል ለብዙ ቅርስና ለሚሊዮን የቤተክርስቲያኒቷ ልጆች መነጠቅ ምክንያት ሆኖ እየፈተናት ይገኛል።

የመንበር ጉዳይ በሕንድ ቤተክርስቲያን ?
✥ °°°°°🌈°°°°°°°🌈°°°°°°°° ✥

ከ፪ ዓመታት ቀድሞ ወንድማችን መኮንን ሀብተሚካኤል Mekonnen Habtemichael እጅግ ቁጭት በተመላ የበረሃ ምንጮች (ማላንካራውያን) በሚል እጅግ አስተማሪ መጽሐፉ ይህን እያነሳ የእኛም በዘርና በጎሳ መከፋፈል ወደ መንበር ጥያቄ ማደጉ እንደማይቀር እንደ ቃለ ትንቢት ሥጋቱን ገልጦ እንነበር እናያለን።

የሕንድ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን የየዘመናቱ ተግዳሮትና ለብዙ ችግሮች ምንጭ እንደሆነ በጥልቅ ምክክር የታመነበት የመንበር ጥያቄ ቤተክርስቲያኗ ራሳን ችላ የሕንድ ማላንካራ ቤተክርስቲያን በሚል ከሲርያ መንበር እንድትለይ ሆኖ ነበር ። (የኢትዮጵያ ቤተክርስቲያን ከግብፅ ቤተክርስቲያን የተለየችውም በተመሳሳይ ርምጃ መሆኑን ልብ ይሏል) ከ1653 ጀምሮ የላቲኑን ቀንበር ጥላ በኦርቶዶክሳዊ ፍኖት ትጓዝ የነበረችው የማላንካራ ሜትሮፖሊታን በ1912 ዓ.ም. በማላንካራ ቤተክርስቲያን በተከሰተው ነውጥ (Turmoil) ስትፈተን የአንጾክያ ቤተክርስቲያን ጣልቃ በመግባት እግድ አስተላልፋባት ነበር። ያኔ ነበር ቤተክርስቲያኗ ራሷን ከአንጾክያ (ሲሪያ) መንበር ነጻ አውጥታ የመጀመርያው የምሥራቅ ማላንካራ ካቶሊኮስ እንዲሆኑ ቅዱስነታቸውን ብፁዕ አቡነ ባስልዮስ ጳውሎስ 【His Holiness Baselios Paulos The First Catholicos ofthe East in Malankara (1912-1913)】በፕትርክና ማዕረግ የሾመችው።

በቅርቡ ግን በሐዋርያት ወራሴ መንበርነት የምትታወቀዋን መንበረ ቶማስ ትተው የንጾክያ መንበር መሥራች የሆኑ በሚል ቅዱስ ጳውሎስና ቅዱስ ጳውሎስን አንስተውና በሮማው የቅዱስ ጴጥሮስ ላዕለ ኵሉ ርእሰ መንበርነት ሐሳብ ተጠልፈው ከ2002 ዓም ጀምሮ ራሳቸውን ከፍለዋል [The Jacobite Syrian Orthodox Church of India accepted the Petrine primacy and supremacy of Patriarchs akin to the Church of Rome.]

በመንበር ሰበብ አንድ ሚሊየን ሕዝብ ይዘው በአሜሪካ ካናዳ እንግሊዝ ምዕራብ አውሮፓ አውስትራሊያና ሌሎች ሀገራት ሀገረ ስብከት በመክፈት የሕንድ ቤተክርስቲያንን አዳክመዋል።

የማርያም መቀነትና የሕንድ አዲሱ መንበር
✥ °°°°°°°🌈°°°°°°°🌈°°°°°°°° ✥

በቅዱስ ቶማስ በኩል የተላከውን የእመቤታችን ሰበን (የጽዮን መቀነት) ሐዋርያቱ ለበረከት ቆራርጠው ከተከፋፈሉ በኋላ ብዙኅ ገቢረ ተአምራት ፡ ታላላቅ ኅብረ መንክራት እያደረጉበት ወደ የአህጉረ ስብከታቸው በደስታ እንደሄዱ ከላይ ዐይተናል።

ርቱዓን ሐዋርያቱ የተከፋፈሉበት ሳይሆን የተከፋፈሉት ይህን መቀነት The Girdle of Thomas, Virgin's Girdle, Holy Belt, Sacra Cintola , the Cincture of the Theotokos … በሚል መጠርያ በዓለማችን በታላቁ የምሥራቃውያን መካነ ምናኔ ማውንት አቶስን (Vatopedi Monastery on Mount Athos) ጨምሮ በብዙ ቦታ በክብር ተቀምጦ ይጎበኛል።

በሕንድ የቀረው የጽዮን መቀነት የቅዱስ ቶማስ በረከት ግን በመንበር ጥያቄ ሰበብ በተከፈለው ቤተክርስቲያን Manarcad Church (The Holy Girdle of the Virgin Mary ) ሥር መውደቁ የእናት ቤተክርስቲያን የሁል ጊዜ ሐዘንና የማይሽር የመከፋፈል ጠባሳ ሆኖ ያለመፍትሔ ቀርቷል!

የእኛውስ በመንበር ሰበብ መከፋፈል ጥያቄ ወዴት እያመራ ይሆን?
አክሱም ጽዮን ሳስባት የሕንዱ የማርያም ሰበን ቤተ መቅደስ ዕጣ ፈንታ የተጋረጠባት ይመስለኛል! የቃልኪዳኑ ምልክት ታቦተ ጽዮንን እጅ መንሳት የባዕዳንን ደጅ እጅ እንደመንሳት ኅሊናችን እንዲቆጥር አስጨናቂዎች ዕረፍት በማጣት የዋሃንን ሲያስቱ እያየን ነው።

ደብረ ዳሞን ፣ ደብረ በንኮልን ፣ ደብረ ሃሌሉያን ፣ እንዳ ገሪማን ፣ አባ ጰንጠሌን ፣ መርዓዊ ክርስቶስን፣ አቡነ ኢዮስያን፣ ገርአልታን ፣ ጉንዳ ጉንዶን፣ አቡነ ቶማስን ፣ አቡነ ይምዓታን ፣ አብርሃ ወአጽብሃን … ፻፲፭ቱ ጥንታውያን ገዳማት … ስንቱን ዘርዝሮ መጨረስ ይቻላል? ብቻ ብዙ የብዙ ብዙ የሆኑ ሀብቶቻችንን ማንም ምእመን የእኔ የሚላቸው የቤተክርስቲያናችን ቅርሶች ዛሬን መንበረ ሰላማ በሚል ሩጫ መከፋፈሉ ተጀምሮ ነገ ላይ የሌላ እንዳይባሉ አርቆ በማሰብ መሥጋትና መጨነቅ ይገባል።

በእኛውም ቢሆን የአባ ሰላማ ከሣቴ ብርሃን ዘመነ ጵጵስና በግብፅ መንበር ጥላ ሥር የነበረ እንጂ መንበረ ሰላማ የሚል ያልነበረም የሌለም የማይኖርም እንደሆነ ታሪክና ቅንነት በአስረጂነት ይቀርባል።

በሰሙንኛው ችግር ዙርያ መወጋገዝን እንደጊዜአዊ እሳት ማጥፊያ እንጂ እንደዘላቂ መፍትኼ ማየት ተገቢ አይመስለኝም። ይህን ያልተረዱና ዐርቀው ያላዩ ግን ለመቁረጥና ለመቆራረጥ እንቅልፍ ሲያጡ ማየት በእጅጉ ያሳምማል።

የከሰመውን ተሐድሶ ለመመለስ ከሚውተረተረው ፍኖተ ድድቅ ሩጫ (ድድቅ ያልታሰበ አደጋ ማለት ነው፤ ጽድቅ ብሎ መጥራት ስለማይገባ «ፍኖተ ጽድቅ« ነን ባዮችን ነው ፍኖተ ድድቅ ያልኩት) እና የመንበር ጥያቄ ሰበብ ሊከፋፍለን እንቅልፍ ከሚያጣ የጊዜው ከፋፋይ አጀንዳ ቤተክርስቲያንን ለመታደግ ዘመን መቅደም ዓለሙን መረዳት ቢቻል መልካም በመሆኑ የሕንድን የጭንቅ ዘመን መፍትሔ መመሪያና መማሪያ ብናደርገው።

የሕንድ ቤተክርስቲያን የወሰደችው ርምጃ ምን ነበር?
✥ °°°°°°°°°°🌈°°°°°°°°°°🌈°°°°°°°°°°° ✥

የሐዋርያው ቅዱስ ቶማስ ፺፩ኛ ወራሴ መንበር የሆኑት ቅዱስነታቸው አቡነ ባስልዮስ ማርቶማ ዲዲሞስ ቀዳማዊ በእርጅና እና ዘመን የዋጀ አገልግሎት በሚፈለገው መጠን በሚጠበቀው ደረጃ እንዲሠጥ በሚሉ አሳማኝ ምክንያቶች በፈቃዳቸው ሥልጣን ሲለቁ (abdication) ገና በ፴፮ ዓመታቸው ለጵጵስና ተመርጠው የነበሩትና ቀድሞውኑ ተተኪ ካቶሊኮስ የነበሩት ረዳት ፓትርያርክ ከ2010 ጀምሮ ቅዱስ ፓትርያርክ አቡነ ማር ቶማ ጳውሎስ ካልዕ ተብለው በካቶሊኮስነት ተሹመው ቤተክርስቲያኗን ወደቀደመ ልዕልናዋ ለመመለስ እስከ ዕለተ ዕረፍታቸው በብዙ ደክመዋል ። ቅዱስነታቸው ከመንፈሳዊ ትምህርት ብቃት ጋር በሶሺዮሎጂና ቢዝነስ አድሚኒስትሬሽን የሁለተኛ ድግሪ ባለቤት መሆናቸው ዓለሙን ለማወቅ ዘመን ለመቅደም ረድቷቸው እንደ 92ኛ የቶማስ መንበር ወራሽ ፣ 8ኛው የማላንካራ ቤተክርስቲያን ካቶሊኮስና 21ኛው የማላንካራ ሜትሮፖሊታን የነበሩት ታላቁ አርቆ አሳቢ ባስልዮስ ማርቶማ
ጳውሎስ በሳንባ ካንሰር ተጠቂነታቸው የሕክምና ክትትል ሲደረግላቸው ቆይቶ ለኮሮና ወረርሽኝ ተጋልጠው በህክምና ሲረዱ ቆይተው 12 July 2021 ማረፋቸው ይታወቃል። በረከታቸው ትደርብን! እግረ መንገድ ከታች የተያያዘውን የወንድማችን መምህር ታደሰ ወርቁን Tadesse Worku + የመንበረ ቅዱስ ቶማስ ትሩፋት + እንድታነቡ እጋብዛለሁ።

በዘር ኮታ በሚሠጥ ሹመት የሰማይ ሀገር ዜጎችን መጠበቅ እንዴት ይቻል ይሆን? የዘር ውክልና ያለው ዘረኛ እረኛስ ከሕዝብና ከነገድ ከወገንም ከቋንቋም ሁሉ ዋጅቶ ለመንግሥቱ የመረጣቸውን ምእመናን መምራትና ማሰማራት እንዴት ይችል? አልተግባብቶም!

“አሁንም በምድር ሁሉ ላይ የሚጸናውን የጥፋት ትእዛዝ ከሠራዊት ጌታ ከእግዚአብሔር ዘንድ ሰምቻለሁና እስራት እንዳይጸናባችሁ አታፊዙ።”【ኢሳ ፳፰፥፳፪】

ጊዜውን መቅደም ያልቻሉ ምናለ እንደ አረጋዊው ባስልዮስ ማርቶማ ዲዲሞስ በቃኝ ቢሉ …

እኔም አበቃሁ!

(በሱባዔው የደስታ ምልክቷን ጽዮን መቀነቷን ድንቅል ማርያም ሰበኗን ለሁላችን ትላክልን! )

☞ ሐምሌ ፳፱ ቀን ፳፻፲፭ ዓ.ም. ከቴዎድሮስ በለጠ ስቶኮልም ስዊዲን የተጻፈ 【ሀ-ግእዝ የገዳማት ቀን ጉባኤ】
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
እንተ በኅሊና እግዚአብሔር ተገብረት (2)
መንፈሳዊት ይእቲ ማርያም
በእግዚአብሔር ሐሳብ የተሠራች (2)
እመቤታችን መንፈሳዊት ( አዝ)

ምክንተ ድኅነት አንቺ በመሆንሽ
የሲኦል ደጆችን ታንቀጠቅጪያለሽ
በአንቺ የተደረገው ይህ ታላቅ ምሥጢፈር
አድርጎታልና ሰይጣንን እንዲያፍር

ስለሰዎች ፍቅር ልቦናሽ ያሰባል
ዐለምን ለማዳን አጅሽ ይዘረጋል
በሲኦል አንድ ሰው እንዳይቀር በስቃይ
ለምሕረት ይዘርጋ እጅሽ ወደሰማይ

የሲኦል እሳቱን ስቃዩን አያየሽ
ለፍጥረታት ሁሉ ድንግል ሆይ ታዝኛለሽ
በዓይነ ምሕረቱ እንዲያየን ክርስቶስ
ለምኝልን ማርያም ፍጥረት እንዲቀደስ

እንደሚነገረው በአበው አንደበት
እኛም እንደምናይ ስንኖር በህይወት
ወላዲተ አምላክ ሩህሩህ  ፍጥረት ናት
ምሕረት የምትለምን ዘወትር ሳትታክት
በአግዚአብሔር ሐሳብ የተሠራች (2)
እመቤታችን መንፈሳዊት

እንተ በኅሊና እግዚአብሔር ተገብረት (2)
መንፈሳዊት ይእቲ ማርያም
በእግዚአብሔር ሐሳብ የተሰራች (2)
እመቤታችን መንፈሳዊት

ሊቀ መዘምራን ይልማ ኃይሉ
Forwarded from ኦርቶዶክስ ተዋህዶ - ‌🇴‌🇷‌🇹‌🇭‌🇴‌🇩‌🇴‌🇽 ‌🇹‌🇪‌🇼‌🇦‌🇭‌🇩‌🇴 (ተεพ๑δr๑ร (አግናጥዮስ) Ignatius Theophoros (Ἰγνάτιος Θεοφόρος))
Forwarded from ኦርቶዶክስ ተዋህዶ - ‌🇴‌🇷‌🇹‌🇭‌🇴‌🇩‌🇴‌🇽 ‌🇹‌🇪‌🇼‌🇦‌🇭‌🇩‌🇴 (ተεพ๑δr๑ร (አግናጥዮስ) Ignatius Theophoros (Ἰγνάτιος Θεοφόρος))
#ከሰማይም_ከወረደ_በቀር_ወደ_ሰማይ_የወጣ_ማንም_የለም (ዮሐ. ፫፥፲፫)
·:···:···:···:···:···:···:···:···:···:···:···:··

ዕለቱ ሞት ለተፈረደበት የሰው ዘር ሕይወትን፣ ወደ መቃብር ለተጋዘው ዓለም ትንሣኤን የወለደች፤ የሕይወት እናቱ የትንሣኤም ወላዲቱ ፦ ድንግል ማርያም ሕንፃ ሕይወቷ የታደሰበት በትንሣኤ የከበረ ሥጋዋ ወደ ልጇ የፈለሰበት ቀን ነውና የትንሣኤ እና የዕርገቷ የፍልሰቷ ተዝካር ተሰኝቷል።

በዚህ ወቅት ለውሉደ ጥምቀት ምስማክ (መጠጊያ) ፣ በፍኖተ ጽድቅ ምሥጋር (መሻገሪያ) ፣ የመንግሥተ ሰማያቷ ታዕካ (ሰፊ አዳራሽ) እመቤታችን ቅድስት ድንግል ወላዲተ አምላክ ማርያም በፍልሰቷ መታሰቢያ በክርስቶስ አምሳል መነሣቷ፤ ብሎም ኀያልና ከኃሊ ማእምርና ጽኑዕ ወደ ሆነ ልጇ ቀኝ ማረጓን ሐዋርያዊት ቅድስት ቤተክርስቲያናችን አምና ልጆችዋን ታስተምራለች።

በየአዝማናቱ ከሚነሱ ሕጹጸ–ፍኖት፣ ዕልዋነ–ሃይማኖት ውስጥ የእመቤታችን መነሳት ብሎም ማረግ የማይዋጥላቸው መናፍቃን አሉ። እንዲያውም ሲሻቸው ርቱዕ የሆነውን ለመርታት ፣ ራትዓን የሆኑትን ለማምታታት ከቅዱስ መጽሐፍ ሳይቀር አስረጂ ይሆነናል የሚሉትን ስበው ያለአገባቡ ሳይገባቸው ጭምር ይጠቅሱታል፤ በተለይማ ጊዜው «አእምሯቸው የላላ፣ ምላሳቸው የሰላ» የገነኑበት የባለጊዜዎች ነውና የቃሉ ምስክር ሥራው ላልሆነ ነፍሰ ዐንካሳ ከመቼውም ይልቅ ብዙኀኑን ያለ–ተው–ባይ ለመንዳት ያመቸ ሆኗል።

በሥነ አመክንዮ (logic) ለመግባባት እንኳ እንደ ባለ አእምሮ ለሚያስብ የነገሮችን አለመኖር ለማስረዳት «አለ» የሚል መታጣቱ ሳይሆን «የለም» የሚለው ከአስረጂው ታማኝ ምንጭ መገኘቱ የሚያሳምን ይሆናል ፤ እንደዚሁ ሁሉ የነገሩ አናዎር (መኖር) ለማሳወቅ አለመኖሩን የሚያስረዳ መታጣቱ ሳይሆን ህሉናውን ገላጭ መገኘቱ በቂ ይሆናል፤ ነገር ግን መሸናነፍ እንጂ መተማመን እንደ ነውር በተቆጠረበት ትውልድ መኻል፤ ኹሉም ኹሉን አውቃለሁ ባይ ነውና የመጻሕፍትን መነሻ በአስረጂነት (Scriptural Root Evidence) አልያም ቀለል ባሉ ምስለታዊ እሰጣገባ (Simple Analogical Arguments) መናበብን አሻፈረኝ መግባባትንም እምቢኝ የሚል በመብዛቱ ጠያቂን ማስረዳት ቀርቶ ተጠያቂንም መርዳት ከብዷል፤

እግዚኦ! በአብዛኛው ዘንድ ርቱዕ ትምህርቷ እንደ ፈጠራ ወሬ (Hoax) ፣ ነገረ ምዕዳንዋ እንደ ዕለት ዜና (Newscast) መምህራኖቿም እንደ እንቶፈንቶ ጋዜጠኛ (Junket journalist) ለተቆጠሩባት እናት ቤተክርስቲያን "መጥኔ" ይስጥልን (ረዳኤ ወዐቃቤ ወመጽንዔ አምላኳ እርሱ ይሁናት)

ወደተነሳንበት እናምራ፤ ለርእሰ ጉዳያችን የበለጠ አስረጂ አድርገን የባህሪ ክብር ባለቤት ጌታችን ለኒቆዲሞሰ የነገረውን ሕያው ቃል በጥቂቱ በማብራራት እንጀምር፦

" ወአልቦ ዘዓርገ ውስተ ሰማይ ዘእንበለ ዘወረደ እምሰማይ ወልደ እጓለ እመሕያው ዘውእቱ ይነብር ውስተ ሰማይ … ከሰማይም ከወረደ በቀር ወደ ሰማይ የወጣ ማንም የለም፥ እርሱም በሰማይ የሚኖረው የሰው ልጅ ነው።” (ዮሐ ፫፥፲፫)

ይኼንን መልእክት ራሳቸውን የሚያመጻድቁ ፣ የቅዱሳንን ጸጋ የሚንቁ ፣ ክብራቸው ኀሳር ፣ ፍፃሜአቸው ሕርትምና የሆኑ መናፍቃን ለሰሙኑ የቤተክርስቲያን በዓል (የድንግል ተዝካረ ትንሣኤ እና ውስተ ሰማይ ዐራጊት መሆንዋን) ለማስተሐቀር ሲዋሱት ይደመጣል፤ "ሌባ ለአመሉ ዳቦ ይልሳል ፣ መናፍቅም ለወጉ ጥቅስ ይጠቅሳል" ሆኖ እንጂ የመጽሐፉስ ቃል የበለጠ የድንግል እናቱን ክብር ልጇ ያስተማረበት ነው!

ይኽ በዮሐንስ ወንጌል ሦስተኛው ምዕራፍ ላይ ለኒቆዲሞስ የተሰጠው ትምህርት አውዱ ስለ ሰው ልጆች ዳግም ልደት የሚያስረዳ መሆኑን እንገነዘባለን፤ ዳግም በጥምቀት የሚገኘውን የውልድና ሀብት ሲሰማ "እንዴት ሊሆን ይችላል?" በሚል ላቀረበው ጥያቄ ነበር ክርስቶስ “ስለ ምድራዊ ነገር በነገርኋችሁ ጊዜ ካላመናችሁ፥ ስለ ሰማያዊ ነገር ብነግራችሁ እንዴት ታምናላችሁ?” በሚል መነሻ «ምድራዊው ሰው ከሰማይ አባት በጸጋ ልጅነት ይከብራል ያልኩትን ሊረዳ ላልተቻለው፣ ሰማያዊው መለኮት በቅድስት ድንግል ሥጋ መገለጡ እንዴት ይገባዋል? » ያለው! ይኽን አስከትሎ "ከሰማይም ከወረደ በቀር ወደ ሰማይ የወጣ ማንም የለም፥ እርሱም በሰማይ የሚኖረው የሰው ልጅ ነው" በሚል ነገሩን ያስረግጥለታል!

————————————————————

ከዚኽ መነሻ ሦስት ነገሮች እንጠይቃለን

፩) ትምህርቱ የተሰጠበት ጊዜ ጌታችን ገና ሳይሰቀል፣ ሳይሞትና ሳይነሳ ብሎም ወደ ሰማየ ሰማያት ከማረጉ በፊት ሆኖ ሳለ ድርጊቱ ቀድሞ የተፈፀመ እንደሆነ በሚመስል «ወደሰማይ የወጣ (ዘዓርገ) ማንም የለም» በሚል መገለጡ ስለምን ነው?

፪) "ወደሰማይ የወጣ ማንም የለም" የሚለው "ወደ ሰማይ የሚወጣ ማንም የለም" ከሚለው ሐሳብ ጋር ያለው ልዩነት ምንድር ነው?

፫) የእርሷን (የእናቱን) ትንሣኤ እና ዕርገት ከትንሣኤ ዘጉባኤ አስቀድሞ ስለምን አደረገው?

————————————————————

⇨ እኒኽን መነሻ በማድረግ የዕርገቷን ምሥጢር ሊቃውንቱ በመጻሕፍት የሚያስረዱንን እናወሳለን፤
እነሆ ለለባውያንና ለንቁሃን በቅድሚያ ፦ ጌታችን ለምን ተነሳ ለምንስ ዐረገ?

የጌታችን ትንሣኤና ዕርገቱስ ከሞት በኋላ ሕይወት ከመቃብር በኋላ ትንሳኤ ሊኖራቸው በፍኖተ መከራው ለሚሳተፉ ውሉደ ጥምቀት ልጆቹ ያላቸውን ተስፋ የሚቀበሉትን ክብር የሚያሳይ ነው! “ሞቱንም በሚመስል ሞት ከእርሱ ጋር ከተባበርን ትንሣኤውን በሚመስል ትንሣኤ ደግሞ ከእርሱ ጋር እንተባበራለ” ይላልና (ሮሜ ፮፥፭)
መጽሐፈ ቅዳሴ እና መጽሐፈ ግንዘትም "ዐርገ ከመ ያለቡ ዕርገተ ጻድቃን… የጻድቃኑን ዕርገት ያስረዳን ዘንድ ዐረገ" ይለናል፤ ስለዚኽ ነው መጽሐፉ "የሚነሳና የሚያርግ የለም" አይልም አላለምም የምንለው! ሐዋርያቱ ሳይቀር በፍፃሜው "በደመና እንነጠቃለን ፤ ሁል ጊዜ ከጌታችን ጋር እንሆናለን" ብለው ሲመሰክሩ ስለዕርገታቸው ሰምተናል (፩ተሰ. ፬፥፲፯)

⇨ ስለዚኽ ቃሉ ለምሥጢራዊው መውጣቱ ፣ በተዋሕዶ ለተገኘ የሥጋ ምልዓቱ፣ «ዕርገቱ» በጽንሰት ለተከናወነለት ትስብእቱ አስረጂ ሆኖ የተነገረ መሆኑን ልብ ይሏል!

ስለተገለጠው ረቂቅ ምሥጢር ለመረዳት አስቀድሞ ስለጥምቀት (ስለ «ምድራዊት» ልደት) ሊገባን ይገባል፤ ይኽ ምድራዊው ሳይሠርፀን የሰማዩን መመርመር እንደምን ይቻለናል? ለዚህ ነው ከዚሁ ቀድሞ ባለቤቱ ክርስቶስ እንዲህ ያለው

☞ “ስለ ምድራዊ ነገር በነገርኋችሁ ጊዜ ካላመናችሁ፥ ስለ ሰማያዊ ነገር ብነግራችሁ እንዴት ታምናላችሁ?” (ዮሐ ፫፥፲፪)

በቅድሚያ ጥምቀትንስ ለምን «ምድራዊት» ይላታል የሚል ደግሞ ካለ፤

ሊቁ እንዲህ ይላል "እስመ ዘይቤ በእንቲአሃ ምድራዊት ይእቲ እስመ ተፈጸመት እምድር ወእፎመ እንከ የዓቢ ወይፈደፍድ ከመ ትእመኑኒ እም ከሰትኩ ለክሙ መንግሥትየ ወልደትየ እም አብ እምቅድመ ኩሉ ዓለም … ስለእርስዋም (ስለጥምቀት) ምድራዊት ናት ማለቱ ከምድር (በምድር እያሉ) ትፈጸማለችና፤ እንግዲህ ከእርሷ መንግሥቴንና ከኹሉ አስቀድሞ ቅድመ ዓለም ከአባቴ መወለዴ እንደምን እጅጉን አይበልጥ"

በዚኽ ልዩ ተዋሕዶ መለኮት በዚኽ ዓለም በደኃራዊ ሥጋ ከድንግል እንደተወለደ ፣ ሥጋም ጥንታዊ ቀዳማዊ ለመሰኘት በመለኮት ከአብ ተወለዶ ወልደ አብ ወልደ ማርያም አልፋ ወኦሜጋ መባልን ገንዘብ አደረገ።

ታላቁም ተርጓሚ (ወመተርጎምሰ ዘየአቢ) እንዲህ ሲል ያስረዳል የ
Forwarded from ኦርቶዶክስ ተዋህዶ - ‌🇴‌🇷‌🇹‌🇭‌🇴‌🇩‌🇴‌🇽 ‌🇹‌🇪‌🇼‌🇦‌🇭‌🇩‌🇴 (ተεพ๑δr๑ร (አግናጥዮስ) Ignatius Theophoros (Ἰγνάτιος Θεοφόρος))
ቃል መጨመር የአምላክ በሥጋ ማደር በፍጹም ተዋሕዶ እንጂ ቱስሕት እና ኅድረት አይደለምና መለኮትም ከአባቱ ሳይለይ በማኅጸን አድሯል፤ "ወአኮ በፈሊስ እምውስተ መካን…ከቦታ ወደ ቦታ በመሻገር አይደለም" ወደዓለም ሲመጣ ከሰማይ ዙፋኑ ሳይታጣ፣ ከመለኮታዊ ክብሩ ሳይወጣ ነውና ከድንግል እናቱ የነሳውን የተዋሐደውን ሥጋ ፍጹም አምላክና በሰማይ መንግሥትም ያለ ያደረገው በእርሷው ማኅጸን እያለ ነው! ስለዚኽ ያረገው ሲጸነስ ነው ያሰኛል!

በቁሳዊው እሳቤስ አንድን አካል "ወርዷል ግን ከወረደበት ሥፍራም አለ" የሚለውን መረዳት እንደምን ይቻላል? [It is not possible by the laws of bodies for the same object to remain and to descend.]

ለዚኽም ነው በሰማያት ያለውን "የሰው ልጅ"ም እያለ የጠራው። አፈወርቅ የተሰኘው ታላቁ መምህር ቅዱስ ዮሐንስ «Son of Man Stands for the Whole Person» የሰው ልጅ የሚለውን በጠቅላላው ለመለኮትና ትስብእት ተናገረው በሚል አውድ እንዲህ ያስረዳል፦

☞ "And in this place he does not refer only to the flesh as “Son of man” but now names, so to speak, his entire self from the inferior substance. Indeed, he often likes to do this, referring to his whole person from either his divinity or his humanity ⇝ በዚኽ ሥፍራ ከሰማይ የወረደ ቃልነቱም ከምድራዊ ሰውነቱ ጋር እንጂ ሥጋን ብቻ የሰው ልጅ ብሎ አልጠራውም ! ስለዚኽም በእውነት ይኽን አብዝቶ ማስገንዘብ ሲሻ ከመለኮትነቱ አልያም ከትስብእትነቱ ለይቶ «ሥግው ቃልነቱን» የሰው ልጅ ሲል ይገልጣል" (Chrysostom: Homilies on the Gospel of John 27.1.4, NPNF 1 14:94)

ስለዚኽ ክርስቶስማ ምን በክበበ ትስብእት ቢወሰን በሁሉ ግን አለ [Christ Is Everywhere] የምእመናን አባት የቁስጠንጥንያው ሊቀ ጳጳሳት ሊቁ አፈወርቅ መልሶ እንዲህ ይላል፤

☞ "See how even what appears very exalted is utterly unworthy of his greatness? For he is not in heaven only but everywhere, and he fills all things. But here he still speaks according to the infirmity of his hearer in the hope that he can lead him up little by little ⇝ እስኪ ይኽን ተመልከት ታላቅ ክብሩ ምን እና እንዴት እንደሆነ የቱንም ያኽል በቃል ቢነገር ፣ ለማብራራት እጅጉን የሚያዳግር "ኢይትነገር አላ ይትነከር" የሚሰኝ መሆኑን፤ «በተለየ አካሉ ከሰማይ ወረደ ወደዚህ ዓለም መጣ» ያለውን መልሶ በሁሉ ያለ እና ሁሉን የመላ ነው ይለዋል፤ ታዲያ በዚህ ስፍራ ግን የሰማኢውን (የኒቆዲሞስን) የመረዳት አቅም ድኩም እና ጽኑስ መሆን ተመልክቶ ጥቂት በጥቂቱ ያጎለብተው ዘንድ እንዲህ ተናገረ" [Homilies on the Gospel of John 27.1 NPNF 1 14:94]

በዚኽ መነሻ ከልዕልና ዙፋኑ ወደ ዐለም ለወረደው ቃል ልዕልት ላዕለ ኩሉ ተሰኝታ የከበረ ዙፋን የሆነችውን ከሳሽ ዲያቢሎስን ከሰው የምታርቅ ሰውን ከመሓሪ አምላኩ የምታስታርቅ የአዛኝቷን ድንግል ማሕጸን ሰማይ እንለዋለንና።

ሰማይስ መባል እንደምን ተገባት? የሚል ቢኖር እርሷ ሰማይን ብትበልጥ እንጂ ሰማይ መባሏስ ምን ያስገርማል፤ ሊቃውንትማ የሚደነቁት "ሰማይ ወምድር ዘኢያገምሮ እፎ እንጋ ማኅፀነ ድንግል ፆሮ?" እያሉ ነው (ሰማይና ምድር የማይወስኑትን የድንግሊቱ ማኅፀን እንደምን ቻለው?) እርስዋማ የሕይወት ፍሬን ያስገኘች በምድር የተተከለች ቅርንጫፎቿ እስከ ሰማይ የደረሱ የወይን ሐረግ "እንተ በምድር ሥረዊሃ ወበሰማይ እዕፁቂሃ" ናት፤ በላይዋ ተቀምጦ ንጉሡ የተገለጠባት መላእክቱ ለተልእኮ የሚፋጠኑባት ከምድር እስከ ሰማይ ደርሳ የተተከለች መሠላል "ሰዋስው እምድር ዘይበጽእ እስከ ሰማይ" ናት፤ ከሰማይ ሲወርድ ዙፋን ከምድር ሲያርግ መሠላል ያደረጋት ሰዎችን ሲያይ መስታወቱ ሰዎች እርሱን ሲያዩት ድልድይ የምትሰኝ "ተንከተም ለዕርገት ውስተ ሰማይ" እመቤታችን ናት!

ከምን ተነስተን ሰማይ እንዳልናት እዩ፦

✧ ሰማይኑ ንብለኪ ፀሐየ ጽድቅ ወልድኪ ሐዋርያቲሁ ከዋክብትኪ ወመዋርስቲሁ ለበኵርኪ ⇝ ሰማይን እንበልሽ? የእውነት ፀሐይ ነውና ልጅሽ የበኩርሽ ወራሾች የሆኑት ከዋክብቶችሽ ናቸው ሐዋርያት!

​✧ ትመስሊ ሰማየ ወትወልዲ ፀሐየ ወታገምሪ አዶናየ
⇝ ሰማይን ትመስያለሽ ፀሐይን ትወልጃለሽ አዶናይን ትወስኛለሽ(ትችያለሽ) !

✧ አባ ጊዮርጊስም በሌሊቱ ሰዓታት " ገነይነ ለኪ ኦ ወለተ ዳዊት ክብረ ኩሉ ዓለም ዳግሚት አርያም እንዘ ድንግል ወእም … ገነይነ ለኪ ኦ ወለተ ዳዊት ዳግሚት ሰማይ ሙጻኣ ፀሐይ ወላዲቱ ለአዶናይ"

✧ ወኵሉ ዘተጽሕፈ ለተግሣጸ ዚአነ ትጽሕፈ መፍትውኪ እንከ አኃውየ ንንግር ወንዜኑ በእንተ ማርያም ድንግልኒ ሰማይኒ ይእቲ ምዕናም ግሩም ዘበእንቲሃ ተአንመ በሥጋ ዕፁብ፤

✧ አመ በከዩ ብካየ ረከቡ ወለተ ዘታሥተሰሪ ጌጋየ ለወንጌላውያን ኵልነ ዘኮነተነ ምጕያየ ኢያቄም ወሐና ወለዱ ሰማየ ሰማዮሙኒ አሥረቀት ፀሐየ ምሥራቀ ምሥራቃት ሙፃአ ፀሐይ እግዝእትየ ዘመና ሙዳይ ተወልደት ዮም ዳግሚት ሰማይ ፤

✧ ከጸሎተ ኪዳኑም መቅድም ላይ የዘወትር ሰላም እንዲህ ይላል ፦ "ይትፌሣሕ ልብኪ ኦ ድንግል ወይትሌዓል ቀርንኪ በክብር ሰማይ ዳግማት ብኪ ድኅነ ዓለም ወበወልድኪ ኮነ ሰላም ⇝ በአንቺ ዓለሙ የዳነ በልጅሽ ሰላም የሆነ ሁለተኛዋ ሰማይ ድንግል ሆይ ልብሽ ደስ ይበለው ቀንድሽም በክብር ከፍ ከፍ ይበል"

✧ ሊቁ የማሕሌት ምንጭ ቅዱስ ያሬድ የመዳን ቅጥር የምስጋና በር የሆነች የእግዚአብሔር ወልድ እናትን ባመሰገነበት አንቀጸ ብርሃን እንዲህ አላት " አንቲ ውእቱ ህየንተ አርያም ዘበሰማያት ዘኮንኪ አርያመ በዲበ ምድር ⇝ በምድር ላይ ከፍተኛ አርያምን የሆንሽ ከሰማያት በላይ ያለ የአርያም የልዑል ሥፍራ ምትክ አንቺ ነሽ"

⇨ ስለዚኽ እርሷን ሰማይ ካላት ከሰማይ ወርዶ ወደ ሰማይ–ዳግሚት ወደ አርያም–ካልኢት ወደ እርሷ ከወጣው ልጇ በቀር በእርሷ ያደረ ሌላ ማንም የለምና "ከሰማይም ከወረደ በቀር ወደ ሰማይ የወጣ ማንም የለም" ይላታል! በዚኽም እርሷ እርሱን ብቻ በድንግልና ወልዳ የእርሱ ብቻ እናት ተሰኝታ በዘለዓለማዊ ድንግልና ጸንታ መኖርዋን እንረዳል፤

ለአንክሮ ፦ ልጇ እንበለ ዘርእ ተፀንሶ በኅቱም ድንግልና ቢወለድ ፣ እናቱ እንበለ ተፈትሖ ጸንታ ታትማ ኖራለች!

ለፍጽምናም ፦ ልጇ አምላክ ወሰብእ ለመባሉ ድንበር እንደሌለው እናቱም ድንግል ወእም ለመባሏ ወሰን የላትም!

ታዲያ «በውስጥ የብፅዓት ልጅ መሆኗ እንደመላእክት ላለ ኑሮ ፣ በአፍኣ ለጠባቂ መታጨቷ ለመንፈሳዊ ተፍኅሮ» ነው!

✧ በዘር በሩካቤ መጽነስ ፣ በእደ ብእሲ መዳሰስ ፈጽሞ የሌለባት ናት ደገኛዋ እናት በትንቢት በታጠረ ፣ በብፅዓት በተቀጠረ ዐውደ ማሕፀኗ ዕሩቅ ብእሲ አያድርም፤

✧ ሠዓሌ ሕፃናት በተሣለበት ሰሌዳዋ ዘርዓ ብእሲ ቀለም ሆኖ ሊሳልበት አይቃጣም፤

✧ የሰውን ልጅ በቅዱሳን እጆቹ የቀረፀው ልዑል ፈጣሪ በተቀረፀበት ሰፋድል ፍጡሩ ያን የከበረ የሥጋ ክርታስ በቅቶ ሊቀረጽበት አይቻለውም!

እስኪ ልብ አድርጉ
Forwarded from ኦርቶዶክስ ተዋህዶ - ‌🇴‌🇷‌🇹‌🇭‌🇴‌🇩‌🇴‌🇽 ‌🇹‌🇪‌🇼‌🇦‌🇭‌🇩‌🇴 (ተεพ๑δr๑ร (አግናጥዮስ) Ignatius Theophoros (Ἰγνάτιος Θεοφόρος))
እንኳን በአምላክ መጾር «በጳጳስ መንበር ቄስ ፣ በንጉሥ ዙፋን ራስ» ደፍሮ እንደማይቀመጥበት የእርሱንም ምዕራፈ ክብር ማንም አይጋራውም።

"ወይከውን ዘዚአሁ ምዕራፈ ክብር … ማረፊያውም የተከበረ ይሆናል።” [ኢሳ ፲፩፥፲]

የተመረጠው ፃድቅ ዮሴፍ ተከታይ ሞግዚቷ መንፈሳዊ አባቷ እየሆነ ፦ አማናዊት መቅደስ እናቱን ፣ ቅድስተ ቅዱሳን ትስብእቱን ሐዲስ ካህን ሆኖ ያገለገለ አረጋዊ ነው! እርሱ ምንም እንኳ በመጀመርያዋ መጽሐፍ (ብእሲቱ) በኩል ልጆች ማንበብ የሚያውቅ ቢሆንም የታተመችውን መጽሐፍ (እመ አምላክ ድንግልን) ግን በግብር አልደረሰባትምና ከመጠበቅ ውጪ እርሷን ማንበብ አይቻለኝም አለ!

“ ማንበብንም ለሚያውቅ፦ ይህን አንብብ ብለው በሰጡት ጊዜ እርሱ፦ ታትሞአልና አልችልም ይላቸዋል፤” [ኢሳ ፳፱፥፲፩]

ወደዓለም የመጣውን በኩር በሥጋ ያሳየች የበኩር እናት ተሰኘች እርሱም የበኩር ልጇ ተብሎ ተከታይ እንዳይኖረው ወልዳ ዘበኩር ተብሎ ተጠርቷል!

ይኽን ካልን ወደ ማሕፀኗ መውጣቱን ፣ በሥጋ እናቱ በምትሆን አርያም ዙፋን ማደሩን በተዋሕዶ አንድነት ምሥጢራዊ ዕርገት ይዘን ወደሰማይ ማረግ ካልነው ኋላ በአርባኛው ቀን በመርቀቅ ሳይሆን በመራቅ ከቅዱሳን ሐዋርያቱ ተለይቶ ወደላይ ሲወጣ ተመለከትንና ይኽንን (በረቀቀው ጽንሰት ስለተከወነ ዕርገት) በትህትና ያንን (በክብር ማረግ በተዋህዶ አካል ወደ ላይ መውጣቱን ) በልዕልና አልነው።
ሐዋርያው ያን በልዕልና የተፈፀመ ከትህትናው ሲለይ "ወአርገ በስብሐት ⇝ በክብር ያረገ ” (፩ኛ ጢሞ ፫፥፲፮) ሲለው ፤ ዳዊት ሁለቱን ሰማይ አካቶ ይኽን ሰማይ ያንን ከሰማያት በላይ ያለ ሰማይ ብሎ "ዘዓርገ ውስተ ሰማየ ሰማይ ዘመንገለ ጽባሕ " በማለት ገለጠው፤
↳ “በምሥራቅ በኩል ወደ ሰማየ ሰማያት ለወጣ ለእግዚአብሔር ዘምሩ፤ ” (መዝ. ፷፰፥፴፫)

በቅዱስ ኤጲፋንዮስ ቅዳሴ "በይእቲ ሥጋ ምስለ ኃይለ መለኮት ውስተ ሰማያት ዐርገ ኀበ ዘትካት ህላዌሁ ⇝ ከእናቱ በነሳው በዚኽ ሥጋ ከመለኮቱ ኃይል ጋር ወደ ቀደመ መኖርያው ወደ ሰማይ ዐረገ" እንዲል፤

————————————————————
ታቦተ መንፈስ ቅዱስ እመቤታችንን ስለምን ቀድሞ አስነሳት? ————————————————————

በፍለሰታው ሱባዕያት በሊቃውንቱ ቅዳሴ ማርያም ሲተረጎምልን እንደምንሰማው "ትምክሕቶሙ ለወራዙት ወደናግል ወመነኮሳት እለ ይተግሁ ውስተ አናቅጺሃ መዓልተ ወሌሊተ … በእርስዋ ደጃፍ (በራፍ) ሌሊትና ቀን ደጅ ለሚጠኑ ወጣቶች ደናግላንና መነኮሳት ትምክሕት ናት" ይላል ሊቁ አባ ሕርያቆስ።

በደጃፎችዋ በሚለው በሕዋሳቶቿ ለሚማጸኑ ትምክሕት ናት ይላል፤ ሕዋሳቶችዋን በሚያነሳ የሰውነት አባላቶቿን በሚያወሳ የመልክ ሰላምታ ለሚያወድሳት ትምክሕት ናት! ለምን? ለእርሱ ማደርያነት የተገቡ ናቸውና ለዘልዓለም ከብረው የሚኖሩ፤ ከፍጥረት ኹሉ ቀድመው ፈጣሪን በከዊን ያወቁና ፈጣሪን በግዘፍ ለፍጥረት ያሳወቁ ደጆች ፦ የተሸከመውን ማሕፀን፣ የጠባውን አጥባት፣ ያዘለውን ዘባን፣ ያቀፈውን እራኅ፣ በፈጣሪ የተሳመ መልታሕት… ከሌሎች ፍጡራን የአካል አባላት እና የሰውነት ሕዋሳት አብልጦ ይወዳቸዋል።

ልበ አምላክ ቅዱስ ዳዊት መዓዛ መለኮቱ የማይለያትን የሽቱ ሙዳይ “ያበድሮን እግዚአብሔር ለአናቅጸ ጽዮን ⇝ እግዚአብሔር የጽዮንን ደጆች አብልጦ ይወድዳቸዋል።” እንዳለ [መዝ ፹፮ (፹፯)፥፪] አብልጦ ይወዳቸዋልና እንደፍጡሩ ለመፍረስ ለመበስበስ አሳልፎ አልሰጠውም!

በእንዚናዙኑ ሊቅ ቅዱስ ጎርጎርዮስ ቅዳሴ ላይ "ለብሰ ሥጋ ዘይማስን ወረሰዮ ዘኢይማስን" እንደተባለ፤ ከሚፈርሰው ከእኛ ሰውነት የማይፈርሰውን ሕያው አምላክ ለማስገኘት የተመረጠችው የአብ መርዓት፣ የወልድ ወላዲት የመንፈስ ቅዱስ ታቦት የደጆችዋ መቆለፊያ በመቃብር መጥፋት በእሳትም መቃጠል ሳያገኛቸው ጸንተው ኖረዋል፤

“ጽዮንም ሆይ፥ ለአምላክሽ እልል በዪ፤ የደጆችሽን መወርወሪያ አጽንቶአልና " እንዲል [መዝ ፻፵፯፥፲፫]

ፀሐይን ያሠረቀች ዳግሚት ሰማይ፣ እግዚአብሔርን የወለደች እመ አዶናይ ፣ በሥጋና በኅሊና ዘልዓለም ድንግል የሆነች እግዝእትነ ማርያም፦
† በእነታውፋንያ ቁጣ የመጡ አይሁድ ሥጋዋን ለማቃጠል ያሰቡበት ምክር ስለምን ፈረሰ?
† በእሳት ያልጠፋውን ሥጋ "ወኢይገድፍ ምዕቅብናየ ⇝ አደራዬንማ አልተዋትም" ሲል ቅዱስ ዮሐንስ በንጽሕና በእጸ ሕይወት ሥር ሲያገለግላት መቆየቱ ለምነው?
ቀድሞ እሳት ያላቃጠለው ፣ ኋላም አፈር ያልበላውማ ስለሥጋዋ ክብር ነው እንጂ! ተረድተነውማ ቢሆን «ተቀብራ አልተነሳችም» ማለት "ወኢአማሰነ በልደቱ" እንዲል በልደቱ ያልለወጠውን የማደርያውን ክብር በሞት መፍረስና በመቃብር መበስበስ አግኝቶታል፤ አፈር ለውጦ አጥፍቶታል ወደማለት ያደርሳል! ላቲ ይደሉ ክብር ወስብሀት ወለወልዳ አምልኮ ወስግደት።

"ወይከውን ዘዚአሁ ምዕራፈ ክብር … ማረፊያውም የተከበረ ይሆናል።” [ኢሳ ፲፩፥፲]

————————————————————
☞ በቴዎድሮስ በለጠ ◆ ከአርባምንጭ ዚጊቲ አቦ ("#ዝግሕት_ይእቲ") ⇨ [ ነሐሴ ኪዳነ ምሕረት ፳፻፲፩ ዓ.ም ]
————————————————————
Forwarded from ኦርቶዶክስ ተዋህዶ - ‌🇴‌🇷‌🇹‌🇭‌🇴‌🇩‌🇴‌🇽 ‌🇹‌🇪‌🇼‌🇦‌🇭‌🇩‌🇴 (ተεพ๑δr๑ร (አግናጥዮስ) Ignatius Theophoros (Ἰγνάτιος Θεοφόρος))
‹‹አዲስ ዓመት መልካሙን የምንሰራበት ይሁንልን!››


:
☞ዘመናትን የሚያቀያይርና አዲስ ዓመትን የሚሰጠን እርሱ
ፈጣሪ ነው።
:
ይህንን የፈጣሪን ምህረትና ቸርነት የምናስብ ስንቶቻችን
ነን?
:
ሰው ደግሞ ተጨማሪ አዲስ ዓመትና እድሜ ካልተሰጠው
ምንም ማድረግ አይችልም፡፡
:
ፈጣሪ እንድንኖር ካልፈቀደልን አዲሱን ዓመት ካልሰጠን
ምንም ነገር ማድረግ አንችልም፡፡
:
# ሌላው ቀርቶ፦

➊.ወጥተን→የምንገባው፣
:
➋.ተቀምጠን→የምንነሣው፣
:
➌.ተምረን ለውጤት→የምንበቃው፣
:
➍.ሠርተን→የምናገኘው፣
:
➎.ነግደን→የምናተርፈው፣
:
➏.ወልደን→የምንስመው፣
:
➐.ለመጪው ዓመት ብለን እቅድ→የምናቅደው ፈጣሪ እንደ
ቸርነቱ ወደ አዲሱ ዓመት እንድንሸጋገር ሲፈቅድልን ነው፡፡
:
√ብዙ ሰዎች ግን የፈጣሪን ቸርነት ረስተዋል፡፡
:
√አዲስ ዘመን ሲሰጠን ዋጋ የሚከፈልበት ቢሆን ኖሮ ዋጋውን
ማን ይችለው ነበር?
:
√ግን ፈጣሪ አዲስ ዓመት የሰጠን ያለዋጋ በነፃ ነው።

√ለምንኖርበት ዕድሜ ለሰጠን ተጨማሪ ዓመት የጠየቀን ዋጋ
የለም፡፡
:
√ታዲያ ጊዜ የሰጠን ፈጣሪ ደግሞ ጊዜ እንድንሰጠው
እንድናመሰግነው ይፈልጋል።
:
❀︵♡︵♔︵♡︵♔︵♡︵♔︵♡︵❀
:
# አዎን ወዳጆቼ፥

☞አንዳንድ ሰዎች እንዲኖሩ፣ እንዲወጡና እንዲወርዱ አዲስ
ዓመትና ጊዜ ፈጣሪ ሰጥቷቸው ሳለ አዲስ ዓመት ለሰጣቸው
ለፈጣሪ ግን ጊዜ መስጠትና ማመስገን ተስኗቸው
ይስተዋላሉ፡፡
:
♡ይህቺን ቀን አስበው እዚህች ቀን ላይ፣ ለዚህች ዓዲስ
ዓመት ያልደረሱ ብዙ ሰዎች አሉ።

♡አንተ እኔ ሁላችንም ግን ደርሰናልና እንደ ቸርነቱና ምህረቱ
ለዚህ ላደረሰን አምላካችን እንዲህ እያልን እንፀልይ፦

➊.አምላካችን ሆይ፥ አዲሱን ዓመት ስለሰጠኸን
እናመሰግናሀለን።
:
➋.አምላካችን ሆይ፥ ከዚህ በኋላ የሚኖረን ቀሪ እድሜ
በፊትህ ያማረ ይሁንልን፡፡
:
➌.አምላካችን ሆይ፥ እድሜና ዘመናችን በቤትህ ይለቅ፡፡
:
ማለዳ ማለዳ በአዲስ ምስጋና፣
:
በአዲስ ዝማሬ፣
:
በአዲስ ሽብሸባ፣
:
በአዲስ ቅኔ፣
:
በአዲስ እልልታ ይህ በረከት የሆነው እድሜና ዘመናችን
በቤትህ ይለቅ፡፡

➍.አምላካችን ሆይ፥ ሳናመሰግንህ ላለፉት የምህረት
አመታት ሁሉ ዛሬ ይቅር በለን፡፡
:
➎.አምላካችን ሆይ፥ የሚከፋፍለን የሚያለያዬንን የጥል፤
የክርክር፤ የዘረኝነት ግድግዳ አንተ አፍርስልን።
:
➏.አምላካችን ሆይ፥ በአዲሱ ዓመት ፍቅርና አንድነትን
ስጠን።
:
➐.አምላካችን ሆይ፥ ሐገራችን ኢትዮጵያንና ሕዝቦቿን ባርክ።
:
➑.አምላካችን ሆይ፥ በሰጠኸንም እንደ ቸርነትህ
በጨመርክልን አዲስ ዓመት መልካሙን እንድንሰራበት አንተ
ይርዳን! # ለዘላለሙ አሜን!
:
♡እስኪ ተመስገን በሉት። ተመስገንንንንንንንንንንንንንንንን
:
❀︵♡︵♔︵♡︵♔︵♡︵♔︵♡︵❀
:
# መጪው አዲስ ዓመት፦

➊.ሀጥያትን→በጽድቅ፣

➋.አለመጸለይን→በመጸለይ፣

➌.ስጋዊነትን→በመንፈሳዊነት፣

➍.አለማገልገልን→በማገልገል፣

➎.ድህነትን→በመስራት፣
:
➏.አለማንበብን→በማንበብ፣
:
➐.አለማወቅን→በመማር፣
:
➑.ጥላቻን→በፍቅር፣
:
➒.ክፉን→በመልካም፣
:
➓.ንፉግነትን→ በመስጠት፣ የምንከርመበትና ፍቅር የበዛበት
ብሩህ ዘመን ይሁንልን!
:
[☞መልካም አዲስ ዓመት☜]
:
«ሼር በማድረግ ለወዳጆ ያካፍሉ»
:
"ሰላማችሁ ይብዛ"
:
2025/07/01 18:56:07
Back to Top
HTML Embed Code: