ኦርቶዶክስ ተዋህዶ - 🇴🇷🇹🇭🇴🇩🇴🇽 🇹🇪🇼🇦🇭🇩🇴
Photo
ለማኅበራዊ ሚዲያ ማድመቂያ በማኅሌቱ የሚታየው የሥርዓተ ቤተክርስቲያ ጥሰት ሊቆም ይገባል ሲሉ ብፁዕ አቡነ ኤርምያስ ለኢኦተቤ መገናኛ ብዙኀን አገልግሎት ተናገሩ አቡነ ኤርሚያስ እንዳሉት ከበሮ ይዞ የሚሽከረከሩ፣ ጭፈራ የሚመስል በፍፁም ከኃይማኖታዊ የማይመስሉ ድርጊቶች በቤተክርስቲያን ላይ እየታዩ ነው ይህን ድርጊት ለማስቆም ሊቃውት መናገር ፈርቷል አሁን ደፍረን መናገር አለብን ይህ ድርጊት መቆም አለበት ብሏል። አሁን አላዋቂዎች እና ደጋፊዎቻቸው እየበዙ አዋቂዎች እያነሱ መጥቷል፣ እነዚህ ከእምነቱ ውጪ የሆኑ ድርጊቶች ሲከናወኑ ማህሌቱ ደመቀ ይባል መሆን የለበትም ሊቃውት ይህን ማስቆም አለባቸው ብለዋል።
ኦርቶዶክስ ተዋህዶ - 🇴🇷🇹🇭🇴🇩🇴🇽 🇹🇪🇼🇦🇭🇩🇴
Photo
[ስምኽ የጣፈጠ መድኃኔ ዓለም]
በመጋቤ ሐዲስ ዶክተር ሮዳስ ታደሰ ጥቅምት 27 የቀረበ ምስጋና
✍️ በአራቱ ወንጌላት ላይ የዳዊት ልጅ፣ የአብርሃም ልጅ፣ ኢየሱስ፣ ክርስቶስ፣ ዐማኑኤል፣ ተወዳጅ ልጅ፣ የእግዚአብሔር ልጅ፣ የሰው ልጅ፣ የአይሁድ ንጉሥ፣ የናዝሬቱ ኢየሱስ፣ ደንጊያና የመአዝን ራስ፣ የእስራኤል ንጉሥ፣ የልዑል ልጅ፣ የመዳን ቀንድ፣ ከላይ የመጣ ብርሃን፣ አቤቱ፣ የተመረጠ ልጅ፣ ሕያው፣ ቃል፣ አንድ ልጁ፣ ረቢ (መምህር)፣ መሲሕ፣ ልጁ፣ የእግዚአብሔር በግ፣ እግዚአብሔር፣ ሰማያዊ ሙሽራ፣ የዓለም መድኀኒት፣ የእግዚአብሔር እንጀራ፣ የሰማይ እንጀራ፣ የሕይወት እንጀራ፣ የዓለም ብርሃን፣ መልካም እረኛ፣ ትንሣኤና ሕይወት፣ መንገድ፣ እውነት፣ ሕይወት፣ በር፣ እውነተኛ የወይን ግንድ የተባልኽ ቸሩ መድኃኔ ዓለም ሆይ አመልክኻለኹ።
✍️ በሐዋርያት ሥራና በመልእክታት ላይ ቅዱስና ጻድቅ፣ የሕያዋንና የሙታን ፈራጅ፣ ጌታ፣ መድኀኒት፣ የእግዚአብሔር ኀይልና የእግዚአብሔር ጥበብ፣ በግዐ ፋሲካ፣ ኋለኛው አዳም፣ የቤተ ክርስቲያን ራስ፣ ሕያው አምላክ፣ በኲር፣ ታላቅ ሊቀ ካህናት፣ የእምነታችን ራስና ፈጻሚ፣ የነፍስ እረኛና ጠባቂ፣ የእረኞች አለቃ፣ የሕይወት ቃል፣ የአብ ልጅ፣ የእግዚአብሔር አንድ ልጅ የተባልኽ መድኃኔ ዓለም ሆይ እወድኻለኹ።
✍️ መጻኢውን በሚናገረው በዮሐንስ ራእይ ላይ በኲረ ሙታን፣ የምድር ነገሥታት ገዢ፣ የታመነው ምስክር፣ የይሁዳ አንበሳ፣ የታረደው በግ፣ የታመነና እውነተኛ፣ የእግዚአብሔር ቃል፣ ፊተኛውና ኋለኛው፣ አልፋና ዖሜጋ፣ የነገሥታት ንጉሥ፣ የጌቶች ጌታ፣ መዠመሪያውና መጨረሻው፣ የዳዊት ሥርና ዘር፣ የሚያበራ የንጋት ኮከብ የተባልኽ መድኃኔ ዓለም ሆይ ምስጋናን ለአንተ አቀርባለኹ።
(ከመጋቤ ሐዲስ ዶክተር ሮዳስ ታደሰ፤ ነገረ ክርስቶስ ከሚለው መጽሐፌ የተወሰደ)
[ውዶች ሆይ በአስተያየት መስጫው ላይ መድኃኔ ዓለምን ብቻ አመስግኑት።]
በመጋቤ ሐዲስ ዶክተር ሮዳስ ታደሰ ጥቅምት 27 የቀረበ ምስጋና
✍️ በአራቱ ወንጌላት ላይ የዳዊት ልጅ፣ የአብርሃም ልጅ፣ ኢየሱስ፣ ክርስቶስ፣ ዐማኑኤል፣ ተወዳጅ ልጅ፣ የእግዚአብሔር ልጅ፣ የሰው ልጅ፣ የአይሁድ ንጉሥ፣ የናዝሬቱ ኢየሱስ፣ ደንጊያና የመአዝን ራስ፣ የእስራኤል ንጉሥ፣ የልዑል ልጅ፣ የመዳን ቀንድ፣ ከላይ የመጣ ብርሃን፣ አቤቱ፣ የተመረጠ ልጅ፣ ሕያው፣ ቃል፣ አንድ ልጁ፣ ረቢ (መምህር)፣ መሲሕ፣ ልጁ፣ የእግዚአብሔር በግ፣ እግዚአብሔር፣ ሰማያዊ ሙሽራ፣ የዓለም መድኀኒት፣ የእግዚአብሔር እንጀራ፣ የሰማይ እንጀራ፣ የሕይወት እንጀራ፣ የዓለም ብርሃን፣ መልካም እረኛ፣ ትንሣኤና ሕይወት፣ መንገድ፣ እውነት፣ ሕይወት፣ በር፣ እውነተኛ የወይን ግንድ የተባልኽ ቸሩ መድኃኔ ዓለም ሆይ አመልክኻለኹ።
✍️ በሐዋርያት ሥራና በመልእክታት ላይ ቅዱስና ጻድቅ፣ የሕያዋንና የሙታን ፈራጅ፣ ጌታ፣ መድኀኒት፣ የእግዚአብሔር ኀይልና የእግዚአብሔር ጥበብ፣ በግዐ ፋሲካ፣ ኋለኛው አዳም፣ የቤተ ክርስቲያን ራስ፣ ሕያው አምላክ፣ በኲር፣ ታላቅ ሊቀ ካህናት፣ የእምነታችን ራስና ፈጻሚ፣ የነፍስ እረኛና ጠባቂ፣ የእረኞች አለቃ፣ የሕይወት ቃል፣ የአብ ልጅ፣ የእግዚአብሔር አንድ ልጅ የተባልኽ መድኃኔ ዓለም ሆይ እወድኻለኹ።
✍️ መጻኢውን በሚናገረው በዮሐንስ ራእይ ላይ በኲረ ሙታን፣ የምድር ነገሥታት ገዢ፣ የታመነው ምስክር፣ የይሁዳ አንበሳ፣ የታረደው በግ፣ የታመነና እውነተኛ፣ የእግዚአብሔር ቃል፣ ፊተኛውና ኋለኛው፣ አልፋና ዖሜጋ፣ የነገሥታት ንጉሥ፣ የጌቶች ጌታ፣ መዠመሪያውና መጨረሻው፣ የዳዊት ሥርና ዘር፣ የሚያበራ የንጋት ኮከብ የተባልኽ መድኃኔ ዓለም ሆይ ምስጋናን ለአንተ አቀርባለኹ።
(ከመጋቤ ሐዲስ ዶክተር ሮዳስ ታደሰ፤ ነገረ ክርስቶስ ከሚለው መጽሐፌ የተወሰደ)
[ውዶች ሆይ በአስተያየት መስጫው ላይ መድኃኔ ዓለምን ብቻ አመስግኑት።]
ኦርቶዶክስ ተዋህዶ - 🇴🇷🇹🇭🇴🇩🇴🇽 🇹🇪🇼🇦🇭🇩🇴
Photo
እሾኹ ተነቅሏል፡፡
አዳም "እሾኽና አሜከላ ይብቀልብህ" ተብሎ ተረግሞ ነበር፡፡
በዚኽም ምክንያት ይህ እሾኽ የአዳምን እግሮች ሲወጋ ኖረ፡፡ ዛሬ ግን እሾኹ እግር እንዲወጋ ኾኖ አልተሠራም፤
አክሊል ኾኖ በመድኃኔዓለም ራስ ላይ ተደፋ እንጂ፡፡ በእሾኽ ምክንያት መቁሰል ከአዳም እግሮች ጀመረ፤ በመድኅን ክርስቶስ ራስ ላይ ተፈመ፡፡
አዳምን "ይብቀልብህ" ያለውን እሾኽ በራሱ ላይ 'እንዲበቅል' አደረገ፡፡
በዚህ እሾኽ አምሳል፥ ፍዳ መርገም፣ ኀጢኣት…ተነቅሏል:: ከኀሳር ወደክብር ተሸጋግረናል፡፡ መርገሙ ተሽሯል፡፡
አዳም "እሾኽና አሜከላ ይብቀልብህ" ተብሎ ተረግሞ ነበር፡፡
በዚኽም ምክንያት ይህ እሾኽ የአዳምን እግሮች ሲወጋ ኖረ፡፡ ዛሬ ግን እሾኹ እግር እንዲወጋ ኾኖ አልተሠራም፤
አክሊል ኾኖ በመድኃኔዓለም ራስ ላይ ተደፋ እንጂ፡፡ በእሾኽ ምክንያት መቁሰል ከአዳም እግሮች ጀመረ፤ በመድኅን ክርስቶስ ራስ ላይ ተፈመ፡፡
አዳምን "ይብቀልብህ" ያለውን እሾኽ በራሱ ላይ 'እንዲበቅል' አደረገ፡፡
በዚህ እሾኽ አምሳል፥ ፍዳ መርገም፣ ኀጢኣት…ተነቅሏል:: ከኀሳር ወደክብር ተሸጋግረናል፡፡ መርገሙ ተሽሯል፡፡
በሰላም ወደየቤቶቻችሁ ተመለሱ!
በ፲፫ቱ ቅዳሴ ማብቂያ ላይ ዲያቆኑ "#እትዉ_በሰላም " ሲል በቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ቅዳሴ ደግሞ ካህኑ በ‘በአንብሮ እድ’ እንዲህ ሲል ያሰናብተናል
🕊 "ሠናይ ለክሙ ሠናይ ለክሙ ሠናይ ለክሙ ኦ አባግዐ መርዔቱ ለክርስቶስ ። በላዕክሙ ወጸገብክሙ ሰተይክሙ ወረወይክሙ #በሰላም_እትዉ_ውስተ_አብያቲክሙ እግዚአብሔር የሀሉ ምስለ ኵልክሙ ⇨ መልካም ይሁንላችሁ (በደህና ሁኑ) የክርስቶስ የመንጋው በጎች በልታችሁ የጠገባችሁ፣ ጠጥታችሁ የረካችሁ #በሰላም_ወደእየቤታችሁ_ግቡ (ተመለሱ) እግዚአብሔር ከሁላችሁ ጋር ይሁን"
እንግዲህ ልብ እናድርግ የቅዳሴው ፍጻሜ በቤተክርስቲያን በአታቸው ለተማጸኑ ምዕመናን በሰላም ሂዱ ሳይሆን በሰላም ግቡ ነው የሚለው! ይኽ "በሰላም እትዉ ውስተ አብያቲክሙ ⇨ በሰላም ወደየቤቶቻችሁ ግቡ" የሚል የልዑካኑ የፍጻሜ ትዕዛዝ "ፃኡ" ሳይሆን "#እትዉ " ነውና ምን መልእክት አለው ይሆን?
"አተወ" የሚለው ግስ ለ"እትዉ" መነሻ ነው በትርጉሙ ገባ ፣ ተመለሰ፣ “መጣ” ማለት ነው። ከዚህ መነሻ መልእክቱ "በሰላም ግቡ፣ በሰላም ተመለሱ፣ በሰላም ኑ… " የሚል መሆኑን ልብ ይሏል። በዚኽም ላይ
↣ "እስመ ውእቱ ሰላምነ ⇨ እርሱ ሰላማችን ነውና" (ኤፌ ፪፥፲፬) በተባለ መስተሳልም (ሰላም አድራጊ) አምላክ በክርስቶስ አምናችሁ፣ እርሱ ባለቤቱ "ሰላምን እተውላችኋለሁ፥ ሰላሜን እሰጣችኋለሁ፤ እኔ የምሰጣችሁ ዓለም እንደሚሰጥ አይደለም።" (ዮሐ ፲፬፥፳፯) እንዳለን የሚሰጠውን ፍጹም ሰላም ደጅ ጠንተን፣
↣ "ሰላመ ሰጣዊት፡ ወንርዓይ ብኪ ሰላመ ⇨ ሰላምን የምትሰጪ በአንቺ ሰላምን የምናይብሽ" የምንላትነ የሰላም እናት ቅድስት ድንግል ወላዲተ አምላክ ማርያም ከስደት መመለሷን በምናስብበት በዚኽ #ሰሙነ_ሚጠት በታመነ ምልጃዋ ከእንግልት ፣ ከስደትና ከሞት ተመልሰን በጥላዋ ተጠልለን በልጇ ርስት በሰላም ቤቱ ለማረፍ እንድንበቃ ትርዳን 🙏
https://youtu.be/mYATwMHT28k?si=9FXkwkNZHNRHyuEV
በ፲፫ቱ ቅዳሴ ማብቂያ ላይ ዲያቆኑ "#እትዉ_በሰላም " ሲል በቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ቅዳሴ ደግሞ ካህኑ በ‘በአንብሮ እድ’ እንዲህ ሲል ያሰናብተናል
🕊 "ሠናይ ለክሙ ሠናይ ለክሙ ሠናይ ለክሙ ኦ አባግዐ መርዔቱ ለክርስቶስ ። በላዕክሙ ወጸገብክሙ ሰተይክሙ ወረወይክሙ #በሰላም_እትዉ_ውስተ_አብያቲክሙ እግዚአብሔር የሀሉ ምስለ ኵልክሙ ⇨ መልካም ይሁንላችሁ (በደህና ሁኑ) የክርስቶስ የመንጋው በጎች በልታችሁ የጠገባችሁ፣ ጠጥታችሁ የረካችሁ #በሰላም_ወደእየቤታችሁ_ግቡ (ተመለሱ) እግዚአብሔር ከሁላችሁ ጋር ይሁን"
እንግዲህ ልብ እናድርግ የቅዳሴው ፍጻሜ በቤተክርስቲያን በአታቸው ለተማጸኑ ምዕመናን በሰላም ሂዱ ሳይሆን በሰላም ግቡ ነው የሚለው! ይኽ "በሰላም እትዉ ውስተ አብያቲክሙ ⇨ በሰላም ወደየቤቶቻችሁ ግቡ" የሚል የልዑካኑ የፍጻሜ ትዕዛዝ "ፃኡ" ሳይሆን "#እትዉ " ነውና ምን መልእክት አለው ይሆን?
"አተወ" የሚለው ግስ ለ"እትዉ" መነሻ ነው በትርጉሙ ገባ ፣ ተመለሰ፣ “መጣ” ማለት ነው። ከዚህ መነሻ መልእክቱ "በሰላም ግቡ፣ በሰላም ተመለሱ፣ በሰላም ኑ… " የሚል መሆኑን ልብ ይሏል። በዚኽም ላይ
↣ "እስመ ውእቱ ሰላምነ ⇨ እርሱ ሰላማችን ነውና" (ኤፌ ፪፥፲፬) በተባለ መስተሳልም (ሰላም አድራጊ) አምላክ በክርስቶስ አምናችሁ፣ እርሱ ባለቤቱ "ሰላምን እተውላችኋለሁ፥ ሰላሜን እሰጣችኋለሁ፤ እኔ የምሰጣችሁ ዓለም እንደሚሰጥ አይደለም።" (ዮሐ ፲፬፥፳፯) እንዳለን የሚሰጠውን ፍጹም ሰላም ደጅ ጠንተን፣
↣ "ሰላመ ሰጣዊት፡ ወንርዓይ ብኪ ሰላመ ⇨ ሰላምን የምትሰጪ በአንቺ ሰላምን የምናይብሽ" የምንላትነ የሰላም እናት ቅድስት ድንግል ወላዲተ አምላክ ማርያም ከስደት መመለሷን በምናስብበት በዚኽ #ሰሙነ_ሚጠት በታመነ ምልጃዋ ከእንግልት ፣ ከስደትና ከሞት ተመልሰን በጥላዋ ተጠልለን በልጇ ርስት በሰላም ቤቱ ለማረፍ እንድንበቃ ትርዳን 🙏
https://youtu.be/mYATwMHT28k?si=9FXkwkNZHNRHyuEV
YouTube
ዲ/ን ዶ/ር ቴዎድሮስ በለጠ «በሰላም ዕትዉ ውስተ አብያቲክሙ» «በሰላም ወደየቤቶቻችሁ ተመለሱ» 1ኛ ነገ 22፥17
✝️✝️✝️የእግዚአብሔር ቃል ለሁሉ ይዳረስ ዘንድ በጸሎት ያግዙን✝️✝️✝️የማኅበራችንን የዩቱዩብ ቻናል +++SUBSCRIBE +++ እያደረጋችሁ ትምህርቶችን እና መዝሙሮችን እንዲደርሶት እና ለሌሎች እንዲደርሳቸው ሼር በማድረግም ይተባበሩን::
ከዚህ በፊት የተለቀቁ ትምህርቶችንና ዝማሬዎችን ለማግኘት ከስር የሚገኘውን ሊንክ ይጠቀሙ
/ @mahiberetsion
እግዚአብሔር ያክብርልን
ከዚህ በፊት የተለቀቁ ትምህርቶችንና ዝማሬዎችን ለማግኘት ከስር የሚገኘውን ሊንክ ይጠቀሙ
/ @mahiberetsion
እግዚአብሔር ያክብርልን
“ነቢይ ዘከመ እሳት ⇨ እሳታዊ ነቢይ”
✥ °°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°° ✥
"ወተንስአ ኤልያስ ነቢይ ዘከመ እሳት ወቃሉኒ ከመ ነድ ያውኢ ⇨ እሳታዊው ነቢይ ኤልያስ ተነሣ ቃሉም እንደ እሳት ያቃጥል ነበር" 【ሲራ. ፵፰፥፩】
መነሻችን የሚሆነው ጥያቄ ነው?
☞ [መኑ ውእቱ] ዘዐርገ በነደ እሳት በሰረገላት ወበአፍራስ ዘእሳት ?
በእሳት ሰረገላና በእሳት ፈረስ ወደሰማይ የወጣ ማነው?
ይህን ጥያቄ የሚያነሳው ሲራክ ብለን የምንጠራው ኢያሱ ወልደ ሲራክ ወይም ኢያሱ ወልደ አልዓዛር በመጽሐፉ ፵፰ኛ ምዕራፍ ቁጥር ፱ ላይ ነው።
በመጽሐፈ ሲራክ መቅድም ሊቃውንቱ ይኽን ነግረውናል
ሲራክ፦ ፀሐፊ ማለት ነው፤ ፀሐፊው ኢያሱ ወልደ አልዓዛር ወልደ ሲራክ ይባላል።
፶፩ ምዕራፎች ፦ በአቀራረቡ ከሰሎሞን መጽሐፈ ምሳሌ ጋር ተመሳሳይነት አለው።
ይዘት ፦ ለመንፈሳዊና ሥጋዊ ሕይወታችን ጥበብና ምክር የሚሰጥ ነው።
ሲራክ ስለእሳታዊ ነቢይ ይጠይቃል፤
ማነው? በእሳት ተጠቅልሎ የተወለደ ፣ በእግዚአብሔር ቃል ሦስት ጊዜ ከሰማይ እሳት ያወረደ ፣ በእሳት ሠረገላና በእሳት ፈረስ ተጭኖ ወደሰማይ የነጎደ ማነው?
በዘይቤ መንፈሳዊ ትምህርትነትና ምክር በስፋት የያዘው ይኽ መጽሐፈ ሲራክ የእሳትን አስተማሪ ምሳሌነ አጉልቶ በብዙ መንገድ ይነግረናል ለአብነት
☞ ወርቅን ወርቅ ለመሆኑ የሚፈትኑት በእሳት እንደሆነው ሁሉ ጻድቅም ችግር በሚያመጣ መከራ ተፈትኖ የሚያልፍ ነው 【፪፥፭】
☞ የሚነድ’ እሳት የሚጠፋው በውኃ እንደሆነው ኃጢዓት የሚሰረየው በምጽዋት ነው 【፫፥፳፰】
☞ ከተናጋሪ ሰው ጋር መከራከር በእሳት ላይ እንጨት እንደመከመር ነው 【፰፥፫】
☞ መልከ መልካምና ደምግባት ያላት ሴት ፍቅር የሚነድ’ እሳት ነው 【፱፥፰】
☞ በነጻ ፈቃድ እንዲመርጥ ለሰው እግዚአብሔር ያቀረበው የጽድቅና የኃጢዓት መንገድ እንደ እሳትና ውኃ ነው 【፲፭፥፲፮】
☞ ሰው በልቡ ሐሳብ መፈተኑ ሸክላ በእሳት እንደሚፈተነው ነው 【፳፯፥፭】
☞ የእግዚአብሔር ፍርድና ቁጣው እሳት ነው 【፳፰፥፳፪】…
እሳት በጠባዩ ይቡስ (ደረቅ) ፣ ውዑይ (የሚያቃጥል) እና ብሩህ (የሚበራ) ነው። በፍጥረትነቱም ከዐራቱ አሥራው ፍጥረታትና ባሕርያት አንዱ ሆኖ በሁሉ የሚገኝ በይብስቱ ከነፋስ በውዕየቱ ከመሬት በብርሃኑ ከውሃ የሚስማማ ፍጥረት ነው።
ሲራክ ምዕራፉን የሚጀምረው የነቢዩን ማንነት እንዲህ ሲል ነግሮን ነው! "ወተንስአ ኤልያስ ነቢይ ዘከመ እሳት ወቃሉኒ ከመ ነድ ያውኢ ⇨ እሳታዊው ነቢይ ኤልያስ ተነሣ ቃሉም እንደ እሳት ያቃጥል ነበር" 【ሲራ. ፵፰፥፩】
አልያስ ማለት ቀናዒ
መደንግጸ አብዳን፡ ሕገ መነኮሳት ሠራዒ
ኤልያስ ማለት ድንግል
ብእሴ ሰላም ፡ መምህረ እስራኤል
ኤልያስ ማለት ቅብዓ ፍሥሐ
ለቤተክርስቲያን ፡ አንቀጸ ጽርሐ
ኤልያስ ማለት ካህነ ኦሪት
ምዑዘ ምግባር ፡ መዝገበ ሃይማኖት
ኤልያስ ማለት ጸዋሚ
ለእግዚአብሔር ቊልኤሁ ፡ ዝጉሐዊ ተሐራሚ
ኤልያስ ማለት…
ኤልያስ ቴስብያዊ ፣ ኤልያስ ቀርሜሎሳዊ ፣ ኤልያስ ታቦራዊ ፣ ኤልያስ ዘሰራጵታ፣ ኤልያስ ነቢየ ፋፃ … በኩረ ሐዋርያት ፣ ቢጸ ነቢያት ፣ ነቢየ ክርስቶስ ፣ ነቢየ ልዑል ባለብዙ ግብር ባለብዙ ስም …
የዚኽ እሳታዊ ነቢይ ስሙ እንዲህ የበዛው ሥራው ስለበዛ ነው "በአምጣነ ዕፁ ለእሳት የዐቢ ነዱ ⇨ በእንጨቱ ብዛት የእሳቱ ነዲዱ ይበዛል" እንዲል【ሲራ. ፳፰፥፲】
ወሬዛ በኃይሉ አረጋዊ በመዋዕሉ ተብሎ የተገለጠ ጸሐፌ ትዕዛዝ ቅዱስ ኤልያስ ጥር ፮ በእሳት ሠረገላና በእሳት ፈረስ ተጭኖ ወደሰማይ ያረገበት ቀን ፣ ታኅሳስ ፩ በአክአብ ፊት በኃይል ለዘለፋ የተገለጠበት(የናቡቴ ዕረፍት) ፣ «ነሐሴ ፳፪ ቀን ደግሞ ልደቱ» ነው፤ በእነዚኽ ቀናት ልንዘክረውና ልናከብረው ይገባል!
እንኳን እሳት ያወረደውን ቀርቶ የወረደውን እሳት ማክበር ተገቢ ነው ፤ አበው እንዴት መያዝ እንደሚገባው ሲነግሩን «እሳትን በገል ውሃን በቅል» ብለዋል።
ሙሴ አንደበቱ ትብ የሆነው እሳት በልቶ ፣ መጻጉዕ እጁ የተኮማተረው እሳት ጸፍቶ መሆኑን እናውቃለን።
ሊቁ እንዲህ ተቀኝቷል
"መጻጉዕ ሕፃን ኢያእማሬ ነፍስ ዓዲ
አኮኑ ፈነወ እዴሁ መንገለ እሳት ነዳዲ
【 መጻጉዕ ሕጻን ነው ነፍስ ማወቅ መች ጀመረ ?
ቢበስልማ ኖሮ ወደሚነደው እሳት እጁን ባልጨመረ 】
ኤልያስ ማለት በእብራይስጡ (ኤል אֵל) እና (ያስ/ ያህ יָהּ)ከሚሉ ሁለት የፈጣሪያችን ስሞች የተገኘ ጥምረት ሆኖ "እግዚአብሔር ጌታዬ ነው" የሚለውን ፍቺ ይሠጣል። በቅዱሱ መጽሐፍም ከታላቁ ነቢይ ውጪ ሌሎች ሁለት እስራኤላውያን በዚህ የከበረ ታላቅ ስም ተጠርተዋል።
በግሪኩ ደግሞ ኤሊያ ἐλαία (አላህያህ) ማለት ወይራ ማለት ነው። ይህን ያዞ ጌታችን የወይራ ዛፍ በበዛበት ተራራ በደብረ ዘይት ሲጸልይበት የነበረውን ዋሻ የኤልዮን ዋሻ እያለ ይጠራዋል
“ወመዐልትሰ ይሜህር በምኵራብ ወሌሊተ ይወፅእ ወይበይት ውስተ ደብር ዘስሙ ኤሌዎን ⇛ዕለት ዕለትም በመቅደስ (በምኩራብ) ያስተምር ነበር፥ ሌሊት ግን [ኤሌዎን በሚባል] ደብረ ዘይት ተራራ ወጥቶ ያድር ነበር ” 【ሉቃስ ፳፩፥፴፯】
መጽሐፍም ኤልያስ ማለት ወይራ ማለት ነው የሚለውን ልሳነ ጽርእ ይዞ የወይራን ተክል ፍሬና ዘይትን ኤልያስ እያለ ይገልጣል (The tree , the fruit or the oil ☞ ዕፀ ዘይት ፣ ፍሬ ዘይት ፣ ቅብዐ ዘይት)
【ኩፋ ፲፯፥፲】 "ወነሥአቶ እሙ ወሐራዊ ወገደፈቶ ታሕተ አሐቲ ኤልያስ ወሖረት ወነበረት አንጻሮ መጠነ አሐቲ ምንጻፍ እስመ ትቤ ኢይርአይ ሞት ለሕጻንየ ወነቢራ በከየት ⇨እናቱ አነሳችውና ሔዳ በአንዲት የወይራ/ዘይት እንጨት ሥር አኖረችው የልጁን ሞት አላይም ብላለችና በዚያ ተቀምጣ አለቀሰች" (13፥31)
【ሔኖ ፫፥፳፬】 "ወአሕቲ መስፈርተ ኤልያስ ትገብር ዐሠርተ ምክያደ ዘይት ⇨አንዲቱም መስፈሪያ ዘይት አስር የዘይት አውድማንበትመላለች "
የእኛ ሊቃውንት ስሙን በዘይቤና በምሥጢር እያራቀቁ «ዕፀ ዘይት ማኅቶት በቅድመ እግዚአብሔር ፣ ሥዩም ላዕለ ምድር ወሥሉጥ ላዕለ ሰማይ ወላዕለ ማይ » በማለት ገልጠውልናል። በ«መልኩ» መነሻ ላይም
ሰላም ለትርጓሜ ስምከ ዘተብህለ ዘይተ
… በጸውኦ ስምከ ኤልሳዕ ዮርዳኖስ አዕተተ" ይላል
የቅዱስ ዮሐንስ ራእይ ቃልም ለእርሱ መነገሩን በምሥጢር አስማምተው ይተረጉማሉ።
"ዕፀ ዘይት ወመኃትው በቅድመ እግዚአብሔር "【ራዕ ፲፩፥፬】
አቡቀለምሲስ በዚህ የራእዩ ክፍል በአምላካቸው ፊት ወይራና መቅረዝ እያለ አክብሮ የጠራው ሔኖክና ኤልያስን ነው።
✧ ወክልኤ ዕፀ ዘይት እለ ቅድመ እግዚአብሔር
(በእግዚአብሔር ፊት ያሉ የእግዚአብሔር ባለሟሎች የሚሆኑ ሁለቱ የወይራ ዛፎች) መባላቸው
☞ ሄኖክ ማለት ተሐድሶ(አዲስ መሆን) ማለት ነው።
ተሐድሶ በዘይት ነውና
☞ ኤልያስም ማለት ከላይ እንዳየነው ዘይት ማለት ነው።
✧ ወክልኤ መኃትው እለ ቅድመ እግዚአብሔር
(በእግዚአብሔር ፊት ያሉ የእግዚአብሔር ባለሟሎች የሚሆኑ ሁለቱ መብራቶች) መባላቸው
☞ በትምህርታቸው የሰውን ልቡና ብሩህ ያደርጋሉና
✥ °°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°° ✥
"ወተንስአ ኤልያስ ነቢይ ዘከመ እሳት ወቃሉኒ ከመ ነድ ያውኢ ⇨ እሳታዊው ነቢይ ኤልያስ ተነሣ ቃሉም እንደ እሳት ያቃጥል ነበር" 【ሲራ. ፵፰፥፩】
መነሻችን የሚሆነው ጥያቄ ነው?
☞ [መኑ ውእቱ] ዘዐርገ በነደ እሳት በሰረገላት ወበአፍራስ ዘእሳት ?
በእሳት ሰረገላና በእሳት ፈረስ ወደሰማይ የወጣ ማነው?
ይህን ጥያቄ የሚያነሳው ሲራክ ብለን የምንጠራው ኢያሱ ወልደ ሲራክ ወይም ኢያሱ ወልደ አልዓዛር በመጽሐፉ ፵፰ኛ ምዕራፍ ቁጥር ፱ ላይ ነው።
በመጽሐፈ ሲራክ መቅድም ሊቃውንቱ ይኽን ነግረውናል
ሲራክ፦ ፀሐፊ ማለት ነው፤ ፀሐፊው ኢያሱ ወልደ አልዓዛር ወልደ ሲራክ ይባላል።
፶፩ ምዕራፎች ፦ በአቀራረቡ ከሰሎሞን መጽሐፈ ምሳሌ ጋር ተመሳሳይነት አለው።
ይዘት ፦ ለመንፈሳዊና ሥጋዊ ሕይወታችን ጥበብና ምክር የሚሰጥ ነው።
ሲራክ ስለእሳታዊ ነቢይ ይጠይቃል፤
ማነው? በእሳት ተጠቅልሎ የተወለደ ፣ በእግዚአብሔር ቃል ሦስት ጊዜ ከሰማይ እሳት ያወረደ ፣ በእሳት ሠረገላና በእሳት ፈረስ ተጭኖ ወደሰማይ የነጎደ ማነው?
በዘይቤ መንፈሳዊ ትምህርትነትና ምክር በስፋት የያዘው ይኽ መጽሐፈ ሲራክ የእሳትን አስተማሪ ምሳሌነ አጉልቶ በብዙ መንገድ ይነግረናል ለአብነት
☞ ወርቅን ወርቅ ለመሆኑ የሚፈትኑት በእሳት እንደሆነው ሁሉ ጻድቅም ችግር በሚያመጣ መከራ ተፈትኖ የሚያልፍ ነው 【፪፥፭】
☞ የሚነድ’ እሳት የሚጠፋው በውኃ እንደሆነው ኃጢዓት የሚሰረየው በምጽዋት ነው 【፫፥፳፰】
☞ ከተናጋሪ ሰው ጋር መከራከር በእሳት ላይ እንጨት እንደመከመር ነው 【፰፥፫】
☞ መልከ መልካምና ደምግባት ያላት ሴት ፍቅር የሚነድ’ እሳት ነው 【፱፥፰】
☞ በነጻ ፈቃድ እንዲመርጥ ለሰው እግዚአብሔር ያቀረበው የጽድቅና የኃጢዓት መንገድ እንደ እሳትና ውኃ ነው 【፲፭፥፲፮】
☞ ሰው በልቡ ሐሳብ መፈተኑ ሸክላ በእሳት እንደሚፈተነው ነው 【፳፯፥፭】
☞ የእግዚአብሔር ፍርድና ቁጣው እሳት ነው 【፳፰፥፳፪】…
እሳት በጠባዩ ይቡስ (ደረቅ) ፣ ውዑይ (የሚያቃጥል) እና ብሩህ (የሚበራ) ነው። በፍጥረትነቱም ከዐራቱ አሥራው ፍጥረታትና ባሕርያት አንዱ ሆኖ በሁሉ የሚገኝ በይብስቱ ከነፋስ በውዕየቱ ከመሬት በብርሃኑ ከውሃ የሚስማማ ፍጥረት ነው።
ሲራክ ምዕራፉን የሚጀምረው የነቢዩን ማንነት እንዲህ ሲል ነግሮን ነው! "ወተንስአ ኤልያስ ነቢይ ዘከመ እሳት ወቃሉኒ ከመ ነድ ያውኢ ⇨ እሳታዊው ነቢይ ኤልያስ ተነሣ ቃሉም እንደ እሳት ያቃጥል ነበር" 【ሲራ. ፵፰፥፩】
አልያስ ማለት ቀናዒ
መደንግጸ አብዳን፡ ሕገ መነኮሳት ሠራዒ
ኤልያስ ማለት ድንግል
ብእሴ ሰላም ፡ መምህረ እስራኤል
ኤልያስ ማለት ቅብዓ ፍሥሐ
ለቤተክርስቲያን ፡ አንቀጸ ጽርሐ
ኤልያስ ማለት ካህነ ኦሪት
ምዑዘ ምግባር ፡ መዝገበ ሃይማኖት
ኤልያስ ማለት ጸዋሚ
ለእግዚአብሔር ቊልኤሁ ፡ ዝጉሐዊ ተሐራሚ
ኤልያስ ማለት…
ኤልያስ ቴስብያዊ ፣ ኤልያስ ቀርሜሎሳዊ ፣ ኤልያስ ታቦራዊ ፣ ኤልያስ ዘሰራጵታ፣ ኤልያስ ነቢየ ፋፃ … በኩረ ሐዋርያት ፣ ቢጸ ነቢያት ፣ ነቢየ ክርስቶስ ፣ ነቢየ ልዑል ባለብዙ ግብር ባለብዙ ስም …
የዚኽ እሳታዊ ነቢይ ስሙ እንዲህ የበዛው ሥራው ስለበዛ ነው "በአምጣነ ዕፁ ለእሳት የዐቢ ነዱ ⇨ በእንጨቱ ብዛት የእሳቱ ነዲዱ ይበዛል" እንዲል【ሲራ. ፳፰፥፲】
ወሬዛ በኃይሉ አረጋዊ በመዋዕሉ ተብሎ የተገለጠ ጸሐፌ ትዕዛዝ ቅዱስ ኤልያስ ጥር ፮ በእሳት ሠረገላና በእሳት ፈረስ ተጭኖ ወደሰማይ ያረገበት ቀን ፣ ታኅሳስ ፩ በአክአብ ፊት በኃይል ለዘለፋ የተገለጠበት(የናቡቴ ዕረፍት) ፣ «ነሐሴ ፳፪ ቀን ደግሞ ልደቱ» ነው፤ በእነዚኽ ቀናት ልንዘክረውና ልናከብረው ይገባል!
እንኳን እሳት ያወረደውን ቀርቶ የወረደውን እሳት ማክበር ተገቢ ነው ፤ አበው እንዴት መያዝ እንደሚገባው ሲነግሩን «እሳትን በገል ውሃን በቅል» ብለዋል።
ሙሴ አንደበቱ ትብ የሆነው እሳት በልቶ ፣ መጻጉዕ እጁ የተኮማተረው እሳት ጸፍቶ መሆኑን እናውቃለን።
ሊቁ እንዲህ ተቀኝቷል
"መጻጉዕ ሕፃን ኢያእማሬ ነፍስ ዓዲ
አኮኑ ፈነወ እዴሁ መንገለ እሳት ነዳዲ
【 መጻጉዕ ሕጻን ነው ነፍስ ማወቅ መች ጀመረ ?
ቢበስልማ ኖሮ ወደሚነደው እሳት እጁን ባልጨመረ 】
ኤልያስ ማለት በእብራይስጡ (ኤል אֵל) እና (ያስ/ ያህ יָהּ)ከሚሉ ሁለት የፈጣሪያችን ስሞች የተገኘ ጥምረት ሆኖ "እግዚአብሔር ጌታዬ ነው" የሚለውን ፍቺ ይሠጣል። በቅዱሱ መጽሐፍም ከታላቁ ነቢይ ውጪ ሌሎች ሁለት እስራኤላውያን በዚህ የከበረ ታላቅ ስም ተጠርተዋል።
በግሪኩ ደግሞ ኤሊያ ἐλαία (አላህያህ) ማለት ወይራ ማለት ነው። ይህን ያዞ ጌታችን የወይራ ዛፍ በበዛበት ተራራ በደብረ ዘይት ሲጸልይበት የነበረውን ዋሻ የኤልዮን ዋሻ እያለ ይጠራዋል
“ወመዐልትሰ ይሜህር በምኵራብ ወሌሊተ ይወፅእ ወይበይት ውስተ ደብር ዘስሙ ኤሌዎን ⇛ዕለት ዕለትም በመቅደስ (በምኩራብ) ያስተምር ነበር፥ ሌሊት ግን [ኤሌዎን በሚባል] ደብረ ዘይት ተራራ ወጥቶ ያድር ነበር ” 【ሉቃስ ፳፩፥፴፯】
መጽሐፍም ኤልያስ ማለት ወይራ ማለት ነው የሚለውን ልሳነ ጽርእ ይዞ የወይራን ተክል ፍሬና ዘይትን ኤልያስ እያለ ይገልጣል (The tree , the fruit or the oil ☞ ዕፀ ዘይት ፣ ፍሬ ዘይት ፣ ቅብዐ ዘይት)
【ኩፋ ፲፯፥፲】 "ወነሥአቶ እሙ ወሐራዊ ወገደፈቶ ታሕተ አሐቲ ኤልያስ ወሖረት ወነበረት አንጻሮ መጠነ አሐቲ ምንጻፍ እስመ ትቤ ኢይርአይ ሞት ለሕጻንየ ወነቢራ በከየት ⇨እናቱ አነሳችውና ሔዳ በአንዲት የወይራ/ዘይት እንጨት ሥር አኖረችው የልጁን ሞት አላይም ብላለችና በዚያ ተቀምጣ አለቀሰች" (13፥31)
【ሔኖ ፫፥፳፬】 "ወአሕቲ መስፈርተ ኤልያስ ትገብር ዐሠርተ ምክያደ ዘይት ⇨አንዲቱም መስፈሪያ ዘይት አስር የዘይት አውድማንበትመላለች "
የእኛ ሊቃውንት ስሙን በዘይቤና በምሥጢር እያራቀቁ «ዕፀ ዘይት ማኅቶት በቅድመ እግዚአብሔር ፣ ሥዩም ላዕለ ምድር ወሥሉጥ ላዕለ ሰማይ ወላዕለ ማይ » በማለት ገልጠውልናል። በ«መልኩ» መነሻ ላይም
ሰላም ለትርጓሜ ስምከ ዘተብህለ ዘይተ
… በጸውኦ ስምከ ኤልሳዕ ዮርዳኖስ አዕተተ" ይላል
የቅዱስ ዮሐንስ ራእይ ቃልም ለእርሱ መነገሩን በምሥጢር አስማምተው ይተረጉማሉ።
"ዕፀ ዘይት ወመኃትው በቅድመ እግዚአብሔር "【ራዕ ፲፩፥፬】
አቡቀለምሲስ በዚህ የራእዩ ክፍል በአምላካቸው ፊት ወይራና መቅረዝ እያለ አክብሮ የጠራው ሔኖክና ኤልያስን ነው።
✧ ወክልኤ ዕፀ ዘይት እለ ቅድመ እግዚአብሔር
(በእግዚአብሔር ፊት ያሉ የእግዚአብሔር ባለሟሎች የሚሆኑ ሁለቱ የወይራ ዛፎች) መባላቸው
☞ ሄኖክ ማለት ተሐድሶ(አዲስ መሆን) ማለት ነው።
ተሐድሶ በዘይት ነውና
☞ ኤልያስም ማለት ከላይ እንዳየነው ዘይት ማለት ነው።
✧ ወክልኤ መኃትው እለ ቅድመ እግዚአብሔር
(በእግዚአብሔር ፊት ያሉ የእግዚአብሔር ባለሟሎች የሚሆኑ ሁለቱ መብራቶች) መባላቸው
☞ በትምህርታቸው የሰውን ልቡና ብሩህ ያደርጋሉና
ነገረ ዘይት/ ወይራ ዛፍ (About Olive Tree)
ከዕለተ ሠሉስ ዕፀው መካከል ዕፀ ዘይት (የወይራ ዛፍ) አንዱ ነው! ቅባት የሚሰጥ ለመብልነት ለመብራትም የሚውል የወይራ ወገን ነው::
* በሕገ ልቡና በሰብአ ትካት ለጥፋት ውኃ መወገድ በሰላም አብሣሪዋ ርግብ የመጣ ምልክት ይኼ ወይራ ነው! "ርግብም በማታ ጊዜ ወደ እርሱ ተመለሰች በአፍዋም እነሆ የለመለመ የወይራ ቅጠል ይዛ ነበር። ኖኅም ከምድር ላይ ውኃ እንደ ቀለለ አወቀ።" 【ዘፍ ፰፥፲፩】
* በሕገ ኦሪት ከምድረ ርስት ከነአን ገጸ በረከት አንዱ ይኼ ወይራ ነው! "ስንዴ ገብስም ወይንም በለስም ሮማንም ወይራም ማርም ወደ ሞሉባት ምድር፥..." 【ዘዳ. ፰፥፰ በቤተ መቅደሱ ያሉ ሁለቱ ኪሩቤል የተቀረጸው : የመቅደሱ መግቢያ መቃን እና የቅድስተ ቅዱሳኑ ደጃፍ አምድ የተሰራው ከዚሁ ከወይራ ነው! 【፩ ነገሥ. ፮፥፳፫-፴፬】
* በሕገ ወንጌል በመዋዕለ ሥጋዌው ሌሊት ሌሊቱን ጌታችን የመረጣት የጸሎት ሥፍራ ምጽአቱን ያስተማረባትና ዕርገቱን የፈጸመባት ደብር የወይራ ዛፍ የበዛባትን ሥፍራ "ደብረ ዘይትን" ነው! 【ሉቃ. ፳፩፥፴፯】 ዕለት ዕለትም በመቅደስ ያስተምር ነበር፥ ሌሊት ግን ደብረ ዘይት ወደምትባል ተራራ ወጥቶ ያድር ነበር።
በነገረ ሃይማኖት ምሥጢራዊ ምሳሌነቱ
➡ የወይራ ዛፍ የቤተ እግዚአብሔር መብራት ምንጭ ነው! የፈጣሪን ገጸ ምህረት ተወካፌ ጸሎትነት ያሳያል "አንተም መብራቱን ሁል ጊዜ ያበሩት ዘንድ ለመብራት ተወቅጦ የተጠለለ ጥሩ የወይራ ዘይት እንዲያመጡልህ የእስራኤልን ልጆች እዘዛቸው።" 【ዘጸ· ፳፯፥፳】
➡ የወይራ ዛፍ ክር የሚነድበት ዘይት መገኛ ነው! ለእግራችን መብራት ለመንገዳችን ብርሃን የሆነ ህጉን ለሚያስተምሩ ምግባር ለሚያሰሩ አበው ምሳሌ ነው! "ሕግህ ለእግሬ መብራት፥ ለመንገዴ ብርሃን ነው።" 【መዝ. ፻፲፰፥፻፭】
➡ የወይራ ዛፍ በቤተ እግዚአብሔር ያማረ የተወደደ እንደሆነ እንዲሁ በሥላሴ ፊት ባለሟልነት በምዕመናን ዘንድ መወደድ በአጋንንት ዘንድ መፈራት ያላቸውን አበውን የመስላል! "ለእስራኤልም እንደ ጠል እሆነዋለሁ... ውበቱም እንደ ወይራ ይሆናል" 【ሆሴ. ፻፬፥፮】
➡ የወይራ ዛፍ ብዙ ፍሬ እንዲያፈራ ባለ ብዙ ጸጋና ክብር የሆኑትን አበውን ይመስላል! " ልጆችህ በማዕድህ ዙሪያ እንደ ወይራ ቡቃያ ናቸው።" 【መዝ. ፻፳፯፥፫】
➡ የወይራ ዛፍ ቀን ከአእዋፍ ሌሊት ከአራዊት በአጥር በቅጥር ተጠብቆ እንዲኖር በረድኤቱ በቤቱ ጥላ ተጠብቀው የሚኖሩ አበውን ይመስላል! "እኔስ በእግዚአብሔር ቤት እንደ ለመለመ እንደ ወይራ ዛፍ ነኝ፤" 【መዝ· ፶፩፥፰】
ለዚህ ነው የኢያሴንዩና የቶና ልጅ ኤልያስን ባለራእዩ ቅዱስ ዮሐንስ በመጽሐፈ ቀለምሲስ «ዕፀ ዘይት ወመኃትው በቅድመ እግዚአብሔር » እያለ የሚጠራው። እነዚህ በምድር ጌታ ፊት የሚቆሙ ሁለቱ ወይራዎችና ሁለቱ መቅረዞች ናቸው። ማንምም ሊጐዳቸው ቢወድ እሳት ከአፋቸው ይወጣል ጠላቶቻቸውንም ይበላል፤ ማንም ሊጐዳቸው ቢወድም እንዲሁ ሊገደል ይገባዋል። እነዚህ ትንቢት በሚናገሩበት ወራት ዝናብ እንዳይዘንብ ሰማይን ሊዘጉ ሥልጣን አላቸው፥ ውኃዎችንም ወደ ደም ሊለውጡ በሚፈልጉበትም ጊዜ ሁሉ በመቅሠፍት ሁሉ ምድርን ሊመቱ ሥልጣን አላቸው። በረከታቸው በሁላችን ይደር !
🍁 [ኦ ኤልያስ] ; ብፁዓን ፡ እለ ፡ የአምሩከ ፤ ወእለ ፡ ስርግዋን ፡ በፍቅርከ ፤ ወንሕነሂ ፡ ሕይወተ ፡ ነሐዩ ፡ (በእንቲአከ) ።
🍁 [ኤልያስ ሆይ] ; የሚያውቁህና በፍቅርህ ያጌጡ ሰዎች ብፁዓን ናቸው፣ እኛም ስለአንተ በሕይወት እንኖራለን።
🍁 [Oh Elijah] ; Blessed are they that saw thee, and slept in love; for we shall surely live.
【ሲራ ፵፰፥፲፩, Sirach 48:11】
መጽሐፍ እጅግ ማግነናችንን ከአምላክ ማስተካከላችን እንዳልሆነ ሲነግረን እንዲህ ይላል ⇨ አኮ ዘናስተአርዮ ምስለ ፈጣሪሁ አላ ናስተማስሎ በኵሉ ግብር ምስለ አምላኩ። ⇨ ከፈጣሪው ጋር የምናስተካክለው አይደለም በሥራዎቹ ሁሉ ከአምላኩ ጋር እናመሳስለዋለን እንጂ ⇨ We do not equate Him with the Creator, but we view him as an example of God in all his works.
አልያስ ፍጥረቱ እንደኛው መሆኑን “ኤልያስ እንደ እኛ የሆነ ሰው ነበረ፥ ዝናብም እንዳይዘንብ አጥብቆ ጸለየ፥ በምድርም ላይ ሦስት ዓመት ከስድስት ወር አልዘነበም፤ ሁለተኛም ጸለየ፥” 【ያዕ፭፥፲፯】 ነገር ግን ከመጠን ይልቅ ማክበራችን ታዘንና ተለምነን መሆኑን ልብ ይሏል “ወንድሞች ሆይ፥ በመካከላችሁ የሚደክሙትን በጌታም የሚገዙአችሁን የሚገሥጹአችሁንም ታውቁ ዘንድ፥ ስለ ሥራቸውም በፍቅር ከመጠን ይልቅ ታከብሩአቸው ዘንድ እንለምናችኋለን። ”【፩ኛ ተሰ ፭፥፲፪】
አንድ #ማስተካከያ በማመልከት መልእክታችንን እንቋጫለን።
ኤልያስ የተወለደው በምን ቀን ነው?
መጽሐፈ ስንክሳራችን ታኅሳስ ፩ ቀን "የተገለጠበት ቀን” የሚለውን ይዘው ናቡቴ ባረፈበት ቀን ተወልዷል የሚሉ መምህራንና አድባራት ጭምር ይታያሉ፤ መገለጡ በጾመ ነቢያት በነቢይነቱ በ’ነ አክአብ ፊት ፣ በሐሳውያን ነቢያትና በካህናተ ጣኦት ዘንድ፣ በእስራኤላውያን መካከል… መሆኑን ለመግለጥ እንጂ መወለዱን የሚገልጥ እንዳልሆነ መጽሐፍ ያብራራል።
ታዲያ ልደቱ መቼ ነው ያሉ እንደሆነ «መልኩ» በዚሕ መልክ አስቀምጦታል
"…ኤልያስ እምከ ካልዕተ ሣራ ጠባብ
ልደትከ አመ እሥራ ወአመ ሰኑዩ ለአብ
እንዘ ኩለንታከ በእሳት ግልቡብ …"
ከዚህ ውሥጥ «ልደትከ አመ እሥራ ወአመ ሰኑዩ ለአብ»
አብ የተባለው ወርኅ የቱ ነው ብለን የአይሁድን ዜና መዝገብ ብንፈትሽ ታሪክ ጸሐፊው ዮሴፍ (Flavius Josephus ⇝Yoseph Ben Mattithyahu) እንዲህ በማለት የወሩን ቁጥር ጭምር ያመለክትልናል
"ወርኃ ኃምስ ወውእቱ ወርኅ ወርኃ አብ ⇨ አምስተኛው ወር እርሱም አብ የሚባለው ወር ነው"【መጽሐፈ ዮሴፍ ኮርዮን ፶፫፥፭】
ይህ በዕብራውያኑ አብ የተባለው ለሚያዝያ ፭ኛው ወር በእኛ ደግሞ ወርኃ ነሐሴ ነው፤ ስለዚህ የኤልያስ ልደቱ "አመ እሥራ ወአመ ሰኑዩ ለአብ" ባለው መነሻ ነሐሴ ፳፪ ይውላል ማለት ነው።
“እነሆ፥ ታላቁና የሚያስፈራው የእግዚአብሔር ቀን ሳይመጣ ነቢዩን ኤልያስን እልክላችኋለሁ።”【ሚል ፬፥፭ 】
የቅዱስ ኤልያስ በረከቱን አምላካችን ለሁላችን ይላክልን 🙏
✍️ ከቴዎድሮስ በለጠ ታኅሳስ ፩/፳፻፲፮ ዓ.ም. ( Edited & Яερ๑šтεd ƒr๑๓ ጥር ግዝረት ፳፻፲፭ ከእንጦጦ ርእሰ አድባራት ደብረ ኃይል ቅዱስ ራጉኤል አልያስ ወኤልሳዕ)
ከዕለተ ሠሉስ ዕፀው መካከል ዕፀ ዘይት (የወይራ ዛፍ) አንዱ ነው! ቅባት የሚሰጥ ለመብልነት ለመብራትም የሚውል የወይራ ወገን ነው::
* በሕገ ልቡና በሰብአ ትካት ለጥፋት ውኃ መወገድ በሰላም አብሣሪዋ ርግብ የመጣ ምልክት ይኼ ወይራ ነው! "ርግብም በማታ ጊዜ ወደ እርሱ ተመለሰች በአፍዋም እነሆ የለመለመ የወይራ ቅጠል ይዛ ነበር። ኖኅም ከምድር ላይ ውኃ እንደ ቀለለ አወቀ።" 【ዘፍ ፰፥፲፩】
* በሕገ ኦሪት ከምድረ ርስት ከነአን ገጸ በረከት አንዱ ይኼ ወይራ ነው! "ስንዴ ገብስም ወይንም በለስም ሮማንም ወይራም ማርም ወደ ሞሉባት ምድር፥..." 【ዘዳ. ፰፥፰ በቤተ መቅደሱ ያሉ ሁለቱ ኪሩቤል የተቀረጸው : የመቅደሱ መግቢያ መቃን እና የቅድስተ ቅዱሳኑ ደጃፍ አምድ የተሰራው ከዚሁ ከወይራ ነው! 【፩ ነገሥ. ፮፥፳፫-፴፬】
* በሕገ ወንጌል በመዋዕለ ሥጋዌው ሌሊት ሌሊቱን ጌታችን የመረጣት የጸሎት ሥፍራ ምጽአቱን ያስተማረባትና ዕርገቱን የፈጸመባት ደብር የወይራ ዛፍ የበዛባትን ሥፍራ "ደብረ ዘይትን" ነው! 【ሉቃ. ፳፩፥፴፯】 ዕለት ዕለትም በመቅደስ ያስተምር ነበር፥ ሌሊት ግን ደብረ ዘይት ወደምትባል ተራራ ወጥቶ ያድር ነበር።
በነገረ ሃይማኖት ምሥጢራዊ ምሳሌነቱ
➡ የወይራ ዛፍ የቤተ እግዚአብሔር መብራት ምንጭ ነው! የፈጣሪን ገጸ ምህረት ተወካፌ ጸሎትነት ያሳያል "አንተም መብራቱን ሁል ጊዜ ያበሩት ዘንድ ለመብራት ተወቅጦ የተጠለለ ጥሩ የወይራ ዘይት እንዲያመጡልህ የእስራኤልን ልጆች እዘዛቸው።" 【ዘጸ· ፳፯፥፳】
➡ የወይራ ዛፍ ክር የሚነድበት ዘይት መገኛ ነው! ለእግራችን መብራት ለመንገዳችን ብርሃን የሆነ ህጉን ለሚያስተምሩ ምግባር ለሚያሰሩ አበው ምሳሌ ነው! "ሕግህ ለእግሬ መብራት፥ ለመንገዴ ብርሃን ነው።" 【መዝ. ፻፲፰፥፻፭】
➡ የወይራ ዛፍ በቤተ እግዚአብሔር ያማረ የተወደደ እንደሆነ እንዲሁ በሥላሴ ፊት ባለሟልነት በምዕመናን ዘንድ መወደድ በአጋንንት ዘንድ መፈራት ያላቸውን አበውን የመስላል! "ለእስራኤልም እንደ ጠል እሆነዋለሁ... ውበቱም እንደ ወይራ ይሆናል" 【ሆሴ. ፻፬፥፮】
➡ የወይራ ዛፍ ብዙ ፍሬ እንዲያፈራ ባለ ብዙ ጸጋና ክብር የሆኑትን አበውን ይመስላል! " ልጆችህ በማዕድህ ዙሪያ እንደ ወይራ ቡቃያ ናቸው።" 【መዝ. ፻፳፯፥፫】
➡ የወይራ ዛፍ ቀን ከአእዋፍ ሌሊት ከአራዊት በአጥር በቅጥር ተጠብቆ እንዲኖር በረድኤቱ በቤቱ ጥላ ተጠብቀው የሚኖሩ አበውን ይመስላል! "እኔስ በእግዚአብሔር ቤት እንደ ለመለመ እንደ ወይራ ዛፍ ነኝ፤" 【መዝ· ፶፩፥፰】
ለዚህ ነው የኢያሴንዩና የቶና ልጅ ኤልያስን ባለራእዩ ቅዱስ ዮሐንስ በመጽሐፈ ቀለምሲስ «ዕፀ ዘይት ወመኃትው በቅድመ እግዚአብሔር » እያለ የሚጠራው። እነዚህ በምድር ጌታ ፊት የሚቆሙ ሁለቱ ወይራዎችና ሁለቱ መቅረዞች ናቸው። ማንምም ሊጐዳቸው ቢወድ እሳት ከአፋቸው ይወጣል ጠላቶቻቸውንም ይበላል፤ ማንም ሊጐዳቸው ቢወድም እንዲሁ ሊገደል ይገባዋል። እነዚህ ትንቢት በሚናገሩበት ወራት ዝናብ እንዳይዘንብ ሰማይን ሊዘጉ ሥልጣን አላቸው፥ ውኃዎችንም ወደ ደም ሊለውጡ በሚፈልጉበትም ጊዜ ሁሉ በመቅሠፍት ሁሉ ምድርን ሊመቱ ሥልጣን አላቸው። በረከታቸው በሁላችን ይደር !
🍁 [ኦ ኤልያስ] ; ብፁዓን ፡ እለ ፡ የአምሩከ ፤ ወእለ ፡ ስርግዋን ፡ በፍቅርከ ፤ ወንሕነሂ ፡ ሕይወተ ፡ ነሐዩ ፡ (በእንቲአከ) ።
🍁 [ኤልያስ ሆይ] ; የሚያውቁህና በፍቅርህ ያጌጡ ሰዎች ብፁዓን ናቸው፣ እኛም ስለአንተ በሕይወት እንኖራለን።
🍁 [Oh Elijah] ; Blessed are they that saw thee, and slept in love; for we shall surely live.
【ሲራ ፵፰፥፲፩, Sirach 48:11】
መጽሐፍ እጅግ ማግነናችንን ከአምላክ ማስተካከላችን እንዳልሆነ ሲነግረን እንዲህ ይላል ⇨ አኮ ዘናስተአርዮ ምስለ ፈጣሪሁ አላ ናስተማስሎ በኵሉ ግብር ምስለ አምላኩ። ⇨ ከፈጣሪው ጋር የምናስተካክለው አይደለም በሥራዎቹ ሁሉ ከአምላኩ ጋር እናመሳስለዋለን እንጂ ⇨ We do not equate Him with the Creator, but we view him as an example of God in all his works.
አልያስ ፍጥረቱ እንደኛው መሆኑን “ኤልያስ እንደ እኛ የሆነ ሰው ነበረ፥ ዝናብም እንዳይዘንብ አጥብቆ ጸለየ፥ በምድርም ላይ ሦስት ዓመት ከስድስት ወር አልዘነበም፤ ሁለተኛም ጸለየ፥” 【ያዕ፭፥፲፯】 ነገር ግን ከመጠን ይልቅ ማክበራችን ታዘንና ተለምነን መሆኑን ልብ ይሏል “ወንድሞች ሆይ፥ በመካከላችሁ የሚደክሙትን በጌታም የሚገዙአችሁን የሚገሥጹአችሁንም ታውቁ ዘንድ፥ ስለ ሥራቸውም በፍቅር ከመጠን ይልቅ ታከብሩአቸው ዘንድ እንለምናችኋለን። ”【፩ኛ ተሰ ፭፥፲፪】
አንድ #ማስተካከያ በማመልከት መልእክታችንን እንቋጫለን።
ኤልያስ የተወለደው በምን ቀን ነው?
መጽሐፈ ስንክሳራችን ታኅሳስ ፩ ቀን "የተገለጠበት ቀን” የሚለውን ይዘው ናቡቴ ባረፈበት ቀን ተወልዷል የሚሉ መምህራንና አድባራት ጭምር ይታያሉ፤ መገለጡ በጾመ ነቢያት በነቢይነቱ በ’ነ አክአብ ፊት ፣ በሐሳውያን ነቢያትና በካህናተ ጣኦት ዘንድ፣ በእስራኤላውያን መካከል… መሆኑን ለመግለጥ እንጂ መወለዱን የሚገልጥ እንዳልሆነ መጽሐፍ ያብራራል።
ታዲያ ልደቱ መቼ ነው ያሉ እንደሆነ «መልኩ» በዚሕ መልክ አስቀምጦታል
"…ኤልያስ እምከ ካልዕተ ሣራ ጠባብ
ልደትከ አመ እሥራ ወአመ ሰኑዩ ለአብ
እንዘ ኩለንታከ በእሳት ግልቡብ …"
ከዚህ ውሥጥ «ልደትከ አመ እሥራ ወአመ ሰኑዩ ለአብ»
አብ የተባለው ወርኅ የቱ ነው ብለን የአይሁድን ዜና መዝገብ ብንፈትሽ ታሪክ ጸሐፊው ዮሴፍ (Flavius Josephus ⇝Yoseph Ben Mattithyahu) እንዲህ በማለት የወሩን ቁጥር ጭምር ያመለክትልናል
"ወርኃ ኃምስ ወውእቱ ወርኅ ወርኃ አብ ⇨ አምስተኛው ወር እርሱም አብ የሚባለው ወር ነው"【መጽሐፈ ዮሴፍ ኮርዮን ፶፫፥፭】
ይህ በዕብራውያኑ አብ የተባለው ለሚያዝያ ፭ኛው ወር በእኛ ደግሞ ወርኃ ነሐሴ ነው፤ ስለዚህ የኤልያስ ልደቱ "አመ እሥራ ወአመ ሰኑዩ ለአብ" ባለው መነሻ ነሐሴ ፳፪ ይውላል ማለት ነው።
“እነሆ፥ ታላቁና የሚያስፈራው የእግዚአብሔር ቀን ሳይመጣ ነቢዩን ኤልያስን እልክላችኋለሁ።”【ሚል ፬፥፭ 】
የቅዱስ ኤልያስ በረከቱን አምላካችን ለሁላችን ይላክልን 🙏
✍️ ከቴዎድሮስ በለጠ ታኅሳስ ፩/፳፻፲፮ ዓ.ም. ( Edited & Яερ๑šтεd ƒr๑๓ ጥር ግዝረት ፳፻፲፭ ከእንጦጦ ርእሰ አድባራት ደብረ ኃይል ቅዱስ ራጉኤል አልያስ ወኤልሳዕ)
ሀለዉ ዝየ ይቀውሙ እለ ኢይጥእምዋ ለሞት
. በዚህ ከቆሙት ሞትን የማይቀምሱ አሉ
✥ °°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°° ✥
ይኽን ቃል የትህትና አባት ከሆነውና የራሱን ክብር ከመግለጥ ከተቆጠበው ቅዱስ ዮሐንስ በቀር ቀሪዎቹ የከበሩ ወንጌላውያን በክታባቸው አኑረውልናል።
ቅዱስ ማቴዎስ
“እውነት እላችኋለሁ፥ የሰው ልጅ በመንግሥቱ ሲመጣ እስኪያዩ ድረስ እዚህ ከሚቆሙት ሞትን የማይቀምሱ አንዳንድ አሉ።” 【ማቴ. ፲፮፥፳፰】
ቅዱስ ማርቆስ
“እውነት እላችኋለሁ፥ በዚህ ከቆሙት ሰዎች የእግዚአብሔር መንግሥት በኃይል ስትመጣ እስኪያዩ ድረስ፥ ሞትን የማይቀምሱ አንዳንዶች አሉ አላቸው።” 【ማር. ፱፥፩】
ቅዱስ ሉቃስ
“እውነት እላችኋለሁ፥ በዚህ ከሚቆሙት ሰዎች የእግዚአብሔርን መንግሥት እስኪያዩ ድረስ ሞትን የማይቀምሱ አንዳንድ አሉ።” 【ሉቃ. ፱፥፳፯ 】
ቅዱስ ዮሐንስ በምድር ላይ የነበረውን የዘመኑን ፍፃሜ በሁለት የታሪክ ዘውጎች የሚተርኩ መዛግብትና ሊቃውንት አሉ።
① አንዳንዶች ሞቷል በሥጋና ነፍስ መለያየት በሚመጣ ሞት ዐረፍተ ዘመን ገቷቸው ነፍሳቸው በገነት እስከ ትንሳኤ ዘጉባኤ ከምትጠበቅ ጻድቃን ተደምሯል ይላሉ
② ሌሎች ደግሞ ‘የለም’ ቅዱስ ዮሐንስ እንደነ ኤልያስ ወደ ብሔረ ሕያዋን የተነቀ በመሆኑ አርጓል ተሠውሯል ይላሉ።
አርፏል ለማለት እንደ ስንክሳር ያሉ መጻሕፍት ድርሳነ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ እና ከውጪ መዛግብት የተገኙ ቀደምት ምስክሮች በአስረጂነት ይቀርባሉ።
«ወበዛቲ ዕለት ዐዕረፈ …» ስንክሳር
«እስመ መብዝኅተ አዕፅምቲሆሙ ለሐዋርያት ኢነአምር አይቴ ውእቱ ወዘያሌቡሰ ላዕለ ዝንቱ ከመ መቃብረ ጴጥሮስ ወጳውሎስ ወዮሐንስ ወቶማስ እሙራን ወክሡታን እሙንቱ» የሚለውን የቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ድርሳን ፳፮ ንባብ ይዘው ሞቷል ተቀብሯል ይላሉ።
አለመሞቱን ለመሞገት «ዐዕረፈ» ፣ «እሙር መቃብሩ» … ያለውን ለማስታረቅ ብዙ አስረጂ የሚያቀርቡ ሊቃውንት እንዲህ ያለ በመጻሕፍት የታሪክ ክፍተት የዘይቤ አለመስማማት ሲገኝ ሁለት መፍትሔ እንዲወሰድ ይመክራሉ።
፩ኛ) ቅድሚያ ለአብያተ ጉባኤ ትርጓሜ የወንበር ትምህርቶች ቦታ መስጠት ብሉያት ሐዲሳት ሊቃውንትና መነኮሳት የምንላቸውን ፬ቱን ትርጓሜ መጻሕፍት ሌሎች የዜማ ቤት የቅዱስ ያሬድ ገጸ በረከቶች እና በቅኔ ቤት የሚነገሩ ታሪኮች ከየቤተ ጉባኤ መምህራን ቀለማት ጋር ማሳተት
፪ኛ) የዘይቤና የታሪክ ክፍተቶችን በምሥጢር አስታርቆ ማስማማት
ለምሳሌ አንድ ታሪክ ቅድሚያ ቦታ ይሰጣቸው ብለን በጠቀስናቸው መጻሕፍት ላይ ቢገኝና እንደአሁኑ ዓይነት ከስንክሳሩ ታሪክ ጋር የተስማማ ባይመስል ሊቃውንት ይኽን ይላሉ
«ስንክሳር ምን ቁም ነገር ነው? ነገር እንደ ጉባኤ ቤቱ መጻሕፍት ነው እንጂ! የለም ይህስ ስንክሳርን መንቀፍ እንደ ሃይማኖተ አበው ያሉ ደገኛ መጻሕፍትን መንቀፍ ነው ምክንያቱም መላሻቸው አንድ ነው ብሎ ማስታረቅ ይገባል እንጂ!» ስለዚህ ያ በዚህ ምክንያት ይህ ደግሞ በዚህ ምክንያት ትክክል ነው ብሎ መጽሐፍ በመጽሐፍና በተጠያቂ ሊቅ ይዳኛል።
✧ በቅድሚያ ሐሳቦችን በአስረጂ ወደመሞገት እንለፍ
ሀ】ከወንጌል የተገኘ ምስክርነት ፩
ተከታዩን የቅዱስ መጽሐፍ ክፍል ልብ ብለን እናንብብ
"ጴጥሮስም ዘወር ብሎ ኢየሱስ ይወደው የነበረውን ደቀ መዝሙር ሲከተለው አየ፤ እርሱም ደግሞ በእራት ጊዜ በደረቱ ተጠግቶ፦ ጌታ ሆይ፥ አሳልፎ የሚሰጥህ ማን ነው? ያለው ነበረ። ጴጥሮስም ይህን አይቶ ኢየሱስን፦ ጌታ ሆይ፥ ይህስ እንዴት ይሆናል? አለው። ኢየሱስም፦ እስክመጣ ድረስ ይኖር ዘንድ ብወድስ፥ ምን አግዶህ? አንተ ተከተለኝ አለው። ስለዚህ፦ ያ ደቀ መዝሙር አይሞትም የሚለው ይህ ነገር ወደ ወንድሞች ወጣ፤ ነገር ግን ኢየሱስ፦ እስክመጣ ድረስ ይኖር ዘንድ ብወድስ ምን አግዶህ? አለው እንጂ አይሞትም አላለውም"
【የዮሐንስ ወንጌል ምዕራፍ ፳፩ ከቁጥር ፳ እስከ ፳፫ 】
ከዚህ ክፍል "እመኬ ፈቀድኩ የሀሉ እስከ ሶበ እመጽእ ሚላዕሌከ⇨ እስክመጣ ድረስ ይኖር ዘንድ ብወድስ ምን አግዶህ" የሚለውን ሲተረጉም አልሞተም አንድም ሞቷል የሚል መልስ እንደሚከተለው አብራርቶ ያኖርልናል
«እኔ ከወደድኩ እስክመጣ ቢኖር ምን አግዶህ አለው እንጂ አትሞትም አላለም። ዮሐንስ ሞቷልን አልሞተም ቢሉ አልሞተም። ይህ እንዳይሆን ሊቁ «መቃብረ ጴጥሮስ ወጳውሎስ ወዮሐንስ እሙራን ወክሡታን እሙንቱ» ይላል ብሎ ሞቷል። ይህም ሊታወቅ መላእክት መቃብሩን ቆፍረዋል ከመቃብሩ ገብቶ ሲጸልይ ደቀ መዝሙሩን ፋጊርን (አብሮኮሮስን?) የኤፌሶንን ሰዎች በተማራችሁት ትምህርት ጸንታችሁ ኑሩ ብለህ ንገራቸው ብሎ ላከው ነግሮ ቢመለስ መቃብሩ የለፋ መስክ ሁኖ አጽፉን መቋሚያውን መነሣንሡን ከዳሩ አግኝቶታል።»
መደረቢያው በትሩና ጭራው መገኘቱ መቃብር ሳትይዘው ለመውጣቱ በአስረጂነት ይቀርባል። በንባቡም ጌታው እስኪመጣ ድረስ እንዲኖር ወዷል ለሞቷል ባይ "ቢኖር ምን አግዶህ?» የሚል መልስ በባለቤቱ መሠጠቱን ማስተዋል ይገባል። ተሰውሯል የሚሉቱም ቢሆኑ አይሞትም ሳይሆን አልሞተም ባዮች መሆናቸውን መረዳት ይገባል።
ለ) ሁለተኛው ከላይ በመነሻነት የተቀመጡ የሦስቱን ወንጌላውያን መልእክት ስናነብ በመጽሐፍ ቤት የሐዲሳቱ ሊቃውንት ደብረ ታቦር አልፎ በተናገረበት አውድ ሲፈቱ ትርጓሜውን ለዮሐንስ ሰጥተው «የእግዚአብሔር መንግሥት በኃይል ስትመጣ እስኪያዩ ድረስ፥ ሞትን የማይቀምሱ አንዳንዶች» የተባለው እርሱን የሚወክል እንደሆነ ነግረዋል
አንዳንዶች ብሎ ማብዛቱ መጽሐፍ ስም ካልጠራ ማብዛት ልማዱ ነውና
ለምሳሌ ፦ በተአምኖ አመ ነገርዎ ለኖኅ (የነገረው አንድ መልአክ ሆኖ ሳለ) ፣ ብፅዕት አንቲ እንተ ተአምኒ ዘነገሩኪ (ያበሠረው አንዱ ቅዱስ ገብርኤል ሆኖ ሳለ)
በሌላ መልኩ በሁሉ ወንጌላውያን ተጠቅሶ በእርሱ አለመጻፉ ራሱን የሚመለከት ቢሆን ነው። ክብሬ ይገለጥልኝ መወደዴ ይነገርልኝ ብሎ ጉዳዩ ባለበት መነገሩን ሳያኖርልን የቀረው ስለትህትና እንደሚሆን ይታመናል።
ሐ) ደብረታቦርን ካነሳን እግረ መንገድ ቅዱሱ አባታችን ጊዮርጊስ ዘጋሥጫ በመጽሐፈ ምሥጢር ምሥጢረ ታቦርን ደጋግሞ ከአማናዊት የሐዲስ ኪዳን መርጡል ጋር እያዛመደ አስተምሮበታል። በሥፍራው የተገኘውን አልያስን አንስቶ ወደብሔረ ሕያዋን እንዴት እንደተነጠቀ ሲነግረን «ወከበቶሙ እግዚአብሔር ውስተ ምድር ኅብእት እንተ ተሠወረት በጥበበ ዚኣሁ ወአልቦ ሥልጣነ ሞት» ይላል።
ታዲያ መሰሉን አብነት ይዘው መምህራን በቦታው የተገኘውን ኤልያስ ከዮሐንስ እንድናነፃፅር ያመለክቱናል። አምላካችን ክርስቶስ እና ቅዱስ ጴጥሮስ ጴጥሮስ በመስቀል ተሰቅለው ቢያልፉ ፣ ሊቀ ነቢያት ሙሴና የዘብዴዎስ ልጅ ያዕቆብ ዕረፍተ ሰላም ይኽን ዓለም ተሰናብተዋል፤ ታላቁ ነቢይ ኤልያስና ተወዳጁ ደቀ መዝሙር ዮሐንስ ወደ ብሔረ ሕያዋን ተጠርተዋልና… በፍጻሜ መገናኛቸው እንደሚገናኙ ሊያሳይ አወዳጅቶ አገናኛቸው ተገናኛቸውም ይላሉ።
. በዚህ ከቆሙት ሞትን የማይቀምሱ አሉ
✥ °°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°° ✥
ይኽን ቃል የትህትና አባት ከሆነውና የራሱን ክብር ከመግለጥ ከተቆጠበው ቅዱስ ዮሐንስ በቀር ቀሪዎቹ የከበሩ ወንጌላውያን በክታባቸው አኑረውልናል።
ቅዱስ ማቴዎስ
“እውነት እላችኋለሁ፥ የሰው ልጅ በመንግሥቱ ሲመጣ እስኪያዩ ድረስ እዚህ ከሚቆሙት ሞትን የማይቀምሱ አንዳንድ አሉ።” 【ማቴ. ፲፮፥፳፰】
ቅዱስ ማርቆስ
“እውነት እላችኋለሁ፥ በዚህ ከቆሙት ሰዎች የእግዚአብሔር መንግሥት በኃይል ስትመጣ እስኪያዩ ድረስ፥ ሞትን የማይቀምሱ አንዳንዶች አሉ አላቸው።” 【ማር. ፱፥፩】
ቅዱስ ሉቃስ
“እውነት እላችኋለሁ፥ በዚህ ከሚቆሙት ሰዎች የእግዚአብሔርን መንግሥት እስኪያዩ ድረስ ሞትን የማይቀምሱ አንዳንድ አሉ።” 【ሉቃ. ፱፥፳፯ 】
ቅዱስ ዮሐንስ በምድር ላይ የነበረውን የዘመኑን ፍፃሜ በሁለት የታሪክ ዘውጎች የሚተርኩ መዛግብትና ሊቃውንት አሉ።
① አንዳንዶች ሞቷል በሥጋና ነፍስ መለያየት በሚመጣ ሞት ዐረፍተ ዘመን ገቷቸው ነፍሳቸው በገነት እስከ ትንሳኤ ዘጉባኤ ከምትጠበቅ ጻድቃን ተደምሯል ይላሉ
② ሌሎች ደግሞ ‘የለም’ ቅዱስ ዮሐንስ እንደነ ኤልያስ ወደ ብሔረ ሕያዋን የተነቀ በመሆኑ አርጓል ተሠውሯል ይላሉ።
አርፏል ለማለት እንደ ስንክሳር ያሉ መጻሕፍት ድርሳነ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ እና ከውጪ መዛግብት የተገኙ ቀደምት ምስክሮች በአስረጂነት ይቀርባሉ።
«ወበዛቲ ዕለት ዐዕረፈ …» ስንክሳር
«እስመ መብዝኅተ አዕፅምቲሆሙ ለሐዋርያት ኢነአምር አይቴ ውእቱ ወዘያሌቡሰ ላዕለ ዝንቱ ከመ መቃብረ ጴጥሮስ ወጳውሎስ ወዮሐንስ ወቶማስ እሙራን ወክሡታን እሙንቱ» የሚለውን የቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ድርሳን ፳፮ ንባብ ይዘው ሞቷል ተቀብሯል ይላሉ።
አለመሞቱን ለመሞገት «ዐዕረፈ» ፣ «እሙር መቃብሩ» … ያለውን ለማስታረቅ ብዙ አስረጂ የሚያቀርቡ ሊቃውንት እንዲህ ያለ በመጻሕፍት የታሪክ ክፍተት የዘይቤ አለመስማማት ሲገኝ ሁለት መፍትሔ እንዲወሰድ ይመክራሉ።
፩ኛ) ቅድሚያ ለአብያተ ጉባኤ ትርጓሜ የወንበር ትምህርቶች ቦታ መስጠት ብሉያት ሐዲሳት ሊቃውንትና መነኮሳት የምንላቸውን ፬ቱን ትርጓሜ መጻሕፍት ሌሎች የዜማ ቤት የቅዱስ ያሬድ ገጸ በረከቶች እና በቅኔ ቤት የሚነገሩ ታሪኮች ከየቤተ ጉባኤ መምህራን ቀለማት ጋር ማሳተት
፪ኛ) የዘይቤና የታሪክ ክፍተቶችን በምሥጢር አስታርቆ ማስማማት
ለምሳሌ አንድ ታሪክ ቅድሚያ ቦታ ይሰጣቸው ብለን በጠቀስናቸው መጻሕፍት ላይ ቢገኝና እንደአሁኑ ዓይነት ከስንክሳሩ ታሪክ ጋር የተስማማ ባይመስል ሊቃውንት ይኽን ይላሉ
«ስንክሳር ምን ቁም ነገር ነው? ነገር እንደ ጉባኤ ቤቱ መጻሕፍት ነው እንጂ! የለም ይህስ ስንክሳርን መንቀፍ እንደ ሃይማኖተ አበው ያሉ ደገኛ መጻሕፍትን መንቀፍ ነው ምክንያቱም መላሻቸው አንድ ነው ብሎ ማስታረቅ ይገባል እንጂ!» ስለዚህ ያ በዚህ ምክንያት ይህ ደግሞ በዚህ ምክንያት ትክክል ነው ብሎ መጽሐፍ በመጽሐፍና በተጠያቂ ሊቅ ይዳኛል።
✧ በቅድሚያ ሐሳቦችን በአስረጂ ወደመሞገት እንለፍ
ሀ】ከወንጌል የተገኘ ምስክርነት ፩
ተከታዩን የቅዱስ መጽሐፍ ክፍል ልብ ብለን እናንብብ
"ጴጥሮስም ዘወር ብሎ ኢየሱስ ይወደው የነበረውን ደቀ መዝሙር ሲከተለው አየ፤ እርሱም ደግሞ በእራት ጊዜ በደረቱ ተጠግቶ፦ ጌታ ሆይ፥ አሳልፎ የሚሰጥህ ማን ነው? ያለው ነበረ። ጴጥሮስም ይህን አይቶ ኢየሱስን፦ ጌታ ሆይ፥ ይህስ እንዴት ይሆናል? አለው። ኢየሱስም፦ እስክመጣ ድረስ ይኖር ዘንድ ብወድስ፥ ምን አግዶህ? አንተ ተከተለኝ አለው። ስለዚህ፦ ያ ደቀ መዝሙር አይሞትም የሚለው ይህ ነገር ወደ ወንድሞች ወጣ፤ ነገር ግን ኢየሱስ፦ እስክመጣ ድረስ ይኖር ዘንድ ብወድስ ምን አግዶህ? አለው እንጂ አይሞትም አላለውም"
【የዮሐንስ ወንጌል ምዕራፍ ፳፩ ከቁጥር ፳ እስከ ፳፫ 】
ከዚህ ክፍል "እመኬ ፈቀድኩ የሀሉ እስከ ሶበ እመጽእ ሚላዕሌከ⇨ እስክመጣ ድረስ ይኖር ዘንድ ብወድስ ምን አግዶህ" የሚለውን ሲተረጉም አልሞተም አንድም ሞቷል የሚል መልስ እንደሚከተለው አብራርቶ ያኖርልናል
«እኔ ከወደድኩ እስክመጣ ቢኖር ምን አግዶህ አለው እንጂ አትሞትም አላለም። ዮሐንስ ሞቷልን አልሞተም ቢሉ አልሞተም። ይህ እንዳይሆን ሊቁ «መቃብረ ጴጥሮስ ወጳውሎስ ወዮሐንስ እሙራን ወክሡታን እሙንቱ» ይላል ብሎ ሞቷል። ይህም ሊታወቅ መላእክት መቃብሩን ቆፍረዋል ከመቃብሩ ገብቶ ሲጸልይ ደቀ መዝሙሩን ፋጊርን (አብሮኮሮስን?) የኤፌሶንን ሰዎች በተማራችሁት ትምህርት ጸንታችሁ ኑሩ ብለህ ንገራቸው ብሎ ላከው ነግሮ ቢመለስ መቃብሩ የለፋ መስክ ሁኖ አጽፉን መቋሚያውን መነሣንሡን ከዳሩ አግኝቶታል።»
መደረቢያው በትሩና ጭራው መገኘቱ መቃብር ሳትይዘው ለመውጣቱ በአስረጂነት ይቀርባል። በንባቡም ጌታው እስኪመጣ ድረስ እንዲኖር ወዷል ለሞቷል ባይ "ቢኖር ምን አግዶህ?» የሚል መልስ በባለቤቱ መሠጠቱን ማስተዋል ይገባል። ተሰውሯል የሚሉቱም ቢሆኑ አይሞትም ሳይሆን አልሞተም ባዮች መሆናቸውን መረዳት ይገባል።
ለ) ሁለተኛው ከላይ በመነሻነት የተቀመጡ የሦስቱን ወንጌላውያን መልእክት ስናነብ በመጽሐፍ ቤት የሐዲሳቱ ሊቃውንት ደብረ ታቦር አልፎ በተናገረበት አውድ ሲፈቱ ትርጓሜውን ለዮሐንስ ሰጥተው «የእግዚአብሔር መንግሥት በኃይል ስትመጣ እስኪያዩ ድረስ፥ ሞትን የማይቀምሱ አንዳንዶች» የተባለው እርሱን የሚወክል እንደሆነ ነግረዋል
አንዳንዶች ብሎ ማብዛቱ መጽሐፍ ስም ካልጠራ ማብዛት ልማዱ ነውና
ለምሳሌ ፦ በተአምኖ አመ ነገርዎ ለኖኅ (የነገረው አንድ መልአክ ሆኖ ሳለ) ፣ ብፅዕት አንቲ እንተ ተአምኒ ዘነገሩኪ (ያበሠረው አንዱ ቅዱስ ገብርኤል ሆኖ ሳለ)
በሌላ መልኩ በሁሉ ወንጌላውያን ተጠቅሶ በእርሱ አለመጻፉ ራሱን የሚመለከት ቢሆን ነው። ክብሬ ይገለጥልኝ መወደዴ ይነገርልኝ ብሎ ጉዳዩ ባለበት መነገሩን ሳያኖርልን የቀረው ስለትህትና እንደሚሆን ይታመናል።
ሐ) ደብረታቦርን ካነሳን እግረ መንገድ ቅዱሱ አባታችን ጊዮርጊስ ዘጋሥጫ በመጽሐፈ ምሥጢር ምሥጢረ ታቦርን ደጋግሞ ከአማናዊት የሐዲስ ኪዳን መርጡል ጋር እያዛመደ አስተምሮበታል። በሥፍራው የተገኘውን አልያስን አንስቶ ወደብሔረ ሕያዋን እንዴት እንደተነጠቀ ሲነግረን «ወከበቶሙ እግዚአብሔር ውስተ ምድር ኅብእት እንተ ተሠወረት በጥበበ ዚኣሁ ወአልቦ ሥልጣነ ሞት» ይላል።
ታዲያ መሰሉን አብነት ይዘው መምህራን በቦታው የተገኘውን ኤልያስ ከዮሐንስ እንድናነፃፅር ያመለክቱናል። አምላካችን ክርስቶስ እና ቅዱስ ጴጥሮስ ጴጥሮስ በመስቀል ተሰቅለው ቢያልፉ ፣ ሊቀ ነቢያት ሙሴና የዘብዴዎስ ልጅ ያዕቆብ ዕረፍተ ሰላም ይኽን ዓለም ተሰናብተዋል፤ ታላቁ ነቢይ ኤልያስና ተወዳጁ ደቀ መዝሙር ዮሐንስ ወደ ብሔረ ሕያዋን ተጠርተዋልና… በፍጻሜ መገናኛቸው እንደሚገናኙ ሊያሳይ አወዳጅቶ አገናኛቸው ተገናኛቸውም ይላሉ።
St. John the Evangelist Orthodox Church
Our Patron Saint - St. John the Evangelist Orthodox Church
The Holy, Glorious All-laudable Apostle and Evangelist, Virgin, and Beloved Friend of Christ, John the Theologian was the son of Zebedee and Salome, a daughter of St Joseph the Betrothed. He was called by our Lord Jesus Christ to be one of His Apostles at…
መ) ከዜማ ቤቱ ደግሞ ዮሐንስን በብሔረ ሕያዋን አየሁት የሚለን የኘቅዱስ ያሬድ ነው። በድጓው ደጋግሞ ምስክርነቱን ሠጥቶናል
«ይኔጽር ዓየራተ
ይነግር ኅቡዓተ
እንዘ ይጽሐፍ በእደዊሑ ዘወንጌል ቃላተ
በቅናተ እግዚኡ ሐቌሁ ቀነተ
ዮሐንስ ድንግል ዘኢጥዕመ ሞተ »
【በድጓ በግእዝ አርያሙ ክፍል ለጥር ፬ቱ ቁመት መነሻ እንዲሆን የጻፈልን ነው። ብራና ገጽ ፻፺፩】
በንጽሕና በድንግልና የኖረው ዮሐንስ ሞትን አልቀመሰም ይልና በሌላም ሥፍራ ከሞት ተለይቶ እንደመላእክቱ በሕይወት አለ ሲል ዳግመኛ ምስክርነቱን እንዲህ እያለ ያጸናዋል «በንጽሕ ከመ መላእክት ተሠርገወ ወእመዊት ከማሆሙ ሐይወ»
ሠ) በመልኩ ክፍልና በገድለ ሐዋርያት ማጠቃለያ የመሰወሩ ምስክርነት ተቀምጦ እናገኛለን
« ሰላም ለልብስከ ወለአሣእኒከ ደርገ፤
ተዝካረ ሕይወትከ ያዑቅ ለአብሮኮሮስ ዘተኃድገ፤
ዮሐንስ ዘኮንከ ምስለ መላእክት ዘውገ፤
ምሉዓ ወድግዱገ ዘሰላምከ ፈለገ፤
በውሣጤ ከርሥየ ኢይኩን ንቱገ፡፡ »
【የመኖርህን ነገር ያስረዳ ዘንድ ለተተወ ፤ ለልብስህ ከጫማህ ጋር ክብር ይገባል፤ ከመላእክት ጋር ወዳጅ የሆንክ ዮሐንስ ሆይ! ሞልቶ የተትረፈረፈ የፍቅር አንድነትህ ወንዝ በሆዴ ውስጥ የጎደለ አይሁን /ይሙላ/።】
ረ) የሊቃውንት ቅኔ ለጊዜው በዝክረ ሊቃውንት ከተዘገቡት ሁለቱን ልጠቁም
« ወልደ ነጐድጓድ ተሰደ እንዘ የኀድግ ሀገረ፤
እምኅበ አጥፍአ ሞተ ሰብእ ሦረ፤
ገራህቱ መቅበርት አምጣነ አብቈለት ሣዕረ»
«ዘማ መቅበርት ለወልደ ነጎድጓድ ትቤሎ፤
እመ ትጸልአኒ አንተ ዘያፈቅረኒ ሀሎ»
ሰ) ከውጭ የተገኙ ቀደምት ምንጮች
በውጭ ሀገራት ቀደምት ድርሳናትና ሊቃውንትም ዘንድ ቢሆን ከላይ ያነሳነውን ጭብጥ የሚደግፍ ታሪክ ተመዝግቦ ይገኛል።
https://www.stjohnaz.org/about-us/our-patron-saint/#:~:text=He%20bade%20them%20prepare%20for,disobedient%2C%20they%20fulfilled%20his%20bidding.
በሌላ ሥፍራ የተገኘው ደግሞ ይህን ይላል ቅዱስ ዮሐንስ የሚነጠቅበት ሠዓት እንደደረሰ ሲያውቅ በመስቀል ቅርጽ የተሰናዳ መቃብር እንዲያዘጋጁለት አርድእቱን አዟል እነርሱም በበዛ እንባ መምህራቸውን እየሳሙ ካለመታዘዝ እንዳይቆጠርባቸው ፊቱን በጨርቅ ሸፍነው ወደ መቃብሩ ሥፍራ አኑረውት ሄደዋል። ከደቀ መዛሙርቱ አንዱ ( ቅዱስ አብሮኮሮስ) ወደቦታው ተመልሶ ቢመጣ መቃብሩን ቢከፍተው ባዶ ሆኖ አግኝቶታል።
«He bade them prepare for him a cross-shaped grave, in which he lay, telling his disciples that they should cover him over with the soil. The disciples tearfully kissed their beloved teacher, but not wanting to be disobedient, they fulfilled his bidding. They covered the face of the saint with a cloth and filled in the grave. Learning of this, other disciples of Saint John came to the place of his burial. #When_they_opened_the_grave, they found it empty.»
በአብሮኮሮስ ስለተሠጠው ምስክርነት (testimony of St. Prochorus) ደግሞ ተከታዩት አስረጂ በሊንኩ ታግዘው ቢያዩ የበከጠ ሐሳባችንን ያግዛል።
https://www.johnsanidopoulos.com/2009/09/repose-of-st-john-theologian-according.html?m=1
✧ ለማስማማት በሚነሳው የማስታረቂያ ሐሳብ
በኤፌሶን/ ቱርክ የመቃብሩ ሥፍራ ይህ ነው እየተባለ ዛሬም ለጎብኚዎች ይታያል።
ይሁንና ግን ☞ገራህቱ መቅበርት አምጣነ አብቈለት ሣዕረ ፣
☞ልብሱ ለዮሐንስ ወአሣእኑ ዘተኃድገ ለአብሮኮሮስ ከመ ያዑቅ ሕይወቱ ፣
☞ When they opened the grave, they found it empty ከሚሉቱ ሳይስማማ ሞቷል ለሚሉቱ ድጋፍ መስሎ ቀርቧል። በመላእክት ቢሎ በደቀመዛሙርቱ መቃብሩ መዘጋጀቱ እውነት ቢሆንም ሥጋው ከዚያ መታጣቱና የአብሮኮሮስ ምስክርነት ተሰውሯል ወደሚለው ያደርሰናል።
የስንክሳሩን አገላለጥ በሚመለከት ደግሞ ወደ ብሔረ ሕያዋን ተነጥቀዋል ብላ ቤ/ክርስቲያን የምትናገርላቸውን ቅዱሳንን ዐዕረፈ ብሎ ማስቀመጥ በአያሌው የተለመደ ነው። ዐረፈ የሚለው በአገባቡ ሞትን ብቻ አይገልጥም ከዚህ ዐለም ድካም መለየትን ካለንበት ዓለመ መሬት (ምድር) በሕይወት ወደ ብሔረ ብፁዓን አልያም ብሔረ ሕያዋን መሻገር ዕረፍት ተብሎ ይነገራል
የሌሎቹን አበው ወደብሔረ ሕያዋን መሔድ ዕረፍት ይለዋል
ለአብነት ግንቦት ፲፩ ስለ ቅዱስ ያሬድ ሲናገር «በዚህች ዕለት የሱራፌል አምሳያቸው ኢትዮጵያዊው ማሕሌታይ ያሬድ ዐረፈ» ይላል።
እንደመውጫ ቅዱስ ዳዊት “ሕያው ሆኖ የሚኖር፥ ሞትንስ የማያይ ማን ነው? ነፍሱንስ ከሲኦል እጅ የሚያድን ማን ነው?” ይላል【መዝ ፹፱ ፥፵፰ 】ከሰው ወገን ሕያው ሆኖ ለዘለዓለም ነዋሪ ሞትንም ሳያይ በምድር ላይ ቀሪ የሆነ ማንም የለም። የሐዋርያው ክብርና ቅድስናም ከመሞቱ አልያም ወደ ብሔረ ሕያዋን ከመነጠቁ ጋር በቀጥታ የሚያያዝበት ልኬት የለውም። ባለመሞቱ የሚከብርበት በመሞቱ የሚቀርበት መንገድ ስለሌለ ክርስቶስ አይሞትም አላለም እስክመጣ ቢኖር… አለ እንጂ።
ሰው ሕያዊት ነፍሱበ በሞት ከተለየችው እንደፈሰሰ ውኃ ነው
ፈሶ የታፈሰ ውኃ 【ማይ ዘገብኣ እምድኅረ ተክዕወ】
የቅዱሱ መጽሐፍ ብሂል እንዲህ ይላል "ዘእምከመ ተክዕወ ማይ ውስተ ምድር ኢይትገባእ" እኛም እንጂ ይህን ይዘን «የፈሰሰ ውኃ አይታፈስም» እንል የለ!?
【፪ኛ ሳሙ፲፬፥፲፬ 】
ዮሐንስ ግን ሞቶ ተቀበረ ሲሉት ተነስቶ የተነጠቀ ነውና የታፈሰ ውኃ ነውና "ማይ ዘገብኣ እምድኅረ ተክዕወ" አልነው።
ሞተ የተባለ በሰዎች ኅሊና የተቀበረውን ማንነታችን ወደልዕልናው በቸርነቱ ይንጠቅልን
ሎቱ ስብሐት ለዘበስብሐተ አቡሁ ይሴባሕ፤ ወሎቱ ቅድሳት
ለዘበቅድሳተ መንፈ ሱይትቄደስ 🙏
በቴዎድሮስ በለጠ ጥር ፬ ቀን ፳፻፲፮ ዓ.ም. ከደብረ ነጎድጓድ
https://m.facebook.com/story.php?story_fbid=pfbid0Gwrw5N6DhSGtkzJqWWYwogjSJc9eyKA8fzp21g7zPCexn89qRvApZNRbfypLLyTpl&id=100001155652281&mibextid=Nif5oz
«ይኔጽር ዓየራተ
ይነግር ኅቡዓተ
እንዘ ይጽሐፍ በእደዊሑ ዘወንጌል ቃላተ
በቅናተ እግዚኡ ሐቌሁ ቀነተ
ዮሐንስ ድንግል ዘኢጥዕመ ሞተ »
【በድጓ በግእዝ አርያሙ ክፍል ለጥር ፬ቱ ቁመት መነሻ እንዲሆን የጻፈልን ነው። ብራና ገጽ ፻፺፩】
በንጽሕና በድንግልና የኖረው ዮሐንስ ሞትን አልቀመሰም ይልና በሌላም ሥፍራ ከሞት ተለይቶ እንደመላእክቱ በሕይወት አለ ሲል ዳግመኛ ምስክርነቱን እንዲህ እያለ ያጸናዋል «በንጽሕ ከመ መላእክት ተሠርገወ ወእመዊት ከማሆሙ ሐይወ»
ሠ) በመልኩ ክፍልና በገድለ ሐዋርያት ማጠቃለያ የመሰወሩ ምስክርነት ተቀምጦ እናገኛለን
« ሰላም ለልብስከ ወለአሣእኒከ ደርገ፤
ተዝካረ ሕይወትከ ያዑቅ ለአብሮኮሮስ ዘተኃድገ፤
ዮሐንስ ዘኮንከ ምስለ መላእክት ዘውገ፤
ምሉዓ ወድግዱገ ዘሰላምከ ፈለገ፤
በውሣጤ ከርሥየ ኢይኩን ንቱገ፡፡ »
【የመኖርህን ነገር ያስረዳ ዘንድ ለተተወ ፤ ለልብስህ ከጫማህ ጋር ክብር ይገባል፤ ከመላእክት ጋር ወዳጅ የሆንክ ዮሐንስ ሆይ! ሞልቶ የተትረፈረፈ የፍቅር አንድነትህ ወንዝ በሆዴ ውስጥ የጎደለ አይሁን /ይሙላ/።】
ረ) የሊቃውንት ቅኔ ለጊዜው በዝክረ ሊቃውንት ከተዘገቡት ሁለቱን ልጠቁም
« ወልደ ነጐድጓድ ተሰደ እንዘ የኀድግ ሀገረ፤
እምኅበ አጥፍአ ሞተ ሰብእ ሦረ፤
ገራህቱ መቅበርት አምጣነ አብቈለት ሣዕረ»
«ዘማ መቅበርት ለወልደ ነጎድጓድ ትቤሎ፤
እመ ትጸልአኒ አንተ ዘያፈቅረኒ ሀሎ»
ሰ) ከውጭ የተገኙ ቀደምት ምንጮች
በውጭ ሀገራት ቀደምት ድርሳናትና ሊቃውንትም ዘንድ ቢሆን ከላይ ያነሳነውን ጭብጥ የሚደግፍ ታሪክ ተመዝግቦ ይገኛል።
https://www.stjohnaz.org/about-us/our-patron-saint/#:~:text=He%20bade%20them%20prepare%20for,disobedient%2C%20they%20fulfilled%20his%20bidding.
በሌላ ሥፍራ የተገኘው ደግሞ ይህን ይላል ቅዱስ ዮሐንስ የሚነጠቅበት ሠዓት እንደደረሰ ሲያውቅ በመስቀል ቅርጽ የተሰናዳ መቃብር እንዲያዘጋጁለት አርድእቱን አዟል እነርሱም በበዛ እንባ መምህራቸውን እየሳሙ ካለመታዘዝ እንዳይቆጠርባቸው ፊቱን በጨርቅ ሸፍነው ወደ መቃብሩ ሥፍራ አኑረውት ሄደዋል። ከደቀ መዛሙርቱ አንዱ ( ቅዱስ አብሮኮሮስ) ወደቦታው ተመልሶ ቢመጣ መቃብሩን ቢከፍተው ባዶ ሆኖ አግኝቶታል።
«He bade them prepare for him a cross-shaped grave, in which he lay, telling his disciples that they should cover him over with the soil. The disciples tearfully kissed their beloved teacher, but not wanting to be disobedient, they fulfilled his bidding. They covered the face of the saint with a cloth and filled in the grave. Learning of this, other disciples of Saint John came to the place of his burial. #When_they_opened_the_grave, they found it empty.»
በአብሮኮሮስ ስለተሠጠው ምስክርነት (testimony of St. Prochorus) ደግሞ ተከታዩት አስረጂ በሊንኩ ታግዘው ቢያዩ የበከጠ ሐሳባችንን ያግዛል።
https://www.johnsanidopoulos.com/2009/09/repose-of-st-john-theologian-according.html?m=1
✧ ለማስማማት በሚነሳው የማስታረቂያ ሐሳብ
በኤፌሶን/ ቱርክ የመቃብሩ ሥፍራ ይህ ነው እየተባለ ዛሬም ለጎብኚዎች ይታያል።
ይሁንና ግን ☞ገራህቱ መቅበርት አምጣነ አብቈለት ሣዕረ ፣
☞ልብሱ ለዮሐንስ ወአሣእኑ ዘተኃድገ ለአብሮኮሮስ ከመ ያዑቅ ሕይወቱ ፣
☞ When they opened the grave, they found it empty ከሚሉቱ ሳይስማማ ሞቷል ለሚሉቱ ድጋፍ መስሎ ቀርቧል። በመላእክት ቢሎ በደቀመዛሙርቱ መቃብሩ መዘጋጀቱ እውነት ቢሆንም ሥጋው ከዚያ መታጣቱና የአብሮኮሮስ ምስክርነት ተሰውሯል ወደሚለው ያደርሰናል።
የስንክሳሩን አገላለጥ በሚመለከት ደግሞ ወደ ብሔረ ሕያዋን ተነጥቀዋል ብላ ቤ/ክርስቲያን የምትናገርላቸውን ቅዱሳንን ዐዕረፈ ብሎ ማስቀመጥ በአያሌው የተለመደ ነው። ዐረፈ የሚለው በአገባቡ ሞትን ብቻ አይገልጥም ከዚህ ዐለም ድካም መለየትን ካለንበት ዓለመ መሬት (ምድር) በሕይወት ወደ ብሔረ ብፁዓን አልያም ብሔረ ሕያዋን መሻገር ዕረፍት ተብሎ ይነገራል
የሌሎቹን አበው ወደብሔረ ሕያዋን መሔድ ዕረፍት ይለዋል
ለአብነት ግንቦት ፲፩ ስለ ቅዱስ ያሬድ ሲናገር «በዚህች ዕለት የሱራፌል አምሳያቸው ኢትዮጵያዊው ማሕሌታይ ያሬድ ዐረፈ» ይላል።
እንደመውጫ ቅዱስ ዳዊት “ሕያው ሆኖ የሚኖር፥ ሞትንስ የማያይ ማን ነው? ነፍሱንስ ከሲኦል እጅ የሚያድን ማን ነው?” ይላል【መዝ ፹፱ ፥፵፰ 】ከሰው ወገን ሕያው ሆኖ ለዘለዓለም ነዋሪ ሞትንም ሳያይ በምድር ላይ ቀሪ የሆነ ማንም የለም። የሐዋርያው ክብርና ቅድስናም ከመሞቱ አልያም ወደ ብሔረ ሕያዋን ከመነጠቁ ጋር በቀጥታ የሚያያዝበት ልኬት የለውም። ባለመሞቱ የሚከብርበት በመሞቱ የሚቀርበት መንገድ ስለሌለ ክርስቶስ አይሞትም አላለም እስክመጣ ቢኖር… አለ እንጂ።
ሰው ሕያዊት ነፍሱበ በሞት ከተለየችው እንደፈሰሰ ውኃ ነው
ፈሶ የታፈሰ ውኃ 【ማይ ዘገብኣ እምድኅረ ተክዕወ】
የቅዱሱ መጽሐፍ ብሂል እንዲህ ይላል "ዘእምከመ ተክዕወ ማይ ውስተ ምድር ኢይትገባእ" እኛም እንጂ ይህን ይዘን «የፈሰሰ ውኃ አይታፈስም» እንል የለ!?
【፪ኛ ሳሙ፲፬፥፲፬ 】
ዮሐንስ ግን ሞቶ ተቀበረ ሲሉት ተነስቶ የተነጠቀ ነውና የታፈሰ ውኃ ነውና "ማይ ዘገብኣ እምድኅረ ተክዕወ" አልነው።
ሞተ የተባለ በሰዎች ኅሊና የተቀበረውን ማንነታችን ወደልዕልናው በቸርነቱ ይንጠቅልን
ሎቱ ስብሐት ለዘበስብሐተ አቡሁ ይሴባሕ፤ ወሎቱ ቅድሳት
ለዘበቅድሳተ መንፈ ሱይትቄደስ 🙏
በቴዎድሮስ በለጠ ጥር ፬ ቀን ፳፻፲፮ ዓ.ም. ከደብረ ነጎድጓድ
https://m.facebook.com/story.php?story_fbid=pfbid0Gwrw5N6DhSGtkzJqWWYwogjSJc9eyKA8fzp21g7zPCexn89qRvApZNRbfypLLyTpl&id=100001155652281&mibextid=Nif5oz
St. John the Evangelist Orthodox Church
Our Patron Saint - St. John the Evangelist Orthodox Church
The Holy, Glorious All-laudable Apostle and Evangelist, Virgin, and Beloved Friend of Christ, John the Theologian was the son of Zebedee and Salome, a daughter of St Joseph the Betrothed. He was called by our Lord Jesus Christ to be one of His Apostles at…
"ወቀዊሞ ማዕከለ ሕያዋን ወሙታን ከተረ መዓተ"
【መጽሐፈ ጥበብ ምዕራፍ ፲፰ ቁጥር ፳፫】
°✞°°°°°°°°°°°°°°°✥°°°°°°°°°°°°°°°°†°(#ነገረ_ከተራ)
«አሁንስ አበዛችሁት!» ይላሉ ዳታንና አቤሮን እንዲሁም ሐሳባቸውን የገዙ ቆሬና ልጆቹ【ዘኁ. ፲፮፥፫】 የዛሬዎቹን ‘ሁላችን የሀዲስ ኪዳን ካህናት ነን’ ባዮቹን መስለውና በሙሴ ፊት በመቆም
‘አሮንን ብቻ ማን ካህን አደረገው እኛስ ካህን ለመሆን ምን ያንሰናል?’ እያሉ
ጨምረው እንዲህ ይላሉ «ማኅበሩ ሁላቸውም እያንዳንዳቸው ቅዱሳን ናቸው» ወይ መመሳሰል እንዴት ይደንቃል! ራሳችሁን ቅዱሳን ቅዱሳን እያላችሁ የምትጠራሩና የምትንጠራሩ ደቂቀ ዳታን ውሉደ አቤሮን ኧረ አድቡ። በእግዚአብሔር ምርጫ ላይ አፍ የሚከፍቱትን መሬት ተከፍታ ውጣቸዋለች እኮ!
ዛሬ በውሥጥ በውጪ የቸገረ ነገር የሆነው እንዲህ ዐይነቱ ግብረ ዕቡያን ነው።
⇄ በውሥጥ «አሁንስ እጅግ አበዛችሁት!» እያሉ ከመንበረ ፓትርያርክ ውጪ <መንበረ ሃሮ ዘኦሮሚያ> እና <መንበረ አክሱም ዘትግራይ> እያሉ ራሳቸውን በየሰፈራቸው የቀባቡና የተቀባቡ በሥልጣነ መለኮት ላይ የተሳለቁ የጥምቀት ማግሥት ጉዶች አየን።
⇆ በውጭ ክርስቲያን ነን የሚሉ ደፍረው ራሳቸውን ቅዱስ እያሉ የጠሩ ባለክህነት ለመሆንስ ማን ከልክሎን ብለው በዘፈቀደ የሚሿሿሙ!
ውጤቱ ምን ነበር?
ሙሴ ለቆሬ ልጆች «እጅግ ያበዛችሁትስ እናንተ ናችሁ» 【ዘኁ ፲፮፥፯】እኛ አልከለከልናችሁ ተፈቀደልን ካላችሁ በሉ ከእግዚአብሔር ጠይቃችሁ አግኙት አላቸው ፤ እነ ሙሴ እነ አሮነን ተሰበሰቡ በጉዳዩ ወደ እግዚአብሔር አመለከቱ ከዚያ ጠሯቸው « አንመጣም! በእኛ ላይ ራስህን አለቃ ታደርጋለህ?" አሉ 【ዘኁ ፲፮፥፲፪/፲፫】
አወይ መመሳሰላችን እናንተዬ። ዛሬም አስኬማውን ከማጀት እንደተገኘ የቤታቸው ድስት አጥልቀው በየጎሳቸው የሚሮጡ ሲጠሩ እምቢኝ ብለው በየጓዳው የሚቀላውጡ አቤሮናውያን አየን።
ብቻ ተክህነናል ያሉቱ መሬት ተከፍታ ዋጠቻቸው 250ዎቹን አጣኝ ነን ባዮች ደቂቀ ቆሬና 14,700 ተከታዮቻቸውን መቅሰፍት እሳት ከሰማይ ወርዳ በልታቸዋለች።
ያን ጊዜ ካህኑ አሮን ወደቀሩት ሕያዋን መቅሰፍት እሳቱ እዳይሻገር ከሙታኑ መንደር እንዲቀር በመካከል ቆሞ ያጥን ጀመር ያን ጊዜ #ከተራ_ሆነ። ‘ወበማዕከሎሙ ቀዊሞ ከተረ መዓተ’ ይለዋል።
“በሙታንና በሕያዋን መካከል ቆመ፤ መቅሠፍቱም ተከለከለ።” 【ዘኁ ፲፮፥፵፰】
ጠቢቡ ሰሎሞን ላለፈው የካህኑ አሮንን ለሚመጣው የሊቀ ካህናቱ የክርሰቶስን አይቶ ነገሩን እንዲህ እያለ በጥበብ መጽሐፍ ያስተምርበታል።
"ወቀዊሞ ማዕከለ ሕያዋን ወሙታን ከተረ መዓተ
አኮ በኃይለ ሥጋ ወኢበግብረ ንዋየ ሐቅል አላ በቃለ ዚአከ በዘአዘከረ ሎቱ መሐላ አበው ወኪዳኖሙ ☞ በሥጋዊ ኃይልና ለጦርነት በሚሆን መሣርያ አይደለም በራስህ ቃል ለቅዱሳን አበው የማለውን መሐላ የገባላቸውን ቃልኪዳን አስቦ በሞታንና በሕያዋን መካከል ቆሞ መዓቱን ከተረ/አቆመ " 【ጥበ. ፲፰፥፳፫】
የቀደመው አሮን በሙታኑና በሕያዋኑ መካከል ቆሞ "ተዘከር አብርሃምሃ ወይስሐቅሃ ወያዕቆብሃ ዘመሐልከ በርእስከ ☞ ለአብርሃም ለይስሐቅና ለያዕቆብ በራስህ የማልከውን መሐላ አስብ" እያለ መዓቱን ከለከለ መቅሰፍቱን አቆመ። ከተራ ይለዋል እንዲህ ያለውን የመዓቱን መቆም የምሕረቱን መምጣት!
ቀዳማዊና ደኃራዊ ፊተኛውና ኋላኛው ዘልዓለማዊው የሐዲሱ ኪዳን ሊቀ ካህናት ክርስቶስ "የማታውቁት በመካከላችሁ ቆሟል" ተብሎ በበረኛው በዮሐንስ መጥምቅ የተመሰከረለት የነፍሳችን እረኛ በጥምቀቱ በኦሪታውያኑ ምውታንና በሀዲስ ኪዳኑ ሕያዋን መካከል ቆሞ በቁጣው እሳት በአዳም ዘር ላይ የነደደውን መርገማችንን ደምስሶ መዓቱን በምሕረት መልሶ ባርነቱን አቆመልን። ይህ #በጥምቀቱ_የተገኘ_ከተራ ነው።
① የበጉ እናት የሊቀ ካህናቱ ወላዲት እመቤታችን ድንግል ማርያም ስለዚህ ከተራ መዓቱን አርቆ ምሕረቱን ልኮ ድኅነቱ ስለተሠጠበት ምሥጢር ይህን ትሰብክልናለች
“እንደዚህ ለአባቶቻችን ምሕረት አደረገ፤ ለአባታችን ለአብርሃምም የማለውን መሐላውን ቅዱሱን ኪዳን አሰበ”
【ሉቃስ ፩፥፸፪-፸፫】
② ይህን ከተራ ከድግል እመቤታችን ቀጥላ የሰበከችው አንቀጽ የተባለች ዮርዳኖስ ናት፤ ራሷ ቆማና ሸሽታ ከተራውን በተግባር እየመሰከረች
“አንቺ ባሕር የሸሸሽ፥ አንቺም ዮርዳኖስ ወደ ኋላሽ የተመለስሽ፥ምን ሆናችኋል?” 【መዝ ፻፲፬፥፭】
③ በጥምቀቱ የተፈጸመልንን የነገረ ከተራውን ምስክርነት ዐጻዌ ኆኅት፣ ጺያሔ ፍኖት የተባለ መጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ እንዲህ ሲል ለሦስተኛ ጊዜ አጽንቶታል “በነገው ዮሐንስ ኢየሱስን ወደ እርሱ ሲመጣ አይቶ እንዲህ አለ፦ እነሆ የዓለምን ኃጢአት የሚያስወግድ (የሚከትር) የእግዚአብሔር በግ።”
【ዮሐ ፩፥፳፱】
ከተራ የሚለው ቃል በቁሙ ከመነሻው ከተረ ብሎ ዘጋ አቆመ አገደ ከለከለ ማለት ነው በቀረበ አውድ ደግሞ ከበበ ዐጠረ ዙሪያውን ያዘ ማለትም ይሆናል በተከበበ ገንዳ በታጠረ ሥፍራ ጥምቀቱን ከከተራ አንስተን ማክበራችን ለዚሁ ነው።
ከወንጌሉ ክፍል ለማጠቃለያ የሚሆነንን አንድ ምንባብ እናንሳና ነገረ ከተራችንን እንቋጭ
"እውነት እውነት እላችኋለሁ፥ ወደ በጎች በረት በበሩ የማይገባ በሌላ መንገድ ግን የሚወጣ እርሱ ሌባ ወንበዴም ነው፤ በበሩ የሚገባ ግን የበጎች እረኛ ነው። ለእርሱ በረኛው ይከፍትለታል፤ በጎቹም ድምፁን ይሰሙታል፥ የራሱንም በጎች በየስማቸው ጠርቶ ይወስዳቸዋል። የራሱንም ሁሉ ካወጣቸው በኋላ በፊታቸው ይሄዳል፥ በጎቹም ድምፁን ያውቃሉና ይከተሉታል፤ ከሌላው ግን ይሸሻሉ እንጂ አይከተሉትም፥ የሌሎችን ድምፅ አያውቁምና"
የዮሐንስ ወንጌል ምዕራፍ ፲ ከቁጥር ፩―፲
በበሩ የማይገቡ «ቅዱሳን ነን ካህናት ነን» ባዮች ብዙ ወንበዴዎች አሉ። እነዚህ መዓት የማይከተርላቸው እሳተ ሲዖል የሚበላቸው የገሃነም አፍ የሚውጣቸው ናቸው። ሊቃውንቱ በሩን ወደእርሱ መግባትን ያገኘንባት እረኛችን ክርስቶስ እኛን ያገኘባት የምሥጢራቱ መግቢያ ቅድስት ጥምቀት ናት ይሉናል።
☞ ኖላዊ ኄር ዘይቤ እግዚእነ ወመድኃኒነ ኢየሱስ ክርስቶስ ውእቱ (‹‹ቸር ጠባቂ›› ያለው ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ነው።)
☞ ወአንቀጽኒ ፈለገ ዮርዳኖስ ውእቱ (‹‹በርም›› የዮርዳኖስ ወንዝ(ጥምቀት) ነው።)
☞ ወዐጻዊሰ ዮሐንስ መጥምቅ ውእቱ (‹‹በረኛውም›› ዮሐንስ መጥምቅ ነው፡፡)
☞ ወዐጸድ መንግሥተ ሰማያት ይእቲ ( ‹‹ስፍራም›› መንግሥተ ሰማያት ናት፡፡ )
አበው ሲተርቱ «ባጤ ሞት የተከተረ በስለት የተመተረ አንድ ነው» ይላሉ። ለእኛ የሕይወታችን ዐጤ የነፍሳችን ንጉሠ ነገሥት ክርስቶስ ከሥፍራችን እንዳንታጣ ከቤቱ እንዳንወጣ በሞት ሳይሆን በሕይወት እንዲከትረን ከዘልዓለማዊ ዐጸድ ከሰማይ ቤቱ እንዳንጎድልና በፍርዱ ሠይፍ እንዳንመተር ከሥላሴ ልጅነታችን ከተዋህዶ ሃይማኖታችን አያናውጸን።
✍️ በቴዎድሮስ በለጠ ከተራ ፳፻፲፮ ዓ.ም. ከደቡብ ሱዳን ጁባ ደብረ ምሕረት ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክርስቲያን
【መጽሐፈ ጥበብ ምዕራፍ ፲፰ ቁጥር ፳፫】
°✞°°°°°°°°°°°°°°°✥°°°°°°°°°°°°°°°°†°(#ነገረ_ከተራ)
«አሁንስ አበዛችሁት!» ይላሉ ዳታንና አቤሮን እንዲሁም ሐሳባቸውን የገዙ ቆሬና ልጆቹ【ዘኁ. ፲፮፥፫】 የዛሬዎቹን ‘ሁላችን የሀዲስ ኪዳን ካህናት ነን’ ባዮቹን መስለውና በሙሴ ፊት በመቆም
‘አሮንን ብቻ ማን ካህን አደረገው እኛስ ካህን ለመሆን ምን ያንሰናል?’ እያሉ
ጨምረው እንዲህ ይላሉ «ማኅበሩ ሁላቸውም እያንዳንዳቸው ቅዱሳን ናቸው» ወይ መመሳሰል እንዴት ይደንቃል! ራሳችሁን ቅዱሳን ቅዱሳን እያላችሁ የምትጠራሩና የምትንጠራሩ ደቂቀ ዳታን ውሉደ አቤሮን ኧረ አድቡ። በእግዚአብሔር ምርጫ ላይ አፍ የሚከፍቱትን መሬት ተከፍታ ውጣቸዋለች እኮ!
ዛሬ በውሥጥ በውጪ የቸገረ ነገር የሆነው እንዲህ ዐይነቱ ግብረ ዕቡያን ነው።
⇄ በውሥጥ «አሁንስ እጅግ አበዛችሁት!» እያሉ ከመንበረ ፓትርያርክ ውጪ <መንበረ ሃሮ ዘኦሮሚያ> እና <መንበረ አክሱም ዘትግራይ> እያሉ ራሳቸውን በየሰፈራቸው የቀባቡና የተቀባቡ በሥልጣነ መለኮት ላይ የተሳለቁ የጥምቀት ማግሥት ጉዶች አየን።
⇆ በውጭ ክርስቲያን ነን የሚሉ ደፍረው ራሳቸውን ቅዱስ እያሉ የጠሩ ባለክህነት ለመሆንስ ማን ከልክሎን ብለው በዘፈቀደ የሚሿሿሙ!
ውጤቱ ምን ነበር?
ሙሴ ለቆሬ ልጆች «እጅግ ያበዛችሁትስ እናንተ ናችሁ» 【ዘኁ ፲፮፥፯】እኛ አልከለከልናችሁ ተፈቀደልን ካላችሁ በሉ ከእግዚአብሔር ጠይቃችሁ አግኙት አላቸው ፤ እነ ሙሴ እነ አሮነን ተሰበሰቡ በጉዳዩ ወደ እግዚአብሔር አመለከቱ ከዚያ ጠሯቸው « አንመጣም! በእኛ ላይ ራስህን አለቃ ታደርጋለህ?" አሉ 【ዘኁ ፲፮፥፲፪/፲፫】
አወይ መመሳሰላችን እናንተዬ። ዛሬም አስኬማውን ከማጀት እንደተገኘ የቤታቸው ድስት አጥልቀው በየጎሳቸው የሚሮጡ ሲጠሩ እምቢኝ ብለው በየጓዳው የሚቀላውጡ አቤሮናውያን አየን።
ብቻ ተክህነናል ያሉቱ መሬት ተከፍታ ዋጠቻቸው 250ዎቹን አጣኝ ነን ባዮች ደቂቀ ቆሬና 14,700 ተከታዮቻቸውን መቅሰፍት እሳት ከሰማይ ወርዳ በልታቸዋለች።
ያን ጊዜ ካህኑ አሮን ወደቀሩት ሕያዋን መቅሰፍት እሳቱ እዳይሻገር ከሙታኑ መንደር እንዲቀር በመካከል ቆሞ ያጥን ጀመር ያን ጊዜ #ከተራ_ሆነ። ‘ወበማዕከሎሙ ቀዊሞ ከተረ መዓተ’ ይለዋል።
“በሙታንና በሕያዋን መካከል ቆመ፤ መቅሠፍቱም ተከለከለ።” 【ዘኁ ፲፮፥፵፰】
ጠቢቡ ሰሎሞን ላለፈው የካህኑ አሮንን ለሚመጣው የሊቀ ካህናቱ የክርሰቶስን አይቶ ነገሩን እንዲህ እያለ በጥበብ መጽሐፍ ያስተምርበታል።
"ወቀዊሞ ማዕከለ ሕያዋን ወሙታን ከተረ መዓተ
አኮ በኃይለ ሥጋ ወኢበግብረ ንዋየ ሐቅል አላ በቃለ ዚአከ በዘአዘከረ ሎቱ መሐላ አበው ወኪዳኖሙ ☞ በሥጋዊ ኃይልና ለጦርነት በሚሆን መሣርያ አይደለም በራስህ ቃል ለቅዱሳን አበው የማለውን መሐላ የገባላቸውን ቃልኪዳን አስቦ በሞታንና በሕያዋን መካከል ቆሞ መዓቱን ከተረ/አቆመ " 【ጥበ. ፲፰፥፳፫】
የቀደመው አሮን በሙታኑና በሕያዋኑ መካከል ቆሞ "ተዘከር አብርሃምሃ ወይስሐቅሃ ወያዕቆብሃ ዘመሐልከ በርእስከ ☞ ለአብርሃም ለይስሐቅና ለያዕቆብ በራስህ የማልከውን መሐላ አስብ" እያለ መዓቱን ከለከለ መቅሰፍቱን አቆመ። ከተራ ይለዋል እንዲህ ያለውን የመዓቱን መቆም የምሕረቱን መምጣት!
ቀዳማዊና ደኃራዊ ፊተኛውና ኋላኛው ዘልዓለማዊው የሐዲሱ ኪዳን ሊቀ ካህናት ክርስቶስ "የማታውቁት በመካከላችሁ ቆሟል" ተብሎ በበረኛው በዮሐንስ መጥምቅ የተመሰከረለት የነፍሳችን እረኛ በጥምቀቱ በኦሪታውያኑ ምውታንና በሀዲስ ኪዳኑ ሕያዋን መካከል ቆሞ በቁጣው እሳት በአዳም ዘር ላይ የነደደውን መርገማችንን ደምስሶ መዓቱን በምሕረት መልሶ ባርነቱን አቆመልን። ይህ #በጥምቀቱ_የተገኘ_ከተራ ነው።
① የበጉ እናት የሊቀ ካህናቱ ወላዲት እመቤታችን ድንግል ማርያም ስለዚህ ከተራ መዓቱን አርቆ ምሕረቱን ልኮ ድኅነቱ ስለተሠጠበት ምሥጢር ይህን ትሰብክልናለች
“እንደዚህ ለአባቶቻችን ምሕረት አደረገ፤ ለአባታችን ለአብርሃምም የማለውን መሐላውን ቅዱሱን ኪዳን አሰበ”
【ሉቃስ ፩፥፸፪-፸፫】
② ይህን ከተራ ከድግል እመቤታችን ቀጥላ የሰበከችው አንቀጽ የተባለች ዮርዳኖስ ናት፤ ራሷ ቆማና ሸሽታ ከተራውን በተግባር እየመሰከረች
“አንቺ ባሕር የሸሸሽ፥ አንቺም ዮርዳኖስ ወደ ኋላሽ የተመለስሽ፥ምን ሆናችኋል?” 【መዝ ፻፲፬፥፭】
③ በጥምቀቱ የተፈጸመልንን የነገረ ከተራውን ምስክርነት ዐጻዌ ኆኅት፣ ጺያሔ ፍኖት የተባለ መጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ እንዲህ ሲል ለሦስተኛ ጊዜ አጽንቶታል “በነገው ዮሐንስ ኢየሱስን ወደ እርሱ ሲመጣ አይቶ እንዲህ አለ፦ እነሆ የዓለምን ኃጢአት የሚያስወግድ (የሚከትር) የእግዚአብሔር በግ።”
【ዮሐ ፩፥፳፱】
ከተራ የሚለው ቃል በቁሙ ከመነሻው ከተረ ብሎ ዘጋ አቆመ አገደ ከለከለ ማለት ነው በቀረበ አውድ ደግሞ ከበበ ዐጠረ ዙሪያውን ያዘ ማለትም ይሆናል በተከበበ ገንዳ በታጠረ ሥፍራ ጥምቀቱን ከከተራ አንስተን ማክበራችን ለዚሁ ነው።
ከወንጌሉ ክፍል ለማጠቃለያ የሚሆነንን አንድ ምንባብ እናንሳና ነገረ ከተራችንን እንቋጭ
"እውነት እውነት እላችኋለሁ፥ ወደ በጎች በረት በበሩ የማይገባ በሌላ መንገድ ግን የሚወጣ እርሱ ሌባ ወንበዴም ነው፤ በበሩ የሚገባ ግን የበጎች እረኛ ነው። ለእርሱ በረኛው ይከፍትለታል፤ በጎቹም ድምፁን ይሰሙታል፥ የራሱንም በጎች በየስማቸው ጠርቶ ይወስዳቸዋል። የራሱንም ሁሉ ካወጣቸው በኋላ በፊታቸው ይሄዳል፥ በጎቹም ድምፁን ያውቃሉና ይከተሉታል፤ ከሌላው ግን ይሸሻሉ እንጂ አይከተሉትም፥ የሌሎችን ድምፅ አያውቁምና"
የዮሐንስ ወንጌል ምዕራፍ ፲ ከቁጥር ፩―፲
በበሩ የማይገቡ «ቅዱሳን ነን ካህናት ነን» ባዮች ብዙ ወንበዴዎች አሉ። እነዚህ መዓት የማይከተርላቸው እሳተ ሲዖል የሚበላቸው የገሃነም አፍ የሚውጣቸው ናቸው። ሊቃውንቱ በሩን ወደእርሱ መግባትን ያገኘንባት እረኛችን ክርስቶስ እኛን ያገኘባት የምሥጢራቱ መግቢያ ቅድስት ጥምቀት ናት ይሉናል።
☞ ኖላዊ ኄር ዘይቤ እግዚእነ ወመድኃኒነ ኢየሱስ ክርስቶስ ውእቱ (‹‹ቸር ጠባቂ›› ያለው ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ነው።)
☞ ወአንቀጽኒ ፈለገ ዮርዳኖስ ውእቱ (‹‹በርም›› የዮርዳኖስ ወንዝ(ጥምቀት) ነው።)
☞ ወዐጻዊሰ ዮሐንስ መጥምቅ ውእቱ (‹‹በረኛውም›› ዮሐንስ መጥምቅ ነው፡፡)
☞ ወዐጸድ መንግሥተ ሰማያት ይእቲ ( ‹‹ስፍራም›› መንግሥተ ሰማያት ናት፡፡ )
አበው ሲተርቱ «ባጤ ሞት የተከተረ በስለት የተመተረ አንድ ነው» ይላሉ። ለእኛ የሕይወታችን ዐጤ የነፍሳችን ንጉሠ ነገሥት ክርስቶስ ከሥፍራችን እንዳንታጣ ከቤቱ እንዳንወጣ በሞት ሳይሆን በሕይወት እንዲከትረን ከዘልዓለማዊ ዐጸድ ከሰማይ ቤቱ እንዳንጎድልና በፍርዱ ሠይፍ እንዳንመተር ከሥላሴ ልጅነታችን ከተዋህዶ ሃይማኖታችን አያናውጸን።
✍️ በቴዎድሮስ በለጠ ከተራ ፳፻፲፮ ዓ.ም. ከደቡብ ሱዳን ጁባ ደብረ ምሕረት ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክርስቲያን
ውእቱሰ ከመ መርዓዊ ዘይወጽእ እምጽርሑ
#አርሱም_ከእልፍኙ_እንደሚወጣ_ሙሽራ_ነው
°°°°°°°°°°[መዝሙር ፲፰(፲፱)፥ ፭ ]°°°°°°°°
ቅዱስ ዳዊት ነገሩን የሚያነሳው "ወውስተ ፀሐይ ሴመ ጽላሎቶ ☞ በፀሐይ ክበብ ውሥጥ ጸዳሉን አደረገ (በእነርሱም ውስጥ የፀሐይን ድንኳን አደረገ)" በማለት ነው።
መልሶም ያ ፀሓይ ከጫጉላ የወጣ ሙሽራን ይመስላል [ውእቱሰ ከመ መርዓዊ ዘይወጽእ እምጽርሑ] በማለት ፀሐዩን በሙሽራ እየመሰለ በማሕጸነ ድንግል የተደረገውን ድንቅ ምሥጢረ ሥጋዌና ነገረ ተዋህዶ ወደእኛ እያቀረበ የበተስፋ ይተነብያ አራቅቆ ይተነትናል።
መተርጉማኑ ምሳሌስ ከተመሰለለት ነገር ቢያንስ እንጂ እንደምን ይበልጥ ብለው (ምሳሌ ዘየሐጽጽ ባለው) መምሰልስ ሙሽራው ነው ፀሐይን የሚመስለው እንጂ እንዴት ፀሐይ ሙሽራን ይመስላል ይላል ? ብለው ወደዘመኑ ተመልሰው ራሱን ዳዊትን ይጠይቁታል! ይመልስላቸዋል እንዲህ ብለው ይታረቁታል «መመሳሰል የጋራ ነው ብሎ እንዲህ አለ» ፤ ከዚህ አለፍ ብለው ደግሞ ሙሽራው ፀሐይን የፈጠረ መርዓዊ ሰማያዊ ክርስቶስ ሆኖ ፀሐይም ራሱ ፀሐየ ጽድቅ አማኑኤል ብለው አንዱን በአንዱ እያወዳጁ ምሥጢሩን በነገረ ምሳሌ ያስማሙታል።
ቅዱሱ ነቢይ የትንቢቱ ማረፊያ የሚያደርገው በፀሐይነቱ ውሳጣዊ ዓይናችን ብሩህ ያደረገልንንና የሕሊናችንን ጨለማ አርቆ ከእርሱ በሚገኝ እውቀት ያከበረንን እውነተኛ ብርሃን ቅዱሳኑን በጸጋ ብርሃናት የሚያሰኛቸውን አምላካችን ክርስቶስን ነው እንደሙሽራ ከጫጉላ ቤቱ ከሰርግ አዳራሹ ከድንግል እናቱ የወጣ ነውና ።
#ክርስቶስ_ፀሐይ
°°°°°°🌞°°°°°°
እርሱ ፀሐየ ጽድቅ ክርስቶስ ምሥራቅና ጽባህ ከተባለች እናቱ ድንግል ሲወጣ ከቆጥ ተሰቅሎ ከማገር ተንጠልጥሎ ያለ ሁሉ እንደሚገለጥ በእርሱም ፊት አንዳች የማይሠወር ፀሐይ [አልቦ ዘይትኀባእ እምላኅቡ] የተባለ፤
እርሱ ፀሐየ ጽድቅ ክርስቶስ በዙፋኑ ከተቀመጠ ንጉሥ አንስቶ በአደባባይ እስከወደቀ ጽኑስ ሁሉ ሊያየው የሚመኝ የሚረባ የሚጠቅም በመንገዱም ለመሮጥ ደስ የሚሰኝ አርበኛ ፀሐይ [ይትፌሳሕ ከመ ይርባሕ ዘይሜርድ ፎኖቶ] የተባለ፤
እርሱ ፀሐየ ዘጽድቅ ክርስቶስ ከባህሪው በሚገኘው ብርሃን የምድርን ጨለማ ያራቀ በጽድቁ ኃጢኣትን በእውቀቱ ድንቁርናን በንጽሕናው ርኩስን ያስወገደ ፀሐይ [ንጹሕ ወይሜይጣ ለነፍስ] የተባለ፤
የከበረች ቤተክርስቲያንን ለራሱ ሙሽሪት ያደረገና እንደሰርግ ቤት (ጫጉላ) የእናቱ ድንግል ማርያምን ማሕጸን ንጽሕት አዳራሽ አድርጎ ሥጋችንን ነስቶ የተዋሐደን የማይጠልቅ ፀሐይ የተባለው ሙሽራው ክርስቶስ በቅዱሳኑ ላይ አድሮባቸው የሚኖርና የዓለም ብርሃን ያደረጋቸው
☀️ #ጊዮርጊስ_ጸሐይ☀️
ፀሐይን የሚገልጥ ፀሐይ ጊዮርጊስ ፀሐየ ልዳ
ፀሐይም ቁምነገር ሁኖ ቅዱሳንን በዚህ መመሰላችን የሚነደው መብዛቱ ያሳዝናል፤ እንኳን በምግባር በሃይማኖት የተገለጠ ቅድስና ብቻውን የሰውነት ተፈጥሮ ከፀሐይ የላቀ ነበር። መጽሐፍ እንዲህ ይላል
"ከፀሐይ የሚነጻ ምን አለ? እርሱስ እንኳ ያልፋል፤ እንዲህ መሆን ሳለ ደማዊና ስጋዊ (ሰው) ክፉ ነገር ያስባል" 【ሲራ ፲፯፥፴፩】
ፀሐይ ይደንቃችኋል? ቅድስናን የባህሪ ገንዘቡ ያደረገ የበጎ ሥጦታና ፍጹም በረከት ምንጭ የተለዩ ፣ የከበሩ ፣ የነጹና የጸኑ ቅዱሳኑን መርጦ በፀጋው ቅድስና ከፍ የሚያደርግ አምላካችን ክርስቶስ ፦ በኑሯቸው እርሱን የመሰሉት እርሱ በእነርሱ ሕይት ቢገለጥ የተገለና አድሮባቸው ቢኖር ቅዱሳንን ክብራቸው ከፀሓይ እጥፍ ድርብ (Resplendently) የሚያበራ እንደሆነ በወንጌል ነግሮናል!
“በዚያን ጊዜ ጻድቃን በአባታቸው መንግሥት እንደ ፀሐይ ይበራሉ።” 【ማቴ ፲፫፥፵፫】
ሊያውም በሃይማኖታቸው ጽናትና በምግባራቸው ተጋድሎ የጽድቃቸው መገለጫ የሆነው ብርሃን ጉድለት ሳይኖርበት የሚጨምር እንደሆነ ጠቢቡ ሰሎሞን ይመሰክራል
“የጻድቃን መንገድ ግን እንደ ንጋት ብርሃን ነው፥ ሙሉ ቀን እስኪሆንም ድረስ እየተጨመረ ይበራል።” 【ምሳ ፬፥፲፰】
በልዳ ምሥራቅነነት ለክርስትናው አርበኝነት ሲወጣና ሲያበራ የታየው ቅዱስ ጊዮርጊስ የልዳው ፀሐይ ነው!
🌟 #ጊዮርጊስ_ኮከብ 🌟
ወደ ኮከብ የሚመራ ኮከብ ጊዮርጊስ ኮከበ ፋርስ
መክብበ ሰማዕታት ኮከበ ክብር ወመስተጋድል ቅዱሱ መንፈሳዊ አርበኛ ጊዮርጊስ ጨለማ በነገሠበት ሥቃይና መከራ በሠለጠነበት ምድራችን በሃይማኖቱ ጽናት በተጋድሎውም ትጋት በላይኛው ሰማይ በከበረች ነፍሱ እንደ ኮከብ ብሩህ ነው። "ወለነፍሰ ጻድቃንሰ ከመ ከዋክብት ብሩሃት በመልዕልተ ሰማያት" እንዲል【፩መቃ ፴፮፥፵】
በተለይም ደግሞ በዛሬዋ ኢራን የቀድሞዋ ፋርስ (persia) ለብዙዎች ከስሑታን ፍኖት መመለስና በእውነተኛው ሃይማኖት መጽናት አብነት ሆኖ በማለፉ ኮከበ ፋርስ ተብሏል።
“ብዙ ሰዎችንም ወደ ጽድቅ የሚመልሱ እንደ ከዋክብት ለዘላለም ይደምቃሉ።” ይላልና【ዳንኤል ፲፪፥፫】
ክርስቶስ ያደመቃቸው ከዋክብት ከእርሱ የተገኙ የእርሱ ስለሆኑ መርተው ወደ እርሱ ያደርሳሉ፤ በዚኽች ጥንት ምሥራቃዊት (ጽባሓዊቷ) ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያናችን በኩል ያየነው ይህ ፍጡነ ረድኤት የተባለው ኮከብ እንደ ሰብአ ሰገል ፈጥኖ እየመራ ከቅድስናው አዳራሽ እያስገባን ለአምላካችን እንድንገዛለት ያደርገናል።
"ርኢነ ኮከበ ዚአሁ በምሥራቅ ወመጻእነ ከመ ንስግድ ሎቱ ☞ የእርሱን ኮከብ በምሥራቅ ዐይተን ልንሰግድለት መጥተናል" 【ማቴ. ፪፥፪】
ደብረ ይድራስ ጽርሐ መርዓሁ ለጊዮርጊስ
#ጊዮርጊስ_የክርስቶስ_ሙሽራ #እልፍኙ_የይድራስ_ተራራ
°°°🏔°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°⛰️°°°
#ይድራስ የሚለው ቃል ምድረ በዳ ማለት እንደሆነ የገድለ ቅዱስ ጊዮርጊስ ጸሐፊ የእንቆራው ኤጲስ ቆጶስ ቅዱስ ቴዎዶጦስ (Saint Theodotus of Ancyra) ይነግረናል።
☞ ወአዲ አዘዘ ይንሥኡ እምድር ከመ ይጹሩ ሐመደ ሥጋሁ ለቅዱስ ወይሰድዎ በከበሮ ወያዕርግዎ ኀበ #ደብር_ልዑል_ዘስሙ_ይድራስ ዘውእቱ መካነ በድው ብሂል ወይዘርዉ በነፋስ መልዕልተ ደብር ከመ ኢይርከብዎ ክርስቲያን ሐመደ ሥጋሁ ወወዓልትሂ ዘረዉ ሐመደ ሥጋሁ ውስተ ደብር ወተመይጡ
ዳግመኛም የቅዱሱን የሥጋውን አመድ አፍሰው በመውሰድ በቀፎ አድርገው ትርጓሜው #ምድረ_በዳ የሆነ ስሙ ይድራስ ተብሎ ወደ ሚጠራ ታላቅ ተራራ ላይ ክርስቲያኖች የሥጋውን አመድ እዳያገኙት በነፋስ እንዲያዘሩት አዘዘ፤ ጭፍሮቹም የሥጋውን አመድ በተራራ ላይ በትነው ተመለሱ።
የተራራውን ትክክለኛ መጠሪያ ስም በሚመለከት በገላትያ ላለችው እንቆራ ኤጲስ ቆጶስ የነበረው ብፁዕ ቴዎዶጦስ [The blessed Abba Theodotus, Bishop of Ancyra in Galatija] #የእውነት_ፀሐይ #የንጋት_ኮከብ (The sun of the truth☀️, the star of the morning🌟) እያለ ጠርቶ ያከብረውና በዱድያኖስ በኩል ከደረሰበት ጸዋትወ መከራ አንዱ ሥጋውን አቃጥለው አመድ አድርገው ከፍ ወዳለ ተራራ ይዘውት እንደወጡና በዚያም እንደበተኑት አመልክቶ የተራራውንም ስም #ደብረ_አሱርዮን ብሎ አስቀምጧል።
Then Dadianus made them take his ashes up to a high mountain called #Asurion, and they scattered them on the mountain to the winds.
#አርሱም_ከእልፍኙ_እንደሚወጣ_ሙሽራ_ነው
°°°°°°°°°°[መዝሙር ፲፰(፲፱)፥ ፭ ]°°°°°°°°
ቅዱስ ዳዊት ነገሩን የሚያነሳው "ወውስተ ፀሐይ ሴመ ጽላሎቶ ☞ በፀሐይ ክበብ ውሥጥ ጸዳሉን አደረገ (በእነርሱም ውስጥ የፀሐይን ድንኳን አደረገ)" በማለት ነው።
መልሶም ያ ፀሓይ ከጫጉላ የወጣ ሙሽራን ይመስላል [ውእቱሰ ከመ መርዓዊ ዘይወጽእ እምጽርሑ] በማለት ፀሐዩን በሙሽራ እየመሰለ በማሕጸነ ድንግል የተደረገውን ድንቅ ምሥጢረ ሥጋዌና ነገረ ተዋህዶ ወደእኛ እያቀረበ የበተስፋ ይተነብያ አራቅቆ ይተነትናል።
መተርጉማኑ ምሳሌስ ከተመሰለለት ነገር ቢያንስ እንጂ እንደምን ይበልጥ ብለው (ምሳሌ ዘየሐጽጽ ባለው) መምሰልስ ሙሽራው ነው ፀሐይን የሚመስለው እንጂ እንዴት ፀሐይ ሙሽራን ይመስላል ይላል ? ብለው ወደዘመኑ ተመልሰው ራሱን ዳዊትን ይጠይቁታል! ይመልስላቸዋል እንዲህ ብለው ይታረቁታል «መመሳሰል የጋራ ነው ብሎ እንዲህ አለ» ፤ ከዚህ አለፍ ብለው ደግሞ ሙሽራው ፀሐይን የፈጠረ መርዓዊ ሰማያዊ ክርስቶስ ሆኖ ፀሐይም ራሱ ፀሐየ ጽድቅ አማኑኤል ብለው አንዱን በአንዱ እያወዳጁ ምሥጢሩን በነገረ ምሳሌ ያስማሙታል።
ቅዱሱ ነቢይ የትንቢቱ ማረፊያ የሚያደርገው በፀሐይነቱ ውሳጣዊ ዓይናችን ብሩህ ያደረገልንንና የሕሊናችንን ጨለማ አርቆ ከእርሱ በሚገኝ እውቀት ያከበረንን እውነተኛ ብርሃን ቅዱሳኑን በጸጋ ብርሃናት የሚያሰኛቸውን አምላካችን ክርስቶስን ነው እንደሙሽራ ከጫጉላ ቤቱ ከሰርግ አዳራሹ ከድንግል እናቱ የወጣ ነውና ።
#ክርስቶስ_ፀሐይ
°°°°°°🌞°°°°°°
እርሱ ፀሐየ ጽድቅ ክርስቶስ ምሥራቅና ጽባህ ከተባለች እናቱ ድንግል ሲወጣ ከቆጥ ተሰቅሎ ከማገር ተንጠልጥሎ ያለ ሁሉ እንደሚገለጥ በእርሱም ፊት አንዳች የማይሠወር ፀሐይ [አልቦ ዘይትኀባእ እምላኅቡ] የተባለ፤
እርሱ ፀሐየ ጽድቅ ክርስቶስ በዙፋኑ ከተቀመጠ ንጉሥ አንስቶ በአደባባይ እስከወደቀ ጽኑስ ሁሉ ሊያየው የሚመኝ የሚረባ የሚጠቅም በመንገዱም ለመሮጥ ደስ የሚሰኝ አርበኛ ፀሐይ [ይትፌሳሕ ከመ ይርባሕ ዘይሜርድ ፎኖቶ] የተባለ፤
እርሱ ፀሐየ ዘጽድቅ ክርስቶስ ከባህሪው በሚገኘው ብርሃን የምድርን ጨለማ ያራቀ በጽድቁ ኃጢኣትን በእውቀቱ ድንቁርናን በንጽሕናው ርኩስን ያስወገደ ፀሐይ [ንጹሕ ወይሜይጣ ለነፍስ] የተባለ፤
የከበረች ቤተክርስቲያንን ለራሱ ሙሽሪት ያደረገና እንደሰርግ ቤት (ጫጉላ) የእናቱ ድንግል ማርያምን ማሕጸን ንጽሕት አዳራሽ አድርጎ ሥጋችንን ነስቶ የተዋሐደን የማይጠልቅ ፀሐይ የተባለው ሙሽራው ክርስቶስ በቅዱሳኑ ላይ አድሮባቸው የሚኖርና የዓለም ብርሃን ያደረጋቸው
☀️ #ጊዮርጊስ_ጸሐይ☀️
ፀሐይን የሚገልጥ ፀሐይ ጊዮርጊስ ፀሐየ ልዳ
ፀሐይም ቁምነገር ሁኖ ቅዱሳንን በዚህ መመሰላችን የሚነደው መብዛቱ ያሳዝናል፤ እንኳን በምግባር በሃይማኖት የተገለጠ ቅድስና ብቻውን የሰውነት ተፈጥሮ ከፀሐይ የላቀ ነበር። መጽሐፍ እንዲህ ይላል
"ከፀሐይ የሚነጻ ምን አለ? እርሱስ እንኳ ያልፋል፤ እንዲህ መሆን ሳለ ደማዊና ስጋዊ (ሰው) ክፉ ነገር ያስባል" 【ሲራ ፲፯፥፴፩】
ፀሐይ ይደንቃችኋል? ቅድስናን የባህሪ ገንዘቡ ያደረገ የበጎ ሥጦታና ፍጹም በረከት ምንጭ የተለዩ ፣ የከበሩ ፣ የነጹና የጸኑ ቅዱሳኑን መርጦ በፀጋው ቅድስና ከፍ የሚያደርግ አምላካችን ክርስቶስ ፦ በኑሯቸው እርሱን የመሰሉት እርሱ በእነርሱ ሕይት ቢገለጥ የተገለና አድሮባቸው ቢኖር ቅዱሳንን ክብራቸው ከፀሓይ እጥፍ ድርብ (Resplendently) የሚያበራ እንደሆነ በወንጌል ነግሮናል!
“በዚያን ጊዜ ጻድቃን በአባታቸው መንግሥት እንደ ፀሐይ ይበራሉ።” 【ማቴ ፲፫፥፵፫】
ሊያውም በሃይማኖታቸው ጽናትና በምግባራቸው ተጋድሎ የጽድቃቸው መገለጫ የሆነው ብርሃን ጉድለት ሳይኖርበት የሚጨምር እንደሆነ ጠቢቡ ሰሎሞን ይመሰክራል
“የጻድቃን መንገድ ግን እንደ ንጋት ብርሃን ነው፥ ሙሉ ቀን እስኪሆንም ድረስ እየተጨመረ ይበራል።” 【ምሳ ፬፥፲፰】
በልዳ ምሥራቅነነት ለክርስትናው አርበኝነት ሲወጣና ሲያበራ የታየው ቅዱስ ጊዮርጊስ የልዳው ፀሐይ ነው!
🌟 #ጊዮርጊስ_ኮከብ 🌟
ወደ ኮከብ የሚመራ ኮከብ ጊዮርጊስ ኮከበ ፋርስ
መክብበ ሰማዕታት ኮከበ ክብር ወመስተጋድል ቅዱሱ መንፈሳዊ አርበኛ ጊዮርጊስ ጨለማ በነገሠበት ሥቃይና መከራ በሠለጠነበት ምድራችን በሃይማኖቱ ጽናት በተጋድሎውም ትጋት በላይኛው ሰማይ በከበረች ነፍሱ እንደ ኮከብ ብሩህ ነው። "ወለነፍሰ ጻድቃንሰ ከመ ከዋክብት ብሩሃት በመልዕልተ ሰማያት" እንዲል【፩መቃ ፴፮፥፵】
በተለይም ደግሞ በዛሬዋ ኢራን የቀድሞዋ ፋርስ (persia) ለብዙዎች ከስሑታን ፍኖት መመለስና በእውነተኛው ሃይማኖት መጽናት አብነት ሆኖ በማለፉ ኮከበ ፋርስ ተብሏል።
“ብዙ ሰዎችንም ወደ ጽድቅ የሚመልሱ እንደ ከዋክብት ለዘላለም ይደምቃሉ።” ይላልና【ዳንኤል ፲፪፥፫】
ክርስቶስ ያደመቃቸው ከዋክብት ከእርሱ የተገኙ የእርሱ ስለሆኑ መርተው ወደ እርሱ ያደርሳሉ፤ በዚኽች ጥንት ምሥራቃዊት (ጽባሓዊቷ) ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያናችን በኩል ያየነው ይህ ፍጡነ ረድኤት የተባለው ኮከብ እንደ ሰብአ ሰገል ፈጥኖ እየመራ ከቅድስናው አዳራሽ እያስገባን ለአምላካችን እንድንገዛለት ያደርገናል።
"ርኢነ ኮከበ ዚአሁ በምሥራቅ ወመጻእነ ከመ ንስግድ ሎቱ ☞ የእርሱን ኮከብ በምሥራቅ ዐይተን ልንሰግድለት መጥተናል" 【ማቴ. ፪፥፪】
ደብረ ይድራስ ጽርሐ መርዓሁ ለጊዮርጊስ
#ጊዮርጊስ_የክርስቶስ_ሙሽራ #እልፍኙ_የይድራስ_ተራራ
°°°🏔°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°⛰️°°°
#ይድራስ የሚለው ቃል ምድረ በዳ ማለት እንደሆነ የገድለ ቅዱስ ጊዮርጊስ ጸሐፊ የእንቆራው ኤጲስ ቆጶስ ቅዱስ ቴዎዶጦስ (Saint Theodotus of Ancyra) ይነግረናል።
☞ ወአዲ አዘዘ ይንሥኡ እምድር ከመ ይጹሩ ሐመደ ሥጋሁ ለቅዱስ ወይሰድዎ በከበሮ ወያዕርግዎ ኀበ #ደብር_ልዑል_ዘስሙ_ይድራስ ዘውእቱ መካነ በድው ብሂል ወይዘርዉ በነፋስ መልዕልተ ደብር ከመ ኢይርከብዎ ክርስቲያን ሐመደ ሥጋሁ ወወዓልትሂ ዘረዉ ሐመደ ሥጋሁ ውስተ ደብር ወተመይጡ
ዳግመኛም የቅዱሱን የሥጋውን አመድ አፍሰው በመውሰድ በቀፎ አድርገው ትርጓሜው #ምድረ_በዳ የሆነ ስሙ ይድራስ ተብሎ ወደ ሚጠራ ታላቅ ተራራ ላይ ክርስቲያኖች የሥጋውን አመድ እዳያገኙት በነፋስ እንዲያዘሩት አዘዘ፤ ጭፍሮቹም የሥጋውን አመድ በተራራ ላይ በትነው ተመለሱ።
የተራራውን ትክክለኛ መጠሪያ ስም በሚመለከት በገላትያ ላለችው እንቆራ ኤጲስ ቆጶስ የነበረው ብፁዕ ቴዎዶጦስ [The blessed Abba Theodotus, Bishop of Ancyra in Galatija] #የእውነት_ፀሐይ #የንጋት_ኮከብ (The sun of the truth☀️, the star of the morning🌟) እያለ ጠርቶ ያከብረውና በዱድያኖስ በኩል ከደረሰበት ጸዋትወ መከራ አንዱ ሥጋውን አቃጥለው አመድ አድርገው ከፍ ወዳለ ተራራ ይዘውት እንደወጡና በዚያም እንደበተኑት አመልክቶ የተራራውንም ስም #ደብረ_አሱርዮን ብሎ አስቀምጧል።
Then Dadianus made them take his ashes up to a high mountain called #Asurion, and they scattered them on the mountain to the winds.
ለበለጠ መረጃ ተከታዮቹን የውጪ ምንጮች ከገድለ ቅዱስ ጊዮርጊስ ጋር ለተጨማሪ ማስረጃ ያገናዝቡ ( በአስተያየት መስጫው በተቀመጠው አስፈንጣሪ ማውረድ ይችላሉ)
✧ THE ENCOMIUM OE BISHOP ABBA THEODOTUS [THE MARTYRDOM AND MIRACLES OF SAINT GEORGE OF CAPPADOCIA. THE COPTIC TEXTS EDITED WITH AN ENGLISH TRANSLATION
ERNEST A. WALLIS BUDGE, M. A] Pp. 307
✧ The Passion of St. George Translated by E. A. W Budge Written by Abba Theodotus, Bishop of Ancyra in Glaatia in 431 AD. Pp. 18
በተራራው ላይ ጥር ፲፰ ቀን ስለተደረው ገቢረ ተአምራት ገድሉ በተጨማሪነት ከላይ በርእስነት ያነሳነውን ቃል በሰማዕቱ ቅዱስ ጊዮርጊስ ሕይወት ውሥጥ እያየ እንዲህ ይነግረናል
☞ ወጸውኦ እግዚእነ ኢየሱስ ክርስቶስ ለማር ሰማዕት ቅዱስ ጊዮርጊስ በቃሉ አምላካዊ … ወሶቤሐ ተንስአ ከመ መርዓዊ ዘይወጽእ እምጽርሑ እንዘ አልቦ ሕማም ለግሙራ
ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስም ሰማዕቱን ቅዱስ ጊዮርጊስን በአምላካዊ ቃሉ ጠራውና "የመረጥኩህ ወዳጄ ጊዮርጊስ ሆይ አሁን ከእንቅልፍህ ተነሥ አትፍራ፡፡ የማዝህ በመከራህ ሁሉ ከአንተ ጋር ያለሁት አምላክህ እኔ ክርስቶስ ነኝ" አለው፡፡ ያን ጊዜም #ቅዱስ_ጊዮርጊስ_ሙሽራ_ከጫጉላው_እንደሚወጣ ምንም ሕማም ሳያገኘው ተነሣ፡፡
#ደብረ_አሱርዮን የክርስቶስ ሙሽራ ሰማዕተ ጽድቅ ቅዱስ ጊዮርጊስን ለመጨረሻው መከራ ለሦስተኛው ሞት የወለደች የሰርግ አዳራሹ ናት። ምንም ሕማም ሳያገኘው በክብር ላይ ክብር እንዲጨመርለት ለበለጠው ተጋድሎ ጥር ፲፰ ሥጋው አጥንቱ ተቃጥሎ አመድ ሆኖ ተዘርቶ ሙሽራ ሲያገባ ተሰበሰበ እንደሚባለው እርሱም የሰርግ አዳራሹ የሙሽርነት እልፍኙ ከተባለችው ከፍ ያለችና ምድረ በዳ ከሆነች/ይድራስ ተራራ በክብር ተሰብስቦ ተነሳ «#ደብረ_ይድራስ_ጽርሐ_መርዓሁ_ለጊዮርጊስ»
የቀደሙቱ በፈተና ሲጨነቁ በጸሎታቸው እንዲህ የምትል «አርኬ» የልብ ለልብ ተማጽኖ ለሰማዕቱ ያደርሳሉ።
«ተማኅጸንኩ በዝርወተ አጽምከ በደብረ ይድራስ በድው
በአምሳለ ጸበል ወሐመድ በእደ ሠገራት እደው
ጊዮርጊስ ኄር ጊዮርጊስ አፈው
ምርሐኒ ለፍቁርከ እምፆታ ፈቃድ ምንትው
በኀበ አስተርአየ ወፈቀደ መለኮት ሕያው»
በግጥም ወደኛው ስንመልሰው ይኽን ሐሳብ ይዟል
በአጥንቶችህ ተማጽኛለሁ
በተራራው የይድራስ አጸድ
በጠባቂዎች እጅ በተበተነው
እንደ ትቢያና እንደ አመድ
ቸር የምትባል ጊዮርጊስ
ምግባርህም የሚያውድ
ወዳጅህን አንተው ምራኝ
ከሥጋ ፈቃድ መንታ መንገድ
በሚገለጥበት ጎዳና
ሕያው የመለኮት ፈቃድ
🙏አሜን 🙏
መልካም በዓል
✍️ በቴዎድሮስ በለጠ ጥር ዝርወተ አጽሙ ለቅዱስ ጊዮርጊስ ፳፻፲፮ ዓ.ም. [📍ከደብረ ወርቅ አትርፎ ቅዱስ ጊዮርጊስ]
✧ THE ENCOMIUM OE BISHOP ABBA THEODOTUS [THE MARTYRDOM AND MIRACLES OF SAINT GEORGE OF CAPPADOCIA. THE COPTIC TEXTS EDITED WITH AN ENGLISH TRANSLATION
ERNEST A. WALLIS BUDGE, M. A] Pp. 307
✧ The Passion of St. George Translated by E. A. W Budge Written by Abba Theodotus, Bishop of Ancyra in Glaatia in 431 AD. Pp. 18
በተራራው ላይ ጥር ፲፰ ቀን ስለተደረው ገቢረ ተአምራት ገድሉ በተጨማሪነት ከላይ በርእስነት ያነሳነውን ቃል በሰማዕቱ ቅዱስ ጊዮርጊስ ሕይወት ውሥጥ እያየ እንዲህ ይነግረናል
☞ ወጸውኦ እግዚእነ ኢየሱስ ክርስቶስ ለማር ሰማዕት ቅዱስ ጊዮርጊስ በቃሉ አምላካዊ … ወሶቤሐ ተንስአ ከመ መርዓዊ ዘይወጽእ እምጽርሑ እንዘ አልቦ ሕማም ለግሙራ
ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስም ሰማዕቱን ቅዱስ ጊዮርጊስን በአምላካዊ ቃሉ ጠራውና "የመረጥኩህ ወዳጄ ጊዮርጊስ ሆይ አሁን ከእንቅልፍህ ተነሥ አትፍራ፡፡ የማዝህ በመከራህ ሁሉ ከአንተ ጋር ያለሁት አምላክህ እኔ ክርስቶስ ነኝ" አለው፡፡ ያን ጊዜም #ቅዱስ_ጊዮርጊስ_ሙሽራ_ከጫጉላው_እንደሚወጣ ምንም ሕማም ሳያገኘው ተነሣ፡፡
#ደብረ_አሱርዮን የክርስቶስ ሙሽራ ሰማዕተ ጽድቅ ቅዱስ ጊዮርጊስን ለመጨረሻው መከራ ለሦስተኛው ሞት የወለደች የሰርግ አዳራሹ ናት። ምንም ሕማም ሳያገኘው በክብር ላይ ክብር እንዲጨመርለት ለበለጠው ተጋድሎ ጥር ፲፰ ሥጋው አጥንቱ ተቃጥሎ አመድ ሆኖ ተዘርቶ ሙሽራ ሲያገባ ተሰበሰበ እንደሚባለው እርሱም የሰርግ አዳራሹ የሙሽርነት እልፍኙ ከተባለችው ከፍ ያለችና ምድረ በዳ ከሆነች/ይድራስ ተራራ በክብር ተሰብስቦ ተነሳ «#ደብረ_ይድራስ_ጽርሐ_መርዓሁ_ለጊዮርጊስ»
የቀደሙቱ በፈተና ሲጨነቁ በጸሎታቸው እንዲህ የምትል «አርኬ» የልብ ለልብ ተማጽኖ ለሰማዕቱ ያደርሳሉ።
«ተማኅጸንኩ በዝርወተ አጽምከ በደብረ ይድራስ በድው
በአምሳለ ጸበል ወሐመድ በእደ ሠገራት እደው
ጊዮርጊስ ኄር ጊዮርጊስ አፈው
ምርሐኒ ለፍቁርከ እምፆታ ፈቃድ ምንትው
በኀበ አስተርአየ ወፈቀደ መለኮት ሕያው»
በግጥም ወደኛው ስንመልሰው ይኽን ሐሳብ ይዟል
በአጥንቶችህ ተማጽኛለሁ
በተራራው የይድራስ አጸድ
በጠባቂዎች እጅ በተበተነው
እንደ ትቢያና እንደ አመድ
ቸር የምትባል ጊዮርጊስ
ምግባርህም የሚያውድ
ወዳጅህን አንተው ምራኝ
ከሥጋ ፈቃድ መንታ መንገድ
በሚገለጥበት ጎዳና
ሕያው የመለኮት ፈቃድ
🙏አሜን 🙏
መልካም በዓል
✍️ በቴዎድሮስ በለጠ ጥር ዝርወተ አጽሙ ለቅዱስ ጊዮርጊስ ፳፻፲፮ ዓ.ም. [📍ከደብረ ወርቅ አትርፎ ቅዱስ ጊዮርጊስ]
Forwarded from Amanuel Ayalew
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ ፩ አምላክ
የህንጻ ቤተክርስቲያን ምርቃት ጥሪ
፡፡፡፡፡፡፡፡፡።።።።።።።።።፡፡።።።።።።።።።
ኑ" የእግዚአብሔርንም ሥራ አዩ
(መዝ66÷5)
በኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ/በአ/አ/ሀ/ስ/በን/ስ/ላ/ክ/ከተማ ቤ/ክ/የምስራቀ ፀሐይ ለቡ መርጡለ አርሴማ ገዳም ቀደም ሲል ክቡር መልአከ ጽዮን ቆሞስ አባ እስጢፋኖስ ይርጋ ወደዚህ ደብር በዋና አስተዳዳሪነት ተመድበው በመጡበት ሰዓት በሚያደርጉት የጉብኝት ወቅት ቦታው መሀል ከተማ ተቀምጦ እንዴት የቅድስት አርሴማ ጽላት ቆርቆሮ በቆርቆሮ በሆነ መቃኞ ውስጥ ይቀመጣል በማለት መንፈሳዊ ቁጭት አድሮባቸው የአካባቢው ምዕመናንም ህንጻ ቤ/ክ እንዲሰራ ፍላጎት ስላላቸው ዋና አስተዳዳሪው ሳይውሉ ሳያድሩ ልዩ ትኩረት በመስጠት ብዙ ውጣ ውረዶችን አልፈው
እግዚአብሔርን ይዘው የንስሐ ልጆቻቸው የሆኑትን አክሊለ ስማዕትና ወለተ ሐና የተባሉ እግዚአብሔር የመረጣቸው ባልና ሚስቶች የቅድስት አርሴማን ህንጻ ቤተክርስቲያን እንዲሰሩ በማሳመን በራሳቸው ወጪ ብቻ ውሃ አንኳን ከቤተክርስቲያን ሳይጠቀሙ በገንዘብ እየገዙ ማንም ሳይጨመር በደብሩ ዋና አስተዳዳሪ ክቡር መልአከ ጽዮን ቆሞስ አባ እስጢፋኖስ ይርጋ የየዕለት ክትትል በ1 ዓመት ከ4 ወር
ህንጻ ቤተክርስቲያኑ በፈቃደ እግዚአብሔር እጀግ ዘመኑን በዋጀና ባማረ ሁኔታ ተሠርቶ ተጠናቆ የካቲት 9 ቀን2016 ዓ/ም እና የካቲት 10 ቀን 2016 ዓ/ም
.ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ለቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት
.ብፁዕ አቡነ አብርሃም የጠቅላይ ቤተክህነት ጠቅላይ ዋና ስራአስኪያጅ እና የባህር ዳር ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ
.ብፁዕ አቡነ ሄኖክ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስና የተዋህዶ ሚዲያ ማዕከል የበላይ ጠባቂ
ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት የጠቅላይ ቤተክህነትና የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የየመምሪያ ኃላፊዎች በተገኙበት እጅግ ባማረና በደመቀ ሁኔታ የህንጻ ቤተክርስቲያኑ ምርቃት ይከናወናል ።
:::::::::::::::::::::::::::::::::::::::::::::::
በመሆኑም አርስዎም በዕለቱ ተገኝተው የበረከቱ ተሳታፊ እንዲሆኑ እና ላልሰሙት ያሰሙ ዘንድ በሰማዕቷ ቅድስት አርሴማ ሰም መንፈሳዊ ጥሪአችንን እናስተላልፋለን ።
የደብሩ ሰ/ጉ/አ/ጽ/ቤት
Mewi Events
Our passion is your perfect event.
For Bookings ☎️ 0979338787
0910611517
የህንጻ ቤተክርስቲያን ምርቃት ጥሪ
፡፡፡፡፡፡፡፡፡።።።።።።።።።፡፡።።።።።።።።።
ኑ" የእግዚአብሔርንም ሥራ አዩ
(መዝ66÷5)
በኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ/በአ/አ/ሀ/ስ/በን/ስ/ላ/ክ/ከተማ ቤ/ክ/የምስራቀ ፀሐይ ለቡ መርጡለ አርሴማ ገዳም ቀደም ሲል ክቡር መልአከ ጽዮን ቆሞስ አባ እስጢፋኖስ ይርጋ ወደዚህ ደብር በዋና አስተዳዳሪነት ተመድበው በመጡበት ሰዓት በሚያደርጉት የጉብኝት ወቅት ቦታው መሀል ከተማ ተቀምጦ እንዴት የቅድስት አርሴማ ጽላት ቆርቆሮ በቆርቆሮ በሆነ መቃኞ ውስጥ ይቀመጣል በማለት መንፈሳዊ ቁጭት አድሮባቸው የአካባቢው ምዕመናንም ህንጻ ቤ/ክ እንዲሰራ ፍላጎት ስላላቸው ዋና አስተዳዳሪው ሳይውሉ ሳያድሩ ልዩ ትኩረት በመስጠት ብዙ ውጣ ውረዶችን አልፈው
እግዚአብሔርን ይዘው የንስሐ ልጆቻቸው የሆኑትን አክሊለ ስማዕትና ወለተ ሐና የተባሉ እግዚአብሔር የመረጣቸው ባልና ሚስቶች የቅድስት አርሴማን ህንጻ ቤተክርስቲያን እንዲሰሩ በማሳመን በራሳቸው ወጪ ብቻ ውሃ አንኳን ከቤተክርስቲያን ሳይጠቀሙ በገንዘብ እየገዙ ማንም ሳይጨመር በደብሩ ዋና አስተዳዳሪ ክቡር መልአከ ጽዮን ቆሞስ አባ እስጢፋኖስ ይርጋ የየዕለት ክትትል በ1 ዓመት ከ4 ወር
ህንጻ ቤተክርስቲያኑ በፈቃደ እግዚአብሔር እጀግ ዘመኑን በዋጀና ባማረ ሁኔታ ተሠርቶ ተጠናቆ የካቲት 9 ቀን2016 ዓ/ም እና የካቲት 10 ቀን 2016 ዓ/ም
.ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ለቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት
.ብፁዕ አቡነ አብርሃም የጠቅላይ ቤተክህነት ጠቅላይ ዋና ስራአስኪያጅ እና የባህር ዳር ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ
.ብፁዕ አቡነ ሄኖክ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስና የተዋህዶ ሚዲያ ማዕከል የበላይ ጠባቂ
ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት የጠቅላይ ቤተክህነትና የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የየመምሪያ ኃላፊዎች በተገኙበት እጅግ ባማረና በደመቀ ሁኔታ የህንጻ ቤተክርስቲያኑ ምርቃት ይከናወናል ።
:::::::::::::::::::::::::::::::::::::::::::::::
በመሆኑም አርስዎም በዕለቱ ተገኝተው የበረከቱ ተሳታፊ እንዲሆኑ እና ላልሰሙት ያሰሙ ዘንድ በሰማዕቷ ቅድስት አርሴማ ሰም መንፈሳዊ ጥሪአችንን እናስተላልፋለን ።
የደብሩ ሰ/ጉ/አ/ጽ/ቤት
Mewi Events
Our passion is your perfect event.
For Bookings ☎️ 0979338787
0910611517
✧ ቃለ እግዚአብሔር ዘይትኀባእ በግእዘ ሕጻናት ✧
【በሕጻናት ባህሪ የተሰወረ የእግዚአብሔር ቃል】
ሰው ምኞቱን በተስፋ እየጠበቀ ፣ ነገውን በእቅድ እየናፈቀ … ገና ብላቴና ሳለ «ወደፊት ሳድግ እንዲህ ብሆን» ይላል ።
ያ በምናባችን የሳልነው ነገ በከንቱ አልፎ የምንቆጭበት ትናንት እየሆነብን እናዝናለን።
የዚህች ሕጻን ንግግር ግን ወደኋላ ልጅ ሳለን እንዲህ ሆነን ቢሆን ኖሮ ያስብለናል።
በዚህ መንገድ የቀረጻችሁ ቤተሰቦች ብድር ይግባችሁ!
ልጃችሁን ባልተለወጠ አንደበት በተመጠነ እድገት በቤቱ ያሰንብትላችሁ🙏
https://youtu.be/bRKiuAEcqOs?si=2CRRVXaQz_ImeLlv
【በሕጻናት ባህሪ የተሰወረ የእግዚአብሔር ቃል】
ሰው ምኞቱን በተስፋ እየጠበቀ ፣ ነገውን በእቅድ እየናፈቀ … ገና ብላቴና ሳለ «ወደፊት ሳድግ እንዲህ ብሆን» ይላል ።
ያ በምናባችን የሳልነው ነገ በከንቱ አልፎ የምንቆጭበት ትናንት እየሆነብን እናዝናለን።
የዚህች ሕጻን ንግግር ግን ወደኋላ ልጅ ሳለን እንዲህ ሆነን ቢሆን ኖሮ ያስብለናል።
በዚህ መንገድ የቀረጻችሁ ቤተሰቦች ብድር ይግባችሁ!
ልጃችሁን ባልተለወጠ አንደበት በተመጠነ እድገት በቤቱ ያሰንብትላችሁ🙏
https://youtu.be/bRKiuAEcqOs?si=2CRRVXaQz_ImeLlv
YouTube
ለመጠየቅ ፈራሁ!! እጹብ ድንቅ ልጆች የሃረገወይን #etsubdinklijoch #comedianeshetu #ethiopia
ማን እንደ ሀገር አዲስ እስታንዳፕ ኮሜዲ ለማየት ይመዝገቡ
https://tally.so/r/nr6ljL
የወጌሻ ዩትዩብ ስልጠና | እስታንዳፕ ኮሜዲ | የእየሩሳሌም ጉዞ እና እጹብ ድንቅ ልጆች ጠቁሞ ለመመዝገብ ከታች ይምረጡ 👇
https://tally.so/r/3ldYl5
ውድ የዶንኪትዩብ ቤተሰቦቻችን የእጹብ ድንቅ ልጆች ፕሮግራማችንን በድጋሜ እነሆ!!!
የዛሬ ፕሮግራም እንግዳችን ህጻን ሃረገወይን ቀለሙ…
https://tally.so/r/nr6ljL
የወጌሻ ዩትዩብ ስልጠና | እስታንዳፕ ኮሜዲ | የእየሩሳሌም ጉዞ እና እጹብ ድንቅ ልጆች ጠቁሞ ለመመዝገብ ከታች ይምረጡ 👇
https://tally.so/r/3ldYl5
ውድ የዶንኪትዩብ ቤተሰቦቻችን የእጹብ ድንቅ ልጆች ፕሮግራማችንን በድጋሜ እነሆ!!!
የዛሬ ፕሮግራም እንግዳችን ህጻን ሃረገወይን ቀለሙ…