Telegram Web Link
#ሕማማት መስቀል " ተብለው የሚዘከሩት አሥራ ሦስት ሲሆኑ እነዚህም፦

1. በብረት ሐብለ መጋፊያና መጋፊያው እስኪጋጠም ድረስ የኋሊት መታሰሩ

2. ከአፍንጫው ደም እስኪውጣ ድረስ 25 ጊዜ በጡጫ መመታቱ

3. 65 ጊዜ ከግንድ ማጋጨታቸው

4. 120 ጊዜ በድንጋይ ፊቱን መመታቱ

5. 365 ጊዜ በሽመል መደብደቡ

6. 80 ጊዜ ጽህሙን መነጨቱ

7. 6666 ጊዜ መገረፉ

8. አክሊለ ሦክ በራሱ ላይ መደፋቱ

9. 136 ጊዜ በምድር ላይ መውደቁ

10. ሳዶር፡ አላዶር፡ ኤዴራ፡ ዳናትና ሮዳስ በሚባሉ 5ቱ ቅንዋተ መስቀልበችንካር መቸንከሩ

11. መራራ ሐሞትን መጠጣቱ

12. መስቀሉን ተሸክሞ መንገላታቱ

13. በመስቀል መሰቀሉ ናቸው።

https://www.tg-me.com/ortodoxtewahedo
👍8👏1
#ቤተ_ክርስቲያን_መሄድ_ለማትችሉ_ሰሙነ_ሕማማትን_በስደት_በሥራ_ለምታሳልፉ_በየቤታችሁ_ሁናችሁ_ለምትሰግዱ_እንዲህ_እያላችሁ_ስገዱ 🙏

👉በመጀመሪያ በስመአብ ብለን የዘወትር ጸሎትን አድርሰን ውዳሴ ማርያምን ቆመን እንደግማለን

በመቀጠል

👉 ለከ ኃይል ክብር ወስብሐት ወእዘዝ እስከ ለዓለመ ዓለም

👉 አማኑኤል አምላኪየ ለከ ኃይል ክብር ወስብሐት ወእዘዝ እስከለዓለመ ዓለም

👉 ኦእግዚእየ ኢየሱስ ክርስቶስ ለከ ኃይል ክብር ወስብሐት ወእዘዝ እስከለዓለመ ዓለም

👉 ኃይልየ ወጸወንየ ውእቱ እግዚእየ እስመ ኮንከኒ ረዳእየ እብል በአኮቴት

🙏 አቡነ ዘበሰማያት / አባታችን ሆይ/

ከቻልን እየመላለስን 12 ግዜ እያልን መስገድ 12 ጊዜ ካልቻልን የቻልነውን ያህል

👇 ይህን ስንጨርስ በዛው ቀጥለን

🙏 ለአምላክ ይደሉ ይደሉ ክብር ወስብሐት ወእዘዝ እስከ ለዓለም

🙏 ለስሉስ ይደሉ ክብር

🙏 ለማኅየዊ ይደሉ ክብር

🙏 ለእዘዙ ይደሉ ክብር

🙏 ለመንግሥቱ ይደሉ ክብር

🙏 ለሥልጣኑ ይደሉ ክብር

🙏 ለምኩናኑ ይደሉ ክብር

🙏 ለኢየሱስ ይደሉ ክብር

🙏 ለክርስቶስ ይደሉ ክብር

🙏 ለሕማሙ ይደሉ ክብር

👉 እስከ አርብ ድረስ እስከዚህ ሲሆን አርብ ለመስቀሉ ይደሉ ይጨምራል

እንዲህ እያልን ከሰገድን በኋላ መዝሙረ ዳዊትን መጽሐፍ ቅዱስ ከኦሪት ከነቢያት ከወንጌል የቻልነውን እናነባለን

ከዛም 👇

👉 ኪርያ ላይሶን ኪርያ ላይሶን ኪርያ ላይሶን ኪርያ ላይሶን

👉 ክርያላይሶን ኪርያላይሶን ዕብኖዲ ናይን ኪርያላስይሶን

🙌 ታኦስ

🙌 ማስያስ

🙌 ኢየሱስ

🙌 ክርስቶስ

🙌 አማኑኤል

🙌 ትስቡጣ

👇 እንዲህ እያልን ከሰገድን በኋላ

41 ጊዜ የቻለ ከዛም በላይ ኪርያላይሶን እያሉ መስገድ ነው።

የቃላት ትርጉም

👉 ኪርያላይሶን ማለት ቃሉ ግሪከኛ ሲሆን አቤቱ ማረን ማለት ነው

👉 ዕብኖዲ ማለት የግጽ ቅብጥኛ ሲሆን አምላክ ማለት ነው

👉 ናይን /ናይናን/ ማለት እኛን ማረን / ቅብጥኛ/

👉 ታኦስ / ግሪከኛ / አምላክ

👉 ማስያስ ።/ እብርይስጥኛ / መሲሕ

👉 ኢየሱስ መድኃኒት

👉 ክርስቶስ ንጉሥ ቅቡዕ የባሕርይ አምላክ

👉 ትስቡጣ /ግሪክኛ / ደግ ገዥ

🤝 የቃሉን ትርጉም እንዲህ እያሰብንና እየተረዳን መስገድ ይገባናል ።ላስተማሩን አባቶቻችን ቃለ ህይወት ያሰማልን።

https://www.tg-me.com/ortodoxtewahedo
👍13🙏32
#ሰሙነ ሕማማት (ዘሰሉስ)
ማክሰኞ

#የጥያቄ ቀን በመባል ይታወቃል፡፡ ምክንያቱም ሹመትን ወይም ሥልጣንን ለሰው ልጅ የሰጠ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስን ሰኞ ባደረገው አንጽሖተ ቤተ መቅደስ ምክንያት በዚህ ዕለት ስለ ሥልጣኑ በጻሕፍት ፈሪሳውያን ተጠይቋልና፡፡

ጥያቄውም ከምድራውያን ነገሥታት፣ ከሌዋውያን ካህናት ያይደለህ ትምህርት ማስተማር፣ ተአምራት ማድረግ፣ ገበያ መፍታት በማን ሥልጣን ታደርጋለህ? የሚል ነበር ይህንስ ሥልጣን እነዚህን እንዳደርግ እነግራችኋለሁ፡፡ የዮሐንስ ጥምቀት ከወዴት ነበረች? ከሰማይ ወይስ ከሰው? አላቸው፡፡ እነርሱም ከሰማይ ነው ብንል ለምን አልተቀበላችሁትም?
ይለናል፡፡

ከሰው ነው ብንል ሕዝቡ ሁሉ ዮሐንስን እንደ አባት ያከብሩታል፤ እንደ መምህርነቱም ይፈሩታልና ሕዝቡን እንፈራለን ተባብለው ወዴት እንደሆነ አናውቅም ብለው መለሱለት፡፡ እርሱም በማን ሥልጣን እነዚህን እንደማደርግ እኔም አልነግራችሁም አላቸው፡፡

ይህንንም መጠየቃቸው እርሱ የሚያደርጋቸውን ሁሉ በራሱ ሥልጣን እንዲያደርግ አጥተውት አልነበረም፡፡

https://www.tg-me.com/ortodoxtewahedo
👍102🙏1
እንበለ ደዌ ወሕማም
እንበለ ፃማ ወድካም
አመ ከመ ዮም
ያብጽሐነ ያብጽሕክሙ ለብርሃነ ትንሣኤሁ
እግዚአብሔር በፍስሓ ወበሰላም!

"ያለ ደዌና ያለ ሕማም፥ ያለ ፃማና ያለ ድካም እግዚአብሔር ለትንሣኤው ብርሃን እንደ ዛሬ ቀን በደስታና በፍቅር በአንድነት ያድርሰን ያድርሳችሁ!"

አሜን!

#ባለ ማዕተቦችን ወደዚህ
   ግሩፕ ይጋብዙ

ለመቀላቀል 👉 
@ortodoxtewahedo
👍19🙏41
🔴 ሆሳዕና || ጌታቸው ይፈልጋቸዋል ...
ፈውስ መንፈሳዊ ጣና ቅ/ቂርቆስ ፬ መጻሕፍተ ጉባኤ ሚዲያ Fews Menfesawi
ጌታቸው ይፈልጋቸዋል
              ሆሳዕና
Size:-111.4MB
Length:-2:00:19

    በርእሰ ሊቃውንት አባ ገብረ ኪዳን ግርማ

ለመቀላቀል

👉 @ortodoxtewahedo
👍7
ከበሮ፣ጸናጽል፣መቋሚያና ከ፲ በላይ ቅዱሳት መጻሕፍትን የኢትዮጵያ አእምሯዊ ንብረት ባለሥልጣን በቅጂና ተዛማች መብቶች ሥራ ተመዝግቦ ከሚያዚያ ፫ ቀን ፳፻ ፲ወ፯ ዓ/ም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን አእምሯዊ ንብረት መሆኑ ተረጋግጧል።

ከዚህ ቀደምም በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የቅርስ ጥበቃ ቤተ መጻሕፍት ወመዘክር መምሪያ በአእምሯዊ ንብረት ዐቢይ ኮሚቴ አማካኝነት በርካታ የቤተክርስቲያን ንብረቶች ተመዝግበው እውቅና ማግኘታቸውን የመምሪያው ኃላፊ መልአከ ሰላም ዳዊት ያሬድ ገልጸዋል።

ምንጭ ፦ የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ

@ortodoxtewahedo
17👍6
ሰሙነ ሕማማት
👉 ረቡዕ

ምክረ አይሁድ ይባላል፦ ረቡዕ እለት የአይሁድ ሊቃነ ካህናትና ጸሐፍት ጌታን እንዴት መያዝ እንዳለባቸው የመከሩበትና ውሳኔ ያሳለፉበት ቀን በመሆኑ ምክረ አይሁድ ይባላል። ወቅቱ የፋሲካን በዓል የሚያከብሩበት ቀን በመሆኑ እና ብዙ ህዝብም ጌታን ይከተለው ስለነበር ሁከት እንዳይነሳ ስጋት ነበራቸው። ነገር ግን ከአስራ ሁለቱ ሐዋርያት አንዱ የአስቆሮቱ ይሁዳ አሳልፎ እንደሚሰጣቸው ስለነገራቸው /ሉቃ ፳፪፥፩-፮/ጭንቀታቸው ተወግዶ በጌታ መያዝ ተስማምተዋል።

የመልካም መዓዛ ቀንም ይባላል፡- ጌታችን በዚህ ዕለት በለምጻሙ በሰምዖን ቤት ተቀምጦ ሳለ መላ ሕይወቷን ለዝሙት አስገዝታ ትኖር የነበረችው ማርያም እንተ እፍረት/ባለሽቶዋ ማርያም/ ዋጋው እጅግ ውድ የሆነ የአልባጥሮስ ሽቱ አምጥታ በራሱ ላይ በማርከፍከፍ ስለቀባቸው ማቴ ፳፮፥፮-፯ የመዓዛ ቀን ይባላል።

የእንባ ቀን ይባላል፡- ባለሽቱዋ ሴት (ማርያም እንተ እፍረት) ኃጢአቷን ይቅር እንዲላት እየለመነች በእግሩ ስር ተደፍታ በእንባዋ እግሩን አርሳለችና ማር ፲፬፥፱ የእንባ ቀን ይባላል።


እንበለ ደዌ ወሕማም እንበለ ጻም ወድካም ያብጽሐነ ያብጽሕክሙ ለብርሃነ ትንሳኤሁ እግዚአብሔር በፍስሐ ወበሰላም።

👉 @ortodoxtewahedo
👍17
#የሰሙነ_ሕማማት_ረቡዕ

#ምክረ_አይሁድ_ይባላል
ምክንያቱም የአይሁድ ሊቃነ ካህናትና ጸሐፍት ጌታን እንዴት መያዝ እንደሚገባቸው ምክር ያጠናቀቁበት ቀን ነውና፡፡ በዚህ ምክራቸው ላይ በጣም ትልቅ ጭንቀት ነበር፡፡ ምክንያቱም ወቅቱ የፋሲካ በዓላቸውን የሚያከብሩበት ቀን የተቃረበ በመሆኑ ብዙው ሕዝብም በጌታችን ትምህርት የተማረኩ ተአምራቱንም የሚያደንቁ ስለ ነበር ሁከት እንዳይፈጠር ነው፡፡ በዚህ ጭንቀት ሳሉ ከደቀ መዛሙርቱ አንዱ የአስቆሮቱ ይሁዳ በመካከላቸው በመገኘት የምክራቸው ተባባሪ ሆኖ ጭንቀታቸውን አስወግዶላቸዋል፡፡ (ማቴ. 26÷1-14፣ ማር. 14÷1-2፣ ሉቃ. 22÷1-6) የሐዲስ ኪዳን ካህናትና ምእመናን በዚሁ ዕለት በቤተ ክርስቲያን ተሰብስበው መላ ሰውነታቸውን ለእግዚአብሔር አስገዝተው የሞት ፍርዱን በማሰብና በማልቀስ ሐዋርያት ከጌታችን መያዝ በኋላ በኀዘን በፍርሐት እንደነበሩ እያሰቡ መጻሕፍትን በማንበብ በጾም በጸሎትና በስግደት ተወስነው ይቆዩና ከአሥራ ሁለት ሰዓት በኋላ ወደ ቤታቸው ይሄዳሉ፡፡

#የመልካም_መዓዛ_ቀንም_ይባላል
ምክንያቱም ጌታችን በዚህ ዕለት በቤተ ስምዖን ዘለምጽ ተቀምጦ ሳለ መላ ሕይወቷን ለዝሙት አስገዝታ ትኖር የነበረችው ማርያም እንተ እፍረት (ባለሽቱዋ ማርያም) "ከእንግዲህ ወዲህ በኃጢአት ተበላሽቶ ይኖር የነበረውን ሕይወቴን እንደዚህ መልካም ሽቱ የሚያጣፍጥ ኃጢአትን ይቅር የሚል አምላክ መጣ" ስትል ዋጋው እጅግ በጣም ውድ የሆነ ከሦስት መቶ ዲናር በላይ የሚያወጣ በአልባስጥሮስ ብልቃጥ የተሞላ ሽቱ ይዛ በመሔድ በጠጉሩ (በራሱ) ላይ በማርከፍከፍ ስለቀባችው ረቡዕ የመዓዛ ቀን ይባላል፡፡

#የእንባ_ቀንም_ይባላል
ማርያም እንተ እፍረት በጌታችን እግር ላይ ተደፍታ መላ ኃጢአቷን ይቅር እንዲላት በእንባዋ እግሩን አጥባዋለችና በጠጉሯም በእንባዋ ያጠበችውን እግሩን አብሳዋለችና። (ማቴ. 26÷6-13፣ ማር. 14÷9፣ ዮሐ. 12÷8) ኃጢአትን በማሰብ ማልቀስና ራስን የተወደደ መሥዋዕት አድርጎ ለእግዚአብሔር ማቅረብን ከምታስተምረን ማርያም እንተ እፍረት እንባን ለንስሐ ሕይወት ልንጠቀምበት ይገባል፡፡

እንበለ ደዌ ወሕማም እንበለ ጻማ ወድካም ያብጽሐነ ያብጽሕክሙ እግዚአብሔር ለብርሃነ ትንሣኤሁ በፍስሐ ወበሰላም።

http://www.tg-me.com/ortodoxtewahedo
👍21🙏1
Audio
ሕማማት

 "በሕማማት የሚደረጉና የማይደረጉ ነገሮች"          
                          
Size:- 26MB
Length:-1:14:43
       
     በርዕሰ ሊቃውንት አባ ገብረ ኪዳን ግርማ

@ortodoxtewahedo
👍21
   "ጌታዬ እጠበኝ"
እግሮቼ የዛሉ ብዙ የተጓዝኩኝ
በቀኝ በግራ ስል መድረሻ ያጣሁኝ
ከጠባቧ መንገድ መርጬ ሰፊውን
በሰፊው ጎዳና ላይ እታች ስኳትን
ንጽሐ ሰውነቴን በበደል ያቆሸኩ
ንጽሐ ልቦናዬን በክፋት ያሳደፍኩ
በኃጥያት ቀንበር ሸክሜ ያጎበጠኝ
ውስጤ ክፋት ሞልቶት ጉልበቴ የከዳኝ
በነፍስ በስጋዬም እጅግ ደካማ ነኝ
ምህረትን የምሻ ተግባር የጎደለኝ
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
ልክ እንደ መጻጉ እንደ ምስኪኑ ሰው
ባህር ውስጥ ሚከተው ዘመድ እንደሌለው
መዳንን ትሻለክ ብለክ የጠየከው
በባህር ውስጥ ሚከት የለኝም መልካም ሰው
ብሎ እንደመለሰው
አይደለሁም እኔ አልጋ ላይ የቀረው
አካሌ የከዳኝ የቆምኩ የመሰለኝ
አልጋህን ተሸክመህ ሂድም እንዳትለኝ
በኃጢያት በሽታ መታመሜን ማላምን
መድኅኒት እንዳላገኝ ህመሜን ምሸሽግ በሽተኛ ሰው ነኝ
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
እንደ ባለሽቶዋ መግደላዊት ማርያም
አንተ ባረፍክበት ማንም ባይጠራትም
ከእግሮችህ ስር ወድቃ ሽቶዋን አፍስሳ
በእንባዋ አጥባ በፀጉራ አብሳ
ከኃጢያት እስራት ስትፈልግ መላቀቅ
በንሰሃ ልንቦናዋ ምህረትን ስጠይቅ
እንደ ሰዎች ሳይሆን ልቧን ተመልክተክ
ዳግም እንዳበድዪ ብለህ እንደማርካትክ
አይደለሁም እኔ ከእግር ስር የምወድቅ
ሽቶን የማላፈስ እንባዬም ነው ደረቅ
ለታይታ የምኖር ሰዎች ምን ይሉኛል ምል
በኃጥያት ቆሽሼ ንጹህ ሰው ስመስል
የምህረት ቀኔን በከንቱ ማሳልፍ
ልበ ደንዳና ነኝ ምግባሬም የሰንፍ
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
ቀድመህ እንደነገርከው ለሐዋርያው ጴጥሮስ
ሥስቴ እንደሚክድህ ፍርሃት በልቡ ሲነግስ
አላቀውም ብሎ ዶሮ እስኪጮህ ድረስ
የንሰሃው ዶሮ ለጸጸት ሲያነቃው
ፊትህን አዙረህ በትዝብት ስታየው
መበደሉን ገብቶት ህሊናውን ሊወቅስ
የንሰሀን እንባ ከአይኖቹ ቢያፈስ
ምህረትን ሲሻ መጸጸቱን አይተክ
በደሉን እረስተክ ንስሀውን ተቀበልክ
እኔ ግን ደካማው በጊዜዬ ያልነቃው
ኃጥያቴን እያወኩ ንስሃ ያልገባው
የንሰሃው ዶሮ ሰልሶ ቢጮህም
ፊትህም ወደኔ በምህረት ቢዞርም
ኅሊናዬ ገብቶት ልቤ አልደነገጠም
የንስሃም እንባም ከዐይኖቼ አሎጣም
።።።።።።።።።።።።።።።፡።፡።።።።።።።።
እናም ጌታዬ ሆይ እኔ ምለምንክ
በኃጥያት ላደፍኩኝ እንዲሆነኝ ምህረትክ
በበደል ዳክሬ ቆሽሻለውና
ሆሳዕና ጌታ ፈጥነህ ወደኔና
ደንዳናውን ልቤን እንድታለሰልሰው
የልቤን መዝጊያ በር በፍቅርህ ስበረው
በኃጥያት ሸክም የዛለ አካሌን
ጉልበቴ ሆነከኝ ልስበረው ቀንበሬን
እንደ መጻጉ አልጋን ባልሸከም
የኃጥያት እግሬ ነጽቶ በንጽሐ እድቆም
ከኃጥያት ልንፃ በፍቅርህ እጠበኝ
ከበረዶም ይልቅ በምህረትህ አንፃኝ
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
                ገጣሚ፦ በላይ ኃ/ሚካኤል

@ortodoxtewahedo
👍121👏1
#ፀሎተ ሀሙስ

#ሀሙስ ምሽት ጌታችን ያደረገልን ትህትና ዮሐንስ 13

እግራቸውንም አጥቦ ልብሱንም አንሥቶ ዳግመኛ ተቀመጠ
እንዲህም አላቸው፦ ያደረግሁላችሁን ታስተውላላችሁን?
እናንተ መምህርና ጌታ ትሉኛላችሁ እንዲሁ ነኝና መልካም
ትላላችሁ።

እንግዲህ እኔ ጌታና መምህር ስሆን እግራችሁን ካጠብሁ
እናንተ ደግሞ እርስ በርሳችሁ እግራችሁን ትተጣጠቡ ዘንድ
ይገባችኋል።

እኔ ለእናንተ እንዳደረግሁ እናንተ ደግሞ ታደርጉ ዘንድ
ምሳሌ ሰጥቻችኋለሁና።

እውነት እውነት እላችኋለሁ ባሪያ ከጌታው አይበልጥም።
መልእክተኛም ከላከው አይበልጥም። 17 ይህን ብታውቁ
ብታደርጉትም ብፁዓን ናችሁ።
ስለ ሁላችሁ አልናገርም እኔ የመረጥኋቸውን አውቃለሁ
ነገር ግን መጽሐፍ፦ እንጀራዬን የሚበላ በእኔ ላይ ተረከዙን
አነሣብኝ ያለው ይፈጸም ዘንድ ነው።

በሆነ ጊዜ እኔ እንደ ሆንሁ ታምኑ ዘንድ ከአሁን ጀምሬ
አስቀድሞ ሳይሆን እነግራችኋለሁ።

ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ለዘላለም ትኑር በመጀመሪያነት ያጋሩት፦
በሰሞነ ህማማት የሚገኙ እለታትና ስያሚያቸው ........እለተ ሀሙስ -በዚህ እለት ጌታችን አምላካችን መድሀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ፍፁም ሰው ፍፁም አምላክ መሆኑን ለመግለፅና ለአርያነት ፀሀፍት ፈሪሳውያን የአይሁድ ካህናት መጥተው እስኪይዙት ድረስ ሲፀልይ በማደሩ ምክንያት ፀሎተ ሀሙስ በመባል ይታወቃል ፡፡

ትህትና ፍቅር መታዘዝ እንድሁም የአገልግሎትም ትርጉም
ለማስረዳትና ለማስገንዘብ እርሱ ጌታ አምላክ ሆኖ ሳለ ዝቅ ብሎ የደቀመዛሙርቱን እግር በማጠቡ ህፅበተ እግር በመባልም እንደሚጠራም ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን ይናገራሉ ፡፡

ሀዋርያው ቅዱስ ዮሀንስም እግራቸውን አጥቦ ልብሱንም አንስቶ ዳግመኛ ተቀመጠ እንድህም አላቸው ያደረኩላችሁን
ታስተውላላችሁን እንግድህ ጌታ መምህር ስሆን እግራችሁን
ካጠብሁ እናንተ ደግሞ ለታናናሾቻችሁ እንድሁ ታደርጉ ዘንድ ይገባችኀል ሲል ተናግራል፡፡ ይኸውም ዮሀንስ ወንጌል 13 ፣12
- 20 በዝርዝር ይገኛል ፡፡

ይህ ለእናንተ በመስቀል ላይ የሚቆረሰው ስጋየ ነው እንካችሁ
ብሉ ይህ ፅዋ ለእናንተ የሚፈሰው የሀዲስ ኪዳን ደሜ ነው ከእርሱ ጠጡ በማለት ሚስጥረ ቁርባንን የመሰረተበት ወይንም
እራሱ ጌታችን አምላካችን መድሀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ
ሚስጥረ ቁርባንን የጀመረበት እለት በመሆኑ የሚስጥር ቀን በመባል ይጠራል ፡፡

ይኸውም የሰው ልጆች ስጋውንና ደሙን ተቀብለው ከእርሱ ጋራ
አንድነትንና ህብረትን እንድኖረን ጥንተ ጠላት ዳቢሎስን ድል
ነስተን ሰማያዊዩን እርስት እንድንወርስ ሊያደርግ ነው፡፡ ይህም በማቴወስ 26 ፣ 26 - 29 በዝርዝር ይገኛል ፡፡

አይሁድ ጌታችንን ለመያዝ በእነርሱ ጥበብና ፍላጎት ቀስ ብለው
መጥተው የያዙበት ስለሆነ በዚህ እለት በለ ሆሳስ ወይም ብዙ
የጩኸት ድምፅ ሳይሰማ የቅዳሴ ስርአት ይፈፀማል ፡፡

ስለሆነም መላው ህዝበ ክርስቲያን በዚህ የህፅበተ ሚስጥር የፀሎት እለት በሆነው በዚህ እለት በንስሀ ታጥበው የጌታን ስጋና ደሙን እንድቀበሉ ቤተ ክርስቲያን በአፅኖት ታስተምራለች ፡፡

እኛም በንስሀ ታጥበን ወደ አምላካችን ቀርበን ስጋወ ደሙን
ልንቀበል ይገባናል የጌታችን ቸርነት ፍቅሩ የእመ አምላክ
የንፅሒተ ንፁሀን የድንግል ማርያም ምልጃ የመላክት ጥበቃ
የሠማአታት ፀጋ በረከታቸው በሁላችን ላይ ይደርብን አሜን
አሜን አሜን !!!

ወስብሐት ለእግዚአብሔር

http://www.tg-me.com/ortodoxtewahedo
👍124🙏4
Forwarded from 🟢ናታኒም ፖሮሞሽን🟢
2025/07/14 02:45:23
Back to Top
HTML Embed Code: