Telegram Web Link
.#የሕማማት_ጥያቄዎችና_መልሶቻቸው

1. በሕማማት ለምን መስቀል አንሳለምም ወይም አናማትብም?
👉🏾የመስቀል ክብር እና ኃይል የታወቀው ጌታ በመስቀለ ከተሰቀለ በኋላ ነው
በሰሞነ ሕማማት ከሰኞ እስከ አርብ ያሉት ቀናት የዓመተ ፍዳ መታሰቢያ ናቸው።
በነዚህ ዘመናት ሰዎች የመስቀልን አገልገሎት እንዳልጀመሩ ለማሳየት
በሰሞነ
ሕማማት በቤተክርስተያን ስርዓት መሰረት መስቀል መሳለምም ሆነ የማማተብ ስርዓት የለም።

2. በሰሞነ ሕማማት ለምን አንሳሳምም?
👉🏾ይሁዳ ጌታውን በመሳም አሳልፎ ሰጥቶአል እኛም እንደ ይሁዳ ክፋት ካለው መሳሳም መለየታችንን ለማሰረዳት።
ከዚሀ በተጨማሪም ፍፁም ሰላም በዘመነ ፍዳ እንዳልነበረ ለማሳየት
በሰሞነ ሕማማት እሰከ መሳሳም የደረሰ ጥብቅ ሰላምታ የለም።
3. በሰሞነ ሕማማት የማይፈቀዱ ሌሎቸ ነገሮች ምን ምን ናቸው?
👉🏾ማንኛውም ለስጋ የሚያደሉ ተግባሮችን መቀነስ እና ቢቻለን አብዛኛውን ጊዜአችንን በቤተ እግዚአብሔር የጌታን መከራ ሕማም በማሰብ በፆም በስግደት
በጸሎት ማሳለፍ
በትዳር ያሉ በመኝታ ከመተዋወቅ መታቀብ
ቢቻል አመጋገባችንን ከወትሮው መቀነስ።
4. ስለ ሰሞነ ሕማማት በመጽሐፍ ቅዱስ የተጻፈ አለን?
👉🏾ነብዩ ኢሳይያስ "በእውነት ደዌአችንን ተቀበለ ሕማማችንንም ተሸክሞአል "
ኢሳ.53፤4 ይላል።
ሕማማት የሚለው ቃለ በቀጥታ ከመጽሐፍ ቅዱስ ተወሰደ ሲሆን የጌታን
መከራ የምናስብበት ሳምንት ነው።
የጌታችንን ሞቱን ሕማሙን ማሰብ መዘከር እንደሚገባ ቅዱስ ጳውሎስ እነዲህ ይላል፦
" ጌታ እስኪመጣ ድረስ ሞቱን ትናገራላችሁና" 1ቆሮ.11፤26።
ይህ ሳምንት ለአይሁድና ለመሰሎቻቸው የደስታ ወቅት ቢሆንም
ለክረስትያኖች በጥልቅ ኅዘን ውስጥ የሚገቡበት ሳምንት ነው
እንዲህ ተብሎ እንደተጻፈ ''እናንተ ታለቅሳላችሁ ሙሾም ታወጣላችሁ
ዓለም ግን ደስ ይለዋል እናንተም ታዝናላችሁ ነገር ግን ኃዘናችሁ ወደ ደስታ
ይለወጣል'' ዮሐ16፤20
በእርግጥ ኃዘናችን ትንሳኤውን እሰክናይ ለጥቂት ጊዜ ቢሆንም ግን እናዝናለን
በትነሳኤው ደግሞ ደስታውን እንካፈላለን።
👉🏾ሰኞ አይሁድ እንዴት እንደሚይዙት ለመማከር ክፉ ጉባኤያቸውን ጀመሩ።
''በዚያን ጊዜ የካህናት አለቆች የሕዝብም ሽማግሎች ቀያፋ በሚባለው
በሊቀ ካህናቱ ግቢ ተሰበሰቡ ጌታ ኢየሱስንም በተንኮል ሊያስይዙት ሊገሉትም ተማከሩ" ማቴ26፡3_4።
ይህንን ጉባዔ ቅዱሰ ዳዊት የከፉዎቸ ጉባዔ እያለ ይጠራዋል።
"ብዙ ውሾች ከበውኛልና የክፋተኞች ጉባኤም ያዘኝ" መዝ21፤16 አይሁድ ሰኞ የጀመሩትን ዕረቡ ውሳኔአቸውን አጠናቀው በምሴተ ሐሙስ ከዕራትና ከቁርባን በኋላ ሰይፍ ጎመድ ይዘው መጡ።

በፈቃዱ ራሱን አሳልፎ ሰጣቸው ያዙትም እስከ አርብ ስድስት ሰአት
ሲያንገላቱት ቆይተው ከብዙ መከራ በኋላ ሰቀሉት ዘጠኝ ሰአት ላይ ቅድስት ነፍሱን በፈቃዱ ከቅዱስ ስጋው ለየ። ከአሰራ አንድ ሰአት በፊት ዮሴፍና ኒቆዲሞስ በምስጋና ገንዘው ቀበሩት።

ከሕማሙ ከመከራው በረከት ያሳትፈን ሰላመ እግዚአብሔር ከሁላችን ጋር ይሁን። አሜን።

👉🏽ትምህርቱ ለሌሎችም ይጠቅማልና ሼር ያድርጉ!
👍10🔥1
#ዕለተ_ዓርብ#ዕለተ_መድኃኒ

#በዲ/ን_በረከት_አዝመራ

"#ለመስቀልከ ንሰግድ ኦ ሊቅነ፤ ጌታችን (መምህራችን) ሆይ! ለመስቀልህ እንሰግዳለን፡፡"
***
"ለከ ኃይል ክብር ወስብሐት ወእዘዝ እስከ ለዓለም፤ ኃይል ክብር ምስጋና እና ብርታት ለአንተ ይገባል"
በሰሙነ ሕማማት #በስግደት ወቅት ደጋግመን የምንለው #ምስጋና ነው:: ጌታችን ለሰው ልጆች #ድኅነት መከራ ተቀብላሏል: በመስቀል ላይ ተሰቅሎ ስለእኛ ሞትን በፈቃዱ ቀምሷል:: ይህ ድካም የመሳላቸው ብዙዎች ናቸው:: (አጋንንት፣ ብዙኃኑ አይሁድ፣ መናፍቃን)
ቤተ ክርስቲያን መከራውና ሞቱ የድካም ሳይሆን የካሳ መሆኑን እና ብርቱ የሰው ልጆች ጠላቶች (ኃጢአት፣ ሞት፣ ዲያብሎስ) የተሸነፉበት መሆኑን በማወቅ 'ኃይል ክብር ምስጋና እና ብርታት የአንተ ነው' በማለት ታመሠግነዋለች:: ይህን ምሥጋና ቀድሞ መላእክት #በመስቀሉ ሥር #እየሠገዱ ተናግረውታል::ኪርያላይሶን (ጌታ ሆይ ማረን)
ክርስቶስን ለመከራ ያደረሰው የሰው ኃጢአት ነው:: መከራና ሞቱም #የምሕረት ምንጭ ነው:: በዚህም ምክንያት ኃጢአታችንን እያሰብን እና በመስቀል የተገለጠውን #ምሕረት እና #ፍቅር እያመንን 'ኪርያላይሶን ጌታ ሆይ ማረን' እያልን እንሰግዳለን:: 'እግዚኦ መሐረነ ክርስቶስ' በማለትም ደጋግመን

#እንማጸናለን::
ምስባካት እና ምንባባት
ዲያቆናት ከዳዊት መዝሙር ስለ መከራው እና ሞቱ የተነገሩ ትንቢቶችን በሚያሳዝን ዜማ ይሰብካሉ፤ ሕዝቡም በስግደት ይቀበላል:: ካህናትም በየሰዓታቱ የተደረጉ ድርጊቶችን የሚገልጹ #የወንጌል ምንባባትን ያነባሉ:: ሁሉም በስግደት ይታጀባሉ፤ በየመካከሉ ካህናት የእጣን ማእጠንት እየወዘወዙ ያጥናሉ:: ይህም #ክርስቶስ መልካም መዓዛ ያለው ንጹሕ #መሥዋዕት ሆኖ መቅረቡን ያዘክራል:: የሕዝበ ክርስቲያኑ #ጸሎትና ተዘክሮም ከዕጣኑ ጋር አብሮ ያርጋል::

"አምነስቲቲ ሙኪርያ አንቲ ፋሲልያሱ..."

ካህናቱ እየመሩ ሕዝቡ እየተከተሉ 'አምንስቲቲ ' እያሉ በሚያሳዝን ዜማ ይጸልያሉ:: 'አቤቱ በመንግስትህ አስበን' ማለት ነው:: በዚህ ጊዜ ቁጭ ተብሎ ራስ በነጠላ ውስጥ ይሸፈናል:: ጸሐይ ስትጨልም እና የክርስቶስ #ዘላለማዊ ንጉሥነት ሲገለጥ በቀኝ የተሰቀለው ወንበዴ (ፈያታዊ ዘየማን) #የጸለየው ጸሎት ነው:: ከሁሉ ቀድሞ #ገነት ያስገባውን ጸሎቱን ጸሎታችን አድርገን እንጸልያለን::
የድል ቀን
ቤተ ክርስቲያን ሕማሙን ትካፈላለች እንጂ ጌታ በግድ የተሰቀለ ይመስል የሽንፈት #ኃዘን አታዝንም:: ይልቁንም በድካም: በሞት የተገለጠ ፍቅሩን እያሰብን ትእዛዙን እየጠበቅን ከእርሱ ጋር ለመኖር ቃል ኪዳናችን እናድሳለን:: የሚታዘነው ፍቅሩ ሊታየው ላልቻለ እና አሁንም ወደ #መድኃኒት ክርስቶስ መቅረብ ላልቻለ ነው::

በዕለቱ የሚነበቡ የነቢያት መጻሕፍት የድል ቀን መሆኑን ነው የሚነግሩን:: ዓርብ በስድስት ሰዓት የሚነበበው የኢሳይያስ ትንቢት "በዚያም ቀን፡— አቤቱ፥ ተቈጥተኸኛልና፥ ቍጣህንም ከእኔ መልሰሃልና፥ አጽናንተኸኛልምና አመሰግንሃለሁ። እነሆ፥ አምላክ መድኃኒቴ ነው፤ ጌታ እግዚአብሔር ኃይሌና ዝማሬዬ ነውና፥ መድኃኒቴም ሆኗልና በእርሱ ታምኜ አልፈራም ትላለህ። ውኃውንም ከመድኃኒት ምንጮች በደስታ ትቀዳላችሁ። በዚያም ቀን እንዲህ ትላላችሁ፡— እግዚአብሔርን አመስግኑ፥ ስሙንም ጥሩ፤ በአሕዛብ መካከል ሥራውን አስታውቁ፤ ስሙ ከፍ ያለ እንደ ሆነ ተናገሩ። ታላቅ ሥራ ሠርቷልና ለእግዚአብሔር ተቀኙ፤ ይህንም በምድር ሁሉ ላይ አስታውቁ። አንቺ በጽዮን የምትኖሪ ሆይ፥ የእስራኤል ቅዱስ በመካከልሽ ከፍ ከፍ ብሏልና ደስ ይበልሽ ፤እልልም በዪ" ይላል:: (ኢሳ. 12:1-6)

በዐሥራ አንድ ሰዓትም "ንሴብሖ ለእግዚአብሔር ስቡሐ ዘተሰብሐ: የተመሰገነ እግዚአብሔርን እናመስግነው" የሚለው የእሥራኤላውያንን መዝሙር እንዘምራለን:: እሥራኤል ይህን #ምሥጋና ያመሰገኑት ባህር ከፍሎ እና ፈርኦንን አስጥሞ ወደ #ተስፋዋ ምድር ስላሻገራቸው ነው:: ቤተ ክርስቲያን የምትዘምረው ሞትን አጥፍቶ፣ ዲያብሎስን አሸንፎ፣ ሲኦልን በርብሮ ወደ #ገነት መንግሥተ ሰማያት ስላሻገረን ነው::

https://www.tg-me.com/ortodoxtewahedo
👍4
✞ ተፈጸመ✞

"ተፈጸመ አለ፥ ራሱንም አዘንብሎ ነፍሱን አሳልፎ ሰጠ" (ዮሐ 19: 30)

ተፈፀመ የሚለው ቃል ጌታችን ኢየሱስ ክርሰቶስ ነፍሱን ለወዳጆቹ ሲሰጥ ከመሞቱ በፊት የተናገረው የመጨረሻ ቃል ነው። " ኢየሱስም ሆምጣጤውን ከተቀበለ በኋላ፦ ተፈጸመ አለ፥ ራሱንም አዘንብሎ ነፍሱን አሳልፎ ሰጠ" (ዮሐ 19: 30)። ተፈፀመ በግሪክ "ቴትለስታ'ይ" (τελείωσε /Tetelestai) ማለት ሲሆን ትርጉሙም ወደ ፍፃሜ ማምጣት፣ መጨረሻ መድረሱን፣ ማከናወንን ፣ ማለቅን የሚያሳይ ነው። በእርግጥ አማኑኤል TETELESTAI/ ተፈፀመ ሲል ምኑ ይሆን የተፈፀመው? ብሎ የሚጠይቅ ህሊና ያስፈልገናል።

አስቀድሞ ጌታችን ኢየሱስ አባቱ የሰጠውን ስራ ለመስራትና ለመፈፀም አምላክነቱን እንደመቀማት ሳይቆጥር በአባቱ በራሱና በመንፈስ ቅዱስ ፈቃድ ወደ ዓለም እንደመጣ አስታውቆናል። ከመጣም በሇላ አባቱን የሚያከብር ስራን ሰርቷል "እኔ ላደርገው የሰጠኸኝን ሥራ ፈጽሜ በምድር አከበርሁህ" (ዮሐ 17: 4) እንዲል። ሊሰራ የመጣው የጠፋነውን የሰው ልጆች ሊፈልግና ሊያድን ዘንድ ነው ። በምድር ሲመላለስ የስራው ፍፃሜ የነበረውንም ነፍሱን ስለወዳጆቹ በመስጠት ፈፀመው ። ክርስቶስ ተፈፀመ ሲል የሽንፈት ቃል አይደለም የድልና የአሸናፊነት እንጂ ወደ ዓለም የመጣሁበትን ስራ በሞት ጨረስኩ፣ ህዝቦቼን በሞት አዳንኩ ፣ የኃጢአትን ኃይል ድል ነሳሁ ፣ በሞቴ ሞትን ገደልኩ ፣ በመከራዬ ለመንግስቴ ህዝብን ማረኩኝ ሲል ተፈፀመ አለ እንጂ!

የአንጾኪያው ሊቀ ጳጳስ ቅዱስ ዲዮናስዮስ ተፈፀመ ብሎ ስለሞቱ ሲናገር "በሞቱ ሞትን ያጠፋው እርሱ ነው፡፡ ሲኦልንም የበዘበዘው እርሱ ነው" አለ።

የእስክንድርያው ሊቀ ጳጳስና ሐዋርያው የነበረው ቅዱስ አትናቴዎስ ስለዚህ ድንቅ ነገር በድርሳኑ ‹‹ነፍሱን ከሥጋው በለየ ጊዜ ያን ጊዜ በሲኦል ፈጥኖ ብርሃን ታየ፡፡ ጌታችን በአካለ ሥጋ ያይደለ በአካለ ነፍስ ወደ ሲኦል ሔደ፡፡ ሲኦል ተነዋወጠች፤ መሠረቶቿም እፈርስ እፈርስ አሉ፡፡ ምድርን ያለ ጊዜዋ እንዳታልፍ ክብርት ደሙን በምድር ላይ አፈሰሰ፡፡ ከኅልፈት ጠበቃት በእርሷ ያለውንም ዂሉ ጠበቀ፡፡ ስለ ፍጥረት ዂሉ ሥጋውን በመስቀል እንደ ተሰቀለ ተወው፡፡ ነፍሱ ግን ወደ ሲኦል ወረደች ከዚያ ተግዘው የነበሩ ነፍሳትን አዳነች፤ ሲኦልንም በዘበዘች፡፡ ፍጥረትንም ዂሉ ገንዘብ አደረገች፡፡ ሥጋውም በመቃብር ያሉ ሙታንን አስነሣ፤ ነፍሱም በሲኦል ተግዘው የነበሩ ነፍሳትን ፈታች፤›› እያለ ያወሳል።

በአማን ኢየሱስ ክርስቶስ ተፈፀመ ሲል አስቀድሞ የገባው የአድናችኋለሁ ተስፋ አርብ ተፈጸመ ፣ የሴቲቱ ዘር የእባቡን ራስ እንደሚቀጠቅጥ የተነገረው ተስፋ ተፈጸመ ፣ የኩነኔና የእርግማን ዘመን በሞቱ ተፈጸመ (ገላ 4፥4) ፣ የእግዚአብሔፍ ፍቅር በመስቀል ሞት ፍጹም ሆኖ በመገለጥ ተፈጸመ/ ተከናወነ/ ፣ እኛ እንጸድቅ ዘንድ የኃጢአት ቅጣት በመስቀል ላይ ተፈጸመ ፣ ወደ ሰማይ እየወጣ በአምላካችን ፊት ይከሰን የነበረው የዲያቢሎስ የክስ መብት በክርስቶስ ሞት ተፈጸመ። ዛሬ ይከሰን ዘንድ ወደ ሰማይ ቢወጣ በጌታ በኢየሱስ እጆች ላይ የሚታዩ ችንካሮችና በልብሱ ላይ የሚታየው የደም ነጠብጣብ አፉን ይዘጋዋል። በሰውና በእግዚአብሔር መካከል ገብቶ የነበረው ጥል በራሱ በጌታችን አስታራቂነት ለአንዴ ተፈጸመ። የሚሰሩትን አያውቁምና ይቅር በላቸው ማለቱ ለእንዴና ለዘላለም የእግዚአብሔርን ምህረት የምናስታውስበት ድምጽ ሆነ ። የበረታ ጌታ ሁላችንንም በቸርነቱ አዳነን እርሱ ተፈፀመ ሲል የኛ ደስታ ፣ የኛ መዳን ፣ የኛ ተስፋ ፣ የኛ መቤዠት በእግዚአብሔር ወልድ በተፈፀመልን የዘላለም ኪዳን ደም መፍሰስ በእውነት ተፈጸመ!!!

ለታረደው በግ ለእርሱ መጀመሪያ ከሌለው አባቱ ጋርና ቅዱስ፣ መልካምና ህይወት ሰጪ ከሆነው መንፈስ ቅዱስ ጋር ክብር ሁሉ ይገባዋል። አሁንና ለዘላለም ለትውልደ ትውልድ አሜን!

https://www.tg-me.com/ortodoxtewahedo
👍6
#ጌታችን በመስቀሉ ከ6-10 ሰዓት በመስቀልላይ ሳለ የተፈጸሙ 7ቱ
ተአምራቶች፤

1ኛ. ፀሐይ ጨለመች
2ኛ. ጨረቃ ደም ሆነች
3ኛ. ከዋክብት ብርሃናቸውን ነሱ
4ኛ. የቤተመቅደስ መጋረጃ ለሁለት ተከፈለ
5ኛ. ዐለቶች ተሰነጣጠቁ
6ኛ. መቃብራት ተከፈቱ
7ኛ. የሞቱት ተነሡ፤ ማቴ.27፤45-46

ጌታችን ከ6-9 ሰዓት በመስቀል ላይ ሳለ የተናገራቸው 7ቱ የፍቅር
ቃላት

1ኛ.ኤሎሄኤሎሄ ኤልማስላማሰበቅታኒ ማቴ.27፤46
2ኛ. እውነት እውነት እልሃለሁ ዛሬ በገነት ከእኔ ጋር ትኖራለህ፡፡
ሉቃ.23፤43
3ኛ.አባት ሆይ ነፍሴን በእጅህ አደራእሰጣለሁ፡፡ ሉቃ.23፤46
4ኛ.አባት ሆይየሚያደርጉትን አየውቁምናይቅር በላቸው፤ሉቃ.2334
5ኛ. እናትህ እነኋት፤ እነሆ ልጅሽ፤ዮሐ.19፤26-27
6ኛ. ተጠማሁ፤ ዮሐ.19፤30
7ኛ. ተፈጸመ፤ ዮሐ.19፤30

13ቱ ሕማማተ መስቀል

1ኛ. ተአስሮ ድኅሪት (ወደኋላ መታሰር)
2ኛ. ተስሕቦ በሐብል (በገመድ መሳብ)
3ኛ. ወዲቅ ውስተ ምድር (በምድር ላይመውደቅ)
4ኛ. ተከይዶ በእግረ አይሁድ (በእግረ አይሁድመረገጥ)
5ኛ. ተገፍዖ ማዕከለ ዓምድ (ከምሶሶ ጋርመላተም)
6ኛ. ተጽፍዖ መልታሕት (በጥፊ መመታት)
7ኛ. ተቀሰፎ ዘባን (ጀርባን በጅራፍ መገረፍ)
8ኛ. ተኰርዖተ ርእስ (ራስን በዱላ መመታት)
9ኛ. አክሊለ ሦክ (የሾህ አክሊል መድፋት)
10ኛ. ፀዊረ መስቀል (መስቀል መሸከም)
11ኛ. ተቀንዎ በቅንዎት (በችንካር መቸንከር)
12ኛ. ተሰቅሎ በዕፅ (በመስቀል ላይመሰቀል)
13ኛ. ሰሪበ ሐሞት (መራራ ሐሞትንመጠጣት)
ስብሐትለእግዚአብሔር
ወለወላዲቱድንግል
ወለመስቀሉክቡር


👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
https://www.tg-me.com/ortodoxtewahedo
👆👆👆👆👆👆👆👇👇👇
👍6😢3
#ሕማሙን ልናገር

#ሊቀ መዘምራን ይልማ ሀይሉ

ሕማሙን ልናገር *አንደበት ቢያጥሩኝም*/2/
መቼም ምንም ቋንቋ *ለዚህ አይገኝም*/2/
ከረጂሙ በጭር *ከሰፊው በጠባብ*/2/
ስለከፈለልኝ *ስለጌታ ላስብ*/2/
አዝ . . . . . . . . . . . //
በጌቴሴማኒ *በአታክልቱ ቦታ*/2/
ምድሪቷ ተሞልታ *በታላቅ ጸጥታ*/2/
የአዳምን ልጅ ስቃይ *በደሉን ሊሸከም*/2/
ጌታችን አዘነ *ተጨለቀ በጣም*/2/
ሐዋርያት ደክመው *ተኝተው ነበረ*/2/
ይሁዳ ከአይሁድ *እንደተማከረ*/2/
ጭፍሮች እየመራ *ጌታውን ሊያስገድል*/2/
የተሠራለትን *ቸርነት ሳይቆጥር*/2/
ፋና እያበሩ *ጭፍሮቹ ሲመጡ*/2/
ጌታን ሊያንገላቱት *እንደዚያ ሲቆጡ*/2/
የአምላኩን ጠላቶች *መንገድ እመራ* /2/
ይሁዳ ብቅ አለ *ከቀያፋ ጋራ* /2/
አዝ . . . . . . . . . . . //
ላቡ ከግንባሩ *እንደ ውኃ ሲወርድ*/2/
በታላቅ ይቅርታ *ጌታችን ሲራመድ*/2/
ምስኪኖችን ሊያጠግብ *ድሆችን ሊታደግ*/2/
ኢየሱስ ቀረበ *እንደሚታረድ በግ*/2/
ይሁዳ ጉንጮቹን *ሳመው በክህደት*/2/
የተማከረውን *የማያውቅ መስሎት*/2/
የአይሁድም ጭፍሮችም *ያዙት ተናጠቁት*/2/
በታላቅ ጭካኔ *በሰንሰለት መቱት*/2/
አዝ . . . . . . . . . . . //
በጲላጦስ ችሎት *አቁመው ከሰሱት*/2/
ንጹሑ እየሱስ *ይሙት በቃ አሉት*/2/
እጆቹን ቸንክረው *በጠንካራ ብረት*/2/
በእፀመስቀሉ *ቀራንዮ ዋለ*/2/
ወልደ እጓለዕመኅያው *ተጠማሁ እያለ*/2/
ሐሞት እና ከርቤ *ቀላቅለው አጠጡት*/2/
እረ እንዴት ጨከኑ *በምሬት ላይ ምሬት*/2/
------------------------------------------
ሕማሙን ልናገር አንደበት ቢያጥሩኝም
መቼም ምንም ቋንቋ ለዚህ አይገኝም
ከረጂሙ በጭር ከሰፊው በጠባብ
ስለከፈለልኝ ስለጌታ ላስብ
አዝ . . . . . . . . . . . //
ፍጥረታት ተጨንቀው በአይሁድ ክፋት
በየተፈጠሯቸው እርቃሉን ሸፈኑት
ጨረቃ ደም ሆነች ፀሐይም ጨለመች
አልፋና ኦሜጋ ተሰቅሎ ስላየች
ከዋክብት እረግፈው ምድር ተናወጠች
መባርቅትም ታዩ ተቆጣ ባሕሩ
መለሳቸው እንጂ ስለፈጹም ፍቅሩ/2/
ከወንበዴ ጋራ ከመሀል አድርገው
ጌታን አንገላቱት በመስቀል ላይ ሰቅለው
በቀኝ የነበረ ወንበዴው ለመነው
በመንግሥትህ ጌታ አስበኝ እያለው
አዝ . . . . . . . . . . . //
ከመስቀሉ በታች ዮሐንስን አየው
እስከመስቀል ድረስ ስለተከተለው
ታላቋን ስጦታ እናቱንም ሰጠው
ተፈፀመ አለ ጌታ ህይወቱን ሰጠ
ሞትንም ከሕዝቡ በፍጹም ቆረጠ/2/
አዝ . . . . . . . . . . . //
እንደተለመደው ዲያቢሎስ ቀረበ
ነፍሳትን ለመብላት እርሱ እንደተራበ
ፍጡር መስሎት ነበር በመስቀል ላይ ያለው
በአራቱም ማዕዝን በንፋስ ወጠረው
በሲኦል ወረደ በኃይሉ ብርሃን
ማረከ ጌታችን የአዳም ልጆችን
በሦስተኛውም ቀን ጌታችን ተነሳ
ሞትን ድል ያረገው የይሁዳ አንበሳ
በቃ ተወገደ የሰው ልጅ አበሳ /2/


#ሼር_share በማድረግ ለወዳጅ ዘመድዎ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ሥርዓት የጠበቁ ፅውፎች ለማንበብ ሆነ ለመማር፡፡

ለመቀላቀል

👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇

💠 http://www.tg-me.com/ortodoxtewahedo 💠
💠 http://www.tg-me.com/ortodoxtewahedo 💠
💠 http://www.tg-me.com/ortodoxtewahedo 💠


እግዚአብሔር ሃገራችንን እና ቤተክርስቲያናችንን ይጠብቅልን የእመቤታችን ምልጃና ጸሎት አይለየን ።
👍6💯1
#ጌታ ሆይ

#ሊቀ መ ዘምራን ኪነጥበብ
......
ጌታ ሆይ
አይሁድ አማፅያን ሰቀሉህ ሆይ
የአለም መድሐኒት የአለም ሲሳይ ሰቀሉህ ሆይ
የአለም መድሐኒት የአለም ሲሳይ ሰቀሉህ ሆይl
የአዳም በደል
አደረሰህ አንተን ለመገደል
የሔዋን ስህተት አበቃህ ለሞት ቸሩ አባት
የሔዋን ስህተት አበቃህ ለሞት ቸሩ አባት
......
ንፁህ ክርስቶስ
ሆንክ ወንጀለኛ ብለህ ስለኛ
መስቀል አሸክመው አስረው ገረፉህ እያዳፉህ
መስቀል አሸክመው አስረው ገረፉህ እያዳፉህ
ግብዞች
እንደራሳቸው መስሏቸው
ምራቅ እየተፉ በፊትህ ቀለዱ አንተን ሊጎዱ
ምራቅ እየተፉ በፊትህ ቀለዱ አንተን ሊጎዱ
......
እጅህና እግርህ
በችንካር ተመታ የአለም ጌታ
የሾህ አክሊል ደፋህ ጎንህን ተወጋህ አልፋ ኦሜጋ
የሾህ አክሊል ደፋህ ጎንህን ተወጋህ አልፋ ኦሜጋ
በመስቀል ላይ
ተጠማሁ ስትል ታላቅ በደል
ሀሞትና ከርቤ ሰጡህ ቀላቅለው ጠጣ ብለው
ሀሞትና ከርቤ ሰጡህ ቀላቅለው ጠጣ ብለው
......
ይቅር ባይ
ግልፅ በደላችን ሁሉን ሳታይ
አንተው ይቅር በለን በእኛው ሳትከፋ እንዳንጠፋ
አንተው ይቅር በለን በእኛው ሳትከፋ እንዳንጠፋ


👇👇👇👇👇
👉 https://www.tg-me.com/ortodoxtewahedo 👈
☝️☝️☝️☝️☝️☝️
👍31
#እውነት_ስለሆነ

#ሊቀ መ ዘምራን ይልማ ሀይሉ

እውነት ስለሆነ ኢየሱስ ክርስቶስ 
ዋለ ባደባባይ ሲሰደብ ሲከሰስ 
የሀሰት ዳኝነት አምላክን ወቀሰው 
ህይወት ሰጠን እንጂ ጥፋቱ ምንድነው/2/ 

ከቃሉ እብለትን ባያገኙበትም 
ዝምታውን አይተው አላዘኑለትም 
ባላወቁት መጠን ጠሉት ካለበደል 
ጥፋቱ ምን ይሆን የሚያደርስ ከመስቀል/2/ 

የልቡን ትህትና ፍቅሩን ሳያስተውሉ 
ቸሩ ጌታችንን አቻኩለው ሰቀሉ 
እሩህሩሁን ጌታ ቸንክረው ሰቀሉት 
ሞትን አስውግዶ ቢሰጣቸው ህይወት/2/ 

ስለ ቸርነቱ ስድብን ከፈሉት 
ስለ ርህራሄው የሾህ አክሊል ሰጡት 
ሀሞትና ከርቤ ሆምጣጤ ደባልቀው 
መራራ አስጎነጩት ጨክኖልባቸው/2/ 

ፈውስን ለሰጣቸው ልባቸውን ሞልተው 
አሉት ወንበዴ ነው ስቀለው ስቀለው 
ከጁ በረከትን የተሻሙ ሁሉ 
ይጮሁ ነበረ ይገደል እያሉ/2/

💚 https://www.tg-me.com/ortodoxtewahedo 💚
💛 https://www.tg-me.com/ortodoxtewahedo 💛
❤️ https://www.tg-me.com/ortodoxtewahedo ❤️
👍81
#አልፋና ኦሜጋ

አልፋና ኦሜጋ ፈጣሪ የሆንክ
በካሃዲዎች እጅ ተይዘህ ቀረብክ

ተገፋህ ተደፋህ በጥፊ ተመታህ
እየደበደቡ ክርስቶስ ሆይ አሉሀ
ጽድቅን ስለ ሠራህ በወንጌል ከሰሱህ
ለአዳም ልጅ ብለህ ብዙ ተንገላታህ
………አዝ…………..
ቅዱሳን እጆችህ የፍጥኝ ታስረው
እንደ በግ ተጎተትክ ልትመራቸው
የትም ቦታ ያለህ ሁሉን የምታውቅ
ፊትህን ሸፈኑህ ለመመጻደቅ
………አዝ…………..
በዓውደ ምኲናን ከጲላጦስ ፊት
አሳልፈው ሰጡህ አጋልጠው ለፍርድ
ከሐና ቀያፋ ከመሳፍንቱ ደጅ
ከሄሮድስም ዘንድ አቀረቡህ በዋጅ
………አዝ…………..
ግርፋት ሕማሙ አልበቃ ብሎህ
በመስቀል ላይ ልትውል ተፈረደብህ
ሳዶርና አላዶር ዳናትና አዴራ
ተፈልገው መጡ ለችንካር በተራ
………አዝ…………..
የሰላም ባለቤት ደረትህ ተወጋ
ሊያያዝ በችንካር እጅህ ተዘረጋ
ግፈኞች አሁዶች በአንተ ላይ ቀለዱ
ምራቅን ተፉብህ እራስህን ሊጎዱ፤

👇👇. 👇👇👇
👉 https://www.tg-me.com/ortodoxtewahedo👈
☝️☝️☝️☝️☝️☝️
👍31🤣1
ኦ አርምሞ ዘመጠነ ዝ አርምሞ ?
ኦ ትዕግስት ዘመጠነ ዝ ትዕግስት?
ኦ ሂሩት ዘመጠነ ዝ ሂሩት ?
ኦ ፍቅር ዘመጠነ ፍቅረ ሠብ ?
( ይህን ያህል ትዕግሥት እንደምን ያለ ትዕግሥት ነው ? ይህን ያህል ዝመታ እንደምን ያለ ዝመታ ነው ? ይህን ያህል ሰውን ማፍቀር እንደምን ያለ ፍቅር ነው ?

ለመቀላቀል

👉 @ortodoxtewahedo
15👍7
"አንዱ ስለ ሁሉ ሞተ"

2ኛ ቆሮ 5 : 4

@ortodoxtewahedo
35😢10👍7🕊4
Forwarded from ኦርቶዶክስ ተዋህዶን እንወቅ (💠 ✞ SAMI ✞ BREAVHEART💠)
#በስመአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!

#በሀገርም ውስጥ ሆነ ከሀገርም ውጭ ለምትኖሩ ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች በሙሉ *እንኳን ለብርሃነ ትንሣኤ በሰላም በጤና፤ በህይወትና በፍቅር አደረሳችሁ አደረሰን አሜን።


*በመስቀሉ ደም ሰላምን አደረገ በሰማያትም ላሉት እርቅን ሰላምን አደረገላቸው*
*( ቆላ፡ 1 ÷ 19 )*

*ለኃጢአት ሞትን ለፅድቅ እንድንኖር፡ እርሱ ራሱ በሥጋዉ ኃጢያታችንን በእንጨት ላይ ተሸከመ፣ በመገረፉ ቁስል ተፈወሳችሁ፣ እንደ በጎች ትቅበዘበዙ ነበረና፣ አሁን ግን ወደ ነፍሳችሁ እረኛና ጠባቂ ተመልሳችሃል*
(2ኛ ጴጥ 2÷24)

🌹 *እ* 🌹
🌹 *ን*🌹
🌹 *ኳ*🌹
🌹 *ን*🌹
🌹 *ለ*🌹
🌹 *ብ*🌹
🌹 *ረ*🌹
🌹 *ሃ*🌹
🌹 *ት*🌹
🌹 *ን*🌹
🌹 *ሣ*🌹
🌹 *ኤ*🌹
🌹 *ዉ*🌹
🌹 *ዋዘማ*🌹
🌹 *በ*🌹
*ሠ*
🌹 *ላ*🌹
🌹 *ም*🌹
🌹 *አ*🌹
🌹 *ደ*🌹
🌹 *ረ*🌹
🌹 *ሳ*🌹
🌹 *ች*🌹
🌹 *ሁ*🌹
🌹 *አ*🌹
🌹 *ደ* 🌹
🌹 *ረ*🌹
🌹 *ሰ*🌹
🌹 *ን*🌹
🌹 *በ*🌹
*ዓ*
🌹 *ሉ*🌹
🌹 *የ*🌹
🌹 *ሠ*🌹
🌹 *ላ*🌹
🌹 *ም*🌹
*የ*
🌹 *ደ*🌹
🌹 *ስ*🌹
🌹 *ታ*🌹
🌹 *የ*🌹
🌹 *መ*🌹
🌹 *ተ*🌹
🌹 *ሳ*🌹
*ሰ*
🌹 *ብ*🌹
🌹 *ና*🌹
🌹 *የ* 🌹
🌹 *በ*🌹
🌹 *ረ*🌹
🌹 *ከ*🌹
🌹 *ት*🌹
🌹 *በ*🌹
*ዓ*
🌹 *ል*🌹
🌹 *ይ*🌹
🌹 *ሁ*🌹
🌹 *ን*🌹
🌹 *ላ*🌹
🌹 *ች*🌹
*ሁ*
🌹 *ይ*🌹
🌹 *ሁ*🌹
🌹 *ን*🌹
🌹 *ል*🌹
🌹 *ን*🌹
🌹 *አ*🌹
🌹 *ሜ*🌹
🌹 *ን* 🌹
🌹፡፡🌹

*የመሰቀሉ ቃልለምጠፉት ሞኝነት ፣ ለእኛ ለምድን ግን የእግዚአብሔር ኃይል ነው ።
(1ኛ ቆሮ 1÷18)_*

*ከጌታችን ከኢየሱስ ክርስቶስ መስቀል በቀር ሌላ ትምክህት ከእኔ ይራቅ፡ ( ገላ ፮ ÷14 )*

❤️ወስብሐት ለእግዚአብሔር❤️
❤️ወለወላዲቱ ድንግል❤️
❤️ወለመስቀሉ ክቡር🕊

http://www.tg-me.com/ortodoxtewahedo
👍164🙏2👏1
Forwarded from ኦርቶዶክስ ተዋህዶን እንወቅ (💠 ✞ SAMI ✞ BREAVHEART💠)
"አሁን ግን ክርስቶስ ላንቀላፉት በኩራት ሆኖ ከሙታን ተነስቷል "

1ቆሮ 15÷20

#እንኳን ለጌታችን ለመድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የትንሣኤ በዓል በሠላምና ጤና አደረሳችሁ አደረሰን!

ክርስቶስ ተንሥአ እሙታን
በዓቢይ ኃይል ወሥልጣን
አሠሮ ለሰይጣን
አግዐዞ ለአዳም
ሰላም
እምይእዜሰ
ኮነ
ፍሥሐ ወሰላም
"እግዚአብሔር ከእንቅልፍ እንደሚነቃ ተነሣ"

መዝ 77÷65

#መልካም የትንሣኤ በዓል ይሁንላችሁ ።

http://www.tg-me.com/ortodoxtewahedo
👍4
Forwarded from ኦርቶዶክስ ተዋህዶን እንወቅ (💠 ✞ SAMI ✞ BREAVHEART💠)
የኦርቶዶክስ ተዋህዶን እንወቅ /OrtdooxTewahido/ አባላት በሙሉ::

እንኳን ለጌታችን ለመድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በዓለ ትንሣኤ አደረሰን አደረሳችሁ!!!



💐💐💐👉
ክርስቶስ ተንሥአ እሙታን
በዐቢይ ኃይል ወሥልጣን
አሠሮ ለሰይጣን
ዓግአዞ ለአዳም
ሰላም እም
ይእዜሰ
ኮነ
ፍስሐ ወሰላም!!!!!💐💐💐

http://www.tg-me.com/ortodoxtewahedo
🙏4👍1👏1
Forwarded from ኦርቶዶክስ ተዋህዶን እንወቅ (💠 ✞ SAMI ✞ BREAVHEART💠)
#እዩና እመኑ ሰዎች

እዩና እመኑ ሰዎች
ድንጋዮ ተፈቃቀወላል
ኢየሱስ በእኩለ ሌሊት
በኃይሉ ሞትን ድል ነስቷል(2)

እልልታ ለዚህ ይገባል
ግርግርታ ለዚህ ይገባል
የሞት ሀይል ተዋርዷል ዛሬ
ሲኦልም ተመሰቃቅሏል(2)

መላእክቱ ነጭ ለብሰው
ምስራቹን አበሰሩ
ተነስቷል ኢየሱስ ብለው
ለዓለም እንዲናገሩ(2)

እዩና እመኑ ሰዎች
ድንጋዮ ተፈነቃቅሏል
እየሱስ በእኩለለሊት
በሃይሉ ሞትን ድል ነስቷል(2)

እልልታ ለዚህ ይገባል
ግርግርታ ለዚህ ይገባል
የሞት ሀይል ተዋርዷል ዛሬ
ሲኦልም ተመሰነቃቅሏል(2)

#ለመቀላቀል #ከታች #ሠማያዊውን #ይጫኑ
👇👇 👇👇
http://t.meortodoxtewahedo
👍81👏1
እንኳን ለጌታችንና ለመድኃኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ የትንሣኤ በዓል በሰላም አደረሳችሁ፤

በክርስቶስ ትንሣኤ ያገኘነው ጸጋ ታላቅ ነው። ከጨለማ ወደ ብርሃን ወጥተናል÷ ከሞት ወደ ሕይወት ተሸጋግረናል ። ሙታን የነበርን ሕያዋን÷ ምድራውያን የነበርን ሰማያውያን÷ ሥጋውያን የነበርን መንፈሳውያን ሆነናል።


"ሞት ድል በመነሣት ተዋጠ ፡ ሞት ሆይ፥ መውጊያህ የት አለ? ሲኦል ሆይ፥ ድል መንሣትህ የት አለ? ፤ የሞት መውጊያ ኃጢአት ነው የኃጢአትም ኃይል ሕግ ነው፤" 1ኛ ቆሮ 15÷55



«እኛ አገራችን በሰማይ ነውና÷ ከዚያም ደግሞ የሚመጣ መድኃኒትን እርሱንም ጌታን ኢየሱስ ክርስቶስን እንጠ ባበቃለን፤ እርሱም ሁሉን እንኳ ለራሱ ሊያስገዛ እንደሚችልበት አሠራር ክቡር ሥጋውን እንዲመስል የተዋረደውን ሥጋች ንን ይለውጣል። » ፊል ፫፥ ፳-፳፩።


ናፍቆታችን ሁሉ በትንሣኤ ያገኘነውን ጸጋ እውን ማድረግ ነው።
«ድንኳን የሚሆነው ምድራዊው መኖሪያችን ቢፈርስ፥ በሰማይ ያለ በእጅ ያልተሠራ የዘላለም ቤት የሚሆን ከእግዚአብሔር የተሠራ ሕንጻ እንዳለን እናውቃለንና። በዚህ ውስጥ በእውነት እንቃትታለንና÷ ከሰማይም የሚሆነውን መኖሪያችንን እንድን ለብስ እንናፍቃለንና ለብሰን ራቁታችንን አንገኝም።» ይላል። ፪ኛቆሮ ፭፥፩-፪።



ሐዋርያው ቅዱስ ጴጥሮስም፡-
«ኢየሱስ ክርስቶስ ከሙታን በመነሣቱ ለሕያው ተስፋና ለማይጠፋ÷ እድፈትም ለሌለበት÷ ለማያልፍም ርስት እንደ ምሕረቱ ብዛት ሁለተኛ የወለደን የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ አባት ይባረክ» ብሏል። ፩ኛጴጥ ፩÷፫።


ቅዱስ ጳውሎስም፡-
«በሚመጡ ዘመ ናትም በክርስቶስ ኢየሱስ ለእኛ ባለው ቸርነት ከሁሉ የሚበልጠውን የጸጋውን ባለጠግነት ያሳ የን ዘንድ ከእርሱ ጋር አስነ ሣን፤ በክርስቶስ ኢየሱስም በሰማያዊው ስፍራ ከእርሱ ጋር አስቀመጠን።» ብሏል። ኤፌ፪÷፮-፯።



መልካም የትንሣኤ በዓል 😊

https://www.tg-me.com/ortodoxtewahedo
7👍4👏1🙏1
Forwarded from ኦርቶዶክሳዊ ቻናል
📍 ሕማማት 📍

📍በዲያቆን ሄኖክ ሃይሌ ተጽፎ በ ቢኒያም ብርሃኑ የተተረከውን ሕማማት የተሰኘውን መጽሐፍ በትረካ ለማግኘት
👇👇👇
1👍1
ወንድሜ ጓደኛህ ማነው?
እህቴ ጓደኛሽ ማናት?

እንደ አርማትያሱ ዮሴፍ ያለ ጓደኛ ካለህ/ሽ እንዳንተ/እንዳንቺ ያለ እድለኛ ሰው በዚህ ምድር የለም፤ ዮሴፍ ከሌሊቱ ተማሪ ኒቆዲሞስ ጋር ለኔ ላንተም ለዓለምም ሁሉ የተቆረሰውን ስጋ የፈሰሰውንም ደም የክርስቶስን አካል ከመስቀል ላይ እንወስድ ዘንድ ንጉሥ ጲላጦስን እንለምነው ብሎ እንደሄደ እናስብ እስኪ፤
እንዲወስዱ ከተፈቀደላቸውም በኋላ ገንዘው ዮሴፍ ለራሱ ባዘጋጀው አዲስ መቃብር እንደቀበሩት ወንጌል ይነግረናል፤

እንደ ዮሴፍ እንደ ኒቆዲሞስ ያለ ጓደኛ ያለህ እንደሆነ ዘወትር የሚያወራህ ነገር ይህን ነው...

ና እንሂድ ፤ ስለኛ ሲል የተቆረሰውን ስጋ እንውሰድ ፡ ስለኛ ሲል የፈሰሰውን ደም እንውሰድ ፤ ለእርሱ በሚሆን በአዲስ ልቦና በንስሐ ባነጻነው አካላችን ሰውነታችንም በልተነው ጠጥተነው የእኛ አካል እናድርገው፤....

በሦስተኛው ዕለት የመቃብሩ ስፍራ በብርሃን እንደተመላ ና እኛም መጠን ምሳሌና ልክ በሌላው በዚህ መለኮታዊ ብርሃን እንሞላ...

ጓደኛ ካሉ እንዲህ የሚል ነው...
ጓደኝነታችንን ለድኅነት ያድርግልን🙏

እንዲህ ያሉትን በእውነት ያብዛልን😊


በብርሃኑ እንድንመላለስ ለዚህች ዕለት ያደረሰን አምላካችን ይክበር ይመስገን🙏

መልካም የትንሣኤ በዓል፤

በዐለ ወልድ ቤተ ክርስቲያን
ሚያዚያ ፲፪ ፳፻፲፯ ዓ.ም
በዓለ ትንሣኤ ሌሊት ፮ ሰዓት

https://www.tg-me.com/ortodoxtewahedo
8👍3👏1
Forwarded from ኦርቶዶክሳዊ ቻናል
የ100 ብር ካርድ ሊለቀቅ ነው 9 ደቂቃ ብቻ ነው የቀራው። ቶሎ ከስር JOIN ሚለውን ነክታቹ JOIN REQUEST ላኩ 🏃‍♀️🏃‍♂️
2025/07/13 18:53:02
Back to Top
HTML Embed Code: