Telegram Web Link
Forwarded from ኦርቶዶክስ ተዋህዶን እንወቅ (💠 ✞ SAMI ✞ BREAVHEART💠)
💚💛❤️💚💛❤️💚💛💚

"ወሀቢተ ፀጋ በከንቱ "
ስጦታን እንዲሁ
የምትሰጪ አንቺ ነሽ

ለመቀላቀል 👉 @ortodoxtewahedo

💚💛❤️💚💛❤️💚💛❤️
Forwarded from ኦርቶዶክስ ተዋህዶን እንወቅ (💠 ✞ SAMI ✞ BREAVHEART💠)
#የምስካየ ኅዙናን መድኃኔ ዓለም ገዳም ታሪክ

#ታቦተ መድኃኔ ዓለም

የመድኃኔ ዓለም ጽላት በ፲፰፻፺፭ዓ.ም. በግርማዊ ዳግማዊ ዐፄ ምኒልክና በእቴጌ ጣይቱ ትእዛዝ በመምህር ፈቀደ እግዚእ አማካኝነት ወደ ኢየሩሳሌም ተወስዶ በዴር ሡልጣን (የንጉሥ ገዳም) ውስጥ ለ፴፬ ዓመታት ሲጸለይበት ቆይቷል፡፡ንጉሠ ነገሥት ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ፋሺስት ኢጣሊያ ኢትዮጵያን በወረረ ጊዜ በስደት እንዳሉ ልመናቸውን እና ጸሎታቸውን የሚያቀርቡበት አንድ ጽላት የሚያስፈልጋቸው መሆኑን ስለአመኑበት ወደ ኢየሩሳሌም ለዕጨጌ ገብረ ጊዮርጊስ (በኋላ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ባስልዮስ) በጥር ፲፫/፲፱፻፳፱ ዓ.ም. “…አንድ ጽላትና አምስት መነኵሳት የሚያስፈልገውን ይዞ እንዲመጣ አባ ሐናን ልኬዋለሁና ከመምህር ገሪማ ጋር ተማክራችሁ ዐቢይ ጾም ሳይገባ እንዲደርስ አድርጋችሁ እንድትልኩልን ይሁን” ብለው በላኩላቸው በስደት በሀገረ እንግሊዝ የሚገኙ ንጉሣውያን ቤተሰቦች እና ለሌሎች ምእመናን ለሥርዓተ አምልኮ መፈጸሚያ ከአምስት ልዑካን ጋር ፲፱፻፳፱ ዓ.ም. ለንደን ሄዶ እስከ ፲፱፻፴፫ ዓ.ም. በእንግሊዝ ሀገር ቆይቷል፡፡

የመድኀኔ ዓለም ታቦት በነሐሴ ፳፫ ቀን ፲፱፻፴፫ ዓ.ም. ግርማዊት እቴጌ መነን ዐዲስ አበባ በገቡበት ቀን አባ ኃይሌ ቡሩክ የተባሉት መነኵሴ ይዘውት ገብተዋል፡፡ ታቦቱም በቤተ መንግሥት የተለየ ቦታ ተደርጎለት በአባ ኃይሌ ቡሩክ ጠባቂነትና አጣኝነት ከቆየ በኋላ ሚያዚያ ፳፯ ቀን ፲፱፻፴፭ ዓ.ም. ደግሞ ቀድሞ ቤተ ሳይዳ ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ሆስፒታል በዛሬው የካቲት ፲፪ ሆስፒታል ቅጥር ግቢ ውስጥ ምስካየ ኅዙናን በመባል ተሰይሞ ተተክሎ ነበር፡፡

የምስካየ ኅዙናን መድኀኔዓለም ገዳም መነኵሳት በኅብረት /የአንድነት ኑሮ/ ለመኖር በመስማማታቸው በግንቦት ፲፮ ቀን በ፲፱፻፴፯ ዓ.ም. በዕጨጌ ገብረ ጊዮርጊስ /በኋላ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ባስልዮስ/ እና መምህራን ሊቃውንት በተገኙበት በቀድሞው ሥፍራ በቅዳሴ ተከብሯል፡፡

ታቦቱ ዐዲስ አበባ ከገባ ከሰባት ዓመታት በኋላ የምስካየ ኅዙናን መድኃኔ ዓለም ገዳም ዐዲስ ሕንጻ ቤተ ክርስቲያን ለመሥራት በሚያዚያ ፳፯ ቀን ፲፱፻፵ ዓ.ም. በንጉሠ ነገሥት ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ የመሠረት ድንጋዩ ተጣለ፡፡ የተጣለውም በተፈሪ መኮንን ት/ቤት ክበብ ውስጥ ነው:: በዚህ ሥፍራም እንዲሠራ የሆነበት ምክንያት ለተፈሪ መኮንን (ወንድ ተማሪዎች) እና ለእቴጌ መነን(ሴት ተማሪዎች) ተማሪዎች ሲባል እንደሆነ ንጉሠ ነገሥት ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ የመሠረት ድንጋይ ሲያኖሩ " ... ይህን መሠረት ስንመሠርት በዚህ ... ወጣቶች የኦርቶዶክሳዊት ሃይማኖታቸውን ሥርዓት እንዲጠብቁበት ሥርዓተ ጸሎትና ሥርዓተ ቁርባን በመፈጸም እንዲጠቀሙበት አስበን ነው። ... ፍሬውንም ለማየት ተስፋችን እርሱ ምስካየ ኅዙናን መድኃኔ ዓለም ነው።" ብለው ባደረጉት ንግግር ገልጸዋል፡፡

የሕንጻ ቤተ ክርስቲያኑ ሥራ ተጠናቅቆ በ፲፱፻፵፪ ዓ.ም. ሚያዚያ ፳፯ ቀን ግርማዊ ንጉሠ ነገሥት ቀ.ኃ.ሥ. ግርማዊት እቴጌ መነን እና ሌሎቹም በተገኙበት ቅዳሴ ቤቱ ተከብሯል፡፡

በዚህ ወቅት ሥርዐተ ቅዳሴውን ያካሄዱት ልዑካን፤ ሠራኤ ካህን፡- ብፁዕ አቡነ ባስልዮስ የሸዋ ጳጳስ፣ ተራዳኢ ካህን፡- ብፁዕ አቡነ ጢሞቴዎስ የሲዳሞ ጳጳስ፣ ሠራኢ ዲያቆን፡- አባ ተክለ ማርያም (ኹለተኛ አስተዳዳሪ የነበሩት)፣ ተራዳኢ ዲያቆን፡- አባ ሐና ጅማ (የመጀመሪያ አስተዳዳሪ)፣ አባ ኃ/ኢየሱስ፣ አባ ገ/ሚካኤል ነበሩ፡፡

የገዳሙ ልዩ አስተዳደራዊ መዋቅር፡-
ገዳሙ የሚተዳደረው ቀጥታ በቅዱስነታቸው ትእዛዝ ነው፡፡ በሊቀ ጳጳስ የሚመራ አስተዳዳር ቦርድ አለው፡፡ የገዳሙ መምህር (አስተዳዳሪ) የሚመሩት የአስተዳደር ጉባኤ አለው፡፡ ከዚሁም ጋር መጋቢ፣ ቄሰ ገበዝ እና ሊቀ ዲያቆናት የየራሳቸው ሐላፊነት አላቸው፡፡

የመጀመሪያውም አስተዳዳሪ አባ ሐና ጅማ ሆነው በ፲፱፻፶፫ ዓ.ም. ግርግር እስከ ተገደሉበት ቀን ድረስ እንደሚገባ አገልግለዋል፡፡

ስያሜው እና ልዩ ሥርዐቱ
ከቤተ ሳይዳ ጀምሮ የገዳሙ ስያሜ ምስካየ ኅዙናን ማለት ያዘኑ መጠጊያ ማለት ነው፡፡ ይኽም ከላይ እንዳየነው የኢትዮጵያን እንባ አብሶሷልና ያዘኑ ምእመናን እየመጡ እንባቸው እንዲታበስ በማመን የተሰየመ ስም ነው፡፡

ልዩ ሥርዓቱ በስሙ ትርጓሜ መሠረት ቤተ ክርስቲያኑ ከበሮ የማይመታበት ጸናጽልም የማይሰማበት ነገር ግን ሥርዓተ ቅዳሴ የሚቀደስበት፣
የሰዓታት ጸሎት፣ የኪዳን ጸሎት፣ የሠርክ ጸሎት የንስሐ መዝሙር የሚቀርብበት የኅዙናን መጠጊያ ነው፡፡

የገዳሙ መምህራን
ከክቡር አባ ሐና ጅማ እስከ አሁኑ መምህር ክቡር መልአከ ገነት አባ ገ/ሥላሴ ይርሳው /ቆሞስ/ ድረስ ሃያ ሁለት አበው ገዳሙን አስተዳድረውታል፡፡
ያዘኑ ሁሉ መጠጊያ እና መጽናኛቸው የሆነ መድኃኔ ዓለም ከሀዘን ከመከራ ሀገራችንን ኢትዮጵያን ይጠብቅ።ለዓለሙም ሁሉ መዳኛውን ይስጥ።

#ወስብሐት ለእግዚአብሔር!!


#ለመቀላቀል

@ortodoxtewahedo

#ለሃሳብ አስተያየት

@ortodoxtewahedoo
Forwarded from ኦርቶዶክስ ተዋህዶን እንወቅ (💠 ✞ SAMI ✞ BREAVHEART💠)
#አባ አጋቶንና አታላይ አጥማቂዎች

" በዘመኑም ሰይጣን ያደረበት ሰው ተገለጠ። ብዙ ወገኖችንም አሳታቸው። እርሱ በቤተ ክርስቲያን ውስጥ የሚቀመጥ ሆኖ ትምህርቱን የሚሰሙ ሕዝቦች የእንጨት ቅርንጫፎችን በመያዝ በዙሪያው ይቀመጣሉ። አባ አጋቶንም ልኮ ወደ እርሱ አስመጣው። በላዩም ጸለየና በሰውየው ላይ አድሮ ለሰዎች በመናገር የሚያስተውን ሰይጣን ከእርሱ አስወጣው።

እንዲሁም ሰማዕት ሚናስ ያነጋግረኛል የምትል ሴት ተነሥታ በቅዱስ ሚናስ ስም የውኃ ጉድጓድ እንዲቆፍሩ በጠበሉ ውኃ ተጠምቀው ከደዌያቸው እንዲፈወሱ የአገርዋን ሰዎች አዘዘቻቸው። ያቺንም ሴት ወደ እርሱ አስመጥቶ በላይዋ ጸለየ፤ ርኩስ መንፈስንም ከእርሷ አስወጣው። የዚያችንም ሀገር ሰዎች ለጠበል ብላ ያስቆፈረችውን ጉድጓድ እንዲደፍኑት አዘዛቸው።

ዳግመኛም ሌላ ሰው ተነሣ። እርሱም ጋኔን ይዞ ያሳበዳቸውን ሰበሰባቸው። ሲደበድባቸውም ለጥቂት ጊዜ ጋኔኑን ያስተዋቸዋል። ብዙዎችም ጋኔን የያዛቸው ወደ እርሱ ተሰበሰቡ። ቅዱስ አባ አጋቶንም ወደ እርሱ እንዲመጣ ወደ ሰውየው ላከ። ሰውየውም ትእዛዙን ሰምቶ አልመጣም። የስሕተት ሥራውንም አልተወም። የዚያችም አገር ገዢ ሲያልፍ የሰበሰባቸው እብዶች ሰደቡት፣ ረገሙትም። ስለዚህ ያን ሰው መኮንኑ ይዞ ጽኑ ሥቃይን አሰቃየውና በሥቃዩ ውስጥ ሞተ።"
/ስንክሳር ፣ መስከረም ፲፬/

ዛሬም በእኛ ዘመን የምናያቸው ከላይ ከተገለጹት ከሦስቱ ታሪኮች በምንም አይለዩም። ዛሬ ማርያም ፣ አርሴማ አዛኛለች ፣ ጽላት አስቆፍሬ አወጣለሁ የሚሉ እንዳሉ ሁሉ ያን ጊዜም ሚናስ ሰማዕት አናግሮኛል የምትል ጠበል ያስቆፈረች ነበረች።
በኃይል እፈውሳለሁ እያለ ለጊዜው የሚያስታግስ አጋንንትን የሚያስለፈልፍ ሰውን የሚያሰድብ የሚያጣላ ዛሬ እንዳለው ሁሉ ያኔም ነበረ። ገዳም ቤተ ክርስቲያን ሆኖ የሚናገርና እንደ በቃ ቅዱስ የሚታይ ሰው ድሮም ነበረ፣ ዛሬም አለም።

አሁን ልዩነቱ እንደ አባ አጋቶን ያለ ጻድቅ ተገልጦ በአሳቾቹ ላይ ያደረውን ሰይጣን አስወጥቶ አጥማቂ ነን ቅዱሳን ያናግሩናል የሚሉትን ስሑታን እስከ ተከታዮቻቸው የሚያድን ስውር ቅዱስ ብቻ ነው።

የአባ አጋቶን በረከት ይደርብን፣ እርሱን የመሰሉትን አስነሥቶም ስተው የሚያስቱትን ይፈውስልን።

ዲ/ን ብርሃኑ አድማስ

#ወስብሐት ለእግዚአብሔር!!


#ለመቀላቀል

@ortodoxtewahedo

#ለሃሳብ አስተያየት

@ortodoxtewahedoo
"ገዳማት ወደ ቀደመ ክብራቸው እንዲመለሱ ገዳማውያኑ እና ሁላችንም ኃላፊነት አለብን!"፡-ብፁዕ አቡነ አብርሃም

ሥርዐተ መነኮሳት ለግብረ ትሩፋት በሚል መሪ ቃል የምክክር መርሐ ግብር ጠቅላይ ቤተ ክህነት የገዳማት መምሪያ አዘጋጅነት ለ3 ተከታታተይ ቀናት የሚቆይ መካሄድ መጀመሩ ተገልጿል፡፡

በጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽርሐ ተዋሕዶ በዛሬው ዕለት በጀመረው የምክክር በጉባኤው ከመላው ኢትዮጵያ የመጡ ገዳማውያን ተሳታፊዎች ሆነዋል፡፡

በመርሐ ግብሩ ብፁዕ አቡነ አብርሃም የጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ፣የባሕርዳር እና የሰሜን ጎጃም አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ተገኝተዋል፡፡

ብፁዕነታቸው በጉባኤው ላይ ባደረጉት ንግግር የኢትዮጵያ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ገዳማት ወደ ቀደመ ክብራቸው እንዲመለሱ ገዳማውያኑ እንዲሁም ሁላችንም ኃላፊነት አለብን ያሉ ሲሆን ለእንግዶችም የእንኳን ደኅና መጣችሁ መልክት አስተላልፈዋል፡፡

አክለውም ከዛሬ ጀምሮ በሚቀጥሉት ተከታታይ ቀናት ለቤተ ክርስቲያን የሚጠቅሙ ሐሳቦች በገዳማውያኑ በኩል እንደሚነሳ ተስፋ አደርጋለው ሲሉ ተናግረዋል።

በተጀመረው ጉባኤ ላይ "ምንኩስና ከአኃት አብያተ ክርስቲያናት አንጻር" በሚል ርእሰ ሊቃውንት በአባ ገብረ ኪዳን በመቅረብ ላይ ሲሆን በቀሪ ቀናት ውስጥ የተለያዩ ጽሑፎች ቀርበው ውይይት እንደሚደረግባቸው የሚጠበቅ ይሆናል፡፡


ለመቀላቀል 👉 @ortodoxtewahedo
💚💛❤️ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ💚💛❤️

🏹ከየአቅጣጫው የምትገፋ
🏹ከየአቅጣጫው የሚሴርባት
🏹ከየአቅጣጫው የምትሰደብ
🏹ከየአቅጣጫው የምትንገላታ

👉ነገር ግን

👉ከየአቅጣጫው ትክክል የሆነች
👉ከየአቅጣጫው እንከን የማይወጣላት
👉ከየአቅጣጫው ውበቷ የበዛ
👉ቅድስት ርትዕት ንፅህት ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ !!!

ኦርቶዶክስ ያደረከኝ አምላክ ክብርና ምስጋና፥ አምልኮትና ውዳሴ ላንተ ይሁን
አሜን

"ቤተ ክርስትያንን ከማጥፋት ፀሀይን ማጨለም ይቀላል ::"

ቅዱስ ዩሀንስ አፈወርቅ

@ortodoxtewahedo
#እንኩዋን ለእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ዓመታዊ የልደት በዓል በሰላም አደረሳችሁ

+*" #ልደታ ለማርያም ድንግል "*+

#ኢያቄም ወሐና ወለዱ ለነ ሰማየ:
ሰማዮሙኒ አስረቀት ለነ ፀሐየ::

" ኢያቄምና ሐና ሰማይን ወለዱልን:
ሰማያቸው ደግሞ ፀሐይን አወጣችልን (ወለደች-አስገኘችልን) "

=>የዓለማችን ወላጆች ነቢያት ሐዋርያትን: ጻድቃን ሰማዕታትን ወልደው ከብረዋል: ተመስግነዋል:: ኢያቄምና ሐና ግን ፍጥረት ሁሉ በአንድነት ቢሰበሰብ በእግሯ የረገጠችውን ትቢያ እንኩዋ መሆን የማይችል: የሰማይና የምድር ንግሥት: የእግዚአብሔርን እናት: እመቤታችን ማርያምን ወለዱልን::

+ኢያቄም ወሐና ለእግዚአብሔር የሥጋዌ አያቶቹም ተባሉ:: እስኪያረጁ ድረስ በመካንነት አዝነው ፀልየዋል:: ንጽሕናቸውና ደግነታቸው ተመስክሮላቸው ድንግል ማርያምን አግኝተዋል::

+እመቤታችን ከአዳም ስሕተት በሁዋላ ያለ ጥንተ አብሶ የተወለደች የመጀመሪያዋ ሰው ድንግል ማርያም ሆናለች:: (ኢሳ. 1:9)

+ለጨለማው ዓለም የብርሃን መቅረዝ ሆና ትጠቅመን ዘንድ: አንድም ትንቢቱና ምሳሌው ይፈጸም ዘንድ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም በዚህ ቀን: በሊባኖስ ተራራ ከ2,022 ዓመታት በፊት ተወልዳለች::

"ሙሽራዬ ሆይ! ከሊባኖስ ከእኔ ጋር ነይ" (መኃልይ. 4:8)

=>ከነገደ ይሁዳ የሚወለድ ቅዱስ ኢያቄም የሚባል ደግ ሰው ከነገደ ሌዊ (አሮን) የተወለደች ሐና የምትባል ደግ ሴት አግብቶ: በሕጉ ጸንተው: በሥርዓቱ ተጠብቀው ይኖሩ ነበር:: ነገር ግን በዘመኑ ሰዎች ልጅ የላችሁም በሚል ይናቁ ነበር::

+ኦሪታውያን ልጅ የሌለውን "ኅጡአ በረከት-ከጸጋ እግዚአብሔር የራቀ" ነው ብለው ያምኑ ነበር:: ኢያቄምና ሐና ልጅ እንዲሰጣቸው ሲያዝኑ: ሲጸልዩ ዘመናቸው አልፎ አረጁ::
እነሱ ግን የሚያመልኩት የአብርሃምና ሣራን አምላክ ነውና ተስፋ አልቆረጡም::

+የለመኑትን የማይነሳ ጌታ በስተእርጅናቸው ድንቅ ነገርን አደረገላቸው:: አንድ ቀን እርግቦች ከጫጩቶቻቸው ጋር ሲጫወቱ የተመለከተች ቅድስት ሐና ፈጽማ አለቀሰች:: "እንስሳትና አራዊትን: እጽዋትን ሳይቀር በተፈጥሯቸው እንዲያፈሩ የምታደርግ አምላክ ምነው ሐናን ድንጋይ አድርገህ ፈጥረሃታልን?" ብላ አዘነች::

+ይህን የተመለከተ ቅዱስ ኢያቄም ወደ ተራራ ወጥቶ ሱባኤ ያዘ:: ለ40 ቀናትም ሲጸልይና ሲማለል ቆየ:: በ40ኛው ቀን 2ቱም ሕልምን ያልማሉ:: እርሱ:- ነጭ ርግብ ሰማያትን ሰንጥቃ ወርዳ: በሐና ቀኝ ጀሮ ገብታ: በማሕጸኗ ስትደርስ አየ::

+እርሷ ደግሞ:- የኢያቄም በትር አብቦ: አፍርቶ: ጣፋጭ ፍሬውን ሰው ሁሉ ሲመገበው ታያለች:: ቅዱስ ኢያቄም ከሱባኤ እንደ ተመለሰ ያዩትን ተጨዋውተው "ፈቃደ እግዚአብሔር ይሁን" አሉ:: ለ7 ቀናትም በጋራ እግዚአብሔርን ሲለምኑ ሰነበቱ::

+በ7ኛው ቀን (ማለትም ነሐሴ 7) መልአከ ብሥራት ቅዱስ ገብርኤል ክንፉን እያማታ ወደ እነርሱ ወረደ:: "ዓለም የሚድንባት: የፍጥረት ሁሉ መመኪያ የሆነች ልጅ ትወልዳላችሁ" ብሏቸው ተሠወራቸው:: እነርሱም ደስ ብሏቸው እግዚአብሔርን አመሰገኑ::

+እንደ ሥርዓቱም አብረው አድረው እመ ብርሃን ተጸነሰች::
"ኦ ድንግል አኮ በፍትወተ ደነስ ዘተጸነስኪ . . .
ድንግል ሆይ! ኃጢአት ባለበት ሥጋዊ ፍትወት የተጸነስሽ አይደለም" እንዳለ ሊቁ:: (ቅዳሴ ማርያም)

+"ለጽንሰትኪ በከርሥ: እንበለ አበሳ ወርኩስ: ወለልደትኪ እማሕጸን ቅዱስ . . ."
"ድንግል ሆይ! መጸነስሽ ያለ በደል (ያለ ጥፋት) ነው: የተወለድሽበት ማሕጸንም ቅዱስ ነው . . ." (መጽሐፈ ሰዓታት, ኢሳ. 1:9)

+እመቤታችን ነሐሴ 7 ቀን ተጸንሳ ግንቦት አንድ ቀን ተወልዳለች::

=>የእመቤታችን የዘር ሐረግ:-
*አዳም-ኖኅ-አብርሃም-ይስሐቅ-ያዕቆብ=
*በእናቷ:-
-ሌዊ-ቀዓት-እንበረም-አሮን-ቴክታና በጥሪቃ-ሔኤሜን-ዴርዴን-ቶና-ሲካር-ሔርሜላና ማጣት-ሐና::
*በአባቷ በኩል:-
-ይሁዳ-ፋሬስ-ሰልሞን-ቦኤዝ-እሴይ-ዳዊት-ሰሎሞን-ሕዝቅያስ-ዘሩባቤል-አልዓዛር-ቅስራ-ኢያቄም ይሆናል::

+ለጨለማው ዓለም የብርሃን መቅረዝ ሆና ትጠቅመን ዘንድ: አንድም ትንቢቱና ምሳሌው ይፈጸም ዘንድ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም: በሊባኖስ ተራራ ከ2,026 ዓመታት በፊት ተወልዳለች::

=>የእመቤታችን ድንግል ማርያም ጣዕሟ: ፍቅሯ: ጸጋዋና በረከቷ ይደርብን::

=>ግንቦት 1 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት=
1.እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም (ልደታ)
2.ቅዱሳን ኢያቄም ወሐና
3.ቴክታና በጥሪቃ
4.አባ ሕርያቆስ ዘሃገረ ብሕንሳ (የእመቤታችንን ቅዳሴ የደረሰበት)

=>ወርኀዊ በዓላት
1.ቅዱስ ራጉኤል ሊቀ መላዕክት
2.ቅዱስ በርተሎሜዎስ ሐዋርያ
3.ቅዱስ ሚልኪ ትሩፈ ምግባር

=>+"+ መሠረቶቿ በተቀደሱ ተራሮች ናቸው::
ከያዕቆብ ድንኩዋኖች ይልቅ እግዚአብሔር የጽዮንን ደጆች ይወዳቸዋል::
የእግዚአብሔር ከተማ ሆይ! በአንቺ የተደረገው ድንቅ ነው . . .
ሰው እናታችን ጽዮን ይላል::
በውስጧም ሰው ተወለደ::
እርሱም ራሱ ልዑል መሠረታት:: +"+ (መዝ. 86:1-6)

<< ወስብሐት ለእግዚአብሔር >>

#አቤቱ ህዝብህን አድን ርስትህንም ባርክ ጌታ ሆይ ማራቸው
ከፍ ከፍ አድርጋቸው/2/

#ወስብሐት ለእግዚአብሔር!!

#ለመቀላቀል

@ortodoxtewahedo

#ለሃሳብ አስተያየት

@ortodoxtewahedoo.
#ልደታ_ለማርያም

“ኦ ድንግል አኮ በፍትወተ ደነስ ዘተፀነስኪ አላ በሩካቤ ዘበሕግ እምሐና ወኢያቄም ተወለድኪ”
"ድንግል ሆይ በኃጢአት ፍትወት የተፀነስሽ አይደለም ፤ በሕግ በሆነ ሩካቤ ከሐና ከኢያቄም ተወለድሽ እንጂ።"

#አባ ሕርያቆስ በቅዳሴው


ምሥራቀ ምሥራቃት ሙፃአ ፀሐይ እግዝእትነ ዘመና ሙዳይ፤
ተወልደት ዮም ዳግሚት ሰማይ፡፡
#እንኲን አምላክን እናት ለሆነች ለቃልኪዳንዋ እመቤት ለእመቤቴቻን ለቅድስት ድንግል
#ማርያም_ክብረ_በዓልና_አደ ረሳቹ::.

#አቤቱ ህዝብህን አድን ርስትህንም ባርክ ጌታ ሆይ ማራቸው
ከፍ ከፍ አድርጋቸው/2/

#ወስብሐት ለእግዚአብሔር!!

#ለመቀላቀል

@ortodoxtewahedo

#ለሃሳብ አስተያየት

@ortodoxtewahedoo.
በኢያቄም በአባትሽ ወገን የንጉሥ ልጅ ሆይ አመሰግንሻለሁ፡፡ የዳዊት ልጅ ነሽና የሊቀ ካህናት ልጅ ሆይ ውዳሴሽን አቀርባለሁ፡፡ ከእናትሽ ወገን የአሮን ልጅ ነሽና፡፡

ገናንነትሽንም አደንቃለሁ፡፡ የነገድሽን ወገን አመሰግናለሁ ከቤተ መንግሥትና ከቤተ ክህነት ተገኝተሻልና፡፡

ስለዚሀም የነጎድጓድ ልጅ ነሽ እልሻለሁ ያዕቆብና ዮሐንስን አኔሬጌስ ብሎ እንደጠራቸው ይኸው የነጎድጓድ ልጆች ማለት ነው፡፡ ከቤተ መንግሥትና ከቤተ ክህነት ናቸውና፡፡
ስለዚህም የነጎድጓድ ልጆች ተባሉ፡፡

እኔም የነጎድጓድ ልጅ ነሽ አልሁሽ፡፡ የመወለድሽ ድምፅ (ወሬ) እንደ ነጎድጓድ ድምፅ ይሰማልና፡፡

ከሁለቱ ከተቀቡት ነገድ በነቢያት አለቃ በሙሴ እጅ ለክህነት ከተቀባው ከአሮን ቤት፡፡ በሳሙኤል እጅ ለመንግስት ከተቀባው ከዳዊት ዘር፡፡ (፩ ሳሙ ፲፮፣ ፲፫) (ዘሌዋ ፰፣ ፲፪)

ደግሞም ያንበሶች ልጅ ነሽ እልሻለሁ እንደ አንበሳ ግልገል ጩኸት እንደ ሴትም አንበሳ ድምፅ የልደትሽ ወሬ ይሰማልና፡፡ አባቱ ያዕቆብ ይሁዳን ያንበሳ ግልገል ብሎታልና፡፡ (ዘፍጥ ፵፣ ፱፣ ፱)

ስለዚህም ያንበሶች ልጅ እልሻለሁ፡፡ ሰሎሞን እንደተናገረ እንዲህ ሲል አንቺ ሙሽራ ከሊባኖስ ጋራ ነይ ከሊባኖስ ጋራ ነይ፡፡ ከአንበሶችም ጉድጓድ ወጥተሽ ነይ፡፡ (መሐ፣ ፬፣ ፰)

ከተመረጠ ነገዱ የተነሣ ከሚመካ ወገን የመወለድሽ ወሬ እጅግ ግሩም ነው፡፡

አርጋኖን ዘሠሉስ

@ortodoxtewahedo
ማርያም ...ናቡከደኖፆሮች ጋር የማይስማማ ስም
***

ዘማዊቷ ማርያም የአልባስጥሮስ ሽቱን በክርስቶስ እግር ላይ አፍስሳ ምስጢረ ንሰኅን ስለፈጸመች ብቻ .....

“ ይህ ወንጌል በዓለም ሁሉ በማናቸውም ስፍራ በሚሰበክበት እርስዋ ያደረገችው ደግሞ ለእርስዋ መታሰቢያ እንዲሆን ይነገራል። ማቴ 26፥13" ....

የተባለው ቃል ላይ አምፆ ዘማዊቷ ሴትን ማክበር ክርስቶስን ይሸፍናል የሚል ኃይል ከዬትም አቅጣጫ አታገኝም።
***

ስለመጥምቁ ዮሐንስ መወለድን በተመለከተ ቅዱሱ መጽሐፍ ...

..."በመወለዱም ብዙዎች ደስ ይላቸዋል። ሉቃ1፥14" ....ብሎ ሲያውጅ "ደስታችን ክርስቶስ እንጅ ዮሐንስ አይደለም" ብሎ አመጽ የሚወጣ አትመለከትም።

***

አብርሐም ኬጣውያን ሣራን የሚቀበርበትን የቀብር ቦታ መስጠታቸውን እንደውለታ ቆጥሮ ለህዝቡ ሲሰግድላቸው //ዘፍ 23፥7//፤......ያዕቆብ ለታላቁ ኤሳው እየወደቀ እየተነሳ ሰባት ጊዜ እየሰገደ ሲያከብረው //ዘፍ 33፥3//......፤ሙሴ ለአማቱ ሲሰግድ// ዘጸ 18፥7//፤......ናቡከደነጾር ለዳንኤል በግንባሩ ተደፍቶ በፍርሃት ሲሰግድ //ዳን 2፥46//..... ስግደት ለእግዚአብሔር ብቻ ነው ብሎ እኝህ ታሪክ የተፃፉትን የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍል ልሰርዝ የሚል አመጸኛም አታገኝም።
***

ጸጋ ሰጭ እና ነሽ ፤ልመናን ከልካይ እና አጽዳቂ እግዚአብሔር ሆኖ ሳለ ኤልሳ ኤልያስን .....“ መንፈስህ በእኔ ላይ ሁለት እጥፍ ይሆን ዘንድ እለምንሃለሁ...2ኛ ነገ 2፥9" .....ብሎ ሲማጸነው ..."ቀጥታ ወደ እግዚአብሔር ለምናለው እንጅ በመሃል ሰው አላስገባም " ብሎ የሚቃወም የለም።

***

ሳሙኤል በዕረፍተ ሥጋ ከተገታ |ሞተ| በኃላ.... “ እግዚአብሔርም መንግሥትህን ከእጅህ ነጥቆ ለጎረቤትህ ለዳዊት ሰጥቶታል። 1ኛ ሳሙ 28፥17" ....ብሎ በምድር ሳለ ያደርግ የነበረውን የነብይነት አገልግሎት ሞትም እንኳን እንደፈጸመ መጽሐፍ ቅዱስ ምስክር ሆኖ ሲናገር .... "ቅዱሳን ከሞቱ በኃላ ምንም አያውቅም ብሎ" የሚከራከር ሰው አታገኝም።

***

ነገር ግን ስለድንግል ማርያም ስትናገር.....ጩኸት እና እሪታ ይቀልጣል። ስታከብራት ዳስ ጥለው ለቅሶ ይቀመጣሉ። በታወረ ልቦና ጥቅስ ፍለጋ አይን ያባክናሉ።

ስታከብራት ጋረደች፣ስትወዳት አመለካት፣ስትሰግድላት ስግደት ለጌታ ብቻ፣ስትማጸናት ሞታለች አትሰማም ብለው ከላይ የተደረጉ ኩነቶችን ሁሉ ይዘነጋሉ።

እውነት ነው ዘማዊቷ ማርያም በንሰኃ ከዲያቢሎስን ወጥመድ አምልጣለች። አብርሃም ከካራን ነጻ ወጥቷል። ሳሙኤልም በአገልግሎት ድል ነስቷል። ዳዊትም ልባም ሆኖ ሰለሞንም ጥበብ ተጎናጽፎ ከብሯል።
***

ማርያም ግን ....ሲዖል የተበረበረበትን ዲያቢሎስን የሞተበትን የመውጊያ ጦር የሆነ ወንድ ልጅ ተገልጦባታል።

እርሷ መድኃኒት የተጠቀለለበት የሞት ገዳይ ምክንያት ሴት ሆናለች።....

ማርያም....ስሟን ውደዱ እንጅ እየተከተላችሁ አታልቅሱ

Kune Demelash kassaye -Arba Minch
#ርዕሰ ባሕታዊ (ስለ ቅዱስ ገብረ መንፈስ ቅዱስ)

በ ቃልና በኑሮህ ሆነሀል ምስክር
እንደ ፀሐይ አበራህ በእግዚአብሔር አገር
ሰማያዊ ነህ እንጂ አይደለህም ምድራዊ
ገብረመንፈስ ርዕሰ ባሕታዊ

አዝ======

በስምሙ ለሚያምኑት አማላጅ ሆነሀል
በፀሎትህም ኃይል ተማምነንብሃል
የክብር ኮከብ ነህ የገዳም መብራት
አስተምረኸኛል ምግባር ሃይማኖት

አዝ======

የሚያልፈውን አለም የምድሩን ንቀሀል
የታመንከው አምላክ ህያው አድርጎሃል
በሥጋ በነፍስህ እግዚአብሔር ከበረ
የማስታረቅን ቃል በአንተ ላይ አኖረ

አዝ======

በተጋድሎህ ብዛት በፆም በፀሎት
ትተጋ ነበረ በፀናች እምነት
ስለ ቃል ኪዳንህ በረከት ይወርዳል
ያንተ ስም ሲጠራ አጋንንት ይርዳል

አዝ======

ገብረመንፈስ ቅዱስ የእምነት አባት
አናብርት አናብስት የታዘዙለት
ከንሂሳ ተነስቶ ኢትዮጲያ ደረሰ
ፀጋው በረከቱ በእኛ ላይ ፈሰሰ

መዝሙር
በሊቀ መዘምራን ቴድሮስ ዮሴፍ

#አቤቱ ህዝብህን አድን ርስትህንም ባርክ ጌታ ሆይ ማራቸው
ከፍ ከፍ አድርጋቸው/2/

#ወስብሐት ለእግዚአብሔር!!

#ለመቀላቀል

@ortodoxtewahedo

#ለሃሳብ አስተያየት

@ortodoxtewahedoo
#መዝሙረ ዳዊት

#Psalms 102፡(103)።

#የዳዊት፡መዝሙር።

1፤ነፍሴ፡ሆይ፥እግዚአብሔርን፡ባርኪ፥ዐጥንቶቼም፡ዅሉ፥የተቀደሰ፡ስሙን።

2፤ነፍሴ፡ሆይ፥እግዚአብሔርን፡ባርኪ፥ምስጋናውንም፡ዅሉ፡አትርሺ፤

3፤ኀጢአትሽን፡ዅሉ፡ይቅር፡የሚል ፥ደዌሽንም፡ዅሉ፡የሚፈውስ፥?

4፤ሕይወትሽን፡ከጥፋት፡የሚያድናት ፥በምሕረቱና፡በቸርነቱ፡የሚከልልሽ፥

5፤ምኞትሽን፡ከበረከቱ፡የሚያጠግባት ፥ጕልማሳነትሽን፡እንደ፡ንስር፡ያድሳል።

6፤እግዚአብሔር፡ይቅርታ፡አድራጊ፡ነው፤ለተበደሉ፡ዅሉ፡ይፈርዳል።

7፤ለሙሴ፡መንገዱን፡አስታወቀ ፥ለእስራኤል፡ልጆችም፡አደራረጉን።

8፤እግዚአብሔር፡መሓሪና፡ይቅር፡ባይ፡ነው፥ከቍጣ፡የራቀ፡ምሕረቱም፡የበዛ።

9፤ዅልጊዜም፡አይቀሥፍም ፥ለዘለዓለምም፡አይቈጣም።

10፤እንደ፡ኀጢአታችን፡አላደረገብንም ፥እንደ፡በደላችንም፡አልከፈለንም።

#ይህ ቻናል የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ ዶግማንና ቀኖናን ትውፊትን እንዲሁም አስተምሮን የጠበቁ የተለያዩ የሚያስተምሩ ነገሮች ይለቀቁበታል ፡፡ የእናንተ አስተያየት ያበረታናልና አስተያየታችሁ! ይለግሱን ።


📖📖📖📖📖📖📖📖📖

‹‹ከትውልዱ ማን አስተዋለ›› ት.ኢሳ 58÷3

#Facebook "አርቶዶክስ ተዋህዶን እንወቅ" በሚለው search በማድረግ #LIKE or #Follow አድርግው ከ17600 በላይ #like አለው ይቀላቀሉን በተጨማሪ #በቴሌግራም ለመቀላቀል

👇👇👇👇👇👇👇👇

@ortodoxtewahedo

ከ17200 በላይ አባል አለው
#የእናንተ አስተያየት ያበረታናልና አስተያየታችሁን በ @BREAVHEARTT ላይ ይለግሱን !

#ኦርቶዶክሳውያንን #share በማድረግ ይጋብዙ።
2025/07/04 21:25:53
Back to Top
HTML Embed Code: