"፻፴፪ኛው መደበኛ የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ ከነገ ጀምሮ ይካሄዳል።
ግንቦት ፭/፳፻፲፯ ዓ/ም የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሚዲያ
፻፴፪ ኛው መደበኛ የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ ከነገ ጀምሮ ይካሄዳል።
በየዓመቱ ትንሣኤ በዋለ 25ኛ ቀን የሚካሔደው ርክበ ካህናት የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ ዛሬ ከሰዓት በኋላ በብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ፓትርያርክ መሪነት የመክፈቻ ሥርዓተ ጸሎቱ ይከናወናል።
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሥርዓትና ትውፊት መሠረት የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ በዓመት ሁለት ጊዜ ይካሔዳል።
በየዓመቱ የሚካሔዱት ሁለቱ ጉባኤያት አንደኛ ቋሚ በሆነ ቀን በጥቅምት 12 ሲጀምር ሁለተኛው ግን የአጽዋማቱን አዋጅ ተከትሎ በሚወጣው የባሕረ ሐሳብ ቀመር መሠረት በዓለ ትንሣኤ በዋለ 25ኛ ቀን የርክበ ካህናት ጉባኤ ይከናወናል።
በዚህ በ2017 ዓ/ም ርክበ ካህናት የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ ነገ ግንቦት 6/2017 ዓ/ም የሚጀምር ሲሆን በዋዜማው ዛሬ ከሰዓት በኋላ በቅዱስ ፓትርያርኩ መሪነት ሥርዓተ ጸሎቱ ይከናወናል።
የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ የፕትርክና መንበሩ ከግብፁ ወደ ኢትዮጵያ ከመጣበት ከሰኔ 21/1951 ዓ/ም ወዲህ አስቸኳይ ጉባኤያትን ሳይጨምር ከ131 መደበኛ የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤያት መካሔዳቸውን ታሪክ ያስረዳል።
ከነዚህ መደበኛ የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ በቅዱሳን ፓትርያርኮች ጥረት ርእሰ መንበርነት የተመሩ ሲሆን በሁለት የተለያዩ ዓመታት ግን የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ ፓትርያርክ ባለመኖሩ ምክንያት በአቃብያነ መንበር በብፁዓን አባቶች ተመርተዋል።
ከእነዚህ አንደኛው ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ቴዎፍሎስ ፓትርያርክ በወቅቱ በነበረው አገዛዝ ምክንያት በግፍ ለግዞት ስለተዳረጉ ግንቦት 11 ቀን 1968 ዓ/ም የዋለውን ርክበ ካህናት የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ አቃቤ መንበር በነበሩት በብፁዕ አቡነ ዮሐንስ የመላ ትግራይ ሊቀ ጳጳስ ርእሰ መንበርነት ተመርቷል።
ሁለተኛው ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ጳውሎስ 5ኛው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ፓትርያርክ ነሐሴ 10/2004 ዓ/ም ከዚህ ዓለም በማረፋቸው ምክንያት የጥቅምቱ 12/2005 ዓ/ም የቅዱስ ሲኖደስ ምልዓተ ጉባኤን የወቅቱ አቃቤ መንበር የነበሩት ብፁዕ አቡነ ናትናኤል የአርሲ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በርእሰ መንበርነት መርተዋል።
የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ በቤተ ክርስቲያን ታላላቅ ጉዳዮች ውሳኔ የሚሰጥበት ሲሆን እምነት የማጽናት ሥርዓትን ማስጠበቅ አስፈላጊ ከሆነም መሻሻል ያለባቸውን ጉዳዮች የማሻሻል ሥልጣን ያለው የቤተ ክርስቲያን የበላይ አካል ነው።
“በገዛ ደሙ የዋጃትን የእግዚአብሔርን ቤተ ክርስቲያን ትጠብቁአት ዘንድ መንፈስ ቅዱስ እናንተን ጳጳሳት አድርጎ ለሾመባት ለመንጋው ሁሉና ለራሳችሁ ተጠንቀቁ።”
ሐዋርያት ፳፥፳፰
🔵የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሚዲያ
ስለ አንዲት ኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያን
✝✝✝✝✝✝✝✝✝
ክርስቶስ ተንሥአ እሙታን
በዐቢይ ኃይል ወሥልጣን
አሰሮ ለሰይጣን
አግዐዞ ለአዳም
ሰላም
እምይእዜሰ
ኮነ
ፍሥሓ ወሰላም
#ወስብሐት ለእግዚአብሔር!!
#ለመቀላቀል
@ortodoxtewahedo
#ለሃሳብ አስተያየት
@ortodoxtewahedoo
ግንቦት ፭/፳፻፲፯ ዓ/ም የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሚዲያ
፻፴፪ ኛው መደበኛ የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ ከነገ ጀምሮ ይካሄዳል።
በየዓመቱ ትንሣኤ በዋለ 25ኛ ቀን የሚካሔደው ርክበ ካህናት የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ ዛሬ ከሰዓት በኋላ በብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ፓትርያርክ መሪነት የመክፈቻ ሥርዓተ ጸሎቱ ይከናወናል።
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሥርዓትና ትውፊት መሠረት የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ በዓመት ሁለት ጊዜ ይካሔዳል።
በየዓመቱ የሚካሔዱት ሁለቱ ጉባኤያት አንደኛ ቋሚ በሆነ ቀን በጥቅምት 12 ሲጀምር ሁለተኛው ግን የአጽዋማቱን አዋጅ ተከትሎ በሚወጣው የባሕረ ሐሳብ ቀመር መሠረት በዓለ ትንሣኤ በዋለ 25ኛ ቀን የርክበ ካህናት ጉባኤ ይከናወናል።
በዚህ በ2017 ዓ/ም ርክበ ካህናት የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ ነገ ግንቦት 6/2017 ዓ/ም የሚጀምር ሲሆን በዋዜማው ዛሬ ከሰዓት በኋላ በቅዱስ ፓትርያርኩ መሪነት ሥርዓተ ጸሎቱ ይከናወናል።
የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ የፕትርክና መንበሩ ከግብፁ ወደ ኢትዮጵያ ከመጣበት ከሰኔ 21/1951 ዓ/ም ወዲህ አስቸኳይ ጉባኤያትን ሳይጨምር ከ131 መደበኛ የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤያት መካሔዳቸውን ታሪክ ያስረዳል።
ከነዚህ መደበኛ የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ በቅዱሳን ፓትርያርኮች ጥረት ርእሰ መንበርነት የተመሩ ሲሆን በሁለት የተለያዩ ዓመታት ግን የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ ፓትርያርክ ባለመኖሩ ምክንያት በአቃብያነ መንበር በብፁዓን አባቶች ተመርተዋል።
ከእነዚህ አንደኛው ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ቴዎፍሎስ ፓትርያርክ በወቅቱ በነበረው አገዛዝ ምክንያት በግፍ ለግዞት ስለተዳረጉ ግንቦት 11 ቀን 1968 ዓ/ም የዋለውን ርክበ ካህናት የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ አቃቤ መንበር በነበሩት በብፁዕ አቡነ ዮሐንስ የመላ ትግራይ ሊቀ ጳጳስ ርእሰ መንበርነት ተመርቷል።
ሁለተኛው ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ጳውሎስ 5ኛው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ፓትርያርክ ነሐሴ 10/2004 ዓ/ም ከዚህ ዓለም በማረፋቸው ምክንያት የጥቅምቱ 12/2005 ዓ/ም የቅዱስ ሲኖደስ ምልዓተ ጉባኤን የወቅቱ አቃቤ መንበር የነበሩት ብፁዕ አቡነ ናትናኤል የአርሲ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በርእሰ መንበርነት መርተዋል።
የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ በቤተ ክርስቲያን ታላላቅ ጉዳዮች ውሳኔ የሚሰጥበት ሲሆን እምነት የማጽናት ሥርዓትን ማስጠበቅ አስፈላጊ ከሆነም መሻሻል ያለባቸውን ጉዳዮች የማሻሻል ሥልጣን ያለው የቤተ ክርስቲያን የበላይ አካል ነው።
“በገዛ ደሙ የዋጃትን የእግዚአብሔርን ቤተ ክርስቲያን ትጠብቁአት ዘንድ መንፈስ ቅዱስ እናንተን ጳጳሳት አድርጎ ለሾመባት ለመንጋው ሁሉና ለራሳችሁ ተጠንቀቁ።”
ሐዋርያት ፳፥፳፰
🔵የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሚዲያ
ስለ አንዲት ኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያን
✝✝✝✝✝✝✝✝✝
ክርስቶስ ተንሥአ እሙታን
በዐቢይ ኃይል ወሥልጣን
አሰሮ ለሰይጣን
አግዐዞ ለአዳም
ሰላም
እምይእዜሰ
ኮነ
ፍሥሓ ወሰላም
#ወስብሐት ለእግዚአብሔር!!
#ለመቀላቀል
@ortodoxtewahedo
#ለሃሳብ አስተያየት
@ortodoxtewahedoo
" ኢትዮጵያን ወደ ተሻለ ልማትና ዕድገት እናሻግራለን ብላችሁ እየደከማችሁ ያላችሁ ወገኖቻችን እባካችሁ መለስ ብላችሁ እናታችሁ የተንገላታችበትን እዩና በቃ በሉ፤ሁሉን የሚያግባባ ነገር ፈልጉና ችግሮችን በሰላማዊ ውይይት ፍቱ፤ በዚህ ኣማራጭ እናት ሀገር እፎይታ እንድታገኝ ኣድርጉ፤ ይህንም ለውድ እናት የሚደረግ ካሣ ኣድርጋችሁ ውሰዱት።"
ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ
መልእክተ ቅዱስ ፓትርያርክ
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ ኣሜን!
ብፁዕ አቡነ አብርሃም
የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽ/ቤት ዋና ስራ አስኪያጅ፣ የባሕር ዳርና የሰሜን ጎጃም አህጉረ ስብከት ሊቀ ጰጳስ፣
ብፁዕ አቡነ ሄኖክ
የአዲስ አበባ ሃገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፤
ብፁዓን ኣበው ሊቃነ ጳጰሳት የቅዱስ ሲኖዶስ ኣባላት!!
እንደዚሁም በዚህ ቀኖናዊና ዓመታዊ የርክበ ካህናት የቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ ላይ የተገኛችሁ በሙሉ፤ ጸጋንና ሓዋርያነትን ያጐናጸፈን ጌታችን ኣምላካችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ቅድስት ትንሣኤውን በሰላም ኣክብረን ይህንን ዓመታዊውን የቅዱስ ሲኖዶስ ጉባኤ ለማካሄድ ስለ ሰበሰበን ክብርና ምስጋና ለእርሱ ይሁን፤ የጉባኤው ኣባላት የሆናችሁ ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳትም እንኳን ለረክበ ካህናት ጉባኤ ኣደረሳችሁ! እንኳንም በሰላም መጣችሁ!
“ረከብነ ጸጋ ወተሰየምነ ሓዋርያተ ከመ ናስምዖሙ ለኣሕዛብ ወይእመኑ በስሙ፡- ከእምነት የሚነሣ መታዘዝ እንዲገኝ ጸጋንና ሓዋርያነትን ተቀበልን” (ሮሜ.፩÷፭)፤
ይህ ሐዋርያዊ ኣስተምህሮ የኛን ተእልኮና ተልእኮው ያስፈለገበትን ምክንያት ኣጉልቶ ያሳያል፤ የተቀበልነው ስጦታም ምን ያህል ታላቅ እንደ ሆነ ምንባቡ ያስረዳል፤ ሓዋርያው በዚህ መልእክት የቅዱስ ወንጌል ኣስተምህሮ ዋና ግብ ከእምነት የሚነሣ መታዘዝ እንዲገኝ ማድረግ ነው በማለት ያስተምረናል፤ እውነት ነው ድሮውኑም ቢሆን ለእግዚኣብሔር መታዘዝ ኣቅቶን ነው የወደቅነው፤ ዛሬም የምንነሣው ከእምነት የተነሣ መታዘዝን ገንዘብ ስናደርግ ነው፤ ከሁሉ በፊት እምነት ይቀድማል፤ ከሱ በኋላ ደግሞ ለእምነቱ በሙሉ ልብ መታዘዝ ይከተላል፤ ይህ ሲሆን መዳንና ትንሣኤ ይገኛል፤ ዓለም በእግዚአብሔር እየተደረገላት ያለ ጥሪ ይኸው የመታዘዝ ጥሪ ነው፤
ይህንን መለኮታዊ ጥሪ ለዓለም የማድረስ ኃላፊነትም ለኛ ለቅዱስ ሲኖዶስ ኣባላት የተሰጠ እንደሆነ ሐዋርያው አስገንዝቦኣል፤ ኃላፊነቱ ሲሰጠን ከነመሳርያው ነው፤ እሱም ጸጋና ሓዋርያነት ነው፤ እኛም እሱን ተቀብለናል፤ እንግዲያውስ የተቀበልነውን ጸጋና ሓዋርያነት በዓለም ውስጥ ላለው ሕዝበ እግዚአብሔር ኣገልግሎት ማዋል ከኛ ይጠበቃል፡፡
ብፁዓን ሊቃነ ጳጰሳት የቅዱስ ሲኖዶስ ኣበላት!!
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ በአሁኑ ጊዜ የሌለበት ክፍለ ዓለም የለም፤ ምክንያቱም የዚህ ሲኖዶስ ወኪሎች ሊቃነ ጳጳሳት በኣፍሪካ፣ በኣውሮፓ፣ በሰሜን ኣሜሪካ፣ በላቲን ኣሜሪካ፣ በካናዳና በመካከለኛው ምሥራቅ፣ በእስያና በኣውስትራሊያ ወዘተ የሚገኙ ሕዝበ እግዚአብሔር ምእመናንን በማገልገል ላይ ይገኛሉና ነው፤ ይህ ዕድል የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ መለኮታዊ ተልኮውን በአጽናፈ ዓለም ሁሉ ለማድረስ ምቹ መደላድል ፈጥሮለታል፡፡ከዚህም በመነሣት በየክፍለ ዓለሙ የሚገኙ የቤተ ክርስቲያናችን ሊቃነ ጳጳሳት ከትውልደ ኢትዮጵያውያን ባሻገር የየአካባቢውን ሕዝብ በማስተማርና በማቀፍ የተጣለባችሁን ሓዋርያዊ ተልእኮ በትጋትና በንቃት መወጣት ይኖርባችኋል፡፡
በማእከል ሆኖ እየመራ የሚገኝ ቅዱስ ሲኖዶስም ለዚህ ተልእኮ ምቹ መደላድል የመፍጠር ኃላፊነቱን በኣግባቡ መወጣት ይገባዋል፡፡ በተለይም ትምህርተ ሃይማኖትንና ቀኖና ቤተ ክርስቲያንን የተማሩና በጥልቀት የተገነዘቡ፣ ብስለትም ያላቸው፤ እንዲሁም በቋንቋና በሥነ ልቦና ዕውቀት የላቀ ሀብተ ጸጋ ያላቸውን በሐዋርያነት እያሠለጠነ በአጽናፈ ዓለም ሁሉ ሊያሰማራ ይገባል፡፡
ብፁዓን ሊቃነ ጳጰሳት የቅዱስ ሲኖዶስ ኣበላት!
በብሂለ አበው (ፀሐይ ለመስኮቷ ሳታበራ…) እንደሚባለው ለሌላው በብቃት መድረስ እንችል ዘንድ እኛ የቅዱስ ሲኖዶስ አባላት የሲኖዶሱ መንበር በሚገኝባት ምድረ ኢትዮጵያ ከመቸውም የተሻለ ስራ በመስራት ለእግዚአብሔር መታዘዝ ሕዝቡንም ማገልገል ይገባናል፤ ሁላችንም እንደ ምንገነዘበው በሲኖዶሳችን ያልታቀፉ ብዙ ወገኖች በሀገር ውስጥ ኣሉን፤ እነዚህ ወገኖች አንዳንዶቹ በተለያየ ምክንያት ከኛ የወጡ ናቸው፡፡ ይሁን እንጂ የሄዱት ወደ ቤታቸው እንዲመለሱ፣ ሌሎችም ወደ መንጋው እንዲቀላቀሉ በርትቶ መስራት የዚህ ጉባኤ ተቀዳሚ ተልእኮ ነው፤ ምክንያቱም ጸጋንና ሐዋርያነትን የተቀበልንበት ዋናው ምክንያት ይህንን ለማድረግ ነውና፡፡ ከዚህ አኳያ የቤተ ክርስቲያናችን ተደራሽነት በሳሳበት ኣካባቢ ሁሉ የተለየ ትኵረት ሰጥተን መስራትና ተጨባጭ ለውጥ ማምጣት ይኖርብናል፤
ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት የቅዱስ ሲኖዶስ ኣባላት!
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ውሉደ ክህነትና ምእመናን የሆን ሁላችን፣ ከሁሉ በፊት ያለንን ዓቅምና ብቃት በኣግባቡ መገንዘብ ይኖርብናል፤ ለእግዚአብሔር ክብርና ምስጋና ይሁንና ለፈጣሪው በቈራጥነት የሚታዘዝ ምእመን፣ ወጣት፣ ካህን ኣለን፤ ይህ ትልቅ ጸጋ ነው፤ ይህንን ጸጋ እግዚአብሔር፡ ለእግዚአብሔር መንግሥት በሚመች ሁናቴ ዝቅ ብሎ ማገልገል የክብር ክብር ነው፡፡ በመሆኑም ይህንን የእግዚአብሔር ሕዝብ በሓቅ፣ በቅንነት፣ በትጋትና በታማኝነት ቆመን ካገለገልነውና ኣባትነታችንንና መሪነታችንን በመልካም አሰራር በትክክል በኅሊናው እንዲቀረጽ ካደረግን፣ ይህ ኃይል ከጐናችን እንደማይለይ እርግጠኞች መሆን እንችላለን፤ ይህንን ካሳካን ለኛ የተሰጠ ኃይልና ብቃት በየትም ኣይገኝም፡፡
በዚህም በዚያም ሃይማኖቱ የሚጠይቀውን ሰብእና እና ቁመና ይዘን ከተገኘን፣ ሕዝበ ክርስቲያኑ ያለውን ብቻ ሳይሆን ሕይወቱን ሳይቀር ለመስጠት ወደ ኋላ የማይል የእግዚአብሔር ሕዝብ ኣለን፤ ስለዚህ ይህንን ማሳካት እንችል ዘንድ ከእምነት የሚነሣ መታዘዝ እንድናስገኝ የተቀበልነውን ጸጋና ሐዋርያነት በክብር እንያዝ፤
ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት የቅዱስ ሲኖዶስ ኣባላት!!
ለሕዝበ እግዚአብሔር የምናበረክተው ኣገልግሎት በመንፈሳዊ ብቻ ሳይሆን በኢኮኖሚውና በማኅበራዊው ኣገልግሎትም ጭምር ነው፤ ከዚህ ኣንጻር ሕዝባችን የተሻለ ማኅበራዊ ኣገልግሎት እንዲያገኝ፣ በኢኮኖሚውም ከድህነት የተላቀቀ እንዲሆን፤ እንደዚሁም ሰላሙና ኣንድነቱ የተጠበቀ እንዲሆን፣ በማስተማርም በተግባር በመሳተፍም የሕዝቡ መሪዎችና ኣርኣያ ሆነን መስራት ይገባናል፤በተለይም ከሰላም እጦት የተነሣ በእጅጉ እየተጎዳ ያለውን ሕዝባችን ሰላምና ፍትሕ እንዲያገኝ በጸሎትም በትምህርትም፣ በምክርም ተግተን መስራት ኣለብን፤
#ወስብሐት ለእግዚአብሔር!!
#ለመቀላቀል
@ortodoxtewahedo
#ለሃሳብ አስተያየት
@ortodoxtewahedoo
ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ
መልእክተ ቅዱስ ፓትርያርክ
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ ኣሜን!
ብፁዕ አቡነ አብርሃም
የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽ/ቤት ዋና ስራ አስኪያጅ፣ የባሕር ዳርና የሰሜን ጎጃም አህጉረ ስብከት ሊቀ ጰጳስ፣
ብፁዕ አቡነ ሄኖክ
የአዲስ አበባ ሃገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፤
ብፁዓን ኣበው ሊቃነ ጳጰሳት የቅዱስ ሲኖዶስ ኣባላት!!
እንደዚሁም በዚህ ቀኖናዊና ዓመታዊ የርክበ ካህናት የቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ ላይ የተገኛችሁ በሙሉ፤ ጸጋንና ሓዋርያነትን ያጐናጸፈን ጌታችን ኣምላካችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ቅድስት ትንሣኤውን በሰላም ኣክብረን ይህንን ዓመታዊውን የቅዱስ ሲኖዶስ ጉባኤ ለማካሄድ ስለ ሰበሰበን ክብርና ምስጋና ለእርሱ ይሁን፤ የጉባኤው ኣባላት የሆናችሁ ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳትም እንኳን ለረክበ ካህናት ጉባኤ ኣደረሳችሁ! እንኳንም በሰላም መጣችሁ!
“ረከብነ ጸጋ ወተሰየምነ ሓዋርያተ ከመ ናስምዖሙ ለኣሕዛብ ወይእመኑ በስሙ፡- ከእምነት የሚነሣ መታዘዝ እንዲገኝ ጸጋንና ሓዋርያነትን ተቀበልን” (ሮሜ.፩÷፭)፤
ይህ ሐዋርያዊ ኣስተምህሮ የኛን ተእልኮና ተልእኮው ያስፈለገበትን ምክንያት ኣጉልቶ ያሳያል፤ የተቀበልነው ስጦታም ምን ያህል ታላቅ እንደ ሆነ ምንባቡ ያስረዳል፤ ሓዋርያው በዚህ መልእክት የቅዱስ ወንጌል ኣስተምህሮ ዋና ግብ ከእምነት የሚነሣ መታዘዝ እንዲገኝ ማድረግ ነው በማለት ያስተምረናል፤ እውነት ነው ድሮውኑም ቢሆን ለእግዚኣብሔር መታዘዝ ኣቅቶን ነው የወደቅነው፤ ዛሬም የምንነሣው ከእምነት የተነሣ መታዘዝን ገንዘብ ስናደርግ ነው፤ ከሁሉ በፊት እምነት ይቀድማል፤ ከሱ በኋላ ደግሞ ለእምነቱ በሙሉ ልብ መታዘዝ ይከተላል፤ ይህ ሲሆን መዳንና ትንሣኤ ይገኛል፤ ዓለም በእግዚአብሔር እየተደረገላት ያለ ጥሪ ይኸው የመታዘዝ ጥሪ ነው፤
ይህንን መለኮታዊ ጥሪ ለዓለም የማድረስ ኃላፊነትም ለኛ ለቅዱስ ሲኖዶስ ኣባላት የተሰጠ እንደሆነ ሐዋርያው አስገንዝቦኣል፤ ኃላፊነቱ ሲሰጠን ከነመሳርያው ነው፤ እሱም ጸጋና ሓዋርያነት ነው፤ እኛም እሱን ተቀብለናል፤ እንግዲያውስ የተቀበልነውን ጸጋና ሓዋርያነት በዓለም ውስጥ ላለው ሕዝበ እግዚአብሔር ኣገልግሎት ማዋል ከኛ ይጠበቃል፡፡
ብፁዓን ሊቃነ ጳጰሳት የቅዱስ ሲኖዶስ ኣበላት!!
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ በአሁኑ ጊዜ የሌለበት ክፍለ ዓለም የለም፤ ምክንያቱም የዚህ ሲኖዶስ ወኪሎች ሊቃነ ጳጳሳት በኣፍሪካ፣ በኣውሮፓ፣ በሰሜን ኣሜሪካ፣ በላቲን ኣሜሪካ፣ በካናዳና በመካከለኛው ምሥራቅ፣ በእስያና በኣውስትራሊያ ወዘተ የሚገኙ ሕዝበ እግዚአብሔር ምእመናንን በማገልገል ላይ ይገኛሉና ነው፤ ይህ ዕድል የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ መለኮታዊ ተልኮውን በአጽናፈ ዓለም ሁሉ ለማድረስ ምቹ መደላድል ፈጥሮለታል፡፡ከዚህም በመነሣት በየክፍለ ዓለሙ የሚገኙ የቤተ ክርስቲያናችን ሊቃነ ጳጳሳት ከትውልደ ኢትዮጵያውያን ባሻገር የየአካባቢውን ሕዝብ በማስተማርና በማቀፍ የተጣለባችሁን ሓዋርያዊ ተልእኮ በትጋትና በንቃት መወጣት ይኖርባችኋል፡፡
በማእከል ሆኖ እየመራ የሚገኝ ቅዱስ ሲኖዶስም ለዚህ ተልእኮ ምቹ መደላድል የመፍጠር ኃላፊነቱን በኣግባቡ መወጣት ይገባዋል፡፡ በተለይም ትምህርተ ሃይማኖትንና ቀኖና ቤተ ክርስቲያንን የተማሩና በጥልቀት የተገነዘቡ፣ ብስለትም ያላቸው፤ እንዲሁም በቋንቋና በሥነ ልቦና ዕውቀት የላቀ ሀብተ ጸጋ ያላቸውን በሐዋርያነት እያሠለጠነ በአጽናፈ ዓለም ሁሉ ሊያሰማራ ይገባል፡፡
ብፁዓን ሊቃነ ጳጰሳት የቅዱስ ሲኖዶስ ኣበላት!
በብሂለ አበው (ፀሐይ ለመስኮቷ ሳታበራ…) እንደሚባለው ለሌላው በብቃት መድረስ እንችል ዘንድ እኛ የቅዱስ ሲኖዶስ አባላት የሲኖዶሱ መንበር በሚገኝባት ምድረ ኢትዮጵያ ከመቸውም የተሻለ ስራ በመስራት ለእግዚአብሔር መታዘዝ ሕዝቡንም ማገልገል ይገባናል፤ ሁላችንም እንደ ምንገነዘበው በሲኖዶሳችን ያልታቀፉ ብዙ ወገኖች በሀገር ውስጥ ኣሉን፤ እነዚህ ወገኖች አንዳንዶቹ በተለያየ ምክንያት ከኛ የወጡ ናቸው፡፡ ይሁን እንጂ የሄዱት ወደ ቤታቸው እንዲመለሱ፣ ሌሎችም ወደ መንጋው እንዲቀላቀሉ በርትቶ መስራት የዚህ ጉባኤ ተቀዳሚ ተልእኮ ነው፤ ምክንያቱም ጸጋንና ሐዋርያነትን የተቀበልንበት ዋናው ምክንያት ይህንን ለማድረግ ነውና፡፡ ከዚህ አኳያ የቤተ ክርስቲያናችን ተደራሽነት በሳሳበት ኣካባቢ ሁሉ የተለየ ትኵረት ሰጥተን መስራትና ተጨባጭ ለውጥ ማምጣት ይኖርብናል፤
ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት የቅዱስ ሲኖዶስ ኣባላት!
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ውሉደ ክህነትና ምእመናን የሆን ሁላችን፣ ከሁሉ በፊት ያለንን ዓቅምና ብቃት በኣግባቡ መገንዘብ ይኖርብናል፤ ለእግዚአብሔር ክብርና ምስጋና ይሁንና ለፈጣሪው በቈራጥነት የሚታዘዝ ምእመን፣ ወጣት፣ ካህን ኣለን፤ ይህ ትልቅ ጸጋ ነው፤ ይህንን ጸጋ እግዚአብሔር፡ ለእግዚአብሔር መንግሥት በሚመች ሁናቴ ዝቅ ብሎ ማገልገል የክብር ክብር ነው፡፡ በመሆኑም ይህንን የእግዚአብሔር ሕዝብ በሓቅ፣ በቅንነት፣ በትጋትና በታማኝነት ቆመን ካገለገልነውና ኣባትነታችንንና መሪነታችንን በመልካም አሰራር በትክክል በኅሊናው እንዲቀረጽ ካደረግን፣ ይህ ኃይል ከጐናችን እንደማይለይ እርግጠኞች መሆን እንችላለን፤ ይህንን ካሳካን ለኛ የተሰጠ ኃይልና ብቃት በየትም ኣይገኝም፡፡
በዚህም በዚያም ሃይማኖቱ የሚጠይቀውን ሰብእና እና ቁመና ይዘን ከተገኘን፣ ሕዝበ ክርስቲያኑ ያለውን ብቻ ሳይሆን ሕይወቱን ሳይቀር ለመስጠት ወደ ኋላ የማይል የእግዚአብሔር ሕዝብ ኣለን፤ ስለዚህ ይህንን ማሳካት እንችል ዘንድ ከእምነት የሚነሣ መታዘዝ እንድናስገኝ የተቀበልነውን ጸጋና ሐዋርያነት በክብር እንያዝ፤
ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት የቅዱስ ሲኖዶስ ኣባላት!!
ለሕዝበ እግዚአብሔር የምናበረክተው ኣገልግሎት በመንፈሳዊ ብቻ ሳይሆን በኢኮኖሚውና በማኅበራዊው ኣገልግሎትም ጭምር ነው፤ ከዚህ ኣንጻር ሕዝባችን የተሻለ ማኅበራዊ ኣገልግሎት እንዲያገኝ፣ በኢኮኖሚውም ከድህነት የተላቀቀ እንዲሆን፤ እንደዚሁም ሰላሙና ኣንድነቱ የተጠበቀ እንዲሆን፣ በማስተማርም በተግባር በመሳተፍም የሕዝቡ መሪዎችና ኣርኣያ ሆነን መስራት ይገባናል፤በተለይም ከሰላም እጦት የተነሣ በእጅጉ እየተጎዳ ያለውን ሕዝባችን ሰላምና ፍትሕ እንዲያገኝ በጸሎትም በትምህርትም፣ በምክርም ተግተን መስራት ኣለብን፤
#ወስብሐት ለእግዚአብሔር!!
#ለመቀላቀል
@ortodoxtewahedo
#ለሃሳብ አስተያየት
@ortodoxtewahedoo
🛑 NEW || ልደታ ለማርያም || እግ...
ፈውስ መንፈሳዊ ጣና ቅ/ቂርቆስ ፬ መጻሕፍተ ጉባኤ ሚዲያ Fews Menfesawi
✝ወደ መቅደሱ ይመጣል✝
Size:-35.7MB
Length:-38:32
በርእሰ ሊቃውንት አባ ገብረ ኪዳን ግርማ
#ወስብሐት ለእግዚአብሔር!!
#ለመቀላቀል
@ortodoxtewahedo
#ለሃሳብ አስተያየት
@ortodoxtewahedoo
Size:-35.7MB
Length:-38:32
በርእሰ ሊቃውንት አባ ገብረ ኪዳን ግርማ
#ወስብሐት ለእግዚአብሔር!!
#ለመቀላቀል
@ortodoxtewahedo
#ለሃሳብ አስተያየት
@ortodoxtewahedoo
#ከኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ ቋሚ ሲኖዶስ የተሰጠ መግለጫ
“ናሁ ውስተ አድባር እገሪሆሙ ለሰብአ ዜና ወይዜንዉ ሰላመ እነሆ የምሥራችን የሚሰብክ ሰላምን የሚያወራ (ሚጠትን የሚናገር) ሰው እግሮች በተራሮች ላይ ናቸው"
(ትን.ናሆም 1፣15 ትርጓሜ ቅዱስ ዮሐንስ አወፈርቅ)
በውጭ አህጉረ ስብከት ተመድበው ሐዋርያዊ አገልግሎታቸውን በመፈጸም ላይ የሚገኙት ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ (ዶ/ር) የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ የኒውዮርክና አካባቢው ሀገረ ስብከት ሊቀጳጳስ 1 ብፁዕ አቡነ ቴዎፍሎስ (ዶ/ር) የሰሜን ካሊፎርኒያና አካባቢው ሀገረ ስብከት ሊቀጳጳስ፣ ብፁዕ አቡነ ያዕቆብ የጆርጅያና አካባቢው ሀገረ ስብከት ሊቀጳጳስ ወደ ሀገር ቤት በመግባት ዓመታዊ የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤን እንዲሳተፉ ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን በቅዱስ ሲኖዶስ በኩል ጥያቄ ማቅረቧ ይታወቃል፡፡
መንግሥትም ሀገራዊ ተቋማትን ለማጠናከር ያለው ቁርጠኝነት የጸና መሆኑን በገለጸበት መግለጫ እንደተመለከትነው የሀገራችንን ሰላም ለማጽናት፣ የቅድስት ቤተ ክርስቲያናችንን የታሪክ ገጽታ ለመጠበቅ ተቀራርቦ መነጋገር የተሻለ መፍትሔ መሆኑን ተረድቶ ሦስቱ ሊቃነ ጳጳሳት ወደ ሀገር ገብተው የቅዱስ ሲኖዶስ ጉባኤን እንዲሳተፉ መፍቀዱን ተረድተናል፡፡
በመሆኑም መንግሥት ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን ያቀረበችውን ጥያቄ ተቀብሎ ሦስቱ ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት ወደ ሀገር እንዲገቡ በመፍቀዱና ተግባራዊ ምላሽ በመስጠቱ ከፍ ያለ ምስጋናችንን እናቀርባለን፡፡
ወደፊትም እግዚአብሔር በሰጠን ምድር፣ አባቶቻችን ባቆዩልን ሀገር አስተማማኝ ሰላም እንዲኖር ለሀገራችንና ለሕዝባችን በሚጠቅሙ ጉዳዮች ላይ ግንኙነታችንን በማጠናከር በጋራ : ለመሥራት ዝግጁዎች መሆናችንን እንገልጻለን፡፡
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
#ለመቀላቀል
@ortodoxtewahedo
“ናሁ ውስተ አድባር እገሪሆሙ ለሰብአ ዜና ወይዜንዉ ሰላመ እነሆ የምሥራችን የሚሰብክ ሰላምን የሚያወራ (ሚጠትን የሚናገር) ሰው እግሮች በተራሮች ላይ ናቸው"
(ትን.ናሆም 1፣15 ትርጓሜ ቅዱስ ዮሐንስ አወፈርቅ)
በውጭ አህጉረ ስብከት ተመድበው ሐዋርያዊ አገልግሎታቸውን በመፈጸም ላይ የሚገኙት ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ (ዶ/ር) የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ የኒውዮርክና አካባቢው ሀገረ ስብከት ሊቀጳጳስ 1 ብፁዕ አቡነ ቴዎፍሎስ (ዶ/ር) የሰሜን ካሊፎርኒያና አካባቢው ሀገረ ስብከት ሊቀጳጳስ፣ ብፁዕ አቡነ ያዕቆብ የጆርጅያና አካባቢው ሀገረ ስብከት ሊቀጳጳስ ወደ ሀገር ቤት በመግባት ዓመታዊ የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤን እንዲሳተፉ ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን በቅዱስ ሲኖዶስ በኩል ጥያቄ ማቅረቧ ይታወቃል፡፡
መንግሥትም ሀገራዊ ተቋማትን ለማጠናከር ያለው ቁርጠኝነት የጸና መሆኑን በገለጸበት መግለጫ እንደተመለከትነው የሀገራችንን ሰላም ለማጽናት፣ የቅድስት ቤተ ክርስቲያናችንን የታሪክ ገጽታ ለመጠበቅ ተቀራርቦ መነጋገር የተሻለ መፍትሔ መሆኑን ተረድቶ ሦስቱ ሊቃነ ጳጳሳት ወደ ሀገር ገብተው የቅዱስ ሲኖዶስ ጉባኤን እንዲሳተፉ መፍቀዱን ተረድተናል፡፡
በመሆኑም መንግሥት ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን ያቀረበችውን ጥያቄ ተቀብሎ ሦስቱ ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት ወደ ሀገር እንዲገቡ በመፍቀዱና ተግባራዊ ምላሽ በመስጠቱ ከፍ ያለ ምስጋናችንን እናቀርባለን፡፡
ወደፊትም እግዚአብሔር በሰጠን ምድር፣ አባቶቻችን ባቆዩልን ሀገር አስተማማኝ ሰላም እንዲኖር ለሀገራችንና ለሕዝባችን በሚጠቅሙ ጉዳዮች ላይ ግንኙነታችንን በማጠናከር በጋራ : ለመሥራት ዝግጁዎች መሆናችንን እንገልጻለን፡፡
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
#ለመቀላቀል
@ortodoxtewahedo
ብፁዕ አቡነ ይስሐቅ የወላይታ ሀገረ ስብከት ሊቀጳጳስ ፻፴፪ ኛው መደበኛው የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዐተ ጉባኤ ከቅዱስ ሲኖዶስ ጽ/ቤት
"በገዛ ደሙ የዋጃትን የእግዚአብሔርን ቤተ ክርስቲያን ትጠብቁአት ዘንድ መንፈስ ቅዱስ እናንተን ጳጳሳት አድርጎ ለሾመባት ለመንጋው ሁሉና ለራሳችሁ ተጠንቀቁ።”
#ሐዋርያት ፳፥፳፰
#ወስብሐት ለእግዚአብሔር!!
#ለመቀላቀል
@ortodoxtewahedo
#ለሃሳብ አስተያየት
@ortodoxtewahedoo
"በገዛ ደሙ የዋጃትን የእግዚአብሔርን ቤተ ክርስቲያን ትጠብቁአት ዘንድ መንፈስ ቅዱስ እናንተን ጳጳሳት አድርጎ ለሾመባት ለመንጋው ሁሉና ለራሳችሁ ተጠንቀቁ።”
#ሐዋርያት ፳፥፳፰
#ወስብሐት ለእግዚአብሔር!!
#ለመቀላቀል
@ortodoxtewahedo
#ለሃሳብ አስተያየት
@ortodoxtewahedoo
Forwarded from 🟢ናታኒም ፖሮሞሽን🟢
📚👉መናፍቃን ከሚያነሷቸው 3 ጥያቄዎች መካከል⁉️
1)የጌታችን እኔ የአዳም የውርስ ኃጢአት/ጥንተ አብሶ/አለበት።
2)የጌታችን እናት አልተነሳችም
3)ኢየሱስ ክርስቶስ አማላጅ ነው።
👉ለነዚህ ጥያቄዎች እና ለመሳሰሉት መልስ የሚያገኙበት ቻናል ነው። አሁኑኑ ይቀላቀሉ በማርያም ❗️
👇👇👇
▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬
◤◢◤◢◤◢◣◥◣◥◣◥
█ 𝐉𝐎𝐈𝐍 𝐔𝐒 ➲ █
◣◥◣◥◣◥◤◢◤◢◤◢
▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬
👇👇👇
🔔
🔺 𝒔𝒖𝒃𝒔𝒄𝒓𝒊𝒃𝒆 𝒏𝒐𝒘🔺
⛪️ኦርቶዶክሳዊ ስብከት⛪️
🤗ኦርቶዶክሳዊ ዝማሬ🤗
❤️ትምህርቱን በይቱብ❤️
ከታች ባለው ሊንክ ሰብስክራቭ በማድረግ ቤተሰብ ይሁኑ።
👇🏽👇🏽
https://youtu.be/yI-3Sl9NB5c?si=1fCKjnh4FjRC2OJ9
https://youtu.be/yI-3Sl9NB5c?si=1fCKjnh4FjRC2OJ9
1)የጌታችን እኔ የአዳም የውርስ ኃጢአት/ጥንተ አብሶ/አለበት።
2)የጌታችን እናት አልተነሳችም
3)ኢየሱስ ክርስቶስ አማላጅ ነው።
👉ለነዚህ ጥያቄዎች እና ለመሳሰሉት መልስ የሚያገኙበት ቻናል ነው። አሁኑኑ ይቀላቀሉ በማርያም ❗️
👇👇👇
▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬
◤◢◤◢◤◢◣◥◣◥◣◥
█ 𝐉𝐎𝐈𝐍 𝐔𝐒 ➲ █
◣◥◣◥◣◥◤◢◤◢◤◢
▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬
👇👇👇
🔔
🔺 𝒔𝒖𝒃𝒔𝒄𝒓𝒊𝒃𝒆 𝒏𝒐𝒘🔺
⛪️ኦርቶዶክሳዊ ስብከት⛪️
🤗ኦርቶዶክሳዊ ዝማሬ🤗
❤️ትምህርቱን በይቱብ❤️
ከታች ባለው ሊንክ ሰብስክራቭ በማድረግ ቤተሰብ ይሁኑ።
👇🏽👇🏽
https://youtu.be/yI-3Sl9NB5c?si=1fCKjnh4FjRC2OJ9
https://youtu.be/yI-3Sl9NB5c?si=1fCKjnh4FjRC2OJ9
Forwarded from 🟢ናታኒም ፖሮሞሽን🟢
🇪🇹 የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክርስቲያን አስተምህሮ ና ስርአትን የጠበቁ የትኞቹን መዝሙራት ማግኝት ይፈልጋሉ❓
እኒህ ሦስቱ:-
፩. የተሸከሙት ሸክም ያላጎበጣቸው
፪. የመከራ ቀን ጥብዐታቸው
፫. መከራውን ያለፉበት ጥበባቸው
፬. ለሲኖዶሳዊ ልዕልና ተጋድሏቸው
እናት ቤተ ክርስቲያንን በጃት!
"በገዛ ደሙ የዋጃትን የእግዚአብሔርን ቤተ ክርስቲያን ትጠብቁአት ዘንድ መንፈስ ቅዱስ እናንተን ጳጳሳት አድርጎ ለሾመባት ለመንጋው ሁሉና ለራሳችሁ ተጠንቀቁ።”
#ሐዋርያት ፳፥፳፰
#ወስብሐት ለእግዚአብሔር!!
#ለመቀላቀል
@ortodoxtewahedo
#ለሃሳብ አስተያየት
@ortodoxtewahedoo
፩. የተሸከሙት ሸክም ያላጎበጣቸው
፪. የመከራ ቀን ጥብዐታቸው
፫. መከራውን ያለፉበት ጥበባቸው
፬. ለሲኖዶሳዊ ልዕልና ተጋድሏቸው
እናት ቤተ ክርስቲያንን በጃት!
"በገዛ ደሙ የዋጃትን የእግዚአብሔርን ቤተ ክርስቲያን ትጠብቁአት ዘንድ መንፈስ ቅዱስ እናንተን ጳጳሳት አድርጎ ለሾመባት ለመንጋው ሁሉና ለራሳችሁ ተጠንቀቁ።”
#ሐዋርያት ፳፥፳፰
#ወስብሐት ለእግዚአብሔር!!
#ለመቀላቀል
@ortodoxtewahedo
#ለሃሳብ አስተያየት
@ortodoxtewahedoo
አባ ሳዊሮስን በአጭሩ - ግቡና መርምሩ
+ + + + +
ባለፉት ሁለት አስርተ ዓመታት ቤተክርስቲያን መከራ በምትቀበልባቸው ወቅቶች፣ በተለያዩ ፈተናዎች ውስጥ ስታልፍ... አንድ አይነት አሻራ ወይም አንድ አካል ከሁነቶቹ ጋር ተያይዞ ሲነሳ መስማት የተለመደ ሆኗል። ከሚነድ እሳት ጀርባ ከሚጨስ ጭስ ጀርባ ክብሪት እጃቸው ላይ የሚገኝ ሰው። ይህ አጋጣሚ ብቻ ለመሆኑ ግራ ያጋባኛል። እስኪ ጥቂት አጋጣሚዎችን እናንሳ፦
👉 ዘጠናዎቹ መጨረሻ የሚሊንየሙ መጀመሪያ ቤተክርስቲያንን ሊውጥ የመጣው ተሐድሶ ልባችንን በእሳት ሲለበልበው በነበረበት ወሳኝ ወቅት... እሳቸው ከሌሎቹ አባቶች በልዩነት የተሐድሶዎችን የቴሌቪዥን ፕሮግራም (የታኦሎጎስ)፣ የአደራሽ (የቦሌ ፋና ፓርክ) ገባኤያቸውን ሲባርኩ ነበር!
👉 በየ ሀገረ ስብከቱ የቤተክርስቲያንን ቀኖና የጣሱ የተሐድሶ አራማጆች ሲታገዱና ሲወገዱ፣ በደቡብ ምዕራብ ሸዋ ሀገረ ስብከት ግን እነዚሁ አራማጆች ያለ ማንም ከልካይ በአውደ ምህረት ላይ ሲፈነጩ... እሳቸው በግልጽ ማንም እንዳይነካቸው ከለላ ይሰጡ ነበር!
👉 ቤተክርስቲያን አንድነቷን ተነጥቃ በሕገወጥ መንገድ "የኦሮሚያ ቤተክህነት" የሚባል አካል ሲመሰረት... ከነ ቀሲስ በላይ ጀርባ እርሳቸው ነበሩ!
👉 የቤተክርስቲያንን መሠረት ያናጋው፣ ልብንም ያቆሰለው መፈንቅለ ሲኖዶስና መፈንቅለ ፓትርያሪክ ሙከራ ሲደረግ፣ ያ የጫካ ውስጥ የሕገወጥ ሹመት ሲካሄድ... አቡነ ሳዊሮስ ከዋነኛ ተዋናዮቹ መካከል ዋነኛው ሰው ነበሩ!
👉 አንዳንድ አባቶች መንበረ ሰላማ በሚል ሽፋን ከእናት ቤተክርስቲያን ህጋዊ ሲኖዶስ ሲለዩና ሲገነጠሉ... እሳቸው መቀሌ ተጉዘው "በርቱ!" የሚል የማበረታቻ መልእክት ያስተላለፉ ሰው ነበሩ!
👉 በተደጋጋሚ በገንዘብ የኑፋቄ እንቅስቃሴዎችን በቤተክርስቲያን ላይ ከሚያደርገው ጸጋዬ ሮቶ (ፍኖተ ጽድቅ) ጀርባ... አለምገና ሰበታ ላይ ባለው ኢንቨስትመንት ተጠቅሞ ቤተክርስቲያንን ሲያደማ ከለላው እሳቸው ነበሩ!
👉 የኦሮሚያ ክልላዊ መንግስት የቤተክርስቲያንን ህልውና ለመጋፋት በሚመስል መልኩ በክልል ደረጃ ከቤተክርስቲያን እውቅና ውጪ የሐይማኖት ጉባኤ አደረጃጀት ሲፈጥር... እሳቸው ከጀርባ ነበሩ! ከፍ ብሎም የኦሮሚያ ኦርቶዶክስ ሃይማኖቶ ሰብሳቢ ሆነዋል!
👉 እነሆ ብልጽግና ጥቅሙን የሚያስከብርለት የቤተክህነት ተሿሚ ሲሻ እሳቸው እጩ ስርአስኪያጅ ሆነው ብቅ ብለዋል።
ምንግዜም ቤተክርስቲያን ላይ ፈተና ሲመጣ እሳቸው ከጀርባ አሉ።
....
በብጹእ አባታችን በጎ በረከቶት ይደርብን አባታችን ይሄ ሁሉ አጋጣሚ ይሆን? እላለሁ፤
እርሶ ከወ/ር እጅጋየሁ ጀርባ ነበሩ፣ የበጋሻውም ከለላ ነበሩ፣ ቤተክርስቲያን ከሚፈትኑ ንኡስ ብሔርተኞችም አጋር ነበሩ፣ ከቀሲስ በላይና ከኃይለ ሚካኤል ጀርባ ሆነው የኦሮሚያ ቤ/ክህነት ምስረታ ላይ ቡራኬ ሰጪ ነበሩ፣ ቀጥሎም የቤተክርስቲያንን ህልውና ተጋፍተው በወሊሶ ጫካ መነኮሳትን ሊያጰጵሱ ሲሞክሩ ነበር፣ ቀጥሎም የፕትርክና ልብስ አሰፍተው መፈንቅለ ፓትርያርክ ሲያደርጉ ነበረ፣ ቀጥሎም የመንበረ ሰላማ ተገንጣዮቹን አይዟቹህ ሊሉ በአካል ሄደው ነበረ፣ ብልጽግና ቤተክርስቲያን ባሳነሰበት መድረክ ሁሉ እርሶ አሉ፣ አሁን ከስርአተ ቤተክርስቲያን ባፈነገጠ ሁኔታ በ5ኪሎ የ4ኪሎ ፖሊት ቢሮ ለመሆን የስርአስኪያጅነት ቅስቀሳ እያስደረጉ ነው.... አባታችን ለቤተክርስቲያን እየጠቀምኳት ነው ብለው ያምናሉ?
...
Maryamawit Henok Lemessa
+ + + + +
ይኽም ኾኖ ሲኖዶስ የጸሐፊነት ዕድል ሰጥቷቸው ነበረ። ያኔ ያጠፉት ብዛት ቀላል አልነበረም። ከሲኖዶሱ አባላት አንድም ጊዜ ወይ በጸሐፊነት ወይ በሥራ አስኪያጅነት ያላገለገሉ ሞልተዋል። ወደዚያ ማማተሩ ይሻላል።
+ + + + +
ባለፉት ሁለት አስርተ ዓመታት ቤተክርስቲያን መከራ በምትቀበልባቸው ወቅቶች፣ በተለያዩ ፈተናዎች ውስጥ ስታልፍ... አንድ አይነት አሻራ ወይም አንድ አካል ከሁነቶቹ ጋር ተያይዞ ሲነሳ መስማት የተለመደ ሆኗል። ከሚነድ እሳት ጀርባ ከሚጨስ ጭስ ጀርባ ክብሪት እጃቸው ላይ የሚገኝ ሰው። ይህ አጋጣሚ ብቻ ለመሆኑ ግራ ያጋባኛል። እስኪ ጥቂት አጋጣሚዎችን እናንሳ፦
👉 ዘጠናዎቹ መጨረሻ የሚሊንየሙ መጀመሪያ ቤተክርስቲያንን ሊውጥ የመጣው ተሐድሶ ልባችንን በእሳት ሲለበልበው በነበረበት ወሳኝ ወቅት... እሳቸው ከሌሎቹ አባቶች በልዩነት የተሐድሶዎችን የቴሌቪዥን ፕሮግራም (የታኦሎጎስ)፣ የአደራሽ (የቦሌ ፋና ፓርክ) ገባኤያቸውን ሲባርኩ ነበር!
👉 በየ ሀገረ ስብከቱ የቤተክርስቲያንን ቀኖና የጣሱ የተሐድሶ አራማጆች ሲታገዱና ሲወገዱ፣ በደቡብ ምዕራብ ሸዋ ሀገረ ስብከት ግን እነዚሁ አራማጆች ያለ ማንም ከልካይ በአውደ ምህረት ላይ ሲፈነጩ... እሳቸው በግልጽ ማንም እንዳይነካቸው ከለላ ይሰጡ ነበር!
👉 ቤተክርስቲያን አንድነቷን ተነጥቃ በሕገወጥ መንገድ "የኦሮሚያ ቤተክህነት" የሚባል አካል ሲመሰረት... ከነ ቀሲስ በላይ ጀርባ እርሳቸው ነበሩ!
👉 የቤተክርስቲያንን መሠረት ያናጋው፣ ልብንም ያቆሰለው መፈንቅለ ሲኖዶስና መፈንቅለ ፓትርያሪክ ሙከራ ሲደረግ፣ ያ የጫካ ውስጥ የሕገወጥ ሹመት ሲካሄድ... አቡነ ሳዊሮስ ከዋነኛ ተዋናዮቹ መካከል ዋነኛው ሰው ነበሩ!
👉 አንዳንድ አባቶች መንበረ ሰላማ በሚል ሽፋን ከእናት ቤተክርስቲያን ህጋዊ ሲኖዶስ ሲለዩና ሲገነጠሉ... እሳቸው መቀሌ ተጉዘው "በርቱ!" የሚል የማበረታቻ መልእክት ያስተላለፉ ሰው ነበሩ!
👉 በተደጋጋሚ በገንዘብ የኑፋቄ እንቅስቃሴዎችን በቤተክርስቲያን ላይ ከሚያደርገው ጸጋዬ ሮቶ (ፍኖተ ጽድቅ) ጀርባ... አለምገና ሰበታ ላይ ባለው ኢንቨስትመንት ተጠቅሞ ቤተክርስቲያንን ሲያደማ ከለላው እሳቸው ነበሩ!
👉 የኦሮሚያ ክልላዊ መንግስት የቤተክርስቲያንን ህልውና ለመጋፋት በሚመስል መልኩ በክልል ደረጃ ከቤተክርስቲያን እውቅና ውጪ የሐይማኖት ጉባኤ አደረጃጀት ሲፈጥር... እሳቸው ከጀርባ ነበሩ! ከፍ ብሎም የኦሮሚያ ኦርቶዶክስ ሃይማኖቶ ሰብሳቢ ሆነዋል!
👉 እነሆ ብልጽግና ጥቅሙን የሚያስከብርለት የቤተክህነት ተሿሚ ሲሻ እሳቸው እጩ ስርአስኪያጅ ሆነው ብቅ ብለዋል።
ምንግዜም ቤተክርስቲያን ላይ ፈተና ሲመጣ እሳቸው ከጀርባ አሉ።
....
በብጹእ አባታችን በጎ በረከቶት ይደርብን አባታችን ይሄ ሁሉ አጋጣሚ ይሆን? እላለሁ፤
እርሶ ከወ/ር እጅጋየሁ ጀርባ ነበሩ፣ የበጋሻውም ከለላ ነበሩ፣ ቤተክርስቲያን ከሚፈትኑ ንኡስ ብሔርተኞችም አጋር ነበሩ፣ ከቀሲስ በላይና ከኃይለ ሚካኤል ጀርባ ሆነው የኦሮሚያ ቤ/ክህነት ምስረታ ላይ ቡራኬ ሰጪ ነበሩ፣ ቀጥሎም የቤተክርስቲያንን ህልውና ተጋፍተው በወሊሶ ጫካ መነኮሳትን ሊያጰጵሱ ሲሞክሩ ነበር፣ ቀጥሎም የፕትርክና ልብስ አሰፍተው መፈንቅለ ፓትርያርክ ሲያደርጉ ነበረ፣ ቀጥሎም የመንበረ ሰላማ ተገንጣዮቹን አይዟቹህ ሊሉ በአካል ሄደው ነበረ፣ ብልጽግና ቤተክርስቲያን ባሳነሰበት መድረክ ሁሉ እርሶ አሉ፣ አሁን ከስርአተ ቤተክርስቲያን ባፈነገጠ ሁኔታ በ5ኪሎ የ4ኪሎ ፖሊት ቢሮ ለመሆን የስርአስኪያጅነት ቅስቀሳ እያስደረጉ ነው.... አባታችን ለቤተክርስቲያን እየጠቀምኳት ነው ብለው ያምናሉ?
...
Maryamawit Henok Lemessa
+ + + + +
ይኽም ኾኖ ሲኖዶስ የጸሐፊነት ዕድል ሰጥቷቸው ነበረ። ያኔ ያጠፉት ብዛት ቀላል አልነበረም። ከሲኖዶሱ አባላት አንድም ጊዜ ወይ በጸሐፊነት ወይ በሥራ አስኪያጅነት ያላገለገሉ ሞልተዋል። ወደዚያ ማማተሩ ይሻላል።