"ኦ ሚካኤል ኦ መተንብል፣ ካህነ አርያም ትሰመይ ቢጸ ሱራፌል፣ ዘእምርዑሳን ርዑስ ወዘእምልዑላን ልዑል፣ ጊዜ ጸዋዕኩከ ቅረበኒ በምሕረት ወሣህል፡፡"
"አማላጃችን ሚካኤል ሆይ ፈጥኖ ደራሻችን ሚካኤል ሆይ የጌታን ዙፋን ከሚያጥኑ ሱራፌል ካህናት አንዱ ሰማያዊ ካህን አንተ ነህ እኮን። የሰማያውያን ሊቃነ መላእክት ሁሉ አንተ አለቃቸው ነህ እኮን። ይልቁንም የልዑላንም ልዑል አንተ ነህና በጠራሁህ ጊዜ ሁሉ በይቅርታና በቸርነት ድረስልኝ አትራቀኝ።"
(መልክአ ሚካኤል)
"አማላጃችን ሚካኤል ሆይ ፈጥኖ ደራሻችን ሚካኤል ሆይ የጌታን ዙፋን ከሚያጥኑ ሱራፌል ካህናት አንዱ ሰማያዊ ካህን አንተ ነህ እኮን። የሰማያውያን ሊቃነ መላእክት ሁሉ አንተ አለቃቸው ነህ እኮን። ይልቁንም የልዑላንም ልዑል አንተ ነህና በጠራሁህ ጊዜ ሁሉ በይቅርታና በቸርነት ድረስልኝ አትራቀኝ።"
(መልክአ ሚካኤል)
🔴 እግዚአብሔር በሚያደርገው በጎ ነገር...
ፈውስ መንፈሳዊ ጣና ቅ/ቂርቆስ ፬ መጻሕፍተ ጉባኤ ሚዲያ Fews Menfesawi
✝እግዚአብሔር በሚያደርገው በጎ ነገር ሚካኤል ይታዘዛል✝
Size 51.2MB
Length 55:18
በርዕሰ ሊቃውንት አባ ገብረ ኪዳን ግርማ
#ለመቀላቀል
@ortodoxtewahedo
#ለሃሳብ አስተያየት
@ortodoxtewahedoo
#ወስብሐት_ለእግዚአብሔር
Size 51.2MB
Length 55:18
በርዕሰ ሊቃውንት አባ ገብረ ኪዳን ግርማ
#ለመቀላቀል
@ortodoxtewahedo
#ለሃሳብ አስተያየት
@ortodoxtewahedoo
#ወስብሐት_ለእግዚአብሔር
//በፓሪስ እጅግ ጥዑም ስብከት// በር...
ፓሪስ ቅዱስ ጊዮርጊስ ወቁስቋም ማርያም ቤተ ክርስቲያን
✝ደስታ ምንድንው?✝
Size:-66.5MB
Length:-1:11:51
በርእሰ ሊቃውንት አባ ገብረ ኪዳን ግርማ
#ለመቀላቀል
@ortodoxtewahedo
#ለሃሳብ አስተያየት
@ortodoxtewahedoo
#ወስብሐት_ለእግዚአብሔር
Size:-66.5MB
Length:-1:11:51
በርእሰ ሊቃውንት አባ ገብረ ኪዳን ግርማ
#ለመቀላቀል
@ortodoxtewahedo
#ለሃሳብ አስተያየት
@ortodoxtewahedoo
#ወስብሐት_ለእግዚአብሔር
#ሰኔ_21_እመቤታችን_ቅድስት_ድንግል_ማርያም ለሕንጸተ ቤተ ክርስቲያን ዘእግዝእትነ ማርያም እና ሰኔ ጐልጐታ እንኳን አደረሰን! የእናታችን ቅድስት ድንግል ማርያም አማላጅነቷ ረድኤቷ በረከቷ ጥበቃዋ አይለየን እመ ብዙኃን የብዙኃን እናት ድንግል ማርያም ሆይ ሳይነግሩሽ የሰውን ችግር ጭንቀት የምታውቂ እሩህሩህ እናት ነሽና የጎደለንን ሙይልን በእግዚአብሔር ዘንድ ተቀባይነት ያለው አማላጅነትሽ ፍፁም ረድኤትሽ አይለየን፤ የቃል ኪዳን ሀገርሽን ቅድስት ሀገር ኢትዮጵያን በምልጃሽ አስቢያት! አሜን፡፡
''በዕንቊ ሰንፔር ትትሐነጽ ወበመረግድ
ሃሌ ሉያ ለአብ ሐጹር የዓውዳ ትበርህ እምከዋክብት
ሃሌ ሉያ ለወልድ ሃሌ ሉያ ወለመንፈስ ቅዱስ
ጽዮን ቅድስት ቤተ ክርስትያን ደብተራ ፍጽምት''
ዚቅ ዘቅዱስ ያሬድ
እንኳን ለእናታችን ለቅድስተ ቅዱሳን ድንግል ማርያም ዓመታዊ በዓል በሰላም አደረሰን አደረሳችሁ።
#ለመቀላቀል
@ortodoxtewahedo
#ለሃሳብ አስተያየት
@ortodoxtewahedoo
#ወስብሐት_ለእግዚአብሔር
''በዕንቊ ሰንፔር ትትሐነጽ ወበመረግድ
ሃሌ ሉያ ለአብ ሐጹር የዓውዳ ትበርህ እምከዋክብት
ሃሌ ሉያ ለወልድ ሃሌ ሉያ ወለመንፈስ ቅዱስ
ጽዮን ቅድስት ቤተ ክርስትያን ደብተራ ፍጽምት''
ዚቅ ዘቅዱስ ያሬድ
እንኳን ለእናታችን ለቅድስተ ቅዱሳን ድንግል ማርያም ዓመታዊ በዓል በሰላም አደረሰን አደረሳችሁ።
#ለመቀላቀል
@ortodoxtewahedo
#ለሃሳብ አስተያየት
@ortodoxtewahedoo
#ወስብሐት_ለእግዚአብሔር
++ሐራሩኤል ጭርዋቅ++
ጥበብን የለበሳት ጠቢብ ሰሎሞን ለራሱ ሐራሩኤል ጭርዋቅ የሚል ስመ አምላክ የሰፈረበት ቀለበት ነበረው። ትእምርተ መንግሥቱ ግርማ ሞገሱ እሱ ነው ከሴት ሲደርስ አንበሳ መደብ ሲወጣ ቀለበቱን አውልቆ ከዙፋኑ ላይ ያኖረው ነበር። በአንድ ወቅት አንበሳ መደብ ደርሱ ሲመጣ ሰይጣን ለምቀኝነት አያርፍምና ቀለበቱን ከዙፋኑ ማንሳት ባይቻለው ከነዙፋኑ ጠቅሎ ባሕር ላይ ጣለው ሰሎሞን ሲመለስ ዙፋን ቤቱ ከለከለው የንግሥናውን ምልክት ግርማ ሞገሱን አጥቷልና ጎስቋላ ሆነ። ከዚህ በኋላ በገዛ ከተማው ሁለት ሳምንት ለምኗል ሰይጣን የሰው ልቡና አጽንቶበት የሚሰጠው አጥቶ ከመሠግራነ ዓሳ ሄዶ ስመ እግዚአብሔር ጠራባቸው ከመሀከላቸው አንዱም ይህ ዘብዛባ ብሎ የሞተ አሳ ጣለለት ሆድ እቃውን አውጥቶ ለመመገብ ቢቀደው ቀለበቱን አገኘ ቀለበቱን እንዳገኘ ግርማ ሞገሱ ከነክብሩ ተመለሰለት። በሰይጣን የተነጠቀው መንግሥቱ ተመለሰ ብዙዎቹም ሰሎሞን መሆነን ሲያውቁ ንጉሥን ከዚህ ምን አመጣው ብለው ከበቡት ቡሀላም መርበበተ ሰሎሞን የሚባል ስመ አምላክ አትሞ ቀብሮታል።ሰሎሞንን እዚህ ያደረሰው ምንድነው ቢሉ ከዕለታት በአንዳቸው የተራበ ሰው ስመ እግዚአብሔር እየጠራ ሲለምነው ይህ ሰው ምን ሆኗል አለ ተርቦ ነው ቢሉት ረኀብ ምንድነው ብሎ ነበርና የረኀብን ጽናት ሊያሳየው ይህ ተፈጸመበት።>>{ቅዳሴ ማርያም ትርጓሜ}
👇👇👇👇👇
የሰሎሞን መንግሥት እና ንግሥና በቀለበት ምክንያት እንደተመለስ በአዳም የሄድ አንድም ያጣነው ልጅነት እንደ ቃልህ ይደረግልኝ በሚለው የእምነት ቃሏ በእርሷ ተመልሱልናልና መርበብት ሰሎሞን ተብሎ የታተመበት ሐሩራኤል ጭርዋቅ የሚል ስመ አምላክ የተጻፈባት የሰሎሞን ቀለበት እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ናት እንላለን።
የሰው ልጅ በጥንት መርገም ተይዞ በነበረበት ዘመን በንጽህናና በቅድስና አጊጣ በምክረ ከይሲ በአዳም ስህተት ያጣነውን ልጅነት ያገኘንባት ለእርሷ ለሰው እንዲረዳ መሰልንላት አንጂ ከሰሎሞን ቀለበት በብዙ ትልቃለች።
በረከቷ ምልጃዋና ጸሎቷ አይለየን
ዲ/ን ሞገስ አብረሃም
ሰኔ 23 የንጉሥ ዳዊት ልጅ ጠቢቡ ሰለሞን ያረፈበት ቀን ነው ::
#ለመቀላቀል
@ortodoxtewahedo
#ለሃሳብ አስተያየት
@ortodoxtewahedoo
#ወስብሐት_ለእግዚአብሔር
ጥበብን የለበሳት ጠቢብ ሰሎሞን ለራሱ ሐራሩኤል ጭርዋቅ የሚል ስመ አምላክ የሰፈረበት ቀለበት ነበረው። ትእምርተ መንግሥቱ ግርማ ሞገሱ እሱ ነው ከሴት ሲደርስ አንበሳ መደብ ሲወጣ ቀለበቱን አውልቆ ከዙፋኑ ላይ ያኖረው ነበር። በአንድ ወቅት አንበሳ መደብ ደርሱ ሲመጣ ሰይጣን ለምቀኝነት አያርፍምና ቀለበቱን ከዙፋኑ ማንሳት ባይቻለው ከነዙፋኑ ጠቅሎ ባሕር ላይ ጣለው ሰሎሞን ሲመለስ ዙፋን ቤቱ ከለከለው የንግሥናውን ምልክት ግርማ ሞገሱን አጥቷልና ጎስቋላ ሆነ። ከዚህ በኋላ በገዛ ከተማው ሁለት ሳምንት ለምኗል ሰይጣን የሰው ልቡና አጽንቶበት የሚሰጠው አጥቶ ከመሠግራነ ዓሳ ሄዶ ስመ እግዚአብሔር ጠራባቸው ከመሀከላቸው አንዱም ይህ ዘብዛባ ብሎ የሞተ አሳ ጣለለት ሆድ እቃውን አውጥቶ ለመመገብ ቢቀደው ቀለበቱን አገኘ ቀለበቱን እንዳገኘ ግርማ ሞገሱ ከነክብሩ ተመለሰለት። በሰይጣን የተነጠቀው መንግሥቱ ተመለሰ ብዙዎቹም ሰሎሞን መሆነን ሲያውቁ ንጉሥን ከዚህ ምን አመጣው ብለው ከበቡት ቡሀላም መርበበተ ሰሎሞን የሚባል ስመ አምላክ አትሞ ቀብሮታል።ሰሎሞንን እዚህ ያደረሰው ምንድነው ቢሉ ከዕለታት በአንዳቸው የተራበ ሰው ስመ እግዚአብሔር እየጠራ ሲለምነው ይህ ሰው ምን ሆኗል አለ ተርቦ ነው ቢሉት ረኀብ ምንድነው ብሎ ነበርና የረኀብን ጽናት ሊያሳየው ይህ ተፈጸመበት።>>{ቅዳሴ ማርያም ትርጓሜ}
👇👇👇👇👇
የሰሎሞን መንግሥት እና ንግሥና በቀለበት ምክንያት እንደተመለስ በአዳም የሄድ አንድም ያጣነው ልጅነት እንደ ቃልህ ይደረግልኝ በሚለው የእምነት ቃሏ በእርሷ ተመልሱልናልና መርበብት ሰሎሞን ተብሎ የታተመበት ሐሩራኤል ጭርዋቅ የሚል ስመ አምላክ የተጻፈባት የሰሎሞን ቀለበት እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ናት እንላለን።
የሰው ልጅ በጥንት መርገም ተይዞ በነበረበት ዘመን በንጽህናና በቅድስና አጊጣ በምክረ ከይሲ በአዳም ስህተት ያጣነውን ልጅነት ያገኘንባት ለእርሷ ለሰው እንዲረዳ መሰልንላት አንጂ ከሰሎሞን ቀለበት በብዙ ትልቃለች።
በረከቷ ምልጃዋና ጸሎቷ አይለየን
ዲ/ን ሞገስ አብረሃም
ሰኔ 23 የንጉሥ ዳዊት ልጅ ጠቢቡ ሰለሞን ያረፈበት ቀን ነው ::
#ለመቀላቀል
@ortodoxtewahedo
#ለሃሳብ አስተያየት
@ortodoxtewahedoo
#ወስብሐት_ለእግዚአብሔር
ሃቢብ ጊዮርጊስ ግን ቤተ ክርስቲያንን አልከሰሰም፤ ሸክሟን ተሸከመ እንጂ።
፩. የዘመኑ ታሪካዊ ቀውስና የቤተ ክርስቲያን ፈተና
በዐሥራ ዘጠነኛው መቶ ክፍለ ዘመን መገባደጃና በሃያኛው መቶ ክፍለ ዘመን መባቻ ላይ፣ የግብጽ ኮፕቲክ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን በታሪኳ እጅግ ውስብስብ ከሆኑት ፈተናዎች እያስተናገደች ነበር። ቀውሱ የውጭ ጫና ብቻ ሳይሆን፣ ከውስጥ የመነጨና የቤተ ክርስቲያኒቱን ሕልውና የሚፈታተን ነበር። ይህ ድክመት በአስተዳደር መላሸቅ፣ በመልካም አስተዳደር እጦት፣ በሙስናና በአንዳንድ አገልጋዮች የሥነ ምግባር ውድቀት ተገልጧል። ከዚህም በላይ፣ የትምህርተ ሃይማኖት ዕውቀት በእጅጉ ተዳክሞ፣ የመንፈሳዊ አገልግሎት ጥራትና ስፋት በእጅጉ ቀንሶ ነበር።
ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ሺኖዳ ሣልሳዊ፣ የዚያን ዘመን አሳሳቢ ገጽታ ሲመሰክሩ እንዲህ በማለት ሁኔታውን ያጠቃልሉታል፡-
“በሃያኛው ክፍለ ዘመን መጀመሪያ ላይ፣ ስብከቶች ደረቅና ሕይወት አልባ ነበሩ፤ መንፈሳዊ ትምህርት ቤቶች ከሞላ ጎደል አልነበሩም፤ ድንቁርና በቤተ ክርስቲያኒቱ ውስጥ፣ እንዲያውም በቀሳውስቱ መካከል እንኳ ሰፍኖ ነበር።”
ይህ ምስክርነት እንደሚያሳየው፣ ችግሩ የገጸ-ድካም ጉዳይ አልነበረም። ይልቁንም፣ የቤተ ክርስቲያኒቱን ሐዋርያዊ ተልዕኮና የአደረጃጀት መሠረት ያናጋ፣ ብዙዎችን ተስፋ ሊያስቆርጥና ለዓመፅ ወይም ለመለያየት ሊዳርግ የሚችል ጥልቅ መንፈሳዊና መዋቅራዊ ቀውስ ነበር። እንዲህ ባለ ከባድ ወቅት፣ የአንድ አማኝ ቤተ ክርስቲያናዊ ንቃተ ህሊና (ecclesiological consciousness) እና ታማኝነት በእጅጉ ይፈተናል።
፪. የዲያቆን ሃቢብ ጊዮርጊስ መነሣትና የመስዋዕትነት መንገድ
በዚህ መንፈሳዊ ጨለማ ውስጥ ነበር ሃቢብ ጊዮርጊስ የተባለው የብርሃን ሰው የተነሳው። እርሱ በቤተ ክርስቲያን ያደገና ዲያቆን እንደመሆኑ፣ የችግሮቹን ስፋትና ጥልቀት ከውስጥ ሆኖ ተመልክቷል። የቤተ ክርስቲያኒቱን የአስተዳደር ድክመት፣ የአገልጋዮቿን የዕውቀት ማነስና የሕዝቡን መንፈሳዊ ጥማት ተገንዝቧል። ነገር ግን፣ እንደ ብዙዎቹ፣ ጣቱን ለመቀሰር፣ ለማሳጣትና ለማጣጣል፣ የውግዘት ድምፅን ለማሰማት ወይንም በራሱ አካሄድ የቤተክርስቲያኒቷን አካሄድ ልከልስ ማለትን አልመረጠም። ይልቁንም፣ በታማኝ አገልግሎትና ሸክምን በመሸከም ለችግሩ ተግባራዊ ምላሽ ሰጠ። መንገዱ የክስ ሳይሆን የመስዋዕትነት ነበር፤ ይህም በገላትያ 6፡2 ላይ ያለውን “የአንዱን ሸክም አንዱ ይሸከም፣ እንዲሁም የክርስቶስን ሕግ ፈጽሙ” የሚለውን ሐዋርያዊ ትዕዛዝ ሕያው ምስክርነት ነው።
ገና ከወጣትነቱ ጀምሮ ለትምህርት በነበረው ጥልቅ ፍቅር፣ የቤተ ክርስቲያኒቱን ቀጣይ ትውልድ የማነጽ ኃላፊነት በራሱ ላይ ጫነ። የሰንበት ትምህርት ቤቶችን ንቅናቄ በመላ ሀገሪቱ በማደራጀት፣ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ሕፃናትና ወጣቶች የኦርቶዶክሳዊት እምነታቸውን እንዲያውቁና እንዲኖሩባት መሠረት ጣለ። በካይሮ ሥነ-መለኮታዊ ኮሌጅ ውስጥ በአካዳሚክ ዲንነትና በመምህርነት ሲያገለግል፣ ዕውቀትና መንፈሳዊነት የተዋሐደላቸውን አገልጋዮች አፈራ። ድርጊቱ ሁሉ ይመነጭ የነበረው፣ ቤተ ክርስቲያንን በአስተዳደራዊ ድክመቶቿ ውስጥ እያየ እንኳ፣ የማይነቀንቅ የክርስቶስ አካልና የድኅነት ታቦት መሆኗን ካመነበት ጥልቅ ሥነ-መለኮታዊ እምነት ነበር።
ለዚህም ነው ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ሺኖዳ ሣልሳዊ፣ የአንድን ሰው ታማኝ አገልግሎት ፍሬያማነት ሲመሰክሩ፣ እንዲህ ያሉት፡-
“የሰንበት ትምህርት ቤት ንቅናቄ ከሃቢብ ጊዮርጊስ በቀር ሌላ ፍሬ ባያፈራ ኖሮ እንኳ፣ እርሱ ብቻ በቂ ነበር።”
፫. የመዋቅር ድክመትን ከሃይማኖት ስህተት መለየት
የሃቢብ ጊዮርጊስ ጥበብና ሥነ-መለኮታዊ ልሕቀት ከሁሉ በላይ የሚገለጠው፣ በዘመኑ የነበረውን የመዋቅር ድክመት ከቤተ ክርስቲያን ንጽሕተ ሃይማኖት ጋር ባለማደባለቁ ነው። ቤተ ክርስቲያን በትምህርተ መለኮቷ ኑፋቄን ታስተምራለች ብሎ አንድም ቀን አልከሰሰም። ሥርዓቷን አላጣጣለም፤ ቀኖናዎቿንና ይትባሕሎቿን "ካልከለስኩ" አላለም። ችግሩ ያለው በሐዋርያት በኩል በተሰጠችው የቀናች እምነት ላይ ሳይሆን፣ ያችን እምነት በሚያገለግሉና በሚያስተዳድሩ ሰዎች ላይ በሚታየው ድካም እንደሆነ በሚገባ ተረድቶ ነበር።
ይህ መረዳት፣ ቤተ ክርስቲያን መለኮታዊ-ሰብዓዊ (Theanthropic) ተቋም መሆኗን ከመቀበል ይመነጫል።
እርሷ፣ እንደ ክርስቶስ አካል፣ በመለኮታዊ ተፈጥሮዋ ቅድስት፣ ፍጽምትና ከስህተት የጸዳች ናት፤ ነገር ግን በውስጧ የሚያገለግሉት ሰዎች የሰብዓዊ ድካም ተገዢዎች ናቸው። ቅዱሳን አባቶች ይህንን ልዩነት በሚገባ አስተምረዋል። ለምሳሌ፣ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ የክህነትን ቅድስናና የአገልጋዩን ግላዊ ድካም ሲለይ፣ የክህነቱ ኃይል የሚመነጨው ከሰውየው ማንነት ሳይሆን ከክርስቶስ ሹመት መሆኑን ያስረዳል። ቅዱስ ቄርሎስ ዘእስክንድርያም ንስጥሮስን የታገለው፣ የአንጾኪያን ቤተ ክርስቲያን መዋቅር ለመናድ ሳይሆን የተሳሳተውን የሃይማኖት ትምህርት ለማረም ነበር።
ስለሆነም፣ የሃቢብ ጊዮርጊስ መፍትሔ ከቤተ ክርስቲያን ውጭ አዲስ ሥርዓት መመሥረት ሳይሆን፣ በውስጧ በመሆን፣ በትሕትናና በመታዘዝ፣ ያንን ሰብዓዊ ድካም መፈወስና ማነጽ ነበር። ሥራው ሁሉ የሚያሳየው ይህንን ነው፡- በገዛ አረዳዱ "የተበላሸውን" ብሎ የገመተውን የቤተ ክርስቲያንን ትምህርት ለማረም አልሞከረም፤ ይልቁንም ያንን ያልተበረዘ ትምህርት ለተራበው ሕዝብ ለማድረስ ራሱን አሳልፎ ሰጠ።
፬. ትምህርቱ ለዛሬው ትውልድ፡- የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ወቅታዊ ተዛምዶ
ይህ የታሪክ ትምህርት በዘመናችን ላለችው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ጥልቅና አስቸኳይ መልእክት አለው። ዛሬ በርካታ ምእመናን በአስተዳደራዊ ብልሽቶች፣ በመንፈሳዊ አመራር ድክመትና በአንዳንድ አገልጋዮች ሥነ ምግባር ጉድለት የተነሣ በብስጭትና በቅሬታ ተሞልተዋል። ይህ ስሜት መነሻው ቅን ሊሆን ይችላል።
ችግሩ ያለው ለዚህ ስሜት በሚሰጠው ምላሽ ላይ ነው። ብዙዎች፣ ልክ በሃቢብ ጊዮርጊስ ዘመን እንደነበሩት ተቺዎች፣ መላዋን ቤተ ክርስቲያንን ይወቅሳሉ፤ ሐዋርያዊ ትውፊቷን ይጠራጠራሉ፤ አልፎ ተርፎም በግል አስተያየታቸውና ፍልስፍናቸው ያንን ትውፊት ለመተካት ይዳዳሉ። ከዚህም የከፋው፣ በቤተ ክርስቲያን ውስጥ ትይዩ መዋቅሮችንና ርዕዮተ ዓለሞችን ለመገንባት መሞከር ነው፤ ይህም አንድነቷንና ሐዋርያዊ ሥርዓቷን በእጅጉ ይጎዳል። ይህ አካሄድ፣ የቅዱስ ኢግናጥዮስ ዘአንጾኪያ "ከኤጲስ ቆጶሱ ውጭ ምንም ነገር አታድርጉ" የሚለውን ሐዋርያዊ መመሪያ የሚጻረር ነው።
፭. ኦርቶዶክሳዊው የማነጽ መንገድ፡-
ኦርቶዶክሳዊ አስተምህሮ ቤተ ክርስቲያንን የምትረዳበትና የማነጽ አካሄዷ ግልጽ ነው። ቅዱስ ጳውሎስ በኤፌሶን 4፡11–13 ላይ፣ ክርስቶስ ራሱ ለቤተ ክርስቲያኑ "ሐዋርያትንና ነቢያትን፣ ወንጌላውያንንም፣ እረኞችንና አስተማሪዎችንም" የሰጠው፣ "ቅዱሳን … ፍጹማን ይሆኑ ዘንድ፣ ለክርስቶስም አካል ሕንጻ" እንደሆነ ያስረዳል። መዋቅርና ሥርዓት የተሰጠው ለማነጽ እንጂ ለመበታተን አይደለም።
የማረምና የማነጽ ሥራ እንዴት መከናወን እንዳለበትም መጽሐፍ ቅዱስ በግልጽ ያስቀምጣል። በይሁዳ መልእክት 1፡22 ላይ "አንዳንዶችንም በምትለዩበት ጊዜ፣ ምሕረት አድርጉላቸው፤ ሌሎችን ግን ከእሳት እየነጠቃችሁ በፍርሃት አድኗቸው" ይላል። ይህ ቃል፣ ችግሮችን የምንቀርብበት መንገድ በጥበብና በልዩነት መሆን እንዳለበት ያስተምራል እንጂ ሁሉን በአንድ ላይ የመውቀስ አካሄድን አይደግፍም።
፩. የዘመኑ ታሪካዊ ቀውስና የቤተ ክርስቲያን ፈተና
በዐሥራ ዘጠነኛው መቶ ክፍለ ዘመን መገባደጃና በሃያኛው መቶ ክፍለ ዘመን መባቻ ላይ፣ የግብጽ ኮፕቲክ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን በታሪኳ እጅግ ውስብስብ ከሆኑት ፈተናዎች እያስተናገደች ነበር። ቀውሱ የውጭ ጫና ብቻ ሳይሆን፣ ከውስጥ የመነጨና የቤተ ክርስቲያኒቱን ሕልውና የሚፈታተን ነበር። ይህ ድክመት በአስተዳደር መላሸቅ፣ በመልካም አስተዳደር እጦት፣ በሙስናና በአንዳንድ አገልጋዮች የሥነ ምግባር ውድቀት ተገልጧል። ከዚህም በላይ፣ የትምህርተ ሃይማኖት ዕውቀት በእጅጉ ተዳክሞ፣ የመንፈሳዊ አገልግሎት ጥራትና ስፋት በእጅጉ ቀንሶ ነበር።
ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ሺኖዳ ሣልሳዊ፣ የዚያን ዘመን አሳሳቢ ገጽታ ሲመሰክሩ እንዲህ በማለት ሁኔታውን ያጠቃልሉታል፡-
“በሃያኛው ክፍለ ዘመን መጀመሪያ ላይ፣ ስብከቶች ደረቅና ሕይወት አልባ ነበሩ፤ መንፈሳዊ ትምህርት ቤቶች ከሞላ ጎደል አልነበሩም፤ ድንቁርና በቤተ ክርስቲያኒቱ ውስጥ፣ እንዲያውም በቀሳውስቱ መካከል እንኳ ሰፍኖ ነበር።”
ይህ ምስክርነት እንደሚያሳየው፣ ችግሩ የገጸ-ድካም ጉዳይ አልነበረም። ይልቁንም፣ የቤተ ክርስቲያኒቱን ሐዋርያዊ ተልዕኮና የአደረጃጀት መሠረት ያናጋ፣ ብዙዎችን ተስፋ ሊያስቆርጥና ለዓመፅ ወይም ለመለያየት ሊዳርግ የሚችል ጥልቅ መንፈሳዊና መዋቅራዊ ቀውስ ነበር። እንዲህ ባለ ከባድ ወቅት፣ የአንድ አማኝ ቤተ ክርስቲያናዊ ንቃተ ህሊና (ecclesiological consciousness) እና ታማኝነት በእጅጉ ይፈተናል።
፪. የዲያቆን ሃቢብ ጊዮርጊስ መነሣትና የመስዋዕትነት መንገድ
በዚህ መንፈሳዊ ጨለማ ውስጥ ነበር ሃቢብ ጊዮርጊስ የተባለው የብርሃን ሰው የተነሳው። እርሱ በቤተ ክርስቲያን ያደገና ዲያቆን እንደመሆኑ፣ የችግሮቹን ስፋትና ጥልቀት ከውስጥ ሆኖ ተመልክቷል። የቤተ ክርስቲያኒቱን የአስተዳደር ድክመት፣ የአገልጋዮቿን የዕውቀት ማነስና የሕዝቡን መንፈሳዊ ጥማት ተገንዝቧል። ነገር ግን፣ እንደ ብዙዎቹ፣ ጣቱን ለመቀሰር፣ ለማሳጣትና ለማጣጣል፣ የውግዘት ድምፅን ለማሰማት ወይንም በራሱ አካሄድ የቤተክርስቲያኒቷን አካሄድ ልከልስ ማለትን አልመረጠም። ይልቁንም፣ በታማኝ አገልግሎትና ሸክምን በመሸከም ለችግሩ ተግባራዊ ምላሽ ሰጠ። መንገዱ የክስ ሳይሆን የመስዋዕትነት ነበር፤ ይህም በገላትያ 6፡2 ላይ ያለውን “የአንዱን ሸክም አንዱ ይሸከም፣ እንዲሁም የክርስቶስን ሕግ ፈጽሙ” የሚለውን ሐዋርያዊ ትዕዛዝ ሕያው ምስክርነት ነው።
ገና ከወጣትነቱ ጀምሮ ለትምህርት በነበረው ጥልቅ ፍቅር፣ የቤተ ክርስቲያኒቱን ቀጣይ ትውልድ የማነጽ ኃላፊነት በራሱ ላይ ጫነ። የሰንበት ትምህርት ቤቶችን ንቅናቄ በመላ ሀገሪቱ በማደራጀት፣ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ሕፃናትና ወጣቶች የኦርቶዶክሳዊት እምነታቸውን እንዲያውቁና እንዲኖሩባት መሠረት ጣለ። በካይሮ ሥነ-መለኮታዊ ኮሌጅ ውስጥ በአካዳሚክ ዲንነትና በመምህርነት ሲያገለግል፣ ዕውቀትና መንፈሳዊነት የተዋሐደላቸውን አገልጋዮች አፈራ። ድርጊቱ ሁሉ ይመነጭ የነበረው፣ ቤተ ክርስቲያንን በአስተዳደራዊ ድክመቶቿ ውስጥ እያየ እንኳ፣ የማይነቀንቅ የክርስቶስ አካልና የድኅነት ታቦት መሆኗን ካመነበት ጥልቅ ሥነ-መለኮታዊ እምነት ነበር።
ለዚህም ነው ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ሺኖዳ ሣልሳዊ፣ የአንድን ሰው ታማኝ አገልግሎት ፍሬያማነት ሲመሰክሩ፣ እንዲህ ያሉት፡-
“የሰንበት ትምህርት ቤት ንቅናቄ ከሃቢብ ጊዮርጊስ በቀር ሌላ ፍሬ ባያፈራ ኖሮ እንኳ፣ እርሱ ብቻ በቂ ነበር።”
፫. የመዋቅር ድክመትን ከሃይማኖት ስህተት መለየት
የሃቢብ ጊዮርጊስ ጥበብና ሥነ-መለኮታዊ ልሕቀት ከሁሉ በላይ የሚገለጠው፣ በዘመኑ የነበረውን የመዋቅር ድክመት ከቤተ ክርስቲያን ንጽሕተ ሃይማኖት ጋር ባለማደባለቁ ነው። ቤተ ክርስቲያን በትምህርተ መለኮቷ ኑፋቄን ታስተምራለች ብሎ አንድም ቀን አልከሰሰም። ሥርዓቷን አላጣጣለም፤ ቀኖናዎቿንና ይትባሕሎቿን "ካልከለስኩ" አላለም። ችግሩ ያለው በሐዋርያት በኩል በተሰጠችው የቀናች እምነት ላይ ሳይሆን፣ ያችን እምነት በሚያገለግሉና በሚያስተዳድሩ ሰዎች ላይ በሚታየው ድካም እንደሆነ በሚገባ ተረድቶ ነበር።
ይህ መረዳት፣ ቤተ ክርስቲያን መለኮታዊ-ሰብዓዊ (Theanthropic) ተቋም መሆኗን ከመቀበል ይመነጫል።
እርሷ፣ እንደ ክርስቶስ አካል፣ በመለኮታዊ ተፈጥሮዋ ቅድስት፣ ፍጽምትና ከስህተት የጸዳች ናት፤ ነገር ግን በውስጧ የሚያገለግሉት ሰዎች የሰብዓዊ ድካም ተገዢዎች ናቸው። ቅዱሳን አባቶች ይህንን ልዩነት በሚገባ አስተምረዋል። ለምሳሌ፣ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ የክህነትን ቅድስናና የአገልጋዩን ግላዊ ድካም ሲለይ፣ የክህነቱ ኃይል የሚመነጨው ከሰውየው ማንነት ሳይሆን ከክርስቶስ ሹመት መሆኑን ያስረዳል። ቅዱስ ቄርሎስ ዘእስክንድርያም ንስጥሮስን የታገለው፣ የአንጾኪያን ቤተ ክርስቲያን መዋቅር ለመናድ ሳይሆን የተሳሳተውን የሃይማኖት ትምህርት ለማረም ነበር።
ስለሆነም፣ የሃቢብ ጊዮርጊስ መፍትሔ ከቤተ ክርስቲያን ውጭ አዲስ ሥርዓት መመሥረት ሳይሆን፣ በውስጧ በመሆን፣ በትሕትናና በመታዘዝ፣ ያንን ሰብዓዊ ድካም መፈወስና ማነጽ ነበር። ሥራው ሁሉ የሚያሳየው ይህንን ነው፡- በገዛ አረዳዱ "የተበላሸውን" ብሎ የገመተውን የቤተ ክርስቲያንን ትምህርት ለማረም አልሞከረም፤ ይልቁንም ያንን ያልተበረዘ ትምህርት ለተራበው ሕዝብ ለማድረስ ራሱን አሳልፎ ሰጠ።
፬. ትምህርቱ ለዛሬው ትውልድ፡- የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ወቅታዊ ተዛምዶ
ይህ የታሪክ ትምህርት በዘመናችን ላለችው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ጥልቅና አስቸኳይ መልእክት አለው። ዛሬ በርካታ ምእመናን በአስተዳደራዊ ብልሽቶች፣ በመንፈሳዊ አመራር ድክመትና በአንዳንድ አገልጋዮች ሥነ ምግባር ጉድለት የተነሣ በብስጭትና በቅሬታ ተሞልተዋል። ይህ ስሜት መነሻው ቅን ሊሆን ይችላል።
ችግሩ ያለው ለዚህ ስሜት በሚሰጠው ምላሽ ላይ ነው። ብዙዎች፣ ልክ በሃቢብ ጊዮርጊስ ዘመን እንደነበሩት ተቺዎች፣ መላዋን ቤተ ክርስቲያንን ይወቅሳሉ፤ ሐዋርያዊ ትውፊቷን ይጠራጠራሉ፤ አልፎ ተርፎም በግል አስተያየታቸውና ፍልስፍናቸው ያንን ትውፊት ለመተካት ይዳዳሉ። ከዚህም የከፋው፣ በቤተ ክርስቲያን ውስጥ ትይዩ መዋቅሮችንና ርዕዮተ ዓለሞችን ለመገንባት መሞከር ነው፤ ይህም አንድነቷንና ሐዋርያዊ ሥርዓቷን በእጅጉ ይጎዳል። ይህ አካሄድ፣ የቅዱስ ኢግናጥዮስ ዘአንጾኪያ "ከኤጲስ ቆጶሱ ውጭ ምንም ነገር አታድርጉ" የሚለውን ሐዋርያዊ መመሪያ የሚጻረር ነው።
፭. ኦርቶዶክሳዊው የማነጽ መንገድ፡-
ኦርቶዶክሳዊ አስተምህሮ ቤተ ክርስቲያንን የምትረዳበትና የማነጽ አካሄዷ ግልጽ ነው። ቅዱስ ጳውሎስ በኤፌሶን 4፡11–13 ላይ፣ ክርስቶስ ራሱ ለቤተ ክርስቲያኑ "ሐዋርያትንና ነቢያትን፣ ወንጌላውያንንም፣ እረኞችንና አስተማሪዎችንም" የሰጠው፣ "ቅዱሳን … ፍጹማን ይሆኑ ዘንድ፣ ለክርስቶስም አካል ሕንጻ" እንደሆነ ያስረዳል። መዋቅርና ሥርዓት የተሰጠው ለማነጽ እንጂ ለመበታተን አይደለም።
የማረምና የማነጽ ሥራ እንዴት መከናወን እንዳለበትም መጽሐፍ ቅዱስ በግልጽ ያስቀምጣል። በይሁዳ መልእክት 1፡22 ላይ "አንዳንዶችንም በምትለዩበት ጊዜ፣ ምሕረት አድርጉላቸው፤ ሌሎችን ግን ከእሳት እየነጠቃችሁ በፍርሃት አድኗቸው" ይላል። ይህ ቃል፣ ችግሮችን የምንቀርብበት መንገድ በጥበብና በልዩነት መሆን እንዳለበት ያስተምራል እንጂ ሁሉን በአንድ ላይ የመውቀስ አካሄድን አይደግፍም።
ዋናው መሠረታዊ እውነት ይህ ነው፡- እውነተኛ ለውጥና ትንሳኤ የሚመጣው ቤተክርስቲያንን በመክስና በግላዊ የክለሳ አካሄድ ሳይሆን፣ በታማኝ አገልግሎትና የጋራ ሸክምን በመሸከም ነው።
፮. ሸክሙን መሸከም ወይስ ጣትን መቀሰር?
ቤተ ክርስቲያን ዛሬ የምትፈልገው ተጨማሪ ከሳሾችንና በማኅበራዊ ሚዲያ ላይ የሚተቹትን አይደለም፤ የምትፈልገው የሃቢብ ጊዮርጊስን ዓይነት መንፈስ የተላበሱ ልጆችን ነው። ችግሩን ከማራገብ ይልቅ የመፍትሔው አካል የሚሆኑትን፤ የቤተ ክርስቲያንን ሸክም በትከሻቸው ተሸክመው የክርስቶስን ሕግ የሚፈጽሙትን።
ስለዚህ፣ እያንዳንዱ የበሰለ ኦርቶዶክሳዊ አማኝ ራሱን ሊጠይቅ ይገባል፡- እኔ የቤተ ክርስቲያንን ሸክም አግዤ እየተሸከምኩ ነው? ወይስ በቁስሏ ላይ ጣቴን እየቀሰርኩ፣ የውግዘት ድንጋይ እየወረወርኩ ነው?
የዛሬው ጥሪ፣ ልክ እንደ ሃቢብ ጊዮርጊስ፣ ኃላፊነትን መውሰድ ነው። ይህ ደግሞ በፍቅር፣ በዲሲፕሊን፣ በትሕትናና በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስና እርሱ አካሉ በሆነችው ቤተ ክርስቲያኑ ላይ ባለ ጽኑ እምነት የሚከናወን የተቀደሰ ተግባር ነው።
©አቦርሃም ሲሳይ
#ለመቀላቀል
@ortodoxtewahedo
#ለሃሳብ አስተያየት
@ortodoxtewahedoo
#ወስብሐት_ለእግዚአብሔር
፮. ሸክሙን መሸከም ወይስ ጣትን መቀሰር?
ቤተ ክርስቲያን ዛሬ የምትፈልገው ተጨማሪ ከሳሾችንና በማኅበራዊ ሚዲያ ላይ የሚተቹትን አይደለም፤ የምትፈልገው የሃቢብ ጊዮርጊስን ዓይነት መንፈስ የተላበሱ ልጆችን ነው። ችግሩን ከማራገብ ይልቅ የመፍትሔው አካል የሚሆኑትን፤ የቤተ ክርስቲያንን ሸክም በትከሻቸው ተሸክመው የክርስቶስን ሕግ የሚፈጽሙትን።
ስለዚህ፣ እያንዳንዱ የበሰለ ኦርቶዶክሳዊ አማኝ ራሱን ሊጠይቅ ይገባል፡- እኔ የቤተ ክርስቲያንን ሸክም አግዤ እየተሸከምኩ ነው? ወይስ በቁስሏ ላይ ጣቴን እየቀሰርኩ፣ የውግዘት ድንጋይ እየወረወርኩ ነው?
የዛሬው ጥሪ፣ ልክ እንደ ሃቢብ ጊዮርጊስ፣ ኃላፊነትን መውሰድ ነው። ይህ ደግሞ በፍቅር፣ በዲሲፕሊን፣ በትሕትናና በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስና እርሱ አካሉ በሆነችው ቤተ ክርስቲያኑ ላይ ባለ ጽኑ እምነት የሚከናወን የተቀደሰ ተግባር ነው።
©አቦርሃም ሲሳይ
#ለመቀላቀል
@ortodoxtewahedo
#ለሃሳብ አስተያየት
@ortodoxtewahedoo
#ወስብሐት_ለእግዚአብሔር
🔴ድንቅ ወቅታዊ መልእክት‼️የዘመኑ የም...
መንክር ሚዲያ-Menker Media
✝የዘመኑ ምንኩስና ሕይወት ከቀደሙት ጋር ሲነጻጸር✝
Size:-76.8MB
Length:-1:22:58
በርእሰ ሊቃውንት አባ ገብረ ኪዳን ግርማ
#ለመቀላቀል
@ortodoxtewahedo
#ለሃሳብ አስተያየት
@ortodoxtewahedoo
#ወስብሐት_ለእግዚአብሔር
Size:-76.8MB
Length:-1:22:58
በርእሰ ሊቃውንት አባ ገብረ ኪዳን ግርማ
#ለመቀላቀል
@ortodoxtewahedo
#ለሃሳብ አስተያየት
@ortodoxtewahedoo
#ወስብሐት_ለእግዚአብሔር
#ወንድማችንን ፍቱት
ሊቀ ትጉኅን ደረጀ ነጋሽ (ዘወይንዬ) ዛሬ ከግል ቢሮአቸዉ ወጥተዉ ወደ ተሽከርካሪያቸዉ ሲያመሩ ለጥያቄ እንፈልግዎታለን ተብለዉ ደህንነት ነን ባሉ አካላት መወሰዳቸዉን ከቤተሰቦቻቸዉና ከሥራ ባልደረቦቻቸው ከሰማን ቀናት አለፊ ።
ይሁን እንጂ መምህር ደረጀ ነጋሽ እስከ አሁን ያሉበትን ፖሊስ ጣቢያ ለማወቅ አልታቻለም።
#ለመቀላቀል
@ortodoxtewahedo
#ለሃሳብ አስተያየት
@ortodoxtewahedoo
#ወስብሐት_ለእግዚአብሔር
ሊቀ ትጉኅን ደረጀ ነጋሽ (ዘወይንዬ) ዛሬ ከግል ቢሮአቸዉ ወጥተዉ ወደ ተሽከርካሪያቸዉ ሲያመሩ ለጥያቄ እንፈልግዎታለን ተብለዉ ደህንነት ነን ባሉ አካላት መወሰዳቸዉን ከቤተሰቦቻቸዉና ከሥራ ባልደረቦቻቸው ከሰማን ቀናት አለፊ ።
ይሁን እንጂ መምህር ደረጀ ነጋሽ እስከ አሁን ያሉበትን ፖሊስ ጣቢያ ለማወቅ አልታቻለም።
#ለመቀላቀል
@ortodoxtewahedo
#ለሃሳብ አስተያየት
@ortodoxtewahedoo
#ወስብሐት_ለእግዚአብሔር
#በከንቱ_አምተናታል
ዮሴፍ በጽኑ መረበሽ የተያዘበት ወቅት ነበር። የእመቤታችን መፀነስ ከሚያወቀው ተፈጥሯዊ አካሔድ ውጪ ስለሆነበት ልቡ ክፉኛ ተሸብሮ ነበር። በእርግጥ ዮሴፍ በእመቤታችን መፀነስ መደናገጡ ብዙም ላያስደንቅ ይችላል። መካን ሆነው ሳለ በልመናቸው ብርታት የወለዱ አሉ÷ እንደነ ሣራ በስተርጅናቸው የፀነሱም አሉ። የእርሷ ግን የተለየ ነው በድንግልና የወለደ ከእርሷ በፊትም ይሁን ከእርሷም በኋላ አልተገኘም።
መጻሕፍት እንደሚነግሩን ዮሴፍ ግን ከመደነቅ ይልቅ ከንግድ ሲመለስ ያገኘው ፈላስፋው ዮሐንስ "ይህቺ ሴት ካንተ ነው የፀነሰችው" ብሎ የተናገረው ቃል ከድንጋጤ አድርሶታል። በዚህም ምክንያት ነበር "መኑ ቀረጸ አክናፈ ድንግልናኪ" ብሎ የመፀነሷን ነገር የጠየቃት። ንጽሕት የሆነች እርሷ ግን "መልአኩ አክብሮ ከነገረኝ ውጪ ሌላ ምንም የማውቀው የለም አለችው" የእመቤታችን ትሕትና መግለጽ የሚቻለው አንደበት የለም ቃሏና ምላሿ ሁሉ በትሕትና የታሹ ናቸው።
ዮሴፍ አሁንም ቢሆን ከጥርጣሬው መዳን አልቻልም አንድ አንድ ጊዜ ፍርሐት እና የሰዎችን ወቀሳ ማስታወስ ወደ ጥርጣሬ አሮንቃ ውስጥ ይከተናል አረጋዊው ዮሴፍም የሆነው እንዲሁ ነው። ይህንን ጥርጣሬውን ልታስወግድለት የወደደች እመቤታችን ግን አአዕዋፍ እንዲራቡ የሚያደርግ አአዕዋም እንዲያፈሩ የሚያደርግ ማን ምስሎሃል? ብላ ከግሰጸችው በኋላ ከደጃቸው የቆመ ደረቅ ግንድ ነበር እርሱን አለምልማ አሳየችው። መልአኩ ትፀንሺያለሽ ብሎ ባበሠራት ወቅት ይህ እንዴት ይሆንልኛል ብትለው "ለእግዚአብሔር የሚሳነው ነገር የለም" ብሎ የመለሰላትና እርሷ በተግባር አሳየችው። በተረቱበት መርታት ልማድ ነው።
እመቤታን ያለውንድ ዘር በድንግልና የመጸነሷ ነገር ምትሐት ሳይሆን የእግዚአብሔር ሥራ መሆኑን ብትገልጥለትም። ለቆጠራ ወቅት ግን ይዟት ይወጣ ዘንድ ፈራ። ከእግዚአብሔር ሥራ ይልቅ ፍርሐታችንን እናምነዋለን በዚህም በተሳሳተ እምነታችን የእግዚአብሔር ዓላማ አደናቃፊዎች ሆነን እንገኛለን። ዮሴፍም ያለ ወንድ ዘር እንድትጸንስ ያደረገውን የእግዚአብሔርን ሐይል ሳያስተውል ይዟት ሲወጣ ግን አይሁዶች ሊፈጥሩት የሚችሉት ትንኮሳ አስፈራው።
ይዟት ቢወጣ ሕጋቸውን ቢያስቀራት ደግሞ ያደረገውን ዓውቆ ጥሏት ወጣ እንዳይሉ ወሪያቸውን ፈርቶ ሳለ መልአኩ ከያዘው ፍርሐት አርቆ ይዟት ይወጣ ዘንድ አዘዘው። ዮሴፍ በመልአኩ ትዕዛዝ ይዟት ቢወጣም የዲያቢሎስ የግብር ልጆች የሚሆኑ በትጠጣው ለሞት የሚያደርሳትን ማየ ዘለፋን ትጠጣልን አሉ። የአምላክ እናት እርሷ ግን ማየ ዘለፋን ከጠጣችው በኋላ እነርሱ እንዳሰቡት ሳይሆን ከወትሮው አበራች ጽድልት ሆና ታየች ከፀሐይ ይልቅ አብርታ ተገኘች በጊዜ የተቀሩት አይሁድም ይህን ቢመለከቱ "ይህችን ብላቴና በከንቱ አምተናታል" አሉ።
የእመቤታችንን ክብር ከመናገር እርቀው በከንቱ የሚያሙ ሰዎች የበቀሉት ገና በማኅጸን ሳለች ነው። መወለዷን የጠሉ ዳግመኛ የመውለዷን ነገር አለወደድዱምና በጊዜው ነውር እንደተገኘባቸው ሴቶች እርሷን በከንቱ አሟት። እውነት ደቆ ሐስት ረቆ ባየለበት በእኛ ዘመንም ዓይነ ልቦናቸው የታወረባቸው በከንቱ ያማሉ። የእግዚአብሔርን ሳይሆን የግብር አባታቸውን የዲያቢሎስን ድምፅ እየሰሙ በቅዱሳኑ ላይ በከንቱ ይናገራሉ። ከሁሉ ልቆ የታየው ግን የአይሁድ ከንቱ የሆነው ሐሜታቸው ሳይሆን ስለ ክፉ ፈንታ ክፉ ያለመለሰች የእመቤታችን ትሕትና ነበር።
ዲ/ን ሞገስ አብርሃም
#ለመቀላቀል
@ortodoxtewahedo
#ለሃሳብ አስተያየት
@ortodoxtewahedoo
#ወስብሐት_ለእግዚአብሔር
ዮሴፍ በጽኑ መረበሽ የተያዘበት ወቅት ነበር። የእመቤታችን መፀነስ ከሚያወቀው ተፈጥሯዊ አካሔድ ውጪ ስለሆነበት ልቡ ክፉኛ ተሸብሮ ነበር። በእርግጥ ዮሴፍ በእመቤታችን መፀነስ መደናገጡ ብዙም ላያስደንቅ ይችላል። መካን ሆነው ሳለ በልመናቸው ብርታት የወለዱ አሉ÷ እንደነ ሣራ በስተርጅናቸው የፀነሱም አሉ። የእርሷ ግን የተለየ ነው በድንግልና የወለደ ከእርሷ በፊትም ይሁን ከእርሷም በኋላ አልተገኘም።
መጻሕፍት እንደሚነግሩን ዮሴፍ ግን ከመደነቅ ይልቅ ከንግድ ሲመለስ ያገኘው ፈላስፋው ዮሐንስ "ይህቺ ሴት ካንተ ነው የፀነሰችው" ብሎ የተናገረው ቃል ከድንጋጤ አድርሶታል። በዚህም ምክንያት ነበር "መኑ ቀረጸ አክናፈ ድንግልናኪ" ብሎ የመፀነሷን ነገር የጠየቃት። ንጽሕት የሆነች እርሷ ግን "መልአኩ አክብሮ ከነገረኝ ውጪ ሌላ ምንም የማውቀው የለም አለችው" የእመቤታችን ትሕትና መግለጽ የሚቻለው አንደበት የለም ቃሏና ምላሿ ሁሉ በትሕትና የታሹ ናቸው።
ዮሴፍ አሁንም ቢሆን ከጥርጣሬው መዳን አልቻልም አንድ አንድ ጊዜ ፍርሐት እና የሰዎችን ወቀሳ ማስታወስ ወደ ጥርጣሬ አሮንቃ ውስጥ ይከተናል አረጋዊው ዮሴፍም የሆነው እንዲሁ ነው። ይህንን ጥርጣሬውን ልታስወግድለት የወደደች እመቤታችን ግን አአዕዋፍ እንዲራቡ የሚያደርግ አአዕዋም እንዲያፈሩ የሚያደርግ ማን ምስሎሃል? ብላ ከግሰጸችው በኋላ ከደጃቸው የቆመ ደረቅ ግንድ ነበር እርሱን አለምልማ አሳየችው። መልአኩ ትፀንሺያለሽ ብሎ ባበሠራት ወቅት ይህ እንዴት ይሆንልኛል ብትለው "ለእግዚአብሔር የሚሳነው ነገር የለም" ብሎ የመለሰላትና እርሷ በተግባር አሳየችው። በተረቱበት መርታት ልማድ ነው።
እመቤታን ያለውንድ ዘር በድንግልና የመጸነሷ ነገር ምትሐት ሳይሆን የእግዚአብሔር ሥራ መሆኑን ብትገልጥለትም። ለቆጠራ ወቅት ግን ይዟት ይወጣ ዘንድ ፈራ። ከእግዚአብሔር ሥራ ይልቅ ፍርሐታችንን እናምነዋለን በዚህም በተሳሳተ እምነታችን የእግዚአብሔር ዓላማ አደናቃፊዎች ሆነን እንገኛለን። ዮሴፍም ያለ ወንድ ዘር እንድትጸንስ ያደረገውን የእግዚአብሔርን ሐይል ሳያስተውል ይዟት ሲወጣ ግን አይሁዶች ሊፈጥሩት የሚችሉት ትንኮሳ አስፈራው።
ይዟት ቢወጣ ሕጋቸውን ቢያስቀራት ደግሞ ያደረገውን ዓውቆ ጥሏት ወጣ እንዳይሉ ወሪያቸውን ፈርቶ ሳለ መልአኩ ከያዘው ፍርሐት አርቆ ይዟት ይወጣ ዘንድ አዘዘው። ዮሴፍ በመልአኩ ትዕዛዝ ይዟት ቢወጣም የዲያቢሎስ የግብር ልጆች የሚሆኑ በትጠጣው ለሞት የሚያደርሳትን ማየ ዘለፋን ትጠጣልን አሉ። የአምላክ እናት እርሷ ግን ማየ ዘለፋን ከጠጣችው በኋላ እነርሱ እንዳሰቡት ሳይሆን ከወትሮው አበራች ጽድልት ሆና ታየች ከፀሐይ ይልቅ አብርታ ተገኘች በጊዜ የተቀሩት አይሁድም ይህን ቢመለከቱ "ይህችን ብላቴና በከንቱ አምተናታል" አሉ።
የእመቤታችንን ክብር ከመናገር እርቀው በከንቱ የሚያሙ ሰዎች የበቀሉት ገና በማኅጸን ሳለች ነው። መወለዷን የጠሉ ዳግመኛ የመውለዷን ነገር አለወደድዱምና በጊዜው ነውር እንደተገኘባቸው ሴቶች እርሷን በከንቱ አሟት። እውነት ደቆ ሐስት ረቆ ባየለበት በእኛ ዘመንም ዓይነ ልቦናቸው የታወረባቸው በከንቱ ያማሉ። የእግዚአብሔርን ሳይሆን የግብር አባታቸውን የዲያቢሎስን ድምፅ እየሰሙ በቅዱሳኑ ላይ በከንቱ ይናገራሉ። ከሁሉ ልቆ የታየው ግን የአይሁድ ከንቱ የሆነው ሐሜታቸው ሳይሆን ስለ ክፉ ፈንታ ክፉ ያለመለሰች የእመቤታችን ትሕትና ነበር።
ዲ/ን ሞገስ አብርሃም
#ለመቀላቀል
@ortodoxtewahedo
#ለሃሳብ አስተያየት
@ortodoxtewahedoo
#ወስብሐት_ለእግዚአብሔር
ወመኑ መሐሪ ዘከማከ፤ ወመኑ መሐሪ ዘከማከ፤ ምስለ ኖኅ
ኪዳነ ዘአቀምከ፤ ለደቂቀ እስራኤል መና ዘአውረድከ፤
ወመኑ መሐሪ ዘከማከ፤ ወበጽጌያት ምድረ አሠርጎከ፤ ወሥነ
ገዳምኒ ምስለ ቅዱሳኒከ፤ ወመኑ መሐሪ ዘከማከ፤ ወከመ
ወሬዛ ኃየል መላትሒሁ ጉርዔሁ መዓርዒር አምሳሉ
ዘወይጠል፤ ወመኑ መሐሪ ዘከማከ፤ ሰማየ ወምድረ ዘአንተ
ፈጠርከ፤ ፀሐየ ወወርኀ ዘአስተዋደድከ፤ ወመኑ መሐሪ
ዘከማከ፤ በከዋክብት ሰማየ ዘከለልከ፤ ወመኑ መሐሪ
ዘከማከ፤ ወበጽጌያት ምድረ አሠርጎከ፤ ወመኑ መሐሪ
ዘከማከ፤ ቀደሳ ወአክበራ አዕበያ ለሰንበት፤ ወአልዓላ
እምኵሉ ዕለት፤ ወመኑ መሐሪ ዘከማከ፤ ወኵሉ ይሴፎ ኪያከ፤
#ትርጉም
ከኖኅ ጋር ቃል ኪዳን የገባህ እንዳንተ ይቅር ባይ ማነው
ለእስራኤል ልጆች መናን ያወረድክ፤ ምድርን በአበቦች
ያስጌጥክ፤ እንዳንተ ይቅር ባይ ማነው ? የምድረ በዳውን
አራዊት ከወዳጆችህ ጋር ያስማማህ እንዳንተ ያለ ይቅር ባይ
ማነው፤ ጉንጮቹ እንደ ዋልያ እንቦሳ ፈጣኖች ናቸው፤
አንደበቱ ጣፋጭ ነው፤ ተወዳጅነቱ እንደ ፌቆ ግልገል ነው፤
ሰማይና ምድርን የፈጠርክ፤ ፀሐይና ጨረቃን ያስማማህ፤
ሰማይን በከዋክብት የሸፈንክ፤ ምድርን በአበቦች ያሸበረቅህ፤
ሰንበትን ያከበርካት ከዕለታትም ለይተህ ከፍከፍያደረግኻት፤
አቤት!! እንዳንተ ይቅር ባይ ማንም የለምና ኹሉም አንተን
ተስፋ ያደርጋሉ።
#እንኳን_ለዓለም_ጌታ_ለፍጥረታት_አምላክ_ለነገስታት_ንጉስ_ልዑለ_ባህሪ_ለሆነው_ለአምላካችን_ለመድሐኒታችን_መድኃኒዓለም_ወርሀዊ_በዓል_አደረሰን !
#ለመቀላቀል
@ortodoxtewahedo
#ለሃሳብ አስተያየት
@ortodoxtewahedoo
#ወስብሐት_ለእግዚአብሔር
ኪዳነ ዘአቀምከ፤ ለደቂቀ እስራኤል መና ዘአውረድከ፤
ወመኑ መሐሪ ዘከማከ፤ ወበጽጌያት ምድረ አሠርጎከ፤ ወሥነ
ገዳምኒ ምስለ ቅዱሳኒከ፤ ወመኑ መሐሪ ዘከማከ፤ ወከመ
ወሬዛ ኃየል መላትሒሁ ጉርዔሁ መዓርዒር አምሳሉ
ዘወይጠል፤ ወመኑ መሐሪ ዘከማከ፤ ሰማየ ወምድረ ዘአንተ
ፈጠርከ፤ ፀሐየ ወወርኀ ዘአስተዋደድከ፤ ወመኑ መሐሪ
ዘከማከ፤ በከዋክብት ሰማየ ዘከለልከ፤ ወመኑ መሐሪ
ዘከማከ፤ ወበጽጌያት ምድረ አሠርጎከ፤ ወመኑ መሐሪ
ዘከማከ፤ ቀደሳ ወአክበራ አዕበያ ለሰንበት፤ ወአልዓላ
እምኵሉ ዕለት፤ ወመኑ መሐሪ ዘከማከ፤ ወኵሉ ይሴፎ ኪያከ፤
#ትርጉም
ከኖኅ ጋር ቃል ኪዳን የገባህ እንዳንተ ይቅር ባይ ማነው
ለእስራኤል ልጆች መናን ያወረድክ፤ ምድርን በአበቦች
ያስጌጥክ፤ እንዳንተ ይቅር ባይ ማነው ? የምድረ በዳውን
አራዊት ከወዳጆችህ ጋር ያስማማህ እንዳንተ ያለ ይቅር ባይ
ማነው፤ ጉንጮቹ እንደ ዋልያ እንቦሳ ፈጣኖች ናቸው፤
አንደበቱ ጣፋጭ ነው፤ ተወዳጅነቱ እንደ ፌቆ ግልገል ነው፤
ሰማይና ምድርን የፈጠርክ፤ ፀሐይና ጨረቃን ያስማማህ፤
ሰማይን በከዋክብት የሸፈንክ፤ ምድርን በአበቦች ያሸበረቅህ፤
ሰንበትን ያከበርካት ከዕለታትም ለይተህ ከፍከፍያደረግኻት፤
አቤት!! እንዳንተ ይቅር ባይ ማንም የለምና ኹሉም አንተን
ተስፋ ያደርጋሉ።
#እንኳን_ለዓለም_ጌታ_ለፍጥረታት_አምላክ_ለነገስታት_ንጉስ_ልዑለ_ባህሪ_ለሆነው_ለአምላካችን_ለመድሐኒታችን_መድኃኒዓለም_ወርሀዊ_በዓል_አደረሰን !
#ለመቀላቀል
@ortodoxtewahedo
#ለሃሳብ አስተያየት
@ortodoxtewahedoo
#ወስብሐት_ለእግዚአብሔር