ሰው ነህ !
💧በሰጡህ ቦታ አትቅር ፣ ሰው እንጂ ድመት አይደለህምና።
💧ማንም ወደ ፈለገው አይቀይስህ፣ ሰው እንጂ የመስኖ ውኃ አይደለህምና።
💧በቁጣ የሠራኸውን አታፍርስ ፣ ሰው እንጂ ጎርፍ አይደለህምና።
💧በወደቅህበት አትቅር፣ ሰው እንጂ ዛፍ አይደለህምና።
🙏ሰው ሁን ከሰውም ሰው ሁን::
የተባለው ከተስማማህ ሼር አድርግ
@Psychoet
💧በሰጡህ ቦታ አትቅር ፣ ሰው እንጂ ድመት አይደለህምና።
💧ማንም ወደ ፈለገው አይቀይስህ፣ ሰው እንጂ የመስኖ ውኃ አይደለህምና።
💧በቁጣ የሠራኸውን አታፍርስ ፣ ሰው እንጂ ጎርፍ አይደለህምና።
💧በወደቅህበት አትቅር፣ ሰው እንጂ ዛፍ አይደለህምና።
🙏ሰው ሁን ከሰውም ሰው ሁን::
የተባለው ከተስማማህ ሼር አድርግ
@Psychoet
🔥👉 ጭንቀትን_ድብርትንና_አሉታዊ ስሜቶችን_ለመከላከል የሚረዱ_ዘዴዎች🔥👈
🎈ባለፈ ጥፋት ወይም ውድቀት ላይ በማተኮር #ፀፀት# ውስጥ አለመግባት። ከባለፈው ስህተት በመማርና አሁን/ዛሬ ላይ ማተኮር።
🎈 ማህበራዊ ተሳትፎዎችን ማድረግ።
🎈 ከተለያዩ እፆችና አልኮል #ሱሰኝነት# መቆጠብ።
🎈 ግጭቶችን፣ ቅራኔዎችንና አለመግባባቶችን በአግባቡ መፍታት።
🎈 ውጥረትንና ጭንቀትን የሚፈጥሩብዎትን ነገሮችና ሁኔታዎችን መለየትና ከእነሱ መራቅ።
🎈 በጎ ማድረግና ምላሹን ከሰዎች አለመጠበቅ።
🎈ጭንቀትና ድብርት ሲሰማዎ ለቅርብ ወዳጅ፣ ጓደኛ ወይም ቤተሰብ ማጋራት።
🎈ድንገተኛ ችግር ሲያጋጥምዎ፤ ራስን ማረጋጋት።
🎈ሌሎች ሰዎች ስለእርስዎ በሚሰጡት ትችት እና አስተያየት አለመረበሽ።
🎈 የህይወትን ጥሩ ገፅታ ማየት።
🎈በአላማና በእቅድ መኖር ፤ ጊዜን በስራ ማሳለፍ።
🎈የአካል ብቃት እንቅስቃሴ ማድረግ፤ ንፅህናን መጠበቅ እና ጤናማ የአመጋገብ ስርአትን መከተል።
🎈ለራስ ጊዜን መስጠትና እረፍት ማድረግ።
🎈ከሁሉም በላይ በፈጣሪ መታመንና እኛ ልንፈታ የማንችላቸውን ነገሮች ለእርሱ መተው።
መልእክቱ ለብዙዎች እንዲደርስ Share & Like አይርሱ።
© Psych ጤና Fb ፔጅ
👉በመአዛ መንክር -ክሊኒካል ሳይኮሎጂስት
ቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ
www.tg-me.com/psychoet
🎈ባለፈ ጥፋት ወይም ውድቀት ላይ በማተኮር #ፀፀት# ውስጥ አለመግባት። ከባለፈው ስህተት በመማርና አሁን/ዛሬ ላይ ማተኮር።
🎈 ማህበራዊ ተሳትፎዎችን ማድረግ።
🎈 ከተለያዩ እፆችና አልኮል #ሱሰኝነት# መቆጠብ።
🎈 ግጭቶችን፣ ቅራኔዎችንና አለመግባባቶችን በአግባቡ መፍታት።
🎈 ውጥረትንና ጭንቀትን የሚፈጥሩብዎትን ነገሮችና ሁኔታዎችን መለየትና ከእነሱ መራቅ።
🎈 በጎ ማድረግና ምላሹን ከሰዎች አለመጠበቅ።
🎈ጭንቀትና ድብርት ሲሰማዎ ለቅርብ ወዳጅ፣ ጓደኛ ወይም ቤተሰብ ማጋራት።
🎈ድንገተኛ ችግር ሲያጋጥምዎ፤ ራስን ማረጋጋት።
🎈ሌሎች ሰዎች ስለእርስዎ በሚሰጡት ትችት እና አስተያየት አለመረበሽ።
🎈 የህይወትን ጥሩ ገፅታ ማየት።
🎈በአላማና በእቅድ መኖር ፤ ጊዜን በስራ ማሳለፍ።
🎈የአካል ብቃት እንቅስቃሴ ማድረግ፤ ንፅህናን መጠበቅ እና ጤናማ የአመጋገብ ስርአትን መከተል።
🎈ለራስ ጊዜን መስጠትና እረፍት ማድረግ።
🎈ከሁሉም በላይ በፈጣሪ መታመንና እኛ ልንፈታ የማንችላቸውን ነገሮች ለእርሱ መተው።
መልእክቱ ለብዙዎች እንዲደርስ Share & Like አይርሱ።
© Psych ጤና Fb ፔጅ
👉በመአዛ መንክር -ክሊኒካል ሳይኮሎጂስት
ቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ
www.tg-me.com/psychoet
ሰው መሆን በቂ ነው!
አንድ ቀን አንድ ሰው በድንገት በአንድ ጉድጓድ ውስጥ ወደቀና መውጣትም አልቻለም፡፡ ከብዙ ጥረት በኋላ ደክሞት በጉድጓዱ መካከል ቁጭ እንዳለ …
• ከንፈር መጣጭ ሰው አየውና - “ሁኔታህን ሳስበው በጣም በሃዘን እሞላለሁ” ብሎት ሄደ፡፡
• ተመራማሪ ሰው አየውና - “ይህ ጉድጓድ ከተማ መሃል ሆኖ ሰው መውደቁ አያስደንቅም” ብሎት ሄደ፡፡
• ፈራጅ ሰው አየውና- “ክፉ ሰዎች ብቻ ናቸው እንደዚህ ሊወድቁ የሚችሉት” ብሎት ሄደ፡፡
• ነጭናጫና አጉረምራሚ ሰው አየውና- “እኔ ወድቄ የነበረበትን ጉድጓድ አላየህ” ብሎት ሄደ፡፡
• አነቃቂ ንግግር አስተማሪው አየውና- “በራስህ ብታምን ከዚህ ትወጣለህ” ብሎት ሄደ፡፡
• ዘረኛ ሰው አየውና - “የምን ሃገር ሰው ነህ?” በማለት ከጠየቀው በኋላ የእርሱን ቋንቋ ስላልተናገረ ጥሎት ሄደ፡፡
•ውሸተኛ የሀይማኖት ሰው አየውና - " የኔ እምነት ተከታይ ብትሆን አወጣህ ነበር " ብሎት ሂደ፡፡
• በመጨረሻ ይህንን ሁሉ ድራማ ሲመለከት የነበረ አንድ ጨዋ ጎልማሳ ሰው ከብዙ ጥረት በኋላ እየሳበ አወጣው ፡፡
ከዚህ ታሪክ ምን እንማራለን? በእርግጥ ሰውነት ከሁሉ ይበልጣል ፡፡
ምንጭ :- ከዚሁ ማህበራዊ ሚዲያ የተገኘ
በቅንነት ሼር ያድርጉ👇
http://www.tg-me.com/psychoet
አንድ ቀን አንድ ሰው በድንገት በአንድ ጉድጓድ ውስጥ ወደቀና መውጣትም አልቻለም፡፡ ከብዙ ጥረት በኋላ ደክሞት በጉድጓዱ መካከል ቁጭ እንዳለ …
• ከንፈር መጣጭ ሰው አየውና - “ሁኔታህን ሳስበው በጣም በሃዘን እሞላለሁ” ብሎት ሄደ፡፡
• ተመራማሪ ሰው አየውና - “ይህ ጉድጓድ ከተማ መሃል ሆኖ ሰው መውደቁ አያስደንቅም” ብሎት ሄደ፡፡
• ፈራጅ ሰው አየውና- “ክፉ ሰዎች ብቻ ናቸው እንደዚህ ሊወድቁ የሚችሉት” ብሎት ሄደ፡፡
• ነጭናጫና አጉረምራሚ ሰው አየውና- “እኔ ወድቄ የነበረበትን ጉድጓድ አላየህ” ብሎት ሄደ፡፡
• አነቃቂ ንግግር አስተማሪው አየውና- “በራስህ ብታምን ከዚህ ትወጣለህ” ብሎት ሄደ፡፡
• ዘረኛ ሰው አየውና - “የምን ሃገር ሰው ነህ?” በማለት ከጠየቀው በኋላ የእርሱን ቋንቋ ስላልተናገረ ጥሎት ሄደ፡፡
•ውሸተኛ የሀይማኖት ሰው አየውና - " የኔ እምነት ተከታይ ብትሆን አወጣህ ነበር " ብሎት ሂደ፡፡
• በመጨረሻ ይህንን ሁሉ ድራማ ሲመለከት የነበረ አንድ ጨዋ ጎልማሳ ሰው ከብዙ ጥረት በኋላ እየሳበ አወጣው ፡፡
ከዚህ ታሪክ ምን እንማራለን? በእርግጥ ሰውነት ከሁሉ ይበልጣል ፡፡
ምንጭ :- ከዚሁ ማህበራዊ ሚዲያ የተገኘ
በቅንነት ሼር ያድርጉ👇
http://www.tg-me.com/psychoet
#መልካም_የጥር_ወር_ይኹንላችሁ!
ይህ ወር የአእምሮ ደስታ ፣ ሰላም ፣ እረፍት የምታገኙበት ፤ ካሳሰባችሁና ካስጨነቃችሁ የማያልቅ የሕይወት ውጣ ውረድ እፎይ የምትሉበት ፣ ሕይወታችሁ የሚለወጥበት ፣ አስተሳሰባችሁ መልካምና ቀና የሚሆንበት ፣ ያላቀዳችሁ የምታቅዱበት ፣ ያቀዳችሁ ያቀዳችሁትን የምታሳኩበት ወር ይሁንላችሁ ፡፡
ለሀገራችን ኢትዮጵያ ደግሞ በኹሉም አካባቢዎች ሰላምን የምንሰማበት ፣ ፍትህን የምናይበት ይሁንልን ፡፡
✍ የሳይኮሎጂና የሕይወት ክህሎት የማሕበራዊ ሚዲያ ትምህርታችን በዚህ ወርም ተጠናክሮ ይቀጥላል ፡፡
ሁሌም የማያልቅ ተስፋ አለ።
ናሁሰናይ ፀዳሉ አበራ
Telegram : www.tg-me.com/psychoet
Facebook : fb.com/psychologyabc
መልዕክቱን #Share #Like በማረግ ለሌሎችም እናጋራ
ይህ ወር የአእምሮ ደስታ ፣ ሰላም ፣ እረፍት የምታገኙበት ፤ ካሳሰባችሁና ካስጨነቃችሁ የማያልቅ የሕይወት ውጣ ውረድ እፎይ የምትሉበት ፣ ሕይወታችሁ የሚለወጥበት ፣ አስተሳሰባችሁ መልካምና ቀና የሚሆንበት ፣ ያላቀዳችሁ የምታቅዱበት ፣ ያቀዳችሁ ያቀዳችሁትን የምታሳኩበት ወር ይሁንላችሁ ፡፡
ለሀገራችን ኢትዮጵያ ደግሞ በኹሉም አካባቢዎች ሰላምን የምንሰማበት ፣ ፍትህን የምናይበት ይሁንልን ፡፡
✍ የሳይኮሎጂና የሕይወት ክህሎት የማሕበራዊ ሚዲያ ትምህርታችን በዚህ ወርም ተጠናክሮ ይቀጥላል ፡፡
ሁሌም የማያልቅ ተስፋ አለ።
ናሁሰናይ ፀዳሉ አበራ
Telegram : www.tg-me.com/psychoet
Facebook : fb.com/psychologyabc
መልዕክቱን #Share #Like በማረግ ለሌሎችም እናጋራ
💪በራስ መተማመንን ማጎልበት💪
Developing Self Confidence
በራስ መተማመን ማለት ሰው ባለው ችሎታ፣ አካላዊ ውበትና ሁለንተናዊ ማንነት አለመፍራት እና ሚዛናዊ በሆነ መልኩ ራስን መቀበል ማለት ነው፡፡ ትእቢት ፣ ትምክህት፣ ያልተገባ አውቃለሁ ባይነት እና ከመጠን ያለፈ ድፍረት በራስ መተማመን አይደለም።
በራስ መተማመንን የሚያጎለብቱ ብልሀቶች
🔥 ራስዎን ከሌሎች ጋር አለማነፃፀር።
🔥 ያለዎትን ክህሎት እና ድክመት መለየት።
🔥 የአካላዊ ገፅታ ውበትን መጠበቅ ደግሞም የሰውን ትኩረት ከልክ ባለፈ ሁኔታ የሚስቡ ጌጣጌጦችንና ሜካፖችን አለመጠቀም።
🔥 ጥሩ እና ምቹ አለባበስ መልበስ።
🔥 ነቃና ቀልጠፍ ብሎ መራመድ ።
🔥 በሰው ፊት ሀሳብዎን መግለፅ ሲኖርብዎ ቀድመው በቂ ዝግጅት ማድረግ።
🔥 መልካም በሆነ የህይወት እንቅስቃሴ የበኩልዎን አስተዋፅዖ ማድርግ።
🔥 ጥሩ የሚሰሩ ሰዎችን ማድነቅ/ ማበረታታት።
🔥 ሰዎች የተቃወሙዎት ወይም የናቁዎት ሲመስልዎ በእርጋታ ምላሽ መስጠት።
🔥 ሰዎች ስህተትዎን ሲነግሩዎ በቀና ማየት(ስለሚጠሉኝ ነው አለማለት)።
🔥 እርዳታ ሲያስፈልግዎ ያለፍርሀት መጠይቅ።
🔥 ሰአት ማክበር።
©በመአዛ መንክር - ክሊኒካል ሳይኮሎጂስት
YouTube: Dink Mikir
#Like #Share በማረግ ለሌሎችም እናስተምር
ቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ
@psychoet
Developing Self Confidence
በራስ መተማመን ማለት ሰው ባለው ችሎታ፣ አካላዊ ውበትና ሁለንተናዊ ማንነት አለመፍራት እና ሚዛናዊ በሆነ መልኩ ራስን መቀበል ማለት ነው፡፡ ትእቢት ፣ ትምክህት፣ ያልተገባ አውቃለሁ ባይነት እና ከመጠን ያለፈ ድፍረት በራስ መተማመን አይደለም።
በራስ መተማመንን የሚያጎለብቱ ብልሀቶች
🔥 ራስዎን ከሌሎች ጋር አለማነፃፀር።
🔥 ያለዎትን ክህሎት እና ድክመት መለየት።
🔥 የአካላዊ ገፅታ ውበትን መጠበቅ ደግሞም የሰውን ትኩረት ከልክ ባለፈ ሁኔታ የሚስቡ ጌጣጌጦችንና ሜካፖችን አለመጠቀም።
🔥 ጥሩ እና ምቹ አለባበስ መልበስ።
🔥 ነቃና ቀልጠፍ ብሎ መራመድ ።
🔥 በሰው ፊት ሀሳብዎን መግለፅ ሲኖርብዎ ቀድመው በቂ ዝግጅት ማድረግ።
🔥 መልካም በሆነ የህይወት እንቅስቃሴ የበኩልዎን አስተዋፅዖ ማድርግ።
🔥 ጥሩ የሚሰሩ ሰዎችን ማድነቅ/ ማበረታታት።
🔥 ሰዎች የተቃወሙዎት ወይም የናቁዎት ሲመስልዎ በእርጋታ ምላሽ መስጠት።
🔥 ሰዎች ስህተትዎን ሲነግሩዎ በቀና ማየት(ስለሚጠሉኝ ነው አለማለት)።
🔥 እርዳታ ሲያስፈልግዎ ያለፍርሀት መጠይቅ።
🔥 ሰአት ማክበር።
©በመአዛ መንክር - ክሊኒካል ሳይኮሎጂስት
YouTube: Dink Mikir
#Like #Share በማረግ ለሌሎችም እናስተምር
ቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ
@psychoet
፩. ትናንትን የምታርመውም ኾነ የምታድሰው ዛሬ ላይ ኾነህ ነው፡፡
፪. ነገ ውብ የምትኾነው ዛሬን ስትንከባከባት ነው፡፡
፫. ነገ ከተስፋነቷ በስተቀር ያንተ አይደለችም፡፡
ተስፋህ እውን ኾኖ የምታገኛት ግን ዛሬን በተጠቀምክባት ልክ ነው፡፡ ስለዚህ፣ ትዝታህ ላይ ተቀምጠህ በተስፋ ጋሪ ተሳፍረህ ዛሬን በደንብ ኑር።
ሜሎሪና❤️
፪. ነገ ውብ የምትኾነው ዛሬን ስትንከባከባት ነው፡፡
፫. ነገ ከተስፋነቷ በስተቀር ያንተ አይደለችም፡፡
ተስፋህ እውን ኾኖ የምታገኛት ግን ዛሬን በተጠቀምክባት ልክ ነው፡፡ ስለዚህ፣ ትዝታህ ላይ ተቀምጠህ በተስፋ ጋሪ ተሳፍረህ ዛሬን በደንብ ኑር።
ሜሎሪና❤️
አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ለ2015ዓ.ም. በማታ መርሃግብር ለመጀመሪያ ዲግሪ ትምህርት አመልካቾችን ይጋብዛል
በዚህም መሰረት አመልካቾች የሚከተሉትን ማሟላት ይጠበቅባቸዋል
1. በዲግሪያችሁ ለምታመለክቱ$ የወጪ መጋራት ያጠናቀቃችሁበትን የሚገልፅ ደብዳቤ ከትምህርት ማስረጃ ጋር ማቅረብ
2. በ12ኛ ክፍል ውጤት የምታመለክቱ አመልካቾች ከ2010-2015ዓ.ም. ድረስ ብቻ ትምህርት ሚኒስቴር ባወጣው መስፈርት መሰረት ለከፍተኛ ትምህርት መግቢያ ነጥብን የምታሟሉ ከትምህርት ማስረጃ ጋር በማያያዝ ማቅረብ
3. ከተለያዩ ዩኒቨርስቲዎች ከ2010-2014ዓ.ም. በተለያየ ምክንያት አቋርጣችሁ ለምታመለክቱ የወጪ መጋራት ያጠናቀቃችሁበትን የሚገልፅ ደብዳቤ ከትምህርት ማስረጃ ጋር በማያያዝ ማቅረብ
4. ለዲፕሎማ ወይም ደረጃ 4 አመልካቾች በ2015ዓ.ም. ቅበላ አይኖረንም
ማሳሰቢያ፡-
1. የማመልከቻ ፎርሙን በዩኒቨርስቲዉ ድረገጽ (https:\\portal.aau.edu.et) መሙላት
2. ከማመልከቻ ፎርም የሚያገኙትን የማመልከቻ ቁጥር (Application Number) በመያዝ ብር 300 (ሶስት መቶ ብር) በኢትዮጲያ ንግድ ባንክ በሞባይል CBE ብር ወይም በወኪሎች ወይም በቅርንጫፍ አማካኝነት በ242424 አጭር ኮድ ክፍያ መፈጸም
3. ክፍያዎትን ካጠናቀቁ በኋላ ወደማመለከቻ ፎርሙ በመመለስ በፒዲኤፍ (PDF) ፎርማት የተለወጠ የትምህርት ማስረጃዎትን የወጪ መጋራት ያጠናቀቁበትን ሰነድ መላክ፤
4. ምዝገባዉ ካከናወኑ በኋላ የትምህርት ማስረጃ በአካል ይዞ በመቅረብ ቢሮ ቁጥር 203 ማስገባት ይኖርብዎታል፡፡
5. የተማሪዎች ቁጥር ከመቀበል አቅም በታች (ዝቅተኛ) ከሆነ የትምህርት ፕሮግራሞች የማይከፈቱ መሆኑን እናሳውቃለን፡፡
6. በዲግሪያችሁ ለምታመለክቱ የመረጣችሁትን ትምህርት ክፍል የምታገኙት 12ኛ ክፍል ጨርሰው ያመለከቱ ከተመደቡ በኋላ በሚተርፉ ቦታዎች ላይ ብቻ መሆኑን እናሳውቃለን፡፡
የምዝገባ ቀን፡ ከየካቲት 10 እስከ ከየካቲት 16 2015ዓ.ም
የምዝገባ ቦታ ፡ በሬጅስትራር ህንፃ ቢሮ ቁጥር 203
አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሬጅስትራር
በዚህም መሰረት አመልካቾች የሚከተሉትን ማሟላት ይጠበቅባቸዋል
1. በዲግሪያችሁ ለምታመለክቱ$ የወጪ መጋራት ያጠናቀቃችሁበትን የሚገልፅ ደብዳቤ ከትምህርት ማስረጃ ጋር ማቅረብ
2. በ12ኛ ክፍል ውጤት የምታመለክቱ አመልካቾች ከ2010-2015ዓ.ም. ድረስ ብቻ ትምህርት ሚኒስቴር ባወጣው መስፈርት መሰረት ለከፍተኛ ትምህርት መግቢያ ነጥብን የምታሟሉ ከትምህርት ማስረጃ ጋር በማያያዝ ማቅረብ
3. ከተለያዩ ዩኒቨርስቲዎች ከ2010-2014ዓ.ም. በተለያየ ምክንያት አቋርጣችሁ ለምታመለክቱ የወጪ መጋራት ያጠናቀቃችሁበትን የሚገልፅ ደብዳቤ ከትምህርት ማስረጃ ጋር በማያያዝ ማቅረብ
4. ለዲፕሎማ ወይም ደረጃ 4 አመልካቾች በ2015ዓ.ም. ቅበላ አይኖረንም
ማሳሰቢያ፡-
1. የማመልከቻ ፎርሙን በዩኒቨርስቲዉ ድረገጽ (https:\\portal.aau.edu.et) መሙላት
2. ከማመልከቻ ፎርም የሚያገኙትን የማመልከቻ ቁጥር (Application Number) በመያዝ ብር 300 (ሶስት መቶ ብር) በኢትዮጲያ ንግድ ባንክ በሞባይል CBE ብር ወይም በወኪሎች ወይም በቅርንጫፍ አማካኝነት በ242424 አጭር ኮድ ክፍያ መፈጸም
3. ክፍያዎትን ካጠናቀቁ በኋላ ወደማመለከቻ ፎርሙ በመመለስ በፒዲኤፍ (PDF) ፎርማት የተለወጠ የትምህርት ማስረጃዎትን የወጪ መጋራት ያጠናቀቁበትን ሰነድ መላክ፤
4. ምዝገባዉ ካከናወኑ በኋላ የትምህርት ማስረጃ በአካል ይዞ በመቅረብ ቢሮ ቁጥር 203 ማስገባት ይኖርብዎታል፡፡
5. የተማሪዎች ቁጥር ከመቀበል አቅም በታች (ዝቅተኛ) ከሆነ የትምህርት ፕሮግራሞች የማይከፈቱ መሆኑን እናሳውቃለን፡፡
6. በዲግሪያችሁ ለምታመለክቱ የመረጣችሁትን ትምህርት ክፍል የምታገኙት 12ኛ ክፍል ጨርሰው ያመለከቱ ከተመደቡ በኋላ በሚተርፉ ቦታዎች ላይ ብቻ መሆኑን እናሳውቃለን፡፡
የምዝገባ ቀን፡ ከየካቲት 10 እስከ ከየካቲት 16 2015ዓ.ም
የምዝገባ ቦታ ፡ በሬጅስትራር ህንፃ ቢሮ ቁጥር 203
አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሬጅስትራር