Telegram Web Link
Quran
: 031-Luqman
Yasir Adewseri
አሥ ሠላሙ ዐለይኩም ወራሕመቱላሂ ወበረካቱሁ

ያ ጀመዓህ! "የተደበቀው እውነት" የሚለው ስድስተኛው መጽሐፌ በገበያ ላይ ውሏል። "የተደበቀው እውነት" የሚያውጠነጥነው ስለ ተወዳጁ ነቢያችን"ﷺ" መምጣት በተውራት እና በኢንጂል ተነግሮ የመጽሐፉ ሰዎች ይህንን እውነት እንዴት እንደደበቁት የሚገልጥ እና የሚያጋልጥ ነው። ዝርዝሩን መጽሐፉ ላይ ያንብቡ እና ለሎች የሂዳያህ ሠበብ እንዲሆን አስነብቡ!

መጽሐፉን መርካርቶ አንዋር መሥጂድ ኢሥላማዊ መጻሕፍት መደብር ውስጥ ያገኙታል፥ የበለጠ ለመረጃ +251920781016 ዐብዱ ብለው ይደውሉ!

መጽሐፉ ተደራሽነት እንዲኖረው ባለው የማኅበራዊ መገናኛ ብዙኃን ሼር በማድረግ ሠበቡል ሂዳያህ ይሁኑ!

ወጀዛኩሙላህ ኸይራ!

ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ
https://www.tg-me.com/Wahidcom
🌿 بسم الله  الرحمن  الرحيم  🌿 

አዲስ  የ ም ዝ ገ ባ  ማ ስ ታ ወ ቂ ያ

🌍 አስደሳች ዜና ለኢልም ፈላጊዎች በሙሉ ከኢብኑ ኡመር ኢስላሚ ሴንተር‼️           

እንደሚታወቀው ኢብኑ-ኡመር Online መድረሳ ቁርዓን እና ኪታብ በግሩፕ እንድሁም በግል በጥራትና በብቃት በማስተማር ላይ ይገኛል፣

👉እናማ በዚህ ዘመን እየኖርን እስከመቼ ይሆን?ቁርዓን አለቀራውም፣ ተጅዊዴም አልተስተካከለም፣ ኪታብም አልቀራውም የምንለው? አላህም ፊትስ ዲኑን ላለመማራችን ምን አይነት ኡዝር ይኖረን ይሆን?

እንንቃ ለዲናችን ከፍተኛ ትኩረትና ግዜ እንስጥ አላህ የሰጠንን ጤንነት፣ግዜ እንዲሁም የሞባይል ስልካችንን ፀጋ በአግባቡ በመጠቀም ለአኬራሽ ስንቅ እንሰንቅበት‼️

👉ምን ይሆን የሚቀራው ካላቹ ? አብሽ
1⃣ ቁርዓን ከአሊፍ እስከ ሂፍዝ !

2⃣ ኪታብ በሁሉም ዘርፍና አይነት በጥራት!

📖 ኪታብ ማሰማት የምትፈልጉ ተማሪዎችንም በአክብሮት እናስተናግዳለን።

🕰በግል በሚመቻቹ ሰዓት መቅራት ትችላላቹ።

📲ቂርዓቴን በምን ልከታተል ይሆን?ካ
ላቹ
አያሳስባቹ በፈለጋቹት አኘልኬሽን በOnline ከፈለጋቹም በመደዋወል አሊያም በሪከርድ አመቻችተንላችኋል ።

ግዜያችን ሂዎታችን ነውና በሂዎት አይቀለድም ለመቅራትና ለመለወጥ ግዜው አሁን ነውና ይፍጠኑ ይጀምሩ ‼️

 🙏 አሁኑኑ ለመመዝገብ ወስናቹ ትክክለኛውን መድረሳችሁን ስለመረጣቹ እንኳን ደስ አላቹ ።እናመሰግናለን ይህንን ዩዘር ሊንክ ፈጥናቹ ነካ በማድረግ ተመዝገቡ👇👇👇👇

  👉 @ebnuomeronlinemedresa ወይም

   👉  @Rewda_umu_nuh

   👉   @ibnuomereslamiccenter

          "እውቀትን እስከ ቤቶ በር ''  
                ከኢብኑ-ኡመር"


የመድረሳው ግሩፑ ጆይን ሼር እናድርግ ባረከሏሁ ፊኪ👇👇👇👇👇

https://www.tg-me.com/IbnuUmaronlinemaderasa
ሴት እርሻ ናት!

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡

2፥223 ሴቶቻችሁ ለእናንተ እርሻ ናቸው፥ እርሻችሁንም በፈለጋችሁት ኹኔታ ድረሱ፡፡ نِسَاؤُكُمْ حَرْثٌ لَّكُمْ فَأْتُوا حَرْثَكُمْ أَنَّىٰ شِئْتُمْ

በቁርኣን አምላካችን አሏህ ወንድ ለሴት "ልብስ" እንደሆነ እንዲሁ ሴት ለወንድ "ልብስ" እንደሆነች ይነግረናል፦
2፥187 በጾም ሌሊት ወደ ሴቶቻችሁ መድረስ ለእናንተ ተፈቀደላችሁ፡፡ እነርሱ ለእናንተ ልብሶች ናቸው፥ እናንተም ለእነርሱ ልብሶች ናችሁ፡፡ أُحِلَّ لَكُمْ لَيْلَةَ الصِّيَامِ الرَّفَثُ إِلَىٰ نِسَائِكُمْ ۚ هُنَّ لِبَاسٌ لَّكُمْ وَأَنتُمْ لِبَاسٌ لَّهُن

እዚህ አንቀጽ ላይ ወንድ ለሴት ሴት ለወንድ "ልብስ" ናቸው ሲል በፍካሬአዊ ሃፍረትን፣ ነውርን እና ገበናን "መሸፈኛ" ማለት እንጂ በእማሬአዊ ወስዶ "ጃኬት" ወይም "ቀሚስ" አሊያም "ሱሪ" ማለት አይደለም። በተመሳሳይ ሴት ለወንድ እርሻ ናት፦
2፥223 ሴቶቻችሁ ለእናንተ እርሻ ናቸው፥ እርሻችሁንም በፈለጋችሁት ኹኔታ ድረሱ፡፡ نِسَاؤُكُمْ حَرْثٌ لَّكُمْ فَأْتُوا حَرْثَكُمْ أَنَّىٰ شِئْتُمْ

መቼም ቂል የሆነ ሰው ካልሆነ ሴት ለወንድ "እርሻ" ናት ሲባል ሞፈርና ቀንበር አዋዶ የሆነው የጓሮ አትክልት አሊያም ሰብል ናት ማለት እንዳልሆነ እሙንና ቅቡል ነው፥ ቃሉ የወከለው እሳቤ እማሬአዊ ሳይሆን ፍካሬአዊ ነው። የሴት ልጅ ማኅፀን ዘር የሚዘራበት "እርሻ" ሲመሰል የእንሥት ማህፀን ላይ ላይ የሚገናኘው የተባእት ዘር ሕዋስ ደግሞ ገበሬ እርሻ ላይ በሚዘራው "ዘር" ተመስሏል፥ ወንድ ዘሩን ዘሪ ሲሆን ሴት ያንን ዘር የምታፈራበት እርሻ ናት። ምክንያቱም አንድ ገበሬ እርሻው ላይ ከዘራ በኃላ ዘሩ ዳብሮ ለፍሬ የሚበቃው በእርሻ ውስጥ እንደሆነ ሁሉ አንድ ተባእትም አንድ እንስት ማኅፀን ውስጥ ዘሩን ተገናኝ ሆኖ ከዘራ በኃላ ሂደቱ ሁሉ ተከናውኖ ለፍሬ የሚበቃው ማኅፀን ውስጥ ስለሆነ ነው። በማኅፀን ውስጥ በመፍሰስ የሚዘራው ዘር የተንጣለለ ደካማ ውኃ የሆነው የፍትወት ሕዋስ ነው፥ ይህም ሕዋስ በተጠበቀ መርጊያ በእርሻው ውስጥ ለፍሬ እስኪበቃ ይቆያል፦
56፥58 በማኅፀኖች የምታፈሱትን አያችሁን? أَفَرَأَيْتُم مَّا تُمْنُونَ
56፥63 የምትዘሩትንም አያችሁን? أَفَرَأَيْتُم مَّا تَحْرُثُون
32፥8 ከዚያም ዘሮቹን ከተንጣለለ ከደካማ ውኃ ያደረገ ነው፡፡ ثُمَّ جَعَلَ نَسْلَهُ مِن سُلَالَةٍ مِّن مَّاءٍ مَّهِينٍ
23፥13 ከዚያም በተጠበቀ መርጊያ ውስጥ የፍትወት ጠብታ አደረግነው፡፡ ثُمَّ جَعَلْنَاهُ نُطْفَةً فِي قَرَارٍ مَّكِينٍ

ታላቁ የቁርኣን ሙፈሢር ኢብኑ ከሲር የኢብኑ ዐባሥን ንግግር ዋቢ በማድረግ የፈሠሩት በዚህ መልክ እና ልክ ነው፦
ተፍሢሩል ኢብኑ ከሲር 2፥223
ንግግሩ፦ "ሴቶቻችሁ ለእናንተ እርሻ ናቸው" የሚለውን ኢብኑ ዐባሥ፦ "እርሻ የሚለው የእርግዝናን ቦታ ነው”" ብሏል"። وقوله : ( نساؤكم حرث لكم ) قال ابن عباس : الحرث موضع الولد

"ሴት" እና "ወንድ" የሚለው የፆታ መደብ የፍትወት ሕዋሳችንን ታሳቢ እና ዋቢ ያደረገ ቢሆንም ነገር ግን አጠቃላይ ስብዕናችንን እንደሚያሳይ ሁሉ በተመሳሳይ "እርሻዎቻችሁ" ማለት "ሴቶቻችሁ" ማለትን ይይዛል፥ እርሻ ዘር የሚዘራበት እንደሆነ ሁሉ ሴትም ዘር ስለሚዘራባት እርሻ ተብላለች። "እርሻችሁንም በፈለጋችሁት ኹኔታ ድረሱ" የሚለው አንቀጽ የወረደበት ሠበቡ አን-ኑዙል መዲና ላይ የነበሩ አይሁዳውያን፦ "ማንም የሚስቱን ሃፍረት በጀርባ በኩል ተራክቦ ያደረገ ልጁ ጠንጋራ ይሆናል" የሚል የተንጋደደ መረዳት ስለያዙ ነው፦
ጃምዒ አት-ቲርሚዚይ መጽሐፍ 47, ሐዲስ 3245
ከጃቢር ኢብኑ ሙንከዲር ሰምቶ እንደተረከው፦ "አይሁዳውያን፦ "ማንም የሚስቱን ሃፍረት በጀርባ በኩል ተራክቦ ያደረገ ልጁ ጠንጋራ ይሆናል" አሉ፥ ከዚያም አላህ፦ "ሴቶቻችሁ ለእናንተ እርሻ ናቸው፥ እርሻችሁንም በፈለጋችሁት ኹኔታ ድረሱ" የሚለውን አንቀጽ አወረደ"። عَنِ ابْنِ الْمُنْكَدِرِ، سَمِعَ جَابِرًا، يَقُولُ كَانَتِ الْيَهُودُ تَقُولُ مَنْ أَتَى امْرَأَتَهُ فِي قُبُلِهَا مِنْ دُبُرِهَا كَانَ الْوَلَدُ أَحْوَلَ فَنَزَلَتْ ‏:‏ ‏(‏نِسَاؤُكُمْ حَرْثٌ لَكُمْ فَأْتُوا حَرْثَكُمْ أَنَّى شِئْتُمْ ‏)‏

"በፈለጋችሁ ሁኔታ" ማለት በጀርባ በኩል ተራክቦ"doggy sex" ማድረግም ክልክል አይደለም ማለትን ይጨምራል፥ ያ ማለት በመቀመጫ በኩል ተራክቦ”anal sex” ማድረግ ይቻላል ማለት እንዳልሆነ ለማሳየት እዛው ዐውድ ላይ፦ "አላህ ካዘዛችሁ ስፍራ ተገናኙዋቸው" በማለት ይናገራል። በመቀመጫ ተራክቦ ማድረግ ሐራም ነው፥ ሐራም ብቻ ሳይሆን ኩፍሩል አስገርም ነው፦
2፥222 ንጹሕ በኾኑም ጊዜ አላህ ካዘዛችሁ ስፍራ ተገናኙዋቸው"፡፡ فَإِذَا تَطَهَّرْنَ فَأْتُوهُنَّ مِنْ حَيْثُ أَمَرَكُمُ اللَّهُ
ጃሚዒ አት-ተርሚዚ : መጽሐፍ 1, ሐዲስ 135
አቢ ሁረይራህ”ረ.ዐ” እንዳለው፦ “ነቢዩ”ﷺ” እንዲህ ሲሉ ሰምቻለው፦ ማንም በሓይድ ላይ ካለች ሴት ወይም በመቀመጫዋ በኩል ተራክቦ ቢያደርግ በሙሐመድ”ﷺ” ላይ በተወረደው ክዷል"። عَنْ أَبِي هُرَيْرَةَ، عَنِ النَّبِيِّ صلى الله عليه وسلم قَالَ ‏”‏ مَنْ أَتَى حَائِضًا أَوِ امْرَأَةً فِي دُبُرِهَا أَوْ كَاهِنًا فَقَدْ كَفَرَ بِمَا أُنْزِلَ عَلَى مُحَمَّدٍ صلى الله عليه وسلم ‏”‏
እዚህ ድረስ ከተግባባን የጴጥሮስ ተማሪ የሮሙ ክሌመንት ሴት እርሻ እንደሆነች አበክሮ እና አዘክሮ ይናገራል፦
ቀለሜንጦስ 10፥50 "አንቲ ገራህት ዕቀቢ ርእሰኪ! ወኢትደምሪ ዘርአ ነኪር፥ እንዘ ሁሉ ዘይናዝዘኪ ሐዘነኪ ሶበ ከመዝ ዘርእኪ ቡሩክ ውእቱ"።

ትርጉም፦ "አንቺ እርሻ ራስሽን ጠብቂ! ሌላ ዘርን አትጨምሪ፥ የሚያጽናናሽ እና ከሐዘንሽ የሚያረጋጋሽ ባልሽ ብቻ ነው"።

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ የአዲስ ኪዳን መጽሐፍት ቀኖና 35 ናቸው፥ የአዲስ ኪዳን መደበኛ የቀኖና መጽሐፍት 27 ሲሆኑ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ መጽሐፍት ተጨማሪ ቀኖና 8 ናቸው። ከስምንቱ አንዱ "መጽሐፈ ቀለሜንጦስ" ነው፥ እና ቀለሜንጦስ ሴትን እርሻ ሲል ሞፈርና ቀንበር አዋዶ የሆነው የጓሮ አትክልት አሊያም ሰብል ናት ማለቱ ነውን? በጣም ስመ ጥርና ገናና የአዲስ ኪዳን አራት እደክታባት መካከል ኮዴክስ ኤፍራኤሚ(ኤፍሬም) ሲሆን በ 450 ድኅረ ልደት ያዘጋጀው ሶርያዊው ኤፍሬም ነው፥ ይህ የሶርያ ኤጲጵ ቆጶስ ድንግል ማርያምን እርሻ እንደሆነች አስረግጦ እና ረግጦ በውዳሴም ማርያም ላይ ይናገራል፦
ውዳሴ ማርያም ዘማክሰኞ ቁጥር 4
"አንቲ ውእቱ ገራህት ዘኢተዘርአ ውስቴታ ዘርእ፥ ወጽአ እምኔኪ ፍሬ ሕይወት"።

ትርጉም፦ "ዘር ያልተዘራባት እርሻ አንቺ ነሽ፥ የሕይወት ፍሬ ከአንቺ ወጣ"።

እዚህ ዐውድ ላይ "ዘር" የተባለው የወንድ የዘር ሕዋስ ነው፥ ድንግል ማርያም ኢየሱስን ስትፀንስ የወንድ የዘር ሕዋስ የሌለው ቢሆንም በተፈጥሮዋ የወንድ የዘር ሕዋስ የሚዘራበት ማኅፀን ስላላት "እርሻ" ተብላለች። እና ድንግል ማርያም ሞፈርና ቀንበር አዋዶ የሆነው የጓሮ አትክልት አሊያም ሰብል ናትን? እሩቅ ሳንሄድ አማንያን እርሻ ተብለዋል፦
1 ቆሮንቶስ 3፥9 እናንተ የእግዚአብሔር እርሻ ናችሁ”*፤ you are God’s field. NIV

መልሳችሁ፦ "ውይ ወሒድ ደግሞ ይህ ቀላል ነገር እኮ ነው፦ "እርሻ ናችሁ" ሲለን "የጓሮ አትክልት ናችሁ" ማለት ሳይሆን ልባችን በእርሻ ተመስሏል፥ ቃሉ ደግሞ በዘር ይመሰላል። ይህ እንዴት አይገባህም?" ትላላችሁ፥ ለራስ ሲቆርሱ አያሳንሱ ነገር ነው። ከላይ ያለውንም በዚህ ቀመር ተረዱት! "አመድ በዱቄት ይስቃል" እንዲሉ የአሏህ ንግግር ላይ ስትስቁ እና ስትሳለቁ ትውፊት ላይ ሴት እርሻ እንደሆነች ኩልል እና ጥርት ብሎ ተቀምጧል። ለነገሩ ባይብል እና አዋልድ ሴት "ደካማ ፍጥረት ናት፥ በተፈጥሮዋ ደካማ ናት፥ የሰማችውን ሁሉ ሳታመዛዝን አሜን ብላ ትቀበላለችና" ይለናል፦
1 ጴጥሮስ 3፥7 እንዲሁም፥ እናንተ ባሎች ሆይ፥ ደካማ ፍጥረት ስለ ሆኑ ከሚስቶቻችሁ ጋር በማስተዋል አብራችሁ ኑሩ፤
ቀለሜንጦስ 2÷14 ሴት በተፈጥሮዋ ደካማ ናት፤ የሰማችውን ሁሉ ሳታመዛዝን አሜን ብላ ትቀበላለችና።

አሏህ ሂዳያህ ይስጣችሁ! ለእኛም ጽናቱን ይስጠን!

ከዐቃቤ እሥልምና ወሒድ
https://www.tg-me.com/Wahidcom

ወሠላሙ ዐለይኩም
ውይይት
የነብያት መንገድ | طريق الأنبياء
●▯ውይይት ▯●

"አይሁድ ሃይማኖት ነው?"

◍ ወንድም ሳለህ
        🅥🅢
◍ ወገናችን ዘካሪያስ
🔊🔊ታላቅ የውይይት ፕሮግራም🔊🔊

የፊታችን እለተ እሑድ[ 21 april ]  ከቀኑ 11:00🕚 እጅግ አጓጊ የሆነ የቴሌግራም ቀጥታ(ላይቭ) የውይይት ፕሮግራም በ ABU HANIF ISLAMIC APOLOGETICS የቴሌግራም  ግሩፕ  ተሰናድቶ እነሆ መምጣትዎን ይጠባበቃል።

         ተወያዮች
»»  ወንድም ኢብራሂም إبراهم [ሙስሊም ]
»» ወገናችን ፓስተር አቡከር [ፕሮቴስታንት ]

         የውይይቱ አርዕስት
      ምስጢረ–ሥላሴ(Trinity)
    
   እንኳን ማርፈድ ቀድሞ አለመገኘት ያስቆጫል 🔷
                  🔜🔜🔜
ውይይቱ ወደ ሚደረግበት ግሩፕ ለመታደም ሊንኩን ይጠቀሙ👉 https://www.tg-me.com/abu_hanif19
               ◻️◻️◻️
ሒጃብ

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ፥ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው።

33፥59 አንተ ነቢዩ ሆይ! ለሚስቶቸህ፣ ለሴቶች ልጆችህም፣ *ለምእምናን ሚስቶችም ከመከናነቢያዎቻቸው በላያቸው ላይ እንዲለቁ ንገራቸው*፡፡ ይህ እንዲታወቁ እና በባለጌዎች እንዳይደፈሩ ለመኾን በጣም የቀረበ ነው፡፡ አላህም መሓሪ አዛኝ ነው፡፡ يَا أَيُّهَا النَّبِيُّ قُل لِّأَزْوَاجِكَ وَبَنَاتِكَ وَنِسَاءِ الْمُؤْمِنِينَ يُدْنِينَ عَلَيْهِنَّ مِن جَلَابِيبِهِنَّ ۚ ذَٰلِكَ أَدْنَىٰ أَن يُعْرَفْنَ فَلَا يُؤْذَيْنَ ۗ وَكَانَ اللَّهُ غَفُورًا رَّحِيمًا

"ሒጃብ" حِجَاب ማለት "መሸፈኛ" "መሸፋፈኛ" "መጋረጃ" "ግርዶ" ማለት ነው፦
19፥17 *ከእነርሱም መጋረጃን አደረገች*፡፡ መንፈሳችንምም ጂብሪልን ወደ እርሷ ላክን፡፡ ለእርሷም ትክክለኛ ሰው ሆኖ ተመሰለላት፡፡ فَاتَّخَذَتْ مِن دُونِهِمْ حِجَابًا فَأَرْسَلْنَا إِلَيْهَا رُوحَنَا فَتَمَثَّلَ لَهَا بَشَرًا سَوِيًّا

እዚህ አንቀጽ ላይ መርየም እንዳያዩአት ያደረገችው መጋረጃ "ሒጃብ" حِجَاب ተብሎ ተቀምጧል። ሒጃብ ሙሥሊም ሴት የምትሰተርበት ኺማር እና ጂልባብ ነው፦
24፥31 *ለምእምናትም ንገራቸው፡- ዓይኖቻቸውን ይከልክሉ፡፡ ብልቶቻቸውንም ይጠብቁ፡፡ ጌጣቸውንም ከእርሷ ግልጽ ከኾነው በስተቀር አይግለጡ፡፡ ጉፍታዎቻቸውንም በአንገትጌዎቻቸው ላይ ያጣፉ*፡፡ የውስጥ ጌጣቸውንም ለባሎቻቸው ወይም ለአባቶቻቸው ወይም ለባሎቻቸው አባቶች ወይም ለወንዶች ልጆቻቸው ወይም ለባሎቻቸው ወንዶች ልጆች ወይም ለወንድሞቻቸው ወይም ለወንድሞቻቸው ወንዶች ልጆች ወይም ለእህቶቻቸው ወንዶች ልጆች ወይም ለሴቶቻቸው ወይም እጆቻቸው ለያዙት ወይም ከወንዶች ለሴት ጉዳይ የሌላቸው ለኾኑ ተከታዮች ወይም ለእነዚያ በሴቶች ሐፍረተ ገላ ላይ ላላወቁ ሕፃኖች ካልኾነ በስተቀር አይግለጹ፡፡ ከጌጣቸውም የሚሸፍኑት ይታወቅ ዘንድ በእግሮቻቸው አይምቱ፡፡ ምእመናኖች ሆይ! ትድኑ ዘንድ ሁላችሁም ወደ አላህ በመመለስ ተጸጸቱ፡፡ وَقُل لِّلْمُؤْمِنَاتِ يَغْضُضْنَ مِنْ أَبْصَارِهِنَّ وَيَحْفَظْنَ فُرُوجَهُنَّ وَلَا يُبْدِينَ زِينَتَهُنَّ إِلَّا مَا ظَهَرَ مِنْهَا ۖ وَلْيَضْرِبْنَ بِخُمُرِهِنَّ عَلَىٰ جُيُوبِهِنَّ ۖ وَلَا يُبْدِينَ زِينَتَهُنَّ إِلَّا لِبُعُولَتِهِنَّ أَوْ آبَائِهِنَّ أَوْ آبَاءِ بُعُولَتِهِنَّ أَوْ أَبْنَائِهِنَّ أَوْ أَبْنَاءِ بُعُولَتِهِنَّ أَوْ إِخْوَانِهِنَّ أَوْ بَنِي إِخْوَانِهِنَّ أَوْ بَنِي أَخَوَاتِهِنَّ أَوْ نِسَائِهِنَّ أَوْ مَا مَلَكَتْ أَيْمَانُهُنَّ أَوِ التَّابِعِينَ غَيْرِ أُولِي الْإِرْبَةِ مِنَ الرِّجَالِ أَوِ الطِّفْلِ الَّذِينَ لَمْ يَظْهَرُوا عَلَىٰ عَوْرَاتِ النِّسَاءِ ۖ وَلَا يَضْرِبْنَ بِأَرْجُلِهِنَّ لِيُعْلَمَ مَا يُخْفِينَ مِن زِينَتِهِنَّ ۚ وَتُوبُوا إِلَى اللَّهِ جَمِيعًا أَيُّهَ الْمُؤْمِنُونَ لَعَلَّكُمْ تُفْلِحُونَ

"ጉፍታዎች" ለሚለው በብዜት የገባው ቃል "ኹሙር" خُمُر ሲሆን በነጠላ ደግሞ "ኺማር" خِمَار ነው። እዚህ አንቀጽ ላይ አጅነቢይ ያልሆኑት ወንዶች ተዘርዝረዋል። “አጅነቢይ” أَجْنَبِيّ ማለት “ባዕድ” ማለት ሲሆን አንዲት ሙሥሊም በተቃራኒ ፆታ ያሉትን ለመጨበጥ ወይም ጸጉሯን ለማየት ሐላል ያልሆነ ሰው ማለት ነው። ይህ አንቀጽ ሲወርድ ሴቶች በኒቃብ ተሰትረዋል፥ "ኒቃብ" نِقَاب ማለት "መሸፈኛ" ማለት ነው፦
ኢማም ቡኻርይ መጽሐፍ 65, ሐዲስ 4759
ሶፊያህ ቢንት ሸይባህ እንደተረከችው፦ "ዓኢሻህ"ረ.ዐ." እንዲህ ትል ነበር፦ *"ጉፍታዎቻቸውንም በአንገትጌዎቻቸው ላይ ያጣፉ" የሚለው አንቀጽ በወረደች ጊዜ ሴቶቹ ከወገቦቻቸውን ጨርቆች በኩል ይቆርጡና ጭንቅላታቸውን እና ፊታቸውን በተቆረጡት የጨርቅ ቁርጥራጮች ይሸፍኑ ነበር"*። عَنْ صَفِيَّةَ بِنْتِ شَيْبَةَ، أَنَّ عَائِشَةَ ـ رضى الله عنها ـ كَانَتْ تَقُولُ لَمَّا نَزَلَتْ هَذِهِ الآيَةُ ‏{‏وَلْيَضْرِبْنَ بِخُمُرِهِنَّ عَلَى جُيُوبِهِنَّ‏}‏ أَخَذْنَ أُزْرَهُنَّ فَشَقَّقْنَهَا مِنْ قِبَلِ الْحَوَاشِي فَاخْتَمَرْنَ بِهَا‏.‏

"ጉፍታዎች" በሌላ አንቀጽ "መከናነቢያዎች" በሚል ተለዋዋጭ ቃል መጥቷል፦
33፥59 አንተ ነቢዩ ሆይ! ለሚስቶቸህ፣ ለሴቶች ልጆችህም፣ *ለምእምናን ሚስቶችም ከመከናነቢያዎቻቸው በላያቸው ላይ እንዲለቁ ንገራቸው*፡፡ ይህ እንዲታወቁ እና በባለጌዎች እንዳይደፈሩ ለመኾን በጣም የቀረበ ነው፡፡ አላህም መሓሪ አዛኝ ነው፡፡ يَا أَيُّهَا النَّبِيُّ قُل لِّأَزْوَاجِكَ وَبَنَاتِكَ وَنِسَاءِ الْمُؤْمِنِينَ يُدْنِينَ عَلَيْهِنَّ مِن جَلَابِيبِهِنَّ ۚ ذَٰلِكَ أَدْنَىٰ أَن يُعْرَفْنَ فَلَا يُؤْذَيْنَ ۗ وَكَانَ اللَّهُ غَفُورًا رَّحِيمًا
እዚህ አንቀጽ ላይ "መከናነቢያዎች" ለሚለው በብዜት የገባው ቃል "ጀላቢብ" جَلَٰبِيب ሲሆን በነጠላ ደግሞ "ጂልባብ" جِلْبَاب‎ ነው። ለባለጌዎች በጂልባብ ከተሰተረች ይልቅ የተራቆተች ሴት ለመተንኮስ፣ ለመለከፍ፣ ለመደፈር ቅርብ ናት። የዚህ አንቀጽ ሠበቡ አን-ኑዙሉ በዚህ ሐዲስ እንዲህ ተገልጿል፦
ኢማም ቡኻርይ መጽሐፍ 4, ሐዲስ 12
ዓኢሻህ"ረ.ዐ." እንደተረከችው፦ *"የነቢዩ"ﷺ" ባልተቤቶች በሌሊት ወደ መናሲዕ በጣም ሰፊ ቦታ ይሔዱ ነበር። ዑመርም ለነቢዩ"ﷺ"፦ "ባለቤቶችዎ መሸፈን አለባቸው" አለ፥ የአላህ መልእክተኛም"ﷺ" ምንም አላደረጉም። በዒሻእ ጊዜ የነቢዩ"ﷺ" ባለቤት ሠውዳህ ቢንት ዘምዓህ ወጣች፥ እርሷም ረጅም እመቤት ነበረች። ዑመርም፦ "ሠውዳህ ሆይ! ዐውቄሻለው" አላት፥ ስለ ሒጃብ ወሕይ እንዲወርድ በጉጉት ተመኘ። አላህም የሒጃብ አንቀጽ አወረደ"*። عَنْ عَائِشَةَ، أَنَّ أَزْوَاجَ النَّبِيِّ، صلى الله عليه وسلم كُنَّ يَخْرُجْنَ بِاللَّيْلِ إِذَا تَبَرَّزْنَ إِلَى الْمَنَاصِعِ ـ وَهُوَ صَعِيدٌ أَفْيَحُ ـ فَكَانَ عُمَرُ يَقُولُ لِلنَّبِيِّ صلى الله عليه وسلم احْجُبْ نِسَاءَكَ‏.‏ فَلَمْ يَكُنْ رَسُولُ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم يَفْعَلُ، فَخَرَجَتْ سَوْدَةُ بِنْتُ زَمْعَةَ زَوْجُ النَّبِيِّ صلى الله عليه وسلم لَيْلَةً مِنَ اللَّيَالِي عِشَاءً، وَكَانَتِ امْرَأَةً طَوِيلَةً، فَنَادَاهَا عُمَرُ أَلاَ قَدْ عَرَفْنَاكِ يَا سَوْدَةُ‏.‏ حِرْصًا عَلَى أَنْ يَنْزِلَ الْحِجَابُ، فَأَنْزَلَ اللَّهُ آيَةَ الْحِجَابِ‏.‏

ሚሽነሪዎች፦ "የሒጃብ አንቀጽ መውረድ ምክንያት ዑመር ነው" ይላሉ። ታዲያ ምን ችግር አለው? ሳራ ለአብርሃም፦ "ይህችን ባሪያ ከነልጅዋ አሳድድ! የዚህች ባሪያ ልጅ ከልጄ ከይስሐቅ ጋር አይወርስም" ብላ አሳቡን አምጥታ እግዚአብሔር ለአብርሃም አሳቧን እንዲቀበል፦ "ሣራም የምትነግርህን ቃል ሁሉ ስማ" ሲለው ለአጋር ብላቴናውንም ሰጥቶ አስወጣት፦
ዘፍጥረት 21፥10 *አብርሃምንም ይህችን ባሪያ ከነልጅዋ አሳድድ! የዚህች ባሪያ ልጅ ከልጄ ከይስሐቅ ጋር አይወርስምና" አለችው*።
ዘፍጥረት 21፥12 *እግዚአብሔርም አብርሃምን አለው፦ ስለ ባሪያህና ስለ ብላቴናው አትዘን፤ ሣራም የምትነግርህን ቃል ሁሉ ስማ"*።
ዘፍጥረት 21፥14 *አብርሃምም ማልዶ ተነሣ፥ እንጀራንም ወሰደ፥ የውኃ አቁማዳንም ለአጋር በትከሻዋ አሸከማት፥ ብላቴናውንም ሰጥቶ አስወጣት"*።

እግዚአብሔር አብርሃምን ያዘዘው ሳራ ባመጣቸው አሳብ ነው። የሒጃብ እሳቤ ዑመር ከመምጣቱ በፊት እኮ ባይብል ላይም አለ። ይስሐቅም ርብቃን ከማግባቱ በፊት አጅነቢይ ስለነበረ እንዳያያት ኺማር ወስዳ ተከናነበች፦
ዘፍጥረት 24፥65 *"እርስዋም መሸፈኛ ወስዳ ተከናነበች"*። فَأخَذَتْ رِفقَةُ الخِمارَ وَغَطَّتْ وَجهَها

"መሸፈኛ" ለሚለው ቃል የገባው "ኺማር" خِمارَ መሆኑ አንባቢ ልብ ይለዋል። "ወጀሀሃ" وَجهَها ማለት "ፊቷን" ማለት ነው፥ በሒጃብ የተሰተረችው ፊቷን ነው። በእስራኤል ሴቶቹ ዓይናቸውን በኒቃብ ይሸፈኑ ነበር። ንጉሥ ሰለሞን የሱላማጢስ ልጃገረጅን በዓይነ ርግብ መሸፈኛሽ ውስጥ ዓይኖች እና ጕንጭና ጕንጯ እንዳሉ መናገሩ በኒቃብ ፊታቸው እና አይናቸው ይሰተሩ እንደነበር አመላካች ነው፦
መኃልይ 4፥1 *በዓይነ ርግብ መሸፈኛሽ ውስጥ ዓይኖችሽ እንደ ርግቦች ናቸው*። عَيْنَاكِ حَمَامَتَانِ مِنْ تَحْتِ نَقَابِكِ
መኃልይ 4፥3 *በዓይነ ርግብ መሸፈኛሽ ውስጥ ጕንጭና ጕንጭሽ እንደ ተከፈለ ሮማን ናቸው*። كَفَلَقَةِ رُمّانَةٍ هُوَ خَدُّكِ تَحتَ خِمارِكِ

ሁለቱም አናቅጽ ላይ "መሸፈኛሽ" ለሚለው ቃል የገባው "ነቃቢኪ" نَقَابِكِ እና "ሒማሪኪ" خِمارِكِ ነው። "ኒቃብ" نِقَاب እና "ኺማር" خِمَار ባይብል ውስጥ እንዲህ በግልጽ ተቀምጧል። በአንድ ወቅት የሱላማጢስ ልጃገረጅን ሒጃብ ቅጥር ጠባቂዎች እንደወሰዱባት መናገሯ በራሱ ሒጃብ ታደርግ እንደነበር ማሳያ ነው፦
መኃልይ 5፥7 *ቅጥር ጠባቂዎችም የዓይነ ርግብ መሸፈኛዬን ወሰዱት*። وَنَزَعَ حُرّاسُ الأسوارِ خِمارِي عَنِّي

“ኺማሪ” خِمارِي የኺማር ቀዳማይ መደብ ነጠላ አገናዛብ ቃል ነው። አንድ ለዐቅመ-ሐዋ የሆነች ሴት ሶላት ላይ በኺማር የተሰተረች መሆን አለባት፦
ሡነን አቢ ዳውድ መጽሐፍ 2, ሐዲስ 251
ዓኢሻህ እንደተረከችው፦ “ነቢዩም”ﷺ” አሉ፦ *”አላህ ለዐቅመ-ሐዋ የሆነች ሴት ሶላት አይቀበል በኺማር የተሰተረች ቢሆን እንጂ”*። عَنْ عَائِشَةَ، عَنِ النَّبِيِّ صلى الله عليه وسلم أَنَّهُ قَالَ ‏ “‏ لاَ يَقْبَلُ اللَّهُ صَلاَةَ حَائِضٍ إِلاَّ بِخِمَارٍ ‏”‏ ‏

በባይብል ሴት ራስዋን በኺማር ሳትሸፍን ወደ ፈጣሪ ልትጸልይ አይገባትም፥ ጭራሽ ዲድስቅልያ ላይ ሴት አማኝ ሁሉም ቦታ እንድትከናነብ ወፍራም ትእዛዝ አለ፦
1 ቆሮንቶስ 11፥13 *በእናንተ በራሳችሁ መካከል ፍረዱ፤ ሴት ራስዋን ሳትሸፍን ወደ እግዚአብሔር ልትጸልይ ይገባታልን?*
ዲድስቅልያ 3፥32 ነገር ግን ላመኑ ሴቶች ራሳቸውን በንጽህና “ሊከናነቡ” ይገባል። እነርሱ “ተከናንበው” በጎዳና ራሳቸውን ዝቅ አድርገው ይሂዱ!።

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ የአዲስ ኪዳን መጽሐፍት ቀኖና 35 ናቸው፥ የአዲስ ኪዳን መደበኛ የቀኖና መጽሐፍት 27 ሲሆኑ ተጨማሪ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ መጽሐፍት ቀኖና 8 ሲሆኑ ከስምንቱ አንዱ "ዲድስቅልያ"didache" ነው።

ከዐቃቤ እሥልምና ወሒድ
https://www.tg-me.com/Wahidcom

ወሠላሙ ዐለይኩም
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
ከረመዳን በኋላ ዲን ላይ ለመፅናት የሚያግዙ 5 ነገሮች! | ኡስታዝ አህመድ አደም | Hadis Amharic | ahmed adem | @QesesTube
📖69-Al-Haqqah
: Yasser Al Dossari🎤
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
"ኢየሱስ በሥጋ ፍጡር ነው" የሚለው የመህር አክሊል ትምህርት በቤ ተክርስቲያን አበው መምህራን የምሥራቅ ኦርቶዶክ ምንፍቅና እንደሆነ ታውቆ ተወገዘ።
ሙሥሊም

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡

15፥2 እነዚያ የካዱት በትንሣኤ ቀን ሙሥሊሞች በኾኑ ኖሩ በብዛት ይመኛሉ፡፡ رُّبَمَا يَوَدُّ الَّذِينَ كَفَرُوا لَوْ كَانُوا مُسْلِمِينَ

"ሙሥሊም" مُسْلِم የሚለው ቃል "አሥለመ" أَسْلَمَ ማለትም "ታዘዘ" ከሚል ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን "ታዛዥ" ማለት ነው፥ የሙሥሊም ብዙ ቁጥር ደግሞ "ሙሥሊሙን" مُّسْلِمُون ወይም "ሙሥሊሚን" مُسْلِمِين ሲሆን "ታዛዦች" ማለት ነው፦
21፥108 «ያ ወደ እኔ የሚወረደው፦ “አምላካችሁ አንድ አምላክ ብቻ ነው” ማለት ነው፥ ታዲያ እናንተ ፍጹም ታዛዦች ናችሁን» በላቸው፡፡ قُلْ إِنَّمَا يُوحَىٰ إِلَيَّ أَنَّمَا إِلَـٰهُكُمْ إِلَـٰهٌ وَاحِدٌ ۖ فَهَلْ أَنتُم مُّسْلِمُون

እዚህ አንቀጽ ላይ "ታዛዦች" ለሚለው የገባው ቃል "ሙሥሊሙን" مُّسْلِمُون ሲሆን "ሙሥሊም" مُسْلِم ማለት "አንዱን አምላክ በብቸኝነት የሚያመልክ ወይም የሚታዘዝ" ማለት ነው፥ የፈጠረንን አሏህን በሙፍረዳት እና በሙሐረማት ወይንም በአምስቱ ሙሐከማት ስንታዘዝ ሙሥሊም እንሰኛለን። አምላካችን አሏህ ወደ አደም ኪዳን ሲያወርድ "ሙሥሊሞች" ብሎ ጠራን፦
20፥115 ወደ አደምም ከዚህ በፊት ኪዳንን በእርግጥ አወረድን፡፡ وَلَقَدْ عَهِدْنَا إِلَىٰ آدَمَ مِن قَبْلُ
22፥78 በአላህም ሃይማኖት ተገቢውን ትግል ታገሉ፡፡ እርሱ መርጧችኋል፡፡ በእናንተም ላይ በሃይማኖቱ ውስጥ ምንም ችግር አላደረገባችሁም፡፡ የአባታችሁን የኢብራሂምን ሃይማኖት ተከተሉ፡፡ እርሱ ከዚህ በፊት ሙሥሊሞች ብሎ ሰይሟችኋል፡፡ وَجَاهِدُوا فِي اللَّهِ حَقَّ جِهَادِهِ ۚ هُوَ اجْتَبَاكُمْ وَمَا جَعَلَ عَلَيْكُمْ فِي الدِّينِ مِنْ حَرَجٍ ۚ مِّلَّةَ أَبِيكُمْ إِبْرَاهِيمَ ۚ هُوَ سَمَّاكُمُ الْمُسْلِمِينَ مِن قَبْلُ

ቁርኣን በወረደበት ጊዜ አሏህ፦ "ሚን ቀብሉ" مِن قَبْلُ ማለትም "ከዚህ በፊት" የሚለውን ኢሥሙል መጅሩር የሚጠቁመን ወደ አደም ወሕይን ያወረደበትን ጊዜ ነው፥ በዚያን ጊዜ "ሙስሊሞች" ብሎ ሰይሟል። "እርሱ" የሚለው ተውላጠ ስም "አሏህ" የሚለውን ስም ተክቶ የመጣ ስለሆነ "ሙስሊሞች" ብሎ የሰየመው ኢብራሂም ሳይሆን አሏህ ነው፥ ምክንያቱም ከኢብራሂም በፊት ኑሕ፦ "ከሙሥሊሞች" እንደሆነ ተናግሯል፦
10፥72 «ብትሸሹም አትጎዱኝም፡፡ ከምንዳ ምንንም አልለምናችሁምና፥ ምንዳዬ በአላህ ላይ እንጂ በሌላ ላይ አይደለም፡፡ ከሙሥሊሞች እንድሆንም ታዝዣለሁ፡፡» فَإِن تَوَلَّيْتُمْ فَمَا سَأَلْتُكُم مِّنْ أَجْرٍ ۖ إِنْ أَجْرِيَ إِلَّا عَلَى اللَّهِ ۖ وَأُمِرْتُ أَنْ أَكُونَ مِنَ الْمُسْلِمِينَ

ከኑሕ በኃላ ኢብራሂም ከልጁ ከኢሥማዒል ጋር፦ "ሙሥሊሞች አርገን" ብሎ ዱዓእ አርጓል፦
2፥128 ጌታችን ሆይ! ለአንተ ታዛዦችም አድርገን፡፡ ከዘሮቻችንም ለአንተ ታዛዦች ሕዝቦችን አድርግ፡፡ رَبَّنَا وَاجْعَلْنَا مُسْلِمَيْنِ لَكَ وَمِن ذُرِّيَّتِنَا أُمَّةً مُّسْلِمَةً لَّكَ

እዚህ አንቀጽ ላይ "ታዛዦች" ለሚለው የገባው ቃል "ሙሥሊማህ" مُّسْلِمَة መሆኑ በራሱ ሙሥሊም ማለት ለአሏህ ታዛዥ መሆኑን ቁልጭ አርጎ አያሳይምን? አሏህ ኢብራሂምን፦ "አሥሊም" أَسْلِمْ ባለው ጊዜ "አሥለምቱ" أَسْلَمْتُ አለው፦
2፥131 ጌታው ለእርሱ ታዘዝ ባለው ጊዜ ለዓለማት ጌታ ታዘዝኩ አለ፡፡ إِذْ قَالَ لَهُ رَبُّهُ أَسْلِمْ ۖ قَالَ أَسْلَمْتُ لِرَبِّ الْعَالَمِينَ

ኢብራሂም ልጆቹን ኢሥማዒልን እና ይስሓቅን እንዲሁ የልጅ ልጁን የዕቁብን በኢሥላም አዘዘ፦
2፥132 በእርሷም ኢብራሂም ልጆቹን አዘዘ፡፡ وَوَصَّىٰ بِهَا إِبْرَاهِيمُ بَنِيهِ
ከዚያም የዕቁብም ልጆቹን፦ "እናንተ ሙሥሊሞች ኾናችሁ እንጂ አትሙቱ" አላቸው፦
2፥132 የዕቁብም፦ «ልጆቼ ሆይ! አላህ ለእናንተ ሃይማኖትን መረጠ፤ ስለዚህ እናንተ ሙሥሊሞች ኾናችሁ እንጂ አትሙቱ» አላቸው፡፡ وَيَعْقُوبُ يَا بَنِيَّ إِنَّ اللَّهَ اصْطَفَىٰ لَكُمُ الدِّينَ فَلَا تَمُوتُنَّ إِلَّا وَأَنتُم مُّسْلِمُونَ

ሙሣም ለሕዝቦቹ፦ "ሙሥሊሞች እንደ ሆናችሁ በአሏህ ላይ ትመካላችሁ" አላቸው፦
10፥84 ሙሣም አለ፡- «ሕዝቦቼ ሆይ! በአላህ አምናችሁ እንደ ሆነ በርሱ ላይ ተጠጉ፡፡ ታዛዦች እንደ ሆናችሁ በአላህ ላይ ትመካላችሁ»። وَقَالَ مُوسَىٰ يَا قَوْمِ إِن كُنتُمْ آمَنتُم بِاللَّهِ فَعَلَيْهِ تَوَكَّلُوا إِن كُنتُم مُّسْلِمِينَ

እዚህ አንቀጽ ላይ "ታዛዦች" ለሚለው የገባው ቃል "ሙሥሊሚን" مُّسْلِمِين እንደሆነ ልብ አድርግ! የዒሣ ሐዋርያትም ለዒሣ፦ "ሙሥሊሞች መኾናችንን መስክር" ማለታቸው በራሱ ከጥንትም የነበሩት ነቢያት እና ሐዋርያት ሙሥሊሞች ነበሩ፦
3፥52 ሐዋርያት፡- «እኛ የአላህ ረዳቶች ነን፤ በአላህ አምነናል፤ እኛም ትክክለኛ "ታዛዦች" መኾናችንን መስክር» አሉ፡፡ قَالَ الْحَوَارِيُّونَ نَحْنُ أَنصَارُ اللَّهِ آمَنَّا بِاللَّهِ وَاشْهَدْ بِأَنَّا مُسْلِمُونَ

እዚህ አንቀጽ ላይ "ታዛዦች" ለሚለው የገባው ቃል "ሙሥሊሙን" مُسْلِمُون መሆኑን ልብ አልክን? እንግዲህ ስለ ሉጥ፣ ዩሡፍ፣ ሡለይማን ወዘተ ነቢያት ሁሉ ሙሥሊሞች መሆናቸውን የጊዜ እና የቦታ ጉዳይ እንጂ በቁና ጥቅስ ማቅረብ ይቻላል።
በጥቅሉ ከቁርኣን መውረድ በፊት አንዱን አምላክ የሚያመልኩ የነበሩት ሙዋሒዱን በእነርሱ ላይ ቁርኣን በሚነበብላቸውም ጊዜ፦ "እኛ ከቁርኣን በፊት ሙሥሊሞች ነበርን" ሲሉ ጥንት ነቢያት እና ሐዋርያት ሲያመልኩት የነበረውን አንዱን አምላክ አምላኪ መሆናቸውን ማሳያ ነው፦
27፥53 በእነርሱ ላይ በሚነበብላቸውም ጊዜ «በእርሱ አምነናል፡፡ እርሱ ከጌታችን የኾነ እውነት ነው፡፡ እኛ ከእርሱ በፊት ሙሥሊሞች ነበርን» ይላሉ፡፡ وَإِذَا يُتْلَىٰ عَلَيْهِمْ قَالُوا آمَنَّا بِهِ إِنَّهُ الْحَقُّ مِن رَّبِّنَا إِنَّا كُنَّا مِن قَبْلِهِ مُسْلِمِينَ
ኢማም ሙሥሊም መጽሐፍ 15, ሐዲስ 457
ኢብኑ ዐባሥ እንደተረከው፦ "ነቢዩ"ﷺ" በረውሓእ ጋላቢዎችን በማግኘት፦ "እናንተ ማን ናችሁ? ብለው ጠይቋቸው፥ እነርሱም "እኛ ሙሥሊሞች ነን" ብለው መለሱላቸው። እነርሱም አንተስ ማን ነህ አሏቸው "እሳቸውም፦ "እኔ የአሏህ መልዕክተኛ ነኝ" አሏቸው"። عَنِ ابْنِ عَبَّاسٍ، عَنِ النَّبِيِّ صلى الله عليه وسلم لَقِيَ رَكْبًا بِالرَّوْحَاءِ فَقَالَ ‏"‏ مَنِ الْقَوْمُ ‏"‏ ‏.‏ قَالُوا الْمُسْلِمُونَ ‏.‏ فَقَالُوا مَنْ أَنْتَ قَالَ ‏"‏ رَسُولُ اللَّهِ ‏"‏

አምላካችን አሏህ በፍርድ ቀን እነዚያ በአንቀጾቹ ያመኑ እና ሙሥሊሞች የነበሩትን፦ "ገነትን ግቡ! እናንተም ጥንዶቻችሁም ትደሰታላችሁ ትከበሩማላችሁ" ይላቸዋል፦
43፥69 እነዚያ በአንቀጾቻችን ያመኑና ፍጹም ታዛዦች የነበሩትን «ገነትን ግቡ! እናንተም ጥንዶቻችሁም ትደሰታላችሁ ትከበሩማላችሁ» ይባላሉ፡፡ الَّذِينَ آمَنُوا بِآيَاتِنَا وَكَانُوا مُسْلِمِينَ ادْخُلُوا الْجَنَّةَ أَنتُمْ وَأَزْوَاجُكُمْ تُحْبَرُونَ
ኢማም ሙሥሊም መጽሐፍ 1, ሐዲስ 212
አቢ ሁረይራህ"ረ.ዐ." እንደተረከው፦ "ነቢዩ"ﷺ" እንዲህ አሉ፦ "እነሆ ሙሥሊም የሆነች ነፍስ እንጂ ሌላው ጀነትን አይገባትም"። ﻋَﻦْ ﺃَﺑِﻲ ﻫُﺮَﻳْﺮَﺓَ، ﺭﺿﻲ ﺍﻟﻠﻪ ﻋﻨﻪ ﻗَﺎﻝ ﻋﻦ ﺍﻟﻨَّﺒِﻲّ ﺻَﻠَّﻰ ﺍﻟﻠﻪُ ﻋَﻠَﻴْﻪِ ﻭَﺳَﻠَّﻢَ ﺃﻧﻪ ﻗَﺎﻝَ ﺃَﻧَّﻪُ ﻟَﺎ ﻳَﺪْﺧُﻞُ ﺍﻟْﺠَﻨَّﺔَ ﺇِﻟَّﺎ ﻧَﻔْﺲٌ ﻣُﺴْﻠِﻤَﺔٌ

በተቃራኒው ከሃድያን በፍርዱ ቀን ሙሥሊሞች በኾኑ ኖሩ በብዛት ይመኛሉ፦
15፥2 እነዚያ የካዱት በትንሣኤ ቀን ሙሥሊሞች በኾኑ ኖሩ በብዛት ይመኛሉ፡፡ رُّبَمَا يَوَدُّ الَّذِينَ كَفَرُوا لَوْ كَانُوا مُسْلِمِينَ

አሏህ እሥልምናን እንደወፈቀን ሙሥሊም አርጎ ያሙተን! አሚን።

ከዐቃቤ እሥልምና ወሒድ
https://www.tg-me.com/Wahidcom

ወሠላሙ ዐለይኩም
ትምህርት
የነብያት መንገድ | طريق الأنبياء
●▯ውይይት ▯●

◍ ወንድም ዒምራን
        🅥🅢
◍ ወገናችን አክሊሉ
ኢሥቲቃማህ

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው።

11፥112 እንደ ታዘዝከውም ቀጥ በል፡፡ ከአንተ ጋር ያመኑትም ቀጥ ይበሉ፡፡ فَاسْتَقِمْ كَمَا أُمِرْتَ وَمَن تَابَ مَعَكَ

በኢሥላም ነገረ-ድኅነት"soteriology" እራሱን የቻለ ትልቅ ነጥብ ሲሆን "ፈላሕ” فَلَّاح ወይም "ነጃህ" نَّجَاة ይባላል፦
40፥41 ወገኖቼም ሆይ! ወደ መዳን የምጠራችሁ ስኾን ወደ እሳት የምትጠሩኝ ስትኾኑ ለእኔ ምን አለኝ? وَيَا قَوْمِ مَا لِي أَدْعُوكُمْ إِلَى النَّجَاةِ وَتَدْعُونَنِي إِلَى النَّارِ

እዚህ አንቀጽ ላይ "መዳን" ለሚለው የገባው ቃል "ነጃህ" نَّجَاة እንደሆነ ልብ በል! ሰዎችን ወደ ኢሥላም ስንጠራ ከእሳት እንዲድኑ ነው። አምላካችን አሏህ ምሕረት አድርጎ ከአሳማሚ ቅጣት የሚያድነን ንስሓ ስንገባ፣ ስናምን፣ መልካም ሥራ ሥንሠራ እና ስንጸና ነው፦
20፥82 እኔም ለተጸጸተ፣ ላመነም፣ መልካምንም ለሠራ፣ ከዚያም ለተመራ ሰው በእርግጥ መሐሪ ነኝ። وَإِنِّي لَغَفَّارٌ لِّمَن تَابَ وَآمَنَ وَعَمِلَ صَالِحًا ثُمَّ اهْتَدَىٰ

"ለተጸጸተ" ሲል ንስሓን፣ "ላመነ" ሲል ኢማንን፣ "መልካምን ለሠራ" ሲል ዐሚሉ ሷሊሓትን፣ "ለተመራ" ሲል ኢሥቲቃማህን ያመለክታል፥ ኢሥቲቃማህ በተጸጸተበት ንስሓ፣ ባመነበት ኢማን እና በምንሠራው መልካም ሥራ መጽናት ነው። "ኢሥቲቃማህ" اِسْتِقَامَة የሚለው ቃል "ኢሥቲቃመ اِسْتَقَامَ ማለትም "ቆመ" ወይም "ጸና" ከሚል ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን "ጽናት" ማለት ነው፦
42፥15 ለዚህም ድንጋጌ ሰዎችን ጥራ፡፡ እንደታዘዝከውም ቀጥ በል፡፡ فَلِذَٰلِكَ فَادْعُ ۖ وَاسْتَقِمْ كَمَا أُمِرْتَ
11፥112 እንደ ታዘዝከውም ቀጥ በል፡፡ ከአንተ ጋር ያመኑትም ቀጥ ይበሉ፡፡ فَاسْتَقِمْ كَمَا أُمِرْتَ وَمَن تَابَ مَعَكَ

እነዚህ አንቀጽ ላይ "ቀጥ በል" ለሚለው የገባው ቃል "ኢሥተቂም" اسْتَقِمْ ሲሆን "ጽና" ማለት ነው፥ በቀጥተኛው መንገድ ላይ መጽናት ፍርሃት እና ሐዘን ሳይኖር የጀነት ለመሆን መበሰር ነው፦
46፥13 እነዚያ «ጌታችን አላህ ነው» ያሉ፣ ከዚያም ቀጥ ያሉ በእነርሱ ላይ ፍርሃት የለባቸውም። እነርሱም አያዝኑም፡፡ إِنَّ الَّذِينَ قَالُوا رَبُّنَا اللَّهُ ثُمَّ اسْتَقَامُوا فَلَا خَوْفٌ عَلَيْهِمْ وَلَا هُمْ يَحْزَنُونَ
41፥30 እነዚያ «ጌታችን አላህ ነው» ያሉ ከዚያም ቀጥ ያሉ «አትፍሩ፤ አትዘኑም፤ በዚያችም ተስፋ ቃል ትደረግላችሁ በነበራችሁት ገነት ተበሰሩ» በማለት በእነርሱ ላይ መላእክት ይወርዳሉ፡፡ إِنَّ الَّذِينَ قَالُوا رَبُّنَا اللَّهُ ثُمَّ اسْتَقَامُوا تَتَنَزَّلُ عَلَيْهِمُ الْمَلَائِكَةُ أَلَّا تَخَافُوا وَلَا تَحْزَنُوا وَأَبْشِرُوا بِالْجَنَّةِ الَّتِي كُنتُمْ تُوعَدُون

እነዚህ አናቅጽ ላይ "ቀጥ ያሉ" ለሚለው ቃል የገባው "ኢሥተቃሙ" اسْتَقَامُوا ሲሆን አምላካችን አሏህ በዲኑል ኢሥላም ለሚጸኑ አማንያን ጀነትን ተስፋ ሰቷቸዋል፦
17፥108 ይላሉም «ጌታችን ጥራት ይገባው! እነሆ የጌታችን ተስፋ ተፈጻሚ ነው፡፡» وَيَقُولُونَ سُبْحَانَ رَبِّنَا إِن كَانَ وَعْدُ رَبِّنَا لَمَفْعُولًا
19፥61 የመኖሪያን ገነቶች ያችን አልረሕማን ለባሮቹ በሩቅ ኾነው ሳሉ ተስፋ ቃል የገባላቸውን ይገባሉ፡፡ እርሱ ተስፋው ተፈጻሚ ነውና። جَنَّاتِ عَدْنٍ الَّتِي وَعَدَ الرَّحْمَـٰنُ عِبَادَهُ بِالْغَيْبِ ۚ إِنَّهُ كَانَ وَعْدُهُ مَأْتِيًّا

ለጽናት ጉልኅ ሚናህ ያለው አሏህን ለመገናኘት ተስፋ ማድረግ ነው፥ ከእዝነቱ ተስፋ መቁረጥ ግን ለጽናት እንቅፋት ነው፦
29፥5 የአላህን መገናኘት ተስፋ የሚያደርግ ሰው ይዘጋጅ፡፡ የአላህ ቀጠሮ በእርግጥ መጪ ነውና፡፡ እርሱም ሰሚው ዐዋቂው ነው፡፡ مَن كَانَ يَرْجُو لِقَاءَ اللَّهِ فَإِنَّ أَجَلَ اللَّهِ لَآتٍ ۚ وَهُوَ السَّمِيعُ الْعَلِيمُ
29፥23 እነዚያም በአላህ አንቀጾችና በመገናኘቱ የካዱ እነዚያ ከእዝነቴ ተስፋን ቆረጡ፡፡ እነዚያም ለእነሱ አሳማሚ ቅጣት አላቸው፡፡ وَالَّذِينَ كَفَرُوا بِآيَاتِ اللَّهِ وَلِقَائِهِ أُولَـٰئِكَ يَئِسُوا مِن رَّحْمَتِي وَأُولَـٰئِكَ لَهُمْ عَذَابٌ أَلِيمٌ

አምላካችን አሏህ አንድ አምላክ ብቻ ነውና በሰጠን ተስፋ ወደ እርሱ ቀጥ ማለት ለጀነት ይዳርጋል፦
31፥6 እንዲህ በላቸው «እኔ መሰላችሁ ሰው ብቻ ነኝ፡፡ አምላካችሁ አንድ አምላክ ብቻ ነው ወደ እርሱም "ቀጥ በሉ" ምሕረትንም ለምኑት» ማለት ወደ እኔ ይወረድልኛል፡፡ ለአጋሪዎቹም ወዮላቸው፡፡ قُلْ إِنَّمَا أَنَا بَشَرٌ مِّثْلُكُمْ يُوحَىٰ إِلَيَّ أَنَّمَا إِلَـٰهُكُمْ إِلَـٰهٌ وَاحِدٌ فَاسْتَقِيمُوا إِلَيْهِ وَاسْتَغْفِرُوهُ ۗ وَوَيْلٌ لِّلْمُشْرِكِينَ

አሏህ በዲኑል ኢሥላም ያጽናን! አሚን።

ከዐቃቤ እሥልምና ወሒድ
https://www.tg-me.com/Wahidcom

ወሠላሙ ዐለይኩም
መርየምን አምልኩ ይላልን?
የነብያት መንገድ | طريق الأنبياء
●▯ጥያቄዎችና መልሶቻቸው▯●

"መርየም በቁርዓን ውስጥ "ሥላሴ" ተብላለችን?"

◍ ወንድም ሳላህ
◍ ወንድም ዒምራን
2024/05/15 23:27:05
Back to Top
HTML Embed Code: