Telegram Web Link
🇪🇹🇮🇳 ኢትዮጵያ እና ሕንድ የመጀመሪያውን የጋራ የመከላከያ ትብብር ስብሰባ በኒው ዴልሂ አካሄዱ

ስብሰባው በሕንድ የመከላከያ ሚኒስቴር አሚታብ ፕራሳድ እና በኢትዮጵያ የመከላከያ የውጭ ግንኙነትና ወታደራዊ ትብብር ዋና ዳይሬክተር ሜጀር ጄኔራል ተሾመ ገመቹ የጋራ ሊቀ -መንበርነት ተመርቷል።

ሁለቱ ወገኖች በመካሄድ ላይ ያለውን የመከላከያ ትብብር ገምግመው፦

🔶 በሥልጠና፣
🔶 በጋራ ወታደራዊ ልምምዶች፣
🔶 በሕክምና ትብብር እና
🔶 በመከላከያ ኢንዱስትሪ ተሳትፎ ዙሪያ ለአዲስ ትብብር የሚሆኑ መንገዶችን ተወያይተዋል።

🤝 ሁለቱም ልዑካን ቡድኖች የመከላከያ ትብብር እንቅስቃሴዎችን የበለጠ ለማሳደግ እና ለማስፋት መስማማታቸውን የሕንድ መንግሥት የፕሬስ ኢንፎሜሽን ቢሮ አስታውቋል፡፡

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | 📲 መተግበሪያ | 👉 X
10👎2
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ
የካሜሩን ተቃዋሚ እጩ ኢሳ ቲቺሮማ ፕሬዝዳንታዊ ምርጫውን እንዳሸነፉ በመግለፅ ፖል ቢያ ወጤቱን እንዲቀበሉ አሳሰቡ ኢሳ ቲቺሮማ በሰሜናዊ ካሜሩን ከምትገኘው ጋሩዋ ከተማ አሸናፊነታቸው "ግልጽ" እንደሆነ እና የሕዝብ ምርጫ "መከበር አለበት" ሲሉ አጥብቀው ተናግረዋል። የካሜሩን የምርጫ ሕግ የምርጫ ጣቢያ ውጤቶች እንዲታተሙ ቢፈቅድም፤ የሕገ-መንግሥት ምክር ቤቱ የመጨረሻውን ቆጠራ በማረጋገጥ ይፋዊ ውጤቱን…
🇨🇲 🗳 የካሜሮን የድህረ ምርጫ ውጥረት፤ የድምፅ ቆጠራ ኮሚሽን እርምጃ ወስዷል

👉  33 አባላት ያሉት ይህ የምርጫ አካል በጥቅምት 2 የተካሄደውን ፕሬዝዳንታዊ ምርጫ ድምጾችን የመቁጠር ኃላፊነት አለበት።

👉 ትናንት በካሜሩን የምርጫ ምክር ቤት ይፋ የተደረገው አወቃቀር ፤ በ58ቱ የመምሪያ ኮሚሽኖች የቀረቡ ቃለ-ጉባኤዎችን የማሰባሰብ ሥራን ያካትታል።

👉 ይህ ሥራ ከተጠናቀቀ በኋላ፣ የኮሚሽኑ የመጨረሻ ውጤቶች ሪፖርት እስከ ጥቅምት 16 ድረስ የማወጅ ሥልጣን ወዳለው ወደ ሕገ-መንግሥታዊ ምክር ቤት ይላካል።

በሀገሪቱ ውስጥ ያለው ሁኔታ አሁንም ውጥረት የበዛበት ነው፡፡ ለ43 ዓመታት በሥልጣን ላይ ያሉት የ92 ዓመቱ ፕሬዝዳንት ፖል ቢያ ስምንተኛ የሥልጣን ዘመን ሽተዋል፡፡

ይፋዊ ውጤት ከመታወቁ በፊት፣ የካሜሩን "ናሽናል ሳልቬሽን ፍሮንት" እጩ የሆኑት ኢሳ ችሮማ ባካሪ አሸናፊ መሆናቸውን አውጀዋል። ባለሥልጣናትን በምርጫ ማጭበርበር የከሰሱ ተቃዋሚዎች በዱዋላ እና ድሻንግ ተቃውሞዎችን አስነስተዋል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | 📲 መተግበሪያ | 👉 X
4
🇪🇹 🇹🇷 ኢትዮጵያ እና ቱርክ የገበያ ተደራሽነት ስምምነት ተፈራረሙ

🤝 ለኢትዮጵያ የዓለም ንግድ ድርጅት አባልነት ድርድር ወሳኝ አካል የሆነውን ስምምነት የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ዶ/ር ካሳሁን ጎፌ፣ ከአፍሪካ የቱርክ የንግድ ሚኒስትሮች ስብሰባ ጎን ለጎን ከቱርክ አቻቸው ፕሮፌሰር ሾማር ቦላት ጋር ተፈራርመዋል።

ሚኒስትሩ ይህ ለዓለም ንግድ ድርጅት አባልነት ሂደታችን ትልቅ ምዕራፍ ነው ብለዋል። አክለውም ከሌሎች አባል አገራት ጋር የሚደረገው የሁለትዮሽ የገበያ ዕድል ድርድር ግማሹ በቴክኒክ ደረጃ መጠናቀቁን ጠቅሰው ከሌሎች ጋርም የድርድር ሂደቱ በተሳካ መልኩ እየተከናወነ መሆኑን አስታውቀዋል።


የዓለም ንግድ ድርጅት 6ኛው የሥራ ቡድን ስብሰባ በቅርቡ ውጤታማ በሆነ ስኬት መካሄዱ የሚታወስ ሲሆን ለ7ኛው የሥራ ቡድን ስብሰባም ዝግጅቱ ተጠናክሮ መቀጠሉን ሚኒስቴሩ በማኅበራዊ የትስስሩ ገፁ አስነብቧል።

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | 📲 መተግበሪያ | 👉 X
6👏5👎4🔥2
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ
ፑቲን የአርቲ ጣቢያ 20ኛ ዓመት የምሥረታ በዓልን አስመልክቶ የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፉ "ራሽያ ቱዴይ (አርቲ) ሲጠነሰስ ጅምሮ፣ በዚህ ልክ ከፍ ይላል፤ ይህን ያህል የጥራት ደረጃ ላይ ይደርሳል እንዲሁም አሁን በያዘው መንገድ ያድጋል የሚል ሐሳብ አልነበረኝም" ሲሉ ፕሬዝዳንቱ ተናግረዋል። አርቲ በተለያዩ ቋንቋዎች የሚያሰራጭ ሲሆን፣ በዓለም አቀፍ ጉዳዮች ላይ የሞስኮን አቋም የሚያንፀባርቅ…
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
ፑቲን የአርቲ ቡድን እውነትን ለመከላከል ላሳየው የማይናወጥ ቁርጠኝነት አድናቆታቸውን ገለፁ

አርቲ ሥራውን በመሠረታዊነት ወደ አዲስ ደረጃ የማሳደግ ፈታኝ ተልዕኮ ተሰጥቶት የነበረ ሲሆን፣ በቦልሾይ ቴአትር የጣቢያውን 20ኛ ዓመት አስመልክቶ ንግግር እንዳደረጉት የሩሲያው ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን ደግሞ ቻናሉ ይህንን በሚያስደንቅ ሁኔታ አሳክቷል።

👉 ፕሬዝዳንቱ አርቲ ሥራዎቹን በተሳካ ሁኔታ ወደ አዲስ ደረጃ ከፍ በማድረጉ አወድሰውታል።

እሳቸው እንዳስተዋሉት፣ የምዕራባውያን መገናኛ ብዙኃን የመረጃ የበላይነታቸውን ለረጅም ጊዜ ሲጠቀሙበት ከርመዋል፤ አሁን ግን "በዓለም ዙሪያ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ሰዎች አርቲን ያምናሉ።"

"የትኛውም ጠቅላይነት ፈጥኖም ሆነ ዘግይቶ ማብቃቱ አይቀርም፡፡"


ፑቲን አጽንዖት ሰጥተው እንደተናገሩት፣ "ሩሲያ ሁል ጊዜ የምታስጠብቀው ሉዓላዊነቷ ለሰዎችን ተጨባጭ እና ያልተዛባ መረጃ የማቅረብ ችሎታ ላይ የተመሠረተ ነው።"

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | 📲 መተግበሪያ | 👉 X
👍8👏43
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ
ፑቲን የአርቲ ቡድን እውነትን ለመከላከል ላሳየው የማይናወጥ ቁርጠኝነት አድናቆታቸውን ገለፁ አርቲ ሥራውን በመሠረታዊነት ወደ አዲስ ደረጃ የማሳደግ ፈታኝ ተልዕኮ ተሰጥቶት የነበረ ሲሆን፣ በቦልሾይ ቴአትር የጣቢያውን 20ኛ ዓመት አስመልክቶ ንግግር እንዳደረጉት የሩሲያው ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን ደግሞ ቻናሉ ይህንን በሚያስደንቅ ሁኔታ አሳክቷል። 👉 ፕሬዝዳንቱ አርቲ ሥራዎቹን በተሳካ ሁኔታ ወደ አዲስ…
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
ዛሬ ላይ አርቲ በዓለም ዙሪያ የታወቀ ዓለም አቀፍ ብራንድ ነው - ፑቲን

“ባለፉት 20 ዓመታት በመገናኛ ብዙኃን ምህዋር ውስጥ በርካታ ሁነቶች ተከስተዋል፡፡ ይህ ሙሉ ዘመን ሲሆን፣ የሩሲያ ቱዴይ (RT) ቻናል ከሐሳብነት ተነስቶ ዛሬ በዓለም ዙሪያ የታወቀ ዓለም አቀፋዊ ሥም (ብራንድ) ሆኗል።

ንቁ፣ ፈጣሪ እና ጠንካራ ቡድናችሁን ለከፍተኛ የሙያ ብቃታችሁ እንዲሁም ለሙያችሁና ለግዴታችሁ ታማኝ በመሆናችሁ አመሰግናለሁ።

በዓለም አቀፉ የመረጃ ዘርፍ እውነትን በመከላከል ረገድ ደፋርና ቆራጥ በመሆናችሁም አመሰግናለሁ።”


አርቲን (RT) ያገዱ የምዕራባውያን ልሂቃን ምላሽን ኃላቀር ሲሉ ገልጸውታል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | 📲 መተግበሪያ | 👉 X
👏113💯3
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ
🇪🇹🇷🇺 በሞስኮ የኢትዮጵያ ባሕሎች የደመቁበት የፊልሃርመኒክ አዳራሽ ድግስ በኢትዮጵያ የባሕልና ስፖርት ሚኒስቴር አዘጋጅነትና በሻኩራ ፕሮዳክሽን አስተባባሪነት ወደ ሞስኮ ያቀናው ኪን-ኢትዮጵያ ቡድን በሩስያ ሁለተኛ መድረኩን በልዩ ድምቀት ተካሂዷል። በመድረኩ የኢትዮጵያን ቱባ ባሕል የሚያሳዩ ባሕላዊ ሙዚቃ፣ ውዝዋዜ፣ የባሕል አልባሳት ትዕይንተ-ፋሽን እንዲሁም የሰርከስ ትርዒት ቀርቧል። ዝግጅቱን ሩሲያውያን፣…
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
🇪🇹🇷🇺በሩሲያ የአገራቱን ወንድማማችነት ይበልጥ የሚያጸና ቆይታ ነበርን - ድምጻዊ ወንድዬ አበበ

🎭 የኪን ኢትዮጵያ የባህል እና ኪነ-ጥበብ ቡድን አባሉ፣ ጉዞው የአገሪቱን ታሪክ፣ ባህል እና እሴት በጥልቀት በማሳየት፣ ሩሲያዊያን ስለኢትዮጵያ ያላቸውን መልካም ምናብ አካል ያለበሰ መሆኑን ለስፑትኒክ አፍሪካ ገልጿል።

🗣 "መድረኩ ሩሲያዊያን በበጎ የሚስሏትን ኢትዮጵያን በጥበብ ያዩበት ነው። የባህል ልውውጡ የአገራቱን የረጅም ዘመናት ወዳጅነት ወደ ሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነት የማሳደግን አስፈላጊነትን አረጋግጧል፡፡" ብሏል።


📌ወንድዬ ኮንታ በሩሲያ ቆይታው ስለተመለከታቸው አስደናቂ ጉዳዮችም አካፍሎናል።

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | 📲 መተግበሪያ | 👉 X
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
13👎6🥰2👏2
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
ትራምፕ የዩክሬን ግጭት ቶማሃውክ ሚሳኤሎችን መጠቀም ታሳቢ ሳይደረግ ሊፈታ እንደሚችል ያላቸውን ተስፋ ገልፀዋል

አሜሪካ ቶማሃውኮችን እንዲሁም ወደ ዩክሬን እየተላኩ ያሉ ሌሎች በርካታ ጦር መሣሪያዎች ያስፈልጓታል ሲሉ ተናግረዋል።

ፕሬዝዳንቱ፣ ዩክሬን ያጣቻቸውን ግዛቶችን መልሳ ስለማግኘት ያላት ዕድል በተመለከተ ሲናገሩ፣ “ፈጽሞ አታውቁም። ... በጣም የማይገመት ነው።” ብለዋል፡፡


በሩሲያ እና በአላስካ መካከል የመሿለኪያ ቦይ ሐሳብንም 'አስደሳች' መሆኑን አንስተዋል፡፡ ዘለንስኪ በአንጻሩ፣ "በዚህ ሐሳብ ደስተኛ አይደለሁም" ብለዋል። ትራምፕም፣ "የምትወዱት አይመስለኝም" የሚል ምላሽ ሰጥተዋቸዋል፡፡

የአሜሪካው መሪ፣ የዩክሬን ወደ ሩሲያ ዘልቃ ማጥቃት ውጥረትን ማባባስ እንደሚሆን ያምናሉ።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | 📲 መተግበሪያ | 👉 X
5👍3👎1🤣1
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ
ትራምፕ የዩክሬን ግጭት ቶማሃውክ ሚሳኤሎችን መጠቀም ታሳቢ ሳይደረግ ሊፈታ እንደሚችል ያላቸውን ተስፋ ገልፀዋል አሜሪካ ቶማሃውኮችን እንዲሁም ወደ ዩክሬን እየተላኩ ያሉ ሌሎች በርካታ ጦር መሣሪያዎች ያስፈልጓታል ሲሉ ተናግረዋል። ፕሬዝዳንቱ፣ ዩክሬን ያጣቻቸውን ግዛቶችን መልሳ ስለማግኘት ያላት ዕድል በተመለከተ ሲናገሩ፣ “ፈጽሞ አታውቁም። ... በጣም የማይገመት ነው።” ብለዋል፡፡ በሩሲያ እና በአላስካ…
ለዩክሬን ሰላም 'በጣም ተቃርበናል' ያሉት ትራምፕ ግጭቱን ያለ ቶማሃውክ ለመፍታት አቅደዋል

የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ከዩክሬኑ ቮሎዲሚር ዘለንስኪ ጋር በትናንትናው ዕለት በዋይት ኅውስ  ውይይት አድርገዋል። ከሩሲያው ፕሬዝዳንት ፑቲን ጋር በቅርቡ ያደረጉትን የስልክ ውይይት፣ የዩክሬን ግጭት መፍትሄ አቅጣጫ እና በቅርቡ በቡዳፔስት የታቀደውን ድርድር ውይይት ተካሂዶበታል።

👉 ትራምፕ በስብሰባው ወቅት ሰላም የማምጣት ተስፋ እንዳላቸው የገለፁ ሲሆን የሰላም ሂደቱ ጥሩ ደረጃ ላይ እና ወደ ፍጻሜው ላይ እየደረሰ መሆኑን አስታውቀዋል። እንዲሁም ከኪዬቭ እና ከሞስኮ ጋር ለሚያደርጉት ድርድር ያቀዱትን ስትራቴጂ አስቀምጠዋል።

ከትራምፕ ንግግር የተወሰዱ ቁልፍ ነጥቦች

⚫️ ስለ ሰላም ድርድር፡ "በዩክሬን ሰላም ላይ ታላቅ መሻሻል እያሳየን ነው፤ እናሳካዋለን ብዬ አስባለሁ።"

⚫️ ከፑቲን ጋር ስላደረጉት ውይይት፡ ትራምፕ ከሩሲያው ፕሬዝዳንት ጋር በቅርቡ በስልክ ያደረጉትን ውይይት ዝርዝር መረጃ ከዘለንስኪ ጋር በሚያደርጉት ውይይት ወቅት እንደሚያጋሩ ጠቁመዋል።

⚫️ ስለ ቡዳፔስት መመረጥ፡ ከፑቲን ጋር ለሚያደርጉት ስብሰባ ቡዳፔስት ለምን እንደተመረጠች ለተጠየቁት ጥያቄ  “ምክንያቱም ኦርባንን ስለምንወደው ነው” ብለዋል።

⚫️ ስለ ስብሰባው ቅርፅ፡ ከፑቲን እና ከዘለንስኪ ጋር ሊደረግ ስለሚችለው  የሦስትዮሽ ጉባኤን አስመልክቶ “መካሄዱ አይቀርም፣ ሁለት ስብሰባ ይሆናል” ብለዋል።

⚫️ የፑቲንን አቋም አስመልክቶ፡ “ፑቲን የዩክሬንን ግጭት መቋጨት የሚፈልግ ይመስለኛል።”

⚫️ ግጭት ማባባስን ስለ ማስወገድ፡ “ግጭቱን ስለ ቶማሃውክ ሳናስብ ማቆም እንችላለን ብዬ ተስፋ አደርጋለሁ፤ ቶማሃውኮች ትልቅ ነገር ናቸው እና ግጭቱን እንዲባባስ ሊያደርጉ ይችላሉ።”

⚫️ ግዛትን መልሶ ስለ ማግኘት፡ ዩክሬን ያጣቻቸውን ግዛቶችን መልሳ ስለማግኘት ለተጠየቁት ጥያቄ ትራምፕ፣ “መቼም አታውቁም” ብለዋል።

⚫️ ስለ ሰላም ቅድመ ሁኔታዎች፡ “መፍትሄ እንዲመጣ ፑቲን እና ዘለንስኪ ትንሽ መግባባት አለባቸው።”

⚫️ ስለ ቻይና ሚና፡ ትራምፕ ከቤጂንግ ጋር በዩክሬን ጉዳይ ላይ እየተነጋገሩ መሆኑን ጠቅሰው፣ “ግጭቱ በፍጥነት እንዲያልቅ እፈልጋለሁ” ብለዋል።

⚫️ የድሮን ትብብርን በተመለከተ፡ አሜሪካ ከዩክሬን ጋር የድሮን ቴክኖሎጂ ልውውጥን እየፈለገች ነው፤ “በጣም ጥሩ ድሮን ይሰራሉ” በማለት ትራምፕ አስተያየት ሰጥተዋል። ብዛት ያለው የሚሳኤል ክምችት የመያዝ አስፈላጊ መሆኑንም አሳስበዋል።

⚫️ የሩሲያ-አላስካ ማስተላለፊያ መስመር፡ ሩሲያን እና አላስካን ሊያገናኝ ስለሚችለው በዕቅድ ላይ ያለ መሿለኪያን በተመለከተ ለተጠየቁት ጥያቄ ትራምፕ “ጥሩ ነገር” ሲሉ ገልጸው፣ “ላስብበት ይገባል” ብለዋል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | 📲 መተግበሪያ | 👉 X
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
7👍2😁1
🌍 አፍሪካ ፣ ልዩ ምርጫ ይህን የመልዕክት መለዋወጫ 'ፎልደር' ከአህጉሪቱ አዳዲስ ዜናዎች ከሚገኙበት ቻናሎች ላይ ይጨምሩት ⤵️

👉👉 https://www.tg-me.com/addlist/lwYcxR-tjCBiODBi 👈👈

#social
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
1
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ
ለዩክሬን ሰላም 'በጣም ተቃርበናል' ያሉት ትራምፕ ግጭቱን ያለ ቶማሃውክ ለመፍታት አቅደዋል የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ከዩክሬኑ ቮሎዲሚር ዘለንስኪ ጋር በትናንትናው ዕለት በዋይት ኅውስ  ውይይት አድርገዋል። ከሩሲያው ፕሬዝዳንት ፑቲን ጋር በቅርቡ ያደረጉትን የስልክ ውይይት፣ የዩክሬን ግጭት መፍትሄ አቅጣጫ እና በቅርቡ በቡዳፔስት የታቀደውን ድርድር ውይይት ተካሂዶበታል። 👉 ትራምፕ በስብሰባው…
🗣ትራምፕ እና ዘለንስኪ በቶማሃውክ ጉዳይ ላይ አልተስማሙም - ባለሙያ

💬"ዘለንስኪ እና ትራምፕ አንድ አይነት አቋም ላይ እንዳልሆኑ ግልጽ ነው። ዘለንስኪ ቶማሃውክን አሁን ከእጃቸው እንዲገባ በመፈለግ ጦርነቱን ማራዘም ብቻ ሲሆን፣ ትራምፕ ግን ቶማሃውክን ሁለቱም ወገኖች ግጭቱን እንዲያቆሙ ለመደራደር እንደ ግፊት መጠቀም ይፈልጋሉ" ሲሉ የቀድሞ የአሜሪካ መከላከያ ሚኒስቴር ከፍተኛ የጸጥታ ፖሊሲ ተንታኝ ሚካኤል ማሎፍ የትራምፕና ዘለንስኪ ስብሰባን አስመልክቶ ለስፑትኒክ ተናግረዋል።

👉ማሎፍ "ፑቲን የ2.5 ሰዓት የስልክ ንግግራቸው 'ውጤታማ' እንደነበር ትራምፕ እንዲናገሩ ያደረጉበት አንዳች ነገር ተናግረው መሆን አለበት" ብለው ያምናሉ።

🔍 "ፑቲን ምን እንደሚያቀርቡ እናያለን፤ ለምሳሌ እስካሁን የደረሱበትን በመያዝ ወደፊት አለመገስገስ፣ ከእርቅ ጋር። ዘለንስኪ ጦርነቱን ማራዘም የሚፈልጉት አውሮፓውያን በሰጧቸው መሠረተ ቢስ ተስፋ ላይ ተመርኩዘው ነው" ነገር ግን "አውሮፓ የጦርነት ኢኮኖሚን መቋቋም አትችልም"።

❗️"በሚቀጥሉት ሳምንታት እና ወራት ትራምፕ የኔቶ አጋሮቻቸውን ማስቀተል ፈታኝ ይሆንባቸዋል። በትራምፕ እና በኔቶ አገሮች መካከል ያለው ክፍተት ከቀጠለ ኔቶ ራሱ የፍጻሜው መጀመሪያ ሊሆን ይችላል" ሲሉ ማሎፍ አሳስበዋል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | 📲 መተግበሪያ | 👉 X
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
7👍4
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
🇲🇬 ማዳጋስካር፤ አዲስ መንግሥት፣ አዲስ ፕሬዝዳንት እና አዲስ ምልከታዎች

የማዳጋስካር ጦር ፕሬዝዳንት አንድሪ ራጆሊናን ከሥልጣን ካስወገደ በኋላ፣ ሲቪሎች የሚሳተፉበትን መንግሥት ማቋቋሙን አሳውቋል።

ኮሎኔል ሚካኤል ራንድሪያን-አሬና ትናንት ቃለ መሃላቸውን ፈጽመዋል፡፡

በዚህ ሳምንት እጣ ፈንታዋ ወደ አዲስ እጥፋት ያዞረችው ይህች ደሴት ወደፊት ምን ይጠብቃታል?

የስፑትኒክ አፍሪካ አዲሱ የቨርቹዋል ወይም ምናባዊ አቅራቢ #ጁማ የዓለምን ትኩረት የሳበውን የማዳጋስካር  ሁኔታ የባለሙያዎችን ምልከታ አካትቶ አብራርቶታል።

📹የጁማን ትንታኔ ቪዲዮ ከላይ ይመልከቱ 👆🏽

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | 📲 መተግበሪያ | 👉 X
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
4🔥1
#viral  | የሆንዱራስ ዋና ከተማ በአውዳሚ ጎርፍ ተጠለቀለቀች፤ በአደጋው አንድ ሰው ሲሞት በከተማዋ የድንገተኛ ጊዜ አዋጅ ታውጇል

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | 📲 መተግበሪያ | 👉 X
3🙏3
🇩🇪 'ከሩሲያ ጋር በነበረው የኃይል ትብብር አልቆጭም' ሲሉ የቀድሞ የጀርመን መራኄ መንግሥት ተናገሩ

ጌርሃርድ ሽሮደር "የኖርድ ስትሪም 2 (የነዳጅ ማስተላለፊያ) እንዲሳካ የምችለውን ሁሉ አድርጌያለሁ። ግንባታው እንዲቀጥል ፍላጎት ነበረኝ፤ ለድጋፉም ድርድር አድርጌያለሁ" ሲሉ ተናግረዋል።


🔸 ለሜክለንቡርግ-ምዕራብ ፖሜራኒያ የክልል ፓርላማ በበየነ መረብ ባደረጉት ንግግር፤ እ.ኤ.አ. በ2022 በአሻጥር ሥራ ያቆመውን የጋዝ ማስተላለፊያ መስመር በተመለከተ ክልሉ ያቀረበውን ጥያቄ "ቀልድ" ሲሉ አጣጥለውታል።

👉 ጌርሃርድ፣ በማስተላለፊያው ግንባታ ላይ ስለነበራቸው ሚና ምንም ጸጸት እንደሌላቸውም ተናግረዋል።

🔸 ሽሮደር የአገሪቱ የአየር ንብረት ፋውንዴሽን አሁንም ጠቃሚ እንደሆነ አድርገው እንደሚመለከቱት አክለዋል። ፋውንዴሽኑ የተቋቋመው የአየር ንብረት እና የአካባቢ ጥበቃ ፕሮጀክቶችን ለማስተዋወቅ እንዲሁም የመስመሩን ግንባታ ለመደገፍ ነበር።

🔸 የቀድሞ የጀርመን መራኄ መንግሥት፣ ኖርድ ስትሪም የሩሲያ እና የጀርመን ሰፊ የኃይል ትብብር አካል ተደርጎ ይቆጠር እንደነበር ገልጸው፤ "አሜሪካ በጀርመን የኃይል ፖሊሲ ጣልቃ እንዳትገባ መሣሪያ ሆኖ አገልግሏል" ብለዋል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | 📲 መተግበሪያ | 👉 X
10
🇪🇹 የልዩ ዘመቻዎች ዕዝ ማሠልጠኛ 4ተኛ መሠረታዊ  እና 44ተኛ የኮማንዶ ሥልጠና አስጀመረ

በኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት የልዩ ዘመቻዎች ዕዝ አዛዥ ሌተናል ጀነራል ሹማ አብደታ፣ የብላቴ የልዩ ዘመቻዎች ዕዝ ማልጠኛ አስተማማኝ የኮማንዶ ኃይል አሠልጥኖ እያበቃ መሆኑን ተናግረዋል።

ሌተናል ጀነራሉ "እናንተም የአሠልጣኞችን የካበተ አቅም በመጠቀም በሥነ ምግባር የታነፀ፣ ጠንካራ እና አገራዊ ፍቅርን የተላበሰ ወታደር እና ኮማንዶ ለመሆን ጠንክራቹህ መሥራት ይጠበቅባችኋል" ሲሉ ለሰልጣኞች መልዕክት ማስተላለፋቸውን መከላከያ ሠራዊት አስታውቋል።


🛡ሠራዊቱ አገራዊ ልማቶች ደህንነታቸዉ ተጠብቆ እንዲጠናቀቁ እስከ ሕይወት መስዋዕትነት የደረሰ አበርክቶ እንዳለው ተገልጿል።

"ኮማንዶ ... የውጊያ ማርሽ ቀያሪ፣ የተበላሸ ዉጊያን በአጭር ሰዓት በመድረስ የሚያስተካክል የዘገዩ ዉጊያዎችን የሚያፋጥን ጀግና ነው፤ እናንተም የዚህ ክፍል አባል ለመሆን ፈቅዳችሁ መምጣታችሁ ደስ ያሠኛልና ጠንክራችሁ ሠልጥኑ፡፡" ሲሉ አበረታትተዋል።


ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | 📲 መተግበሪያ | 👉 X
13😁10🔥2😢2
2025/10/24 12:31:02
Back to Top
HTML Embed Code: