"አስተሳሳሪ ምልክት"
✍️(አሮን ሙሉጌታ)
ዛሬ ላይ እንደ ሀገር የት ነን? አለም እንድህ ይለናል ፦ኢትዮጲያ የሰው ዘር መገኛ ፤ ቀደምት ስልጣኔን ያስተማረች ፤ የጀግኖች ሀገር ፤ በማንም ያልተደፈረች በባርነት ያልተገዛች ሀገር ኢትዮጲያ ::
እኛ ግን ዛሬ የት ነን? አለም ከሗላችን ተነስታ ወደ ኋላ ትታን ሂዳለች ኋላ ቀርተናልም ፤ እኛ ምንም ሳንሰራ በአባቶቻችን ገድል እየፎከርን ፤ ከሰው ህይወት ርስት ፣ ጥቅም በልጦብን ፤ የኔ ብቻ ትክክል የኔ ብቻ የበላይ እየተባባልን ፤ ጥላቻ ነግሶ የቀደመው ተከባብሮ መኖርና መቻቻል ተረስቶ ፤ በዚች ምድር ዘላለም እንደምንኖርባት አስበን ጥለናት እንደምንሄድ እና እንግዳ መሆናችንን ረስተን አይደለም ለፀብ ለፍቅር የማይበቃ ጊዜያችንን አሁን ባለንበት ሁኔታ ለኛ ፀፀትን አትርፈን ለመጪው ትውልድ ጥላቻን አውርሰን አሁንም ከኛ የባሰ ራስ ወዳድ ትውልድ እንዳንፈጥር እሰጋለሁ!
አንድ የሚያደርገን ታሪክ እየተፋቀ የሚያለያዩን ትንሽ ታሪኮች ደምቀው በሚፃፉበት በዚህ ዘመን ሁሉን በአንድነት ለማስተሳሰር የሚታትር አለም ስለሚያወራላት ኢትዮጲያ ፤ ወዳኋላ ለቀረችው ኢትዮጲያ እንደሳት የሚበላው ከልቡ የሚቆረቆር ሰው አውቃለሁ ቴዎድሮስ ካሳሁን (ቴዲ አፍሮ)...
✍️(አሮን ሙሉጌታ)
ዛሬ ላይ እንደ ሀገር የት ነን? አለም እንድህ ይለናል ፦ኢትዮጲያ የሰው ዘር መገኛ ፤ ቀደምት ስልጣኔን ያስተማረች ፤ የጀግኖች ሀገር ፤ በማንም ያልተደፈረች በባርነት ያልተገዛች ሀገር ኢትዮጲያ ::
እኛ ግን ዛሬ የት ነን? አለም ከሗላችን ተነስታ ወደ ኋላ ትታን ሂዳለች ኋላ ቀርተናልም ፤ እኛ ምንም ሳንሰራ በአባቶቻችን ገድል እየፎከርን ፤ ከሰው ህይወት ርስት ፣ ጥቅም በልጦብን ፤ የኔ ብቻ ትክክል የኔ ብቻ የበላይ እየተባባልን ፤ ጥላቻ ነግሶ የቀደመው ተከባብሮ መኖርና መቻቻል ተረስቶ ፤ በዚች ምድር ዘላለም እንደምንኖርባት አስበን ጥለናት እንደምንሄድ እና እንግዳ መሆናችንን ረስተን አይደለም ለፀብ ለፍቅር የማይበቃ ጊዜያችንን አሁን ባለንበት ሁኔታ ለኛ ፀፀትን አትርፈን ለመጪው ትውልድ ጥላቻን አውርሰን አሁንም ከኛ የባሰ ራስ ወዳድ ትውልድ እንዳንፈጥር እሰጋለሁ!
አንድ የሚያደርገን ታሪክ እየተፋቀ የሚያለያዩን ትንሽ ታሪኮች ደምቀው በሚፃፉበት በዚህ ዘመን ሁሉን በአንድነት ለማስተሳሰር የሚታትር አለም ስለሚያወራላት ኢትዮጲያ ፤ ወዳኋላ ለቀረችው ኢትዮጲያ እንደሳት የሚበላው ከልቡ የሚቆረቆር ሰው አውቃለሁ ቴዎድሮስ ካሳሁን (ቴዲ አፍሮ)...
.. .ለዚህም ነው "የመጪው ዘመን ፊት ናት መሪ፣ ዛሬ አለም ቢላት ኋላ ቀሪ" ብሎ ያዜመላት በሄደበት ስሟን ጠርቶ የማይጠግበው አንድነታችነን አብዝቶ የሚሻ ሀገር ወደቀድሞው ገናንነቷ እንድትመለስ በሚችለው ሁሉ የሚታትር እንደ አባቱ ቴዎድሮስ (መይሰው ካሳ)ሀገሩ ከሰለጠኑት ሀገሮች ተርታ እንድትሰለፍ ፤ ስልጣኔን አስተምራ እንደካሮት ቁልቁል ላደገች ሀገር የሚያመው እሱ ነው እሱ ብቻ ከፍቅርና አንድነት ግምጃ ተራቁተን ባዶ በቀረንበት በዚህ ዘመን፣ እንደ ኢትዮጵያዊ፤ የቀረን አስተሳሳሪ ምልክት፣ አንድ ግለሰብ ብቻ መሆኑን ስናይ ደግሞ ሆድ ያስብሳል ቂምን ይቅርታ እንባባል አንድ እንሁን ከወረስነው ቂም ይልቅ የምናወርሰው ፍቅር ይበልጣል ይላል ሰውዬው ዘረኝነትን ቀብረን አንድነትን የምናነግስበት ቀን እሩቅ አይሆንም የሚል እምነት አለኝ ከሁሉም ነገር ፍቅር ይበልጣል ፍቅር ያሸንፋል ::
ዘጽአት ለኢትዮጵያ ወደ ተስፋ ጉዞ
ባህሩን የሚያሻግር አንድ ሙሴ ይዞ
ቅርብ ነው አይርቅም የኢትዮጵያ ትንሳኤ
በአንድነት ከገባን የፍቅር ሱባኤ
ከከፈልክልን ዋጋ አንፃር ሁሉ ነገር ያንስብሀል እንጅ አይበዙብህም መልካም ነገሮች ሁሉ ለአንተ ይገቡሀል ክብር ዶክተር ሎሬት አርቲስት ቴዎድሮስ ካሳሁን!
በያላችሁበት ሰላም ፍቅር ጤና ለናንተ ለሀገሬ ልጆች! ♦️አሮን
ዘጽአት ለኢትዮጵያ ወደ ተስፋ ጉዞ
ባህሩን የሚያሻግር አንድ ሙሴ ይዞ
ቅርብ ነው አይርቅም የኢትዮጵያ ትንሳኤ
በአንድነት ከገባን የፍቅር ሱባኤ
ከከፈልክልን ዋጋ አንፃር ሁሉ ነገር ያንስብሀል እንጅ አይበዙብህም መልካም ነገሮች ሁሉ ለአንተ ይገቡሀል ክብር ዶክተር ሎሬት አርቲስት ቴዎድሮስ ካሳሁን!
በያላችሁበት ሰላም ፍቅር ጤና ለናንተ ለሀገሬ ልጆች! ♦️አሮን
Forwarded from ታታ አፍሮ -Tata Afro
የእኔን ጩኸት በአደባባይ መሰከሩት...
አንጋፋው ገጣሚና የዜማ ደራሲ ሙሉ ገበየሁ ስለ ቴዲ አፍሮና ስለ ኪነጥበቡ እንዲህ አሉ....
"ምናልባትም በዚ ሙያ ብዙ አንጋፋ ሙያተኞች ጥረዋል ደክመዋል ለፍተዋል። ሙያተኞቹም በዋዛ ፈዛዛ አልፈዋል። ይኼ ሙያ ከጥንተ ጀምሮ ሲወድቅ ሲነሳ፣ ክብር አጥቶ፣ ለሙያው ትኩረት ሳይሰጠው፣ ክብር ተነፍጎ፣ ለባለሙያውም ፍቅር ሳይሰጠው ኖሮ ኖሮ ኖሮ አሁን ላይ ህዝቡ ለሙያው የሚሰጠው ፍቅር እየበለጠ ትኩረት እና አክብሮት እንዲሰጠው ዋጋ እንዲሰጠው እንደ ቴዲ አፍሮ ክስተት ሆኖ ሙያው የተፈጠረ ሰው በመገኘቱ በአገር ደረጃ የቀደሙትንም ዋጋ ያስከበረ ለጥበቡ ፈርጥ የሆነ ሰው ነው። ቴዲ አፍሮ ጥበብን አክብሯት ጥበብም አክብራዋለች።"
የኔ ኩሩ የኔ ቀብራራ የአገሬ ሙያተኞች በሙያቸው መኩራት ካለባቸው ሙያው ላይ አንተ ስላለ መሆን አለበት ብዬ በግልጽ ከትቤ ነበር። እነሆ የመከበራቸው ምክኒያት የሙያውም መግዘፍ ምክኒያት አንተ ነህ። ይኼ የኔ ስሜት ብቻ ሳይሆን አንተ የምታከብራቸው ሰዎች እውነተኛ ቃል ነው። ይኼ እውነት የተነገር አልያም የሚነገር ብቻ አይደለም ይልቁንም በራሱ ጸንቶ የቆመ ልሸሽገው ቢሉ የማይ ሸሸግ አላወራውም ቢሉ አፍ አውጥቶ የሚናገር በራሱ የጸና ብሎም የገዘፈ እውነት ነው። ለዚህም ነው በአደባባይ ቆመው አንጋፋዎች የኔን ጩኸት ያሰሙት። ይኼንን የጸና እውነት ሙያተኞች አንደበታቸውን ከፍተው ለሀቅ በመመስከራቸው ደስ አለኝ። እኔ ወዳጅህ ሁሌም ባንተ የምኮራ ሰው ነኝ። የከፈልካትን እያንዳንዷን ዋጋ ስለማውቅ ስላንተ እውነት ለመመስከር በፍጹም አልሰንፍም። ገና ብዙ ክብር ብዙ ፍቅር ብዙ አድናቆት አብረን እናያለን። በቁመህ የውለታክ ዋጋ እስኪከፈልህ ድረስ ብዕራችን በነጻነት እውነታውን ይከትባል።
✎✍#ታታ_አፍሮ /ነፃ ብዕር/
አንጋፋው ገጣሚና የዜማ ደራሲ ሙሉ ገበየሁ ስለ ቴዲ አፍሮና ስለ ኪነጥበቡ እንዲህ አሉ....
"ምናልባትም በዚ ሙያ ብዙ አንጋፋ ሙያተኞች ጥረዋል ደክመዋል ለፍተዋል። ሙያተኞቹም በዋዛ ፈዛዛ አልፈዋል። ይኼ ሙያ ከጥንተ ጀምሮ ሲወድቅ ሲነሳ፣ ክብር አጥቶ፣ ለሙያው ትኩረት ሳይሰጠው፣ ክብር ተነፍጎ፣ ለባለሙያውም ፍቅር ሳይሰጠው ኖሮ ኖሮ ኖሮ አሁን ላይ ህዝቡ ለሙያው የሚሰጠው ፍቅር እየበለጠ ትኩረት እና አክብሮት እንዲሰጠው ዋጋ እንዲሰጠው እንደ ቴዲ አፍሮ ክስተት ሆኖ ሙያው የተፈጠረ ሰው በመገኘቱ በአገር ደረጃ የቀደሙትንም ዋጋ ያስከበረ ለጥበቡ ፈርጥ የሆነ ሰው ነው። ቴዲ አፍሮ ጥበብን አክብሯት ጥበብም አክብራዋለች።"
የኔ ኩሩ የኔ ቀብራራ የአገሬ ሙያተኞች በሙያቸው መኩራት ካለባቸው ሙያው ላይ አንተ ስላለ መሆን አለበት ብዬ በግልጽ ከትቤ ነበር። እነሆ የመከበራቸው ምክኒያት የሙያውም መግዘፍ ምክኒያት አንተ ነህ። ይኼ የኔ ስሜት ብቻ ሳይሆን አንተ የምታከብራቸው ሰዎች እውነተኛ ቃል ነው። ይኼ እውነት የተነገር አልያም የሚነገር ብቻ አይደለም ይልቁንም በራሱ ጸንቶ የቆመ ልሸሽገው ቢሉ የማይ ሸሸግ አላወራውም ቢሉ አፍ አውጥቶ የሚናገር በራሱ የጸና ብሎም የገዘፈ እውነት ነው። ለዚህም ነው በአደባባይ ቆመው አንጋፋዎች የኔን ጩኸት ያሰሙት። ይኼንን የጸና እውነት ሙያተኞች አንደበታቸውን ከፍተው ለሀቅ በመመስከራቸው ደስ አለኝ። እኔ ወዳጅህ ሁሌም ባንተ የምኮራ ሰው ነኝ። የከፈልካትን እያንዳንዷን ዋጋ ስለማውቅ ስላንተ እውነት ለመመስከር በፍጹም አልሰንፍም። ገና ብዙ ክብር ብዙ ፍቅር ብዙ አድናቆት አብረን እናያለን። በቁመህ የውለታክ ዋጋ እስኪከፈልህ ድረስ ብዕራችን በነጻነት እውነታውን ይከትባል።
✎✍#ታታ_አፍሮ /ነፃ ብዕር/
የአጤ ምኒልክ እና የእቴጌ ጣይቱ የልደት በዓል መታሰቢያ
#የዝግጅት_አቅራቢዎች ፥ ጋዜጠኛ ንጉሴ አክሊሉ፣ ጋዜጠኛ ጥበቡ በለጠ፣ ተጓዡ ጋዜጠኛ ሔኖክ ስዩም፣ ያሬድ ሹመቴ ፣ ገጣሚ በላይ በቀለ ወያ፣ ቶማስ አድማሱ፣ ሙሉጌታ ታዬ እንዲሁም ሕብረቀለም የቴአትር ቡድን ናቸው::
#ቀን- ማክሰኞ ነሐሴ 11 ቀን 2013 ዓ.ም
#ሰዓት - ከቀኑ 11 ሰዓት ጀምሮ
#ቦታ- ዋቢ ሸበሌ ሆቴል
#አዘጋጆች - የእምዬ ምኒልክ ወዳጆች
- አርማ ሕትመትና ማስታወቂያ
ማሳሰቢያ...
መግቢያው በነፃ ነው:: ከኮቪድ ጋር በተያያዘ የሚገኘውን ሰው መገደብ አስፈላጊ በመሆኑ የመግቢያ ካርድ 22 ጎላጎል ሕንፃ ሁለተኛ ፎቅ አርማ ማስታወቂያ እና ስታዲየም አካባቢ መንገድ ትራንስፖርት ፊትለፊት አዳም ፀጉር ቤት ሄደው በነፃ ይውሰዱ።
#የዝግጅት_አቅራቢዎች ፥ ጋዜጠኛ ንጉሴ አክሊሉ፣ ጋዜጠኛ ጥበቡ በለጠ፣ ተጓዡ ጋዜጠኛ ሔኖክ ስዩም፣ ያሬድ ሹመቴ ፣ ገጣሚ በላይ በቀለ ወያ፣ ቶማስ አድማሱ፣ ሙሉጌታ ታዬ እንዲሁም ሕብረቀለም የቴአትር ቡድን ናቸው::
#ቀን- ማክሰኞ ነሐሴ 11 ቀን 2013 ዓ.ም
#ሰዓት - ከቀኑ 11 ሰዓት ጀምሮ
#ቦታ- ዋቢ ሸበሌ ሆቴል
#አዘጋጆች - የእምዬ ምኒልክ ወዳጆች
- አርማ ሕትመትና ማስታወቂያ
ማሳሰቢያ...
መግቢያው በነፃ ነው:: ከኮቪድ ጋር በተያያዘ የሚገኘውን ሰው መገደብ አስፈላጊ በመሆኑ የመግቢያ ካርድ 22 ጎላጎል ሕንፃ ሁለተኛ ፎቅ አርማ ማስታወቂያ እና ስታዲየም አካባቢ መንገድ ትራንስፖርት ፊትለፊት አዳም ፀጉር ቤት ሄደው በነፃ ይውሰዱ።
Forwarded from ታታ አፍሮ -Tata Afro
መጣና መጣና ደጁን ልንጠና
መጣና ባመቱ እንዴት ሰነበቱ
ክፈት በለው በሩን የንጉሱን*፪
ሙልሙል በላት ንግስቲቱን የቡሄውን
ሆያ ሆዬ ጉዴ ቴዲ ነው ኩራቴ...*፪
ሆያ ሆዬ......... ሆ
እዛማዶ.....ሆ
ነብር ይዘላል...ሆ
እዚህ ማዶ.....ሆ
አንበሳ ይዘላል.....ሆ
የኛማ ቴዲ.....ሆ
ፍቅርን ይዘምራል...
ሆያ ሆዬ ጉዴ ቴዲ ነው ኩራቴ....፪
ይሄ የማነው ቤት...."ሆ" የኮራ የደራ...."ሆ"
የቴዲ ነው ወይ...."ሆ" የዛ የቀብራራ...."ሆ"
እንደ ባሮ ውሃ ...."ሆ" ፀጥ ረጭ ያለው...."ሆ"
እንደ መቅደላ አቀበት..."ሆ" ክብሩ ያየለው...."ሆ"
የኛማ ቴዲ ...."ሆ" የዘመን ዘውድ አለው!
ሆያ ሆዬ ጉዴ ጨዋታ ነው ጨዋታ ነው ልማዴ
ሆያ ሆዬ ጉዴ ቴዲን ቴዲን ቴዲን ቴዲን ይላል ሆዴ..
ተው ጥራልኝ እና...ሆ አይኑን ልየው...ሆ
እንደ ሌት ኮከብ...ሆ የሚያበራው...ሆ
ከሩቅ ይስባል...ሆ የቴዲ ግርማው።
ክፈት በለው ተነሳ ያንን አንበሳ!...
ክፈት በለው ተነሳ ቴዲ ነው አንበሳ
ተው ስጠኝ እና ልሂድልህ
እንደ አረጀ ጅብ አልጭውብህ
ያረጀ ጅብስ ጮሆ ያባራል
እንደኔ ያለው ሺ አመት ይወድሃል!
ሆያ ሆዬ ጉዴ ብሯን ብሯን ብሯን ብሯን ይላል ሆዴ
ሆያ ሆዬ ነው የምንለው*፪
ኢትዮጵያ ሀገሬ ...."ሆ" ደስ ይበልሽ ...."ሆ"
ቡሄው በአልሽ ...."ሆ" ደረሰልሽ ...."ሆ"
አመት አውደ አመት ድገምና አመት ድገማና
የቴዲዬን ቤት ድገምና አመት ድገምና
ወርቅ አዝንብበት ድገምና አመት ድገምና
የነጭ ጤፍ ዘርፋፋ የወለዱት ይፋፋ
የነጭ ጤፍ ደግ ደግ የወለዱትም ይደግ
የገብስ እስር ዘለላ ቴዲን የጠላው ይጠላ
የጥንጅት ጢስ መአዛ የቴዲ ወዳጁ ይብዛ።
ክበር በሙዚቃ ንገስ በሀገር ማንም አይናገር
ክበር በክራር ክበር ጥፍ የጠላክ ይርገፍ።
ግጥም ሀገረሰብ እና @PoetTataAfro
መጣና ባመቱ እንዴት ሰነበቱ
ክፈት በለው በሩን የንጉሱን*፪
ሙልሙል በላት ንግስቲቱን የቡሄውን
ሆያ ሆዬ ጉዴ ቴዲ ነው ኩራቴ...*፪
ሆያ ሆዬ......... ሆ
እዛማዶ.....ሆ
ነብር ይዘላል...ሆ
እዚህ ማዶ.....ሆ
አንበሳ ይዘላል.....ሆ
የኛማ ቴዲ.....ሆ
ፍቅርን ይዘምራል...
ሆያ ሆዬ ጉዴ ቴዲ ነው ኩራቴ....፪
ይሄ የማነው ቤት...."ሆ" የኮራ የደራ...."ሆ"
የቴዲ ነው ወይ...."ሆ" የዛ የቀብራራ...."ሆ"
እንደ ባሮ ውሃ ...."ሆ" ፀጥ ረጭ ያለው...."ሆ"
እንደ መቅደላ አቀበት..."ሆ" ክብሩ ያየለው...."ሆ"
የኛማ ቴዲ ...."ሆ" የዘመን ዘውድ አለው!
ሆያ ሆዬ ጉዴ ጨዋታ ነው ጨዋታ ነው ልማዴ
ሆያ ሆዬ ጉዴ ቴዲን ቴዲን ቴዲን ቴዲን ይላል ሆዴ..
ተው ጥራልኝ እና...ሆ አይኑን ልየው...ሆ
እንደ ሌት ኮከብ...ሆ የሚያበራው...ሆ
ከሩቅ ይስባል...ሆ የቴዲ ግርማው።
ክፈት በለው ተነሳ ያንን አንበሳ!...
ክፈት በለው ተነሳ ቴዲ ነው አንበሳ
ተው ስጠኝ እና ልሂድልህ
እንደ አረጀ ጅብ አልጭውብህ
ያረጀ ጅብስ ጮሆ ያባራል
እንደኔ ያለው ሺ አመት ይወድሃል!
ሆያ ሆዬ ጉዴ ብሯን ብሯን ብሯን ብሯን ይላል ሆዴ
ሆያ ሆዬ ነው የምንለው*፪
ኢትዮጵያ ሀገሬ ...."ሆ" ደስ ይበልሽ ...."ሆ"
ቡሄው በአልሽ ...."ሆ" ደረሰልሽ ...."ሆ"
አመት አውደ አመት ድገምና አመት ድገማና
የቴዲዬን ቤት ድገምና አመት ድገምና
ወርቅ አዝንብበት ድገምና አመት ድገምና
የነጭ ጤፍ ዘርፋፋ የወለዱት ይፋፋ
የነጭ ጤፍ ደግ ደግ የወለዱትም ይደግ
የገብስ እስር ዘለላ ቴዲን የጠላው ይጠላ
የጥንጅት ጢስ መአዛ የቴዲ ወዳጁ ይብዛ።
ክበር በሙዚቃ ንገስ በሀገር ማንም አይናገር
ክበር በክራር ክበር ጥፍ የጠላክ ይርገፍ።
ግጥም ሀገረሰብ እና @PoetTataAfro
Forwarded from ታታ አፍሮ -Tata Afro
Forwarded from ታታ አፍሮ -Tata Afro
ዛሬ ጎልምሰ አይደለም እኔ አንተን የማውቅህ። ያኔ ገና እነ አቦጊዳን ስታዜም እንጂ! ያኔ ገና ባይገርምሽ እያልክ በተንቀሳቃሽ ምስል ስትመጣ እንጂ። ያኔ ነው...! ስትጀምር ጀምሮ ያለ አንዳች ማመንታት በለጋ ልቤ መርጬኃለሁ። ከእናት እና ከአባቴ በቀር ሌላ ሰው መውደድ ሳላውቅበት በፊት አንተን በኃይል ወድጄኃለሁ። በያንዳዱ ጉዞዎችህ አብሬ ቆሚያለሁ! ብዙ አልፈ ብዙ ተጋፍጠ የራስህን ቤት መመስረት ችለኃል። የራስህን ጎጆ ሳትመሰርት የሌሎችን ጎጆ ቀልሰኃል። ከአብራክ የወጡ ልጆች ሳይኖሩህ ለሌሎች ልጆች አባት ሆነኃቸዋል። የብዙ ምስኪኖችን እንባ አብሰኃል። ለወገኖቻችን የዋልከውን የሰው ልጅ ቢቆጥረው ያጎለዋል በማይረሳው በእግዚአብሔር ዘንድ ግን በክብር ተቀምጧል።
በወጣትነት ዘመንህ ዝና ሸውዶ የገንዘብ መብዛት አታሎህ ከምትወደው እና ከሚወድህ ህዝብህ አልነጠለኽም ነበር። ትላንትም ዛሬም ስለ ወገኖችህ መጎሳቆል የሚሰማህን የቅርብ አይደለም የሩቅም ያውቀዋል። በዝምታክ ውስጥ ያለውን ጩኸት እንሰማለን። አገርህን ወገንህን ወደህ ዋጋ ከፍለኃል። የማይገባህን ሁሉ በህይወትህ አስተናግደኃል። አገሬን ወገኔን ባትል በኪነ ጥበቡ ዘርፍ ዓለም ላይ የሚኖርህ ተጽኖ ቀላል አልነበረም። አንተ ግን ፍቅር በልጦብህ ከእኛ ጋ ኖርክ። በተሰጠክ ጸጋ ልክ ሳይሆን በኛ ኑሮ ልክ አዘገምክ። ስለሰጠኸን ሁሉ እናመሰግናለን!
የብዙዎች አባት የድኃዎች እንባን አባሽ የሆንከው የአገር ባለውለታው ክቡር ዶ/ር አርቲስት ቴዎድሮስ ካሳሁን /ቴዲ አፍሮ/ እ...ን...ወ...ድ...ሀ...ለ...ን...!
✎✍#ታታ_አፍሮ /ነፃ ብዕር/
Photo credit #ጆሲ /Artist/
https://youtu.be/cD30bSzW7E0
በወጣትነት ዘመንህ ዝና ሸውዶ የገንዘብ መብዛት አታሎህ ከምትወደው እና ከሚወድህ ህዝብህ አልነጠለኽም ነበር። ትላንትም ዛሬም ስለ ወገኖችህ መጎሳቆል የሚሰማህን የቅርብ አይደለም የሩቅም ያውቀዋል። በዝምታክ ውስጥ ያለውን ጩኸት እንሰማለን። አገርህን ወገንህን ወደህ ዋጋ ከፍለኃል። የማይገባህን ሁሉ በህይወትህ አስተናግደኃል። አገሬን ወገኔን ባትል በኪነ ጥበቡ ዘርፍ ዓለም ላይ የሚኖርህ ተጽኖ ቀላል አልነበረም። አንተ ግን ፍቅር በልጦብህ ከእኛ ጋ ኖርክ። በተሰጠክ ጸጋ ልክ ሳይሆን በኛ ኑሮ ልክ አዘገምክ። ስለሰጠኸን ሁሉ እናመሰግናለን!
የብዙዎች አባት የድኃዎች እንባን አባሽ የሆንከው የአገር ባለውለታው ክቡር ዶ/ር አርቲስት ቴዎድሮስ ካሳሁን /ቴዲ አፍሮ/ እ...ን...ወ...ድ...ሀ...ለ...ን...!
✎✍#ታታ_አፍሮ /ነፃ ብዕር/
Photo credit #ጆሲ /Artist/
https://youtu.be/cD30bSzW7E0
አንጋፋው እና በዓለም ዙሪያ ትልቅ ተቀባይነት የነበረው፤ በአገራችን የሙዚቃ ኢንዱስትሪ የራሱን አሻራ ያሳረፈው፤ የምንወደው እና የምናከብረው በአርቲስት አለማየሁ እሸቴ ህልፈተ ህይወት የተሰማንን ጥልቅ ሀዘን እየገለጽን ለመላው የአገራችን ህዝቦች እና ለወዳጅ ዘመዶቹ እንዲሁም ለአድናቂዎቹ መጽናናትን እንመኛለን።
ነፍስ ይማር!
ነፍስ ይማር!
በሀገራችን የዘመናዊ ሙዚቃ ዘርፍ ፈር ቀዳጅ ከነበሩት ስመ ገናና እና አንጋፋ ድምፃውያን መካከል ግንባር ቀደም የነበረው ታላቁ የሙዚቃ ሰውና የሙያ አባታችን ድምፃዊ ዓለማዬሁ እሸቴ ድንገተኛ ኅልፈተ ሕይወት የተሰማኝን ኀዘን ስገልፅ በተሰበረ ልብና ጥልቅ በሆነ የኅዘን ስሜት ነው።
ጋሽ ዓለማዬሁ ከ1950ዎቹ አጋማሽ ጀምሮ ከ60 ዓመታት በላይ ባስቆጠረው የሙዚቃ ሕይወቱ የተጫወታቸው ሕዝብን አስተማሪ፣ ታሪክን ነጋሪ፣ ሰላምን ዘማሪ፣ ትውልድን ቀራጭና ሀገርን አወዳሽ የሆኑት ዘመን ተሻጋሪ ታላላቅ ስራዎቹ በተለይ በዚህ ሙያ ውስጥ ላለነው የሙዚቃ ባለሙያዎች ዘርፈ ብዙ ትርጉም አላቸው።
በኢትዮጵያ የሙዚቃ ኅትመት ታሪክ የመጀመሪያውን የግል ሸክላ በማሳተምና የመጀመሪያውን ዘመናዊ የግል የሙዚቃ ባንድ ከሙያ አጋሩ አርቲስት ግርማ በየነ ጋር ( ግርማ ዓለም ባንድ/ ግርማና ዓለማዬሁ) በማቋቋም ፈር ቀዳጅ የነበረው ጋሽ ዓለማዬሁ በድንገት በአካል ቢለየንም ዘመን በማይሽራቸውና ትውልድ በሚቀባበላቸው ስራዎቹ ሲታወስና ሲዘከር ይኖራል።
ለመላው ቤተሰቦቹ፣ ለሙያ አጋሮቹ፣ ለሙዚቃው አፍቃሪዎቹና ለመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ መጽናናትን እየተመኘሁ፤ ፈጣሪ ነፍሱን በአፀደ ገነት እንዲያኖርልን ከልብ እመኛለሁ።
ቴዎድሮስ ካሳሁን
(ቴዲ አፍሮ)
ጋሽ ዓለማዬሁ ከ1950ዎቹ አጋማሽ ጀምሮ ከ60 ዓመታት በላይ ባስቆጠረው የሙዚቃ ሕይወቱ የተጫወታቸው ሕዝብን አስተማሪ፣ ታሪክን ነጋሪ፣ ሰላምን ዘማሪ፣ ትውልድን ቀራጭና ሀገርን አወዳሽ የሆኑት ዘመን ተሻጋሪ ታላላቅ ስራዎቹ በተለይ በዚህ ሙያ ውስጥ ላለነው የሙዚቃ ባለሙያዎች ዘርፈ ብዙ ትርጉም አላቸው።
በኢትዮጵያ የሙዚቃ ኅትመት ታሪክ የመጀመሪያውን የግል ሸክላ በማሳተምና የመጀመሪያውን ዘመናዊ የግል የሙዚቃ ባንድ ከሙያ አጋሩ አርቲስት ግርማ በየነ ጋር ( ግርማ ዓለም ባንድ/ ግርማና ዓለማዬሁ) በማቋቋም ፈር ቀዳጅ የነበረው ጋሽ ዓለማዬሁ በድንገት በአካል ቢለየንም ዘመን በማይሽራቸውና ትውልድ በሚቀባበላቸው ስራዎቹ ሲታወስና ሲዘከር ይኖራል።
ለመላው ቤተሰቦቹ፣ ለሙያ አጋሮቹ፣ ለሙዚቃው አፍቃሪዎቹና ለመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ መጽናናትን እየተመኘሁ፤ ፈጣሪ ነፍሱን በአፀደ ገነት እንዲያኖርልን ከልብ እመኛለሁ።
ቴዎድሮስ ካሳሁን
(ቴዲ አፍሮ)
መልካም አዲስ አመት!
በቅድሚያ ለመላው የአገራችን ህዝቦች እንኳን ለኢትዮጵያ የዘመን መለወጫ ቀን በሰላም አደረሳችሁ!
ኢትዮጵያ አገራችን የራሷ የሆነ የቀን መቁጠሪ ቀመር ያላት ታሪካዊት አገር ነች። ይህችን ታላቅ አገር አባቶቻችን በብዙ መስዋዕትነት ዳር ድንበሯን አስከብረው፣ ባህልና ወጓን ጠብቀው፣ ቋንቋችንን ከነ ፊደሉ አውርሰውናል። እኛም በአደራ የተቀበልናትን ይህችን ታላቅ አገር ለቀጣይ ትውልድ የማስረከብ ኃላፊነት ብቻ ሳይሆን ግዴታም ጭምር አለብን።
አባቶቻችን በዘመናቸው ተከባብረው እና ተዋደው የውስጥ ችግሮቻቸውን በሰለጠነ መልኩ እየፈቱ ይህችን አገር ለኛ ያስረከቡት ከጸብ ይልቅ ፍቅር እንደሚበልጥ ተሰብከው ሳይሆን በህገ ልቦና ፍቅር የእግዚአብሔር መንገድ መሆኑን ስለተረዱ ነው። እኛም ከነሱ መልካሙን ነገር በመድገም የተሻለች አገር ለመገንባት እንድንጥር እመኛለሁ።
በዚህ አዲስ ዓመት ላለፉት አመታቶች በፖለቲካ እና በኢኮኖሚ ቀውስ ብሎም በጎጠኝነት መንፈስ የተነሳ ብዙ ጸያፍ ዜናዎችን የሰማው ጆሯችን መልካም እና የሠላም ወሬን የሚሰማበት ዘመን ይሁንለት! በተለያዩ ሁኔታዎች የተጎዱ ወገኖቻችን ካሉበት መከራ ተላቀው ቀሪ ህይወታቸውን በደስታና በተድላ የሚያሳልፉበት፣ በስደት ህይወት ያሉ፣ በእስር ቤት የሚሰቃዩ ወገኖቻችን ወደየቤታቸው የሚመለሱበት መልካም ዘመን ይሁንልን።
እኛም በየግላችን እርስ በእርሳችን እየተጋገዝን አቅመ ደካሞችን በቻልነው መጠን እየደገፍን መጪውን አዲስ ዓመት በፍቅር እና በሰላም እንድንጨርሰው እግዚአብሔር ዘመኑን ባርኮ ይጀምርልን።
✎✍#ታታ_አፍሮ /ነፃ ብዕር/
በቅድሚያ ለመላው የአገራችን ህዝቦች እንኳን ለኢትዮጵያ የዘመን መለወጫ ቀን በሰላም አደረሳችሁ!
ኢትዮጵያ አገራችን የራሷ የሆነ የቀን መቁጠሪ ቀመር ያላት ታሪካዊት አገር ነች። ይህችን ታላቅ አገር አባቶቻችን በብዙ መስዋዕትነት ዳር ድንበሯን አስከብረው፣ ባህልና ወጓን ጠብቀው፣ ቋንቋችንን ከነ ፊደሉ አውርሰውናል። እኛም በአደራ የተቀበልናትን ይህችን ታላቅ አገር ለቀጣይ ትውልድ የማስረከብ ኃላፊነት ብቻ ሳይሆን ግዴታም ጭምር አለብን።
አባቶቻችን በዘመናቸው ተከባብረው እና ተዋደው የውስጥ ችግሮቻቸውን በሰለጠነ መልኩ እየፈቱ ይህችን አገር ለኛ ያስረከቡት ከጸብ ይልቅ ፍቅር እንደሚበልጥ ተሰብከው ሳይሆን በህገ ልቦና ፍቅር የእግዚአብሔር መንገድ መሆኑን ስለተረዱ ነው። እኛም ከነሱ መልካሙን ነገር በመድገም የተሻለች አገር ለመገንባት እንድንጥር እመኛለሁ።
በዚህ አዲስ ዓመት ላለፉት አመታቶች በፖለቲካ እና በኢኮኖሚ ቀውስ ብሎም በጎጠኝነት መንፈስ የተነሳ ብዙ ጸያፍ ዜናዎችን የሰማው ጆሯችን መልካም እና የሠላም ወሬን የሚሰማበት ዘመን ይሁንለት! በተለያዩ ሁኔታዎች የተጎዱ ወገኖቻችን ካሉበት መከራ ተላቀው ቀሪ ህይወታቸውን በደስታና በተድላ የሚያሳልፉበት፣ በስደት ህይወት ያሉ፣ በእስር ቤት የሚሰቃዩ ወገኖቻችን ወደየቤታቸው የሚመለሱበት መልካም ዘመን ይሁንልን።
እኛም በየግላችን እርስ በእርሳችን እየተጋገዝን አቅመ ደካሞችን በቻልነው መጠን እየደገፍን መጪውን አዲስ ዓመት በፍቅር እና በሰላም እንድንጨርሰው እግዚአብሔር ዘመኑን ባርኮ ይጀምርልን።
✎✍#ታታ_አፍሮ /ነፃ ብዕር/