Forwarded from ታታ አፍሮ -Tata Afro
ከባራክ ኦባማ ምርጥ ሙዚቃዎች ውስጥ አንዱ የቴዲ አፍሮ ሙዚቃ ነው።
የቀድሞው የአሜሪካ ፕሬዝዳንት የነበሩት ባራክ ኦባማ ዛሬ ታህሳስ 7/2014 ዓ.ም ከምሽቱ አንድ ሰዓት ገደማ፥ በህጋዊ የፌስቡክ ገፃቸው ላይ የተለያዩ ሙዚቃዎችን የማዳመጥ ልማድ እንዳላቸው ጠቅሰው በዚህ አመት /በ2021/ ዓለማችን ላይ ከተለቀቁ ሙዚቃዎች መኃል አዳምጠው ከወደዷቸው የሙዚቃ ዝርዝሮች ውስጥ "አርማሽ" የተሰኘው የቴዲ አፍሮ ሙዚቃ አንዱ እንደሆነ በህጋዊ የፌስቡክ እና የኢንስታግራም ገጻቸው ላይ አጋርተዋል።
በህጋዊ የፌስቡክ እና የኢንስታግራም ገጻቸው የኔ ምርጥ ሙዚቃ ብለው 27 ሙዚቃዎችን ያጋሩ ሲሆን ከነዚህ መኃል በ45 ቀናቶች ውስጥ ብቻ ስድስት ሚሊየን አድማጮችን ያገኘው የክቡር ዶ/ር አርቲስት ቴዎድሮስ ካሳሁን ሙዚቃ በመካተቱ ለኢትዮጵያ የሙዚቃ አፍቃሪያን እና ለመላው የቴዲ አፍሮ አድናቂዎች እንኳን ደስ ያላችሁ ለማለት እንወዳለን።
የአገራችን የሙዚቃ ስልት ከዚህም በላይ ልቆ እንዲደመጥ ምኞታችን ነው።
✎✍#ታታ_አፍሮ /ነፃ ብዕር/
#አርማሽ
https://youtu.be/PkOstq4GuLk
የሚከተለው ጽሁፍ የ Barack Obama ነው...
I've always enjoyed listening to a wide variety of music, so it’s no surprise that I listened to a little bit of everything this year. I hope you find a new artist or song to add to your own playlist.
የቀድሞው የአሜሪካ ፕሬዝዳንት የነበሩት ባራክ ኦባማ ዛሬ ታህሳስ 7/2014 ዓ.ም ከምሽቱ አንድ ሰዓት ገደማ፥ በህጋዊ የፌስቡክ ገፃቸው ላይ የተለያዩ ሙዚቃዎችን የማዳመጥ ልማድ እንዳላቸው ጠቅሰው በዚህ አመት /በ2021/ ዓለማችን ላይ ከተለቀቁ ሙዚቃዎች መኃል አዳምጠው ከወደዷቸው የሙዚቃ ዝርዝሮች ውስጥ "አርማሽ" የተሰኘው የቴዲ አፍሮ ሙዚቃ አንዱ እንደሆነ በህጋዊ የፌስቡክ እና የኢንስታግራም ገጻቸው ላይ አጋርተዋል።
በህጋዊ የፌስቡክ እና የኢንስታግራም ገጻቸው የኔ ምርጥ ሙዚቃ ብለው 27 ሙዚቃዎችን ያጋሩ ሲሆን ከነዚህ መኃል በ45 ቀናቶች ውስጥ ብቻ ስድስት ሚሊየን አድማጮችን ያገኘው የክቡር ዶ/ር አርቲስት ቴዎድሮስ ካሳሁን ሙዚቃ በመካተቱ ለኢትዮጵያ የሙዚቃ አፍቃሪያን እና ለመላው የቴዲ አፍሮ አድናቂዎች እንኳን ደስ ያላችሁ ለማለት እንወዳለን።
የአገራችን የሙዚቃ ስልት ከዚህም በላይ ልቆ እንዲደመጥ ምኞታችን ነው።
✎✍#ታታ_አፍሮ /ነፃ ብዕር/
#አርማሽ
https://youtu.be/PkOstq4GuLk
የሚከተለው ጽሁፍ የ Barack Obama ነው...
I've always enjoyed listening to a wide variety of music, so it’s no surprise that I listened to a little bit of everything this year. I hope you find a new artist or song to add to your own playlist.
Forwarded from ታታ አፍሮ -Tata Afro
የዕልፍ ብዕረኞች ሙገሳ ያልገለፃቸው የኛ አጤ ምኒልክ ዓለም አቀፍ ጀግና ናቸው። የሀሰት ትርክት ፈፅሞ ገናና ስማቸውን ሊያደበዝዘው አይችልም። ምክኒያቱም የተራሮች ግዝፈት የፀሐይን ብርኃን ፍፅሞ ማጥፋት አይችልም።
ትላንት፣ ዛሬም፣ ነገም፣ ለዘለዓለሙም የሚኖር ጀብድ የፈጸሙ ጥቂት ሰዎች በምድራችን አሉ! ከሁሉ ታላቅ ሰው የምንላቸው ግን አጤ ምኒልክ ናቸው! ዘለዓለማዊ ክብርና ሞገስ ለጥቁሩ አጤ ምኒልክ ይሁን!!!
💚💛❤
"አባቴ ወኔውን ተኮሰው
ምኒልክ ጥቁር ሰው..."
https://youtu.be/3ec4HRr6I0g
ትላንት፣ ዛሬም፣ ነገም፣ ለዘለዓለሙም የሚኖር ጀብድ የፈጸሙ ጥቂት ሰዎች በምድራችን አሉ! ከሁሉ ታላቅ ሰው የምንላቸው ግን አጤ ምኒልክ ናቸው! ዘለዓለማዊ ክብርና ሞገስ ለጥቁሩ አጤ ምኒልክ ይሁን!!!
💚💛❤
"አባቴ ወኔውን ተኮሰው
ምኒልክ ጥቁር ሰው..."
https://youtu.be/3ec4HRr6I0g
#ጥቁር_ሰው
ለአገር ክብር ለተዋደቁ የዘመናችን ጀግኖች ምስጋና ይሆን ዘንድና በጦርነቱ ለተጎዱ ወገኖቻችን የገንዘብ ድጋፍና የተለያዩ ቁሶችን ማሰባሰቢያ እንዲሆን ያለመ እንደዚህ አይነት ግዙፍ ኮንሰርት በኢትዮጵያ ዋና ዋና ከተሞች እንዲዘጋጅ እመኛለሁ! እንደሚደረግም ባለሙሉ ተስፋ ነኝ። ምክኒያቱም እንዲህ አይነት ዝግጅት ሲያዘጋጅ ለክቡር ዶ/ር ቴዎድሮስ ካሳሁን /ቴዲ አፍሮ/ የመጀመሪያው አይደለም! ይልቁንም የኖረበት ነው።
በኮንሰርቱ ላይ የሶስቱ ነገስታት ስም ይጠራል። /የዳግማዊ አጤ ቴዎድሮስ፣ የዳግማዊ አጤ ምኒልክ እና የቀዳማዊ አጤ ኃይለ ሥላሴ/ እነዚህ ነገስታቶች የኢትዮጵያ ታላቅነት ምንጭ ናቸውና ዳግም በዘመናችን ይታወሳሉ። ይሄ መሆኑ ደግሞ ዛሬም ድረስ የአባቶቻችን ስም ለወገኖቻችን የድጋፍና የጥንካሬ ብሎም የጀግንነት፣ የአንድነትና የአሸናፊነትን መንፈስ በፅኑ የሚያጎናጽፈን መሆኑን ለዓለም የምንመሰክርበት አጋጣሚ ሆኖ ያልፋል። የተጠቀሱት ታላላቅ መንፈሶች በኢትዮጵያ ታላቅነት ለሚኮሩ የድል ዜና ሲሆን ይህችን አገር ለሚጠሏት ደግሞ መራር መርዶ ይሆንባቸዋል።
ኢትዮጵያ የአባቶቻችን አገር ነች እኛም የአባቶችን ልጆች ነንና ተደጋግፈን ማለፍ ያለብንን ሁሉ እናልፋለን። የኛ ኢትዮጵያ ሁሉን አሸንፋ ዳግም በኩራት ትቆማለች።
✎✍#ታታ_አፍሮ /ነፃ ብዕር/
https://vm.tiktok.com/ZM8wRUGfp
ለአገር ክብር ለተዋደቁ የዘመናችን ጀግኖች ምስጋና ይሆን ዘንድና በጦርነቱ ለተጎዱ ወገኖቻችን የገንዘብ ድጋፍና የተለያዩ ቁሶችን ማሰባሰቢያ እንዲሆን ያለመ እንደዚህ አይነት ግዙፍ ኮንሰርት በኢትዮጵያ ዋና ዋና ከተሞች እንዲዘጋጅ እመኛለሁ! እንደሚደረግም ባለሙሉ ተስፋ ነኝ። ምክኒያቱም እንዲህ አይነት ዝግጅት ሲያዘጋጅ ለክቡር ዶ/ር ቴዎድሮስ ካሳሁን /ቴዲ አፍሮ/ የመጀመሪያው አይደለም! ይልቁንም የኖረበት ነው።
በኮንሰርቱ ላይ የሶስቱ ነገስታት ስም ይጠራል። /የዳግማዊ አጤ ቴዎድሮስ፣ የዳግማዊ አጤ ምኒልክ እና የቀዳማዊ አጤ ኃይለ ሥላሴ/ እነዚህ ነገስታቶች የኢትዮጵያ ታላቅነት ምንጭ ናቸውና ዳግም በዘመናችን ይታወሳሉ። ይሄ መሆኑ ደግሞ ዛሬም ድረስ የአባቶቻችን ስም ለወገኖቻችን የድጋፍና የጥንካሬ ብሎም የጀግንነት፣ የአንድነትና የአሸናፊነትን መንፈስ በፅኑ የሚያጎናጽፈን መሆኑን ለዓለም የምንመሰክርበት አጋጣሚ ሆኖ ያልፋል። የተጠቀሱት ታላላቅ መንፈሶች በኢትዮጵያ ታላቅነት ለሚኮሩ የድል ዜና ሲሆን ይህችን አገር ለሚጠሏት ደግሞ መራር መርዶ ይሆንባቸዋል።
ኢትዮጵያ የአባቶቻችን አገር ነች እኛም የአባቶችን ልጆች ነንና ተደጋግፈን ማለፍ ያለብንን ሁሉ እናልፋለን። የኛ ኢትዮጵያ ሁሉን አሸንፋ ዳግም በኩራት ትቆማለች።
✎✍#ታታ_አፍሮ /ነፃ ብዕር/
https://vm.tiktok.com/ZM8wRUGfp
Forwarded from ታታ አፍሮ -Tata Afro
ክቡር ዶክተር አርቲስት Teddy Afro በአንድ ወቅት ለፈረሳዩ ዓለም አቀፍ ሚድያ ጣቢያ (AFP News Agency) ከሰጠው ቃለምልልስ የተወሰደ..!!
"... ሁሉም ሰው ኢትዮጵያዊነት ውስጡ ያለ ፣ የነበረ ነው! ኢትዮጵያዊነት ሊጠፋ የሚችል አይደለም። እንደሃይማኖት የጠለቀ ነው። ኢትዮጵያዊነት ረቂቅ ሚስጥር አለው። ኢትዮጵያዊነት በጣም ትልቅ መሠረት ያለው ነው። ይህን ባለመረዳት አብረን ባደረግናቸው ብዙ መልካም ነገሮች ላይ መስማማት ስንችል ፣ አብረን ባጎደልናቸው ላይ ዝም ብለን ግዜ ማጥፋት ጠቃሚ አይደለም። ምንግዜም.. .. እኔ ትላንት አዲስ ልጅ ወልጃለሁ። አሁን 4 ዓመት ሆኖታል። ይህ ልጅ ከፍቅርና ከጥላቻ የቱ እንደሚሻል ብጠይቀው የሚነግረኝ ሰለፍቅር ነው። ከአንድነትና ከልዩነት የቱ እንደሚሻል ብጠይቀው ያንተም ልጅ ሊነግረኝ የሚችለው አንድነት ነው። ይሄ ልጆች ሊመልሱት የሚችሉትን ጥያቄዎች በዕድሜ በልጽገን እንኳን ለመግባባት የማንችልባቸው ነጥቦች ላይ በማተኮር ነው ብዙ ወጣቶች ጉዞ ሊደናቀፍ የሆነው። ይሄ ደግሞ ከታላላቆቻችን ግፊያ ነው። የቀድሞ አያቶቻችን ግን ከዚህ የላቀ ቅርጽ የነበራቸው ናቸው። ለዚህም ነው እነሱ ላይ ያተኮረ ሰራ የምሰራው። ስለዚህ ሁሉም የራሱን አመለካከት መግለጽ ደግሞ የተፈጥሮአዊ መብት ነው። ሁሉንም ማስደሰት ባይቻልም ፣ በተቻለ መጠን ሁሉንም የሚያግባባ ቅርጽ ይዞ ለመቅረብ ነው የምሞክረው..."
ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር!!
ፍቅር ያሸንፋል!!
https://youtube.com/channel/UCQKyrC0xnEk1KhSQqrv2JBg
"... ሁሉም ሰው ኢትዮጵያዊነት ውስጡ ያለ ፣ የነበረ ነው! ኢትዮጵያዊነት ሊጠፋ የሚችል አይደለም። እንደሃይማኖት የጠለቀ ነው። ኢትዮጵያዊነት ረቂቅ ሚስጥር አለው። ኢትዮጵያዊነት በጣም ትልቅ መሠረት ያለው ነው። ይህን ባለመረዳት አብረን ባደረግናቸው ብዙ መልካም ነገሮች ላይ መስማማት ስንችል ፣ አብረን ባጎደልናቸው ላይ ዝም ብለን ግዜ ማጥፋት ጠቃሚ አይደለም። ምንግዜም.. .. እኔ ትላንት አዲስ ልጅ ወልጃለሁ። አሁን 4 ዓመት ሆኖታል። ይህ ልጅ ከፍቅርና ከጥላቻ የቱ እንደሚሻል ብጠይቀው የሚነግረኝ ሰለፍቅር ነው። ከአንድነትና ከልዩነት የቱ እንደሚሻል ብጠይቀው ያንተም ልጅ ሊነግረኝ የሚችለው አንድነት ነው። ይሄ ልጆች ሊመልሱት የሚችሉትን ጥያቄዎች በዕድሜ በልጽገን እንኳን ለመግባባት የማንችልባቸው ነጥቦች ላይ በማተኮር ነው ብዙ ወጣቶች ጉዞ ሊደናቀፍ የሆነው። ይሄ ደግሞ ከታላላቆቻችን ግፊያ ነው። የቀድሞ አያቶቻችን ግን ከዚህ የላቀ ቅርጽ የነበራቸው ናቸው። ለዚህም ነው እነሱ ላይ ያተኮረ ሰራ የምሰራው። ስለዚህ ሁሉም የራሱን አመለካከት መግለጽ ደግሞ የተፈጥሮአዊ መብት ነው። ሁሉንም ማስደሰት ባይቻልም ፣ በተቻለ መጠን ሁሉንም የሚያግባባ ቅርጽ ይዞ ለመቅረብ ነው የምሞክረው..."
ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር!!
ፍቅር ያሸንፋል!!
https://youtube.com/channel/UCQKyrC0xnEk1KhSQqrv2JBg
Forwarded from ታታ አፍሮ -Tata Afro
የእውነት ቃል!
ዐይንህን ለማየት፥ ደምጽህን ለመስማት የሚጓጉ ዕልፍ ወዳጆች ያሉህ አንተ ትከሻዬ ላይ እጅህ አረፈ። ዕልፍ አዕላፍ አገር ወዳድና እውነተኛ የሙዚቃ አፍቃሪያን፦ ያዜምከውን የጥበብ ዜማ ብቻ ሳይሆን የተነፈስካትን አንዳች ቃል ለማዳመጥ የሚመኙልህ አንተን፤ ፊት ለፊትህ ቆሜ ሞገስ ያለውን ድምጽህን ሰማሁ። የምስጋና እና የአክብሮት ቃሎችህን አደመጥኩ። ሩቅ የሚመስል የልጅነት ምኞቴ በተደጋጋሚ ተሳክቷል። ሳታውቀኝ ወድጄህ ስሜን እንድትጠራ መልኬን እንድትለይ ያስቻለኸ ከልቤ ውስጥ ያለው እውነተኛ ፍቅር በመሆኑ እደሰታለሁ። ይኼንንም ሳስብ "መውደድ እንዴት ያለ መታደል ነው?" እላለሁ በልቤ።
ብዙዎች ባንተ ሊያከብሩኝና ሊቀርቡኝ ችለዋል። የኪነጥበብ ባለሙያዎች ሳይቀሩ ላንተ ባለኝ ፍቅር ለኔ ዋጋ መስጠት ችለዋል። አሁን ላለሁበት የህይወት ደረጃና ላለኝ ስብዕና አንተን መከተሌ ትልቅ አስተዋጽኦ አለው። ብዙ ቁምነገረኛ ሰዎችን ባንተ ማትረፍ ችያለሁ። ሰው መውደድ ዋጋ ሊያስከፍል ባይገባም እኔ ግን ብዙ አይቻለሁ። ተሰድቤ፣ ተተችቼ፣ ተገላምጬ እንዲሁም ሊፈጸሙልኝ የሚገባቸው ብዙ ጉዳዮችን እስከማጣት ደርሻለሁ። በስልክ እየደወሉና በውስጥ መስመር ባገኙት አጋጣሚ የዛቻ መልዕክቶችን የሚያደርሱኝ ጥቂቶች አይደሉም። የእነዚህ ነገሮች መደጋገም ግን ላንተ ያለኝን ፍቅር እንድተው አልያም እንድቀንስ ጉልበት አላገኙም። እኔም ብሆን በገጠሙኝ ነገሮች የምቆጭና የምጨነቅ ሳልሆን ይልቁንም ፍቅሬን እየጨመርኩ ባንተ ላይ ያለኝን አቋም እያጠበኩኝ መቀጠል ችያለሁ።
"አይሰለችህም? አይደክምህም? ያንተስ በዛ..." ወዘተ ተብዬ አውቃለሁ። ሰዎች ግን ምን ያህል ሞኞች ናቸው? እንዴት መውደድ ይሰለቻል? እንዴት ፍቅር ያደክማል? እግዚአብሔር የማያልቅ፣ የማይደበዝዝ አድርጎ ካጸናቸው መንፈሶች ዋነኛው ፍቅር መሆኑን እንዴት ልብ ማለት አቃታቸው? ዳሩ ሰው ለመውደድ ካልኩኝ ደከመኝ ያኔ ገና ውስጤን /ነፍሴን/ አመመኝ ነው ቁም ነገሩ። የሰውን ልጅ ለመፍጠር ካሳበበት ጊዜ አንስቶ ሰውን በጽኑ መውደድ ሲወድ የኖረ ቅዱስ እግዚአብሔር ክብር ምስጋና ይግባው። አምላካችን የመዋደድ መንፈስን በልባችን ያሳደረ፣ የፍቅርንም ዋጋ በመስቀል ላይ ከፍ አድርጎ የሰቀለ ነውና ክብሩ አይጉደልበት። የከበረ ምስጋና ዘውትር ይድረሰው።
ለዘመናት በገጠሙህ መልካምም ሆነ ፈታኝ ነገሮች ላይ ያንተን ያህል ተደስቼም አዝኜም አውቃለሁ። የኔና ያንተ ነገር አፍንጫ ሲነካ ዐይን እንደሚያለቅስ አይነት ነው። ጤንነትህ ያሳስበኛል። ያሰብከው እንዲሳካ የዘራኸው እንዲያፈራ ካንተ እኩል እመኛለሁ። እንደ አንድ የኪነጥበብ ሰው ብቻ ሳይሆን ከቤተሰቦቼ አንዱ የሆንክ ያህል ነፍሴ አጥብቃ ትወድሃለች። ለአጤ ቴዎድሮስ ገብርዬ በጽናት እንደቆመለት ሁሉ እኔም ላንተ እጸናለሁ። ለአገር የከፈልከው በዋጋ የማይተመነው መስዋዕትነትህ ነው ይኼንን ፍቅር በልቤ ውስጥ የፈጠረው። በብዙ የቃላት ክምር ስላንተ የሚሰማኝን /የውስጤን/ የመግለጽ ጥበቡ ቢኖረኝ ያንን እወነት እየከተብኩ ለዘመናት በተቀመጥኩበት እቆይ ነበር። ግን የማይገለጹ ብዙ ነገሮች አሉ። ልቤ ውስጥ ካሉት ያነሱ ቢሆኑም የጻፍኳቸው ሁሉ የልቤ ውስጥ የእውነት ቃላቶች ናቸው። ብቻ ግን በእውነተኛ መውደድ ሁሌም እ...ወ...ድ...ኃ...ለ...ው...!
✎✍#ታታ_አፍሮ /ነፃ ብዕር/
ዐይንህን ለማየት፥ ደምጽህን ለመስማት የሚጓጉ ዕልፍ ወዳጆች ያሉህ አንተ ትከሻዬ ላይ እጅህ አረፈ። ዕልፍ አዕላፍ አገር ወዳድና እውነተኛ የሙዚቃ አፍቃሪያን፦ ያዜምከውን የጥበብ ዜማ ብቻ ሳይሆን የተነፈስካትን አንዳች ቃል ለማዳመጥ የሚመኙልህ አንተን፤ ፊት ለፊትህ ቆሜ ሞገስ ያለውን ድምጽህን ሰማሁ። የምስጋና እና የአክብሮት ቃሎችህን አደመጥኩ። ሩቅ የሚመስል የልጅነት ምኞቴ በተደጋጋሚ ተሳክቷል። ሳታውቀኝ ወድጄህ ስሜን እንድትጠራ መልኬን እንድትለይ ያስቻለኸ ከልቤ ውስጥ ያለው እውነተኛ ፍቅር በመሆኑ እደሰታለሁ። ይኼንንም ሳስብ "መውደድ እንዴት ያለ መታደል ነው?" እላለሁ በልቤ።
ብዙዎች ባንተ ሊያከብሩኝና ሊቀርቡኝ ችለዋል። የኪነጥበብ ባለሙያዎች ሳይቀሩ ላንተ ባለኝ ፍቅር ለኔ ዋጋ መስጠት ችለዋል። አሁን ላለሁበት የህይወት ደረጃና ላለኝ ስብዕና አንተን መከተሌ ትልቅ አስተዋጽኦ አለው። ብዙ ቁምነገረኛ ሰዎችን ባንተ ማትረፍ ችያለሁ። ሰው መውደድ ዋጋ ሊያስከፍል ባይገባም እኔ ግን ብዙ አይቻለሁ። ተሰድቤ፣ ተተችቼ፣ ተገላምጬ እንዲሁም ሊፈጸሙልኝ የሚገባቸው ብዙ ጉዳዮችን እስከማጣት ደርሻለሁ። በስልክ እየደወሉና በውስጥ መስመር ባገኙት አጋጣሚ የዛቻ መልዕክቶችን የሚያደርሱኝ ጥቂቶች አይደሉም። የእነዚህ ነገሮች መደጋገም ግን ላንተ ያለኝን ፍቅር እንድተው አልያም እንድቀንስ ጉልበት አላገኙም። እኔም ብሆን በገጠሙኝ ነገሮች የምቆጭና የምጨነቅ ሳልሆን ይልቁንም ፍቅሬን እየጨመርኩ ባንተ ላይ ያለኝን አቋም እያጠበኩኝ መቀጠል ችያለሁ።
"አይሰለችህም? አይደክምህም? ያንተስ በዛ..." ወዘተ ተብዬ አውቃለሁ። ሰዎች ግን ምን ያህል ሞኞች ናቸው? እንዴት መውደድ ይሰለቻል? እንዴት ፍቅር ያደክማል? እግዚአብሔር የማያልቅ፣ የማይደበዝዝ አድርጎ ካጸናቸው መንፈሶች ዋነኛው ፍቅር መሆኑን እንዴት ልብ ማለት አቃታቸው? ዳሩ ሰው ለመውደድ ካልኩኝ ደከመኝ ያኔ ገና ውስጤን /ነፍሴን/ አመመኝ ነው ቁም ነገሩ። የሰውን ልጅ ለመፍጠር ካሳበበት ጊዜ አንስቶ ሰውን በጽኑ መውደድ ሲወድ የኖረ ቅዱስ እግዚአብሔር ክብር ምስጋና ይግባው። አምላካችን የመዋደድ መንፈስን በልባችን ያሳደረ፣ የፍቅርንም ዋጋ በመስቀል ላይ ከፍ አድርጎ የሰቀለ ነውና ክብሩ አይጉደልበት። የከበረ ምስጋና ዘውትር ይድረሰው።
ለዘመናት በገጠሙህ መልካምም ሆነ ፈታኝ ነገሮች ላይ ያንተን ያህል ተደስቼም አዝኜም አውቃለሁ። የኔና ያንተ ነገር አፍንጫ ሲነካ ዐይን እንደሚያለቅስ አይነት ነው። ጤንነትህ ያሳስበኛል። ያሰብከው እንዲሳካ የዘራኸው እንዲያፈራ ካንተ እኩል እመኛለሁ። እንደ አንድ የኪነጥበብ ሰው ብቻ ሳይሆን ከቤተሰቦቼ አንዱ የሆንክ ያህል ነፍሴ አጥብቃ ትወድሃለች። ለአጤ ቴዎድሮስ ገብርዬ በጽናት እንደቆመለት ሁሉ እኔም ላንተ እጸናለሁ። ለአገር የከፈልከው በዋጋ የማይተመነው መስዋዕትነትህ ነው ይኼንን ፍቅር በልቤ ውስጥ የፈጠረው። በብዙ የቃላት ክምር ስላንተ የሚሰማኝን /የውስጤን/ የመግለጽ ጥበቡ ቢኖረኝ ያንን እወነት እየከተብኩ ለዘመናት በተቀመጥኩበት እቆይ ነበር። ግን የማይገለጹ ብዙ ነገሮች አሉ። ልቤ ውስጥ ካሉት ያነሱ ቢሆኑም የጻፍኳቸው ሁሉ የልቤ ውስጥ የእውነት ቃላቶች ናቸው። ብቻ ግን በእውነተኛ መውደድ ሁሌም እ...ወ...ድ...ኃ...ለ...ው...!
✎✍#ታታ_አፍሮ /ነፃ ብዕር/
Forwarded from ታታ አፍሮ -Tata Afro
Forwarded from ታታ አፍሮ -Tata Afro
ስለ ቦብ ማርሊ በጥቂቱ
ሙሉ ስም ሮበርት ኔስታ ማርሊ ይባላል እ.ኤ.አ Feb 6/1945 ተወልዶ May 11/1981 በ36 ዓመቱ ከዚህ ዓለም በሞት ተለየ። ቦብ ማርሊ እናቱ ሴዴላ ቡከር የምትባል ጥቁር ጃማይካዊት ስትሆን አባቱ ደግሞ ኖርቫል ማርሊ የተባለ ነጭ እንግሊዛዊ ነበር። የሙዚቃ ሕይወቱንም የጀመረው በ1960ዎቹ ፒተር ቶሽ እና በኒ ዌይለር ከተባሉ ጓደኞቹ ጋር ዘ ዌይለርስ የተባለ ቡድን በመመስረት ነበር። ከዚያም ከደጋፊ ዘፋኞቹ አንዲቱ የነበረችውን ሪታ ማርሊን በማግበት 5 ልጆች አፍርቷል። ከቦብ ታላቁ የሙዚቃ ስራ "ኖ ውማን ኖ ክራይ" /ቃል በቃል ሲተረጎም/ "አንድም ሴት አታልቅስ" የሚለው ነበር።
ቦብ በአገሩ ጃማይካ እንደ ታላቅ ጀግና የሚቆጠር ሰው ነው። ብሎም ዘፈኖቹ ስለ ፍቅር ከመተረክ ይልቅ ወደ ፖለቲካና ወደ ሃይማኖት ያጋደሉ ስለነበር በዓለም ተቀባይነትን አግኝቷል። እንዲሁም የሬጌን ሙዚቃ ዘዴ በዓለም አቀፍ ደረጃ ታዋቂ እንዲሆን ያደረገ ሙዚቀኛ ነው። እስካሁንም ድረስ ተፈቃሪነቱ የቀጠለ ሙዚቀኛ ነው። ዛሬ ከተወለደ በህይወት ቢቆይ 77ኛ የልደት በዓሉን ያከብር ነበር።
ቦብ ከመሞቱ ጥቂት ሴኮንዶች በፊት ለልጁ ለዚጊ የተናገረዉ የመጨረሻ ቃል «ገንዘብ ህይወትን አይገዛም» የሚል ነበር።
ቦብ ባንድ ወቅት በህይወት እያለ ስለሚያቀነቅነው የሙዚቃ ስልት ሲጠየቅ ከተናገረው....
👉ጋዜጠኛ>> «የሬጌ ሙዚቃ ስልት እንዴት ተፈጠረ? የማንስ ነው?»
👉ቦብ>> «ሬጌ እኮ በጃማይካውያን ሳይንቲስቶች አማካኝነት ከኦርቶዶክስ ቤ/ክርስትያን መንፈሳዊ የከበሮ ምት ዜማ (bit of z drum in z orthodox church's spiritual ceremony) በመጠቀም ተቀናብሮ እና ጣፍጦ የተፈለሰፈ ወይም derived የሆነ የንጉሱ (z king's) ሙዚቃ ነው!» ሲል ቃሉን ሰቷል።
ሙሉ ስም ሮበርት ኔስታ ማርሊ ይባላል እ.ኤ.አ Feb 6/1945 ተወልዶ May 11/1981 በ36 ዓመቱ ከዚህ ዓለም በሞት ተለየ። ቦብ ማርሊ እናቱ ሴዴላ ቡከር የምትባል ጥቁር ጃማይካዊት ስትሆን አባቱ ደግሞ ኖርቫል ማርሊ የተባለ ነጭ እንግሊዛዊ ነበር። የሙዚቃ ሕይወቱንም የጀመረው በ1960ዎቹ ፒተር ቶሽ እና በኒ ዌይለር ከተባሉ ጓደኞቹ ጋር ዘ ዌይለርስ የተባለ ቡድን በመመስረት ነበር። ከዚያም ከደጋፊ ዘፋኞቹ አንዲቱ የነበረችውን ሪታ ማርሊን በማግበት 5 ልጆች አፍርቷል። ከቦብ ታላቁ የሙዚቃ ስራ "ኖ ውማን ኖ ክራይ" /ቃል በቃል ሲተረጎም/ "አንድም ሴት አታልቅስ" የሚለው ነበር።
ቦብ በአገሩ ጃማይካ እንደ ታላቅ ጀግና የሚቆጠር ሰው ነው። ብሎም ዘፈኖቹ ስለ ፍቅር ከመተረክ ይልቅ ወደ ፖለቲካና ወደ ሃይማኖት ያጋደሉ ስለነበር በዓለም ተቀባይነትን አግኝቷል። እንዲሁም የሬጌን ሙዚቃ ዘዴ በዓለም አቀፍ ደረጃ ታዋቂ እንዲሆን ያደረገ ሙዚቀኛ ነው። እስካሁንም ድረስ ተፈቃሪነቱ የቀጠለ ሙዚቀኛ ነው። ዛሬ ከተወለደ በህይወት ቢቆይ 77ኛ የልደት በዓሉን ያከብር ነበር።
ቦብ ከመሞቱ ጥቂት ሴኮንዶች በፊት ለልጁ ለዚጊ የተናገረዉ የመጨረሻ ቃል «ገንዘብ ህይወትን አይገዛም» የሚል ነበር።
ቦብ ባንድ ወቅት በህይወት እያለ ስለሚያቀነቅነው የሙዚቃ ስልት ሲጠየቅ ከተናገረው....
👉ጋዜጠኛ>> «የሬጌ ሙዚቃ ስልት እንዴት ተፈጠረ? የማንስ ነው?»
👉ቦብ>> «ሬጌ እኮ በጃማይካውያን ሳይንቲስቶች አማካኝነት ከኦርቶዶክስ ቤ/ክርስትያን መንፈሳዊ የከበሮ ምት ዜማ (bit of z drum in z orthodox church's spiritual ceremony) በመጠቀም ተቀናብሮ እና ጣፍጦ የተፈለሰፈ ወይም derived የሆነ የንጉሱ (z king's) ሙዚቃ ነው!» ሲል ቃሉን ሰቷል።
የሀዘን መግለጫ!
ኢትዮጵያ ለተባለች ውድ አገር ትልቅ ስጦታን ከሰጡን አባቶች መኃል አንዱ የሆኑት የሁላችን አባት አባ በቀለ አይናለም ነበሩ። የህልፈተ ህይወታቸውን ዜና በመስማታችን የተሰማን ሀዘን ጥልቅ መሆኑን እየገለጽን ለመላው ህዝባችን መጽናናትን እንዲሰጥልን እንመኛለን።
የብዙ ዜጎችን ምኞት ለመፈጸም በርኻ የወረደው የእርሳቸው የአብራክ ክፋይ የሆነው ጀግናው ኢንጂነር ስመኘው በቀለ ነው። አገራችን ኢትዮጵያ የኒህን ታላቅ አባት ስም በፍጹም አትዘነጋም። የአብራካቸው ክፋይ ለአገሩና ለወገኑ ኩራት ሆኖ አልፏል። በእርግጥም እኒህ አባት በህይወታቸው ብዙ አሳዛኝ ነገር አልፏል። ብዙ ያልተቋጨ እና ያልተመለሰ የፍትህ ጥያቄም እንዳላቸው ግልጽ ነው። ቢሆንም ግን ይኼን ስሜታቸውን ሁላችን እንደምንጋራቸው ያውቁ ከነበር ብቻቸውን እንዳልተከፉና እንዳላዘኑ ስለሚያውቁ ይኼ መልካም ነው ብለን እናምናለን። የእርሳቸው የአብራክ ክፋይ የሁላችን ጀግና ነውና....
አባታችን እንደሚረዱት እርግጠኞች ነን። አገራችን ኢትዮጵያ እንደ ጽጌሬዳ አበባ ነች። የሚወዷት ዜጎቿ መስዋዕትነትን ሲከፍሉላት እያበበች ማራኪ ጠረኗንም እያበዛች የምትመጣ ስትሆን ሊቀጥፏት ቢጠጓት የጀግኖቿ መስዋዕትነት በዘንጓ ላይ እንዳለው እሾህ ይዋጋልና እንደ እሾህ በከበባት የልጆቿ በመስዋዕትነት ታፍራ እና ተከብራ ትኖራለች። ለዚህች ውድ አገር መስዋዕትነት ከከፈሉላት ጀግኖች መኃል የአባ በቀለ አይናለም ልጅ የሆነው ኢንጂነር ስመኘው በቀለ አንዱ ነው።
የአባት እና የልጁን ነፍሥ በሰላም ያሳርፍልን ዘንድ የእስራኤል አምላክ መልካም ፍቃዱ ይሁን!
ኢትዮጵያ ለተባለች ውድ አገር ትልቅ ስጦታን ከሰጡን አባቶች መኃል አንዱ የሆኑት የሁላችን አባት አባ በቀለ አይናለም ነበሩ። የህልፈተ ህይወታቸውን ዜና በመስማታችን የተሰማን ሀዘን ጥልቅ መሆኑን እየገለጽን ለመላው ህዝባችን መጽናናትን እንዲሰጥልን እንመኛለን።
የብዙ ዜጎችን ምኞት ለመፈጸም በርኻ የወረደው የእርሳቸው የአብራክ ክፋይ የሆነው ጀግናው ኢንጂነር ስመኘው በቀለ ነው። አገራችን ኢትዮጵያ የኒህን ታላቅ አባት ስም በፍጹም አትዘነጋም። የአብራካቸው ክፋይ ለአገሩና ለወገኑ ኩራት ሆኖ አልፏል። በእርግጥም እኒህ አባት በህይወታቸው ብዙ አሳዛኝ ነገር አልፏል። ብዙ ያልተቋጨ እና ያልተመለሰ የፍትህ ጥያቄም እንዳላቸው ግልጽ ነው። ቢሆንም ግን ይኼን ስሜታቸውን ሁላችን እንደምንጋራቸው ያውቁ ከነበር ብቻቸውን እንዳልተከፉና እንዳላዘኑ ስለሚያውቁ ይኼ መልካም ነው ብለን እናምናለን። የእርሳቸው የአብራክ ክፋይ የሁላችን ጀግና ነውና....
አባታችን እንደሚረዱት እርግጠኞች ነን። አገራችን ኢትዮጵያ እንደ ጽጌሬዳ አበባ ነች። የሚወዷት ዜጎቿ መስዋዕትነትን ሲከፍሉላት እያበበች ማራኪ ጠረኗንም እያበዛች የምትመጣ ስትሆን ሊቀጥፏት ቢጠጓት የጀግኖቿ መስዋዕትነት በዘንጓ ላይ እንዳለው እሾህ ይዋጋልና እንደ እሾህ በከበባት የልጆቿ በመስዋዕትነት ታፍራ እና ተከብራ ትኖራለች። ለዚህች ውድ አገር መስዋዕትነት ከከፈሉላት ጀግኖች መኃል የአባ በቀለ አይናለም ልጅ የሆነው ኢንጂነር ስመኘው በቀለ አንዱ ነው።
የአባት እና የልጁን ነፍሥ በሰላም ያሳርፍልን ዘንድ የእስራኤል አምላክ መልካም ፍቃዱ ይሁን!
ዜና ኪነጥበብ
የክቡር ዶ/ር አርቲስት ቴዎድሮስ ካሳሁን /ቴዲ አፍሮ/ ከሐምሌ 1/2011 ዓ.ም - ሰኔ 30/2013 ዓ.ም ድረስ ከወጡ ነጠላ ዜማዎች ጋ በለዛ አዋርድ ላይ 'ምርጥ ነጠላ ዜማ' በሚል ዘርፍ "ደሞ በአባይ" የተሰኘው ነጠላ ዜማው እጩ ሆኖ ቀርቧል። ስለሆነም ከታች በተቀመጠው ማስፈንጠሪያ እየገባችሁ ድምጻችሁን ለቴዲ አፍሮ እንድትሰጡት ለመጠቆም እንወዳለን።
#ማሳሰቢያ
አንድ ሰው በአንድ ዘርፍ ከታጩ ሙዚቃዎች ውስጥ ከአንድ ጊዜ በላይ መምረጥ ስለማይችል ስለአመራረጥ ሂደቱ ግልጽ ያልሆነ ነገር ከገጠምዎ ከአንድ ደቂቃ በታች የሆነ የአመራረጥ ሂደቱን የሚያስረዳ ቪዲዮ ከሰዓታት በኋላ ስለምናደርስዎ እንዲጠብቁን እንጠቁማለን።
https://vote.lezashow.com/
የክቡር ዶ/ር አርቲስት ቴዎድሮስ ካሳሁን /ቴዲ አፍሮ/ ከሐምሌ 1/2011 ዓ.ም - ሰኔ 30/2013 ዓ.ም ድረስ ከወጡ ነጠላ ዜማዎች ጋ በለዛ አዋርድ ላይ 'ምርጥ ነጠላ ዜማ' በሚል ዘርፍ "ደሞ በአባይ" የተሰኘው ነጠላ ዜማው እጩ ሆኖ ቀርቧል። ስለሆነም ከታች በተቀመጠው ማስፈንጠሪያ እየገባችሁ ድምጻችሁን ለቴዲ አፍሮ እንድትሰጡት ለመጠቆም እንወዳለን።
#ማሳሰቢያ
አንድ ሰው በአንድ ዘርፍ ከታጩ ሙዚቃዎች ውስጥ ከአንድ ጊዜ በላይ መምረጥ ስለማይችል ስለአመራረጥ ሂደቱ ግልጽ ያልሆነ ነገር ከገጠምዎ ከአንድ ደቂቃ በታች የሆነ የአመራረጥ ሂደቱን የሚያስረዳ ቪዲዮ ከሰዓታት በኋላ ስለምናደርስዎ እንዲጠብቁን እንጠቁማለን።
https://vote.lezashow.com/