ክቡር ዶክተር አርቲስት ቴዎድሮስ ካሣሁን (ቴዲ አፍሮ)
ቤተልሔም፣ ኒው ኢራ እና የካቲት 12 የተማረባቸ ትመህርት ቤቶች ናቸው፡፡ ክስተቶችን፣ ስሜቶችን፣ እውነቶችን ኹሉ ይዘፍናቸዋል ብቻም ሳይኾን ይተርካቸዋል፣ ይሰንዳቸዋልም። ለበርካታ ድምፃውያንም ግጥም እና ዜማ ደርሶ አበርክቷል። በአቡጊዳ፣ በያስተሠርያል እና በጥቁር ሰው (በ 2004 ዓ/ም በለዛ ምርጥ አድማጮች ምርጫ፥ የዓመቱ ምርጥ አልበም ተሸላሚ ነበር።) ኢትዮጵያ የተሰኘው አልበሙም ባለፈው ዓመት በለዛ ምርጥ አድማጮች ምርጫ፥ የዓመቱ ምርጥ አልበም ተሸላሚ ነበር።) ከላይ የተዘረዘሩት ክቡር ዶክተር አርቲስት ቴዎድሮስ ካሳሁን የሠራቸው የአልበሞች ስያሜዎች ናቸው፡፡ በ2007 ዓ/ም ደግሞ የዓመቱ ምርጥ ነጠላ ዜማ በሚል ዘርፍ በሰባ ደረጃ ተሸላሚም ነበር። ዘንድሮም የሁለት አመት ሙዚቃዎች በአንድ ተሰብስበው ለውድድር ሲቀርቡ እጩ ሆኖ የቀረበው ደሞ በአባይ የተሰኘው ነጠላ ዜማው ነው።
የአመቱ ምርጥ ነጠላ ዜማ በሚል ዘርፍ እጩ ሆኖ የቀረበውን ቴዲ አፍሮን እዚህ ይምረጡ👇
https://vote.lezashow.com/
ቤተልሔም፣ ኒው ኢራ እና የካቲት 12 የተማረባቸ ትመህርት ቤቶች ናቸው፡፡ ክስተቶችን፣ ስሜቶችን፣ እውነቶችን ኹሉ ይዘፍናቸዋል ብቻም ሳይኾን ይተርካቸዋል፣ ይሰንዳቸዋልም። ለበርካታ ድምፃውያንም ግጥም እና ዜማ ደርሶ አበርክቷል። በአቡጊዳ፣ በያስተሠርያል እና በጥቁር ሰው (በ 2004 ዓ/ም በለዛ ምርጥ አድማጮች ምርጫ፥ የዓመቱ ምርጥ አልበም ተሸላሚ ነበር።) ኢትዮጵያ የተሰኘው አልበሙም ባለፈው ዓመት በለዛ ምርጥ አድማጮች ምርጫ፥ የዓመቱ ምርጥ አልበም ተሸላሚ ነበር።) ከላይ የተዘረዘሩት ክቡር ዶክተር አርቲስት ቴዎድሮስ ካሳሁን የሠራቸው የአልበሞች ስያሜዎች ናቸው፡፡ በ2007 ዓ/ም ደግሞ የዓመቱ ምርጥ ነጠላ ዜማ በሚል ዘርፍ በሰባ ደረጃ ተሸላሚም ነበር። ዘንድሮም የሁለት አመት ሙዚቃዎች በአንድ ተሰብስበው ለውድድር ሲቀርቡ እጩ ሆኖ የቀረበው ደሞ በአባይ የተሰኘው ነጠላ ዜማው ነው።
የአመቱ ምርጥ ነጠላ ዜማ በሚል ዘርፍ እጩ ሆኖ የቀረበውን ቴዲ አፍሮን እዚህ ይምረጡ👇
https://vote.lezashow.com/
Forwarded from ታታ አፍሮ -Tata Afro
የመልካም ልደት መግለጫ!
ውዷ አምለሰት ሙጬ እንኳን ተወለድሽ! እንኳንም በሰላምና በጤና ለዚህች ዕለት አደረሰሽ! ኤሚዬ ብሩ እና መልካም ልደት ይሁንልሽ። ቀሪው ዘመንሽ በደስታና በብዙ በረከቶች የተሞላ ይሁን። የልጆችሽን ወግ ማዕረግ የባለቤትሽንም የስኬት ጥግ በዘመንሽ እንዲያሳይሽና የልብሽም መሻቶች በዘመንሽ የተፈጸሙ እንዲሆኑልሽ እመኛለሁ።
ከአክባሪ ወንድምሽ ✎✍#ታታ_አፍሮ /ነፃ ብዕር/
ውዷ አምለሰት ሙጬ እንኳን ተወለድሽ! እንኳንም በሰላምና በጤና ለዚህች ዕለት አደረሰሽ! ኤሚዬ ብሩ እና መልካም ልደት ይሁንልሽ። ቀሪው ዘመንሽ በደስታና በብዙ በረከቶች የተሞላ ይሁን። የልጆችሽን ወግ ማዕረግ የባለቤትሽንም የስኬት ጥግ በዘመንሽ እንዲያሳይሽና የልብሽም መሻቶች በዘመንሽ የተፈጸሙ እንዲሆኑልሽ እመኛለሁ።
ከአክባሪ ወንድምሽ ✎✍#ታታ_አፍሮ /ነፃ ብዕር/
ቴዲ አፍሮ ከእስር ከተፈታ በኋላ ጥቁር ሰው የተሰኘ ግዙፍ አልበም ነበር የገነባው። ይህ ድንቅ አልበም ሚያዝያ 6/2004 ዓ.ም በገበያ ላይ የዋለው። ሚያዝያ 6/2014 ዓ.ም ይህ አልበም 10ኛ አመቱን ደፍኗል። እልፍ ሰዎች በጉጉት ሲጠብቁት የነበረው አርቲስት ቴዲ አፍሮ ከሰባት አመት ቆይታ በኋላ ነበር አልበም ይዞ ብቅ ያለው። በመሆኑም በኢትዮጵያ እና በመላው ዓለም ለሚገኙ ኢትዮጵያውያን እና ለሌሎች የሙዚቃ አፍቃሪያን እንዲሁም የአርቲስቱ የኪነ ጥብብ ቱርፋት ወዳጅ ለሆኑ ሁሉ ይኽ አልበም መለቀቁ እጅግ አስደሳች ዜና ሲሆን በአልበሙ የተካተቱት ሙዚቃዎችም ተወዳጅ ነበረ። በወቅቱ ትልቅ የገበያ መነቃቃትን የፈጠረው ጥቁር ሰው አልበም በአገር ውስጥ እና በዓለም ዙሪያ ሁሉ ታላላቅ ኮንሰርቶች እንዲዘጋጁ ትልቅ እድልን ያመቻቸ ነበር። ጥቁር ሰው አልበም እንደሌሎቹ የአርቲስቱ የጥበብ ቱርፋቶች ዛሬም ድረስ እንደ አዲስ ዜማ ይደመጣል። እንደ ወይን እያደር ጣዕሙ ይጎመራል።
#Ethiopia
ኢትዮጵያ የተሰኘው ነጠላ ዜማ በቴዲ አፍሮ ህጋዊ የዩትዩብ ቻናል ከተለቀቀ ዛሬ አምስተኛ አመቱን ደፈነ። ይኼ ሙዚቃ ሚያዝያ 7/2009 ዓ.ም ምሽት ላይ ነበር የተለቀቀው። በተለቀቀ በሰዓታት ውስጥ ግን ድፍን አዲስ አበባ በዚህ ሙዚቃ ዳንኪራ ስትረግጥ አምሽታለች። ከተማይቱ አዲስ ዘመንን የምታከብር ያህል በየ ስፍራው እንደ ብሔራዊ መዝሙር ይኼ ሙዚቃ ብቻ ሲደመጥ አነጋ... በዕለቱ በተለያዩ ስፍራዎች እየተዘዋወርኩ ለሊቱን ሙሉ ስሜቱን ለማጣጣም የሞከርኩ ሲሆን በየ ቦታው የሚታየው የህዝቡ ስሜት እጅግ ልዩ ነበር። የአገር ፍቅር ልኩ የገባው የአገሬ ሰው ዛሬም ድረስ በዚህ ሙዚቃ ኢትዮጵያን ከፍ ከፍ ያደርጋታል። ዘፈኑ ከተለቀቀ በአምስት አመታት ውስጥ በዩትዩብ ብቻ 23 ሚልየን አድማጭን አግኝቷል። በተጨማሪም ይኼው ሙዚቃ በምስል ተቀናብሮ በአርቲስቱ ህጋዊ የዩትዩብ ቻናል ላይ 5.7 ሚሊየን ጊዜ መታየት ችሏል። በጥቅሉ ኢትዮጵያ የተሰኘው ነጠላ ዜማ በዩትዩብ ብያ ከ28.7 ሚሊየን በላይ አድማጮችን አግኝቷል። ይኼ ደግሞ በኢትዮጵያ ያለ ተንቀሳቃሽ ምስል ተለቆ ብዙ አድማጮችን ያገኘ የመጀመሪያው ነጠላ ዜማ ነው።
✎✍#ታታ_አፍሮ /ነፃ ብዕር/
Teddy Afro🤴 ደረጃቸውን ስለጠበቁ ውብ የሙዚቃ አልበሞችህ ከልብ እናመሰግናለ
#Ethiopia
ኢትዮጵያ የተሰኘው ነጠላ ዜማ በቴዲ አፍሮ ህጋዊ የዩትዩብ ቻናል ከተለቀቀ ዛሬ አምስተኛ አመቱን ደፈነ። ይኼ ሙዚቃ ሚያዝያ 7/2009 ዓ.ም ምሽት ላይ ነበር የተለቀቀው። በተለቀቀ በሰዓታት ውስጥ ግን ድፍን አዲስ አበባ በዚህ ሙዚቃ ዳንኪራ ስትረግጥ አምሽታለች። ከተማይቱ አዲስ ዘመንን የምታከብር ያህል በየ ስፍራው እንደ ብሔራዊ መዝሙር ይኼ ሙዚቃ ብቻ ሲደመጥ አነጋ... በዕለቱ በተለያዩ ስፍራዎች እየተዘዋወርኩ ለሊቱን ሙሉ ስሜቱን ለማጣጣም የሞከርኩ ሲሆን በየ ቦታው የሚታየው የህዝቡ ስሜት እጅግ ልዩ ነበር። የአገር ፍቅር ልኩ የገባው የአገሬ ሰው ዛሬም ድረስ በዚህ ሙዚቃ ኢትዮጵያን ከፍ ከፍ ያደርጋታል። ዘፈኑ ከተለቀቀ በአምስት አመታት ውስጥ በዩትዩብ ብቻ 23 ሚልየን አድማጭን አግኝቷል። በተጨማሪም ይኼው ሙዚቃ በምስል ተቀናብሮ በአርቲስቱ ህጋዊ የዩትዩብ ቻናል ላይ 5.7 ሚሊየን ጊዜ መታየት ችሏል። በጥቅሉ ኢትዮጵያ የተሰኘው ነጠላ ዜማ በዩትዩብ ብያ ከ28.7 ሚሊየን በላይ አድማጮችን አግኝቷል። ይኼ ደግሞ በኢትዮጵያ ያለ ተንቀሳቃሽ ምስል ተለቆ ብዙ አድማጮችን ያገኘ የመጀመሪያው ነጠላ ዜማ ነው።
✎✍#ታታ_አፍሮ /ነፃ ብዕር/
Teddy Afro🤴 ደረጃቸውን ስለጠበቁ ውብ የሙዚቃ አልበሞችህ ከልብ እናመሰግናለ
Forwarded from ታታ አፍሮ -Tata Afro
የክቡር ዶ/ር ቴዎድሮስ ካሳሁን /ቴዲ አፍሮ/ አንተ ጽኑ እና ጀግና አባት ነህ። ከአብራኮችህ ለወጡ ልጆችህ ብቻ ሳይሆን ለብዙዎች ምርጥ አባት ሆነህ በመቆምህ ከልብ እናመሰግንኃለን።
የአገሬ ማህጸን እንዳንተ አይነት ቅን ሰዎችን ስለምታፈራ ክብር ሊሰማት ይገባል።
መልካም የአባቶች ቀን ይሁንልህ!
በጽኑ መውደድ እ...ን...ወ...ድ...ኃ...ለ...ን!
የአገሬ ማህጸን እንዳንተ አይነት ቅን ሰዎችን ስለምታፈራ ክብር ሊሰማት ይገባል።
መልካም የአባቶች ቀን ይሁንልህ!
በጽኑ መውደድ እ...ን...ወ...ድ...ኃ...ለ...ን!
የኢትዮጵያ ሙዚቃ በዓለም ጆሮዎች...
ድምጻችን በዓለም እየተሰማ ነው። "ናዕት" አርባ ሺ Subscribers፣ ከ90 ሺህ በላይ መውደዶች እና ከአንደ ሚሊየን በላይ ተመልካቾችን በአስራ ሰባት /17/ሰዓታት ውስጥ ብቻ አግኝቷል። ይኽ የህዝብ ድምጽ የሆነው የክቡር ዶ/ር ቴዎድሮስ ካሳሁን /ቴዲ አፍሮ/ አዲስ ሙዚቃ ዓለማችን ላይ በዚህን ሰዓት በስፋት እየተደመጡ ካሉ ሙዚቃዎች ውስጥ የሁለተኛ ደረጃነትን የያዘ ሲሆን በዘመናዊ የሙዚቃ ማድመጫ ድረገጽ /You Tube/ ላይ ከእራሱ ከቴዲ አፍሮ በቀር በኢትዮጵያ በዚህ ፍጥነት የተደመጠ ሙዚቃ በፍጹም የለም።
ናዕት /እያመመው ቁ፪/ ሙዚቃ ገና 24 ሰዓት ሳይሞላው በዚህ ፍጥነት በዓለም ደረጃ መዳረስ መቻሉ እጅግ ሊደነቅ የሚገባ ክስተት ነው። የህዝብ ድምጽ ሁሌም ኃያል ነው። ናዕት የኢትዮጵያውያን ድምጽ ነው። እንደ አገር ከገባንበት ማጥ ለመውጣት እንደ ዜጋ ከተረገጥንበት ትቢያ ለመነሳት እንዲህ ያሉ አስገምጋሚ ድምጾች ያሹናል። እንደ ሰማይ ማስገምገም እንደ ነጋሪት ጉሰማ የአምባ ገነኖችን ልብ የሚያሸብር የነፍስ ጩኸት።
✎✍#ታታ_አፍሮ /ነፃ ብዕር/
አሁንም ከፍ ብሎ ይደመጥ
የሚያዜም ይመስላል ሲያጣጥር ተጨንቆ
ውስጡን ሲሰብቅለት ኡ... እያለ ማሲንቆ
ኡ...ኡ...
https://youtu.be/1hMVeENjVew
ድምጻችን በዓለም እየተሰማ ነው። "ናዕት" አርባ ሺ Subscribers፣ ከ90 ሺህ በላይ መውደዶች እና ከአንደ ሚሊየን በላይ ተመልካቾችን በአስራ ሰባት /17/ሰዓታት ውስጥ ብቻ አግኝቷል። ይኽ የህዝብ ድምጽ የሆነው የክቡር ዶ/ር ቴዎድሮስ ካሳሁን /ቴዲ አፍሮ/ አዲስ ሙዚቃ ዓለማችን ላይ በዚህን ሰዓት በስፋት እየተደመጡ ካሉ ሙዚቃዎች ውስጥ የሁለተኛ ደረጃነትን የያዘ ሲሆን በዘመናዊ የሙዚቃ ማድመጫ ድረገጽ /You Tube/ ላይ ከእራሱ ከቴዲ አፍሮ በቀር በኢትዮጵያ በዚህ ፍጥነት የተደመጠ ሙዚቃ በፍጹም የለም።
ናዕት /እያመመው ቁ፪/ ሙዚቃ ገና 24 ሰዓት ሳይሞላው በዚህ ፍጥነት በዓለም ደረጃ መዳረስ መቻሉ እጅግ ሊደነቅ የሚገባ ክስተት ነው። የህዝብ ድምጽ ሁሌም ኃያል ነው። ናዕት የኢትዮጵያውያን ድምጽ ነው። እንደ አገር ከገባንበት ማጥ ለመውጣት እንደ ዜጋ ከተረገጥንበት ትቢያ ለመነሳት እንዲህ ያሉ አስገምጋሚ ድምጾች ያሹናል። እንደ ሰማይ ማስገምገም እንደ ነጋሪት ጉሰማ የአምባ ገነኖችን ልብ የሚያሸብር የነፍስ ጩኸት።
✎✍#ታታ_አፍሮ /ነፃ ብዕር/
አሁንም ከፍ ብሎ ይደመጥ
የሚያዜም ይመስላል ሲያጣጥር ተጨንቆ
ውስጡን ሲሰብቅለት ኡ... እያለ ማሲንቆ
ኡ...ኡ...
https://youtu.be/1hMVeENjVew
በክቡር ዶ/ር አርቲስት ቴዎድሮስ ካሳሁን /ቴዲ አፍሮ/ የህይወት ጉዞ ላይ የሚያውጠነጥን "ቴዎድሮስ እስኪነግሥ" የተሰኘ አዲስ መጽሐፍ ከሀምሌ 20/2014 ዓ.ም ጀምሮ ለአንባቢያን ይቀርባል።
ከመጽሐፉ...
"...ቴዲ በሥነ-ግጥሙ ዘርፍ የነበረው ሀሳብን በተመጠነ ቃል የመግለጽና ለሰዎች በድምጹ የማቅረብ ልምዱ አድጎና ጎልብቶ እዚህ ደረጃ መድረሱ እጅግ አስገርሞኛል፡፡ ስለ ኢትዮጵያ ህዝቦች በጋራ የመኖር ውበት የሚገልጽባቸው መንገዶች ልዩ ናቸው፡፡ አርቲስቱ ከፖለቲካ ነጻ መሆኑና ቀደምት ሀገሪቷን በከፍታ ላስጓዟት መሪዎች የሚሰጠው ክብር ከድምጻውያን መካከል በግንባር ቀደምትነት የሚያሰልፈው ነው፡፡"
የቴዲ አፍሮ የቀድሞ አማርኛ መምህር ስለሺ ከበደ
ከመጽሐፉ...
"...ቴዲ በሥነ-ግጥሙ ዘርፍ የነበረው ሀሳብን በተመጠነ ቃል የመግለጽና ለሰዎች በድምጹ የማቅረብ ልምዱ አድጎና ጎልብቶ እዚህ ደረጃ መድረሱ እጅግ አስገርሞኛል፡፡ ስለ ኢትዮጵያ ህዝቦች በጋራ የመኖር ውበት የሚገልጽባቸው መንገዶች ልዩ ናቸው፡፡ አርቲስቱ ከፖለቲካ ነጻ መሆኑና ቀደምት ሀገሪቷን በከፍታ ላስጓዟት መሪዎች የሚሰጠው ክብር ከድምጻውያን መካከል በግንባር ቀደምትነት የሚያሰልፈው ነው፡፡"
የቴዲ አፍሮ የቀድሞ አማርኛ መምህር ስለሺ ከበደ
Forwarded from ታታ አፍሮ -Tata Afro
በቅድሚያ ጀግናው ልጃችን ቴዲ አፍሮ፦ እንኳን ለኢትዮጵያ ልጇ፥ ለልጆቿም ወንድሞቿ ሆነህ ተወለድክልን። ብዙዎች በዚህ ዓለም ላይ "ከከባድ ነገሮች ውስጥ አንዱ ከባድ ነገር የሚወዱትን ሰው በሚመጥኑ ቃላቶች ለመግለጽ መሞከር ነው" ሲሉ አውቃለሁ። በዚህ ጉዳይ በተወሰነ መልኩ ብስማማም ልቤ ግን አንደበት ከሚገልጸው በላይ ተግባር የሚገልጸው ፍቅር ይልቃል ብሎ ስለሚያምን ይኼን ሰው ለመግለጽ ቸገረኝ ብሎ ከማውራቱ ይልቅ እሱን በእውነተኛ የመውደድ ስሜት መውደዴ ብቻ በቂ ሆኖ ይሰማኛል። እንደ ቴዲ አፍሮ በጀግንነት እና በእርሱ ጽናት ልክ ባይሆንም ጥቂት ነገሮቹን በመውረስ ለአንዲትም ሰከንድ ቢሆን ሀሳቡን ሳልቋወም ከ20 አመታቶች በላይ ከርሱ ጋ ተጉዣለሁ። ይኼ እና ያልገለጽኳቸው እውነታዎች በተግባር የተገለጸውን ፍቅሬን በመጠኑም ቢሆን ይልጻሉ ብዬ አምናለሁ።
ሰውን ለመውደድ ሰው ከመሆን የላቀ ምክኒያት ባያስፈልግም የሰዎች አፍ ግን ስለምን ወደድከው ሲል ዕልፍ ጊዜ ጠይቆኛል። በመጀመሪያ ሰው በመሆኑ እንደ ሁሉ ሰው እንደወደድኩህ በኩራት ተናገርኩ። በመቀጠልም የእርሱን ስብዕናዎች እንዲ እያልኩ መጥቀስ ጀመርኩ። ቴዲ አፍሮን በጣም የወደድኩት ከሌሎቹ በተለየ መልኩ በሙዚቃዎቹ ስለ ፍቅር በጽኑ መንፈስ ስለሚያቀነቅን ነው። እኔ ደግሞ የፍቅርን ኃያልነት የማምን ሰው ነኝ። ፍቅር በእግዚአብሔር ከመወደድ እና እግዚአብሔርን ከመውደድ ይጀምራል። እግዚአብሔርን የሚወድ ሁሉ ሌሎችን ይወዳል። ይኼ የፍቅር ሉዓላዊ /ነጻ/ ህግ ነው።
ታዲያ ስለፍቅር ሌልች አላዜሙም እንዴ ብሉኝ ነጥቤ እሱ አይደለምና ሃሳቤን እንዲህ ስል እቀጥላሉ። ፍቅር ማለት መውደድ ብቻ አይደለም። መፍራት እና ማክበርም ጭምር ነው። በመፍራት የሆነ ማክበር እና አምልኮ ለእግዚአብሔር፥ በማክበር የሆነ መፍራት ደግሞ ለሰው ልጆች እና ለፍጥረት ሁሉ ይገባል። ይኼን መንፈስ የተጎናጸፈ ሰው ደግሞ ታላቁንም ታናሹንም ያከብራል፣ ይወዳል ይፈራልም። መፍራት በሃይለ ቃል ላላመናገር ነው። መፍራት ከላይም ከታችም በማሃከልም ለቆመው ለመታዘዝ መፍቀድን እንደ ሆነ ልብ ይሏል። ከዚህ አንጻር በኪነጥበቡ ዘርፍ እንዲህ ሆኖ ያገኘሁት ይኼንን ሰው ነው። ይኼንን ሰው መውደድ፣ ማክበር፣ መታዘዝ እንዲሁም እንደ ታላቅ ወንድም ማየት ፍጹም ጤናማ ከሆነ ልብ እና አዕምሮ የሚመነጭ ነው። በእግዚአብሔርም ዘንድ መውደድ ለሰው ልጆች ሁሉ የቀረበ የክርስቶስ አዋጅ ነውና ይኼን ሰው በመውደዴ ደስተኛ ነኝ እላለሁ በኩራት።
በመጨረሻም ለኢትዮጵያ አገራችን እና ለወገኖቻችን ላበረከተው አስተዋጽኦ ከፍ ያለ ምስጋናዬን ለማቅረብ እወዳለሁ። የኪነጥበብ ሙያው እንዲከበርና እንዲታፈር ጭምር የእርሱ በዚህ ደረጃ መግዘፍ ዋናውን ሚና ተጫውቷል ለዚህም ትልቅ ክብርን እሰጠዋለሁ። ቴዲ አፍሮ በሚወዱት፣ በሚጠሉት፣ በሚተቹት /በሚቀኑበት/ ባለሙያዎች ልብ ውስጥ ሳይቀር ትልቅነቱ ሊገዝፍ የቻለው እግዚአብሔርን ይዞ በመቆሙ ስለሆነ እግዚአብሔር እስከ ፍጻሜው ድረስ አብሮት ይሆን ዘንድ መልካም ምኞቴ ነው።
ትንሽ ልከትብ ፈልጌ ብዕሬን አነሳሁት ግን ትልቅ ሰው ሆነብኝ እና በትንሽ አንቀጽ ልቋጨው ተሳነኝ። አሁንም ብዙ ጠልቄ መውጫው እንዳይጠፋኝ የልቤን ሀሳብ ገትቼ ምኞቴን ገልጬ ልተው። በእውነተኛ መውደድ የምወድህ የክቡር ዶ/ር አርቲስት ቴዎድሮስ ካሳሁን /ቴዲ አፍሮ/ መልካም ልደት ይሁንልህ። የሚወድህ ልቤ የጸነሰውን ሀሳብ በሚያከብርህ ብዕሬ እንዲህ ከተብኩት።
✎✍#ታታ_አፍሮ /ነፃ ብዕር/
ሰውን ለመውደድ ሰው ከመሆን የላቀ ምክኒያት ባያስፈልግም የሰዎች አፍ ግን ስለምን ወደድከው ሲል ዕልፍ ጊዜ ጠይቆኛል። በመጀመሪያ ሰው በመሆኑ እንደ ሁሉ ሰው እንደወደድኩህ በኩራት ተናገርኩ። በመቀጠልም የእርሱን ስብዕናዎች እንዲ እያልኩ መጥቀስ ጀመርኩ። ቴዲ አፍሮን በጣም የወደድኩት ከሌሎቹ በተለየ መልኩ በሙዚቃዎቹ ስለ ፍቅር በጽኑ መንፈስ ስለሚያቀነቅን ነው። እኔ ደግሞ የፍቅርን ኃያልነት የማምን ሰው ነኝ። ፍቅር በእግዚአብሔር ከመወደድ እና እግዚአብሔርን ከመውደድ ይጀምራል። እግዚአብሔርን የሚወድ ሁሉ ሌሎችን ይወዳል። ይኼ የፍቅር ሉዓላዊ /ነጻ/ ህግ ነው።
ታዲያ ስለፍቅር ሌልች አላዜሙም እንዴ ብሉኝ ነጥቤ እሱ አይደለምና ሃሳቤን እንዲህ ስል እቀጥላሉ። ፍቅር ማለት መውደድ ብቻ አይደለም። መፍራት እና ማክበርም ጭምር ነው። በመፍራት የሆነ ማክበር እና አምልኮ ለእግዚአብሔር፥ በማክበር የሆነ መፍራት ደግሞ ለሰው ልጆች እና ለፍጥረት ሁሉ ይገባል። ይኼን መንፈስ የተጎናጸፈ ሰው ደግሞ ታላቁንም ታናሹንም ያከብራል፣ ይወዳል ይፈራልም። መፍራት በሃይለ ቃል ላላመናገር ነው። መፍራት ከላይም ከታችም በማሃከልም ለቆመው ለመታዘዝ መፍቀድን እንደ ሆነ ልብ ይሏል። ከዚህ አንጻር በኪነጥበቡ ዘርፍ እንዲህ ሆኖ ያገኘሁት ይኼንን ሰው ነው። ይኼንን ሰው መውደድ፣ ማክበር፣ መታዘዝ እንዲሁም እንደ ታላቅ ወንድም ማየት ፍጹም ጤናማ ከሆነ ልብ እና አዕምሮ የሚመነጭ ነው። በእግዚአብሔርም ዘንድ መውደድ ለሰው ልጆች ሁሉ የቀረበ የክርስቶስ አዋጅ ነውና ይኼን ሰው በመውደዴ ደስተኛ ነኝ እላለሁ በኩራት።
በመጨረሻም ለኢትዮጵያ አገራችን እና ለወገኖቻችን ላበረከተው አስተዋጽኦ ከፍ ያለ ምስጋናዬን ለማቅረብ እወዳለሁ። የኪነጥበብ ሙያው እንዲከበርና እንዲታፈር ጭምር የእርሱ በዚህ ደረጃ መግዘፍ ዋናውን ሚና ተጫውቷል ለዚህም ትልቅ ክብርን እሰጠዋለሁ። ቴዲ አፍሮ በሚወዱት፣ በሚጠሉት፣ በሚተቹት /በሚቀኑበት/ ባለሙያዎች ልብ ውስጥ ሳይቀር ትልቅነቱ ሊገዝፍ የቻለው እግዚአብሔርን ይዞ በመቆሙ ስለሆነ እግዚአብሔር እስከ ፍጻሜው ድረስ አብሮት ይሆን ዘንድ መልካም ምኞቴ ነው።
ትንሽ ልከትብ ፈልጌ ብዕሬን አነሳሁት ግን ትልቅ ሰው ሆነብኝ እና በትንሽ አንቀጽ ልቋጨው ተሳነኝ። አሁንም ብዙ ጠልቄ መውጫው እንዳይጠፋኝ የልቤን ሀሳብ ገትቼ ምኞቴን ገልጬ ልተው። በእውነተኛ መውደድ የምወድህ የክቡር ዶ/ር አርቲስት ቴዎድሮስ ካሳሁን /ቴዲ አፍሮ/ መልካም ልደት ይሁንልህ። የሚወድህ ልቤ የጸነሰውን ሀሳብ በሚያከብርህ ብዕሬ እንዲህ ከተብኩት።
✎✍#ታታ_አፍሮ /ነፃ ብዕር/