Telegram Web Link
" በተለያዩ ማስታወቂያዎች የሚጭበረበረውን ማኅበረሰብ መጠበቅ ኃላፊነታችን ነው " - ወ/ሮ ትዕግስት ሃሚድ

የሳይበር ደኅንነት ወር " የሳይበር ደኅንነት - የዲጂታል ኢትዮጵያ መሰረት " በሚል መሪ ቃል ለ6ኛ ጊዜ በሀገር አቀፍ ደረጃ ከጥቅምት 1 - 30 እንደሚከበር የኢንፎርሜሽን መረብ ደኅንነት አስተዳደር አስታውቋል።

የአስተዳደሩ ዋና ዳይሬክተር ወ/ሮ ትዕግስት ሃሚድ በዚህ ዓመት በሁለት ዋና ዋና ጉዳዮች ላይ ትኩረት እንደሚደረግ አስታውቀዋል።

ምንድናቸው ?

1. በኤ አይ ዘመን የሀሰተኛ መረጃ ሥርጭት እና ቁጥጥርን በተመለከተ ነው የመጀመሪያው ርዕስ። በመክፈቻው ዕለት በዚህ ዙሪያ የተጠና ጥናት ይፋ እንደሚደረግ ገልጸዋል።

ዋና ዳይሬክተሯ ፤ " ብዙዎችችን የምንሸወደው እውቀቱ ስለሌለን ነው " ብለዋል።

" በተለያዩ ማስታወቂያዎች የሚጭበረበረውን ማኅበረሰብ መጠበቅ በኃላፊነት የተሰጠን ማንዴት ስለሆነ ይሄንን ዘልቆ ለማሳየት ስለፈለግን ነው " ሲሉ የወሩ ርዕስ ሆኖ የተመረጠበትን ምክንያት አስረድተዋል።

2. የዲጂታላይዜሽን ደኅንነት የሚለው ሁለተኛው ርዕስ ነው።

" ከአምስት ዓመት በፊት ስናከብር የሳይበር ደኅንነት መሪ ጉዳዮች ብቻ ሳይሆን ሳይበር የሚለውን ብዙ የሚረዳ ዜጋም ተቋማትም በጣም ጥቂት ነበሩ አሁን ላይ እኩል ከእኛ ጋር መናገር የሚችሉ ተቋማትና ዜጎች በእኩል ደረጃ ፈጥረናል ብለን እናምናለን " ሲሉ ተናግረዋል።

ኢትዮጵያ በ2016 ዓ.ም 8854 የሳይበር ጥቃት ሙከራዎች እንዲሁም በ2017 ዓ.ም ደግሞ ቁጥሩ ከፍ ብሎ 13496 የጥቃት ሙከራዎች አስተናግዳለች። እነዚህ  ጥቃቶች ውስጥ በሌሎች አካላት የሚደረጉ የመሰረተ ልማት ቅኝቶች ጭምር እንደ ጥቃት መቆጠራቸው ተገልጿል።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
499😡25🤔13🙏12💔9😭7😱6🕊5
" የፋይናንስ ባለሙያዎችን ጨምሮ 6 ተጠርጣሪዎች ናቸው በቁጥጥር ስር የዋሉት " - የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ፖሊስ

➡️ " ግለሰቦቹ ቀድሞ ተዘጋጅቶ ቮይድ በተደረገ ቼክ ተመሳሳይ አሳትመዉ ነበር ለማጭበርበር የሞከሩት " - የጎፋ ዞን አስተዳደር

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል፣ ጎፋ ዞን ገዜ ጎፋ ወረዳ ኬንቾ ሻቻ ጎዝዲ ቀበሌ ሐምሌ 15 ቀን 2016 ዓ/ም ድንገት ተከስቶ የበርካቶችን ሕይወት የቀጠፈውን የመሬት መንሸራተት አደጋ ተከትሎ የተከሰተውን አጠቃላይ ጉዳት ለማካካስና የተፈናቀሉ ዜጎችን መልሶ ለማቋቋም ድጋፍ ሲሰበሰብ እንደነበር ይታወሳል።

ለተጎጂዎች የተሰበሰበ ከ60 ሚሊዮን ብር በላይ የተወሰኑ ግለሰቦች ተመሳጥረው በተጭበረበረ መንገድ ከባንክ ለማውጣት ሲሞክሩ በቁጥጥር ስር መዋላቸውን ‎የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን የሕዝብ ግንኙነት እና ገፅታ ግንባታ ዘርፍ ዳይረክቶሬት ዳይሬክተር ም/ኮማንደር አሸናፊ ሃይለ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።

" ‎ገንዘቡን ከፋይናስ ባለሙያዎችና አስተባባሪዎች ጋር በመመሳጠር በአንድ ግለሰብ አማካኝነት በአዲስ አበባ ከተማ ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ሸገር ቅርንጫፍ ለማስወጣት ሲሞክሩ ባንኩ በሰጠው ጥቆማ መሰረት የደቡብ ኢትዮጵያ ፖሊስ ከአዲስ አበባ ፖሊስ እና የፌዴራል ፖሊስ ጋር በመተባበር ግለሰቡን በቁጥጥር ስር በማዋል ለክልሉ ፖሊስ ተላልፎ ተሰጥቷል " ሲሉ ገልፀዋል።

‎ከጉዳዩ ጋር ግንኙነት ያላቸዉን የፋይናስ ባለሙያዎችን ጨምሮ 6 ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር መዋላቸዉን ገልፀው በአሁኑ ወቅት ምርመራ እየተደረገባቸው መሆኑንም ተናግረዋል።

የዞኑ መንግስት  ምን ይላል ?

‎የጎፋ ዞን አስተዳደር 60 ሚሊዮን 276 ሺህ 383 (ስልሳ ሚልዮን ሁለት መቶ ሰባ ስድሰት ሺ ሶስት መቶ ሰማንያ ሶስት ብር ) ቀደም ሲል ተሠርቶ ቮይድ በተደረገ ቼክ ቁጥር ' 42221123 ' ተመሳሳይ በማሳተም ገንዘቡን ለመዝረፍ ካመቻቹ በኋላ ከአዲስ አበባ ንግድ ባንክ ሸገር ቅርንጫፍ ለጎፋ ዞን አስተዳደር በተደረገ ጥቆማ ከአዲስ አበባ እና የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ፖሊስ ጋር በመተባበር ገንዘቡ ሳይወጣ ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ስር መዋላቸውን አስታውቋል።

‎" በተለያዩ ሚዲያዎች ለህብረተሰቡ ትክክለኛና ተጨባጭ መረጃ ከመስጠት ይልቅ ሐሰተኛና የተዛባ መረጃ የሚያሰራጩ የማህበራዊ ሚዲያዎች ከድርጊታቸው እንዲቆጠቡ " ሲል አሳስቧል።

በቀጣይ ከጉዳዩ ጋር በተያያዘ የምርመራው ሂደት ሲጣራ ለሕብረተሰቡ እንደሚያሳውቅ ገልጿል፡፡

‎ቲክቫህ ኢትዮጵያ ባደረገው ማጣራት የተለያዩ ማህበራዊ ሚዲያዎች ገንዘቡን ሲያጭበረብሩ የተያዙት ግለሰቦች የመንግስት የስራ ኃላፊዎች እንደሆኑ የገለፁ ሲሆን ፖሊስ እስካሁን በጉዳዩ ላይ የሰጠዉ መረጃ የለም።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
ሀዋሳ
#TikvahEthiopiaFamilyHawassa

@tikvahethiopia
727😢56👏27😭25🙏23😱22😡17🤔8🕊6
TIKVAH-ETHIOPIA
የጤና ሚኒስቴር እስከ መስከረም 30/2018 ዓም የታደሰ የሙያ ፈቃድ ያልያዙ እና ያላወጡ የጤና ባለሙያዎች አገልግሎት መስጠት እንደማይችሉ አሳውቋል። የጤና ባለሙያዎች የሙያ ፈቃድን በሚመለከት በጤና ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ፍሬህይወት አበበ ተፈርሞ በ 30/12/2017 ዓም ለሁሉም ክልሎች የተላከው ደብዳቤ " ሁሉም ክልሎች እስከ መስከረም 30/2018 ዓም ድረስ የንቅናቄ ስራ በመስራት ሁሉም ባለሙያ…
#ተራዝሟል

የጤና ሚኒስቴር እስከ መስከረም 30 ቀን 2018 ዓ/ም ድረስ የአገልግሎት ጊዜዉ ባለፈበት የሙያ ፍቃድ አገልግሎት እየሰጡ ያሉ ጤና ባለሞያዎች ማሳደስ እንዳለባቸውና የሞያ ፍቃድ የሌላቸው ደግሞ አዲስ እንዲያወጡ ለሁሉም ክልሎች እና ለሁለቱ ከተማ አስተዳደሮች ሰርኩላር አውርዶ ነበር።

ነገር ግን በተባለው ጊዜ ለማደስ የIhris-HrI ስርዓት እያስቸገረ መሆኑን ጠቅሶ እስከ ጥቅምት 30 ቀን 2018 ዓ/ም ድረስ ለ1 ወር ጤና ሚኒስቴር ያራዘመ መሆኑን የአዲስ አበባ ምግብና መድኃኒት ባለስልጣን አሳውቋል።

ከጥቅምት 30 ቀን 2018 ዓ/ም በኃላ " no license, no practice " በሚል መሪ ቃል የሙያ ፍቃድ ያላወጡ እና ያላሳደሰ ባለሞያዎች በሞያዉ መስራት እንደማይችሉ ማሳሰቢያ ተላልፏል።

@tikvahethiopia
796🙏87😡47👏44🤔34🥰21🕊20😢17😭14😱9💔2
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
Addis Bank

🌟 Where Trust Meets Success 🌟
At Addis Bank, we believe that success is built on a strong foundation — That foundation is trust, and your success is our mission.

Addis Bank — Where Trust Meets Success.

Follow us

Website- (http://www.addisbanksc.com/)
Telegram- (www.tg-me.com/AddisBank_sc)
Facebook- (http://facebook.com/addisinternationalbank)
Linked in- (https://www.linkedin.com/company/addis-international-bank/)
174🙏12😢3😭3💔2🥰1🕊1
#Tecno

የኢትዮጲያ ትልቁ የፎቶግራፊ ዝግጅት!

ሀገራችሁን በፎቶ በነፃ የምትጎበኙበት፣ የቴክኖ ምርቶችን ጨምሮ በርካታ ሽልማቶችን ጌሞችን እየተጫወታችሁ ምትሸለሙበት፣ አዲሱን ቴክኖ ካሞን 40 በቅርበት የማየት እና የመሞከር ዕድል የሚያገኙበት እና አጅግ አጓጉ የሆነ የሙዚቃ ድግስን የሚካፈሉበት ምርጥ ዝግጅት ቅዳሜ ጥቅምት 1 ጀምሮ ሲ ኤም ሲ የተባበሩት አደባባይ በሚገኘው በአዲስ ኢንተርናሽናል ኮንቬንሽን ሴንተር ቴክኖ ኢትዮጵያ አዘጋጅቶላችኋል፡፡

ኑ ሀገሮን እያዩ፣ እየተሸለሙ፣ አዲሱን ቴክኖ ካሞን 40 እየሞከሩ አብረን እንዋል፡፡

#TecnoCamon40Series #FlashSnap #TecnoAI

@tecno_et
221😡21🙏11🕊8
“ በዚህ አመት 11 አዳዲስ የስልጠና ፕሮግራሞች ይከፈታሉ ” - ብሩክ ከድር (ዶ/ር)

በዚህ አመት 11 የሥልጠና ፕሮግራሞችን እንደሚከፈቱ የኢፌዴሪ ቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኢንስቲትዩት አስታወቀ።

የኢንስቲትዩቱ ዋና ዳይሬክተር ብሩክ ከድር (ዶ/ር) “በደረጃ 8 (በ3ኛ ዲግሪ) በቴክኒክና ሙያ ስልጠና ስርዓት ውስጥ ለመጀመሪያ ጊዜ በሁለት ፕሮግራሞች ስልጠና ይሰጠል” ብለዋል።

አዳዲስ በሚከፈቱት ፕሮግራሞች ኢንስቲትዩቱ የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ውጤት ያመጡ ተማሪዎችን በደረጃ 6 (የመጀመሪያ ድግሪ)፣ በደረጃ 7 (ሁለተኛ ዲግሪ)፣ በደረጃ 8 (ሦስተኛ ዲግሪ) በቴክኒክና ሙያ ስልጠና እንደሚሰጥ አስረድተዋል።

የሚከፈቱት 11ዱ አዳዲስ ፕሮግራሞች ምን ምን ናቸው ?
በደረጃ 6፦
- ባዮሜዲካል ቲክኖሎጂ፣ 
- የሳይበርሰኩሪቲ ቴክኖሎጂ፣
- የአርቲፊሻል ኢንተሌጀንስ ቴክኖሎጂ፣
- የኢንተሌጀንስ ሮቦቲክስ ቴክኖሎጂ፣
- ኒውኢነርጂይ ቪሄክል ቴክኖሎጂ፣
- ፕላስቲክ ቴክኖሎጂ እና
- ሆርቲካልቸር ናቸው።

በደረጃ 7፦
- ኢንቲሪየር ዲዛይን እና ፊኒሽንግ ቴክኖሎጂ
- ሌዘርፕሮዳክት ቴክኖሎጂ ናቸው።

በደረጃ 8፦
- ማኑፋክቸሪንግ እና ቲቪቲሊደርሽፕ የተሰኙ የስልጠና ፕሮግራሞች ናቸው ተብሏል።

ከደረጃ 1 እስከ ደረጃ 5 የመግቢያ ነጥብ የሥራ እና ክህሎት ሚኒስቴር በኩል ይፋ የሚሆን ሲሆን በደረጃ 6፣ 7 እና 8 (መጀመሪያ ዲግሪ፣ ሁለተኛ ዲግሪና 3ኛ ዲግሪ) የመቁረጫ ነጥባቸው በትምህርት ሚኒስቴር የሚወሰን ሲሆን የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ውጤት ያላቸውና NGAT ተፈትነው ውጤት ያላቸው በኢንስቲትዩቱ ይስተናገዳሉ ተብሏል።

ዘርፉ ብዙም ተፈላጊ እንዳልሆነ ነው ግንዛቤው ያለው፣ ሰልጣኞች በአዳዲሶቹ ፕሮግራሞች እንዲሰለጥኑ የሚያደርግ ምን የተለዬ ነገር አለ? በሚል ለቀረበው ጥያቄ ብሩክ (ዶ/ር)፣ “አዳዲስ የስልጠና ዘርፎች ገበያው የሚፈልጋቸው መሆኑን አረጋግጠን ነው የከፈትናቸው” ብለዋል። 

የቴክኒክና ሙያ ሰልጣኞች ከምረቃ በኋላ የሥራ እድሉ ስለመኖሩ ሲጠየቁም፣ “ስልጠናውን ሊያጠናቅቁ ሲሉ የሚቀጠሩ ሰልጣኞች ሰልጣኞች ቁጥር ከፍተኛ ነው” የሚል ምላሽ ሰጥተዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
1.16K👏92🕊30💔26😢18🙏18🥰17🤔17😡11😱8😭5
#NobelPeacePrize

" በዓለም ላይ ግጭቶችን በማስቆም ሰላም እና መግባባት እንዲሰፍን ባደረኳቸው ጥረቶች የኖቤል ሰላም ሽልማት ለእኔ ይገባኛል " በማለት ሲናገሩ የነበሩትና የተለያዩ የሀገራት መሪዎችም " የዘንድሮው ሽልማት ለእሳቸው ይገባቸዋል " ያሉላቸው የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ የኖቤል የሰላም አሸናፊ ሳይሆኑ ቀሩ።

የ2025 የኖቤል የሰላም ሽልማት ለቬንዝዌላዊቷ የተቃዋሚ መሪ ማሪያ ኮሪና ማቻዶ ተበርክቷል። ማቻዶ በቬንዙዌላ ለዲሞክራሲ እና ለሰብዓዊ መብት መከበር አድርገውታል በተባለ ያላሰለሰ ትግል ነው ተሸላሚ የሆኑት።

@tikvahethiopia
22.3K👏519😭138🙏78😡53💔47🥰43🤔41🕊40😢16😱15
🌟 የአሜሪካ ደርሶ መልስ ትኬት መግዣን ጨምሮ የተለያዩ አጓጊ ሸልማቶችን ከ11% የገንዘብ ስጦታ ጋር ይሸለሙ!!

የግራንድ አፍሪካ ሩጫን አስመልክቶ እስከ ጥቅምት 21 ቀን 2018 ዓ.ም ከአሜሪካ በቴሌብር ሬሚት እና በአጋሮቻችን በኩል የተላከልዎን ዓለም አቀፍ ሐዋላ በቴሌብር ሲቀበሉ 11% የገንዘብ ስጦታ ያገኛሉ።

በተጨማሪ 300 ዶላር እና ከዚያ በላይ ሲቀበሉ
✈️ 💰 300ሺህ ብር አሜሪካ ደርሶ መልስ ነጻ የበረራ ትኬት
💻 ላፕቶፕ ኮምፒተሮች
📲 የስልክ ቀፎዎች
🌐 የብሮድባንድ ኢንተርኔት የ6 ወር ክፍያዎች
📶 ከ10,000 በላይ 1GB የሞባይል ዳታ ስጦታዎችን ለሚያሸልመው የዕድል ጨዋታ ብቁ ይሆናሉ!

ዕጣዎቹ ቴሌብር ሱፐርአፕ https://bit.ly/telebirr_SuperApp ላይ ከጥቅምት 22 እስከ ጥቅምት 28/2018 ዓ.ም ክፍት ይሆናሉ!


#Ethiotelecom #telebirr #telebirrSuperApp #DigitalEthiopia #DigitalAfrica #RealizingDigitalEthiopia
242😱6🥰5🕊4😡3😢2👏1
" በሚቀጥሉት ዓመታት የተማሪዎች ምደባ ይቆማል " - ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ

ትምህርት ሚኒስቴር በሚቀጥሉት ዓመታት የተማሪዎች ምደባ እንደሚያቆም ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሀኑ ነጋ አስታወቁ።

ይህ ያሳወቁት የትምህርት ሚኒስቴር ከመንግስት ዩኒቨርስቲዎች ጋር የ2018 ዓ.ም የትምህርት ዘመን የቁልፍ ተግባራት የፊርማ ስነስርዓት ባከናወነበት ወቅት ነው።

በዚሁ ወቅት ፕሮፌሰር ብርሀኑ ነጋ ጠንካራ የስራ አቅጣጫ አስቀምጠዋል፡፡

ፕሮፌሰር ብርሀኑ ነጋ እንደገለፁት፤ በሚቀጥሉት ዓመታት የትምህርት ሚኒስቴር የተማሪዎችን ምደባ እንደሚያቆምና የማለፊያ ነጥብ የሚያስመዘግቡ ተማሪዎች በሚፈልጓቸው ዩኒቨርሲቲዎችና የትምህርት መስኮች እንዲያመለክቱ ይደረጋል፡፡

" የዩኒቨርሲቲ ትምህርት እንደከዚህ ቀደሙ በትምህርት ሚኒስቴር ምደባ ሳይሆን በተማሪዎቹ ምርጫ ይሆናል " ብለዋል።

" ተማሪዎች የሚማሩበትን ዩኒቨርሲቲ ሲመርጡም ምክንያታዊ በመሆን በዬትኛው ዩኒቨርሲቲ የተሻለ የትምህርት መስክ፣ እውቀትና የስራ እድል ላገኝ እችላለሁ በማለት ይመርጣሉ " ሲሉ ገልጸዋል። #ኢፕድ

@tikvahethiopia
13.84K👏1.01K😡192🤔114😱96😭81🙏58🕊37😢34💔27🥰24
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#Ethiopia

በተፈጥሮ ጋዝ የሚሰሩ ማናቸውም አይነት የደረቅና የፈሳሽ ጭነት እንዲሁም የህዝብ ማመላለሻ ተሽከርካሪዎች ከጉምሩክ ቀረጥ ነጻ ወደ ሀገር እንዲገቡ መፈቀዱን የገንዘብ ሚኒስቴር አሳውቋል።

" ኢትዮጵያ ከፍተኛ መጠን ያለው የተፈጥሮ ጋዝ ክምችት ያላት መሆኑ ቢታወቅም ለዘመናት የዚህ የተፈጥሮ ሃብት ተጠቃሚ ሳትሆን ቆይታለች " ያለው ሚኒስቴሩ " ይህንን ሁኔታ ለመለወጥ መንግስት ሲያደርግ የቆየው እልህ አስጨራሽ ጥረት ተሳክቶ በቅርቡ በካሉብ አካባቢ የሚገኘውን የተፈጥሮ ጋዝ ጥቅም ላይ ማዋል የሚያስችል ኢንዱስትሪ ተመርቆ የተፈጥሮ ጋዝ የማምረት ስራ በይፋ ተጀምሯል " ብሏል።

" ይህን ምርት ለሀገር ውስጥ ገበያ በማቅረብ ቤንዚንና ናፍታ የሚጠቀሙ ተሽከርካሪዎችን የተፈጥሮ ጋዝ በሚጠቀሙ ተሽከርካሪዎች መተካት አስፈላጊ ሆኖ ተገኝቷል " ሲል ገልጿል።

" የተፈጥሮ ጋዝ የሚያመነጨው በካይ አየር እጅግ በጣም ዝቅተኛ የሆነ፤ ለተለያየ የኃይል ምንጭ አገልግሎት ሊውል የሚችል፤ በኃይል አጠቃቀም ረገድ ውጤታማነት ያለው ነው " ብሏል።

" የተፈጥሮ ጋዝ በኢትዮጵያ የሚመረት በመሆኑ ለነዳጅ ግዥ ታወጣ የነበረውን የውጭ ምንዛሬ የሚያስቀር በመሆኑ መንግስት የተፈጥሮ ጋዝ አጠቃቀምን ለማበረታታት ወስኗል፤ በዚህም መሰረት ይህ መመሪያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ሙሉ በሙሉ በተፈጥሮ ጋዝ የሚሰሩ ማናቸውም አይነት የደረቅ እና የፈሳሽ ጭነት እና የህዝብ ማመላለሻ ተሽከርካሪዎች ከጉምሩክ ቀረጥ ነጻ ወደ ሀገር እንዲገቡ ተፈቅዷል " ሲል አሳውቋል።

ይህ መመሪያ ከወጣበት ቀን በፊት በትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር እና በሌሎች ተቋማት ወደ ሀገር እንዲገቡ ከተፈቀደላቸውና በስድስት ወር ጊዜ ውስጥ ወደ ሀገር ከሚገቡት በስተቀር በቤንዚን እና በናፍጣ የሚሰሩ የጭነት እና የህዝብ ማመላለሻ ተሽከርካሪዎች ወደ ሀገር እንዳይገቡ ጥብቅ ቁጥጥር እንዲደረግ ሚኒስቴሩ አዟል።

@tikvahethiopia
1.31K👏121🙏46😭35😡34🤔30🕊18💔16🥰11😢1
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#Ethiopia

በቤንዚን እና በናፍጣ የሚሰሩ ከባድ ተሽከርካሪዎች ወደ ሀገር እንዳይገቡ ተከልክሏል።

በተፈጥሮ ጋዝ የሚሰሩ የጭነትና የህዝብ ማመላለሻ ተሽከርካሪዎች ከጉምሩክ ቀረጥ ነፃ እንዲገቡ መመሪያ ወጥቷል።

ይህ መመሪያ ከወጣበት ቀን በፊት በትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር እና በሌሎች ተቋማት ወደ ሀገር እንዲገቡ ከተፈቀደላቸውና በስድስት ወር ጊዜ ውስጥ ወደ ሀገር ከሚገቡት በስተቀር በቤንዚን እና በናፍጣ የሚሰሩ የጭነት እና የህዝብ ማመላለሻ ተሽከርካሪዎች ወደ ሀገር እንዳይገቡ ክልከላ ተላልፏል።

@tikvahethiopia
2701😡170👏78😢30🕊23🙏22😭21🤔16😱16💔6🥰5
TIKVAH-ETHIOPIA
" በሚቀጥሉት ዓመታት የተማሪዎች ምደባ ይቆማል " - ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ትምህርት ሚኒስቴር በሚቀጥሉት ዓመታት የተማሪዎች ምደባ እንደሚያቆም ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሀኑ ነጋ አስታወቁ። ይህ ያሳወቁት የትምህርት ሚኒስቴር ከመንግስት ዩኒቨርስቲዎች ጋር የ2018 ዓ.ም የትምህርት ዘመን የቁልፍ ተግባራት የፊርማ ስነስርዓት ባከናወነበት ወቅት ነው። በዚሁ ወቅት ፕሮፌሰር ብርሀኑ ነጋ ጠንካራ የስራ አቅጣጫ…
#MoE

ዩኒቨርሲቲዎች ስለተማሪዎቻቸው ትክክለኛ መረጃ ካላቀረቡ ፕሬዝዳንቱን ጨምሮ ሀላፊዎቻቸው ከስራ ይባረራሉ ተባለ።

የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በቀጣይ 6 ወራት ዩኒቨርሲቲዎች ስለተማሪዎቻቸውና ሌሎችም ጉዳዮች መረጃ በትክክል ለትምህርት ሚኒስቴር ማቅረብ አለባቸው ብለዋል።

ይህንን ያላደረገ የዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት በስራው አይቀጥልም ሲሉ አስጠንቅቀዋል።

" ይህንን ስራ እኔ በቀጥታ እከታተለዋለሁ " ማለታቸውን ሸገር ኤፍ ኤም ዘግቧል።

ከወራት በፊት ሚኒስትሩ " ዩኒቨርሲቲዎች ተማሪዎቻቸውን ከነፎቶ እንዲሁም ስለሚሠሩት ሥራ ትክክለኛ መረጃ ስጡን ብለን ከጠየቅን ሦስት ዓመት አልፎናል፡፡ ሆኖም እስካሁን የተሟላ መረጃ ለማግኘት ችግር ሆኖብናል፡፡ በዩኒቨርሲቲዎች ዘንድ እውነተኛ መረጃ መስጠት አልተለመደም " ማለታቸው ይታወሳል።

ዩኒቨርስቲዎች ከተማሪዎች ምገባ ጋር ተያይዞ የውሸት ሪፖርት ያቀርቡ እንደነበር ዩኒቨርሲቲዎች የተማሪ ቁጥር በውሸት በመጨመር በጀት እንዲጨመርላቸው ያደርጉም እንደበር ተናግረው ነበር።

#TikvahEthiopiaFamily

@tikvahethiopia
1.66K👏371😡69😱38🤔33🥰27🙏27😭24🕊13😢11💔9
2025/10/27 18:11:01
Back to Top
HTML Embed Code: