#Cameroon
የ92 ዓመቱ ፖል ቢያ የካሜሩንን ምርጫ ለስምንተኛ ጊዜ ማሸነፋቸው ተነገረ።
የ43 ዓመት የስልጣን ዘመን ቆይታቸው ተራዝሟል።
ፖል ቢያ በቅርብ በሀገራቸው የተደረገውን ፕሬዚዳንታዊ ምርጫ 53.66% ድምጽ በማግኘት እንዳሸነፉ ለሀገሪቱ ለሕገ-መንግሥት ጉዳዮች ም/ቤት የቀረበው ይፋዊ ውጤት አሳይቷል።
የቅርብ ተቀናቃኛቸው ኢሳ ቲቺሮማ ባካሪ በ18 በመቶ ነጥብ ርቀው 35% ድምጽ አግኝተዋል ተብሏል።
ስምንተኛ የሥልጣን ዘመናቸው የ43 ዓመት ፕሬዝዳንትነታቸውን ያራዘመ እንደሆነ ስፑትኒክ ዘግቧል።
@tikvahethiopia
የ92 ዓመቱ ፖል ቢያ የካሜሩንን ምርጫ ለስምንተኛ ጊዜ ማሸነፋቸው ተነገረ።
የ43 ዓመት የስልጣን ዘመን ቆይታቸው ተራዝሟል።
ፖል ቢያ በቅርብ በሀገራቸው የተደረገውን ፕሬዚዳንታዊ ምርጫ 53.66% ድምጽ በማግኘት እንዳሸነፉ ለሀገሪቱ ለሕገ-መንግሥት ጉዳዮች ም/ቤት የቀረበው ይፋዊ ውጤት አሳይቷል።
የቅርብ ተቀናቃኛቸው ኢሳ ቲቺሮማ ባካሪ በ18 በመቶ ነጥብ ርቀው 35% ድምጽ አግኝተዋል ተብሏል።
ስምንተኛ የሥልጣን ዘመናቸው የ43 ዓመት ፕሬዝዳንትነታቸውን ያራዘመ እንደሆነ ስፑትኒክ ዘግቧል።
@tikvahethiopia
🤔642❤230😭186😡78😱42😢16🙏13🕊10👏9💔6🥰3
🙏1.5K❤597🥰70🕊48😡30🤔12😭11😢10😱2
TIKVAH-ETHIOPIA
" ባለቤቴንና አምስት ልጆቼን ነው ያጣሁት " - ተጎጂ አባት ➡️ " ጥቃቱን ያደረሱት ጽንፈኛ የሚባሉ በዚሁ በወሰን አከባቢ ሸምቀው ያሉ ታጣቂዎች ናቸው ! " - የአካባቢው ነዋሪ በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን ኖኖ ወረዳ ቆንዳላ ቀበሌ ታጣቂዎች ባደረሱት ጥቃት ቢያንስ 14 ሰዎች ተገደሉ። ጥቃቱ ከትናንት በስቲያ ሃሙስ ሃምሌ 03 ቀን 2017 ዓ.ም. ምሽት ነው የተፈጸመው። የታጠቁ አካላት በመደዳው…
" 22 ሰዎች ወዲያው መገደላቸው ሲረጋገጥ ቀሪዎቹ አስከሬናቸው በየጥሻው የወደቁና በሆስፒታል ህይወታቸው ያለፉ ናቸው አጠቃላይ ሟቾች 29 ናቸው " - ነዋሪዎች
➡️ " ' የተገደሉት 22 ናቸው ' የሚባለው ውሸት ነው። 12 ናቸው የተገደሉት። ከ22 በላይ የተገደሉት ከታጣቂዎቹ ወገን ነው " - የወረዳው አስተዳዳሪ
በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን ታጣቂዎች ህጻናትና ሴቶችን ጨምሮ በርካታ ንጹሃንን ገድለዋል።
የንጹሃን ግድያ ተደጋግሞ በተሰማበት በምዕራብ ሸዋ ዞን ኖኖ ወረዳ ሃሎዲንቂ ቀበሌ እሁድ ምሽት በግምት ሁለት ሰዓት ግድም የታጠቁ አካላት ባደረሱት ጥቃት ከ20 በላይ ሰዎች ወዲያው መገደላቸውን ተጎጂዎች እና የአከባቢው ነዋሪዎች ለዶቼ ቨለ ተናግረዋል፡፡
ነዋሪዎቹ ምን አሉ ?
" ጥቃቱ እሁድ ምሽት ነው የተፈጸመው።
አገር ሰላም ብለው እንደወትሮው ወደ ቤታቸው በገቡ ንጹሃን የኖኖ ወረዳ ሃሎዲንቂ ቀበሌ ነዋሪዎች ላይ ነው የተፈጸመው።
በአጎራባች የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ጉራጌ ዞን ወረዳዎች የሚንቀሳቀሱ ታጣቂዎች ወሰን ተሻግረው ነው ጥቃቱን ያደረሱት።
ምንም ያልታጠቁ ሰላማዊ ዜጎች ላይ ዘግናኝ ግድያ ነው የተፈጸመው። ጥቃቱን ያደረሱት ደግሞ በአከባቢው የሚንቀሳቀሱ ጽንፈኛ የተባሉ ታጣቂዎች ናቸው።
በእሁድ ምሽቱ ድንገተኛ ጥቃት 22 ሰዎች ወዲያው ተገድለዋል።
ዳርጌ በሚባል ስፍራ ምሽት ከአንድ እስከ ሁለት ሰዓት ግድም በተወሰደው በዚህ ጥቃት ህጻናት እና ሴቶች በስፋት ተጠቂ ሆነዋል። " ብለዋል።
ቤተሰቦቻቸው የጥቃቱ ሰለባ የሆኑባቸውና ለደህንነታቸው ስማቸውን መናገር ያልፈለጉ አንድ ነዋሪ " ሰላማዊ ዜጎችን በጭለማ ገብተው ነው የፈጁዋቸው፡፡ አሁን በእሁድ ምሽቱ በዚህ ጥቃት የተገደሉ ሰዎች ቁጥር 29 ደርሰዋል " ሲሉ ተናግረዋል።
" 22 ሰዎች ወዲያው መገደላቸው ሲረጋገጥ ቀሪዎቹ አስከሬናቸው በየጥሻው የወደቁና በሆስፒታል ህይወታቸው ያለፉ ናቸው " ብለዋል፡፡
ነዋሪዎቹ የተገደሉትን ለመለየት ሰኞ እስከ ምሽት የአስከሬን አሰሳ በአከባቢው ሲደረግ እንደነበር ጠቁመዋል።
ከሟቾች አባወራ የሆኑ ትልልቅ ሰዎች ከስድስት የማያልፉ ሲሆን ቀሪዎቹ ህጻናት እና አብዛኛው ደግሞ ታዳጊ ተማሪዎች እና ሴቶች ናቸው ሲሉ ተናግረዋል።
የኖኖ ወረዳ አስተዳዳሪ አቶ ወንዳፍራሽ ሉሌሳ ፥ " የተገደሉት 22 ናቸው የሚባለው ውሸት ነው። 12 ናቸው የተገደሉት። ከ22 በላይ የተገደሉት ከታጣቂዎቹ ወገን ነው " ብለዋል።
ጥቃቱ ከተፈጸመ በኋላ የመንግሥት የፀጥታ ኃይሎች በአካባቢው ተሰማርተው እርምጃ መውሰዳቸውን ገልጸዋል።
በዚህ ወረዳ ተመሳሳይ ጥቃት ለምን ተደጋገመ ?
ነዋሪዎች እንደሚሉት በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን አጎራባች በሆነው የጉራጌ ዞን አበሽጌ ወረዳ ውስጥ ወታደራዊ ስልጠና የሚወስዱ ታጣቂዎች አሉ።
እኚህ ታጣቂዎች በተደጋጋሚ እየገቡ ህጻናትን ጨምሮ ያገኙትን በምንም ፖለቲካ ውስጥ የሌሉ ሰላማዊ ሰዎችን እያጠቁ ይመለሳሉ፡፡
" እነዚህ ሟቾች ምንም ውስጥ የሌሉና ምንም ጥፋት የሌለባቸው ናቸው " የሚሉት ነዋሪዎቹ ፥ ጥላቻ እና ማንነት ላይ የሚያተኩር ጥቃት እንደሆነ ገልጸዋል።
ይህ ካልሆነ ከሶስት ዓመት እስከ 14 ዓመት እድሜ ክልል ውስጥ የሚገኙ ህጻናት ምን ውስጥ ይሆናሉ ተብሎ ይታሰባል ? ሲሉ ጠይቀዋል።
በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ጉራጌ ዞን አበሽጌ ወረዳ በተለያዩ ቀበሌዎች የሚንቀሳቀሱ ጥቃት አድራሾቹ በምዕራብ ሸዋ ዞን ኖኖ ወረዳ በተለያዩ ጊዜያት በተፈጠረ ግጭት ቤተሰቦቻቸውን ይዘው የተፈናቀሉም እንደሚገኙባቸው ገልጸዋል፡፡
" ወደ ጉራጌ ዞን የሄዱት ሰዎች የኦሮሞ ነጻነት ጦር የሚፈጽመውን ጥቃት እንዲሁም በአካባቢው አስተዳደር ከመሬት ይዞታ ጋር በተያያዘ በወጣ አዲስ አሠራር ምክንያት ነው " ሲሉ ነዋሪዎች አመልክተዋል።
" አሁን ላይ ጥቃት ከሚያደርሱ ታጣቂዎቹ አብዛኞቹ በ2016 ዓ.ም. በአንድ ሰርግ ላይ ቦምብ ተጥሎ 36 ሰዎች ግድም መገደላቸውን ተከትሎ ከአከባቢው የተፈናቀሉ ናቸው " ብለዋል።
ሰኔ ወር 2016 ዓ.ም. በዚሁ ኖኖ ወረዳ ቆንዳላ ቀበሌ በአንድ ሰርግ ቤት ላይ ቦምብ ተጥሎ ሙሽሮችን ጨምሮ 36 ሰዎች ከተገደሉ በኋላ ተደጋጋሚ የንጹሃን ጥቃቶች እና የግድያ ዜናዎች ከዚህ አከባቢ ተለይቶ አያውቅም፡፡
በቅርቡ 2017 ዓ.ም. ሰኔ ወር ላይ ዳግም በንጹሃን ላይ ባነጣጠረው የዚሁ አከባቢ ጥቃት ከአንድ ቤት የተገደሉ ስድስት የቤተሰብ አባላትን ጨምሮ 14 ሰላማዊ ነዋሪዎች አልቀዋል።
የጸጥታ ስጋቱ በተደጋገመበት የኖኖ ወረዳ አዋሳኝ ቀበሌያት አከባቢ የነዋሪዎቹ ስጋት ከጊዜ ወደ ጊዜ ዘላቂ እልባት ከማግኘት ይልቅ እያደር እየከፋና እየተባባሰ መምጣቱን የአከባቢው ነዋሪዎች ገልጸዋል።
የኖኖ ወረዳ አስተዳዳሪ አቶ ወንድአፍራሽ ሉሌሳ ጥቃት የሚያደርሱት ወገኖች ፤ የመንግሥት የፀጥታ አካላት የኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት ላይ ሲዘምት በሚያገኙት አጋጣሚ ጥቃት እንደሚፈጽም ይናግራሉ።
" ዓላማቸው በሕገ ወጥ መንገድ ሰፍረው መሬት በመውረር ግብር የማይከፍሉበት መሬት ማግኘት ነው። ' ከመሬቱ ተፈናቅለናል አሁን መመለስ አለብን ' በሚል ነው ጥቃት የፈጸሙት። ይህ ግን ሕልም ነው " ብለዋል።
ይህ መረጃ ባለቤትነቱ የዶቼ ቨለ ሬድዮ ጣቢያ እና ቢቢሲ አማርኛ ነው።
ከዚህ ወረዳ ጋር በተያያዘ ከዚህ ቀደም ምን መረጃዎች ተላልፈው ነበር ?
በጥቂቱ ፦
✅https://www.tg-me.com/tikvahethiopia/86904
✅https://www.tg-me.com/tikvahethiopia/87947
✅https://www.tg-me.com/tikvahethiopia/88299
✅https://www.tg-me.com/tikvahethiopia/98393
@tikvahethiopia
➡️ " ' የተገደሉት 22 ናቸው ' የሚባለው ውሸት ነው። 12 ናቸው የተገደሉት። ከ22 በላይ የተገደሉት ከታጣቂዎቹ ወገን ነው " - የወረዳው አስተዳዳሪ
በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን ታጣቂዎች ህጻናትና ሴቶችን ጨምሮ በርካታ ንጹሃንን ገድለዋል።
የንጹሃን ግድያ ተደጋግሞ በተሰማበት በምዕራብ ሸዋ ዞን ኖኖ ወረዳ ሃሎዲንቂ ቀበሌ እሁድ ምሽት በግምት ሁለት ሰዓት ግድም የታጠቁ አካላት ባደረሱት ጥቃት ከ20 በላይ ሰዎች ወዲያው መገደላቸውን ተጎጂዎች እና የአከባቢው ነዋሪዎች ለዶቼ ቨለ ተናግረዋል፡፡
ነዋሪዎቹ ምን አሉ ?
" ጥቃቱ እሁድ ምሽት ነው የተፈጸመው።
አገር ሰላም ብለው እንደወትሮው ወደ ቤታቸው በገቡ ንጹሃን የኖኖ ወረዳ ሃሎዲንቂ ቀበሌ ነዋሪዎች ላይ ነው የተፈጸመው።
በአጎራባች የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ጉራጌ ዞን ወረዳዎች የሚንቀሳቀሱ ታጣቂዎች ወሰን ተሻግረው ነው ጥቃቱን ያደረሱት።
ምንም ያልታጠቁ ሰላማዊ ዜጎች ላይ ዘግናኝ ግድያ ነው የተፈጸመው። ጥቃቱን ያደረሱት ደግሞ በአከባቢው የሚንቀሳቀሱ ጽንፈኛ የተባሉ ታጣቂዎች ናቸው።
በእሁድ ምሽቱ ድንገተኛ ጥቃት 22 ሰዎች ወዲያው ተገድለዋል።
ዳርጌ በሚባል ስፍራ ምሽት ከአንድ እስከ ሁለት ሰዓት ግድም በተወሰደው በዚህ ጥቃት ህጻናት እና ሴቶች በስፋት ተጠቂ ሆነዋል። " ብለዋል።
ቤተሰቦቻቸው የጥቃቱ ሰለባ የሆኑባቸውና ለደህንነታቸው ስማቸውን መናገር ያልፈለጉ አንድ ነዋሪ " ሰላማዊ ዜጎችን በጭለማ ገብተው ነው የፈጁዋቸው፡፡ አሁን በእሁድ ምሽቱ በዚህ ጥቃት የተገደሉ ሰዎች ቁጥር 29 ደርሰዋል " ሲሉ ተናግረዋል።
" 22 ሰዎች ወዲያው መገደላቸው ሲረጋገጥ ቀሪዎቹ አስከሬናቸው በየጥሻው የወደቁና በሆስፒታል ህይወታቸው ያለፉ ናቸው " ብለዋል፡፡
ነዋሪዎቹ የተገደሉትን ለመለየት ሰኞ እስከ ምሽት የአስከሬን አሰሳ በአከባቢው ሲደረግ እንደነበር ጠቁመዋል።
ከሟቾች አባወራ የሆኑ ትልልቅ ሰዎች ከስድስት የማያልፉ ሲሆን ቀሪዎቹ ህጻናት እና አብዛኛው ደግሞ ታዳጊ ተማሪዎች እና ሴቶች ናቸው ሲሉ ተናግረዋል።
የኖኖ ወረዳ አስተዳዳሪ አቶ ወንዳፍራሽ ሉሌሳ ፥ " የተገደሉት 22 ናቸው የሚባለው ውሸት ነው። 12 ናቸው የተገደሉት። ከ22 በላይ የተገደሉት ከታጣቂዎቹ ወገን ነው " ብለዋል።
ጥቃቱ ከተፈጸመ በኋላ የመንግሥት የፀጥታ ኃይሎች በአካባቢው ተሰማርተው እርምጃ መውሰዳቸውን ገልጸዋል።
በዚህ ወረዳ ተመሳሳይ ጥቃት ለምን ተደጋገመ ?
ነዋሪዎች እንደሚሉት በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን አጎራባች በሆነው የጉራጌ ዞን አበሽጌ ወረዳ ውስጥ ወታደራዊ ስልጠና የሚወስዱ ታጣቂዎች አሉ።
እኚህ ታጣቂዎች በተደጋጋሚ እየገቡ ህጻናትን ጨምሮ ያገኙትን በምንም ፖለቲካ ውስጥ የሌሉ ሰላማዊ ሰዎችን እያጠቁ ይመለሳሉ፡፡
" እነዚህ ሟቾች ምንም ውስጥ የሌሉና ምንም ጥፋት የሌለባቸው ናቸው " የሚሉት ነዋሪዎቹ ፥ ጥላቻ እና ማንነት ላይ የሚያተኩር ጥቃት እንደሆነ ገልጸዋል።
ይህ ካልሆነ ከሶስት ዓመት እስከ 14 ዓመት እድሜ ክልል ውስጥ የሚገኙ ህጻናት ምን ውስጥ ይሆናሉ ተብሎ ይታሰባል ? ሲሉ ጠይቀዋል።
በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ጉራጌ ዞን አበሽጌ ወረዳ በተለያዩ ቀበሌዎች የሚንቀሳቀሱ ጥቃት አድራሾቹ በምዕራብ ሸዋ ዞን ኖኖ ወረዳ በተለያዩ ጊዜያት በተፈጠረ ግጭት ቤተሰቦቻቸውን ይዘው የተፈናቀሉም እንደሚገኙባቸው ገልጸዋል፡፡
" ወደ ጉራጌ ዞን የሄዱት ሰዎች የኦሮሞ ነጻነት ጦር የሚፈጽመውን ጥቃት እንዲሁም በአካባቢው አስተዳደር ከመሬት ይዞታ ጋር በተያያዘ በወጣ አዲስ አሠራር ምክንያት ነው " ሲሉ ነዋሪዎች አመልክተዋል።
" አሁን ላይ ጥቃት ከሚያደርሱ ታጣቂዎቹ አብዛኞቹ በ2016 ዓ.ም. በአንድ ሰርግ ላይ ቦምብ ተጥሎ 36 ሰዎች ግድም መገደላቸውን ተከትሎ ከአከባቢው የተፈናቀሉ ናቸው " ብለዋል።
ሰኔ ወር 2016 ዓ.ም. በዚሁ ኖኖ ወረዳ ቆንዳላ ቀበሌ በአንድ ሰርግ ቤት ላይ ቦምብ ተጥሎ ሙሽሮችን ጨምሮ 36 ሰዎች ከተገደሉ በኋላ ተደጋጋሚ የንጹሃን ጥቃቶች እና የግድያ ዜናዎች ከዚህ አከባቢ ተለይቶ አያውቅም፡፡
በቅርቡ 2017 ዓ.ም. ሰኔ ወር ላይ ዳግም በንጹሃን ላይ ባነጣጠረው የዚሁ አከባቢ ጥቃት ከአንድ ቤት የተገደሉ ስድስት የቤተሰብ አባላትን ጨምሮ 14 ሰላማዊ ነዋሪዎች አልቀዋል።
የጸጥታ ስጋቱ በተደጋገመበት የኖኖ ወረዳ አዋሳኝ ቀበሌያት አከባቢ የነዋሪዎቹ ስጋት ከጊዜ ወደ ጊዜ ዘላቂ እልባት ከማግኘት ይልቅ እያደር እየከፋና እየተባባሰ መምጣቱን የአከባቢው ነዋሪዎች ገልጸዋል።
የኖኖ ወረዳ አስተዳዳሪ አቶ ወንድአፍራሽ ሉሌሳ ጥቃት የሚያደርሱት ወገኖች ፤ የመንግሥት የፀጥታ አካላት የኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት ላይ ሲዘምት በሚያገኙት አጋጣሚ ጥቃት እንደሚፈጽም ይናግራሉ።
" ዓላማቸው በሕገ ወጥ መንገድ ሰፍረው መሬት በመውረር ግብር የማይከፍሉበት መሬት ማግኘት ነው። ' ከመሬቱ ተፈናቅለናል አሁን መመለስ አለብን ' በሚል ነው ጥቃት የፈጸሙት። ይህ ግን ሕልም ነው " ብለዋል።
ይህ መረጃ ባለቤትነቱ የዶቼ ቨለ ሬድዮ ጣቢያ እና ቢቢሲ አማርኛ ነው።
ከዚህ ወረዳ ጋር በተያያዘ ከዚህ ቀደም ምን መረጃዎች ተላልፈው ነበር ?
በጥቂቱ ፦
✅https://www.tg-me.com/tikvahethiopia/86904
✅https://www.tg-me.com/tikvahethiopia/87947
✅https://www.tg-me.com/tikvahethiopia/88299
✅https://www.tg-me.com/tikvahethiopia/98393
@tikvahethiopia
❤788😭727😡59💔32🕊20😢16🙏8😱6🥰2🤔1
TIKVAH-ETHIOPIA
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የቅዱስ ሲኖዶስ ዓቢይ ጉባኤ በዛሬው ዕለት በጸሎት መከፈቱን ቤተክርስቲያኗ አሳውቃናለች። @tikvahethiopia
" የሰላምና የዕርቅ ዕድል ቅድሚያ እንዲሰጠው ጉባኤው የበኩሉን ጥረት ማድረግ ይገባዋል " - ቅዱስነታቸው
ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ
ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ
ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት የቅዱስ ሲኖዶስ ዓቢይ ጉባኤ መጀመሩን አስመልክቶ መልዕክት አስተላልፈዋል።
በዚህም መልዕክታቸው የርስ በርስ ግጭቶች ቆመው ግጭቶች በውይይት እና በድርድር እንዲፈቱ ጉባኤው የበኩሉን ጥረት ማድረግ እንደሚገባው አስገንዝበዋል።
ቅዱስነታቸው ምን አሉ ?
" በሀገራችን ያለው ያለመረጋጋት በሕዝባችን አጠቃላይ ሥነ ልቡና በሀገሪቱ አንድነትና ዕድገት የሚያስከትለውን ጫና በቀላሉ የሚታይ አይሆንም፤ የሕዝቡ ሥነ ልቡና ከተጐዳ የነገው ዕድል ጤናማ ይሆናል ተብሎ አይታሰብም፡፡
ችግሩ እየታየ ያለው በዋናነት በሀገራችን ፖለቲከኞች በመሆኑ ነገሩ የተወሳሰበና የተራዘመ እንዲሆን አድርጎታል፤ በመሆኑም ይህ የርስ በርስ ግጭት ቆሞ ችግሮች በውይይትና በድርድር በመፍታት የወንድማማች እልቂት የሚያስቆም የሰላምና የዕርቅ ዕድል ቅድሚያ እንዲሰጠው ጉባኤው የበኩሉን ጥረት ማድረግ ይገባዋል፡፡
የነገው ትውልድ ልማታዊ ተስፋ እውን ሊሆን የሚችለው ሰላምና አንድነት ሲኖር ነውና መንግሥት፣ ተፎካካሪ ፖለቲከኞችና ነፍጥ ያነሡ ወገኖች ሁሉ ለሰላም መስፈንና ለልማት ዕድገት መረጋገጥ ሲባል ወደ መግባባት እንዲመጡ በእግዚአብሔር ስም አባታዊ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን፡፡ " ብለዋል።
(የቅዱስነታቸው ሙሉ መልዕክት ከላይ ተያይዟል)
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
@tikvahethiopia
ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ
ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ
ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት የቅዱስ ሲኖዶስ ዓቢይ ጉባኤ መጀመሩን አስመልክቶ መልዕክት አስተላልፈዋል።
በዚህም መልዕክታቸው የርስ በርስ ግጭቶች ቆመው ግጭቶች በውይይት እና በድርድር እንዲፈቱ ጉባኤው የበኩሉን ጥረት ማድረግ እንደሚገባው አስገንዝበዋል።
ቅዱስነታቸው ምን አሉ ?
" በሀገራችን ያለው ያለመረጋጋት በሕዝባችን አጠቃላይ ሥነ ልቡና በሀገሪቱ አንድነትና ዕድገት የሚያስከትለውን ጫና በቀላሉ የሚታይ አይሆንም፤ የሕዝቡ ሥነ ልቡና ከተጐዳ የነገው ዕድል ጤናማ ይሆናል ተብሎ አይታሰብም፡፡
ችግሩ እየታየ ያለው በዋናነት በሀገራችን ፖለቲከኞች በመሆኑ ነገሩ የተወሳሰበና የተራዘመ እንዲሆን አድርጎታል፤ በመሆኑም ይህ የርስ በርስ ግጭት ቆሞ ችግሮች በውይይትና በድርድር በመፍታት የወንድማማች እልቂት የሚያስቆም የሰላምና የዕርቅ ዕድል ቅድሚያ እንዲሰጠው ጉባኤው የበኩሉን ጥረት ማድረግ ይገባዋል፡፡
የነገው ትውልድ ልማታዊ ተስፋ እውን ሊሆን የሚችለው ሰላምና አንድነት ሲኖር ነውና መንግሥት፣ ተፎካካሪ ፖለቲከኞችና ነፍጥ ያነሡ ወገኖች ሁሉ ለሰላም መስፈንና ለልማት ዕድገት መረጋገጥ ሲባል ወደ መግባባት እንዲመጡ በእግዚአብሔር ስም አባታዊ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን፡፡ " ብለዋል።
(የቅዱስነታቸው ሙሉ መልዕክት ከላይ ተያይዟል)
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
@tikvahethiopia
4❤1.7K🙏149🕊72🥰35😭17👏13😢5😡5😱2💔1
#National_ID
የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ላይ ለመቀመጥ ብሔራዊ መታወቂያ (National ID) ቅድመ ሁኔታ ተደረገ።
የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት " ብሔራዊ መታወቂያ (National ID) ለፈተና ለመቀመጥ ቅድመ ሁኔታ ነው " ብሏል።
" ማንኛውም የ2018 ትምህርት ዘመን 12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ተፈታኝ ብሔራዊ መታወቂያ (National ID) ከፈተና ምዝገባ ቀድሞ ማውጣትና በእጁ መያዝ ይገባዋል " ሲል አሳውቋል።
" ብሔራዊ መታወቂያ (National ID) የሌለው ተማሪ ለፈተና መመዝገብ ሆነ በማንኛውም ሁኔታ መፈተን አይችልም " ሲል አስገንዝቧል።
ተማሪዎች የብሔራዊ መታወቂያ (National ID) ይዘው እንዲገኙ ፦
- የተማሪ ቤተሰብ
- መምህራን
- የትምህርት አመራሮች
- የሚዲያ አካላት ተገቢውን ድጋፍ እንዲያደርጉ ጥሪ ቀርቧል።
#National_ID
@tikvahethiopia
የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ላይ ለመቀመጥ ብሔራዊ መታወቂያ (National ID) ቅድመ ሁኔታ ተደረገ።
የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት " ብሔራዊ መታወቂያ (National ID) ለፈተና ለመቀመጥ ቅድመ ሁኔታ ነው " ብሏል።
" ማንኛውም የ2018 ትምህርት ዘመን 12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ተፈታኝ ብሔራዊ መታወቂያ (National ID) ከፈተና ምዝገባ ቀድሞ ማውጣትና በእጁ መያዝ ይገባዋል " ሲል አሳውቋል።
" ብሔራዊ መታወቂያ (National ID) የሌለው ተማሪ ለፈተና መመዝገብ ሆነ በማንኛውም ሁኔታ መፈተን አይችልም " ሲል አስገንዝቧል።
ተማሪዎች የብሔራዊ መታወቂያ (National ID) ይዘው እንዲገኙ ፦
- የተማሪ ቤተሰብ
- መምህራን
- የትምህርት አመራሮች
- የሚዲያ አካላት ተገቢውን ድጋፍ እንዲያደርጉ ጥሪ ቀርቧል።
#National_ID
@tikvahethiopia
❤604😡222😭43🤔39🙏22🕊20👏16💔15😱11😢9
#AddisAbaba
የዘረፋ ወንጀል ፈፅመው ለማምለጥ የሞከሩ ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ስር ውለው ምርመራ እየተጣራ እንደሚገኝ የአዲስ አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ ገለፀ፡፡
ተጠርጣሪዎቹ የፀጥታ አካል የሚመስል የደንብ ልብስ በመልበስ የዘረፋ ወንጀል ፈፅመው በቁጥጥር ስር የዋሉት ጥቅምት 11 ቀን 2018 ዓ/ም በቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 14 ጃክሮስ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ነው፡፡
አብርሃም አሸናፊ እና ዳግም ብርሃን የተባሉት ሁለት ተጠርጣሪዎች ወንጀሉን የፈፀሙት ረድኤት አህመድ በተባለች ግለሰብ ላይ እንደሆነ ፖሊስ ገልጿል።
የግል ተበዳይ በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ወረዳ 3 ልዩ ቦታው አባ ሳሙኤል መቶ አርባ ሰፈር ተብሎ በሚጠራው አካባቢ የሚገኝ የንግድ ሱቋን ዘግታ በመውጣት የሰሌዳ ቁጥር ኮድ 2B- 88595 አ.አ የሆነ ተሽከርካሪ እያሽከረከረች ስትጓዝ ከጥቂት ሜትሮች ጉዞ በኋላ እንዳስቆሟት ታውቋል፡፡
ተጠርጣሪዎቹ የግል ተበዳይን ከሾፌር መቀመጫ ላይ አስወርደው ከኋላ እንድትቀመጥ ካደረጉ በኋላ ተሽከርካሪውን ራሳቸው እያሽከረከሩ በሚፈልጉት አቅጣጫ እንደወሰዷት እና 500 ሺህ ብር ወደ አካውንታቸው እንድታስገባ እንዳስገደዷት የፖሊስ ምርመራ መዝገቡ ያስረዳል፡፡
የግል ተበዳይ የተጠየቀችውን ያህል ገንዘብ እንደሌላት ስትገልፅላቸው በወቅቱ በእጇ ይዛው የነበረውን 8ሺህ 700 ብር ጥሬ ገንዘብ እና ሁለት ሞባይል ስልኮችን ዘርፈው እሷን ካስወረዱ በኋላ መኪናውን እየነዱ በተቃራኒ አቅጣጫ ተጉዘውለማምለጥ ሲሞክሩ ከሌላ ተሽከርካሪ ጋር ተጋጭተው የትራፊክ አደጋ አድርሰዋል፡፡
ከአደጋው በኋላ ከተሽከርካሪው ወርደው በመሮጥ ሰው ቤት ገብተው ሊሰወሩ ቢሞክሩም ሳጅን ፋንታሁን አለምነህ በተባለ የአዲስ አበባ ፖሊስ ሞተረኛ ትራፊክ እና በህብረተሰቡ ትብብር ከነ ኤግዚቢቱ በቁጥጥር ስር ውለዋል፡፡
ግለሰቦቹ ከፀጥታ አካል ጋር ተመሳሳይነት ያለው የደንብ ልብስ ይልበሱ እንጂ የፀጥታ አካል እንዳልሆኑ መረጋገጡን እና ከወንጀሉ ጋር ተያይዞ ተጨማሪ ምርመራ እየተካሄደ መሆኑን የአዲስ አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ ገልጿል፡፡
የፀጥታ አካል በመምሰል እና ተመሳሳይነት ያለው የደንብ ልብስ በመልበስ ወንጀል የሚፈፅሙ ግለሰቦች ሊያጋጥሙ እንደሚችሉ ህብረተሰቡ ተገንዝቦ አጠራጣሪ ሁኔታዎች ሲያጋጥሙት ለሚመለከተው የፀጥታ አካል ጥቆማ እና መረጃ በመስጠት ትብብሩን እንዲያጠናክር ፖሊስ ጥሪውን አቅርቧል።
#AddisAbabPolice
@tikvahethiopia
የዘረፋ ወንጀል ፈፅመው ለማምለጥ የሞከሩ ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ስር ውለው ምርመራ እየተጣራ እንደሚገኝ የአዲስ አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ ገለፀ፡፡
ተጠርጣሪዎቹ የፀጥታ አካል የሚመስል የደንብ ልብስ በመልበስ የዘረፋ ወንጀል ፈፅመው በቁጥጥር ስር የዋሉት ጥቅምት 11 ቀን 2018 ዓ/ም በቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 14 ጃክሮስ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ነው፡፡
አብርሃም አሸናፊ እና ዳግም ብርሃን የተባሉት ሁለት ተጠርጣሪዎች ወንጀሉን የፈፀሙት ረድኤት አህመድ በተባለች ግለሰብ ላይ እንደሆነ ፖሊስ ገልጿል።
የግል ተበዳይ በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ወረዳ 3 ልዩ ቦታው አባ ሳሙኤል መቶ አርባ ሰፈር ተብሎ በሚጠራው አካባቢ የሚገኝ የንግድ ሱቋን ዘግታ በመውጣት የሰሌዳ ቁጥር ኮድ 2B- 88595 አ.አ የሆነ ተሽከርካሪ እያሽከረከረች ስትጓዝ ከጥቂት ሜትሮች ጉዞ በኋላ እንዳስቆሟት ታውቋል፡፡
ተጠርጣሪዎቹ የግል ተበዳይን ከሾፌር መቀመጫ ላይ አስወርደው ከኋላ እንድትቀመጥ ካደረጉ በኋላ ተሽከርካሪውን ራሳቸው እያሽከረከሩ በሚፈልጉት አቅጣጫ እንደወሰዷት እና 500 ሺህ ብር ወደ አካውንታቸው እንድታስገባ እንዳስገደዷት የፖሊስ ምርመራ መዝገቡ ያስረዳል፡፡
የግል ተበዳይ የተጠየቀችውን ያህል ገንዘብ እንደሌላት ስትገልፅላቸው በወቅቱ በእጇ ይዛው የነበረውን 8ሺህ 700 ብር ጥሬ ገንዘብ እና ሁለት ሞባይል ስልኮችን ዘርፈው እሷን ካስወረዱ በኋላ መኪናውን እየነዱ በተቃራኒ አቅጣጫ ተጉዘውለማምለጥ ሲሞክሩ ከሌላ ተሽከርካሪ ጋር ተጋጭተው የትራፊክ አደጋ አድርሰዋል፡፡
ከአደጋው በኋላ ከተሽከርካሪው ወርደው በመሮጥ ሰው ቤት ገብተው ሊሰወሩ ቢሞክሩም ሳጅን ፋንታሁን አለምነህ በተባለ የአዲስ አበባ ፖሊስ ሞተረኛ ትራፊክ እና በህብረተሰቡ ትብብር ከነ ኤግዚቢቱ በቁጥጥር ስር ውለዋል፡፡
ግለሰቦቹ ከፀጥታ አካል ጋር ተመሳሳይነት ያለው የደንብ ልብስ ይልበሱ እንጂ የፀጥታ አካል እንዳልሆኑ መረጋገጡን እና ከወንጀሉ ጋር ተያይዞ ተጨማሪ ምርመራ እየተካሄደ መሆኑን የአዲስ አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ ገልጿል፡፡
የፀጥታ አካል በመምሰል እና ተመሳሳይነት ያለው የደንብ ልብስ በመልበስ ወንጀል የሚፈፅሙ ግለሰቦች ሊያጋጥሙ እንደሚችሉ ህብረተሰቡ ተገንዝቦ አጠራጣሪ ሁኔታዎች ሲያጋጥሙት ለሚመለከተው የፀጥታ አካል ጥቆማ እና መረጃ በመስጠት ትብብሩን እንዲያጠናክር ፖሊስ ጥሪውን አቅርቧል።
#AddisAbabPolice
@tikvahethiopia
2❤2.41K👏615🙏160🤔81😱62💔44😭40😡35🕊22🥰18😢18