Telegram Web Link
ዘኔክሰስ፡-
☑️ ለተጠቃሚ ምቹ የሆኑ (keypad + touchscreen) በመጠቀም የተጠቃሚዎችን ልምድ ያቀላል
☑️ ለገጠራማ እና አነስተኛ የኤሌክትሪክ ኃይል ላላቸው አካባቢዎች ረጅም የባትሪ ዕድሜ አለው
☑️ በተገጠመ የቴሌስቶሬጅ (teleStorage) አማካኝነት የፋይል ማከማቻ ገደቦችን ያስወግዳል
☑️ እንደ ቴሌብር፣ የትምህርት ይዘት፣ ሚዲያዎች ያሉ ወሳኝ አፕሊኬሽኖችን ተጭኖባቸዋል
☑️ ከሁሉም በላይ ደግሞ የመጀመሪያ ጊዜ ተጠቃሚዎች በቀላሉ አገልግሎቶችን እንዲጠቀሙ ያስችላል

ዘኔክሰስ ስማርት ስልክ ላይ የሚገኙ ወሳኝ መተግበሪያዎችን በክላውድ አማካይነት በማቅረብ በኢትዮጵያ ብሎም በአፍሪካ የዲጂታል ተጠቃሚነት ተግዳሮት የሆነውን የዋጋ ውድነት በዘላቂነት በመፍታት የDigital-First ማኅበረሰቦችን ዕውን ለማድረግ ያስችላል።

ለበለጠ መረጃ፡ https://bit.ly/3Wb9TgX

#Ethiotelecom #Znexus #NextHorizon #telebirr #DigitalEthiopia #RealizingDigitalEthiopia
170👏14🙏6🥰1💔1
ሜሪ ጆይ ኢትዮጵያ የኩላሊት እጥበት ህክምና መስጫ ሀዋሳ ማዕከል ማስመረቁን ገልጾልናል።

በምረቃ ስነ-ስርዓቱ ላይ ተገኝተው የነበሩት የጤና ሚኒስቴር ሚንስትር ክብርት ዶ/ር መቅደስ ዳባ " የኩላሊት በሽታ ከዕድሜ መግፋት ጋር ተያይዞ የሚመጣ ነገር ግን ነው በአሁኑ ወቅት ግን ወጣቶች ጭምር በበሽታው በስፋት እየታየዙ እና ህይወታቸውን እያጡ ነው " ብለዋል።

ዶ/ር መቅደስ ዳባ ዲጂታል ኤክስ ሬይ(Digital x-ray) እንዲሁም ምርቃቱ ላይ የተገኙት የሲዳማ ክልል ፕሬዝዳንት አቶ ደስታ ሌዳሞ በክልሉ መንግስት እና ህዝብ ስም 10 ሚሊዮን ብር እና የሲዳማ ጤና ቢሮ ኃላፊ ዶ/ር ሰላማዊት መንገሻ ለሜሪጆይ ኢትዮጵያ ሀዋሳ ማዕከል የአምቡላንስ መኪና ድጋፍ አድርገዋል፡፡

ሌሎች የተደረጉ ድጋፎች ፦
• የሀዋሳ ከተማ ከንቲባ፦ 5 ሚሊዮን ብር
• ሲዳማ ልማት ማህበር፦ 300,000 ብር
• ያኔት ሆስፒታል፦ 500,000 ብር
• ይርጋለም ኮንስትራክሽን፦ 1 ሚሊዮን ብር
• ሀዋሳ ኢንዱስትሪ ፓርክ፦ 500,000 ብር

የሜሪ ጆይ ኢትዮጵያ መስራች እና ስራ አስኪያጅ የሆኑት ሲ/ር ዘቢደር ዘውዴም ለተደረገው ድጋፍ እንዲሁም በእዚህ ላይ ስማቸው ያልተገለፀ እና ለፕሮግራሙ መሳካት እገዛ ያደረጉትን በሙሉ አመስገነዋል፡፡

@tikvahethiopia
664🙏104👏53🥰12🤔7😱2🕊2😭1
" የ2018 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ከ9-12ኛ ክፍል ይሸፍናል " - ትምህርት ሚኒስቴር

ትምህርት ሚኒስቴር የ2018 ትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተናን በተመለከት ለሁሉም ክልሎች እና ለሁለቱ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮዎች እንዲሁም ለትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ትናንት ጥቅምት 10/2018 ዓ.ም ደብዳቤ ልኳል፡፡

የደብዳቤውን ትክክለኝነት ቲክቫህ ኢትዮጵያ አረጋግጧል።

በሚኒስቴሩ የስርዓተ ትምህርት ማበልጸጊያ መሪ ሥራ አስፈጻማ ቴዎድሮስ ሽዋርገጥ (ዶ/ር) የተፈረመው ደብዳቤው፤ የ2018 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ፈተና ከ9-12ኛ ክፍል እንደሚሸፍንና ተማሪዎች የተማሩትን ይዘቶች የሚፈተኑ መሆኑን ይገልጻል፡፡

ብሔራዊ ፈተናው ከ10ኛ እስከ 12ኛ ክፍሎች የአዲሱ ስርዓተ ትምህርት ይዘቶችን መሠረት ያደረገ እንደሚሆን ተጠቁሟል፡፡

በ2015 ዓ.ም የሙከራ ትምህርት ቤቶች 9ኛ ክፍልን በአዲሱ ስርዓተ ትምህርት፤ ሌሎቹ ደግሞ በቀድሞው ስርዓተ ትምህርት የተማሩ በመሆኑ ፈተናው ከሁለቱ ስርዓተ ትምህርቶች የጋራ የሆኑ ይዘቶች ተጣጥሞ የሚወጣ መሆኑ ተገልጿል፡፡

በአጠቃላይ ትምህርት ስርዓተ ትምህርት ሪፎርም መሠረት የሁለተኛ ደረጃ አዲሱ ስርዓተ ትምህርት በ2015 ዓ.ም የሙከራ ትግበራ በማካሔድ ከ2016 ዓ.ም ጀምሮ ወደ ሙሉ ትግበራ መገባቱ ይታወቃል፡፡

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ

Via @tikvahuniversity
427😭114😡47😱21🤔19👏17🙏13💔11🕊8😢6🥰5
‎" ከ6 ዓመታት በፊት የተጀመረዉ መንገድ አለመጠናቀቁ ለዘርፈ ብዙ ችግሮች ዳርጎናል " - የሸካ ዞን ነዋሪዎች

‎በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል የሸካ ዞን ነዋሪዎች ፥ የሸካ ዞንን ከተለያዩ ከተሞች የሚያገናኘው መንገድ ተጀምሮ ለረጅም ዘመናት አለመጠናቀቅ ለዘርፈ ብዙ ችግሮች እየዳረገን ነዉ ሲሉ ቅሬታቸዉን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አሰምተዋል።

‎ስማቸዉ እንዲገለፅ ያልፈለጉ ሁለት የሸካ ዞን ቴፒ ከተማ  ነዋሪዎች " ዞኑን ከጎሬ ቴፒ ማሻ፣ ከጪዳ ታርጫ፣ ዋቻ ጀሙ፣ ሚዛን ቴፒ  የሚያገናኘው መንገድ ከ6 እና 7 ዓመታት በፊት የተጀመረ ቢሆንም እስካሁን አልተጠናቀቀም " ብለዋል።

" በዚህም ምክንያት በንግድ እንቅስቃሴ፣ በሕዝብ ትራንስፖርትና በከተማዋ ሁለንተናዊ ዕድገት ላይ አሉታዊ ተፅዕኖ አሳርፏል " ሲሉ ተናግረዋል።

‎የአከባቢዉ ነዋሪዎች በተለይም የዞኑ አርሶአደሮች ዞኑ ካሽ ክሮፕ ከመሆኑም በላይ የቡና፣ የሻይ ቅጠል፣ የኮረሪማ፣ ዝንጅብል፣ እርድና ሌሎችም የግብርና ምርቶችን ለገበያ ለማቅረብ መቸገራቸዉን ገልፀዋል።

‎ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ሀሳባቸውን ያጋሩ ስማቸው እንዲገለፅ ያልፈለጉ አንድ የቴፒ ከተማ አመራር የሸካ ዞን የመንገድ ጉዳይ ከዞኑ መንግስት አቅም በላይ ነዉ ያሉ ሲሆን ከሕዝቡ ጩኸት በዘለለ አመራሩ በተደጋጋሚ በተለያዩ መድረኮች የሚያነሳው ቢሆንም የዞኑ መንግስት የማስፈፀም አቅም ስለሌለው ለዘመናት እልባት ሊያስገኝ አልቻለም ብለዋል።

ሌላ ስማቸዉ እንዲገለፅ ያልፈለጉ የሸካ ዞን የቀድሞ አመራር " ከመንገድ ችግሮች ጋር በተያያዘ ጥያቄዎች ሲበረቱ ማዘናጊያ እንቅስቃሴዎች የማድረግና ' ከኢትዮጵያ መንገዶች ባለሥልጣን ጋር እየተነጋገርን ነዉ ' የሚሉ ዜናዎችን በዞንና ወረዳ የሕዝብ ግንኙነት ገፆች ማሰራጨት ልማድ በዞኑ ተደጋግሞ ይስተዋላል " ሲሉ ገልጸዋል።

ሰሞኑንም ይኸው ድርጊት እየተስተዋለ መሆኑን አንስተዉ ይህ ተደጋጋሚ ድርጊት አሁን ላይ ሕዝቡን አስመርሯል ሲሉ ተናግረዋል።

" ‎አሁን ላይ ለሸካ ዞን የመንገድ መሰረተ ልማት ጉዳይ የህልውና ጉዳይ ነዉ " የሚሉት ቅሬታ አቅራቢዎቹ " በየትኛውም መመዘኛ የሕዝብ የመሠረተ ልማት ጥያቄ በአግባቡ ሊመለስ እንጂ ሌላ ትርጉም ሊሰጠው አይገባም " ብለዋል።

በማህበራዊ ሚዲያዎች የአከባቢውን የመንገድ ችግር ጥያቄ ያስተጋቡ ግለሰቦችን የማስፈራራት ሁኔታዎች በመንግስት አመራሮች ሲፈጸሙ እንደሚስተዋልም ጠቁመዋል።

‎ቲክቫህ ኢትዮጵያ በጉዳዩ ዙሪያ የሸካ ዞን መንገድ ልማትና ትራንስፖርት መምሪያ ኃላፊ አቶ ሀብታሙ ሀራን ለማነጋገር ያደረገዉ ሙከራ በተደጋጋሚ ቀጠሮ ምክንያት ሳይሳካ ቀርቷል። ሀሳባቸውን ማግኘት ስንችል የምናካትት ይሆናል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
ሀዋሳ
#TikvahEthiopiaFamilyHawassa

@tikvahethiopia
1812😡98🙏68😭66💔29🕊28👏16😢13🤔9
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
#SamiTech

አዳዲስ ላፕቶፕች ከአንድ ዓመት ዋስትና ጋር!!
@samcomptech

በጥራት፣ በብራንድና በባትሪ ቆይታ አስተማማኝ የሆኑ የተለያዩ ሞዴል ላፕቶፖች በፈለጉት ስክሪን መጠን፣ ኮር አይ እና ጀነሬሽን አሉን።

ለቢሮዎች፣ ለተማሪዎች፣ ለዲዛይን ባለሙያዎች፣ ለጌመሮች ወ.ዘ.ተ. ሁሉም አሉን።

የዕቃዎች ዋጋ፣ ዓይነት እና አድራሻ ለማግኘት 👉 @samcomptech

@sww2844
0928442662 / 0940141114

Telgram : https://www.tg-me.com/samcomptech
126🙏7
ለተስካር ሊውል የነበረውን 3.2 ሚሊዮን ብር ለተፈናቃይና ለተቸገሩ ወገኖች የለገሱት ቤተሰቦች !

ተወልደ ግደይ ገብረዋህድ ቤተሰቦቻቸው በትግራይ ሰሜን ምዕራብ ዞን የእንዳስላሰ-ሽረ ከተማ ነዋሪ ናቸው።

ቤተሰቦቹ ለነፍስሄር ወላጅ እናታቸውና ወንድማቸው ለተስካር ሊውል የተዘጋጀው 3.2 ሚሊዮን ብር በከተማዋ በከፋ ሁኔታ ኑሮዋቸው በመግፋት ላይ ለሚገኙት ተፈናቃዮችና የተቸገሩ ወገኖች ለግሰዋል።

ጥቅምት 10/2018 ዓ.ም በተከናወነው የልገሳ ስነ-ስርዓት ፦ 2 ሚሊዮን ብር በከተማዋ ለሚገኙ ተፈናቃዮች ሲከፋፈል ፤ የተቀረው በስራ ለተሰማሩት የተሰው ቤተሰቦች ማጠናከሪያ ለአረጋውያን ማህበር፣ ለህፃናት ማሳደጊያ ማእከልና ለ6 ገዳማትና አብያተ ቤተክርስትያን መርጃ ተከፋፍሏል።

" ለጋሽ ቤተሰቦች ገንዘቡ ለተስካር ከማባከን በችግር ለተጎዱ ወገኖች ማዋል ምድራዊና ሰማያዊ ሀሴት ያስገኛል " በማለት መፈፀማቸውንና ሌሎችም የነሱ ዳና መከተል እንደሚገባቸው ገልፀዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
መቐለ
#TikvahEthiopiaFamilyMekelle

@tikvahethiopia      
1👏1.62K588🙏113🤔36🥰19🕊13😡5😱4😢3
2025/10/23 06:59:48
Back to Top
HTML Embed Code: