Telegram Web Link
TIKVAH-ETHIOPIA
አዲሱ የተሽከርካሪ ሰሌዳ የኢትዮጵያ ሰንደቅ አላማ ለምን አልተካተተበትም ? (ቲክቫህ ኢትዮጵያ - Tikvah Ethiopia) አዲሱ የተሽከርካሪ መለያ ሰሌዳ ቁጥር (ታርጋ) የኢትዮጵያ አለም አቀፍ መለያ ኮድ "ETH" ፣ የኢትዮጵያ ካርታ ፣ ጦር እና ጋሻ ወይም የአድዋ ምልክት በግልጽ እና በአንጸባራቂ መብራት በመታገዝ በሚታይ  መልኩ ቢኖረውም የኢትዮጵያ ሰንደቅ አላማ ግን አልተካተተበትም። የኢትዮጵያን…
አዲሱን የተሽከርካሪ መለያ ሰሌዳ (ታርጋ) ለመቀየር ስንት ነው የሚከፈለው ?

አዲሱ የተሽከርካሪ መለያ ሰሌዳ (ታርጋ) በሚቀየርበት ጊዜ ወጪውን እራሳቸው የተሽከርካሪ ባለንብረቶች እንደሚሸፍኑት የትራንስፖርት እና ሎጅስቲክስ ሚኒስቴር ማሳወቁ ይታወሳል።

ክፍያውን በተመለከተ ግን እስካሁን ምን ያህል ይሁን የሚለው ተቆርጦ አልተቀመጠም ሲል ሚኒስቴሩ ገልጿል።

በሚኒስቴሩ አማካሪ የሆኑት የድልማግስት ኢብራሂም ለፋና ቴሌቪዥን በሰጡት ቃል " እስካሁን ክፍያው ተቆርጦ አልተቀመጠም። አሁን እየተሰራ ያለው ሲስተም የመዘርጋት ነው። ይህ ነው መጀመሪያ የሚጠናቀቀው " ብለዋል።

የተሽከርካሪ ባለንብረቶች እስከዛው የተሽከርካሪውን ሙሉ መረጃ አደራጅተው መጠበቅ እንዳለባቸው ጠቁመዋል።

ታርጋ በመቀየሩ ሂደት የምርመራ ማዕከላት እንደሚኖሩና ተሽከርካሪዎቹ ሄደው መመርመር እንዳለባቸው ፤ ተመርምረውም ህጋዊ ሰነዳቸውን ይዘው በሚወጣላቸው የጊዜ ሰሌዳ መሰረት ቀጥታ ሰሌዳቸውን እንደሚቀይሩ አስረድተዋል።

#ታርጋ #ኢትዮጵያ

@tikvahethiopia
637😡177🤔37😭32🕊24👏22😱9💔7😢4
TIKVAH-ETHIOPIA
አዲሱን የተሽከርካሪ መለያ ሰሌዳ (ታርጋ) ለመቀየር ስንት ነው የሚከፈለው ? አዲሱ የተሽከርካሪ መለያ ሰሌዳ (ታርጋ) በሚቀየርበት ጊዜ ወጪውን እራሳቸው የተሽከርካሪ ባለንብረቶች እንደሚሸፍኑት የትራንስፖርት እና ሎጅስቲክስ ሚኒስቴር ማሳወቁ ይታወሳል። ክፍያውን በተመለከተ ግን እስካሁን ምን ያህል ይሁን የሚለው ተቆርጦ አልተቀመጠም ሲል ሚኒስቴሩ ገልጿል። በሚኒስቴሩ አማካሪ የሆኑት የድልማግስት ኢብራሂም…
በአዲሱ ታርጋ ላይ የሚቀመጡት 3ቱ ፊደላት ምንድናቸው ? የታርጋ ቁጥሩስ እንዴት ነው የሚቀጥለው ?

በትራንስፖርት እና ሎጅስቲክስ ሚኒስቴር አማካሪ አቶ የድልማግስት ኢብራሂም (ለኤፍኤምሲ)  ፦

" ሶስቱ ፊደላት የተቀመጡት ከዚህ ቀደም ከነበሩት ከቁጥሮች አያያዝ አንጻር ችግሮች አጋጥመውን ብዙ የተሽከርካሪ ቁጥርን ሰሌዳችን ሊመዘግብ ባለመቻሉ ምክንያት ነው።

ከዚህ ቀደም የነበረው ሰሌዳ 5 ነበር ቁጥሩ ከፊት ለፊት አልፋ ቤት አለው ያ አጠቃላይ ሆኖ 9 ሚሊዮን ሰሌዳዎችን ነው ሊይዝልን የሚችለው። አሁን 1.6 ሚሊዮን ሰሌዳዎችን መዝግበናል ግን እንለጥጠው ብንል 9 ሚሊዮን ሰሌዳ ብቻ ነው የሚችለው።

አሁን በመጣው ታርጋ አልፋቤቱና አራቱ ዲጅት እስከ 121 ሚሊዮን ተሽከርካሪ ድረስ መመዝገብ ይቻላል።

ለምሳሌ ፦ AAA0000 የሚለውን ታርጋ እንውሰድ። በቀኝ በኩል ያለችው ሶስተኛዋ A የምትቀየረው ቁጥሩ 9999 (AAA9999) በሚሆንበት ጊዜ ነው። ልክ AAA9999 ሲሆን AAA የነበረው ሰሌዳ ወደ AAB ይሄዳል። ልክ AAB ሲሆን 0001 ብሎ (AAB0001) ይቀጥላል። አሁንም AAB9999 ሲደርስ B ወደ C ትሄዳለች ማለትም AAC0001 ይሆናል። "

#ማሳያ

የአዲሱ ታርጋ ቁጥር የሚሄደው በዚህ መልኩ ነው።

AAA0000
⬇️
AAA9999
⬇️
AAB0001
⬇️
AAB9999
⬇️
AAC0001

... እያለ ይቀጥላል።

#TikvahEthiopiaFamilyAA
#ቲክቫህ_ኢትዮጵያ

@tikvahethiopia
2.69K👏318😡162🤔96🙏65🕊41💔40😭29🥰16😢16😱15
#AbayBank

ዓባይ ባንክ የ15ኛ ዓመት የምስረታ በዓሉን ምክንያት በማድረግ ከኢትዮጵያ ደም ባንክና የሕብረ ሕዋስ አገልግሎት ጋር በመተባበር በሀገር አቀፍ ደረጃ የደም ልገሳ መርሀ ግብር ማካሄድ ጀምሯል።

በደም ልገሳ ማስጀመሪያ መርሀ ግብሩ ላይ ንግግር ያደረጉት የዓባይ ባንክ የስትራቴጂ ዋና መኮንን አቶ ወንድይፍራው ታደስ በዛሬው እለት በአዲስ አበባ ከተማ ውስጥ በ6 ቅርንጫፎች ደም እየተለገሰ መሆኑን ገልጸዋል።

"በቀጣይ ሰኞም ደም ልገሳው ይቀጥላል፣ ወደ 90 የሚሆኑ ሰዎችም ደም ይለግሳሉ የሚል እቅድ አለን። በሀገር አቀፍ ደረጃ ከ600 በላይ ለጋሾች ደም ይለግሳሉ ብለን እናስባለን" ሲሉ ተናግረዋል።

አክለው በሁሉም ቅርንጫፍቻችን ከሚገኙ ሠራተኞቻችን፣ ደንበኞቻችንና ከመላው የባንካችን ቤተሰቦች ከተውጣጡ ከ1ሺህ በላይ በጎ ፈቃደኛ ደም ለጋሾችን በማንቀሳቀስ ለሕይወት አድን ዓላማ ቀጥተኛ አስተዋጽዖ በማድረጋችን ደስተኞች ነን ብለዋል፡፡

"ይህ የበጎ አድራጎት ሥራ የ15 ዓመት ጉዟችንን በድምቀት ለማክበርና ለማኅበራዊ ኃላፊነት ያለንን ዘላቂ ቁርጠኝነት ያጠናክራል" ሲሉ ነው የተናገሩት።

በዚህ መርሐግብር ላይ የተገኙት በኢትዮጵያ ደም ባንክና የሕብረ ሕዋስ አገልግሎት ውስጥ የደም ለጋሾች ተወካይ ደስክ ሃላፊ  ሙላት በቀለ በበኩላቸው አባይ ባንክ በመላዊ ሀገሪቱ በሚገኙ ቅርንጫፎቹ የደም ልገሳ ፕሮግራም በማካሄድ የወገንን ህይወት እየታደገ ነው ሲሉ ተናግረዋል።

በባለፉት በዓላት ወቅት ከፍተኛ የሆነ የደም እጥረት ተከስቶ እንደነበር ያስታወሱት ሃላፊው "አባይ ባንክ እጥረቱን በመገንዘብ በዛሬው እለት ሰራተኞቹ ደም እንድለግሱ እያደረገ ነው። በሚተካ ደም የማይተካውን የሰው ልጅ ህይወት ለማዳን ፕሮግራሙን በማዘጋጀቱም ደስ ብሎናል" ሲሉ ነው የገለጹት።

አባይ ባንክ ከ71 ቢሊዮን በላይ ተቀማጭ ገንዘብ፣ 7 ቢሊዮን ብር የተከፈለ ካፒታል እንዲሁም ጠቅላላ ሀብቱ 91 ቢሊዮን ብር መድረሱም ተነስቷል።

#ዓባይባንክ
Proud to D🩸nate
499🙏32😡8👏6🥰2
#YonatanBTFurniture

የቢሮዎን እቃዎች ለመቀየር አስበዋል?

ዮናታን ቢቲ ፈርኒቸር ለቢሮዎ ግርማሞገስ፣ ምቾት፣ ጥንካሬ እና ዘመናዊነትን የሚያላብሱ የቢሮ ወንበሮች፣ ጠረጴዛዎች እንዲሁም ለቢሮዎ ያስፈልገኛል ብለው የሚያስቧቸውን ምርቶች በፈለጉት አማራጭ እና ዲዛይን አቅርበንሎታል።

ይምጡ እና ይጎብኙን!

📍አድራሻችን

1. ፒያሳ እሪ በከንቱ ቢቲ ታወር
2. ከዊንጌት አደባባይ አለፍ ብሎ ከአቢሲኒያ ባንክ ፊትለፊት
3. ከሲኤምሲ አደባባይ ወደ አያት መንገድ መሪ ሳይደርስ (ዘመን ባንክ አጠገብ)

☎️ ይደውሉልን
+251957868686/ +251995272727/ +251993828282

Telegram/Facebook/Instagram/TikTok

#OfficeFurniture #ConferenceTables #OfficeTable
144🙏4👏2🕊1
#SafaricomEthiopia

ቀጣይ የ1 ሚሊየን ዕደለኛ ማን ይሆን! 2ቀን ብቻ ቀረው! 🏆💚 ዛሬዉኑ የበሽ ጥቅልን ይግዙ፤ ሚሊየነር የመሆን እድሎን ያስፉ!

📲 የM-PESA መተግበሪያን አሁኑኑ ያውርዱ፡
https://onelink.to/ewsb22

የቴሌግራም ቦታችን: https://www.tg-me.com/official_safaricomet_bot

ወደ *777*0# ይደውሉ ወይም በM-PESA የበሽ ጥቅል ይግዙ!

#MPESASafaricom
#furtheraheadtogether
#Besh
71🙏10😡7🕊2👏1
የሰዎችን_ከቦታ_ቦታ_የመዘዋወር_ነጻነት_በተሟላ_ሁኔታ_መፈጸም_የሚያስችሉ_እርምጃዎች_በአፋጣኝ_ሊወሰዱ.pdf
271.1 KB
የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን ን የሰዎችን ከቦታ ቦታ የመዘዋወር ነጻነት በተሟላ ሁኔታ መፈጸም የሚያስችሉ እርምጃዎች በአፋጣኝ እንዲወሰዱ አሳሰበ።

በተለያዩ ክልሎች በመንገድ ላይ ለሚደርሱ ጥቃቶች ፣ እገታዎች፣ የንብረት ዘረፋዎች እና ውድመቶች የሰዎች ከቦታ ቦታ የመዘዋወር ነጻነት አደጋ ላይ እንደወደቀ ገልጿል።

መንግሥት በተለያዩ ቦታዎች የተፈጸሙ የሰብአዊ መብቶች ጥሰቶች ላይ የተሟላ ማጣራት በማድረግ ተጠያቂነትን ሊያረጋግጥ እንዲሁም በድርጊቶቹ ተጎጂ ለሆኑ ሰዎች ፍትሕ ሊያሰፍን እንደሚገባ አሳስቧል።

(ኮሚሽኑ የላከው መግለጫ ከላይ ተያይዟል)

@tikvahethiopia
309👏52😢13🕊13🥰10😭6🙏2
“ጠዋት በተኙበት ነው እናትና አባቴን የገደሉብኝ፤ ታናሽ እህታችንም ታግታለች” - የሟቾች ልጅ

➡️ “ አራት ሰዎች ተገድለዋል፤ ስድስት ደግሞ ታግተዋል፣ 81 የግለሰብ ከብቶች ተወስደዋል ” ባለስልጣን

በኦሮሚያ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን ወረጃርሶ ወረዳ ጊርሚጎባ ቀበሌ ታጣቂዎች በንጹሐን ላይ የሞትና እገታ፣ በንብረት ላይ የውድመት ጥቃት ማድረሳቸውን ነዋሪዎችና ባለስልጣን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገለጹ፡፡

ነዋሪዎቹ፣ መስከረም 29 ቀን 2018 ዓ/ም፣ “ህዝቡ በተኛበት ንጋት 11 ሰዓት አካባቢ ተኩስ ከፍተው አራት ሰዎች ገድለዋል፤ ስድስት ሰዎች አግተዋል፤ ቤትም አቃጥለዋል” ብለዋል፡፡

“ወደ 100 ከብቶች” እንደተነዱና “ወደ 100 ቤቶች” እንደተቃጠሉ፣ ጥቃቱን ያደረሰው "ሸኔ" እንደሆነ ገልጸው፣ “ከሦስት ወራት በፊትም ተራራ ላይ መሳሪያ አጥምደው አጋምሳ መንደርን አቃጥለው ዘጠኝ ሰዎች ገድለዋል” ሲሉም አስታውሰዋል።

ቃላቸውን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ የሰጡ የሁለት ሟቾች ልጅ፣  "ጠዋት 12 ሰዓት አካባቢ በተኙበት ነው እናትና አባቴን የገደሉብኝ፤ ታናሽ እህታችንም ታግታለች፡፡ ከብቶችንም ወስደዋል " ብለዋል።

“አባቴ ከአመት በላይ ታሞ ተኝቶ ነበር፤ እግሩ ተዘርግቶ መሄድ አይችልም በበሽታ ምክንያት፤ እናቴ ደግሞ ሌላው ሰው ሲሸሽ 'ባለቤቴን ትቼ አልሄድም' ብላ እዚያው ሲያገኟቸው ገደሏቸው " ሲሉ ገልጸዋል።

" ሸሽቶ ስለነበር በሰዓቱ ብዙ ሰው የለም ነበር፤ ባለው ትንሽ ሰው በአንድ ጉድጓድ ነው የተቀሩት፡፡ እኔ የሟቾች ልጅ ነኝ። መንግስት እንዲህ ያለጥቃት እንዲቆም መስራትና ለተጎጂዎች መድረስ አለበት ” ሲሉ አስገንዝሸዋል።

ስለጥቃቱ ማረጋገጫ የተጠየቅናቸው አንድ የቀበሌው ከፍተኛ አመራር በበኩላቸው፣ “አራት ሰዎች ገድለዋል፤ ስድስት ታግተዋል፣ 81 የግለሰብ ከብቶች ተወስደዋል። በአካባቢው ነበርኩ በርካታ ጥይቶች ተተኩሰውብናል፡፡ 50 የሚጠጉ ቤቶች ተቃጥለዋል፡፡ አንድ የህዝብ ወፍጮ ተቃጥሏል” ሲሉ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል።

ቀበሌውን ከወረዳው በስተደቡብ “አብዛኛዎቹ በሸኔ ታጣቂዎች የተያዙ” ቀበሌዎች እንደሚያዋስኑት ገልጸው፣ “ከዚህም በፊትም ከአንዴም ሁለት ጊዜ ነዋሪውን ለማጥቃት ተሞክሯል፡፡ መስከረም 29/2018 ዓ/ም የደረሰው ጥቃት ግን ከምንም በላይ የከፋ ነበር” ነው ያሉት፡፡

እኝሁ አካል፣ ጥቃቱ ከተፈጸመት “ከንጋት ከ11 ሰዓት ጀምሮ ለሚመለከተው አካል ደውለናል፤ ግን ጎሃጽዮን ታጣቂዎች መኪና ራሱ እንዳይወጣ የሚያደርጉበት በመሆኑ መከላከያ አልደረሰልንም” ነው ያሉት፡፡

“ከዚህ በፊት ጥቃት ተፈጽሞ በአንድ ቀን ስምንት ሰዎች ተገድለዋል፡፡ 47 ቤቶች ተቃጥለዋል፤ በርካታ ሰዎችም ታግተው ገንዘብ ከፍለው የተመለሱ አሉ” ሲሉ ያስታወሱት አመራሩ፣ ጥቃቱ እየተደጋገመ መሆኑን አልደበቁም፡፡

ቀሪ ነዋሪዎች ዳግም እንዳይጠቁ ምን እየተሰራ እንደሆነ ሲያስረዱ ደግሞ፣ መከላከያ በቋሚነት በአካባቢው እንዲመደብ እንዳሳሰቡና ህዝቡ ራሱን እንዲከላከል አቅጣጫ እንደተቀመጠ ገልጸዋል፡፡

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
😭900648😡69💔31😢28🕊26🙏20🤔7😱4🥰3
#SocialMedia

የአሜሪካዋ ኒውዮርክ ከተማ ታላላቅ የሚባሉ የማህበራዊ ሚዲያዎችን ህፃናትን ሱስ በማስያዝ ከሳለች።

ከተማዋ ፌስቡክ፣ ጎግል፣ ስናፕቻትና እንደ ቲክቶክ ያሉ የማህበራዊ ሚዲያዎች ህፃናትን ሱስ በማስያዝ አዕምሯዊ ጤናቸውን እየጎዱ ነው በማለት 327 ገፅ ያለው ክስ በፍርድ ቤት አቅርባለች።

በኒውዮርክ ከተማ ከሚኖሩ 8 ሚሊየን ሰዎች ውስጥ 1.8 ሚሊየኑ ህፃናት ናቸው።

የጎግል ቃለ አቀባይ በዩቲዩብ ላይ የተከፈተው ክስ ትክክል አይደለም ሲሉ ዩቲዩብ ሰዎች ቪዲዮ የሚያዩበት እንጂ ከጓደኞቻቸው ጋር የሚገናኙበት የማህበራዊ ሚዲያ አይደለም ብለዋል።

በክሱ 77.3% የሚሆኑት በኒውዮርክ የሚኖሩ የሁለተኛ ደረጃ ተማሪዎች በቀን ከሶስት ሰዓት በላይ በስክሪን ላይ እንደሚያጠፉ ተገልፆ ይህም የተማሪዎቹን ጤና እየጎዳ ነው ተብሏል።

ከዚሁ ከማህበራዊ ሚዲያ ጋር በተያያዘ ዜና ዴንማርክ ከ15 ዓመት በታች ያሉ ህፃናት ማህበራዊ ሚዲያዎችን እንዳይጠቀሙ እገዳ ለማስቀመጥ እየሰራች ነው።

የዴንማርክ ጠቅላይ ሚኒስትር ሜት ፍሬድሪክሰን ማህበራዊ ሚዲያዎች" የልጆቻችንን ህፃንነት እየሰረቁ" ነው ብለዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትሯ የሃገሪቱ ህግ አውጪዎች ከ15 አመት በታች ያሉ ህፃናት ማህበራዊ ሚዲያን እንዳይጠቀሙ እንዲከለክሉ ጠይቀዋል።

በአውሮፓ ህብረት ሃገራት ህፃናት 13 አመት ሳይሞላቸው የማህበራዊ ሚዲያ አካውንት መክፈት እንደማይችሉ ቢቀመጥም ጠቅላይ ሚኒስትሯ 94 በመቶ የዴንማርክ ህፃናት እዚህ ዕድሜ ላይ ሳይደርሱ ይከፍታሉ ብለዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትሯ " ህፃናት ማህበራዊ ሚዲያ ላይ ማየት የሌለባቸውን ነገሮች ያያሉ" ያሉ ሲሆን ይህም ጭንቀትና ድብርትን ጨምሮ ሌሎቸ መዘዞችን እያዋለደ ነው ብለዋል።

ዘገባዎቹ የተገኙት ከዩሮ ኒውስና ከአሌጄዘራ ነው።

Via @TikvahethMagazine
1.18K👏173🙏48😭21😡19🤔17🕊15😢8😱5💔2
#Afar #Tigray

ዛሬ በትግራይ እና አፋር ክልል የተለያዩ አካባቢዎች ተደጋግሞ የተሰማ የመሬት መንቀጥቀጥ ንዝረት ተከስቷል።

የአሜሪካ ጂኦሎጂካል ሰርቬይ ይፋ ባደረገው መረጃ በተደጋጋሚ የመሬት መንቀጥቀጥ ንዝረት ተሰምቷል።

የመጀመሪያው ከመቐለ ሰሜን ምስራቅ 47 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ 4.2 በሬክተር ስኬል የተለካ የመሬት መንቀጥቀጥ ተከስቶ ነበር ፤ ንዝረቱ በተለያዩ የትግራይ እና አፋር አካባቢዎች ተሰምቷል።

ከዚህ ቀጥሎ ከመቐለ ሰሜን ምስራቅ 58 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ 5.3 በሬክተር ስኬል የተለካ የመሬት መንቀጥቀጥ ተከስቶ ንዝረቱ መቐለን ጨምሮ በርካታ ከተሞች ተሰምቷል።

ቅርብ ሰዓት ደግሞ በሬክተር ስኬል 5.6 የተለካ የመሬት መንቀጥቀጥ ከመቐለ ሰሜን ምስራቅ 53 ኪሎ ሜትር ላይ ተከስቶ ነበር።

@tikvahethiopia
2😢600516🙏128🕊63😭57💔28😱26🥰12🤔10😡6👏2
2025/10/21 22:14:54
Back to Top
HTML Embed Code: