TIKVAH-ETHIOPIA
#Tigray በጦርነት ላይ ተሳታፊ የነበሩ የትግራይ ኃይል አባላት በዛሬው ቀንና በአሁኑ ሰዓት በመቐለ ዋና ዋና መንገዶች የመብት ጥያቄ አንስተው ሰላማዊ ሰልፍ በማካሄድ ላይ ይገኛሉ። አባላቱ ከሚያሰሙት መፈክር የደመወዝ ጭማሪ እና የጥቅማ ጥቅም ጥያቄ ጎልቶ ተደምጧል። ሰላማዊ ሰልፈኞቹ በአሁኑ ሰዓት ወደ ትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደር የፕሬዜዳንት ፅ/ቤት በማምራት ላይ ይገኛሉ። ቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ…
#Update
" ሰላምን እንሻለን ! " - የትግራይ ኃይል አባላት
➡️ " የኛን ጥያቄ መመለስ ከማይችል አመራር የሌላው ህዝብ ጥያቄ ሊመልስ አይችልም ! "
የትግራይ ኃይል አባላት ዛሬ ሰኞ ጥቅምት 3/2018 ዓ.ም ከጥዋቱ 2:30 ጀምረው የመብት ጥያቄ አንስተው በከተማዋ ዋና ዋና መንገዶች ሰላማዊ ሰልፍ አካሂደዋል።
ሰልፈኛቹ ቁጣን ባዘለ ድምፅ ፦
- " የደመወዝና ጥቅማጥቅም ጥያቄያችን ይመለስ ! "
- " የሰራዊት ጥያቄ የማይመልስ አመራር የሌላው ህዝብ ጥያቄ መመለስ አይችልም ! "
- " የሰራዊት ድምፅ ይሰማ ! "
- " ሰላምን እንሻለን ! "
- " ክብር ለሰራዊትና ለተሰው ቤተሰብ አባላት ! "
የሚሉና ሌሎች መፈክሮች አሰምተዋል።
ሰላማዊ ሰልፈኞቹ መፈክራቸው እያሰሙ ወደ ትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደር የፕሬዜዳንት ፅህፈት ቢያመሩም ፕሬዜዳንቱ ማግኘት አልቻሉም።
ጥያቄያቸው ስምቶ መልስ የሚሰጥ ሃላፊ በማጣታቸው የተቆጡት ሰልፈኛቹ ከቀኑ 7:00 እስከ 11:00 ከመቐለ ወደ አሉላ አባነጋ አውሮፕላን ማረፍያ የሚወስደው ዋናው የመኪና መንገድ በድንጋይና በአካል ዘግተውት ውለዋል።
ይህንን መረጃ ከተዘጋጀበት ጥቂት ደቂቃዎች በፊት የሰላማዊ ሰልፈኞቹ ተወካዮቹ ከጊዚያዊ አስተዳደሩ ከፍተኛ አመራሮች ጋር ለውይይት መቀመጣቸው ተከትሎ የተዘጋው መንገድ መከፈቱን ቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ አረጋግጧል።
በተጀመረው ውይይት የጊዚያዊ አስተዳደሩ ፕሬዜዳንት ታደሰ ወረደ (ሌ/ጀ) መገኘታቸውና አለመገኘታቸው ማረጋገጥ አልቻልንም።
የውይይቱን ውጤት ተከታትለን እናቀርባለን።
#Update - በአሁኑ ሰዓት የሰላማዊ ሰልፈኞቹ ተወካዮች የጊዚያዊ አስተዳደሩ ፕሬዜዳንት ታደሰ ወረደ (ሌ/ጀ) ከሚገኙባቸው ከፍተኛ ወታደራዊና የስቪል አመራሮች በመነጋገር ላይ ይገኛሉ።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
መቐለ
#TikvahEthiopiaFamilyMekelle
@tikvahethiopia
" ሰላምን እንሻለን ! " - የትግራይ ኃይል አባላት
➡️ " የኛን ጥያቄ መመለስ ከማይችል አመራር የሌላው ህዝብ ጥያቄ ሊመልስ አይችልም ! "
የትግራይ ኃይል አባላት ዛሬ ሰኞ ጥቅምት 3/2018 ዓ.ም ከጥዋቱ 2:30 ጀምረው የመብት ጥያቄ አንስተው በከተማዋ ዋና ዋና መንገዶች ሰላማዊ ሰልፍ አካሂደዋል።
ሰልፈኛቹ ቁጣን ባዘለ ድምፅ ፦
- " የደመወዝና ጥቅማጥቅም ጥያቄያችን ይመለስ ! "
- " የሰራዊት ጥያቄ የማይመልስ አመራር የሌላው ህዝብ ጥያቄ መመለስ አይችልም ! "
- " የሰራዊት ድምፅ ይሰማ ! "
- " ሰላምን እንሻለን ! "
- " ክብር ለሰራዊትና ለተሰው ቤተሰብ አባላት ! "
የሚሉና ሌሎች መፈክሮች አሰምተዋል።
ሰላማዊ ሰልፈኞቹ መፈክራቸው እያሰሙ ወደ ትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደር የፕሬዜዳንት ፅህፈት ቢያመሩም ፕሬዜዳንቱ ማግኘት አልቻሉም።
ጥያቄያቸው ስምቶ መልስ የሚሰጥ ሃላፊ በማጣታቸው የተቆጡት ሰልፈኛቹ ከቀኑ 7:00 እስከ 11:00 ከመቐለ ወደ አሉላ አባነጋ አውሮፕላን ማረፍያ የሚወስደው ዋናው የመኪና መንገድ በድንጋይና በአካል ዘግተውት ውለዋል።
ይህንን መረጃ ከተዘጋጀበት ጥቂት ደቂቃዎች በፊት የሰላማዊ ሰልፈኞቹ ተወካዮቹ ከጊዚያዊ አስተዳደሩ ከፍተኛ አመራሮች ጋር ለውይይት መቀመጣቸው ተከትሎ የተዘጋው መንገድ መከፈቱን ቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ አረጋግጧል።
በተጀመረው ውይይት የጊዚያዊ አስተዳደሩ ፕሬዜዳንት ታደሰ ወረደ (ሌ/ጀ) መገኘታቸውና አለመገኘታቸው ማረጋገጥ አልቻልንም።
የውይይቱን ውጤት ተከታትለን እናቀርባለን።
#Update - በአሁኑ ሰዓት የሰላማዊ ሰልፈኞቹ ተወካዮች የጊዚያዊ አስተዳደሩ ፕሬዜዳንት ታደሰ ወረደ (ሌ/ጀ) ከሚገኙባቸው ከፍተኛ ወታደራዊና የስቪል አመራሮች በመነጋገር ላይ ይገኛሉ።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
መቐለ
#TikvahEthiopiaFamilyMekelle
@tikvahethiopia
❤1.09K🕊130🙏34😡28🤔22😭17👏15😱10😢9💔8🥰7
በአፍሪካዊቷ ሀገር #ማዳጋስካር 🇲🇬 የሆነው ምንድነው ?
(በአጭሩ)
- ከ15 ቀን ገደማ በፊት የማዳጋስካር ወጣቶች የመሩት ተቃውሞ ይቀሰቀሳል። ይኸው ተቃውሞው በዋና ከተማዋ አንታናናሪቮ ካለ የኃይል መቆራረጥ እና የውሃ እጥረት ጋር የሚያያዝ ነበር። የወጣቶቹ ተቃውሞ ' Gen Z Madagascar ' የሚል ስያሜ ነበረው።
- በኃላ የወጣቶቹ ተቃውሞ ቁጣ የታከለበትና መልካም አስተዳደር እንዲሰፍን፣ ተጠያቂነት እንዲረጋገጥ፣ ሙስና እንዲያበቃ ፣ የዜጎች ህይወት እንዲሻሻል ወደመጠየቅ ተሸጋገረ።
- የመንግሥት ምላሽ የነበረው ሰልፈኞችን በአስለቃሽ ጭስ መበተን፣ የሰዓት እላፊ መጣል፣ ሰልፈኞች ላይ መተኮስ ሆነ። በተቃውሞ 22 ሰዎች ሲገደሉ ሌሎች በርካቶች ተጎድተዋል።
- የሀገሪቱ ፕሬዚደንት አንድሪ ራጆኤሊና መንግስታቸውን በትነው ወታደራዊ ጠቅላይ ሚኒስትር ሾሙ፣ ጄነራል ሩፊን ፎርቱናት የሚባሉ። ግን አለመረጋጋቱ ለሚቆም አልቻለም።
- አንድ የማዳጋስካር የጦር ክንፍ ተቃዋሚዎችን ተቀላቀቀለ። ከፕሬዜዳንቱ ትእዛዝ ማቀበል አቆመ። ይኸው ኃይል ወደ ተቃዋሚዎች ምንም እንዳይተኮስ አዘዘ። ፕሬዚዳንቱም ሁኔታውን የመፈንቅለ መንግሥት ሙከራ እንደሆነ ገለጹ።
- ፕሬዝዳንቱ አሁን ላይ የት እንዳሉ ባይታወቅም ፤ አንዳንድ ሪፖርቶች ግን በፈረንሳይ ወታደራዊ አውሮፕላን በሞሪሺየስ አድርገው ወደ ዱባይ ሄደዋል ብለዋል።
- ዛሬ ምሽት 1:00 ላይ ማብራሪያ እንደሚሰጡ የፕሬዜዳንት ፅ/ቤታቸው ቢያሳውቅም የታጠቁ ወታደሮች የሀገሪቱን ሚዲያ ዋና መስሪያ ቤት ለመቆጣጠር መዛታቸውን ተከትሎ ፕሬዝዳንቱ የሚሰጡት ማብራሪያ እንዲራዘም ሆኗል።
መረጃው ከተለያዩ መገናኛ ብዙሃን የተሰባሰበ ነው።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
(በአጭሩ)
- ከ15 ቀን ገደማ በፊት የማዳጋስካር ወጣቶች የመሩት ተቃውሞ ይቀሰቀሳል። ይኸው ተቃውሞው በዋና ከተማዋ አንታናናሪቮ ካለ የኃይል መቆራረጥ እና የውሃ እጥረት ጋር የሚያያዝ ነበር። የወጣቶቹ ተቃውሞ ' Gen Z Madagascar ' የሚል ስያሜ ነበረው።
- በኃላ የወጣቶቹ ተቃውሞ ቁጣ የታከለበትና መልካም አስተዳደር እንዲሰፍን፣ ተጠያቂነት እንዲረጋገጥ፣ ሙስና እንዲያበቃ ፣ የዜጎች ህይወት እንዲሻሻል ወደመጠየቅ ተሸጋገረ።
- የመንግሥት ምላሽ የነበረው ሰልፈኞችን በአስለቃሽ ጭስ መበተን፣ የሰዓት እላፊ መጣል፣ ሰልፈኞች ላይ መተኮስ ሆነ። በተቃውሞ 22 ሰዎች ሲገደሉ ሌሎች በርካቶች ተጎድተዋል።
- የሀገሪቱ ፕሬዚደንት አንድሪ ራጆኤሊና መንግስታቸውን በትነው ወታደራዊ ጠቅላይ ሚኒስትር ሾሙ፣ ጄነራል ሩፊን ፎርቱናት የሚባሉ። ግን አለመረጋጋቱ ለሚቆም አልቻለም።
- አንድ የማዳጋስካር የጦር ክንፍ ተቃዋሚዎችን ተቀላቀቀለ። ከፕሬዜዳንቱ ትእዛዝ ማቀበል አቆመ። ይኸው ኃይል ወደ ተቃዋሚዎች ምንም እንዳይተኮስ አዘዘ። ፕሬዚዳንቱም ሁኔታውን የመፈንቅለ መንግሥት ሙከራ እንደሆነ ገለጹ።
- ፕሬዝዳንቱ አሁን ላይ የት እንዳሉ ባይታወቅም ፤ አንዳንድ ሪፖርቶች ግን በፈረንሳይ ወታደራዊ አውሮፕላን በሞሪሺየስ አድርገው ወደ ዱባይ ሄደዋል ብለዋል።
- ዛሬ ምሽት 1:00 ላይ ማብራሪያ እንደሚሰጡ የፕሬዜዳንት ፅ/ቤታቸው ቢያሳውቅም የታጠቁ ወታደሮች የሀገሪቱን ሚዲያ ዋና መስሪያ ቤት ለመቆጣጠር መዛታቸውን ተከትሎ ፕሬዝዳንቱ የሚሰጡት ማብራሪያ እንዲራዘም ሆኗል።
መረጃው ከተለያዩ መገናኛ ብዙሃን የተሰባሰበ ነው።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
❤1.48K👏357🕊75🙏40😭26😢20🤔16💔14😡3🥰2
" ዘንድሮ ኮሪደር ብለን እንደ አዲስ የምንጀምረው አይኖርም፤ ...ትልቁ ትኩረት የቤት ግንባታ እና የውሃ አቅርቦት ነው " - ከንቲባ አዳነች አቤቤ
በዘንድሮው ዓመት 2018 በአዲስ አበባ ከተማ " የኮሪደር ስራ " ተብሎ እንደ አዲስ የሚጀመር ስራ እንደማይኖር ፤ የዘንድሮ ትኩረት ቤቶችን መገንባት እና የውሃ አቅርቦትን ማሻሻል እንደሆነ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ተናግረዋል።
ከንቲባ አዳነች አቤቤ ይህን ያሉት ለአዲስ አበባ ምክር ቤት በሰጡት ማብራሪያ ነው።
በማብራሪያቸው እስካሁን በኮሪደር ስራ የተገኙ ውጤቶች ከከተማው ስፋት አንጻር ገና እንደሆነ ገልጸዋል።
ስራዎቹ የተሰሩት ታቅዶባቸው፣ የበጀት ዝግጅት ተደርጎ፣ ቤቶች ተዘጋጅተው ፣ የበጀት ቅደም ተከተል ተስተካክሎ መሆኑን አንስተዋል ፤ ስራው ሰፊ ዝግጅት የሚፈልግ እንደሆነም አመልክተዋል።
በዚህም በዘንድሮ ዓመት 2018 በከተማው ' የኮሪደር ስራ ' ተብሎ እንደ አዲስ የሚጀመር ነገር እንደማይኖር አሳውቀዋል።
" የ2018 ትልቁ ትኩረት የቤት ግንባታና የውሃ አቅርቦት ነው ብለን አፀድቀናል ምክር ቤቱን " ያሉት ከንቲባ አዳነች " ዘንድሮ ዋናውና ትልቁ ትኩረታችን የመኖሪ ቤት ግንባታ ይሆናል ብለዋል።
ይህም ቢሆን ግን ስታንዳርዳቸውን መጠበቅ ያለባቸው የከተማው መንገዶች እንደሚሰሩ ፣ እንደሚታደሱ አመልክተዋል።
እነዚህ መንገዶች የትራፊክ ፍሰቱን የሚያስተካክሉ፣ ቅድሚያ የሚሰጣቸው፣ ህዝብ የጠየቃቸው መንገዶች እንደሆኑ ተናግረዋል።
የመንገዶቹ ስራ ሲሰራም የኮሪደር ልማት ስታንዳርድን እንደሚከተሉ ገልጸዋል።
- የተሽከርካሪ መንገዶች ስራና እድሳት
- የተሽከርካሪ መንገዶች ማስፋት ስራ
- የእግረኛ መንገዶች ስራ
- የሳይክል መንገዶች ስራ እንደሚኖር ጠቁመዋል።
" ሁሉንም በአንዴ መጀመር አንችልም። አሁን ላይ አጥንተን የጨረስነው ከዑራኤል - ቦሌ ብራስ VIP የሚገናኘው ነው እሱ እየተሰራ ነው። በፍጥነት ካልሰራነው ቢዝነስ ላይ ተፅእኖ ያሳድራል ፣ በአካባቢው ላይ የትራፊክ ፍሰቱ ላይ ጫና ያሳድራል ለዛም የጀመርነውን በፍጥነት እየጨረስን ነው ሌላ የምንጀምረው " ብለዋል።
" በዚህ አመት ኮሪደር ብለን እንደ አዲስ የምንጀምረው አይኖርም፤ ጥናት እናደርጋለን ቤቶችን እንገነባለን፣ ቅድሚያ ሊሰጣቸው ይገባል በተባሉት ላይ ከህዝብ ጋር ውይይት እናደርጋለን ፣ ተግባቦት እንፈጥራለን " ሲሉ አስረድተዋል።
የመንገድ ግንባታዎች ግን ፦
- ቀድሞ የተጠየቁ፣
- የተጀመሩ ፣
- ከልማት ተነሺዎች ጋር ችግሮች ገጥመዋቸው የነበሩ በራስ ኃይል መሰራታቸውን እንደሚቀጥሉ አሳውቀዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
በዘንድሮው ዓመት 2018 በአዲስ አበባ ከተማ " የኮሪደር ስራ " ተብሎ እንደ አዲስ የሚጀመር ስራ እንደማይኖር ፤ የዘንድሮ ትኩረት ቤቶችን መገንባት እና የውሃ አቅርቦትን ማሻሻል እንደሆነ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ተናግረዋል።
ከንቲባ አዳነች አቤቤ ይህን ያሉት ለአዲስ አበባ ምክር ቤት በሰጡት ማብራሪያ ነው።
በማብራሪያቸው እስካሁን በኮሪደር ስራ የተገኙ ውጤቶች ከከተማው ስፋት አንጻር ገና እንደሆነ ገልጸዋል።
ስራዎቹ የተሰሩት ታቅዶባቸው፣ የበጀት ዝግጅት ተደርጎ፣ ቤቶች ተዘጋጅተው ፣ የበጀት ቅደም ተከተል ተስተካክሎ መሆኑን አንስተዋል ፤ ስራው ሰፊ ዝግጅት የሚፈልግ እንደሆነም አመልክተዋል።
በዚህም በዘንድሮ ዓመት 2018 በከተማው ' የኮሪደር ስራ ' ተብሎ እንደ አዲስ የሚጀመር ነገር እንደማይኖር አሳውቀዋል።
" የ2018 ትልቁ ትኩረት የቤት ግንባታና የውሃ አቅርቦት ነው ብለን አፀድቀናል ምክር ቤቱን " ያሉት ከንቲባ አዳነች " ዘንድሮ ዋናውና ትልቁ ትኩረታችን የመኖሪ ቤት ግንባታ ይሆናል ብለዋል።
ይህም ቢሆን ግን ስታንዳርዳቸውን መጠበቅ ያለባቸው የከተማው መንገዶች እንደሚሰሩ ፣ እንደሚታደሱ አመልክተዋል።
እነዚህ መንገዶች የትራፊክ ፍሰቱን የሚያስተካክሉ፣ ቅድሚያ የሚሰጣቸው፣ ህዝብ የጠየቃቸው መንገዶች እንደሆኑ ተናግረዋል።
የመንገዶቹ ስራ ሲሰራም የኮሪደር ልማት ስታንዳርድን እንደሚከተሉ ገልጸዋል።
- የተሽከርካሪ መንገዶች ስራና እድሳት
- የተሽከርካሪ መንገዶች ማስፋት ስራ
- የእግረኛ መንገዶች ስራ
- የሳይክል መንገዶች ስራ እንደሚኖር ጠቁመዋል።
" ሁሉንም በአንዴ መጀመር አንችልም። አሁን ላይ አጥንተን የጨረስነው ከዑራኤል - ቦሌ ብራስ VIP የሚገናኘው ነው እሱ እየተሰራ ነው። በፍጥነት ካልሰራነው ቢዝነስ ላይ ተፅእኖ ያሳድራል ፣ በአካባቢው ላይ የትራፊክ ፍሰቱ ላይ ጫና ያሳድራል ለዛም የጀመርነውን በፍጥነት እየጨረስን ነው ሌላ የምንጀምረው " ብለዋል።
" በዚህ አመት ኮሪደር ብለን እንደ አዲስ የምንጀምረው አይኖርም፤ ጥናት እናደርጋለን ቤቶችን እንገነባለን፣ ቅድሚያ ሊሰጣቸው ይገባል በተባሉት ላይ ከህዝብ ጋር ውይይት እናደርጋለን ፣ ተግባቦት እንፈጥራለን " ሲሉ አስረድተዋል።
የመንገድ ግንባታዎች ግን ፦
- ቀድሞ የተጠየቁ፣
- የተጀመሩ ፣
- ከልማት ተነሺዎች ጋር ችግሮች ገጥመዋቸው የነበሩ በራስ ኃይል መሰራታቸውን እንደሚቀጥሉ አሳውቀዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
1❤2.17K🙏194😡185👏98😭52🤔40🕊39😱15🥰12😢10💔9
#ደሴ
“ ህይወቷ በማለፉ አዝነናል ነገር ግን ተማሪዋ የደሴ ካምፓስ ተማሪ አይደለችም ” - ወሎ ዩኒቨርሲቲ
➡️ “ የምርመራ ኬዝ ስለሆነ ጥንቃቄ ያስፈልገዋል ” - ጉዳዩን የሚከታተሉት ኢንስፔተክር
ተማሪ ሊዛ ደሳለ የተባለች ወጣት ሰሞኑን በደሴ ከተማ “ የአስገድዶ መድፈርና ግድያ ጥቃት ተፈጽሞባት ” መገኘቷ ተሰምቷል፡፡
መረጃዎች እንደሚያመላክቱት ወጣቷ መስከረም 27 ቀን 2018 ዓ/ም ስልኳን ለማሰራት በደሴ ከተማ ወደ ፒያሳ በወጣችበት አልተመለሰችም፡፡
ይህን ተከትሎ ፍለጋ ሲደረግ ግን “ተደፍራና ተገድላ ተገኝታለች” የተባለ ሲሆን፣ “ፍትህ ለተማሪ ሊዛ” የሚል ጥያቄዎች ኢንተርኔቱን አጨናንቀውታል።
ወጣቷ “ የወሎ ዩኒቨርሲቲ ተማሪ ናት ” የሚሉ መረጃዎች መሰራጨታቸውን ተከትሎ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ምላሽ የጠየቃቸው አንድ የዩኒቨርሲቲው አካል ጉዳዩን አጣርተው በሰጡት ምላሽ፣ “ የተማሪዎች አገልግሎት ጋር ደውየ ነበር፤ 'እንዲህ አይነት ነገር እኛ አልተከሰተም፡፡ ተከሰተ የሚባለውም ከወይዘሮ ስህን ኮሌጅ ነው' ” እንዳሏቸው ገልጸዋል፡፡
እኝሁ የዩኒቨርሲቲው አካል፣ “የደሴ ካምፓስ ተማሪ አይደለችም፡፡ የወይዘሮ ስህን ኮሌጅ ተማሪ ናት፡፡ የኛ ተማሪ አለመሆኗን አሁን ከተማሪ አገልግሎት ደውዬ አጣርቻለሁ ” ሲሉም አክለዋል፡፡
ዩኒቨርሲቲው በማህበራዊ ሚዲያ ስሙ በሀሰት መነሳቱን ገልጾ ይህን ባደረጉት ላይ ተጠያቂነት እንደሚከተል ገልጿል።
በሊዛ ደሳለ ሞት ማዘኑንም ገልጾ ለወዳጅ ዘመዶች መፅናናትን ተመኝቷል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ፣ የተማሪዋን ቤተሰቦች ለማግኘት ያደረገው ጥረት ባይሳከለትም፣ ከቆቦ ከተማ ነዋሪዎች ባደረገው ማጣራት ግን ተማሪ ሊዛ ደሳለ በሰሜን ወሎ ዞን የራያ ቆቦ ወረዳ ቆቦ ከተማ ታዲጊ መሆኗን ለማወቅ ችሏል፡፡
የወይዘሮ ስህን ኮሌጅ ኃላፊዎችን ፣ የደሴ ከተማ ፓሊስን ለማግኘት ያደረግነው ሙከራ ለጊዜው አልተሳካም።
የደሴ ከተማ ኮሚዩኒኬሽን መምሪያ ኃላፊ አቶ ነስረዲን ኃይሌ፣ " መድረክ እየመራሁ ነው " በማለታቸው ሀሳባቸውን ማካተት አልተቻለም። ኃላፊው ቆየተው በላኩት የፅሑፍ መልዕክት ዝርዝር መረጃ ይሰጧችኋል ሲሉ ኮማንደር ሰይድ የሚባሉ አካል ጠቁመዋል።
" ጉዳዩን ተከታትለውታል " የተባሉት ኮማንደር ሰይድ አሊ ምላሽ ብንጠይቃቸውም፣ “ እኔ አልሰጥም፤ ፖሊስ ነው መግለጫ የሚሰጠው፤ ፖሊስ መምሪያ ኃላፊው ናቸው የሚሰጡት ” ብለዋል።
“ የምርመራ ኬዝ ስለሆነ ጥንቃቄ ያስፈልገዋል ” ያሉት እኝሁ አካል፣ የምርመራውን ሂደት ሳይሆን የግድያውንና ሁነት እንዲያስረዱ ስንጠይቃቸው ማብራሪያ ለመስጠት ፈቃደኛ ሳይሆኑ ቀርተዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthioiaFamilyAA
@tikvahethiopia
“ ህይወቷ በማለፉ አዝነናል ነገር ግን ተማሪዋ የደሴ ካምፓስ ተማሪ አይደለችም ” - ወሎ ዩኒቨርሲቲ
➡️ “ የምርመራ ኬዝ ስለሆነ ጥንቃቄ ያስፈልገዋል ” - ጉዳዩን የሚከታተሉት ኢንስፔተክር
ተማሪ ሊዛ ደሳለ የተባለች ወጣት ሰሞኑን በደሴ ከተማ “ የአስገድዶ መድፈርና ግድያ ጥቃት ተፈጽሞባት ” መገኘቷ ተሰምቷል፡፡
መረጃዎች እንደሚያመላክቱት ወጣቷ መስከረም 27 ቀን 2018 ዓ/ም ስልኳን ለማሰራት በደሴ ከተማ ወደ ፒያሳ በወጣችበት አልተመለሰችም፡፡
ይህን ተከትሎ ፍለጋ ሲደረግ ግን “ተደፍራና ተገድላ ተገኝታለች” የተባለ ሲሆን፣ “ፍትህ ለተማሪ ሊዛ” የሚል ጥያቄዎች ኢንተርኔቱን አጨናንቀውታል።
ወጣቷ “ የወሎ ዩኒቨርሲቲ ተማሪ ናት ” የሚሉ መረጃዎች መሰራጨታቸውን ተከትሎ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ምላሽ የጠየቃቸው አንድ የዩኒቨርሲቲው አካል ጉዳዩን አጣርተው በሰጡት ምላሽ፣ “ የተማሪዎች አገልግሎት ጋር ደውየ ነበር፤ 'እንዲህ አይነት ነገር እኛ አልተከሰተም፡፡ ተከሰተ የሚባለውም ከወይዘሮ ስህን ኮሌጅ ነው' ” እንዳሏቸው ገልጸዋል፡፡
እኝሁ የዩኒቨርሲቲው አካል፣ “የደሴ ካምፓስ ተማሪ አይደለችም፡፡ የወይዘሮ ስህን ኮሌጅ ተማሪ ናት፡፡ የኛ ተማሪ አለመሆኗን አሁን ከተማሪ አገልግሎት ደውዬ አጣርቻለሁ ” ሲሉም አክለዋል፡፡
ዩኒቨርሲቲው በማህበራዊ ሚዲያ ስሙ በሀሰት መነሳቱን ገልጾ ይህን ባደረጉት ላይ ተጠያቂነት እንደሚከተል ገልጿል።
በሊዛ ደሳለ ሞት ማዘኑንም ገልጾ ለወዳጅ ዘመዶች መፅናናትን ተመኝቷል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ፣ የተማሪዋን ቤተሰቦች ለማግኘት ያደረገው ጥረት ባይሳከለትም፣ ከቆቦ ከተማ ነዋሪዎች ባደረገው ማጣራት ግን ተማሪ ሊዛ ደሳለ በሰሜን ወሎ ዞን የራያ ቆቦ ወረዳ ቆቦ ከተማ ታዲጊ መሆኗን ለማወቅ ችሏል፡፡
የወይዘሮ ስህን ኮሌጅ ኃላፊዎችን ፣ የደሴ ከተማ ፓሊስን ለማግኘት ያደረግነው ሙከራ ለጊዜው አልተሳካም።
የደሴ ከተማ ኮሚዩኒኬሽን መምሪያ ኃላፊ አቶ ነስረዲን ኃይሌ፣ " መድረክ እየመራሁ ነው " በማለታቸው ሀሳባቸውን ማካተት አልተቻለም። ኃላፊው ቆየተው በላኩት የፅሑፍ መልዕክት ዝርዝር መረጃ ይሰጧችኋል ሲሉ ኮማንደር ሰይድ የሚባሉ አካል ጠቁመዋል።
" ጉዳዩን ተከታትለውታል " የተባሉት ኮማንደር ሰይድ አሊ ምላሽ ብንጠይቃቸውም፣ “ እኔ አልሰጥም፤ ፖሊስ ነው መግለጫ የሚሰጠው፤ ፖሊስ መምሪያ ኃላፊው ናቸው የሚሰጡት ” ብለዋል።
“ የምርመራ ኬዝ ስለሆነ ጥንቃቄ ያስፈልገዋል ” ያሉት እኝሁ አካል፣ የምርመራውን ሂደት ሳይሆን የግድያውንና ሁነት እንዲያስረዱ ስንጠይቃቸው ማብራሪያ ለመስጠት ፈቃደኛ ሳይሆኑ ቀርተዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthioiaFamilyAA
@tikvahethiopia
😭1.75K❤1.17K💔220😡72😢48🕊47😱19🙏13🤔10👏5🥰4
#ኢትዮጵያ🇪🇹
" አያሰማን ፍጹም ያንቺን ክፉ
ኢትዮጵያ
ጠባቂሽ ነው ህዝብሽ እልፍ አእላፉ
ላንቺ ክብር
ላንቺ ክብር ሞትን የማይፈሩ
ኢትዮጵያ
ልጆች አሉሽ ዛሬም የሚያኮሩ
🇪🇹
አረንጓዴ ቢጫ ቀዩ ሰንደቅሽ
አልብሽን አንድ ላይ ልጆቼ ብለሽ፤
አረንጓዴ ቢጫ ቀዩ ሰንደቅሽ
ሰላም ፣ ልምላሜ ፣ ጸጋ ያልብስሽ። "
#ኢትዮጵያ #ETHIOPIA
@tikvahethiopia
" አያሰማን ፍጹም ያንቺን ክፉ
ኢትዮጵያ
ጠባቂሽ ነው ህዝብሽ እልፍ አእላፉ
ላንቺ ክብር
ላንቺ ክብር ሞትን የማይፈሩ
ኢትዮጵያ
ልጆች አሉሽ ዛሬም የሚያኮሩ
አረንጓዴ ቢጫ ቀዩ ሰንደቅሽ
አልብሽን አንድ ላይ ልጆቼ ብለሽ፤
አረንጓዴ ቢጫ ቀዩ ሰንደቅሽ
ሰላም ፣ ልምላሜ ፣ ጸጋ ያልብስሽ። "
#ኢትዮጵያ #ETHIOPIA
@tikvahethiopia
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
40❤1.95K🙏111🥰60🕊56😡56😭41🤔33👏12😢12💔8
የአዕምሮ ህሙማን ቁጥር በዓመት ውስጥ እስከ 15 ሺሕ ጨምሯል።
አማኑኤል የአዕምሮ ህሙማን ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል በሆስፒታሉ የሚስተናገዱ የአዕምሮ ህሙማን ቁጥር በዓመት ውስጥ እስከ 15 ሺሕ መጨመሩን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገለጸ፡፡
ይህን ያሉን፣ የአዕምሮ ህሙማን ቁጥር እየጨመረ ወይስ እየቀነሰ ነው ? ግጭትና ጦርነት የህሙማኑን ቁጥር ለመጨመር ገፊ መንስኤ አልሆነም ? ስንል የጠየቅናቸው የአዕምሮ ሐኪምና የሆስፒታሉ ሜዲካል ዳይሬክተር ዶ/ር ክብሮም ኃይሌ ናቸው።
ዳይሬክተሩ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በዝርዝር ምን አሉ ?
" የመሬት መንቀጥቀጥ፣ ግጭት፣ ድርቅ፣ ጦርነትና መፈናቀሎች በተደጋጋሚ አጋጥመዋል። እነዚህ ክስተቶች የአዕምሮ ጤና ችግርን እንደሚጨምሩ የሚያሻማ አይደለም።
ካለፈው ዓመት መጠነኛ ጭማሪ አለው፡፡ የ2017 እስከ ሰኔ ያለው ከ130 ሺሕ ትንሽ ከፍ ይላል፤ በዚያኛው ዓመት ካየነው 10 ሺሕ፣ 15 ሺሕ ጭማሪ አለው።
ስለዚህ የመጨመር ሁኔታዎች አሉ፤ እንደሚጨምርም ይታወቃል፡፡ ግን ሁሉም (ታማሚ) አይመጣም፡፡ ስለዚህ የሆስፒታሉ ዳታ ማህበረሰቡ ውስጥ ያለውን ሁኔታ ላያሳይ ይችላል። ስለዚህ እኛ ጋር ያለው የታካሚ ቁጥር መጨመር አለመጨመሩ የችግሩን መኖር አለመኖሩን (ሙሉ በሙሉ) አያሳይም።
የአማኑኤል ሆስፒታል የህሙማን ፍሰትን የሚያግዱ የተለያዩ ምክንያቶች አሉ። ለአብነትም በገንዘብ አቅም ማነስ፣ በሚያግዝ ሰው አለመኖር ህሙማን ላይመጡ ይችላሉ።
የመፍትሄ ሀሳብ ምን ሰጡ ?
" እኛ ነን ችግሩ ወዳጋጠመበት ቦታ መሄድ ያለብን፡፡ በአንድ ቦታ ግጭት ሲያጋጥም 'ወገኖቼ ይሞታሉ' በሚል መሸበር ይኖራል፡፡ በተለይ በዚያ ወቅት ስነ ልቦናዊ ድጋፍ ካልተገኘ ችግሩ ይብሳል።
ስለዚህ አዕምሮ ጤናም ጉዳይ ሌሎች እርዳታዎች ጋር አብሮ መሄድ አለበት፡፡ በግንዛቤ እጥረት በትራንስፖርትና በሌሎች ምክንያቶች ሰዎች ወደ ህክምና ላይመጡ ይችላሉ፡፡ ስነልቦናዊና ማኀበራዊ ድጋፉን በዚያው ማቅረብ ያስፈልጋል፣ የታመሙ ከሆኑም እኛ መሄድ አለብን።
በሌላ በኩል፣ ሰዎች ድባቴ ውስጥ በሚገቡበት ወቅት ከሚያወቋቸው ሰዎች ጋር ጊዜ ቢያሳልፉ፣ ችግራቸውን ቢወያዩ ለአዕምሮ ህመም የመጋለጥ ሁኔታው ይቀንሳል።
የሆስፒታሉ ተመላላሽ ህክምና ክፍል ኃላፊስ ምን አሉ ?
የሆስፒታሉ የተመላላሽ ህክምና ክፍል ኃላፊ ሳሙኤል ቶለሳ፣ የዘንድሮው የአዕምሮ ጤና ቀን " በድንገተኛ አደጋዎችና ሰብዓዊ ቀውስ ወቅት የአዕምሮ ጤና አገልግሎት ተደራሽነት ምን ይመስላል ? " የሚለው ላይ እንዳተኮረ ገልጸዋል።
" ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የእርስበርስ ግጭቶች አሉ፣ ያን ተከትሎ የሚመጡ ማኅበራዊ ቀውሶች አሉ " ያሉት ኃላፊው፣ በዚህም የተደራሽነት ውስነት መኖሩን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል፡፡
" በተለያዩ ክልሎች ያለው ቀውስ ራሱን የቻለ ተፅዕኖ አለው፣ ተማሪዎች እንዳይማሩ የማድረግ ሂደቶች አሉ " ብለው፣ ሰዎች ቀጥተኛ የጦርነቱ ተጠቂ ሲሆኑና የሚያስጨንቁ ነገሮች ሲፈጠሩ ለአዕምሮ ህመም ተጋላጭነታቸው እያደገ እንደሚመጣ ገልጸዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
አማኑኤል የአዕምሮ ህሙማን ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል በሆስፒታሉ የሚስተናገዱ የአዕምሮ ህሙማን ቁጥር በዓመት ውስጥ እስከ 15 ሺሕ መጨመሩን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገለጸ፡፡
ይህን ያሉን፣ የአዕምሮ ህሙማን ቁጥር እየጨመረ ወይስ እየቀነሰ ነው ? ግጭትና ጦርነት የህሙማኑን ቁጥር ለመጨመር ገፊ መንስኤ አልሆነም ? ስንል የጠየቅናቸው የአዕምሮ ሐኪምና የሆስፒታሉ ሜዲካል ዳይሬክተር ዶ/ር ክብሮም ኃይሌ ናቸው።
ዳይሬክተሩ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በዝርዝር ምን አሉ ?
" የመሬት መንቀጥቀጥ፣ ግጭት፣ ድርቅ፣ ጦርነትና መፈናቀሎች በተደጋጋሚ አጋጥመዋል። እነዚህ ክስተቶች የአዕምሮ ጤና ችግርን እንደሚጨምሩ የሚያሻማ አይደለም።
ካለፈው ዓመት መጠነኛ ጭማሪ አለው፡፡ የ2017 እስከ ሰኔ ያለው ከ130 ሺሕ ትንሽ ከፍ ይላል፤ በዚያኛው ዓመት ካየነው 10 ሺሕ፣ 15 ሺሕ ጭማሪ አለው።
ስለዚህ የመጨመር ሁኔታዎች አሉ፤ እንደሚጨምርም ይታወቃል፡፡ ግን ሁሉም (ታማሚ) አይመጣም፡፡ ስለዚህ የሆስፒታሉ ዳታ ማህበረሰቡ ውስጥ ያለውን ሁኔታ ላያሳይ ይችላል። ስለዚህ እኛ ጋር ያለው የታካሚ ቁጥር መጨመር አለመጨመሩ የችግሩን መኖር አለመኖሩን (ሙሉ በሙሉ) አያሳይም።
የአማኑኤል ሆስፒታል የህሙማን ፍሰትን የሚያግዱ የተለያዩ ምክንያቶች አሉ። ለአብነትም በገንዘብ አቅም ማነስ፣ በሚያግዝ ሰው አለመኖር ህሙማን ላይመጡ ይችላሉ።
የመፍትሄ ሀሳብ ምን ሰጡ ?
" እኛ ነን ችግሩ ወዳጋጠመበት ቦታ መሄድ ያለብን፡፡ በአንድ ቦታ ግጭት ሲያጋጥም 'ወገኖቼ ይሞታሉ' በሚል መሸበር ይኖራል፡፡ በተለይ በዚያ ወቅት ስነ ልቦናዊ ድጋፍ ካልተገኘ ችግሩ ይብሳል።
ስለዚህ አዕምሮ ጤናም ጉዳይ ሌሎች እርዳታዎች ጋር አብሮ መሄድ አለበት፡፡ በግንዛቤ እጥረት በትራንስፖርትና በሌሎች ምክንያቶች ሰዎች ወደ ህክምና ላይመጡ ይችላሉ፡፡ ስነልቦናዊና ማኀበራዊ ድጋፉን በዚያው ማቅረብ ያስፈልጋል፣ የታመሙ ከሆኑም እኛ መሄድ አለብን።
በሌላ በኩል፣ ሰዎች ድባቴ ውስጥ በሚገቡበት ወቅት ከሚያወቋቸው ሰዎች ጋር ጊዜ ቢያሳልፉ፣ ችግራቸውን ቢወያዩ ለአዕምሮ ህመም የመጋለጥ ሁኔታው ይቀንሳል።
የሆስፒታሉ ተመላላሽ ህክምና ክፍል ኃላፊስ ምን አሉ ?
የሆስፒታሉ የተመላላሽ ህክምና ክፍል ኃላፊ ሳሙኤል ቶለሳ፣ የዘንድሮው የአዕምሮ ጤና ቀን " በድንገተኛ አደጋዎችና ሰብዓዊ ቀውስ ወቅት የአዕምሮ ጤና አገልግሎት ተደራሽነት ምን ይመስላል ? " የሚለው ላይ እንዳተኮረ ገልጸዋል።
" ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የእርስበርስ ግጭቶች አሉ፣ ያን ተከትሎ የሚመጡ ማኅበራዊ ቀውሶች አሉ " ያሉት ኃላፊው፣ በዚህም የተደራሽነት ውስነት መኖሩን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል፡፡
" በተለያዩ ክልሎች ያለው ቀውስ ራሱን የቻለ ተፅዕኖ አለው፣ ተማሪዎች እንዳይማሩ የማድረግ ሂደቶች አሉ " ብለው፣ ሰዎች ቀጥተኛ የጦርነቱ ተጠቂ ሲሆኑና የሚያስጨንቁ ነገሮች ሲፈጠሩ ለአዕምሮ ህመም ተጋላጭነታቸው እያደገ እንደሚመጣ ገልጸዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
❤958😭746💔83😢63🕊45🙏42😱26😡23🤔19👏9🥰7
📣 𝐉𝐢𝐦𝐦𝐚 𝐔𝐧𝐢𝐯𝐞𝐫𝐬𝐢𝐭𝐲 𝐢𝐬 𝐍𝐨𝐰 𝐢𝐧 𝐭𝐡𝐞 𝐂𝐢𝐭𝐲!
Registration is officially 𝐎𝐏𝐄𝐍 for our selected undergraduate programs at the JU-ABH Campus in Addis Ababa. Your opportunity to earn a prestigious degree has arrived!
𝐎𝐮𝐫 𝐏𝐫𝐨𝐠𝐫𝐚𝐦𝐬
1. BA degree in Accounting & Finance 💰
2. BA degree in Management 💼
3. BSc degree in Computer Science 💻
4. Bachelor of Laws (LLB) ⚖️
𝐑𝐞𝐚𝐝𝐲 𝐭𝐨 𝐀𝐩𝐩𝐥𝐲?
Visit www.allianceacademy.edu.et/degree-program
𝐐𝐮𝐞𝐬𝐭𝐢𝐨𝐧𝐬? We are ready to assist!
📞 +251978464748 / +251979464748
𝐂𝐨𝐧𝐧𝐞𝐜𝐭 𝐰𝐢𝐭𝐡 𝐮𝐬
LinkedIn|Telegram |Facebook |Twitter/X |Instagram |TikTok |YouTube |Threads
Registration is officially 𝐎𝐏𝐄𝐍 for our selected undergraduate programs at the JU-ABH Campus in Addis Ababa. Your opportunity to earn a prestigious degree has arrived!
𝐎𝐮𝐫 𝐏𝐫𝐨𝐠𝐫𝐚𝐦𝐬
1. BA degree in Accounting & Finance 💰
2. BA degree in Management 💼
3. BSc degree in Computer Science 💻
4. Bachelor of Laws (LLB) ⚖️
𝐑𝐞𝐚𝐝𝐲 𝐭𝐨 𝐀𝐩𝐩𝐥𝐲?
Visit www.allianceacademy.edu.et/degree-program
𝐐𝐮𝐞𝐬𝐭𝐢𝐨𝐧𝐬? We are ready to assist!
📞 +251978464748 / +251979464748
𝐂𝐨𝐧𝐧𝐞𝐜𝐭 𝐰𝐢𝐭𝐡 𝐮𝐬
LinkedIn|Telegram |Facebook |Twitter/X |Instagram |TikTok |YouTube |Threads
❤197🤔5🥰4😱4😢1😡1
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
ወረቀት የለም! ጊዜ ማባከን የለም!
ቀላልና ፈጣን የባንክ አገልግሎት ብቻ!
የጣት አሻራንና የፊት ገጽን እንደ መለያ የሚጠቀመው አዲሱ የአቢሲንያ ባንክ ወረቀት አልባ አገልግሎት ደንበኞች በጊዜና ቦታ ሳይገደቡ ያለማንም እርዳታ በራስ-አገዝ (Self-Service) ወይም በሠራተኞች በመታገዝ (Assisted Service) ደህንነቱ በተጠበቀና ፈጣን በሆነ መልኩ የሚፈልጉትን የባንክ አገልግሎት መጠቀም ይችላሉ፡፡ #ወረቀትአልባየባንክአገልግሎት #Paperlessbranchmodel #BanksinEthiopia #AddisAbaba #Ethiopia #የሁሉም_ምርጫ
ቀላልና ፈጣን የባንክ አገልግሎት ብቻ!
የጣት አሻራንና የፊት ገጽን እንደ መለያ የሚጠቀመው አዲሱ የአቢሲንያ ባንክ ወረቀት አልባ አገልግሎት ደንበኞች በጊዜና ቦታ ሳይገደቡ ያለማንም እርዳታ በራስ-አገዝ (Self-Service) ወይም በሠራተኞች በመታገዝ (Assisted Service) ደህንነቱ በተጠበቀና ፈጣን በሆነ መልኩ የሚፈልጉትን የባንክ አገልግሎት መጠቀም ይችላሉ፡፡ #ወረቀትአልባየባንክአገልግሎት #Paperlessbranchmodel #BanksinEthiopia #AddisAbaba #Ethiopia #የሁሉም_ምርጫ
❤304😡61👏39🙏13