#ኢትዮጵያ🇪🇹
" አያሰማን ፍጹም ያንቺን ክፉ
ኢትዮጵያ
ጠባቂሽ ነው ህዝብሽ እልፍ አእላፉ
ላንቺ ክብር
ላንቺ ክብር ሞትን የማይፈሩ
ኢትዮጵያ
ልጆች አሉሽ ዛሬም የሚያኮሩ
🇪🇹
አረንጓዴ ቢጫ ቀዩ ሰንደቅሽ
አልብሽን አንድ ላይ ልጆቼ ብለሽ፤
አረንጓዴ ቢጫ ቀዩ ሰንደቅሽ
ሰላም ፣ ልምላሜ ፣ ጸጋ ያልብስሽ። "
#ኢትዮጵያ #ETHIOPIA
@tikvahethiopia
" አያሰማን ፍጹም ያንቺን ክፉ
ኢትዮጵያ
ጠባቂሽ ነው ህዝብሽ እልፍ አእላፉ
ላንቺ ክብር
ላንቺ ክብር ሞትን የማይፈሩ
ኢትዮጵያ
ልጆች አሉሽ ዛሬም የሚያኮሩ
አረንጓዴ ቢጫ ቀዩ ሰንደቅሽ
አልብሽን አንድ ላይ ልጆቼ ብለሽ፤
አረንጓዴ ቢጫ ቀዩ ሰንደቅሽ
ሰላም ፣ ልምላሜ ፣ ጸጋ ያልብስሽ። "
#ኢትዮጵያ #ETHIOPIA
@tikvahethiopia
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
40❤1.97K🙏112🥰62🕊56😡56😭42🤔33😢14👏12💔8
የአዕምሮ ህሙማን ቁጥር በዓመት ውስጥ እስከ 15 ሺሕ ጨምሯል።
አማኑኤል የአዕምሮ ህሙማን ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል በሆስፒታሉ የሚስተናገዱ የአዕምሮ ህሙማን ቁጥር በዓመት ውስጥ እስከ 15 ሺሕ መጨመሩን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገለጸ፡፡
ይህን ያሉን፣ የአዕምሮ ህሙማን ቁጥር እየጨመረ ወይስ እየቀነሰ ነው ? ግጭትና ጦርነት የህሙማኑን ቁጥር ለመጨመር ገፊ መንስኤ አልሆነም ? ስንል የጠየቅናቸው የአዕምሮ ሐኪምና የሆስፒታሉ ሜዲካል ዳይሬክተር ዶ/ር ክብሮም ኃይሌ ናቸው።
ዳይሬክተሩ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በዝርዝር ምን አሉ ?
" የመሬት መንቀጥቀጥ፣ ግጭት፣ ድርቅ፣ ጦርነትና መፈናቀሎች በተደጋጋሚ አጋጥመዋል። እነዚህ ክስተቶች የአዕምሮ ጤና ችግርን እንደሚጨምሩ የሚያሻማ አይደለም።
ካለፈው ዓመት መጠነኛ ጭማሪ አለው፡፡ የ2017 እስከ ሰኔ ያለው ከ130 ሺሕ ትንሽ ከፍ ይላል፤ በዚያኛው ዓመት ካየነው 10 ሺሕ፣ 15 ሺሕ ጭማሪ አለው።
ስለዚህ የመጨመር ሁኔታዎች አሉ፤ እንደሚጨምርም ይታወቃል፡፡ ግን ሁሉም (ታማሚ) አይመጣም፡፡ ስለዚህ የሆስፒታሉ ዳታ ማህበረሰቡ ውስጥ ያለውን ሁኔታ ላያሳይ ይችላል። ስለዚህ እኛ ጋር ያለው የታካሚ ቁጥር መጨመር አለመጨመሩ የችግሩን መኖር አለመኖሩን (ሙሉ በሙሉ) አያሳይም።
የአማኑኤል ሆስፒታል የህሙማን ፍሰትን የሚያግዱ የተለያዩ ምክንያቶች አሉ። ለአብነትም በገንዘብ አቅም ማነስ፣ በሚያግዝ ሰው አለመኖር ህሙማን ላይመጡ ይችላሉ።
የመፍትሄ ሀሳብ ምን ሰጡ ?
" እኛ ነን ችግሩ ወዳጋጠመበት ቦታ መሄድ ያለብን፡፡ በአንድ ቦታ ግጭት ሲያጋጥም 'ወገኖቼ ይሞታሉ' በሚል መሸበር ይኖራል፡፡ በተለይ በዚያ ወቅት ስነ ልቦናዊ ድጋፍ ካልተገኘ ችግሩ ይብሳል።
ስለዚህ አዕምሮ ጤናም ጉዳይ ሌሎች እርዳታዎች ጋር አብሮ መሄድ አለበት፡፡ በግንዛቤ እጥረት በትራንስፖርትና በሌሎች ምክንያቶች ሰዎች ወደ ህክምና ላይመጡ ይችላሉ፡፡ ስነልቦናዊና ማኀበራዊ ድጋፉን በዚያው ማቅረብ ያስፈልጋል፣ የታመሙ ከሆኑም እኛ መሄድ አለብን።
በሌላ በኩል፣ ሰዎች ድባቴ ውስጥ በሚገቡበት ወቅት ከሚያወቋቸው ሰዎች ጋር ጊዜ ቢያሳልፉ፣ ችግራቸውን ቢወያዩ ለአዕምሮ ህመም የመጋለጥ ሁኔታው ይቀንሳል።
የሆስፒታሉ ተመላላሽ ህክምና ክፍል ኃላፊስ ምን አሉ ?
የሆስፒታሉ የተመላላሽ ህክምና ክፍል ኃላፊ ሳሙኤል ቶለሳ፣ የዘንድሮው የአዕምሮ ጤና ቀን " በድንገተኛ አደጋዎችና ሰብዓዊ ቀውስ ወቅት የአዕምሮ ጤና አገልግሎት ተደራሽነት ምን ይመስላል ? " የሚለው ላይ እንዳተኮረ ገልጸዋል።
" ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የእርስበርስ ግጭቶች አሉ፣ ያን ተከትሎ የሚመጡ ማኅበራዊ ቀውሶች አሉ " ያሉት ኃላፊው፣ በዚህም የተደራሽነት ውስነት መኖሩን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል፡፡
" በተለያዩ ክልሎች ያለው ቀውስ ራሱን የቻለ ተፅዕኖ አለው፣ ተማሪዎች እንዳይማሩ የማድረግ ሂደቶች አሉ " ብለው፣ ሰዎች ቀጥተኛ የጦርነቱ ተጠቂ ሲሆኑና የሚያስጨንቁ ነገሮች ሲፈጠሩ ለአዕምሮ ህመም ተጋላጭነታቸው እያደገ እንደሚመጣ ገልጸዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
አማኑኤል የአዕምሮ ህሙማን ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል በሆስፒታሉ የሚስተናገዱ የአዕምሮ ህሙማን ቁጥር በዓመት ውስጥ እስከ 15 ሺሕ መጨመሩን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገለጸ፡፡
ይህን ያሉን፣ የአዕምሮ ህሙማን ቁጥር እየጨመረ ወይስ እየቀነሰ ነው ? ግጭትና ጦርነት የህሙማኑን ቁጥር ለመጨመር ገፊ መንስኤ አልሆነም ? ስንል የጠየቅናቸው የአዕምሮ ሐኪምና የሆስፒታሉ ሜዲካል ዳይሬክተር ዶ/ር ክብሮም ኃይሌ ናቸው።
ዳይሬክተሩ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በዝርዝር ምን አሉ ?
" የመሬት መንቀጥቀጥ፣ ግጭት፣ ድርቅ፣ ጦርነትና መፈናቀሎች በተደጋጋሚ አጋጥመዋል። እነዚህ ክስተቶች የአዕምሮ ጤና ችግርን እንደሚጨምሩ የሚያሻማ አይደለም።
ካለፈው ዓመት መጠነኛ ጭማሪ አለው፡፡ የ2017 እስከ ሰኔ ያለው ከ130 ሺሕ ትንሽ ከፍ ይላል፤ በዚያኛው ዓመት ካየነው 10 ሺሕ፣ 15 ሺሕ ጭማሪ አለው።
ስለዚህ የመጨመር ሁኔታዎች አሉ፤ እንደሚጨምርም ይታወቃል፡፡ ግን ሁሉም (ታማሚ) አይመጣም፡፡ ስለዚህ የሆስፒታሉ ዳታ ማህበረሰቡ ውስጥ ያለውን ሁኔታ ላያሳይ ይችላል። ስለዚህ እኛ ጋር ያለው የታካሚ ቁጥር መጨመር አለመጨመሩ የችግሩን መኖር አለመኖሩን (ሙሉ በሙሉ) አያሳይም።
የአማኑኤል ሆስፒታል የህሙማን ፍሰትን የሚያግዱ የተለያዩ ምክንያቶች አሉ። ለአብነትም በገንዘብ አቅም ማነስ፣ በሚያግዝ ሰው አለመኖር ህሙማን ላይመጡ ይችላሉ።
የመፍትሄ ሀሳብ ምን ሰጡ ?
" እኛ ነን ችግሩ ወዳጋጠመበት ቦታ መሄድ ያለብን፡፡ በአንድ ቦታ ግጭት ሲያጋጥም 'ወገኖቼ ይሞታሉ' በሚል መሸበር ይኖራል፡፡ በተለይ በዚያ ወቅት ስነ ልቦናዊ ድጋፍ ካልተገኘ ችግሩ ይብሳል።
ስለዚህ አዕምሮ ጤናም ጉዳይ ሌሎች እርዳታዎች ጋር አብሮ መሄድ አለበት፡፡ በግንዛቤ እጥረት በትራንስፖርትና በሌሎች ምክንያቶች ሰዎች ወደ ህክምና ላይመጡ ይችላሉ፡፡ ስነልቦናዊና ማኀበራዊ ድጋፉን በዚያው ማቅረብ ያስፈልጋል፣ የታመሙ ከሆኑም እኛ መሄድ አለብን።
በሌላ በኩል፣ ሰዎች ድባቴ ውስጥ በሚገቡበት ወቅት ከሚያወቋቸው ሰዎች ጋር ጊዜ ቢያሳልፉ፣ ችግራቸውን ቢወያዩ ለአዕምሮ ህመም የመጋለጥ ሁኔታው ይቀንሳል።
የሆስፒታሉ ተመላላሽ ህክምና ክፍል ኃላፊስ ምን አሉ ?
የሆስፒታሉ የተመላላሽ ህክምና ክፍል ኃላፊ ሳሙኤል ቶለሳ፣ የዘንድሮው የአዕምሮ ጤና ቀን " በድንገተኛ አደጋዎችና ሰብዓዊ ቀውስ ወቅት የአዕምሮ ጤና አገልግሎት ተደራሽነት ምን ይመስላል ? " የሚለው ላይ እንዳተኮረ ገልጸዋል።
" ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የእርስበርስ ግጭቶች አሉ፣ ያን ተከትሎ የሚመጡ ማኅበራዊ ቀውሶች አሉ " ያሉት ኃላፊው፣ በዚህም የተደራሽነት ውስነት መኖሩን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል፡፡
" በተለያዩ ክልሎች ያለው ቀውስ ራሱን የቻለ ተፅዕኖ አለው፣ ተማሪዎች እንዳይማሩ የማድረግ ሂደቶች አሉ " ብለው፣ ሰዎች ቀጥተኛ የጦርነቱ ተጠቂ ሲሆኑና የሚያስጨንቁ ነገሮች ሲፈጠሩ ለአዕምሮ ህመም ተጋላጭነታቸው እያደገ እንደሚመጣ ገልጸዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
❤966😭746💔83😢63🕊45🙏42😱26😡23🤔19👏9🥰7
📣 𝐉𝐢𝐦𝐦𝐚 𝐔𝐧𝐢𝐯𝐞𝐫𝐬𝐢𝐭𝐲 𝐢𝐬 𝐍𝐨𝐰 𝐢𝐧 𝐭𝐡𝐞 𝐂𝐢𝐭𝐲!
Registration is officially 𝐎𝐏𝐄𝐍 for our selected undergraduate programs at the JU-ABH Campus in Addis Ababa. Your opportunity to earn a prestigious degree has arrived!
𝐎𝐮𝐫 𝐏𝐫𝐨𝐠𝐫𝐚𝐦𝐬
1. BA degree in Accounting & Finance 💰
2. BA degree in Management 💼
3. BSc degree in Computer Science 💻
4. Bachelor of Laws (LLB) ⚖️
𝐑𝐞𝐚𝐝𝐲 𝐭𝐨 𝐀𝐩𝐩𝐥𝐲?
Visit www.allianceacademy.edu.et/degree-program
𝐐𝐮𝐞𝐬𝐭𝐢𝐨𝐧𝐬? We are ready to assist!
📞 +251978464748 / +251979464748
𝐂𝐨𝐧𝐧𝐞𝐜𝐭 𝐰𝐢𝐭𝐡 𝐮𝐬
LinkedIn|Telegram |Facebook |Twitter/X |Instagram |TikTok |YouTube |Threads
Registration is officially 𝐎𝐏𝐄𝐍 for our selected undergraduate programs at the JU-ABH Campus in Addis Ababa. Your opportunity to earn a prestigious degree has arrived!
𝐎𝐮𝐫 𝐏𝐫𝐨𝐠𝐫𝐚𝐦𝐬
1. BA degree in Accounting & Finance 💰
2. BA degree in Management 💼
3. BSc degree in Computer Science 💻
4. Bachelor of Laws (LLB) ⚖️
𝐑𝐞𝐚𝐝𝐲 𝐭𝐨 𝐀𝐩𝐩𝐥𝐲?
Visit www.allianceacademy.edu.et/degree-program
𝐐𝐮𝐞𝐬𝐭𝐢𝐨𝐧𝐬? We are ready to assist!
📞 +251978464748 / +251979464748
𝐂𝐨𝐧𝐧𝐞𝐜𝐭 𝐰𝐢𝐭𝐡 𝐮𝐬
LinkedIn|Telegram |Facebook |Twitter/X |Instagram |TikTok |YouTube |Threads
❤199🤔5🥰4😱4😢2😡1
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
ወረቀት የለም! ጊዜ ማባከን የለም!
ቀላልና ፈጣን የባንክ አገልግሎት ብቻ!
የጣት አሻራንና የፊት ገጽን እንደ መለያ የሚጠቀመው አዲሱ የአቢሲንያ ባንክ ወረቀት አልባ አገልግሎት ደንበኞች በጊዜና ቦታ ሳይገደቡ ያለማንም እርዳታ በራስ-አገዝ (Self-Service) ወይም በሠራተኞች በመታገዝ (Assisted Service) ደህንነቱ በተጠበቀና ፈጣን በሆነ መልኩ የሚፈልጉትን የባንክ አገልግሎት መጠቀም ይችላሉ፡፡ #ወረቀትአልባየባንክአገልግሎት #Paperlessbranchmodel #BanksinEthiopia #AddisAbaba #Ethiopia #የሁሉም_ምርጫ
ቀላልና ፈጣን የባንክ አገልግሎት ብቻ!
የጣት አሻራንና የፊት ገጽን እንደ መለያ የሚጠቀመው አዲሱ የአቢሲንያ ባንክ ወረቀት አልባ አገልግሎት ደንበኞች በጊዜና ቦታ ሳይገደቡ ያለማንም እርዳታ በራስ-አገዝ (Self-Service) ወይም በሠራተኞች በመታገዝ (Assisted Service) ደህንነቱ በተጠበቀና ፈጣን በሆነ መልኩ የሚፈልጉትን የባንክ አገልግሎት መጠቀም ይችላሉ፡፡ #ወረቀትአልባየባንክአገልግሎት #Paperlessbranchmodel #BanksinEthiopia #AddisAbaba #Ethiopia #የሁሉም_ምርጫ
❤309😡61👏42🙏13
TIKVAH-ETHIOPIA
Video
#ETHIOPIA🇪🇹
የሚኒስትሮች ምክር ቤት በዛሬው ዕለት ባካሄደው መደበኛ ስብሰባዉ የኢትዮጵያ ኒውክሊየር ኃይል ኮሚሽን ማቋቋሚያ ደንብን መርምሮ በሙሉ ድምጽ አጸደቀ።
ይህ ደንብ በነጋሪት ጋዜጣ በይፋ ታትሞ ከወጣ በኋላ ተግባራዊ የሚሆን ሲሆን፣ ኢትዮጵያ የኒውክሌር ቴክኖሎጂን ለሰላማዊ ልማት የመጠቀም ጥረቷን ወደ ላቀ ደረጃ እንደሚያሸጋግር ይጠበቃል።
ኮሚሽኑ በዓለም አቀፍ ማዕቀፎች መሰረት የኒውክሌር ቴክኖሎጂን ለሰላማዊ ዓላማዎች የመጠቀም ሀገራዊ ጥረትን የመምራትና የማስተባበር ዋነኛ ኃላፊነት ይኖረዋል ተብሏል።
ትኩረት አድርጎ የሚሠራባቸው ቁልፍ ዘርፎችም የኤሌክትሪክ ኃይል ተደራሽነት፣ የኢንዱስትሪ ልማት፣ የምግብ ዋስትና፣ የጤና አገልግሎት እንዲሁም ሳይንስና ምርምር መሆናቸው ተመላክቷል።
በሌላ በኩል ፥ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከጥቅምት 4 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ አቶ ሳንዶካን ደበበ የኢትዮጵያ ኒውክሊየር ኃይል ኮሚሽን ኮሚሽነር አድርገው ሾመዋል።
@tikvahethiopia
የሚኒስትሮች ምክር ቤት በዛሬው ዕለት ባካሄደው መደበኛ ስብሰባዉ የኢትዮጵያ ኒውክሊየር ኃይል ኮሚሽን ማቋቋሚያ ደንብን መርምሮ በሙሉ ድምጽ አጸደቀ።
ይህ ደንብ በነጋሪት ጋዜጣ በይፋ ታትሞ ከወጣ በኋላ ተግባራዊ የሚሆን ሲሆን፣ ኢትዮጵያ የኒውክሌር ቴክኖሎጂን ለሰላማዊ ልማት የመጠቀም ጥረቷን ወደ ላቀ ደረጃ እንደሚያሸጋግር ይጠበቃል።
ኮሚሽኑ በዓለም አቀፍ ማዕቀፎች መሰረት የኒውክሌር ቴክኖሎጂን ለሰላማዊ ዓላማዎች የመጠቀም ሀገራዊ ጥረትን የመምራትና የማስተባበር ዋነኛ ኃላፊነት ይኖረዋል ተብሏል።
ትኩረት አድርጎ የሚሠራባቸው ቁልፍ ዘርፎችም የኤሌክትሪክ ኃይል ተደራሽነት፣ የኢንዱስትሪ ልማት፣ የምግብ ዋስትና፣ የጤና አገልግሎት እንዲሁም ሳይንስና ምርምር መሆናቸው ተመላክቷል።
በሌላ በኩል ፥ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከጥቅምት 4 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ አቶ ሳንዶካን ደበበ የኢትዮጵያ ኒውክሊየር ኃይል ኮሚሽን ኮሚሽነር አድርገው ሾመዋል።
@tikvahethiopia
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
❤713🤔129😡71👏43🕊14😱9😭8🥰6🙏2💔1
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update " ሰላምን እንሻለን ! " - የትግራይ ኃይል አባላት ➡️ " የኛን ጥያቄ መመለስ ከማይችል አመራር የሌላው ህዝብ ጥያቄ ሊመልስ አይችልም ! " የትግራይ ኃይል አባላት ዛሬ ሰኞ ጥቅምት 3/2018 ዓ.ም ከጥዋቱ 2:30 ጀምረው የመብት ጥያቄ አንስተው በከተማዋ ዋና ዋና መንገዶች ሰላማዊ ሰልፍ አካሂደዋል። ሰልፈኛቹ ቁጣን ባዘለ ድምፅ ፦ - " የደመወዝና ጥቅማጥቅም ጥያቄያችን ይመለስ…
#Update
የትግራይ ኃይል አባላት ሰልፍ ዛሬም በሌላ አቅጣጫ ሰልፍ ማድረግ ቀጥለዋል።
በመቐለና ዙሪያዋ የሚገኙ የትግራይ ኃይል አባላይ ትናንት ሰኞ ጥቅምት 3/2018 ዓ.ም ከጥዋቱ 2:30 እስከ ምሽት ሰላማዊ ሰልፍ አካሂደው ነበር።
በዚያው ቀን ምሸት የሰላማዊ ሰልፈኞቹ ተወካዮች የጊዚያዊ አስተዳደሩ ፕሬዚዳንት ታደሰ ወረደ (ሌ/ጀ) ከሚገኙባቸው የህወሓትና የሰራዊት አዛዦች ቢነጋገሩም ፤ ስለተደረሰው ስምምነት በይፋ ለህዝብ የተሰጠ መረጃ የለም።
ሆኖም ከሰብሰባው አዳራሽ ተቆርጦ የወጣው ቪድዮ እንደሚያመለክተው ሰላማዊ ሰልፈኞቹ የደመወዝ ፣ የጥቅማጥቅምና ለቤተሰቦቻቸው መኖሪያ የሚውል የመስሪያ ቦታ ጥያቄ አንስተዋል።
የትናንትናው ውይይት ውጤት ለህዝብ ሳይነገር ታድያ ዛሬ ማክሰኞ ጥቅምት 4/2018 ዓ.ም ከትግራይ ምስራቃዊ ዞን ወደ መቐለ ከተማ የሚያስገባው ዋና አስፋልት ከጥዋት ጀምሮ ይህ መረጃ እስከተጠናቀረበት ሰዓትና ደቂቃ በሁለት ቦታ ተዘግተዋል።
የትግራይ ኃይል አባላት ሰላማዊ ሰልፈኞች ኣጉላዕና ጉርመዶ በሚባሉ ሁለት ቦታዎች መንገድ በመዝጋታቸው ምክንያት መኪኖች ቆመዋል ተጓዦች ተስተጓጉለዋል።
ሰላማዊ ሰልፈኞቹ ጥያቄያቸው ከትናንትናው ሰልፍ ተመሳሳይ እንደሆነ ቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ ቦታው ድረስ ደውሎ አረጋግጠዋል።
በዚህ ዙሪያ የሚኖሩ አዳዲስ መረጃዎች ተከታትለን እናቀርባለን።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
መቐለ
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
የትግራይ ኃይል አባላት ሰልፍ ዛሬም በሌላ አቅጣጫ ሰልፍ ማድረግ ቀጥለዋል።
በመቐለና ዙሪያዋ የሚገኙ የትግራይ ኃይል አባላይ ትናንት ሰኞ ጥቅምት 3/2018 ዓ.ም ከጥዋቱ 2:30 እስከ ምሽት ሰላማዊ ሰልፍ አካሂደው ነበር።
በዚያው ቀን ምሸት የሰላማዊ ሰልፈኞቹ ተወካዮች የጊዚያዊ አስተዳደሩ ፕሬዚዳንት ታደሰ ወረደ (ሌ/ጀ) ከሚገኙባቸው የህወሓትና የሰራዊት አዛዦች ቢነጋገሩም ፤ ስለተደረሰው ስምምነት በይፋ ለህዝብ የተሰጠ መረጃ የለም።
ሆኖም ከሰብሰባው አዳራሽ ተቆርጦ የወጣው ቪድዮ እንደሚያመለክተው ሰላማዊ ሰልፈኞቹ የደመወዝ ፣ የጥቅማጥቅምና ለቤተሰቦቻቸው መኖሪያ የሚውል የመስሪያ ቦታ ጥያቄ አንስተዋል።
የትናንትናው ውይይት ውጤት ለህዝብ ሳይነገር ታድያ ዛሬ ማክሰኞ ጥቅምት 4/2018 ዓ.ም ከትግራይ ምስራቃዊ ዞን ወደ መቐለ ከተማ የሚያስገባው ዋና አስፋልት ከጥዋት ጀምሮ ይህ መረጃ እስከተጠናቀረበት ሰዓትና ደቂቃ በሁለት ቦታ ተዘግተዋል።
የትግራይ ኃይል አባላት ሰላማዊ ሰልፈኞች ኣጉላዕና ጉርመዶ በሚባሉ ሁለት ቦታዎች መንገድ በመዝጋታቸው ምክንያት መኪኖች ቆመዋል ተጓዦች ተስተጓጉለዋል።
ሰላማዊ ሰልፈኞቹ ጥያቄያቸው ከትናንትናው ሰልፍ ተመሳሳይ እንደሆነ ቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ ቦታው ድረስ ደውሎ አረጋግጠዋል።
በዚህ ዙሪያ የሚኖሩ አዳዲስ መረጃዎች ተከታትለን እናቀርባለን።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
መቐለ
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
❤936👏89🕊75🤔38😡19😭17😢16🙏16🥰7💔1
ደንበኛዎትን በቀላሉ ካሉበት ለመድረስ የሚያስችልዎትን የዲጂታል ሱቅ በዘመን ገበያ ላይ አሁኑኑ ይክፈቱ፣ ተደራሽነትዎን ያስፉ።
የበለጠ መረጃ ለማግኘት 3131 ላይ ይደውሉ!
ዘመን ገበያ የዲጂታል ኢትዮጵያ የግብይት መዳረሻ!
#ZemenGEBEYA
#Ethiotelecom #telebirr #telebirrSuperApp #DigitalAfrica #DigitalEthiopia #RealizingDigitalEthiopia
የበለጠ መረጃ ለማግኘት 3131 ላይ ይደውሉ!
ዘመን ገበያ የዲጂታል ኢትዮጵያ የግብይት መዳረሻ!
#ZemenGEBEYA
#Ethiotelecom #telebirr #telebirrSuperApp #DigitalAfrica #DigitalEthiopia #RealizingDigitalEthiopia
❤133😢5🙏5😱4🕊1
ብሔራዊ ባንክ ዛሬ የውጭ ምንዛሪ ጨረታ አካሂዷል።
ባንኩ መሰል ጨረታ ሲያወጣ ለ10ኛው ዙር ሲሆን በዚህ ዙር 150 ሚሊዮን ዶላር ነበር ያቀረበው።
በጨረታው የአንድ የአሜሪካን ዶላር አማካይ የምንዛሪ ተመን 148.1007 ብር ሆኖ ተመዝግቧል። / 1 ዶላር በ148.1007 ተሽጧል /
ይህ አዲስ አማካኝ ዋጋ ከሁለት ወራት በፊት በ9ኛው ዙር ጨረታ ከተመዘገበው 138.2 ብር አማካይ ዋጋ ጋር ሲነጻጸር፣ የ9 ብር ከ90 ሳንቲም ወይም የ 7.16 በመቶ ጭማሪ አሳይቷል።
ዛሬ በተካሄደው የውጭ ምንዛሪ ድልድል 31 ባንኮች የውጭ ምንዛሪ በማግኘት ተሳክቶላቸዋል።
ብሔራዊ ባንክ የውጭ ምንዛሪ ገበያው በሚፈቅደው ጊዜ ጨረታዎቹን ማካሄዱን እንደሚቀጥል አስታውቋል። #ካፒታል
@tikvahethiopia
ባንኩ መሰል ጨረታ ሲያወጣ ለ10ኛው ዙር ሲሆን በዚህ ዙር 150 ሚሊዮን ዶላር ነበር ያቀረበው።
በጨረታው የአንድ የአሜሪካን ዶላር አማካይ የምንዛሪ ተመን 148.1007 ብር ሆኖ ተመዝግቧል። / 1 ዶላር በ148.1007 ተሽጧል /
ይህ አዲስ አማካኝ ዋጋ ከሁለት ወራት በፊት በ9ኛው ዙር ጨረታ ከተመዘገበው 138.2 ብር አማካይ ዋጋ ጋር ሲነጻጸር፣ የ9 ብር ከ90 ሳንቲም ወይም የ 7.16 በመቶ ጭማሪ አሳይቷል።
ዛሬ በተካሄደው የውጭ ምንዛሪ ድልድል 31 ባንኮች የውጭ ምንዛሪ በማግኘት ተሳክቶላቸዋል።
ብሔራዊ ባንክ የውጭ ምንዛሪ ገበያው በሚፈቅደው ጊዜ ጨረታዎቹን ማካሄዱን እንደሚቀጥል አስታውቋል። #ካፒታል
@tikvahethiopia
❤434😡200🤔42😱27😢22🙏8💔5😭3
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#MoE
" ውጤት በቅርቡ ይፋ ይደረጋል " - ትምህርት ሚኒስቴር
በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ሲሰጥ የነበረው የ2018 የድህረ ምረቃ ትምህርት መግቢያ ፈተና መጠናቀቁን ትምህርት ሚኒስቴር አሳውቋል።
ፈተናው ለመውሰድ ከተመዘገቡ 29 ሺ491 አመልካቾች መካከል 96 በመቶ ፈተናውን እንደወሰዱ አመልክቷል።
በ2017 ዓ.ም. መጨረሻ ላይ ይሰጥ የነበረው የድህረ ምረቃ መግቢያ ፈተና በተለያዩ ምክንያቶች ተራዝሞ ጥቅምት 3 ቀን 2018 ዓ.ም. በ53 የፈተና ማዕከላት ነው የተሰጠው።
የፈተናው ውጤትም በቅርቡ ለተማሪዎች ይፋ እንደሚደረግ ሚኒስቴሩ አመልክቷል።
የድህረ ምረቃ ትምህርት መግቢያ ፈተና (NGAT) ከሌሎች አገር አቀፍ ፈተናዎች የተለየና የ2ኛ እና የ3ኛ ዲግሪ ትምህርታቸውን መቀጠል የሚፈልጉ አመልካቾች ለትምህርቱ ምን ያክል ዝግጁ ናቸው የሚለውን ለማረጋገጥ ደረጃውን ጠብቆ የሚሰጥ ምዘና ነው።
#DrEbaMijena
መረጃው የትምህርት ሚኒስቴር ነው።
@tikvahethiopia
" ውጤት በቅርቡ ይፋ ይደረጋል " - ትምህርት ሚኒስቴር
በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ሲሰጥ የነበረው የ2018 የድህረ ምረቃ ትምህርት መግቢያ ፈተና መጠናቀቁን ትምህርት ሚኒስቴር አሳውቋል።
ፈተናው ለመውሰድ ከተመዘገቡ 29 ሺ491 አመልካቾች መካከል 96 በመቶ ፈተናውን እንደወሰዱ አመልክቷል።
በ2017 ዓ.ም. መጨረሻ ላይ ይሰጥ የነበረው የድህረ ምረቃ መግቢያ ፈተና በተለያዩ ምክንያቶች ተራዝሞ ጥቅምት 3 ቀን 2018 ዓ.ም. በ53 የፈተና ማዕከላት ነው የተሰጠው።
የፈተናው ውጤትም በቅርቡ ለተማሪዎች ይፋ እንደሚደረግ ሚኒስቴሩ አመልክቷል።
የድህረ ምረቃ ትምህርት መግቢያ ፈተና (NGAT) ከሌሎች አገር አቀፍ ፈተናዎች የተለየና የ2ኛ እና የ3ኛ ዲግሪ ትምህርታቸውን መቀጠል የሚፈልጉ አመልካቾች ለትምህርቱ ምን ያክል ዝግጁ ናቸው የሚለውን ለማረጋገጥ ደረጃውን ጠብቆ የሚሰጥ ምዘና ነው።
#DrEbaMijena
መረጃው የትምህርት ሚኒስቴር ነው።
@tikvahethiopia
❤973🙏82🤔46😡43😭40👏17😢14🕊12🥰11💔9😱2
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update የትግራይ ኃይል አባላት ሰልፍ ዛሬም በሌላ አቅጣጫ ሰልፍ ማድረግ ቀጥለዋል። በመቐለና ዙሪያዋ የሚገኙ የትግራይ ኃይል አባላይ ትናንት ሰኞ ጥቅምት 3/2018 ዓ.ም ከጥዋቱ 2:30 እስከ ምሽት ሰላማዊ ሰልፍ አካሂደው ነበር። በዚያው ቀን ምሸት የሰላማዊ ሰልፈኞቹ ተወካዮች የጊዚያዊ አስተዳደሩ ፕሬዚዳንት ታደሰ ወረደ (ሌ/ጀ) ከሚገኙባቸው የህወሓትና የሰራዊት አዛዦች ቢነጋገሩም ፤ ስለተደረሰው…
#Tigray
በመቐለና ዙሪያዋ የሚገኙ የትግራይ ኃይል አባላት ትናንት ሰኞ ጥቅምት 3/2018 ዓ.ም የጀመሩት የመኪና መንገድ በመዝጋት የተደገፈ የተቃውሞ ሰልፍ ዛሬም በሌሎች አቅጣጫዎች ሲካሄድ ውሏል።
ዛሬ ማክሰኞ ጥቅምት 4/2018 ዓ.ም ከትግራይ ምስራቃዊ ዞን ወደ መቐለ ከተማ የሚያስገባው ዋና አስፋልት ከጥዋት ጀምሮ ተዘግቶ ነበር።።
ሰልፈኞቹ ኣጉላዕና ጉርመዶ በሚባሉ ሁለት ቦታዎች መንገድ በመዝጋታቸው ምክንያት መኪኖች ቆመው ተጓዦች መስተጓጎላቸው የታወቀ ሲሆን ማምሻውን መንገዶች ተከፍተዋል ብለዋል ተጓዦች።
መንገድ በመዘጋቱ ምክንያት ከፍተኛ እንግልት እንደደረሰባቸውና ሰላማዊ ሰልፈኞቹ ተቋውሟቸውን ከመንገድ መዝጋት ውጪ ቢያደርጉት የሚል ምክረ ሃሳብ ሰጥቷል።
ዛሬ ጥቅምት 4/2018 ዓ.ም ከሰዓት በኃላ መግለጫ ያወጣው የትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደር ፕሬዜዳንት ፅህፈት ቤት " የሰራዊት አባላት ሰልፈኞቹ ጥያቄ ልክ ነው " ብሏል።
የሰላማዊ ሰልፈኞቹ ጥያቄዎች ኑሮን ማሻሻልና የደመወዝ ጭማሪ መሆናቸው ያስታወቀውና የተቀበለው የጊዚያዊ አስተዳዳሩ ጥያቄዎቹ እንዲፈቱ ከሚመለከታቸው አካላት በመቀናጀት እሰራለሁ ብሏል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
መቐለ
#TikvahEthiopiaFamilyMekelle
@tikvahethiopia
በመቐለና ዙሪያዋ የሚገኙ የትግራይ ኃይል አባላት ትናንት ሰኞ ጥቅምት 3/2018 ዓ.ም የጀመሩት የመኪና መንገድ በመዝጋት የተደገፈ የተቃውሞ ሰልፍ ዛሬም በሌሎች አቅጣጫዎች ሲካሄድ ውሏል።
ዛሬ ማክሰኞ ጥቅምት 4/2018 ዓ.ም ከትግራይ ምስራቃዊ ዞን ወደ መቐለ ከተማ የሚያስገባው ዋና አስፋልት ከጥዋት ጀምሮ ተዘግቶ ነበር።።
ሰልፈኞቹ ኣጉላዕና ጉርመዶ በሚባሉ ሁለት ቦታዎች መንገድ በመዝጋታቸው ምክንያት መኪኖች ቆመው ተጓዦች መስተጓጎላቸው የታወቀ ሲሆን ማምሻውን መንገዶች ተከፍተዋል ብለዋል ተጓዦች።
መንገድ በመዘጋቱ ምክንያት ከፍተኛ እንግልት እንደደረሰባቸውና ሰላማዊ ሰልፈኞቹ ተቋውሟቸውን ከመንገድ መዝጋት ውጪ ቢያደርጉት የሚል ምክረ ሃሳብ ሰጥቷል።
ዛሬ ጥቅምት 4/2018 ዓ.ም ከሰዓት በኃላ መግለጫ ያወጣው የትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደር ፕሬዜዳንት ፅህፈት ቤት " የሰራዊት አባላት ሰልፈኞቹ ጥያቄ ልክ ነው " ብሏል።
የሰላማዊ ሰልፈኞቹ ጥያቄዎች ኑሮን ማሻሻልና የደመወዝ ጭማሪ መሆናቸው ያስታወቀውና የተቀበለው የጊዚያዊ አስተዳዳሩ ጥያቄዎቹ እንዲፈቱ ከሚመለከታቸው አካላት በመቀናጀት እሰራለሁ ብሏል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
መቐለ
#TikvahEthiopiaFamilyMekelle
@tikvahethiopia
1❤528🕊56👏24😡17🙏9😭8🥰2😱1
