Telegram Web Link
#Haile

“ በየቦታው የሰራናቸውን ሆቴሎች አይነት አንዷን ድሬዳዋ እናስቀምጣለን ብለን አቅደናል” - ሻለቃ ኃይሌ

➡️ “ደብረ ብርሃን ሆቴል የመጨረሻው ምዕራፍ ላይ ነው፤ በቀጣዮቹ ሦስት፣ አራት ወራት ወደ ሥራ ይገባል” - አቶ ጋዲሳ ግርማ

አትሌት ሻለቃ ኃይሌ ገ/ስላሴ በሆቴልና ሪዞርት ግንባታ ረገድ ወደ ድሬዳዋ ከተማ እየገቡ መሆኑን፣ የከተማዋን ከንቲባና ካቢኔውን አግኝተውም ቃል እንደተገባላቸው ዛሬ ገልጸዋል፡፡

የኃይሌ ሆቴሎች ሪዞርቶች ግሩፕ ማኔጅንግ ዳይሬክተር አቶ ጋዲሳ ግርማ በበኩላቸው፣ ድሬዳዋ ላይ የሆቴልና ሪዞት ግንባታ በቅርቡ እንደሚጀመር ዛሬ ምሽት ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አረጋግጠዋል፡፡

ሻለቃ ኃይሌ፣ በድሬ ከተማ ተገኝተው ባደረጉት ንግግር፣ “ኃይሌ ሆቴልና ሪዞርት በየከተማዎቹ እየገነባን ነን፡፡ እስካሁን በአስር ከተሞች ተከፍተዋል፡፡ ሌላ ሦስት ደግሞ በግንባታ ላይ ናቸው፡፡ አሁን ደግሞ የድሬው 14ኛው ይሆናል” ብለዋል፡፡

“መምጣት ካለብን በጣም የዘገየንበት ቦታ ነው፡፡ ግን አሁን ድሬዳዋ እየገባን ነው፤ ክቡር ከንቲባውንም ካቢኔውንም አግኝተን በጣም ጥሩ ቃል ገብተውልናል” ሲሉም ተናግረዋል፡፡

ሥራው ቶሎ እንደሚጀመር ጠቁመው፣ “በየቦታው የሰራናቸውን ሆቴሎች አይነት አንዷን ድሬዳዋ እናስቀምጣለን ብለን አቅደናል፡፡ መጀመሪያ ስናጠና ቢዝነሱ እንዴት ነው ? የሚለውን ነው፤ ድሬዳዋም ከኢትዮጵያ ቀደምት ከተሞች አንዷ ነች፤ በቢዝነሱም” ነው ያሉት፡፡

ስለድሬዳዋው ሆቴል ግንባታ ተጨማሪ ማብራሪያ የጠየቅናቸው የኃይሌ ሆቴሎች ሪዞርቶች ግሩፕ ማኔጅንግ ዳይሬክተር አቶ ጋዲሳ ግርማ፣ “የቦታ ልየታና ገበያውን ለማየት ሂደን ነበር ዛሬ፡፡ ኢንቨስትመንት ላይ የሚሰሩ የመንግስት አካላት ቦታዎችን አሳይተውናል፤ ወደ ቀጣዩ ሂደት እንቀጥላለን” ብለዋል፡፡

ግንባታውን በቅርቡ የመጀመር እቅድ እንዳላቸው፣ በዚህ ቀን ይጀመራል የሚል ቀን ገና እንዳላስቀመጡ ገልጸው፣ “የመሬት ርክክብ ባለቀ በማግስቱ ግንባታ እንጀምራለን” ሲሉ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል፡፡

የጎንደርና ደብረ ብርሃን ፕሮጀክቶችን እያጠናቀቁ በመሆኑ ቀጣዩ አቅጣጫ ወደ ድሬ እንደሆነ የጠቆሙት አቶ ጋዲሳ፣ “ደብረ ብርሃን ሆቴል የመጨረሻው ምዕራፍ ላይ ነው ያለው፤ በቀጣዮቹ ሦስት አራት ወራት ውስጥ ወደ ሥራ ይገባል፡፡ የጎንደር ደግሞ ከሰባት ውራት እስከ አንድ አመት ይወስዳል” ብለዋል፡፡

በጎንደሩ ፕሮጀክት የጸጥታው ሁኔታ ምን አይነት እንቅፋት እንዳፈጠረባቸው ማብራሪያ ሲጠየቁም፣ በዚህ ረገድ አስተያየት አለመስጠትን መርጠዋል፡፡

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
2.09K👏292🥰33😡29🙏27🕊23😭17🤔14😢12💔12😱6
የኢትዮጵያ መንግስት ለአካል ጉዳተኞች ጤና-ነክ መልሶ ማቋቋም እና ፆታን ታሳቢ ያደረጉ አገልግሎቶች ተደራሽ መሆናቸውን ለማረጋገጥ አግባብነት ያላቸውን እርምጃዎች በሙሉ ለመውሰድ በአለምአቀፉ የአካል ጉዳተኞች ስምምነት አንቀጽ 25 መሰረት ግዴታዎችን ተቀብሏል! በተለይም የአካል ጉዳተኞች የስነተዋልዶ እና የቤተሰብ እቅድ አገልግሎት መብቶች እውን እንዲሆኑ፤ አካል ጉዳተኞች ጾታዊ ግንኙነት፣ የስነ ተዋልዶ ጤና አገልግሎትን እንዲሁም ስነ ህዝብን መሠረት ያደረገ የህዝብ ጤና ፕሮግራሞችን በሚመለከት ከአድልዎ በጸዳ ሑኔታ እና ከሌሎች ሰዎች ጋር እኩል በሆነ መልኩ አገልግሎቶቹን የማግኘት መብት አላቸው! አካል ጉዳተኞች እነዚህን አገልግሎቶችን በሚያገኙበት ወቅት ለሌሎች ሰዎች እንደሚሰጠው ባለ ተመሳሳይ አይነት፣፣ ጥራትና ደረጃ መሆኑን ማረጋገጥ ይገባል! የስነተዋልዶ እና የቤተሰብ አገልግሎቶች በነፃ ወይም የአካል ጉዳተኞችን የመክፈል አቅምን ያገናዘቡ መሆን አለባቸው!
አካል ጉዳተኞች በአካል ጉዳታቸው ምክንያት አድልዎ ሳይደረግባቸው ሊደረስበት ለሚቻለው ከፍተኛው የጤና ደረጃ ባለቤትነት መብት እንሰራለን!
አካል ጉዳተኞችን ያካተተ የስነተዋልዶ እና የቤተሰብ እቅድ አገልግሎት ስርአት፤ለጤናማ ማህበረሰብ የእድገት እና የጥንካሬ ጉልላት።
የኢትዮጵያ የሕግ ባለሞያ አካል ጉዳተኞች ማህበር


Tel: 9110/ +251115581164
Website:
Facebook,
Twitter:
LinkedIn
346👏22🥰7😢6🙏6😡5😭1
#Kenya

የኬንያው ጉምቱ ፖለቲከኛ ራይላ ኦዲንጋ ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ።

የቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር ራይላ ኦዲንጋ ህንድ ሀገር በህክምና ሲረዱ ቆይተው በ80 ዓመታቸው ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል።

ራይላ ኦዲንጋ ለኬንያ ፕሬዚዳንትነት 5 ጊዜ ዕጩ ሆነው ቢቀርቡም አልተሳካላቸውም።

በተጨማሪ በቅርቡ ለአፍሪካ ኅብረት ኮሚሽን ሊቀመንበርነት ቦታ ቢወዳደሩም ማሸነፍ ሳይችሉ ቀርተዋል።

ለረጅም አመታት በፖለቲካ ውስጥ የቆዩት ኦዲንጋ በኬንያ የበዛ ድጋፍ ያላቸው ሲሆን የኦሬንጅ ዴሞክራቲክ ሙቭመንት መሪ ነበሩ።

ለዴሞክራሲ፣ ለመድብለ ፓርቲ ስርዓት፣ ከህገመንግስት ሪፎርም በመታገል ይታወቃል።

ከዚሁ ጋር በተያያዘ የኢፌዴሪ ጠ/ሚ ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) በራይላ ኦዲንጋ ህልፈት የተሰማቸውን ሀዘን በኢትዮጵያ ህዝብ ስም ገልጸዋል።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
468😭413🕊66😢31👏27😱13🙏13🤔12💔7😡4🥰1
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#Update

ወደ መቐለ የሚያመሩ መንገዶች ዛሬም ለሁለተኛ ቀን በሁለት አቅጣጫ በትግራይ ኃይል ሰልፈኞች ተዘግተዋል።

የተዘጉት መንገዶች በትግራይ ምስራቃዊ ዞን ከመቐለ በ35 ኪሎ ሜትር ርቀት በምትገኘው የኣጉላዕ ከተማ ፤ በደቡባዊ ዞን ከመቐለ 100 ኪሎ ሜትር አከባቢ በምትርቀው የመኾኒ ከተማ መሆኑ ቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ መረጃ ደርሶታል።

በተጨማሪ በሰሜን ምዕራብ ዞን ወደ እንዳስላሰ-ሽረ ከተማ የሚወስደው መንገድ ከከተማዋ 20 ኪሎ ሜትር ርቀት በሚገኘው እንዳባጉና ከተማ በሰልፈኞች ተዘግቷል።

ሰልፈኞቹ ጥቅምት 3/2018 ዓ.ም ከመቐለ ከተማ ወደ አሉላ አባነጋ አውሮፕላን ማረፍያ የሚወስደው ዋና መንገድ ዘግተው ውለው በዚያው ቀን ምሸት ከጊዚያዊ አስተዳደሩ ፕረዜዳንት ታደሰ ወረደ (ሌ/ጀ) ተወያይተው " ጥያቄያችሁ ልክ ነው ፤ በየደረጃው ይመለሳል " ተብለው ነበር።

ጉዳዩን ተከታትለን መረጃውን የምንልክ ይሆናል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
መቐለ
#TikvahEthiopiaFamilyMekelle

@tikvahethiopia            
500👏56🕊36😭34😡21🤔12😱6
‎" የ12 ዓመት ህጻን ልጅ ላይ የግብረ ስጋ ድፍረት ወንጀል የፈፀመው የ65 ዓመት አዛዉንት የ23 ዓመት ፅኑ እስራት ተፈርዶበታል " - የይርጋለም ከተማ ፖሊስ

➡️ ‎" ግለሰቡ የኤችአይቪ/ኤድስ ታማሚና የመድሐኒት ተጠቃሚ ነበር "


‎በሲዳማ ክልል ማዕከላዊ ሲዳማ ዞን የይርጋለም ከተማ አስተዳደር የ12 ዓመት ህጻን ልጅ ላይ የግብረ ስጋ ድፍረት ወንጀል የፈጸመው የ65 ዓመት ግለሰብ የ23 ዓመት እስራት ተፈርዶበታል።

የከተማው ፖሊስ አዛዥ ኢንስፔክተር ደግነት ደስታ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ እንደገለፁት ፥ የከተማው ነዋሪ የሆነ አቶ ናስር ኑር የተባለ የ65 ዓመት ግለሰብ ነሐሴ 6/12/2017 ዓ.ም በከተማው 06 ቀበሌ የ12 አመት ታዳጊ ላይ የግብረ ስጋ ድፍረት መፈጸሙን የሚገለፅ መረጃ ለፖሊስ ይመጣል።

ፖሊስም ጉዳዩን ከፍትህ መዋቅር ጋር በመመርመር በሰውና በህክምና ማስረጃ በማጣራት ለከተማው ዐቃቤ ህግ አስተላልፏል።

‎በምርመራና መረጃ በማሰባሰብ ሂደትም ግለሰቡ ይህን አስነዋሪ ድርጊት ከመፈፀሙ ባሻገር የኤችአይቪ /ኤድስ (HIV/AIDS) ታማሚና እንደሆነና እራሱን አውቆ የመድሐኒት ተጠቃሚ እንደነበር ማወቅ መቻሉን አዛዡ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል።

‎ጉዳዩን የያዘዉ የይርጋለም ከተማ አስተዳደር ዐቃቤ ህግ በተከሳሹ ላይ ያቀረበውን የክስ መዝገብ ሲያጣራ የቆየው የከተማ አስተዳደር መጀመሪያ ደረጃ ፍ/ቤት ተከሳሹን " ጥፋተኛ ነህ " በማለት ተከሳሹ  እንዲከላከል ቢጠይቅም መከላከል አልቻለም።

‎እንዲሁም የኤችአይቪ/ኤድስ ታማሚ መሆኑን እያወቀ በታዳጊዋ ላይ በፈፀመው አስነዋሪ ድርጊት ጥፋቱን በማክበድ በቀን 4/2/2018 በዋለው ወንጀል ችሎት ተከሳሹን በ23 ዓመት ከ6 ወር ፅኑ እስራት እንዲቀጣ ወስኗል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
ሀዋሳ
#TikvahEthiopiaFamilyHawassa

@tikvahethiopia
1😡4.65K1.05K😭668💔236😢164😱62👏57🤔52🙏49🕊30🥰9
#SafaricomEthiopia

እያንዳንዱ የሚገዙት የበሽ ጥቅል ወደ ሚሊየነርነት አንድ እርምጃ ያስጠጋዎታል! ከእለታዊ ጉርሻዎች እስከ በሕይወት ቀያሪ ሽልማቶች ይንበሽበሹ!

📲 የM-PESA መተግበሪያን አሁኑኑ ያውርዱ፡ https://onelink.to/ewsb22

የቴሌግራም ቦታችን👉🏽 https://www.tg-me.com/official_safaricomet_bot

ወደ *777*0# ይደውሉ ወይም በM-PESA የበሽ ጥቅል ይግዙ!

#MPESASafaricom
#furtheraheadtogether
#besh
169🥰4🙏4😢2😭2😡2😱1
TIKVAH-ETHIOPIA
በአፍሪካዊቷ ሀገር #ማዳጋስካር 🇲🇬 የሆነው ምንድነው ? (በአጭሩ) - ከ15 ቀን ገደማ በፊት የማዳጋስካር ወጣቶች የመሩት ተቃውሞ ይቀሰቀሳል። ይኸው ተቃውሞው በዋና ከተማዋ አንታናናሪቮ ካለ የኃይል መቆራረጥ እና የውሃ እጥረት ጋር የሚያያዝ ነበር። የወጣቶቹ ተቃውሞ ' Gen Z Madagascar ' የሚል ስያሜ ነበረው። - በኃላ የወጣቶቹ ተቃውሞ ቁጣ የታከለበትና መልካም አስተዳደር እንዲሰፍን፣…
#Madagascar

" እኛ ስልጠን ይዘናል " - የማዳጋስካር ጦር

" ህ ገወጥ መግለጫ ነው " - የፕሬዝዳንት ፅሕፈት ቤት

የማዳጋስካር ጦር የሀገሪቱን ስልጣን መቆጣጠሩን ገለጸ።

የጦሩ ዋና መሪ ኮሎኔል ሚኬል ራኔድሪኒራ በመድናዋ በሚገኘው አንታናሪቮ ፕሬዝዳንታዊ ፅህፈት ቤት በሰጡት መግለጫ " እኛ ስልጠን ይዘናል " ብለዋል።

" በቅርቡ መንግስት የሚያዋቅሩ ጠቅላይ ሚኒስትር እንመርጣለን " ሲሉ ተናግረዋል።

የፕሬዝዳንት ራጆሊና ፅህፈት ቤት በበኩሉ የጦሩን እርምጃ፣ " መፈንቅለ መንግስት ተፈፅሟል፣ ህገወጥ መግለጫ ነው " ሲል ተቃውሟል።

ፅህፈት ቤቱ አክሎ፣ "ፕሬዝዳንት ራጆሊና ለደህንነታቸው ሲባል ደህንነቱ ወደተጠበቀ ቦታ ተዘዋውረዋል" ብሏል።  

ፕሬዝዳንት አንድሬ ራጆሊና ሀገር ጥለው በፈረንሳይ የጦር አውሮፕላን ሸሽተዋል ቢባልም አስተባብለዋል።
#sana

Via @ThiqahEth
419👏88🤔38😭21😢6😡6🙏5🕊3🥰1😱1
2025/10/25 03:18:54
Back to Top
HTML Embed Code: