በዓመት ከሚያስፈልገው የኮንዶም መጠን ወደ ሀገር እየገባ ያለው 40 በመቶው ብቻ መሆኑ ተገለጸ።
በኢትዮጵያ በዓመት ከ270 እስከ 300 ሚሊየን ኮንዶም ያስፈልጋል ቢባልም ወደ አገር ውስጥ የሚገባው ከ1መቶ ሚሊየን በታች ወይም 40 በመቶ ብቻ መሆኑ ተገልጿል።
ከዚህ ቀደም ወደ አገር ውስጥ በሚገባ የኮንዶም ምርት ላይ የሚጣሉ የቀረጥ፤ የኤክሳይዝም ሆነ የተጨማሪ ዕሴት ታክስ አሁን ላይ በመነሳታቸው የግል አስመጪዎች በዘርፉ እንዲሳተፉ አበታች ነው ተብሏል።
ይህ የተገለጸው ይህ የተባለው ኤ ኤች ኤፍ ኢትዮጵያ ከጤና ሚኒስቴር ፣ ከህክምና ግብዓት አምራቾች፣ አከፋፋዮች፣ እንዲሁም ከሌሎች ተቋማት ጋር በመሆን ባዘጋጀው ስለ ኮንዶም ፖሊሲ ፣ጥራት እና የገበያ ስርዓት ላይ ትኩረት ያደረገ ውይይት ላይ ነው።
በመድረኩ የተመዘገቡ የኮንዶም አስመጪዎች እና የህክምና ግብዓት አምራች እና አስመጪዎች ወደ አገር ውስጥ ለሚያስገቡት የኮንዶም ምርት ተጥሎ የነበረው የ35 በመቶ ቀረጥ መነሳቱ ነው የተገለጸው።
በተጨማሪም በሀገር ውስጥ ኮንዶም የሚያመርቱ ፋብሪካዎች ለ5 ዓመት የገቢ ግብር ታክስ እንደማይጠየቁ እና የኮንስትራክሽን ዕቃዎች፣ ስፔር ፓርት እና ሌላ ወደ አገር ውስጥ ማስገባት የሚፈልጉትን ግብዓት ማስገባት ይችላሉ ተብሏል።
ከጊዜ ወደ ጊዜ የኤች አይ ቪ ሥርጭት በሀገራችን እየጨመረ መምጣቱ ሲገለጽ ይህም በአገራችን በየዓመቱ ወደ 8 ሺህ የሚጠጉ ሰዎች በቫይረሱ እንደሚያዙ መረጃዎች ያሳያሉ።
ዘገባው የኢትዮ ኤፍ ኤም 107.8 ነው
@TikvahethMagazine
በኢትዮጵያ በዓመት ከ270 እስከ 300 ሚሊየን ኮንዶም ያስፈልጋል ቢባልም ወደ አገር ውስጥ የሚገባው ከ1መቶ ሚሊየን በታች ወይም 40 በመቶ ብቻ መሆኑ ተገልጿል።
ከዚህ ቀደም ወደ አገር ውስጥ በሚገባ የኮንዶም ምርት ላይ የሚጣሉ የቀረጥ፤ የኤክሳይዝም ሆነ የተጨማሪ ዕሴት ታክስ አሁን ላይ በመነሳታቸው የግል አስመጪዎች በዘርፉ እንዲሳተፉ አበታች ነው ተብሏል።
ይህ የተገለጸው ይህ የተባለው ኤ ኤች ኤፍ ኢትዮጵያ ከጤና ሚኒስቴር ፣ ከህክምና ግብዓት አምራቾች፣ አከፋፋዮች፣ እንዲሁም ከሌሎች ተቋማት ጋር በመሆን ባዘጋጀው ስለ ኮንዶም ፖሊሲ ፣ጥራት እና የገበያ ስርዓት ላይ ትኩረት ያደረገ ውይይት ላይ ነው።
በመድረኩ የተመዘገቡ የኮንዶም አስመጪዎች እና የህክምና ግብዓት አምራች እና አስመጪዎች ወደ አገር ውስጥ ለሚያስገቡት የኮንዶም ምርት ተጥሎ የነበረው የ35 በመቶ ቀረጥ መነሳቱ ነው የተገለጸው።
በተጨማሪም በሀገር ውስጥ ኮንዶም የሚያመርቱ ፋብሪካዎች ለ5 ዓመት የገቢ ግብር ታክስ እንደማይጠየቁ እና የኮንስትራክሽን ዕቃዎች፣ ስፔር ፓርት እና ሌላ ወደ አገር ውስጥ ማስገባት የሚፈልጉትን ግብዓት ማስገባት ይችላሉ ተብሏል።
ከጊዜ ወደ ጊዜ የኤች አይ ቪ ሥርጭት በሀገራችን እየጨመረ መምጣቱ ሲገለጽ ይህም በአገራችን በየዓመቱ ወደ 8 ሺህ የሚጠጉ ሰዎች በቫይረሱ እንደሚያዙ መረጃዎች ያሳያሉ።
ዘገባው የኢትዮ ኤፍ ኤም 107.8 ነው
@TikvahethMagazine
🤣160❤53👎6😢4🙏1
ሚኒስትሩ ሀሰተኛ የትምህርት ማስረጃ እንዳቀረቡ ዘገባ ከተሰራባቸው በኋላ ከኃላፊነታቸው ለቀዋል።
ኡቼ ንናጂ የናይጄሪያ የሳይንስ፣ ቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን ሚኒስቴር ሆነው በ2023 የተሾሙ ሹመኛ ነበሩ።
ፕሪሚየም በተባለ ጋዜጣ የሁለት ዓመት ፈጀ በተባለ ምርምራው ሀሰተኛ የትምህርት ማስረጃ እንዳቀረቡ በጋዜጣው ከዘገበ በኋላ ከኃላፊነታቸው በገዛ ፈቃዳቸው ለቀዋል።
ሚኒስትሩ፥ በ2023 ሹመት ሲሰጣቸው ሀሰተኛ የትምህርት ማስረጃቸውን ማስገባታቸው ሲነገር እሳቸው ግን በማይክሮባዮሎጂ የመጀመሪያ ድግሪ አለኝ በማለት የምርመራ ዘገባውን አጣጥለዋል።
ሚኒስትሩ ተማርኩ ያሉበት ዩኒቨርሲቲ እሳቸው የመጀመሪያ ድግሪዬን ተመረቅኩ ባሉበት በ1985 ስለመመረቃቸው ምንም ማስረጃ እንደሌለ ለጋዜጣው አሳውቋል ተብሏል።
በዩኒቨርሲቲው ውስጥ ያለ አመራር ንናጂ ወደ ዩኒቨርሲቲው በ1981 እንደገባ ግን ትምህርቱን እንዳልጨረሰ ተናግረዋል።
በናይጄሪያ ሚኒስትሮች መባረራቸውና ከኃላፊነት መልቀቅ ያልተለመደ ነው ሲባል የአሁኑ ፕሬዚዳንት ቦላ ቲኑቡ በ2023 ወደ ስልጣን ከመጡ በኋላ ባለፈው አመት ከሙስና ጋር በተያያዘ ከተነሱት የሰብዓዊ ጉዳዮችና ድህነት ቅነሳ ሚኒስትር ቀጥሎ ንናጂ ከኃላፊነታቸው የለቀቁ ሁለተኛ ሚኒስተር ሆነዋል።
ከቲኑቡ በፊት የነበሩት መሐመዱ ቡሃሪም በ8 አመት የስልጣን ቆይታ ወቅት ያባረሩት ሁለት ሚኒስትሮችን ብቻ ነበር።
የሃሰተኛ የትምህርት ማስረጃውን በተመለከተ ተቃዋሚ ፓርቲዎች ገለልተኛ ምርመራ እንዲደረግ ጠይቀዋል።
ዘገባው የቢቢሲ ነው።
@TikvahethMagazine
ኡቼ ንናጂ የናይጄሪያ የሳይንስ፣ ቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን ሚኒስቴር ሆነው በ2023 የተሾሙ ሹመኛ ነበሩ።
ፕሪሚየም በተባለ ጋዜጣ የሁለት ዓመት ፈጀ በተባለ ምርምራው ሀሰተኛ የትምህርት ማስረጃ እንዳቀረቡ በጋዜጣው ከዘገበ በኋላ ከኃላፊነታቸው በገዛ ፈቃዳቸው ለቀዋል።
ሚኒስትሩ፥ በ2023 ሹመት ሲሰጣቸው ሀሰተኛ የትምህርት ማስረጃቸውን ማስገባታቸው ሲነገር እሳቸው ግን በማይክሮባዮሎጂ የመጀመሪያ ድግሪ አለኝ በማለት የምርመራ ዘገባውን አጣጥለዋል።
ሚኒስትሩ ተማርኩ ያሉበት ዩኒቨርሲቲ እሳቸው የመጀመሪያ ድግሪዬን ተመረቅኩ ባሉበት በ1985 ስለመመረቃቸው ምንም ማስረጃ እንደሌለ ለጋዜጣው አሳውቋል ተብሏል።
በዩኒቨርሲቲው ውስጥ ያለ አመራር ንናጂ ወደ ዩኒቨርሲቲው በ1981 እንደገባ ግን ትምህርቱን እንዳልጨረሰ ተናግረዋል።
በናይጄሪያ ሚኒስትሮች መባረራቸውና ከኃላፊነት መልቀቅ ያልተለመደ ነው ሲባል የአሁኑ ፕሬዚዳንት ቦላ ቲኑቡ በ2023 ወደ ስልጣን ከመጡ በኋላ ባለፈው አመት ከሙስና ጋር በተያያዘ ከተነሱት የሰብዓዊ ጉዳዮችና ድህነት ቅነሳ ሚኒስትር ቀጥሎ ንናጂ ከኃላፊነታቸው የለቀቁ ሁለተኛ ሚኒስተር ሆነዋል።
ከቲኑቡ በፊት የነበሩት መሐመዱ ቡሃሪም በ8 አመት የስልጣን ቆይታ ወቅት ያባረሩት ሁለት ሚኒስትሮችን ብቻ ነበር።
የሃሰተኛ የትምህርት ማስረጃውን በተመለከተ ተቃዋሚ ፓርቲዎች ገለልተኛ ምርመራ እንዲደረግ ጠይቀዋል።
ዘገባው የቢቢሲ ነው።
@TikvahethMagazine
❤57🤣26👏4👍3💔2🔥1🤔1🕊1
የጃፖን መንግስት በ3.5 ሚልዮን ዶላር የተገዙ 13 ተንቀሳቃሽ ክሊኒክ ያላቸው አምቡላንሶችን በድጋፍ መልክ ማበርከቱን የጤና ሚኒስቴር አስታወቀ።
@TikvahethMagazine
@TikvahethMagazine
❤143🙏29👏6🤔6🤷♂5👍3
📍 ፒያሳ ላይ የንግድ ሱቅ
3ኛ ፎቅ
➣ ቅድመ ክፍያ ሲከፍሉ 15% ቅናሽ 3,570,000 ብር ጠቅላላ ዋጋ
➣ 100% ለከፈለ 25% ቅናሽ 3,150,000 ብር ጠቅላላ ዋጋ
2ኛ ፎቅ
➣ ቅድመ ክፍያ ሲከፍሉ 15% ቅናሽ
4,080,000 ብር ጠቅላላ ዋጋ
➣ 100% ለከፈለ 25% ቅናሽ 3,600,000 ብር ጠቅላላ ዋጋ
1ኛ ፎቅ
➣ ቅድመ ክፍያ ሲከፍሉ 15% ቅናሽ 4,675,000 ብር ጠቅላላ ዋጋ
➣100% ለከፈለ 25% ቅናሽ 4,125,000 ብር ጠቅላላ ዋጋ
ግራውንድ
➣ቅድመ ክፍያ ሲከፍሉ 15% ቅናሽ 5,950,000 ብር ጠቅላላ ዋጋ
➣ 100% ለከፈለ 25% ቅናሽ 5,250,000 ብር ጠቅላላ ዋጋ
ለበለጠ መረጃ
👇
☎️+251986687513
WhatsApp:- +251986687513
Email:- [email protected]
3ኛ ፎቅ
➣ ቅድመ ክፍያ ሲከፍሉ 15% ቅናሽ 3,570,000 ብር ጠቅላላ ዋጋ
➣ 100% ለከፈለ 25% ቅናሽ 3,150,000 ብር ጠቅላላ ዋጋ
2ኛ ፎቅ
➣ ቅድመ ክፍያ ሲከፍሉ 15% ቅናሽ
4,080,000 ብር ጠቅላላ ዋጋ
➣ 100% ለከፈለ 25% ቅናሽ 3,600,000 ብር ጠቅላላ ዋጋ
1ኛ ፎቅ
➣ ቅድመ ክፍያ ሲከፍሉ 15% ቅናሽ 4,675,000 ብር ጠቅላላ ዋጋ
➣100% ለከፈለ 25% ቅናሽ 4,125,000 ብር ጠቅላላ ዋጋ
ግራውንድ
➣ቅድመ ክፍያ ሲከፍሉ 15% ቅናሽ 5,950,000 ብር ጠቅላላ ዋጋ
➣ 100% ለከፈለ 25% ቅናሽ 5,250,000 ብር ጠቅላላ ዋጋ
ለበለጠ መረጃ
👇
☎️+251986687513
WhatsApp:- +251986687513
Email:- [email protected]
❤22
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
#SamiTech
አዳዲስ ላፕቶፕች ከአንድ ዓመት ዋስትና ጋር!!
@samcomptech
በጥራት፣ በብራንድና በባትሪ ቆይታ አስተማማኝ የሆኑ የተለያዩ ሞዴል ላፕቶፖች በፈለጉት ስክሪን መጠን፣ ኮር አይ እና ጀነሬሽን አሉን።
ላፕቶፕ ከመገዛትዎ በፊት ማወቅ ያለባችሁን ወሳኝ ነገሮች እናስረዳለን። በላፕቶፖቻችን ጥራት ላይ አንደራደርም!
ለቢሮዎች፣ ለተማሪዎች፣ ለዲዛይን ባለሙያዎች፣ ለጌመሮች ወ.ዘ.ተ. ሁሉም አሉን።
የዕቃዎች ዋጋ፣ ዓይነት እና አድራሻ ለማግኘት 👉 @samcomptech
@sww2844
0928442662 / 0940141114
Telgram
👇
https://www.tg-me.com/samcomptech
አዳዲስ ላፕቶፕች ከአንድ ዓመት ዋስትና ጋር!!
@samcomptech
በጥራት፣ በብራንድና በባትሪ ቆይታ አስተማማኝ የሆኑ የተለያዩ ሞዴል ላፕቶፖች በፈለጉት ስክሪን መጠን፣ ኮር አይ እና ጀነሬሽን አሉን።
ላፕቶፕ ከመገዛትዎ በፊት ማወቅ ያለባችሁን ወሳኝ ነገሮች እናስረዳለን። በላፕቶፖቻችን ጥራት ላይ አንደራደርም!
ለቢሮዎች፣ ለተማሪዎች፣ ለዲዛይን ባለሙያዎች፣ ለጌመሮች ወ.ዘ.ተ. ሁሉም አሉን።
የዕቃዎች ዋጋ፣ ዓይነት እና አድራሻ ለማግኘት 👉 @samcomptech
@sww2844
0928442662 / 0940141114
Telgram
👇
https://www.tg-me.com/samcomptech
❤9
TIKVAH-MAGAZINE
ዶናልድ ትራምፕ እስራኤልና ሃማስ በጋዛ የመጀመሪያ ዙር የሰላም ስምምነት ላይ መድረሳቸውን አስታወቁ። ትራምፕ " ሁሉም ታጋቾች ይለቀቃሉ፤ እስራኤልም በስምምነቱ መሰረት ጦሯን ታስወጣለች" ብለዋል። ሃማስ ስምምነቱ መፈፀሙን አስታውቆ እስራኤል የምትለቃቸውን እስረኞችን ዝርዝር አለማወቁን ገልጿል። የእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤኒያሚን ኔታኔያሁ " ቀኑ ለእስራኤል ታላቅ ቀን ነው " ብለዋል። የተኩስ…
#Update
የእስራኤል መንግሥት የተኩስ ማቆም እና ታጋቾችን እና እስረኞችን ወደ መፍታት የሚያመራውን የጋዛ ስምምነት የመጀመሪያ ምዕራፍ አጽድቋል።
የእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ አርብ ዕለት በኤክስ ገጻቸው ላይ "መንግሥት አሁን ሁሉንም ታጋቾች (በሕይወት ያሉትን እና የሞቱትን) የሚፈቱበትን ማዕቀፍ አጽድቋል" ሲሉ ጽፈዋል።
የእስራኤል ጦር 53 በመቶ ጋዛን ወደ ሚቆጣጠርበት መስመር ይወጣል።
ሐማስ በሕይወት ያሉ 20 ታጋቾችን በ72 ሰዓታት ውስጥ መልቀቅ አለበት። በመቀጠልም የሞቱትን የ28 ታጋቾች አስከሬን መመለስ ይጠበቅበታል።
እስራኤል በበኩሏ 250 የሚጠጉ ፍልስጤማውያን የዕድሜ ልክ እስረኞችን እና ከጋዛ የተያዙ አንድ ሺህ 700 እስረኞችን እንደምትለቅ የፍልስጤም ምንጭ መግለጹን ቢቢሲ ዘግቧል።
@TikvahethMagazine
የእስራኤል መንግሥት የተኩስ ማቆም እና ታጋቾችን እና እስረኞችን ወደ መፍታት የሚያመራውን የጋዛ ስምምነት የመጀመሪያ ምዕራፍ አጽድቋል።
የእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ አርብ ዕለት በኤክስ ገጻቸው ላይ "መንግሥት አሁን ሁሉንም ታጋቾች (በሕይወት ያሉትን እና የሞቱትን) የሚፈቱበትን ማዕቀፍ አጽድቋል" ሲሉ ጽፈዋል።
የእስራኤል ጦር 53 በመቶ ጋዛን ወደ ሚቆጣጠርበት መስመር ይወጣል።
ሐማስ በሕይወት ያሉ 20 ታጋቾችን በ72 ሰዓታት ውስጥ መልቀቅ አለበት። በመቀጠልም የሞቱትን የ28 ታጋቾች አስከሬን መመለስ ይጠበቅበታል።
እስራኤል በበኩሏ 250 የሚጠጉ ፍልስጤማውያን የዕድሜ ልክ እስረኞችን እና ከጋዛ የተያዙ አንድ ሺህ 700 እስረኞችን እንደምትለቅ የፍልስጤም ምንጭ መግለጹን ቢቢሲ ዘግቧል።
@TikvahethMagazine
❤56👏10🕊7
የ2025 የኖቤል የሰላም ሽልማት አሸናፊ ዛሬ ይፋ ይሆናል።
ከ1901 ጀምሮ ለ105 ጊዜ የተሰጠው የኖቤል የሰላም ሽልማት እስካሁን 92 ወንዶች፣ 19 ሴቶችና 28 ተቋማት አሸንፈዋል።
ሽልማቱ ለመጀመሪያ ጊዜ የተሰጠው ለፍሬድሪክ ፓሲና ለቀይ መስቀል መስራቹ ሄነሪ ዱራንት ነበር።
በተደጋጋሚ የኖቤል የሰላም ሽልማት ላቋምኳቸው ጦርነቶች ይገባኛል ሲሉ የቆዩት ፕሬዚዳንት ትራምፕ ለሽልማቱ በእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤኒያሚን ኔታኔያሁና በፓኪስታን መታጨታቸው ይታወሳል።
በዚህ አመት 338 እጩዎች ለሽልማቱ ሲቀርቡ 94 ያህሉ ተቋማት መሆናቸው ተገልጿል።
በኖቤል የሰላም ሽልማት ኮሚቴ በኩል እጩዎቹ እነማን እንደሆኑ ያልተገለፀ ሲሆን አሸናፊው ዕውቅናን ጨምሮ ከ1 ሚሊየን ዶላር በላይ የገንዘብ ሽልማትም ይሰጠዋል።
የኖቤል የሰላም ሽልማት ከተጀመረ ወዲህ እንደ ባራክ ኦባማ ያሉ የአሜሪካ መሪዎች ሲያሸንፉ ከአፍሪካ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) ፣ ኤለን ጆንሰን ሰርሊፍ ከላይቤሪያ፣ ዋንጋሪ ማታይ ከኬንያ ፣ ኮፊ አናን ከጋና፣ አንዋር ሳዳት ከግብፅና ማንዴላ ከደቡብ አፍሪካ ማሸነፋቸው ይታወሳል።
ከግለሰቦች በተጨማሪ ሽልማቱን እንደ የቀይ መስቀል፣ የተመድ የስደተኞች ኮሚሽን፣ የአለም ምግብ ፕሮግራምና የኒውኪሊየር መሳሪያን የማጥፋት ዘመቻ ያሉ ተቋማት አሸንፈዋል።
የዘንድሮው የኖቤል ሽልማት በተለያዩ ዘርፎች አሸናፊዎችን እያሳወቀ ሲሆን በህክምና፣ በፊዚክስና ኬሚስትሪ ዘርፍ ያሸነፉ ተመራማሪዎችም ታውቀዋል።
ዘገባው የCBS ነው።
@TikvahethMagazine
ከ1901 ጀምሮ ለ105 ጊዜ የተሰጠው የኖቤል የሰላም ሽልማት እስካሁን 92 ወንዶች፣ 19 ሴቶችና 28 ተቋማት አሸንፈዋል።
ሽልማቱ ለመጀመሪያ ጊዜ የተሰጠው ለፍሬድሪክ ፓሲና ለቀይ መስቀል መስራቹ ሄነሪ ዱራንት ነበር።
በተደጋጋሚ የኖቤል የሰላም ሽልማት ላቋምኳቸው ጦርነቶች ይገባኛል ሲሉ የቆዩት ፕሬዚዳንት ትራምፕ ለሽልማቱ በእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤኒያሚን ኔታኔያሁና በፓኪስታን መታጨታቸው ይታወሳል።
በዚህ አመት 338 እጩዎች ለሽልማቱ ሲቀርቡ 94 ያህሉ ተቋማት መሆናቸው ተገልጿል።
በኖቤል የሰላም ሽልማት ኮሚቴ በኩል እጩዎቹ እነማን እንደሆኑ ያልተገለፀ ሲሆን አሸናፊው ዕውቅናን ጨምሮ ከ1 ሚሊየን ዶላር በላይ የገንዘብ ሽልማትም ይሰጠዋል።
የኖቤል የሰላም ሽልማት ከተጀመረ ወዲህ እንደ ባራክ ኦባማ ያሉ የአሜሪካ መሪዎች ሲያሸንፉ ከአፍሪካ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) ፣ ኤለን ጆንሰን ሰርሊፍ ከላይቤሪያ፣ ዋንጋሪ ማታይ ከኬንያ ፣ ኮፊ አናን ከጋና፣ አንዋር ሳዳት ከግብፅና ማንዴላ ከደቡብ አፍሪካ ማሸነፋቸው ይታወሳል።
ከግለሰቦች በተጨማሪ ሽልማቱን እንደ የቀይ መስቀል፣ የተመድ የስደተኞች ኮሚሽን፣ የአለም ምግብ ፕሮግራምና የኒውኪሊየር መሳሪያን የማጥፋት ዘመቻ ያሉ ተቋማት አሸንፈዋል።
የዘንድሮው የኖቤል ሽልማት በተለያዩ ዘርፎች አሸናፊዎችን እያሳወቀ ሲሆን በህክምና፣ በፊዚክስና ኬሚስትሪ ዘርፍ ያሸነፉ ተመራማሪዎችም ታውቀዋል።
ዘገባው የCBS ነው።
@TikvahethMagazine
❤110👎27🕊5👍4😢1
TIKVAH-MAGAZINE
የ2025 የኖቤል የሰላም ሽልማት አሸናፊ ዛሬ ይፋ ይሆናል። ከ1901 ጀምሮ ለ105 ጊዜ የተሰጠው የኖቤል የሰላም ሽልማት እስካሁን 92 ወንዶች፣ 19 ሴቶችና 28 ተቋማት አሸንፈዋል። ሽልማቱ ለመጀመሪያ ጊዜ የተሰጠው ለፍሬድሪክ ፓሲና ለቀይ መስቀል መስራቹ ሄነሪ ዱራንት ነበር። በተደጋጋሚ የኖቤል የሰላም ሽልማት ላቋምኳቸው ጦርነቶች ይገባኛል ሲሉ የቆዩት ፕሬዚዳንት ትራምፕ ለሽልማቱ በእስራኤሉ ጠቅላይ…
🟡 #BreakingNews
የ2025 የኖቤል የሰላም ሽልማት ተሸላሚ ማሪያ ኮሪና ማቻዶ ሆናለች። ማቻዶ በቬንዙዌላ ለዲሞክራሲ እና ለሰብዓዊ መብት መከበር ባደረገችው ያላሰለሰ ትግል ነው ተሸላሚ የሆነችው።
@TikvahethMagazine
የ2025 የኖቤል የሰላም ሽልማት ተሸላሚ ማሪያ ኮሪና ማቻዶ ሆናለች። ማቻዶ በቬንዙዌላ ለዲሞክራሲ እና ለሰብዓዊ መብት መከበር ባደረገችው ያላሰለሰ ትግል ነው ተሸላሚ የሆነችው።
@TikvahethMagazine
🤣164❤86👍31🕊19👏16👎6
የዘንድሮዋ የኖቤል የሰላም ሽልማት አሸናፊ ማሪያ ማቻዶ ማናት?
ኒኮላስ ማዱሮ በሚያስተዳድሯት በነዳጅ በበለፀገችው ቬንዙዌላ አሉ ከሚባሉ ዋነኛ ተቃዋሚዎች መካከል ማሪያ ኮሪና ማቻዶ ቀዳሚዋ ነች።
ማቻዶ በሃገሯ ዲምክራሲያዊ መብቶች እንዲከበሩ እና ወደ ዲሞክራሲ የሚደረግ ሽግግር ላይ ላደረጉት ትግልም የዘንድሮው የኖቤል የሰላም ሽልማት ተበርክቶላቸዋል።
የ58 ዓመቷ ማቻዶ ውልደቷ በቬንዙዌላ ዋና ከተማ ካራካስ ሲሆን በሙያዋ ኢንዱስትሪያል ኢንጂነር ነች።
በ2023 በነበረው ቅድመ ምርጫ ወቅት ድጋፍ እያገኘች የነበረ ቢሆንም ቢሮ እንዲኖራት ስላልተፈቀደላት በ2024 ምርጫ መሳተፍ አልቻለችም።
ከምርጫው በኋላ ተደብቃ የነበረችው ማቻዶ በኋላ ላይ ተቃውሞ በመጥራቷ ታስራ የነበረ ሲሆን ከዛ በኋላ ተፈትታለች።
በኢኮኖሚው ማቻዶ የቬንዙዌላ የመንግስት ተቋማት ወደ ግል እንዲዞሩ የምትሟገት ስትሆን ይህም የቬኔዙዌላ ዋነኛ የገቢ ምንጭ የሆነው የነዳጅ ተቋምንም ይጨምራል።
ማቻዶ የፖለቲካ ህይወቷን በ2002 ከጀመረች በኋላ በ2014 በነበረው ተቃውሞ ስትሳተፍ ታስራ በሃገር ክህደት ወንጀልም ተከሳ ነበር።
በተደጋጋሚ ስትታሰር የቆየችው ማቻዶ አሁንም በተደጋጋሚ ከማዱሮ አገዛዝ ማስፈራሪያ ቢገጥማትም ሃገሯን ለቃ ሳትሄድ ቆይታለች።
የኖቤል የሰላም ሽልማት አሸናፊ መሆኗ ከታወቀ በኋላ ማቻዶ በሰጠችው አሰተያየት በደስታ መደንገጧን ተናግራለች።
በርካታ የሰብዓዊ መብት ተቋማትና መንግስታትም ማቻዶ በቬኔዙዌላ እያደረገች ላለችው ትግል ሽልማቱ ይገባታል ብለዋል።
ዘገባው ከሮይተርስ የተወሰደ ነው።
@TikvahethMagazine
ኒኮላስ ማዱሮ በሚያስተዳድሯት በነዳጅ በበለፀገችው ቬንዙዌላ አሉ ከሚባሉ ዋነኛ ተቃዋሚዎች መካከል ማሪያ ኮሪና ማቻዶ ቀዳሚዋ ነች።
ማቻዶ በሃገሯ ዲምክራሲያዊ መብቶች እንዲከበሩ እና ወደ ዲሞክራሲ የሚደረግ ሽግግር ላይ ላደረጉት ትግልም የዘንድሮው የኖቤል የሰላም ሽልማት ተበርክቶላቸዋል።
የ58 ዓመቷ ማቻዶ ውልደቷ በቬንዙዌላ ዋና ከተማ ካራካስ ሲሆን በሙያዋ ኢንዱስትሪያል ኢንጂነር ነች።
በ2023 በነበረው ቅድመ ምርጫ ወቅት ድጋፍ እያገኘች የነበረ ቢሆንም ቢሮ እንዲኖራት ስላልተፈቀደላት በ2024 ምርጫ መሳተፍ አልቻለችም።
ከምርጫው በኋላ ተደብቃ የነበረችው ማቻዶ በኋላ ላይ ተቃውሞ በመጥራቷ ታስራ የነበረ ሲሆን ከዛ በኋላ ተፈትታለች።
በኢኮኖሚው ማቻዶ የቬንዙዌላ የመንግስት ተቋማት ወደ ግል እንዲዞሩ የምትሟገት ስትሆን ይህም የቬኔዙዌላ ዋነኛ የገቢ ምንጭ የሆነው የነዳጅ ተቋምንም ይጨምራል።
ማቻዶ የፖለቲካ ህይወቷን በ2002 ከጀመረች በኋላ በ2014 በነበረው ተቃውሞ ስትሳተፍ ታስራ በሃገር ክህደት ወንጀልም ተከሳ ነበር።
በተደጋጋሚ ስትታሰር የቆየችው ማቻዶ አሁንም በተደጋጋሚ ከማዱሮ አገዛዝ ማስፈራሪያ ቢገጥማትም ሃገሯን ለቃ ሳትሄድ ቆይታለች።
የኖቤል የሰላም ሽልማት አሸናፊ መሆኗ ከታወቀ በኋላ ማቻዶ በሰጠችው አሰተያየት በደስታ መደንገጧን ተናግራለች።
በርካታ የሰብዓዊ መብት ተቋማትና መንግስታትም ማቻዶ በቬኔዙዌላ እያደረገች ላለችው ትግል ሽልማቱ ይገባታል ብለዋል።
ዘገባው ከሮይተርስ የተወሰደ ነው።
@TikvahethMagazine
❤140👎21👍1🤬1
"የኖቤል ኮሚቴ ከሰላም በላይ ፖለቲካን እንደሚያስቀድም አሳይቷል"- የኋይት ሃውስ ቃለ አቀባይ
የኋይት ሃውስ ቃለ አቀባይ ስቴቨን ቼኡንግ ዶናልድ ትራምፕ የኖቤል የሰላም ሽልማትን አለማሸነፋቸውን ተከትሎ ባስተላለፉት መልዕክት ኮሚቴው ከሰላም በላይ ፖለቲካን ማስበለጡን አሳይቷል ብለዋል።
ቃለ አቀባዩ " ትራምፕ የሰብዓዊነት ማዕከል ናቸው" በማለት ሌሎች ሊሞክሩ የማይደፍሩትን ነገር አሳክተዋል ሲሉ ገልፀዋል።
ትራምፕ በተደጋጋሚ ላቆምኳቸው ጦርነቶች የሰላም ሽልማት አልተሰጠኝም ሲሉ ዘንድሮ በተለይ የእስራኤል እና ኢራንን ጦርነት በማስቆም እንደዚሁም ደግሞ ከሰሞኑ በጋዛ ለተፈፀመው የሰላም ስምምነት በነበራቸው ሚና ሽልማቱን ይገባኛል ሲሉ በተደጋጋሚ በግልጽ ተናግረው ነበር።
ትራምፕ ኢትዮጵያ እና ግብፅ ያልተዋጉትን ጦርነት ጨምሮ የሰርቢያና ኮሶቮ፣ የአርሜኒያ እና አዘርባጃን እንደዚሁም የህንድ እና ፓኪስታንን ግጭቶች አስቁሜያለሁ ብለው መናገራቸው ይታወሳል።
ዘገባው የአልጄዚራ ነው።
@TikvahethMagazine
የኋይት ሃውስ ቃለ አቀባይ ስቴቨን ቼኡንግ ዶናልድ ትራምፕ የኖቤል የሰላም ሽልማትን አለማሸነፋቸውን ተከትሎ ባስተላለፉት መልዕክት ኮሚቴው ከሰላም በላይ ፖለቲካን ማስበለጡን አሳይቷል ብለዋል።
ቃለ አቀባዩ " ትራምፕ የሰብዓዊነት ማዕከል ናቸው" በማለት ሌሎች ሊሞክሩ የማይደፍሩትን ነገር አሳክተዋል ሲሉ ገልፀዋል።
ትራምፕ በተደጋጋሚ ላቆምኳቸው ጦርነቶች የሰላም ሽልማት አልተሰጠኝም ሲሉ ዘንድሮ በተለይ የእስራኤል እና ኢራንን ጦርነት በማስቆም እንደዚሁም ደግሞ ከሰሞኑ በጋዛ ለተፈፀመው የሰላም ስምምነት በነበራቸው ሚና ሽልማቱን ይገባኛል ሲሉ በተደጋጋሚ በግልጽ ተናግረው ነበር።
ትራምፕ ኢትዮጵያ እና ግብፅ ያልተዋጉትን ጦርነት ጨምሮ የሰርቢያና ኮሶቮ፣ የአርሜኒያ እና አዘርባጃን እንደዚሁም የህንድ እና ፓኪስታንን ግጭቶች አስቁሜያለሁ ብለው መናገራቸው ይታወሳል።
ዘገባው የአልጄዚራ ነው።
@TikvahethMagazine
🤣251❤61👎21🤔6👍2
ቡርኪናፋሶ ሲሰልሉ ነበር ያለቻቸውን 8 የሰብዓዊ ተቋም ሰራተኞች ማሰሯን ገለፀች።
ተቋሙ መቀመጫውን በኔዘርላንድስ ያደረገ ነው ሲባል ተይዘው ከታሰሩት ውስጥ የተቋሙ የቡርኪናፋሶ ዳይሬክተርና ምክትሉ እንዳሉበት ተገልጿል።
የሃገሪቱ የደህንነት ሚኒስቴር የግብረ ሰናይ ድርጅቱ " ለብሔራዊ ደህንነታችን ስጋት የሆኑ ወሳኝ የደህንነት መረጃዎችን ሰብስቦ ለውጪ አካላት ሲሰጥ ነበር" ብለዋል።
ከ2019 ጀምሮ በቡርኪናፋሶ ሲሰራ የነበረው ተቋሙ ከሐምሌ ወር ጀምሮ "ያለፈቃድ መረጃ በመሰብሰብ" በሚል የ3 ወር እገዳ እንደጣለበትም ተዘግቧል።
የደህንነት ሚኒስትሩ ተቋሙ ቢታገድም አሁን የተያዙት ሰዎች በድብቅ ስብሰባ ያደርጉ እንደነበርና መረጃ እንደሚሰበስቡ ተናግረዋል።
ተቋሙ በበኩሉ ይሰበሰብ የነበረው መረጃ ሚስጥራዊ እንዳልሆነና ለሰራተኞቹ ደህንነት ተብሎ እንደሚሰበሰብ አስታውቋል።
መረጃው የቢቢሲ ነው።
@TikvahethMagazine
ተቋሙ መቀመጫውን በኔዘርላንድስ ያደረገ ነው ሲባል ተይዘው ከታሰሩት ውስጥ የተቋሙ የቡርኪናፋሶ ዳይሬክተርና ምክትሉ እንዳሉበት ተገልጿል።
የሃገሪቱ የደህንነት ሚኒስቴር የግብረ ሰናይ ድርጅቱ " ለብሔራዊ ደህንነታችን ስጋት የሆኑ ወሳኝ የደህንነት መረጃዎችን ሰብስቦ ለውጪ አካላት ሲሰጥ ነበር" ብለዋል።
ከ2019 ጀምሮ በቡርኪናፋሶ ሲሰራ የነበረው ተቋሙ ከሐምሌ ወር ጀምሮ "ያለፈቃድ መረጃ በመሰብሰብ" በሚል የ3 ወር እገዳ እንደጣለበትም ተዘግቧል።
የደህንነት ሚኒስትሩ ተቋሙ ቢታገድም አሁን የተያዙት ሰዎች በድብቅ ስብሰባ ያደርጉ እንደነበርና መረጃ እንደሚሰበስቡ ተናግረዋል።
ተቋሙ በበኩሉ ይሰበሰብ የነበረው መረጃ ሚስጥራዊ እንዳልሆነና ለሰራተኞቹ ደህንነት ተብሎ እንደሚሰበሰብ አስታውቋል።
መረጃው የቢቢሲ ነው።
@TikvahethMagazine
❤126👏24👍7👎4🤔4😢2🕊2
📍 ፒያሳ ላይ የንግድ ሱቅ
3ኛ ፎቅ
➣ ቅድመ ክፍያ ሲከፍሉ 15% ቅናሽ 3,570,000 ብር ጠቅላላ ዋጋ
➣ 100% ለከፈለ 25% ቅናሽ 3,150,000 ብር ጠቅላላ ዋጋ
2ኛ ፎቅ
➣ ቅድመ ክፍያ ሲከፍሉ 15% ቅናሽ
4,080,000 ብር ጠቅላላ ዋጋ
➣ 100% ለከፈለ 25% ቅናሽ 3,600,000 ብር ጠቅላላ ዋጋ
1ኛ ፎቅ
➣ ቅድመ ክፍያ ሲከፍሉ 15% ቅናሽ 4,675,000 ብር ጠቅላላ ዋጋ
➣100% ለከፈለ 25% ቅናሽ 4,125,000 ብር ጠቅላላ ዋጋ
ግራውንድ
➣ቅድመ ክፍያ ሲከፍሉ 15% ቅናሽ 5,950,000 ብር ጠቅላላ ዋጋ
➣ 100% ለከፈለ 25% ቅናሽ 5,250,000 ብር ጠቅላላ ዋጋ
ለበለጠ መረጃ
👇
☎️+251986687513
WhatsApp:- +251986687513
Email:- [email protected]
3ኛ ፎቅ
➣ ቅድመ ክፍያ ሲከፍሉ 15% ቅናሽ 3,570,000 ብር ጠቅላላ ዋጋ
➣ 100% ለከፈለ 25% ቅናሽ 3,150,000 ብር ጠቅላላ ዋጋ
2ኛ ፎቅ
➣ ቅድመ ክፍያ ሲከፍሉ 15% ቅናሽ
4,080,000 ብር ጠቅላላ ዋጋ
➣ 100% ለከፈለ 25% ቅናሽ 3,600,000 ብር ጠቅላላ ዋጋ
1ኛ ፎቅ
➣ ቅድመ ክፍያ ሲከፍሉ 15% ቅናሽ 4,675,000 ብር ጠቅላላ ዋጋ
➣100% ለከፈለ 25% ቅናሽ 4,125,000 ብር ጠቅላላ ዋጋ
ግራውንድ
➣ቅድመ ክፍያ ሲከፍሉ 15% ቅናሽ 5,950,000 ብር ጠቅላላ ዋጋ
➣ 100% ለከፈለ 25% ቅናሽ 5,250,000 ብር ጠቅላላ ዋጋ
ለበለጠ መረጃ
👇
☎️+251986687513
WhatsApp:- +251986687513
Email:- [email protected]
❤24😢2🤔1
ሹመት እየተሰጠው ያለው የሰው ሰራሽ አስተውህሎት (AI) !
ከሰሞኑ የካዛኪስታን የመንግስት ፈንድ በማዕከላዊ እስያ የመጀመሪያ ነው የተባለለትን የሰው ሰራሽ አስተውህሎት ገለልተኛ የቦርድ ዳይሬክተር አስተዋውቋል።
ሥርዓቱ "SKAI" የሚባል ሲሆን እንደ ፋይናንስ እና አስተዳደር ያሉ የፈንዱ ተግባራት ውሳኔ ላይም ድምፅ መስጠት ይችላል።
ከ2008 ጀምሮ ባሉ የውስጥ ዶክመንቶች መሰልጠኑ ደግሞ ሚዛናዊ ውሳኔ እንዲሰጥ ያደርገዋል ተብሏል።
ካዛኪስታን በሰው ሰራሽ አስተውሎት ላይ ሰፊ ሥራዎችን እየሰራች የምትገኝ ሲሆን የሰው ሰራሽም አስተውህሎት ምርምር ላይ የሚሰራ ዩኒቨርሲቲ መመስረቷም ተገልጿል።
በተመሳሳይ ዜና ከዚህ በፊት አልባኒያ በዓለማችን የመጀመሪያውን የሰው ሰራሽ አስተውህሎት የሆነች ሚኒስትር መሾሟ ይታወሳል።
የሰው ሰራሽ አስተውሎት ሚኒስትር በጠቅላይ ሚኒስትሩ በተሾማበት ወቀትም ሙሉ ለሙሉ ከሙስና ነፃ መሆኑ ተገልፆ ነበር።
የሰው ሰራሽ አስተውሎት ሚኒስትሯ በፓርላማ ንግግር ባደረገችበት ወቅትም " ሰዎችን ለመተካት ሳይሆን ለመርዳት ነው የመጣውት" ብላለች።
ዲዬላ የሚል ስያሜ የተሰጣት ይቺ በሰው ሰራሽ አስተውህሎት የለማች ሚኒስትር የተሾመችው የሰው ሰራሽ አስተውህሎት ሚኒስትር ተደረጋ ነው።
ፈጣን ለውጥን እያመጣ ያለው የሰው ሰራሽ አስተውህሎት አሁን አሁን በከፍተኛ ውሳኔ ሰጪ ቦታዎች ላይም ጭምር እየገባ ሲሆን አንዳንዶች ነገሩን ከጥቅሙ ይልቅ በስጋትነት እያነሱት ይገኛሉ።
መረጃው የተገኘው ከዩሮ ኒውስ እና ከኤቢሲ ነው።
@TikvahethMagazine
ከሰሞኑ የካዛኪስታን የመንግስት ፈንድ በማዕከላዊ እስያ የመጀመሪያ ነው የተባለለትን የሰው ሰራሽ አስተውህሎት ገለልተኛ የቦርድ ዳይሬክተር አስተዋውቋል።
ሥርዓቱ "SKAI" የሚባል ሲሆን እንደ ፋይናንስ እና አስተዳደር ያሉ የፈንዱ ተግባራት ውሳኔ ላይም ድምፅ መስጠት ይችላል።
ከ2008 ጀምሮ ባሉ የውስጥ ዶክመንቶች መሰልጠኑ ደግሞ ሚዛናዊ ውሳኔ እንዲሰጥ ያደርገዋል ተብሏል።
ካዛኪስታን በሰው ሰራሽ አስተውሎት ላይ ሰፊ ሥራዎችን እየሰራች የምትገኝ ሲሆን የሰው ሰራሽም አስተውህሎት ምርምር ላይ የሚሰራ ዩኒቨርሲቲ መመስረቷም ተገልጿል።
በተመሳሳይ ዜና ከዚህ በፊት አልባኒያ በዓለማችን የመጀመሪያውን የሰው ሰራሽ አስተውህሎት የሆነች ሚኒስትር መሾሟ ይታወሳል።
የሰው ሰራሽ አስተውሎት ሚኒስትር በጠቅላይ ሚኒስትሩ በተሾማበት ወቀትም ሙሉ ለሙሉ ከሙስና ነፃ መሆኑ ተገልፆ ነበር።
የሰው ሰራሽ አስተውሎት ሚኒስትሯ በፓርላማ ንግግር ባደረገችበት ወቅትም " ሰዎችን ለመተካት ሳይሆን ለመርዳት ነው የመጣውት" ብላለች።
ዲዬላ የሚል ስያሜ የተሰጣት ይቺ በሰው ሰራሽ አስተውህሎት የለማች ሚኒስትር የተሾመችው የሰው ሰራሽ አስተውህሎት ሚኒስትር ተደረጋ ነው።
ፈጣን ለውጥን እያመጣ ያለው የሰው ሰራሽ አስተውህሎት አሁን አሁን በከፍተኛ ውሳኔ ሰጪ ቦታዎች ላይም ጭምር እየገባ ሲሆን አንዳንዶች ነገሩን ከጥቅሙ ይልቅ በስጋትነት እያነሱት ይገኛሉ።
መረጃው የተገኘው ከዩሮ ኒውስ እና ከኤቢሲ ነው።
@TikvahethMagazine
❤50👎7👍3🤔2😢2🕊1
ተመድ በመላው አለም ያለውን የሰላም ጠባቂ ኃይሉን ቁጥር በ25 በመቶ ሊቀንስ ነው።
ተመድ በመላው አለም ካሰማራቸው የሰላም ጠባቂ ኃይሎች ውስጥ 25 በመቶውን ከአሜሪካ የድጋፍ መቀነስ ጋር በተያያዘ ይቀንሳል ተብሏል።
በ9 አለም አቀፍ ተልዕኮዎች በተመድ ስር ከተሰማሩ 50 ሺህ የፀጥታ ኃይሎች መካከል 14 ሺህ ያህሉ በመጪዎቹ ወራት ወደመጡበት ሃገር ይመለሳሉ ተብሏል።
በሶማሊያ ያለው ተልዕኮ ተጠቂ ነው ሲባል ተመድ በዚህ አመት የተልዕኮው በጀት በ15% ይቀነሳል ተብሏል።
አሜሪካ ባለፈው አመት ለነዚህ ተልዕኮዎች ከ1 ቢሊየን ዶላር በላይ ድጋፍ ስትሰጥ ዘንድሮ 680 ሚሊየን ዶላር ብቻ ለመስጠት ፈቃደኝነቷን መግለጿ ተልዕኮውን እንደጎዳው ተገልጿል።
ተመድ የአሜሪካ ድጋፍ መቀነስን ተከትሎም የ20 በመቶ የስራ ቅነሳ ለማድረግ ማቀዱ ተዘግቧል።
ዘገባው የፍራንስ 24 ነው።
@TikvahethMagazine
ተመድ በመላው አለም ካሰማራቸው የሰላም ጠባቂ ኃይሎች ውስጥ 25 በመቶውን ከአሜሪካ የድጋፍ መቀነስ ጋር በተያያዘ ይቀንሳል ተብሏል።
በ9 አለም አቀፍ ተልዕኮዎች በተመድ ስር ከተሰማሩ 50 ሺህ የፀጥታ ኃይሎች መካከል 14 ሺህ ያህሉ በመጪዎቹ ወራት ወደመጡበት ሃገር ይመለሳሉ ተብሏል።
በሶማሊያ ያለው ተልዕኮ ተጠቂ ነው ሲባል ተመድ በዚህ አመት የተልዕኮው በጀት በ15% ይቀነሳል ተብሏል።
አሜሪካ ባለፈው አመት ለነዚህ ተልዕኮዎች ከ1 ቢሊየን ዶላር በላይ ድጋፍ ስትሰጥ ዘንድሮ 680 ሚሊየን ዶላር ብቻ ለመስጠት ፈቃደኝነቷን መግለጿ ተልዕኮውን እንደጎዳው ተገልጿል።
ተመድ የአሜሪካ ድጋፍ መቀነስን ተከትሎም የ20 በመቶ የስራ ቅነሳ ለማድረግ ማቀዱ ተዘግቧል።
ዘገባው የፍራንስ 24 ነው።
@TikvahethMagazine
❤28👍3🕊1🤣1
#SocialMedia
የአሜሪካዋ ኒውዮርክ ከተማ ታላላቅ የሚባሉ የማህበራዊ ሚዲያዎችን ህፃናትን ሱስ በማስያዝ ከሳለች።
ከተማዋ ፌስቡክ፣ ጎግል፣ ስናፕቻትና እንደ ቲክቶክ ያሉ የማህበራዊ ሚዲያዎች ህፃናትን ሱስ በማስያዝ አዕምሯዊ ጤናቸውን እየጎዱ ነው በማለት 327 ገፅ ያለው ክስ በፍርድ ቤት አቅርባለች።
በኒውዮርክ ከተማ ከሚኖሩ 8 ሚሊየን ሰዎች ውስጥ 1.8 ሚሊየኑ ህፃናት ናቸው።
የጎግል ቃለ አቀባይ በዩቲዩብ ላይ የተከፈተው ክስ ትክክል አይደለም ሲሉ ዩቲዩብ ሰዎች ቪዲዮ የሚያዩበት እንጂ ከጓደኞቻቸው ጋር የሚገናኙበት የማህበራዊ ሚዲያ አይደለም ብለዋል።
በክሱ 77.3% የሚሆኑት በኒውዮርክ የሚኖሩ የሁለተኛ ደረጃ ተማሪዎች በቀን ከሶስት ሰዓት በላይ በስክሪን ላይ እንደሚያጠፉ ተገልፆ ይህም የተማሪዎቹን ጤና እየጎዳ ነው ተብሏል።
ከዚሁ ከማህበራዊ ሚዲያ ጋር በተያያዘ ዜና ዴንማርክ ከ15 ዓመት በታች ያሉ ህፃናት ማህበራዊ ሚዲያዎችን እንዳይጠቀሙ እገዳ ለማስቀመጥ እየሰራች ነው።
የዴንማርክ ጠቅላይ ሚኒስትር ሜት ፍሬድሪክሰን ማህበራዊ ሚዲያዎች" የልጆቻችንን ህፃንነት እየሰረቁ" ነው ብለዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሯ የሃገሪቱ ህግ አውጪዎች ከ15 አመት በታች ያሉ ህፃናት ማህበራዊ ሚዲያን እንዳይጠቀሙ እንዲከለክሉ ጠይቀዋል።
በአውሮፓ ህብረት ሃገራት ህፃናት 13 አመት ሳይሞላቸው የማህበራዊ ሚዲያ አካውንት መክፈት እንደማይችሉ ቢቀመጥም ጠቅላይ ሚኒስትሯ 94 በመቶ የዴንማርክ ህፃናት እዚህ ዕድሜ ላይ ሳይደርሱ ይከፍታሉ ብለዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሯ " ህፃናት ማህበራዊ ሚዲያ ላይ ማየት የሌለባቸውን ነገሮች ያያሉ" ያሉ ሲሆን ይህም ጭንቀትና ድብርትን ጨምሮ ሌሎቸ መዘዞችን እያዋለደ ነው ብለዋል።
ዘገባዎቹ የተገኙት ከዩሮ ኒውስና ከአሌጄዘራ ነው።
@TikvahethMagazine
የአሜሪካዋ ኒውዮርክ ከተማ ታላላቅ የሚባሉ የማህበራዊ ሚዲያዎችን ህፃናትን ሱስ በማስያዝ ከሳለች።
ከተማዋ ፌስቡክ፣ ጎግል፣ ስናፕቻትና እንደ ቲክቶክ ያሉ የማህበራዊ ሚዲያዎች ህፃናትን ሱስ በማስያዝ አዕምሯዊ ጤናቸውን እየጎዱ ነው በማለት 327 ገፅ ያለው ክስ በፍርድ ቤት አቅርባለች።
በኒውዮርክ ከተማ ከሚኖሩ 8 ሚሊየን ሰዎች ውስጥ 1.8 ሚሊየኑ ህፃናት ናቸው።
የጎግል ቃለ አቀባይ በዩቲዩብ ላይ የተከፈተው ክስ ትክክል አይደለም ሲሉ ዩቲዩብ ሰዎች ቪዲዮ የሚያዩበት እንጂ ከጓደኞቻቸው ጋር የሚገናኙበት የማህበራዊ ሚዲያ አይደለም ብለዋል።
በክሱ 77.3% የሚሆኑት በኒውዮርክ የሚኖሩ የሁለተኛ ደረጃ ተማሪዎች በቀን ከሶስት ሰዓት በላይ በስክሪን ላይ እንደሚያጠፉ ተገልፆ ይህም የተማሪዎቹን ጤና እየጎዳ ነው ተብሏል።
ከዚሁ ከማህበራዊ ሚዲያ ጋር በተያያዘ ዜና ዴንማርክ ከ15 ዓመት በታች ያሉ ህፃናት ማህበራዊ ሚዲያዎችን እንዳይጠቀሙ እገዳ ለማስቀመጥ እየሰራች ነው።
የዴንማርክ ጠቅላይ ሚኒስትር ሜት ፍሬድሪክሰን ማህበራዊ ሚዲያዎች" የልጆቻችንን ህፃንነት እየሰረቁ" ነው ብለዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሯ የሃገሪቱ ህግ አውጪዎች ከ15 አመት በታች ያሉ ህፃናት ማህበራዊ ሚዲያን እንዳይጠቀሙ እንዲከለክሉ ጠይቀዋል።
በአውሮፓ ህብረት ሃገራት ህፃናት 13 አመት ሳይሞላቸው የማህበራዊ ሚዲያ አካውንት መክፈት እንደማይችሉ ቢቀመጥም ጠቅላይ ሚኒስትሯ 94 በመቶ የዴንማርክ ህፃናት እዚህ ዕድሜ ላይ ሳይደርሱ ይከፍታሉ ብለዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሯ " ህፃናት ማህበራዊ ሚዲያ ላይ ማየት የሌለባቸውን ነገሮች ያያሉ" ያሉ ሲሆን ይህም ጭንቀትና ድብርትን ጨምሮ ሌሎቸ መዘዞችን እያዋለደ ነው ብለዋል።
ዘገባዎቹ የተገኙት ከዩሮ ኒውስና ከአሌጄዘራ ነው።
@TikvahethMagazine
❤86👏21👍6🤣6🕊4😢2👎1
ዶናልድ ትራምፕ ከዘንድሮዋ የኖቤል የሰላም ሽልማት አሸናፊ ማሪያ ማቻዶ ስልክ እንደተደወለላቸው ተናገሩ።
ትራምፕ " የኖቤል ሽልማትን ዛሬ ያሸነፈችው ሰው ደውላልኝ ሽልማቱ ለአንተ ይገባካል ብላኛለች" ሲሉ ተናግረዋል።
ትራምፕ እንደዛ ማድረጓ ጥሩ ነገር ነው ብለው " እንደዛ ከሆነ ስጪኝ ግን አላልኳትም" ሲሉ አዝናኝ አስተያየታቸውን ሰጥተዋል።
ትራምፕ ትናንት ምሽት ባደረጉትም ንግግር አመታትን የፈጁ ጦርነቶችን ጨምሮ 8 ጦርነቶችን ማስቆማቸውን ዳግም ተናግረዋል።
ምንም እንኳን ማሪያ ማቻዶን ለሽልማቱ ዕጩ አድርገው ያቀረቡት የወቅቱ የአሜሪካ የውጪ ጉዳይ መስሪያ ቤት ኃላፊ ማርክ ሩቢዮ ያሉበት የህግ ቡድን ቢሆንም ኋይት ሃውስ የሽልማቱን ውጤት መኮነኑ ይታወሳል።
የሩሲያው ፕሬዚዳንት ፑቲን ሽልማቱ ላይ ጥያቄያቸውን ያነሱ ሲሆን ሽልማቱ ለሰላም ምንም አስተዋፅኦ ያላደረጉ ሰዎች እያሸነፉትም ነው ብለዋል።
ፑቲን "የወቅቱ የአሜሪካ ፕሬዚዳንት የኖቤል ሽልማት ይገባቸው አይገባቸው አላውቅም፤ ነገር ግን አመታት የፈጁ የተወሳሰቡ ግጭቶችን ፈትተዋል" በማለት በተዘዋዋሪ ሽልማቱ ለትራምፕ እንደሚገባ አንስተዋል።
ትራምፕ የፑቲንን ንግግር ተከትሎም በማህበራዊ ሚዲያቸው " አመሰግናለሁ ፕሬዚዳንት ፑቲን" ብለዋል።
ዘገባው የሲኤንኤን ነው።
@TikvahethMagazine
ትራምፕ " የኖቤል ሽልማትን ዛሬ ያሸነፈችው ሰው ደውላልኝ ሽልማቱ ለአንተ ይገባካል ብላኛለች" ሲሉ ተናግረዋል።
ትራምፕ እንደዛ ማድረጓ ጥሩ ነገር ነው ብለው " እንደዛ ከሆነ ስጪኝ ግን አላልኳትም" ሲሉ አዝናኝ አስተያየታቸውን ሰጥተዋል።
ትራምፕ ትናንት ምሽት ባደረጉትም ንግግር አመታትን የፈጁ ጦርነቶችን ጨምሮ 8 ጦርነቶችን ማስቆማቸውን ዳግም ተናግረዋል።
ምንም እንኳን ማሪያ ማቻዶን ለሽልማቱ ዕጩ አድርገው ያቀረቡት የወቅቱ የአሜሪካ የውጪ ጉዳይ መስሪያ ቤት ኃላፊ ማርክ ሩቢዮ ያሉበት የህግ ቡድን ቢሆንም ኋይት ሃውስ የሽልማቱን ውጤት መኮነኑ ይታወሳል።
የሩሲያው ፕሬዚዳንት ፑቲን ሽልማቱ ላይ ጥያቄያቸውን ያነሱ ሲሆን ሽልማቱ ለሰላም ምንም አስተዋፅኦ ያላደረጉ ሰዎች እያሸነፉትም ነው ብለዋል።
ፑቲን "የወቅቱ የአሜሪካ ፕሬዚዳንት የኖቤል ሽልማት ይገባቸው አይገባቸው አላውቅም፤ ነገር ግን አመታት የፈጁ የተወሳሰቡ ግጭቶችን ፈትተዋል" በማለት በተዘዋዋሪ ሽልማቱ ለትራምፕ እንደሚገባ አንስተዋል።
ትራምፕ የፑቲንን ንግግር ተከትሎም በማህበራዊ ሚዲያቸው " አመሰግናለሁ ፕሬዚዳንት ፑቲን" ብለዋል።
ዘገባው የሲኤንኤን ነው።
@TikvahethMagazine
🤣264❤111