TIKVAH-MAGAZINE
#SIT በሸገር ከተማ እየተገነባ ያለውና ትኩረቱን የህዋ ሳይንስ፣ ኒውኪሊየር ሳይንስና ሰው ሰራሽ አስተውህሎት ላይ ያደረገው ሸገር የቴክኖሎጂ ኢንስቲቲዩት ከዚህ ወር ጀምሮ ተማሪዎችን መቀበል ይጀምራል። ይህ ተቋም የኦሮሚያ ክልላዊ መንግስት ብዙ ቢሊየኖችን መድቦ እያስገነባው ያለው ሲሆን በ50 ሄክታር ላይ ያረፈው ተቋም ግንባታውም በኮዬ ፈጬ ክፍለ ከተማ እየተከናወነ ነው። በዚህ ተቋም በልዩ ልዩ…
#Update
የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሽመልስ አብዲሳ የሸገር የቴክኖሎጂ ኢንስቲቲዩትን መርቀው ከፍተዋል።
በሸገር ከተማ ኮዬ ፈጬ ክፍለ ከተማ የተገነባው ኢንስቲቲዩቱ ትኩረቱን የህዋ ሳይንስ፣ የኑውኪሊየር ሳይንስና የሰው ሰራሽ አስተውህሎት ላይ እንደሚያደርግ መነገሩ ይታወሳል።
መረጃው የተገኘው ከኦሮሚያ ክልል ፕሬዚዳንት ጽህፈት ቤት ነው።
@TikvahethMagazine
የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሽመልስ አብዲሳ የሸገር የቴክኖሎጂ ኢንስቲቲዩትን መርቀው ከፍተዋል።
በሸገር ከተማ ኮዬ ፈጬ ክፍለ ከተማ የተገነባው ኢንስቲቲዩቱ ትኩረቱን የህዋ ሳይንስ፣ የኑውኪሊየር ሳይንስና የሰው ሰራሽ አስተውህሎት ላይ እንደሚያደርግ መነገሩ ይታወሳል።
መረጃው የተገኘው ከኦሮሚያ ክልል ፕሬዚዳንት ጽህፈት ቤት ነው።
@TikvahethMagazine
❤76👎41🤣16👍11
አፍጋኒስታን እና ፓኪስታን በድንበር አካባቢያቸው ግጭት ውስጥ ገብተዋል።
ሁለቱ ሃገራት ግጭት ውስጥ የገቡት ታሊባን ፓኪስታን የአየር ክልሌን ጥሳ ጥቃት ፈፅማለች ካለ በኋላ በወሰደው እርምጃ ነው።
ባለፈው ሳምንት መጨረሻ ፓኪስታን በአፍጋኒስታን ዋና ከተማ ካቡልና በድንበር ከተማ የአየር ጥቃት የፈፀመች ሲሆን ፓኪስታን የካቡሉ ጥቃት የፓኪስታኑ ታሊባን(TTP) ተብሎ የሚታወቀውን ታጣቂ መሪ ኑር ዋሊ መስሁድን ለመግደል ኢላሚ ያደረገ ነበር ብለዋል።
ታጣቂው በዚህ አመት ብቻ በፓኪስታን በፈፀመው ጥቃት ከ2400 በላይ ሰዎችን ሲገድል ፓኪስታን ታሊባን ለዚህ ታጣቂ ምሽግ ሆኗል ብላ በተደጋጋሚ ስትከስ ነበር።
በድንበር አካባቢ በነበረው ግጭት 58 የፓኪስታን ታጣቂዎች መገደላቸውን ታሊባን ሲገልፅ ፓኪስታን በበኩሏ የሞቱት 23 መሆናቸውን ገልፃ በበኩሏ ከ200 በላይ የታሊባን ጦርና ታጣቂዎችን ገድያለሁ ብላለች።
የሁለቱም ሃገራት ከፍተኛ ባለስልጣናት አንዱ ለሌላኛው ማስጠንቀቂያ እየሰጡ ሲሆን የቀጣናው ሃገራት ወደባሰ ግጭት እንዳይገቡ አስጠንቅቀዋል።
ፓኪስታን ከ1996-2001 ለነበረው የታሊባን መንግስት ዕውቅና ከሰጡ ሶስት ሃገራት አንዷ ስትሆን ከአሜሪካ ጋር በነበራቸው ውጊያም ድጋፍ ለታሊባን አድርጋለች።
በ2021 ታሊባን ወደ ስልጣን ከተመለሰ በኋላ ፓኪስታን TTP ለተሰኘው ታጣቂ መደበቂያ ሰጥታለች በሚልም ፓኪስታን ግንኙነቷን አሻክራለች።
ፓኪስታን ከወራት በፊትም በህንድ ካሽሚር ግዛት ጥቃት ፈፅማ ከህንድ ጋር ግጭት ውስጥ እንደገባች ይታወሳል።
መረጃው የተሰባሰበው ከቢቢሲና አልጄዚራ ነው።
@TikvahethMagazine
ሁለቱ ሃገራት ግጭት ውስጥ የገቡት ታሊባን ፓኪስታን የአየር ክልሌን ጥሳ ጥቃት ፈፅማለች ካለ በኋላ በወሰደው እርምጃ ነው።
ባለፈው ሳምንት መጨረሻ ፓኪስታን በአፍጋኒስታን ዋና ከተማ ካቡልና በድንበር ከተማ የአየር ጥቃት የፈፀመች ሲሆን ፓኪስታን የካቡሉ ጥቃት የፓኪስታኑ ታሊባን(TTP) ተብሎ የሚታወቀውን ታጣቂ መሪ ኑር ዋሊ መስሁድን ለመግደል ኢላሚ ያደረገ ነበር ብለዋል።
ታጣቂው በዚህ አመት ብቻ በፓኪስታን በፈፀመው ጥቃት ከ2400 በላይ ሰዎችን ሲገድል ፓኪስታን ታሊባን ለዚህ ታጣቂ ምሽግ ሆኗል ብላ በተደጋጋሚ ስትከስ ነበር።
በድንበር አካባቢ በነበረው ግጭት 58 የፓኪስታን ታጣቂዎች መገደላቸውን ታሊባን ሲገልፅ ፓኪስታን በበኩሏ የሞቱት 23 መሆናቸውን ገልፃ በበኩሏ ከ200 በላይ የታሊባን ጦርና ታጣቂዎችን ገድያለሁ ብላለች።
የሁለቱም ሃገራት ከፍተኛ ባለስልጣናት አንዱ ለሌላኛው ማስጠንቀቂያ እየሰጡ ሲሆን የቀጣናው ሃገራት ወደባሰ ግጭት እንዳይገቡ አስጠንቅቀዋል።
ፓኪስታን ከ1996-2001 ለነበረው የታሊባን መንግስት ዕውቅና ከሰጡ ሶስት ሃገራት አንዷ ስትሆን ከአሜሪካ ጋር በነበራቸው ውጊያም ድጋፍ ለታሊባን አድርጋለች።
በ2021 ታሊባን ወደ ስልጣን ከተመለሰ በኋላ ፓኪስታን TTP ለተሰኘው ታጣቂ መደበቂያ ሰጥታለች በሚልም ፓኪስታን ግንኙነቷን አሻክራለች።
ፓኪስታን ከወራት በፊትም በህንድ ካሽሚር ግዛት ጥቃት ፈፅማ ከህንድ ጋር ግጭት ውስጥ እንደገባች ይታወሳል።
መረጃው የተሰባሰበው ከቢቢሲና አልጄዚራ ነው።
@TikvahethMagazine
❤28🕊10
"የእንጀራ ምጣድ እና ማብሰያ ምድጃ ዝቅተኛ ኢነርጅ አጠቃቀም ብቃት ደረጃን ለማሻሻል በተለያዩ ምርቶች ላይ ልኬት እያከናወንኩ ነው" - የነዳጅና ኢነርጂ ባለሥልጣን
በኃይል አጠቃቀም ብቃታቸው ከፍተኛ ኃይል አባካኝ ተብለው በጥናት ከተለዩ ምርቶች መካከል በሀገር ውስጥ የሚመረቱ እንጀራ ምጣዶችና የማብሰያ ምድጃ ቀዳሚዎቹ ናቸው፡፡
በሀገር ውስጥ የሚመረቱ የእንጀራ ምጣድ እና ማብሰያ ምድጃ ዝቅተኛ ኢነርጅ አጠቃቀም ብቃት ደረጃን ለመሻሻል በተለያዩ ምርቶች ላይ ልኬት የመውሰድ ሥራ እየተሠራ ይገኛል ሲል የነዳጅና ኢነርጂ ባለሥልጣን አስታውቋል።
ብሔራዊ ኢነርጂ ብቃት ስትራቴጂን ለማስፈጸም በባለስልጣን መ/ቤቱ ከተቀረጹ ፕሮግራሞች መካከል የተለጣፊ ምልክት ፕሮግራም (labeling program) ተግባራዊ እየተደረገ ይገኛል ተብሏል።
በዚህም፥ የምርት ስታንዳርድ እና ዝቅተኛ ኢነርጂ አጠቃቀም ብቃት በደረጃዎች ኢንስቲትዊት በ2009 ዓ.ም እና በ2011 ዓ.ም እንዲጸድቅ ተደርጓል፡፡
የደረጃዎቹን መጽደቅ ተከትሎም ሳይንሣዊ አመራረት ዘዴን በልኬት ላይ በተመሠረተ ለመስራት እንዲቻል ከአዲስ አበባ ዩንቨርስቲ ጋር በመተባበር የምጣድ ማሳያ (Prototype) በማስመረት አምራቾች ተደጋጋሚ ስልጠና እንዲያገኙ ተደርጓል ሲል ገልጿል።
ስልጠናውን መሠረት በማድረግ የተመረቱ ምርቶችን በባለስልጣን መ/ቤቱ ላብራቶሪ በማስፈተሸ የተለጣፊ ምልክት የመስጠት ሥራ እየተከናወነ ይገኛል፡፡
አሁን ላይ የተቀመጡ ስታንዳርዶችን በድጋሚ ማየትና መፈተሸ አስፈላጊ በመሆኑ የምርቱን ዝቅተኛ ኢነርጂ አጠቃቀም ደረጃ ለማሻሻል በመስራት ላይ ይገኛል ተብሏል፡፡
@TikvahethMagazine
በኃይል አጠቃቀም ብቃታቸው ከፍተኛ ኃይል አባካኝ ተብለው በጥናት ከተለዩ ምርቶች መካከል በሀገር ውስጥ የሚመረቱ እንጀራ ምጣዶችና የማብሰያ ምድጃ ቀዳሚዎቹ ናቸው፡፡
በሀገር ውስጥ የሚመረቱ የእንጀራ ምጣድ እና ማብሰያ ምድጃ ዝቅተኛ ኢነርጅ አጠቃቀም ብቃት ደረጃን ለመሻሻል በተለያዩ ምርቶች ላይ ልኬት የመውሰድ ሥራ እየተሠራ ይገኛል ሲል የነዳጅና ኢነርጂ ባለሥልጣን አስታውቋል።
ብሔራዊ ኢነርጂ ብቃት ስትራቴጂን ለማስፈጸም በባለስልጣን መ/ቤቱ ከተቀረጹ ፕሮግራሞች መካከል የተለጣፊ ምልክት ፕሮግራም (labeling program) ተግባራዊ እየተደረገ ይገኛል ተብሏል።
በዚህም፥ የምርት ስታንዳርድ እና ዝቅተኛ ኢነርጂ አጠቃቀም ብቃት በደረጃዎች ኢንስቲትዊት በ2009 ዓ.ም እና በ2011 ዓ.ም እንዲጸድቅ ተደርጓል፡፡
የደረጃዎቹን መጽደቅ ተከትሎም ሳይንሣዊ አመራረት ዘዴን በልኬት ላይ በተመሠረተ ለመስራት እንዲቻል ከአዲስ አበባ ዩንቨርስቲ ጋር በመተባበር የምጣድ ማሳያ (Prototype) በማስመረት አምራቾች ተደጋጋሚ ስልጠና እንዲያገኙ ተደርጓል ሲል ገልጿል።
ስልጠናውን መሠረት በማድረግ የተመረቱ ምርቶችን በባለስልጣን መ/ቤቱ ላብራቶሪ በማስፈተሸ የተለጣፊ ምልክት የመስጠት ሥራ እየተከናወነ ይገኛል፡፡
አሁን ላይ የተቀመጡ ስታንዳርዶችን በድጋሚ ማየትና መፈተሸ አስፈላጊ በመሆኑ የምርቱን ዝቅተኛ ኢነርጂ አጠቃቀም ደረጃ ለማሻሻል በመስራት ላይ ይገኛል ተብሏል፡፡
@TikvahethMagazine
❤71🤣26👎2🤬2👍1
ሶማሊያ ገለልተኛ የሆነ የሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን መስርታለች።
በ1993 የሶማሊያ ማዕከላዊ መንግስትን መፍረስ ተከትሎ የሃገሪቱ የሰብዓዊ መብት ሁኔታ በውጪ ገለልተኛ አካላት እና በአለም አቀፍ ተቋማት ቁጥጥር ስር ነበረ።
በዚህ ሳምንት የተመድ የሰብዓዊ መብቶች ካውንስል ይህንን የመቆጣጣር ኃላፊነቱን ባለማራዘሙ ሶማሊያ የራሷን ብሔራዊ ገለልተኛ ብሔራዊ የሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን መስርታለች።
ምሰረታው የሶማሊያ ራስን የመቻል ምልክት ተደርጎ ሲወሰድ ፓርላማው የኮሚሽኑን 9 አባላትንም መምረጡና አባላቱ ደግሞ ኮሚሽነር እንደሚመርጡ ተነግሯል።
ዘገባው የዳዋን አፍሪካ ነው።
@TikvahethMagazine
በ1993 የሶማሊያ ማዕከላዊ መንግስትን መፍረስ ተከትሎ የሃገሪቱ የሰብዓዊ መብት ሁኔታ በውጪ ገለልተኛ አካላት እና በአለም አቀፍ ተቋማት ቁጥጥር ስር ነበረ።
በዚህ ሳምንት የተመድ የሰብዓዊ መብቶች ካውንስል ይህንን የመቆጣጣር ኃላፊነቱን ባለማራዘሙ ሶማሊያ የራሷን ብሔራዊ ገለልተኛ ብሔራዊ የሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን መስርታለች።
ምሰረታው የሶማሊያ ራስን የመቻል ምልክት ተደርጎ ሲወሰድ ፓርላማው የኮሚሽኑን 9 አባላትንም መምረጡና አባላቱ ደግሞ ኮሚሽነር እንደሚመርጡ ተነግሯል።
ዘገባው የዳዋን አፍሪካ ነው።
@TikvahethMagazine
❤36🙏4🕊4🤔2🤣2
TIKVAH-MAGAZINE
#Update
በቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 12 የነዋሪዎች ቡድን መሪ የሆኑትን ጨምሮ አገልግሎቶችን በገንዘብ ሲሸጡ እና ህብረተሰቡን ሲያንገላቱ የነበሩ ባለሙያዎች ከመንግስት ስራ እንዲሰናበቱ ዉሳኔ መተላለፉን የሲቪል ምዝገባ እና የነዋሪነት አገልግሎት ኤጀንሲ አስታውቋል።
ኤጀንሲው ደረሰኝ ያለውን የተገልጋይ ጥቆማ መሰረት አድርጎ የቦሌ ክ/ከተማ ወረዳ 12 የነዋሪዎች አገልግሎት ቡድን መሪ የሆኑት አቶ ክብረት ቦጋለ እንዲሁም የነዋሪዎች አገልግሎት ባለሙያ የሆኑት አቶ ሞላ ልንገረዉ ላይ ነው እርምጃ የወሰደው።
ግለሰቦቹ በተለያዩ ግዜያት ተገልጋዮችን ማንገላታትና አገልግሎትን ያለአግባብ በገንዘብ ሲሸጡ የነበረ መሆኑን በማስረጃ በማረጋገጥ በአዋጅ 87/2017 ዓ.ም ላይ በተቀመጠዉ አሰራር መሰረት ከስራ እንዲሰናበቱ ዉሳኔ መሰጠቱን ነው የገለጸው።
ኤጀንሲው ከህገ-ወጥ ደላሎች እና አገልግሎትን በገንዘብ ከሚሸጡ ህብረተሰቡ ራሱን እንዲጠብቅ አሳስቦ ተመሳሳይ አይነት ነገር ሲገጥም በ7533 የነፃ የስልክ መስመር እንዲሰጡ ጥሪ አስተላልፏል።
ከዚህ ቀደም ቲክቫህ ኢትዮጵያ በጉዳዩ ላይ የሰራው ዘገባ ከላይ ተያይዟል።
@TikvahethMagazine
በቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 12 የነዋሪዎች ቡድን መሪ የሆኑትን ጨምሮ አገልግሎቶችን በገንዘብ ሲሸጡ እና ህብረተሰቡን ሲያንገላቱ የነበሩ ባለሙያዎች ከመንግስት ስራ እንዲሰናበቱ ዉሳኔ መተላለፉን የሲቪል ምዝገባ እና የነዋሪነት አገልግሎት ኤጀንሲ አስታውቋል።
ኤጀንሲው ደረሰኝ ያለውን የተገልጋይ ጥቆማ መሰረት አድርጎ የቦሌ ክ/ከተማ ወረዳ 12 የነዋሪዎች አገልግሎት ቡድን መሪ የሆኑት አቶ ክብረት ቦጋለ እንዲሁም የነዋሪዎች አገልግሎት ባለሙያ የሆኑት አቶ ሞላ ልንገረዉ ላይ ነው እርምጃ የወሰደው።
ግለሰቦቹ በተለያዩ ግዜያት ተገልጋዮችን ማንገላታትና አገልግሎትን ያለአግባብ በገንዘብ ሲሸጡ የነበረ መሆኑን በማስረጃ በማረጋገጥ በአዋጅ 87/2017 ዓ.ም ላይ በተቀመጠዉ አሰራር መሰረት ከስራ እንዲሰናበቱ ዉሳኔ መሰጠቱን ነው የገለጸው።
ኤጀንሲው ከህገ-ወጥ ደላሎች እና አገልግሎትን በገንዘብ ከሚሸጡ ህብረተሰቡ ራሱን እንዲጠብቅ አሳስቦ ተመሳሳይ አይነት ነገር ሲገጥም በ7533 የነፃ የስልክ መስመር እንዲሰጡ ጥሪ አስተላልፏል።
ከዚህ ቀደም ቲክቫህ ኢትዮጵያ በጉዳዩ ላይ የሰራው ዘገባ ከላይ ተያይዟል።
@TikvahethMagazine
❤83👏30👍7🤣5👎1🕊1
በሱዳን ጦርነት ለሚዋጉ የኮሎምቢያ ተዋጊዎች የቦሳሶ ወደብ መሸጋገሪያ መሆኑ ተነገረ።
የተባበሩት አረብ ኤምሬቶች የምታስተዳድረው በቦሳሶ የሚገኝ ወታደራዊ ማዘዣ ለተዋጊዎቹ መሸጋገሪያ መሆኑ ተገልጿል።
የቀድሞ የኮሎምቢያ ጦር አባላት ለግለሰባዊ ደህንነት ከተመለመሉ በኋላ ለሱዳን የፈጥኖ ደራሽ ኃይል እንዲዋጉ ይደረጋሉ ተብሏል።
አንድ የኮሎምቢያ ተዋጊ 2600 ዶላር በወር የሚያስገኝለትን ኮንትራት መፈረሙን ገልፆ #በኢትዮጵያ በኩል አድርጎ ወደ ፑንትላንድ ቦሳሶ ወደብ መወሰዱን በኋላም በዳርፉር መስፈሩን ገልጿል።
የቦሳሶ ወደብ መጀመሪያ በተባበሩት አረብ ኤምሬቶች ሲሰራ የፑንትላንድ የባህር ኃይልን ለማሰልጠን ነበር ሲባል አሁን ሙሉ ለሙሉ የተባበሩት አረብ ኤምሬቶች የምትቆጣጠረው ማዘዣ ነው ተብሏል።
ምንም እንኳን የተባበሩት አረብ ኤምሬቶች በሱዳን ጦርነት ያላትን ተሳተፎ ብትክድም ከሰሞኑ የቦሳሶ ወደብ እንዴት የኮሎምቢያ ተዋጊዎች መሸጋገሪያ እንደሆነና የተባበሩት አረብ ኤምሬቶች እየተጠቀመች እንደሆነ የሚያሳይ የምርመራ ዘገባ ወጥቷል።
ዘ ጋርዲያንና La Silla Vacia የተሰኘ የኮሎምቢያ ጋዜጣ በጉዳዩ ላይ የሰሩትን የምርመራ ሪፖርት ከዚህ ማንበብ ይችላሉ።
@TikvahethMagazine
የተባበሩት አረብ ኤምሬቶች የምታስተዳድረው በቦሳሶ የሚገኝ ወታደራዊ ማዘዣ ለተዋጊዎቹ መሸጋገሪያ መሆኑ ተገልጿል።
የቀድሞ የኮሎምቢያ ጦር አባላት ለግለሰባዊ ደህንነት ከተመለመሉ በኋላ ለሱዳን የፈጥኖ ደራሽ ኃይል እንዲዋጉ ይደረጋሉ ተብሏል።
አንድ የኮሎምቢያ ተዋጊ 2600 ዶላር በወር የሚያስገኝለትን ኮንትራት መፈረሙን ገልፆ #በኢትዮጵያ በኩል አድርጎ ወደ ፑንትላንድ ቦሳሶ ወደብ መወሰዱን በኋላም በዳርፉር መስፈሩን ገልጿል።
የቦሳሶ ወደብ መጀመሪያ በተባበሩት አረብ ኤምሬቶች ሲሰራ የፑንትላንድ የባህር ኃይልን ለማሰልጠን ነበር ሲባል አሁን ሙሉ ለሙሉ የተባበሩት አረብ ኤምሬቶች የምትቆጣጠረው ማዘዣ ነው ተብሏል።
ምንም እንኳን የተባበሩት አረብ ኤምሬቶች በሱዳን ጦርነት ያላትን ተሳተፎ ብትክድም ከሰሞኑ የቦሳሶ ወደብ እንዴት የኮሎምቢያ ተዋጊዎች መሸጋገሪያ እንደሆነና የተባበሩት አረብ ኤምሬቶች እየተጠቀመች እንደሆነ የሚያሳይ የምርመራ ዘገባ ወጥቷል።
ዘ ጋርዲያንና La Silla Vacia የተሰኘ የኮሎምቢያ ጋዜጣ በጉዳዩ ላይ የሰሩትን የምርመራ ሪፖርት ከዚህ ማንበብ ይችላሉ።
@TikvahethMagazine
❤86😢9🕊9👎4👍3
🤙 ኑሮዎን ፒያሳ ላይ ያድርጉ
➣ ውብ አፓርትመንቶቻችን ለኑሮ ምቹ በሆነችው አዲሲቷ ፒያሳ ላይ እርሰዎን ይጠብቃል
66 ካሬ ባለ 1 መኝታ
➣ 40% ሲከፍሉ 20% ቅናሽ 6,072,000 ብር ጠቅላላ ዋጋ
➣ 100% ለከፈለ 30% ቅናሽ 5,313,000 ብር ጠቅላላ ዋጋ
2 መኝታ 75 ካሬ
➣ 40% ሲከፍሉ 20% ቅናሽ
6,900,000 ብር ጠቅላላ ዋጋ
➣ 100% ለከፈለ 30% ቅናሽ 6,037,500 ብር ጠቅላላ ዋጋ
3 መኝታ 106 ካሬ
➣ 40% ሲከፍሉ 20% ቅናሽ 9,752,000 ብር ጠቅላላ ዋጋ
➣100% ለከፈለ 30% ቅናሽ 8,533,000 ብር ጠቅላላ ዋጋ
❗️ልብ ይበሉ ከላይ የተፃፉት አነስተኛ ካሬዎች ለ ምሳሌ ሲሆኑ ከፍ ያለ ካሬ ማግኜት ትችላላችሁ
ለበለጠ መረጃ
👇
☎️+251986687513
WhatsApp:- +251986687513
Email:- [email protected]
➣ ውብ አፓርትመንቶቻችን ለኑሮ ምቹ በሆነችው አዲሲቷ ፒያሳ ላይ እርሰዎን ይጠብቃል
66 ካሬ ባለ 1 መኝታ
➣ 40% ሲከፍሉ 20% ቅናሽ 6,072,000 ብር ጠቅላላ ዋጋ
➣ 100% ለከፈለ 30% ቅናሽ 5,313,000 ብር ጠቅላላ ዋጋ
2 መኝታ 75 ካሬ
➣ 40% ሲከፍሉ 20% ቅናሽ
6,900,000 ብር ጠቅላላ ዋጋ
➣ 100% ለከፈለ 30% ቅናሽ 6,037,500 ብር ጠቅላላ ዋጋ
3 መኝታ 106 ካሬ
➣ 40% ሲከፍሉ 20% ቅናሽ 9,752,000 ብር ጠቅላላ ዋጋ
➣100% ለከፈለ 30% ቅናሽ 8,533,000 ብር ጠቅላላ ዋጋ
❗️ልብ ይበሉ ከላይ የተፃፉት አነስተኛ ካሬዎች ለ ምሳሌ ሲሆኑ ከፍ ያለ ካሬ ማግኜት ትችላላችሁ
ለበለጠ መረጃ
👇
☎️+251986687513
WhatsApp:- +251986687513
Email:- [email protected]
❤16🤔1
የብፁዕ ወቅዱስ አቡነ መርቆሬዎስ ፓትርያርክ መታሰቢያ ሐውልት በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ጥቅምት 9 ቀን 2018 ዓ.ም ይመረቃል።
ምንጭ : EOTC
@TikvahethMagazine
ምንጭ : EOTC
@TikvahethMagazine
❤186🤣13😢5👍4
በጠለፋና በአስገድዶ መድፈር የተከሰሰው ግለሰብ በ15 አመት ጽኑ እስራት ተቀጣ።
በካፋ ዞን በቢጣ ወረዳ ኦጊ ዳኪቲ ቀበሌ የካቲት 16 ቀን 2017 ዓ.ም ከቀኑ 7:00 ሰዓት ላይ ገበያ ለመገበያየት እየሄደች ያለች የግል ተበዳይን ጠልፎ በመድፈር ወንጀል ተከሶ በ15 ዓመት እስራት መቀጣቱን ወረዳው አስታውቋል።
ተከሳሽ ለጊዜው እጃቸውን ለፖሊስ ካልሰጡ ግብራበሮቹ ጋር በመሆንና ስለታማ ቁስ በእጁ ይዞ በማስፈራራት የጠለፋ ወንጀል በመፈፀም ወደ ጌሻ ወረዳ ሀነቶ ቀበሌ አስገድዶ ስለመውሰዱ ነው ፖሊስ ያስረዳው።
በዚሁ መሠረት የቢጣ ወረዳ ፍርድ ቤት ጥቅምት 3 ቀን 2018 ዓ.ም በዋለው የወንጀል ችሎት ተከሳሹ ኤልያስ ቆጭቶ በሁለት ወንጀሎች ጥፋተኛ ሆኖ በመገኘቱ በ15 አመት ፅኑ እስራት እንዲቀጣ ወስኖበታል።
@TikvahethMagazine
በካፋ ዞን በቢጣ ወረዳ ኦጊ ዳኪቲ ቀበሌ የካቲት 16 ቀን 2017 ዓ.ም ከቀኑ 7:00 ሰዓት ላይ ገበያ ለመገበያየት እየሄደች ያለች የግል ተበዳይን ጠልፎ በመድፈር ወንጀል ተከሶ በ15 ዓመት እስራት መቀጣቱን ወረዳው አስታውቋል።
ተከሳሽ ለጊዜው እጃቸውን ለፖሊስ ካልሰጡ ግብራበሮቹ ጋር በመሆንና ስለታማ ቁስ በእጁ ይዞ በማስፈራራት የጠለፋ ወንጀል በመፈፀም ወደ ጌሻ ወረዳ ሀነቶ ቀበሌ አስገድዶ ስለመውሰዱ ነው ፖሊስ ያስረዳው።
በዚሁ መሠረት የቢጣ ወረዳ ፍርድ ቤት ጥቅምት 3 ቀን 2018 ዓ.ም በዋለው የወንጀል ችሎት ተከሳሹ ኤልያስ ቆጭቶ በሁለት ወንጀሎች ጥፋተኛ ሆኖ በመገኘቱ በ15 አመት ፅኑ እስራት እንዲቀጣ ወስኖበታል።
@TikvahethMagazine
👎44❤24😢17👏7🤔1🤬1