ኦሲሜን በጋላታሳራይ መቆየት ይፈልጋል !
ናይጄሪያዊው የፊት መስመር አጥቂ ቪክቶር ኦሲሜን ስኬታማ የውሰት አመት ባሳለፈበት ጋላታሳራይ ለመቀጠል ማሰቡ ተገልጿል።
ተጨዋቹ በክለቡ በቋሚነት ለመቀጠል ከስምምነት መድረሱን የቱርክ መገናኛ ብዙሃን ዘግበዋል።
ቪክቶር ኦሲሜን ከሳውዲ አረቢያው ክለብ አል ሂላል የቀረበለትን አመታዊ 40 ሚልዮን ዩሮ ክፍያ ውድቅ ማድረጉ አይዘነጋም።
ጋላታሳራይ በቀጣይ ከናፖሊ ጋር ከስምምነት ለመድረስ ጥረት እንደሚጀምሩ ሲገለፅ ከውል ማፍረሻው ባነሰ ዋጋ ይሸጣል የሚል እምነት አላቸው ተብሏል።
ጋላታሳራይ የተጨዋቾች የዝውውር መስኮቱ ቀን እየተጠናቀቀ ሲሄድ ናፖሊ የሚጠይቀው ክፍያ ዝቅ ያደርጋል የሚል እምነት እንዳላቸው ተገልጿል።
ቪክቶር ኦሲሜን ባለፈው አመት በውሰት ከናፖሊ ጋላታሳራይን ተቀላቅሎ በ 41 ጨዋታዎች 37 ጎሎችን ማስቆጠር ችሏል።
@Tikvahethsport @kidusyoftahe
ናይጄሪያዊው የፊት መስመር አጥቂ ቪክቶር ኦሲሜን ስኬታማ የውሰት አመት ባሳለፈበት ጋላታሳራይ ለመቀጠል ማሰቡ ተገልጿል።
ተጨዋቹ በክለቡ በቋሚነት ለመቀጠል ከስምምነት መድረሱን የቱርክ መገናኛ ብዙሃን ዘግበዋል።
ቪክቶር ኦሲሜን ከሳውዲ አረቢያው ክለብ አል ሂላል የቀረበለትን አመታዊ 40 ሚልዮን ዩሮ ክፍያ ውድቅ ማድረጉ አይዘነጋም።
ጋላታሳራይ በቀጣይ ከናፖሊ ጋር ከስምምነት ለመድረስ ጥረት እንደሚጀምሩ ሲገለፅ ከውል ማፍረሻው ባነሰ ዋጋ ይሸጣል የሚል እምነት አላቸው ተብሏል።
ጋላታሳራይ የተጨዋቾች የዝውውር መስኮቱ ቀን እየተጠናቀቀ ሲሄድ ናፖሊ የሚጠይቀው ክፍያ ዝቅ ያደርጋል የሚል እምነት እንዳላቸው ተገልጿል።
ቪክቶር ኦሲሜን ባለፈው አመት በውሰት ከናፖሊ ጋላታሳራይን ተቀላቅሎ በ 41 ጨዋታዎች 37 ጎሎችን ማስቆጠር ችሏል።
@Tikvahethsport @kidusyoftahe
❤129🔥17😁12👍7👎7🥰3
TIKVAH-SPORT
ሼዝኒ አዲስ ኮንትራት ቀረበለት ! ፖላንዳዊው ግብ ጠባቂ ሼዝኒ ከባርሴሎና አዲስ ኮንትራት እንደቀረበለት ተናግሯል። “ ባርሴሎና አዲስ የሁለት አመት ኮንትራት አቅርቦልኛል “ ሲል ሼዝኒ አስተያየቱን ሰጥቷል። አክሎም " አሁን በተጨዋችነት ልቀጥል ወይስ ጓንቴን ልስቀል የሚለውን ከቤተሰቤ ጋር ተነጋግሬ እወስናለሁ “ ሲል ተናግሯል። ከአመት በፊት ጓንቱን ሰቅሎ የነበረው ሼዝኒ ባለፈው አመት ለባርሴሎና…
ባርሴሎና የሼዝኒን ውል አራዘመ !
የካታላኑ ክለብ ባርሴሎና የፖላንዳዊውን ግብ ጠባቂ ሼዝኒ ኮንትራት ለተጨማሪ አመታት ማራዘማቸውን በይፋ አስታውቀዋል።
የ 35ዓመቱ ሼዝኒ በባርሴሎና እስከ 2027 የሚያቆየውን የሁለት አመታት ውል መፈረሙ ይፋ ሆኗል።
ከአመት በፊት ጓንቱን ሰቅሎ የነበረው ሼዝኒ ባለፈው አመት ለባርሴሎና ፈርሞ ድንቅ የሚባል ጊዜ ማሳለፉ አይዘነጋም።
ባርሴሎና በቀጣይ የቡድኑ አምበል ቴር ስቴገን ክለቡን እንዲለቅ እንደሚፈልጉ ተገልጿል።
ባርሴሎና በዚህ አመት የእስፓኞሉን ግብ ጠባቂ ሁዋን ጋርሺያ ለቡድኑ ቁጥር አንድ ግብ ጠባቂነት ማስፈረማቸው አይዘነጋም።
@tikvahethsport @kidusyoftahe
የካታላኑ ክለብ ባርሴሎና የፖላንዳዊውን ግብ ጠባቂ ሼዝኒ ኮንትራት ለተጨማሪ አመታት ማራዘማቸውን በይፋ አስታውቀዋል።
የ 35ዓመቱ ሼዝኒ በባርሴሎና እስከ 2027 የሚያቆየውን የሁለት አመታት ውል መፈረሙ ይፋ ሆኗል።
ከአመት በፊት ጓንቱን ሰቅሎ የነበረው ሼዝኒ ባለፈው አመት ለባርሴሎና ፈርሞ ድንቅ የሚባል ጊዜ ማሳለፉ አይዘነጋም።
ባርሴሎና በቀጣይ የቡድኑ አምበል ቴር ስቴገን ክለቡን እንዲለቅ እንደሚፈልጉ ተገልጿል።
ባርሴሎና በዚህ አመት የእስፓኞሉን ግብ ጠባቂ ሁዋን ጋርሺያ ለቡድኑ ቁጥር አንድ ግብ ጠባቂነት ማስፈረማቸው አይዘነጋም።
@tikvahethsport @kidusyoftahe
❤136👍25😁9🔥5
TIKVAH-SPORT
ኤዱ ጋስፐር ለምን ከአርሰናል ጋር ይለያያሉ ? የሰሜን ለንደኑ ክለብ አርሰናል ብሬዚላዊ ስፖርቲንግ ዳይሬክተር ኤዱ ጋስፐር ከክለቡ ጋር ለመለያየት መወሰናቸውን ዘ አትሌቲክ አረጋግጧል። ስፖርቲንግ ዳይሬክተሩ ከአምስት አመታት በላይ ከቆዩበት አርሰናል ለመልቀቅ የወሰኑት አዲስ ሀላፊነት በማግኘታቸው መሆኑ ተገልጿል። ኤዱ ጋስፐር መድፈኞቹን የሚለቁት በኖቲንግሀም ፎረስት ባለቤት ኢቫንጄሎስ ማሪናኪስ…
ኤዱ ጋስፐር በሀላፊነት ተሾመዋል !
የቀድሞ የአርሰናል ስፖርቲንግ ዳይሬክተር ኤዱ ጋስፐር በኖቲንግሀም ፎረስት በሀላፊነት መሾማቸው ተገልጿል።
ኤዱ ጋስፐር በኖቲንግሀም ፎረስት የክለቡ ዋና የእግርኳስ የበላይ ሀላፊ በመሆን መሾማቸው ተገልጿል።
ኤዱ ጋስፐር በቀጣይ በኖቲንግሀም የዝውውር ጉዳይ ፣ የቡድኑን አቋም እና ተጨዋቾችን እድገት ጨምሮ ሁሉንም የእግርኳስ ነክ ስራ እንደሚቆጣጠሩ ተነግሯል።
“ በዚህ አዲስ ምዕራፍ ደስተኛ ነኝ እኔ ላይ በተጣለው እምነት ኮርቻለሁ ፤ የፕሬዝዳንቱን ምኞት ለመገንባት እና ለማሳካት ጓጉቻለሁ “ ሲሉ ኤዱ ተናግረዋል።
ኤዱ ጋስፐር ከወራት በፊት አርሰናልን ከአምስት አመታት በኋላ መልቀቃቸው አይዘነጋም።
@tikvahethsport @kidusyoftahe
የቀድሞ የአርሰናል ስፖርቲንግ ዳይሬክተር ኤዱ ጋስፐር በኖቲንግሀም ፎረስት በሀላፊነት መሾማቸው ተገልጿል።
ኤዱ ጋስፐር በኖቲንግሀም ፎረስት የክለቡ ዋና የእግርኳስ የበላይ ሀላፊ በመሆን መሾማቸው ተገልጿል።
ኤዱ ጋስፐር በቀጣይ በኖቲንግሀም የዝውውር ጉዳይ ፣ የቡድኑን አቋም እና ተጨዋቾችን እድገት ጨምሮ ሁሉንም የእግርኳስ ነክ ስራ እንደሚቆጣጠሩ ተነግሯል።
“ በዚህ አዲስ ምዕራፍ ደስተኛ ነኝ እኔ ላይ በተጣለው እምነት ኮርቻለሁ ፤ የፕሬዝዳንቱን ምኞት ለመገንባት እና ለማሳካት ጓጉቻለሁ “ ሲሉ ኤዱ ተናግረዋል።
ኤዱ ጋስፐር ከወራት በፊት አርሰናልን ከአምስት አመታት በኋላ መልቀቃቸው አይዘነጋም።
@tikvahethsport @kidusyoftahe
❤170👍42😁27👎6
የአርሰናል የዮከሬሽ ዝውውር ምን ላይ ደረሰ ?
አርሰናል ቪክቶር ዮከሬሽን ለማስፈረም ከስፖርቲንግ ሊስበን ጋር እስካሁን ከስምምነት እንዳልደረሱ ተገልጿል።
አሁንም የሚቀሩ ስራዎች ይኑሩ እንጂ አርሰናል ተጫዋቹን ለማስፈረም የሚያደርገው ንግግር ለስምምነት የቀረበ ደረጃ ላይ መድረሱ ተነግሯል።
መድፈኞቹ ተጫዋቹን በአምስት አመት ኮንትራት ለማስፈረም ከወዲሁ በግል ከስምምነት መድረሳቸው ታውቋል።
ስዊድናዊ አጥቂ ቪክቶር ዮከሬሽ በበኩሉ አርሰናልን ለመቀላቀል ዝግጁ መሆኑ ሲገለፅ ሚኬል አርቴታ ዝውውሩ በቶሎ እንዲፈፀም ግፊት እያደረጉ መሆኑ ተዘግቧል።
የአርሰናል ሌሎች ዝውውሮች ምን ይመስላሉ ?
አርሰናል ኖኒ ማዱኬን ለማስፈረም እስካሁን በይፋ ከቼልሲ ጋር ለንግግር አለመቀመጣቸው ተገልጿል።
ኖኒ ማዱኬ በበኩሉ ወደ አርሰናል ለመዘዋወር እንደሚፈልግ እና በቀረበለት ጥያቄ መደሰቱ ተነግሯል።
መድፈኞቹ አሁንም በኦሊ ዋትኪንስ ላይ ያላቸው ፍላጎት እንዳለ እና ሁኔታውን እንደሚከታተሉ ተጠቁሟል።
@Tikvahethsport @kidusyoftahe
አርሰናል ቪክቶር ዮከሬሽን ለማስፈረም ከስፖርቲንግ ሊስበን ጋር እስካሁን ከስምምነት እንዳልደረሱ ተገልጿል።
አሁንም የሚቀሩ ስራዎች ይኑሩ እንጂ አርሰናል ተጫዋቹን ለማስፈረም የሚያደርገው ንግግር ለስምምነት የቀረበ ደረጃ ላይ መድረሱ ተነግሯል።
መድፈኞቹ ተጫዋቹን በአምስት አመት ኮንትራት ለማስፈረም ከወዲሁ በግል ከስምምነት መድረሳቸው ታውቋል።
ስዊድናዊ አጥቂ ቪክቶር ዮከሬሽ በበኩሉ አርሰናልን ለመቀላቀል ዝግጁ መሆኑ ሲገለፅ ሚኬል አርቴታ ዝውውሩ በቶሎ እንዲፈፀም ግፊት እያደረጉ መሆኑ ተዘግቧል።
የአርሰናል ሌሎች ዝውውሮች ምን ይመስላሉ ?
አርሰናል ኖኒ ማዱኬን ለማስፈረም እስካሁን በይፋ ከቼልሲ ጋር ለንግግር አለመቀመጣቸው ተገልጿል።
ኖኒ ማዱኬ በበኩሉ ወደ አርሰናል ለመዘዋወር እንደሚፈልግ እና በቀረበለት ጥያቄ መደሰቱ ተነግሯል።
መድፈኞቹ አሁንም በኦሊ ዋትኪንስ ላይ ያላቸው ፍላጎት እንዳለ እና ሁኔታውን እንደሚከታተሉ ተጠቁሟል።
@Tikvahethsport @kidusyoftahe
❤253😁53👍33👎20🥰14👏3
“ የክለቦች አለም ዋንጫ ምርጥ ውድድር ነው “ ካይሴዶ
የሰማያዊዎቹ የመሐል ሜዳ ተጨዋች ሞይሰስ ካይሴዶ የክለቦች አለም ዋንጫ ውድድርን “ ድንቅ ውድድር “ ሲል ገልፆታል።
“ እውነታው የክለቦች አለም ዋንጫ ምርጥ ውድድር መሆኑ ነው “ ሲል ሞይሰስ ካይሴዶ ቅሬታ የለኝም ብሏል።
አክሎም “ ግማሽ ፍፃሜ ደርሰናል እዚህ በመሆናችን እና ባሳካነው ነገር ደስተኞች ነን። “ ብሏል።
“ ለመሻሻል ያስቀመጥኩት ገደብ የለም ከአለም ምርጥ ተጨዋቾች አንዱ መሆን እፈልጋለሁ “ ሞይሰስ ካይሴዶ
@Tikvahethsport @kidusyoftahe
የሰማያዊዎቹ የመሐል ሜዳ ተጨዋች ሞይሰስ ካይሴዶ የክለቦች አለም ዋንጫ ውድድርን “ ድንቅ ውድድር “ ሲል ገልፆታል።
“ እውነታው የክለቦች አለም ዋንጫ ምርጥ ውድድር መሆኑ ነው “ ሲል ሞይሰስ ካይሴዶ ቅሬታ የለኝም ብሏል።
አክሎም “ ግማሽ ፍፃሜ ደርሰናል እዚህ በመሆናችን እና ባሳካነው ነገር ደስተኞች ነን። “ ብሏል።
“ ለመሻሻል ያስቀመጥኩት ገደብ የለም ከአለም ምርጥ ተጨዋቾች አንዱ መሆን እፈልጋለሁ “ ሞይሰስ ካይሴዶ
@Tikvahethsport @kidusyoftahe
😁181❤178👍30👎11👏1
“ በትክክለኛው መንገድ ላይ ነን “ ማሬስካ
የለንደኑ ክለብ ቼልሲ ዋና አሰልጣኝ ኢንዞ ማሬስካ ቡድናቸው በትክክለኛው መንገድ ላይ እየተጓዘ መሆኑን ገልጸዋል።
“ ለመሻሻል ሁልጊዜም ቦታ አለ “ ያሉት ማሬስካ “ በትክክለኛው መንገድ ላይ ነን ነገርግን ብዙ ነገሮችን የተሻለ ማድረግ እንችላለን “ ብለዋል።
“ በጨዋታዎች ላይ የበለጠ ማጥቃት እና የበለጠ መከላከል ይኖርብናል “ ማሬስካ
የነገው የፍሉሚኔንስ ጨዋታ " አስቸጋሪ ይሆናል " ያሉት አሰልጣኝ ኢንዞ ማሬስካ አሰልጣኛቸውን አውቀዋለሁ የተለየ አሰልጣኝ ነው ሲሉ ተናግረዋል።
አሰልጣኝ ኢንዞ ማሬስካ በንግግራቸው ወቅት ሮሚዮ ላቪያ ለነገው ጨዋታ ዝግጁ አይደለም በማለት ገልጸዋል።
@Tikvahethsport @kidusyoftahe
የለንደኑ ክለብ ቼልሲ ዋና አሰልጣኝ ኢንዞ ማሬስካ ቡድናቸው በትክክለኛው መንገድ ላይ እየተጓዘ መሆኑን ገልጸዋል።
“ ለመሻሻል ሁልጊዜም ቦታ አለ “ ያሉት ማሬስካ “ በትክክለኛው መንገድ ላይ ነን ነገርግን ብዙ ነገሮችን የተሻለ ማድረግ እንችላለን “ ብለዋል።
“ በጨዋታዎች ላይ የበለጠ ማጥቃት እና የበለጠ መከላከል ይኖርብናል “ ማሬስካ
የነገው የፍሉሚኔንስ ጨዋታ " አስቸጋሪ ይሆናል " ያሉት አሰልጣኝ ኢንዞ ማሬስካ አሰልጣኛቸውን አውቀዋለሁ የተለየ አሰልጣኝ ነው ሲሉ ተናግረዋል።
አሰልጣኝ ኢንዞ ማሬስካ በንግግራቸው ወቅት ሮሚዮ ላቪያ ለነገው ጨዋታ ዝግጁ አይደለም በማለት ገልጸዋል።
@Tikvahethsport @kidusyoftahe
❤169😁29👍14🥰1
TIKVAH-SPORT
ኒውካስል የዝውውር ጥያቄ አቀረበ ! ኒውካስል ዩናይትድ የኖቲንግሀም ፎረስቱን የፊት መስመር ተጨዋች አንቶኒ ኢላንጋ ለማስፈረም 55 ሚልዮን ፓውንድ ማቅረባቸው ተገልጿል። ኖቲንግሀም ፎረስት በቅርቡ ኒውካስል ዩናይትድ ያቀረበውን 45 ሚልዮን ፓውንድ ውድቅ ማድረጉ አይዘነጋም። ኒውካስል አሁን ላይ ዝውውሩን እውን ለማድረግ ከኖቲንግሀም ፎረስት ጋር ንግግር ላይ መሆናቸው ተዘግቧል። የ 23ዓመቱ አንቶኒ…
ኒውካስል ኢላንጋን ለማስፈረም ተስማማ !
ኒውካስል ዩናይትድ የኖቲንግሀም ፎረስቱን የፊት መስመር ተጨዋች አንቶኒ ኢላንጋ ለማስፈረም ከስምምነት ደርሰዋል።
ኒውካስል ተጫዋቹን 55 ሚልዮን ፓውንድ በሚደርስ የዝውውር ሒሳብ ለማስፈረም ከስምምነት መድረሳቸው ተገልጿል።
አንቶኒ ኢላንጋ በኒውካስል ዩናይትድ ቤት የረጅም ጊዜ ውል እንደሚፈርም ፋብሪዝዮ ሮማኖ ዘግቧል።
የ 23ዓመቱ አንቶኒ ኢላንጋ ባለፈው አመት በሁሉም የፕርሚየር ሊግ ጨዋታዎች ለኖቲንግሀም ግልጋሎት ሰጥቷል።
ተጨዋቹ በጨዋታዎቹ ስድስት ጎሎች አስቆጥሮ 11 አመቻችቶ ማቀበልም ችሏል።
@Tikvahethsport @kidusyoftahe
ኒውካስል ዩናይትድ የኖቲንግሀም ፎረስቱን የፊት መስመር ተጨዋች አንቶኒ ኢላንጋ ለማስፈረም ከስምምነት ደርሰዋል።
ኒውካስል ተጫዋቹን 55 ሚልዮን ፓውንድ በሚደርስ የዝውውር ሒሳብ ለማስፈረም ከስምምነት መድረሳቸው ተገልጿል።
አንቶኒ ኢላንጋ በኒውካስል ዩናይትድ ቤት የረጅም ጊዜ ውል እንደሚፈርም ፋብሪዝዮ ሮማኖ ዘግቧል።
የ 23ዓመቱ አንቶኒ ኢላንጋ ባለፈው አመት በሁሉም የፕርሚየር ሊግ ጨዋታዎች ለኖቲንግሀም ግልጋሎት ሰጥቷል።
ተጨዋቹ በጨዋታዎቹ ስድስት ጎሎች አስቆጥሮ 11 አመቻችቶ ማቀበልም ችሏል።
@Tikvahethsport @kidusyoftahe
❤152👍32😁6😱1
ሩበን አሞሪም የክለቡን ውሳኔ ውድቅ አደረጉ !
ማንችስተር ዩናይትድ ዘጋቢ ፊልም ለማዘጋጀት ከአሜሪካው ግዙፉ መዝናኛ ተቋም አማዞን ጋር ሲያደርገው የነበረውን ንግግር ማቋረጡ ተገልጿል።
ማንችስተር ዩናይትድ በሚቀጥለው የውድድር አመት ቡድኑ ከመጋረጃ ጀርባ የሚኖረውን ሁነት ዘጋቢ ፊልም ለማዘጋጀት ከአማዞን ጋር ንግግር ላይ ነበር።
አማዞን የቡድኑን ያልታዩ የመጋረጃ ጀርባ ሁነቶች ቀርፆ ለማቅረብ ለማንችስተር ዩናይትድ 10 ሚልዮን ፓውንድ ክፍያ አቅርበው እንደነበር ተገልጿል።
የክለቡ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኦማር ቤራዳ በሀሳቡ ተስማምተው የነበረ ቢሆንም አሰልጣኝ ሩበን አሞሪም ውድቅ ማድረጋቸው ተነግሯል።
ስምምነቱ ቢፈፀም አማዞን ማንችስተር ዩናይትድ ውስጥ ሁሉንም ቦታዎች የሚያካልል ያልተገደበ መዳረሻ ይኖረው እንደነበር ተዘግቧል።
ሩበን አሞሪም በበኩላቸው ቀድሞውን ችግር ውስጥ በሚገኘው መልበሻ ቤት ይህንን ማድረግ አላስፈላጊ ትኩረት ይስባል ማለታቸው ተገልጿል።
በተጨማሪም አሰልጣኙ መልበሻ ቤት ውስጥ የሚያሳዩት ባህሪ ተቀርጾ እንዳይወጣ መስጋታቸው ተነግሯል።
አሰልጣኝ ሩበን አሞሪም ባለፈው አመት በቡድኑ አቋም በመበሳጨት የመልበሻ ቤቱን ስክሪን መስበራቸው አይዘነጋም።
@Tikvahethsport @kidusyoftahe
ማንችስተር ዩናይትድ ዘጋቢ ፊልም ለማዘጋጀት ከአሜሪካው ግዙፉ መዝናኛ ተቋም አማዞን ጋር ሲያደርገው የነበረውን ንግግር ማቋረጡ ተገልጿል።
ማንችስተር ዩናይትድ በሚቀጥለው የውድድር አመት ቡድኑ ከመጋረጃ ጀርባ የሚኖረውን ሁነት ዘጋቢ ፊልም ለማዘጋጀት ከአማዞን ጋር ንግግር ላይ ነበር።
አማዞን የቡድኑን ያልታዩ የመጋረጃ ጀርባ ሁነቶች ቀርፆ ለማቅረብ ለማንችስተር ዩናይትድ 10 ሚልዮን ፓውንድ ክፍያ አቅርበው እንደነበር ተገልጿል።
የክለቡ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኦማር ቤራዳ በሀሳቡ ተስማምተው የነበረ ቢሆንም አሰልጣኝ ሩበን አሞሪም ውድቅ ማድረጋቸው ተነግሯል።
ስምምነቱ ቢፈፀም አማዞን ማንችስተር ዩናይትድ ውስጥ ሁሉንም ቦታዎች የሚያካልል ያልተገደበ መዳረሻ ይኖረው እንደነበር ተዘግቧል።
ሩበን አሞሪም በበኩላቸው ቀድሞውን ችግር ውስጥ በሚገኘው መልበሻ ቤት ይህንን ማድረግ አላስፈላጊ ትኩረት ይስባል ማለታቸው ተገልጿል።
በተጨማሪም አሰልጣኙ መልበሻ ቤት ውስጥ የሚያሳዩት ባህሪ ተቀርጾ እንዳይወጣ መስጋታቸው ተነግሯል።
አሰልጣኝ ሩበን አሞሪም ባለፈው አመት በቡድኑ አቋም በመበሳጨት የመልበሻ ቤቱን ስክሪን መስበራቸው አይዘነጋም።
@Tikvahethsport @kidusyoftahe
❤421😁173👏61👍31👎5
ክረምትን በምን ሊያሳልፋ አስበዋል?
Can PlayStation 🎮 መፍትሄ ይዞ ብቅ ብሎሎታል🫴
-Sony
PlayStation 2
PlayStation 3
PlayStation 4
PlayStation 5
-Microsoft
Xbox 360
Xbox one
Xbox one s
Xbox Series
ምርቶችን አዘጋጅቶ እናንተን በመጠበቅ ላይ ነን
እንግዲያውስ እርሶ በተመቻቹ ሰአት ብቅ በማለት ሱቃችን መጎብኘት ይችላሉ
እቃዎቻችን 6 ወር ዋስትና ስላለው የለ ሀሳብ ይዝናኑ
ለልጅም ለአዋቂ የሚሆኑ PlayStation Cidi Game ስላሉን ይደውሉልን
Tv በተለያየ Brand እና Size እኛ ዘንድ ያገኛሉ
ባሎት ማንኛውም እቃ መቀያየር ይቻላል
ለክፍለ ሀገር እናቀርባለን ይደውሉ
🤝Tanks for choice
አድራሻ፡፦
ቁጥር 1፦ መገናኛ
ቁጥር 2፦ ቦሌ
ስልክ፦ 0904658609 ወይም 0910529770
0977349492 ይደውሉ
ለአዳዲስ መረጃ Telegram channel join ይበሉ ፦
https://www.tg-me.com/CanPlaystation
👍Update Your Life
Can PlayStation እና Tv Market
Can PlayStation 🎮 መፍትሄ ይዞ ብቅ ብሎሎታል🫴
-Sony
PlayStation 2
PlayStation 3
PlayStation 4
PlayStation 5
-Microsoft
Xbox 360
Xbox one
Xbox one s
Xbox Series
ምርቶችን አዘጋጅቶ እናንተን በመጠበቅ ላይ ነን
እንግዲያውስ እርሶ በተመቻቹ ሰአት ብቅ በማለት ሱቃችን መጎብኘት ይችላሉ
እቃዎቻችን 6 ወር ዋስትና ስላለው የለ ሀሳብ ይዝናኑ
ለልጅም ለአዋቂ የሚሆኑ PlayStation Cidi Game ስላሉን ይደውሉልን
Tv በተለያየ Brand እና Size እኛ ዘንድ ያገኛሉ
ባሎት ማንኛውም እቃ መቀያየር ይቻላል
ለክፍለ ሀገር እናቀርባለን ይደውሉ
🤝Tanks for choice
አድራሻ፡፦
ቁጥር 1፦ መገናኛ
ቁጥር 2፦ ቦሌ
ስልክ፦ 0904658609 ወይም 0910529770
0977349492 ይደውሉ
ለአዳዲስ መረጃ Telegram channel join ይበሉ ፦
https://www.tg-me.com/CanPlaystation
👍Update Your Life
Can PlayStation እና Tv Market
❤25
የሊዮኔል ሜሲ ቀጣይ ማረፊያ የት ይሆናል ?
የ 38ዓመቱ ሊዮኔል ሜሲ ከ ኢንተር ሚያሚ ጋር ያለው ኮንትራት በ 2025 የውድድር ዘመን መጨረሻ የሚጠናቀቅ ይሆናል።
አርጀንቲናዊውን ኮከብ ለማስፈረም የሳውዲ አረቢያው የ እስያ ሻምፒየንስ ሊግ አሸናፊ አል አህሊ ከፍተኛ ፍላጎት ማሳየታቸው ታውቋል።
ኢንተር ሚያሚ ሊዮኔል ሜሲ በክለቡ ለማቆየት ቆየት ብለው ድርድር የጀመሩ ሲሆን በሚያሚ የሚያቆየውን ኮንትራት እንደሚፈርም እርግጠኞች ናቸው።
ኢንተር ሚያሚ ከዛሬ ጀምሮ በሚቀጥሉት ጥቂት ቀናት የሊዮኔል ሜሲን ውል ማራዘም ይፋ ያደርጋሉ ተብሎ ይጠበቃል።
ሊዮኔል ሜሲ ክለቡን ከተቀላቀለ በኃላ በ 42 የሊግ ጨዋታዎች 34 ጎሎችን ማስቆጠር ችሏል።
@tikvahethsport @kidusyoftahe
የ 38ዓመቱ ሊዮኔል ሜሲ ከ ኢንተር ሚያሚ ጋር ያለው ኮንትራት በ 2025 የውድድር ዘመን መጨረሻ የሚጠናቀቅ ይሆናል።
አርጀንቲናዊውን ኮከብ ለማስፈረም የሳውዲ አረቢያው የ እስያ ሻምፒየንስ ሊግ አሸናፊ አል አህሊ ከፍተኛ ፍላጎት ማሳየታቸው ታውቋል።
ኢንተር ሚያሚ ሊዮኔል ሜሲ በክለቡ ለማቆየት ቆየት ብለው ድርድር የጀመሩ ሲሆን በሚያሚ የሚያቆየውን ኮንትራት እንደሚፈርም እርግጠኞች ናቸው።
ኢንተር ሚያሚ ከዛሬ ጀምሮ በሚቀጥሉት ጥቂት ቀናት የሊዮኔል ሜሲን ውል ማራዘም ይፋ ያደርጋሉ ተብሎ ይጠበቃል።
ሊዮኔል ሜሲ ክለቡን ከተቀላቀለ በኃላ በ 42 የሊግ ጨዋታዎች 34 ጎሎችን ማስቆጠር ችሏል።
@tikvahethsport @kidusyoftahe
❤164😁23👍8👎8👏2
TIKVAH-SPORT
አርሰናል ተጨዋች ማስፈረም ተቃረበ ! የሰሜን ለንደኑ ክለብ አርሰናል የብሬንትፎርዱን የመሐል ሜዳ ተጨዋች ክርስቲያን ኖርጋርድ ለማስፈረም ከጫፍ መድረሳቸው ተገልጿል። መድፈኞቹ የ 31ዓመቱን አማካይ ክርስቲያን ኖርጋርድ በ 11 ሚልዮን ፓውንድ ለማስፈረም ከብሬንትፎርድ ጋር ለስምምነት መቃረባቸው ተነግሯል። አርሰናል ከተጨዋቹ በኩል በግል ጥቅማጥቅም ዙሪያ ከስምምነት መድረሳቸው ተገልጿል። ዴንማርካዊው…
አርሰናል የኖርጋርድን ዝውውር አጠናቀቀ !
የሰሜን ለንደኑ ክለብ አርሰናል የብሬንትፎርዱን የመሐል ሜዳ ተጨዋች ክርስቲያን ኖርጋርድ ዝውውር ማጠናቀቃቸው ተገልጿል።
መድፈኞቹ ለ 31ዓመቱ አማካይ ክርስቲያን ኖርጋርድ ዝውውር 10 ሚልዮን ፓውንድ እና ተጨማሪ ሁለት ሚልዮን ማውጣታቸው ተነግሯል።
ተጨዋቹ የህክምና ምርመራውን በማጠናቀቅ የአርሰናል ተጨዋች መሆኑ መረጋገጡን ለክለቡ ቅርብ የሆኑ ምንጮች አሳውቋል።
አርሰናል በሚቀጥሉት 48 ሰዓት የተጫዋቹን ፊርማ በይፋ ያሳውቃል ተብሎ ይጠበቃል።
ዴንማርካዊው አማካይ ክርስቲያን ኖርጋርድ ለብሬንትፎርድ በሁሉም ውድድሮች 192 ጨዋታዎች ሲያደርግ 13 ግቦችን ማስቆጠር ችሏል።
@Tikvahethsport @kidusyoftahe
የሰሜን ለንደኑ ክለብ አርሰናል የብሬንትፎርዱን የመሐል ሜዳ ተጨዋች ክርስቲያን ኖርጋርድ ዝውውር ማጠናቀቃቸው ተገልጿል።
መድፈኞቹ ለ 31ዓመቱ አማካይ ክርስቲያን ኖርጋርድ ዝውውር 10 ሚልዮን ፓውንድ እና ተጨማሪ ሁለት ሚልዮን ማውጣታቸው ተነግሯል።
ተጨዋቹ የህክምና ምርመራውን በማጠናቀቅ የአርሰናል ተጨዋች መሆኑ መረጋገጡን ለክለቡ ቅርብ የሆኑ ምንጮች አሳውቋል።
አርሰናል በሚቀጥሉት 48 ሰዓት የተጫዋቹን ፊርማ በይፋ ያሳውቃል ተብሎ ይጠበቃል።
ዴንማርካዊው አማካይ ክርስቲያን ኖርጋርድ ለብሬንትፎርድ በሁሉም ውድድሮች 192 ጨዋታዎች ሲያደርግ 13 ግቦችን ማስቆጠር ችሏል።
@Tikvahethsport @kidusyoftahe
❤250😁35👍27🔥5🤔1
ባየር ሙኒክ ንኩንኩን ማስፈረም ይፈልጋል !
የጀርመን ቡንደስሊጋ ክለብ ባየር ሙኒክ ፈረንሳዊውን የፊት መስመር ተጨዋች ክርስቶፈር ንኩንኩ ለማስፈርም በድጋሜ ኢላማ ማድረጋቸው ተገልጿል።
የቡንደስሊጋው አሸናፊ ባየር ሙኒክ ባለፈው አመት ተጫዋቹን ለማስፈረም እንቅስቃሴ አድርገው እንዳልተሳካላቸው ይታወሳል።
በዚህ ክረምት ኢላማ ያደረጓቸውን ፍሎሪያን ቨርትዝ እና ኒኮ ዊሊያምስ ያጡት ባየር ሙኒኮች ንኩንኩን ወደ ጀርመን ለመመለስ እንደሚፈልጉ ተዘግቧል።
ቼልሲዎች በበኩላቸው ተጨዋቹን መሸጥ የሚፈልጉት በቋሚ ዝውውር ብቻ መሆኑ ተገልጿል።
@Tikvahethsport @kidusyoftahe
የጀርመን ቡንደስሊጋ ክለብ ባየር ሙኒክ ፈረንሳዊውን የፊት መስመር ተጨዋች ክርስቶፈር ንኩንኩ ለማስፈርም በድጋሜ ኢላማ ማድረጋቸው ተገልጿል።
የቡንደስሊጋው አሸናፊ ባየር ሙኒክ ባለፈው አመት ተጫዋቹን ለማስፈረም እንቅስቃሴ አድርገው እንዳልተሳካላቸው ይታወሳል።
በዚህ ክረምት ኢላማ ያደረጓቸውን ፍሎሪያን ቨርትዝ እና ኒኮ ዊሊያምስ ያጡት ባየር ሙኒኮች ንኩንኩን ወደ ጀርመን ለመመለስ እንደሚፈልጉ ተዘግቧል።
ቼልሲዎች በበኩላቸው ተጨዋቹን መሸጥ የሚፈልጉት በቋሚ ዝውውር ብቻ መሆኑ ተገልጿል።
@Tikvahethsport @kidusyoftahe
❤66😁51👍7
ሊድስ ዩናይትድ ሎንግስታፍን ሊያስፈርም ነው !
አዲስ አዳጊው ክለብ ሊድስ ዩናይትድ ሎንግስታፍን ከኒውካስል ዩናይትድ ለማስፈረም በጥረት ላይ መሆናቸው ተገልጿል።
ሊድስ ዩናይትድ ለ 27ዓመቱ አማካይ 10 ሚልዮን ፓውንድ እና ተጨማሪ ሁለት ሚልዮን ክፍያ ማቅረባቸው ተነግሯል።
ኒውካስል ዩናይትድ እስካሁን ለዝውውር ጥያቄው ምላሽ አለመስጠታቸው ተነግሯል።
ሊድስ ከኒውካስል ዩናይትድ ጋር ከስምምነት መድረስ ካልቻሉ ወደ ሌላ አማራጭ እንደሚሄዱ ተጠቁሟል።
የኒውካስል አካዳሚ ውጤት ሎንግስታፍ በሚቀጥለው አመት በነፃ ከሚለቅ በዚህ አመት ክለቡ ተጠቃሚ እንዲሆን እንደሚፈልግ ተዘግቧል።
@Tikvahethsport @kidusyoftahe
አዲስ አዳጊው ክለብ ሊድስ ዩናይትድ ሎንግስታፍን ከኒውካስል ዩናይትድ ለማስፈረም በጥረት ላይ መሆናቸው ተገልጿል።
ሊድስ ዩናይትድ ለ 27ዓመቱ አማካይ 10 ሚልዮን ፓውንድ እና ተጨማሪ ሁለት ሚልዮን ክፍያ ማቅረባቸው ተነግሯል።
ኒውካስል ዩናይትድ እስካሁን ለዝውውር ጥያቄው ምላሽ አለመስጠታቸው ተነግሯል።
ሊድስ ከኒውካስል ዩናይትድ ጋር ከስምምነት መድረስ ካልቻሉ ወደ ሌላ አማራጭ እንደሚሄዱ ተጠቁሟል።
የኒውካስል አካዳሚ ውጤት ሎንግስታፍ በሚቀጥለው አመት በነፃ ከሚለቅ በዚህ አመት ክለቡ ተጠቃሚ እንዲሆን እንደሚፈልግ ተዘግቧል።
@Tikvahethsport @kidusyoftahe
❤63👍13
ዩናይትድ ግብ ጠባቂ ለማስፈረም ተመልክቷል !
ማንችስተር ዩናይትድ ሌላ ግብ ጠባቂ ማስፈረምን ከእቅዳቸው አለማውጣታቸው እና ሊያስፈርሙ እንደሚችሉ ተነግሯል።
ቀያዮቹ ሴጣኖች ግብ ጠባቂ ለማስፈረም ከወሰኑ የ 29ዓመቱን የቦታፎጎ ግብ ጠባቂ ጆን ለማስፈረም ኢላማ ማድረጋቸው ተገልጿል።
የቡድኑ ቁጥር አንድ ግብ ጠባቂ አንድሬ ኦናና በዚህ አመት በክለቡ ይቀጥላል የሚል እምነት እንዳለ መዘገቡ አይዘነጋም።
አሰልጣኝ ሩበን አሞሪም በተጨማሪም የመሐል ሜዳውን ማጠናከር እንደሚፈልጉ ተገልጿል።
ይህንንም ተከትሎ ማንችስተር ዩናይትድ የቫሌንሽያውን ዣቪ ጉዌራ ለማስፈረም ፍላጎት ማሳየታቸው ተዘግቧል።
@Tikvahethsport @kidusyoftahe
ማንችስተር ዩናይትድ ሌላ ግብ ጠባቂ ማስፈረምን ከእቅዳቸው አለማውጣታቸው እና ሊያስፈርሙ እንደሚችሉ ተነግሯል።
ቀያዮቹ ሴጣኖች ግብ ጠባቂ ለማስፈረም ከወሰኑ የ 29ዓመቱን የቦታፎጎ ግብ ጠባቂ ጆን ለማስፈረም ኢላማ ማድረጋቸው ተገልጿል።
የቡድኑ ቁጥር አንድ ግብ ጠባቂ አንድሬ ኦናና በዚህ አመት በክለቡ ይቀጥላል የሚል እምነት እንዳለ መዘገቡ አይዘነጋም።
አሰልጣኝ ሩበን አሞሪም በተጨማሪም የመሐል ሜዳውን ማጠናከር እንደሚፈልጉ ተገልጿል።
ይህንንም ተከትሎ ማንችስተር ዩናይትድ የቫሌንሽያውን ዣቪ ጉዌራ ለማስፈረም ፍላጎት ማሳየታቸው ተዘግቧል።
@Tikvahethsport @kidusyoftahe
😁124❤86👍21👎6
ዩናይትድ ሞይስ ኪንን ማስፈረም ይፈልጋል !
ማንችስተር ዩናይትድ በቡድኑ ውስጥ ክፍተት የሚያገኝ ከሆነ ተጨማሪ የፊት መስመር አጥቂ ለማስፈረም ማሰባቸው ተገልጿል።
ቀያዮቹ ሴጣኖች ለማስፈረም ከተመለከቷቸው አጥቂዎች መካከል የፊዮሬንቲናው ሞይስ ኪን ቀዳሚው መሆኑ ተነግሯል።
ተጨዋቹ በኮንትራቱ ውስጥ በቀጣይ አንድ ሳምንት ውስጥ ሊሰራ የሚችል 52 ሚልዮን ዩሮ የውል ማፍረሻ እንዳለው ተዘግቧል።
ዩናይትድ ተጫዋቹን አጥብቆ የፈለገ የፕርሚየር ሊግ ክለብ መሆኑ ሲገለፅ ከሳውዲ አረቢያ ሊግም ተጨዋቹን ማስፈረም እንደሚፈልጉ ተጠቁሟል።
ሞይስ ኪን ፊዮሬንቲናን ከተቀላቀለ ወዲህ እውነተኛ የፍፁም ቅጣት ምት ክልል አጥቂ ሆኖ መጎልበቱ ተገልጿል።
ባለፈው አመት 19 የሊግ ጎል ያገባ ሞይስ ኪን በአማካይ ከሚነካቸው 100 ኳሶች ስድስት ኢላማውን የጠበቀ ሙከራ ሲያደርግ በሴርያው ትልቁ ቁጥር መሆኑ ተዘግቧል።
በተጨማሪም ማንችስተር ዩናይትድ ከኮንትራት ነፃ የሆኑት አጥቂዎች ጄሚ ቫርዲ ፣ ካሉም ዊልሰን እና ካልቨርት ሌዊን ቀርበውለታል።
ማንችስተር ዩናይትድ አጥቂ ሳያስፈርም አመቱ ከተጠናቀቀ ከኮንትራት ነፃ ተጨዋቾችን ይመለከታል ተብሎ እንደሚጠበቅ ተዘግቧል።
@Tikvahethsport @kidusyoftahe
ማንችስተር ዩናይትድ በቡድኑ ውስጥ ክፍተት የሚያገኝ ከሆነ ተጨማሪ የፊት መስመር አጥቂ ለማስፈረም ማሰባቸው ተገልጿል።
ቀያዮቹ ሴጣኖች ለማስፈረም ከተመለከቷቸው አጥቂዎች መካከል የፊዮሬንቲናው ሞይስ ኪን ቀዳሚው መሆኑ ተነግሯል።
ተጨዋቹ በኮንትራቱ ውስጥ በቀጣይ አንድ ሳምንት ውስጥ ሊሰራ የሚችል 52 ሚልዮን ዩሮ የውል ማፍረሻ እንዳለው ተዘግቧል።
ዩናይትድ ተጫዋቹን አጥብቆ የፈለገ የፕርሚየር ሊግ ክለብ መሆኑ ሲገለፅ ከሳውዲ አረቢያ ሊግም ተጨዋቹን ማስፈረም እንደሚፈልጉ ተጠቁሟል።
ሞይስ ኪን ፊዮሬንቲናን ከተቀላቀለ ወዲህ እውነተኛ የፍፁም ቅጣት ምት ክልል አጥቂ ሆኖ መጎልበቱ ተገልጿል።
ባለፈው አመት 19 የሊግ ጎል ያገባ ሞይስ ኪን በአማካይ ከሚነካቸው 100 ኳሶች ስድስት ኢላማውን የጠበቀ ሙከራ ሲያደርግ በሴርያው ትልቁ ቁጥር መሆኑ ተዘግቧል።
በተጨማሪም ማንችስተር ዩናይትድ ከኮንትራት ነፃ የሆኑት አጥቂዎች ጄሚ ቫርዲ ፣ ካሉም ዊልሰን እና ካልቨርት ሌዊን ቀርበውለታል።
ማንችስተር ዩናይትድ አጥቂ ሳያስፈርም አመቱ ከተጠናቀቀ ከኮንትራት ነፃ ተጨዋቾችን ይመለከታል ተብሎ እንደሚጠበቅ ተዘግቧል።
@Tikvahethsport @kidusyoftahe
❤156😁84👍25👎13
የሮድሪጎ የአርሰናል ዝውውር ?
የሰሜን ለንደኑ ክለብ አርሰናል በቀጣይ የግራ ክንፍ ተጨዋች በማስፈረም ቦታውን ለማጠናከር ማሰቡ ይታወሳል።
አርሰናሎች በሮድሪጎ ዝውውር ዙሪያ ከመጋረጃ ጀርባ ትልቅ የሚባል ስራ መስራታቸው ተገልጿል።
መድፈኞቹ ተጫዋቹን በሚያስፈርሙበት ሁኔታ ላይ የመጀመሪያ ንግግር ማድረጋቸው ተዘግቧል።
አርሰናል በተጨማሪም እንደ ኢዜ አይነት ፈጣሪ የሚባል የመሐል ሜዳ ተጨዋች ለማስፈረም መመልከቱ ተነግሯል።
አርሰናል ዝውውሮቹን የሚፈፅመው ከቪክቶር ዮከሬሽ ዝውውር የሚቀረውን በጀት በመመልከት መሆኑ ተገልጿል።
መድፈኞቹ የሮድሪጎ እና ኢዜን ዝውውር የሚያደርጉት በሚለቁ ተጨዋቾች ላይ ተመርኩዘው ሊሆንም እንደሚችል ተዘግቧል።
@Tikvahethsport @kidusyoftahe
የሰሜን ለንደኑ ክለብ አርሰናል በቀጣይ የግራ ክንፍ ተጨዋች በማስፈረም ቦታውን ለማጠናከር ማሰቡ ይታወሳል።
አርሰናሎች በሮድሪጎ ዝውውር ዙሪያ ከመጋረጃ ጀርባ ትልቅ የሚባል ስራ መስራታቸው ተገልጿል።
መድፈኞቹ ተጫዋቹን በሚያስፈርሙበት ሁኔታ ላይ የመጀመሪያ ንግግር ማድረጋቸው ተዘግቧል።
አርሰናል በተጨማሪም እንደ ኢዜ አይነት ፈጣሪ የሚባል የመሐል ሜዳ ተጨዋች ለማስፈረም መመልከቱ ተነግሯል።
አርሰናል ዝውውሮቹን የሚፈፅመው ከቪክቶር ዮከሬሽ ዝውውር የሚቀረውን በጀት በመመልከት መሆኑ ተገልጿል።
መድፈኞቹ የሮድሪጎ እና ኢዜን ዝውውር የሚያደርጉት በሚለቁ ተጨዋቾች ላይ ተመርኩዘው ሊሆንም እንደሚችል ተዘግቧል።
@Tikvahethsport @kidusyoftahe
❤339😁59👍23👎5
ቼልሲ ንዋኔሪን ለማስፈረም እየተመለከተ ነው !
የምዕራብ ለንደኑ ክለብ ቼልሲ የአርሰናሉን የፊት የመስመር ተጨዋች ኢታን ንዋኔሪ ለማስፈረም የኮንትራት ሁኔታውን በቅርበት እየተከታተሉ መሆኑ ተገልጿል።
ቼልሲ ተጨዋቹ ከዚህ በፊት በአርሰናል ውሉን ከማራዘሙ በፊት ሊያስፈርሙት ከፍተኛ ጥረት አድርገው እንደነበር ይታወሳል።
አሁን ላይ ኢታን ንዋኔሪ በአርሰናል ቤት ያለው ኮንትራት አንድ አመት የሚቀረው ሲሆን ውሉን ለማራዘም ንግግር ላይ ነው።
አርሰናል የተጫዋቹን ውል ለማራዘም እስካሁን ከስምምነት ባይደርሩም በቅርቡ አዲስ ውል እንደሚፈርም እርግጠኞች ናቸው።
ቼልሲ በተጨማሪም እንግሊዛዊውን የአስቶን ቪላ ተጨዋች ሞርጋን ሮጀርስ እንደሚያደንቁ ተገልጿል።
@Tikvahethsport @kidusyoftahe
የምዕራብ ለንደኑ ክለብ ቼልሲ የአርሰናሉን የፊት የመስመር ተጨዋች ኢታን ንዋኔሪ ለማስፈረም የኮንትራት ሁኔታውን በቅርበት እየተከታተሉ መሆኑ ተገልጿል።
ቼልሲ ተጨዋቹ ከዚህ በፊት በአርሰናል ውሉን ከማራዘሙ በፊት ሊያስፈርሙት ከፍተኛ ጥረት አድርገው እንደነበር ይታወሳል።
አሁን ላይ ኢታን ንዋኔሪ በአርሰናል ቤት ያለው ኮንትራት አንድ አመት የሚቀረው ሲሆን ውሉን ለማራዘም ንግግር ላይ ነው።
አርሰናል የተጫዋቹን ውል ለማራዘም እስካሁን ከስምምነት ባይደርሩም በቅርቡ አዲስ ውል እንደሚፈርም እርግጠኞች ናቸው።
ቼልሲ በተጨማሪም እንግሊዛዊውን የአስቶን ቪላ ተጨዋች ሞርጋን ሮጀርስ እንደሚያደንቁ ተገልጿል።
@Tikvahethsport @kidusyoftahe
😁145❤106👎18😢8👍3🤬3🔥2
TIKVAH-SPORT
አርኔ ስሎት ቡድኑን መርዳት ላይ ያተኩራሉ ! አሰልጣኝ አርኔ ስሎት ባለፈው ሳምንት ሶስቱን አዳዲስ ፈራሚዎች ከቡድናቸው ጋር የማዋሀድ ስራ ቀዳሚው ተግባራቸው አድርገው አንደነበር ተገልጿል። ከቡድኑ ተጨዋች ዲያጎ ጆታ ድንገተኛ ህልፈት በኋላ አሁን ላይ የአሰልጣኙ ቀዳሚ እቅድ አስፈላጊ ነገር ተደርጎ አይታይም። አሰልጣኝ አርኔ ስሎት በቀጣይ ቀዳሚው ፈታኝ ተግባራቸው በቡድን አጋራቸው አሳዛኝ ህልፈት…
ሊቨርፑል የዝግጅት ጊዜውን ጀመረ !
በድንገተኛ የመኪና አደጋ ተጫዋቹ ዲያጎ ጆታን ያጣው ሊቨርፑል ዛሬ በልምምድ ማዕከሉ በመገኘት ዝግጅቱን ይጀመራል።
በሊቨርፑሉ " AXA " ልምምድ ማዕከል በር ላይ ዲያጎ ጆታን የሚገልጹ በርካታ መልዕክቶች እና አበባዎች ተቀምጠው ታይተዋል።
መሐመድ ሳላህ በልምምድ ማዕከሉ ሲገኝ አዲሱ ፈራሚ ፍሪምፖንግ እንዲሁም ሌሎች ተጨዋቾች ቀድመው በማዕከሉ ተገኝተዋል።
ሊቨርፑል ከአምስት ቀናት በኋላ ከፕሪስተን ጋር የመጀመሪያ የወዳጅነት ጨዋታ ሲያደርግ ጨዋታው የቀጥታ ስርጭት ሽፋን ያገኛል ተብሏል።
@Tikvahethsport @kidusyoftahe
በድንገተኛ የመኪና አደጋ ተጫዋቹ ዲያጎ ጆታን ያጣው ሊቨርፑል ዛሬ በልምምድ ማዕከሉ በመገኘት ዝግጅቱን ይጀመራል።
በሊቨርፑሉ " AXA " ልምምድ ማዕከል በር ላይ ዲያጎ ጆታን የሚገልጹ በርካታ መልዕክቶች እና አበባዎች ተቀምጠው ታይተዋል።
መሐመድ ሳላህ በልምምድ ማዕከሉ ሲገኝ አዲሱ ፈራሚ ፍሪምፖንግ እንዲሁም ሌሎች ተጨዋቾች ቀድመው በማዕከሉ ተገኝተዋል።
ሊቨርፑል ከአምስት ቀናት በኋላ ከፕሪስተን ጋር የመጀመሪያ የወዳጅነት ጨዋታ ሲያደርግ ጨዋታው የቀጥታ ስርጭት ሽፋን ያገኛል ተብሏል።
@Tikvahethsport @kidusyoftahe
❤190👏21👎10👍6🔥1😁1