የእረፍት ሰዓት !

በእንግሊዝ ፕርሚየር ሊግ ሰላሳ ሰባተኛ ሳምንት መርሐ ግብር አርሰናል ከማንችስተር ዩናይትድ ጋር እያደረጉ የሚገኙትን ጨዋታ 1ለ0 በሆነ ውጤት እየመሩ ወደ መልበሻ ቤት አምርተዋል።

የአርሰናልን የመሪነት ግብ ሊያንድሮ ትሮሳርድ ማስቆጠር ችሏል።

የጨዋታው የኳስ ቁጥጥር ምን ይመስላል ?

- በመጀመሪያው አጋማሽ ማንችስተር ዩናይትድ 55% - 45% የኳስ ቁጥጥር ብልጫ ነበራቸው።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
50 ' ማንችስተር ዩናይትድ 0 - 1 አርሰናል

                             ትሮሳርድ

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
59 ' ማንችስተር ዩናይትድ 0 - 1 አርሰናል

                             ትሮሳርድ

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
66 ' ማንችስተር ዩናይትድ 0 - 1 አርሰናል

                             ትሮሳርድ

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
73 ' ማንችስተር ዩናይትድ 0 - 1 አርሰናል

                             ትሮሳርድ

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
82 ' ማንችስተር ዩናይትድ 0 - 1 አርሰናል

                             ትሮሳርድ

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
90+1 ' ማንችስተር ዩናይትድ 0 - 1 አርሰናል

                             ትሮሳርድ

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
ባየር ሙኒክ ድል አድርጓል !

በጀርመን ቡንደስሊጋ ሰላሳ ሶስተኛ ሳምንት መርሐግብር ባየር ሙኒክ ከዎልፍስበርግ ጋር ያደረጉትን ጨዋታ 2 ለ 0 በሆነ ውጤት ማሸነፍ ችለዋል።

የባየር ሙኒክን የማሸነፊያ ግቦች ሎቭሮ ዝቮናሬግ እና ሊዮን ጎሬዝካ ከመረብ ማሳረፍ ችለዋል።

የሊግ ደረጃቸው ምን ይመስላል ?

2️⃣ ባየር ሙኒክ :- 72 ነጥብ

1️⃣2️⃣ ዎልፍስበርግ :- 37 ነጥብ

ባየር ሙኒክ በቀጣይ የሊጉ መርሐ ግብር ከሆፌንሄም ጋር የሚገናኙ ይሆናል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
መድፈኞቹ የሊጉን መሪነት ተረከቡ !

በእንግሊዝ ፕርሚየር ሊግ የሰላሳ ሰባተኛ ሳምንት መርሐ ግብር አርሰናል ከማንችስተር ዩናይትድ ጋር ያደረጉትን ጨዋታ 1 ለ 0 በሆነ ውጤት ማሸነፍ ችለዋል።

የመድፈኞቹን ብቸኛ የማሸነፊያ ግብ ሊያንድሮ ትሮሳርድ ከመረብ ማሳረፍ ችሏል።

ሊያንድሮ ትሮሳርድ በዘንድሮው የውድድር አመት ለአርሰናል በሁሉም ውድድሮች አስራ ሰባት ግቦችን ማስቆጠር ችሏል።

ማንችስተር ዩናይትድ በሁሉም ውድድሮች ሰማንያ ሁለት ግቦች ሲቆጠሩበት ይህም ከሀምሳ አራት አመታት በኋላ በአንድ የውድድር አመት የተቆጠረበት ከፍተኛው ቁጥር መሆኑ ተገልጿል።

በሊጉ የደረጃ ሰንጠረዥ ስንተኛ ናቸው ?

1️⃣ አርሰናል :- 86 ነጥብ

8️⃣ ማንችስተር ዩናይትድ :- 54 ነጥብ

ቀጣይ ጨዋታ ምን ይመስላል ?

እሮብ - ማንችስተር ዩናይትድ ከ ኒውካስል

እሁድ - አርሰናል ከ ኤቨርተን

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
#Premiereleague 🏴󠁧󠁢󠁥󠁮󠁧󠁿

ማንችስተር ዩናይትድ በታሪኩ ለመጀመሪያ ጊዜ በአንድ የውድድር አመት አስራ አራት የእንግሊዝ ፕርሚየር ሊግ ጨዋታዎች ተሸንፏል።

አርሰናል ከአስራ ስምንት አመት በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ ማንችስተር ዩናይትድን በአንድ የውድድር አመት ሁለት የሊግ ጨዋታዎችን አሸንፎታል።

አርሰናል ማሸነፉን ተከትሎ የዘንድሮው የእንግሊዝ ፕርሚየር ሊግ ዋንጫ አሸናፊ ክለብ ሳምንት ከሚደረጉ የመጨረሻ ሳምንት ጨዋታዎች በኋላ ይታወቃል።

የአሰልጣኝ ሚኬል አርቴታው ቡድን አርሰናል በዘንድሮው የውድድር አመት በሊግ ምርጥ #ስድስት ክለቦች ጋር ያደረገውን ጨዋታ አልተሸነፈም።

አርሰናል በውድድር አመቱ ሀያ ሰባት ጨዋታዎችን በአሸናፊነት ሲወጣ በፕርሚየር ሊጉ ታሪክ የክለቡ ትልቅ ድል ሆኖ መመዝገብ ችሏል።

ከሊጉ መሪ አርሰናል በአንድ ነጥብ ዝቅ ብሎ ሁለተኛ ደረጃ ላይ የሚገኘው ማንችስተር ሲቲ ያለውን ቀሪ አንድ ጨዋታ ማክሰኞ ከቶተንሀም ጋር የሚያደርግ ይሆናል።

የሊጉን ዋንጫ ማን ያሳካል ?

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
" ምርጥ የቶተንሀም ደጋፊ እሆናለሁ " ሀቨርትዝ

የሰሜን ለንደኑ ክለብ አርሰናል የፊት መስመር ተጨዋች ካይ ሀቨርትዝ ማንችስተር ሲቲ ከቶተንሀም ጋር በሚያደርገው ጨዋታ ቶተንሀምን እንደሚደግፍ ተናግሯል።

" ማክሰኞ ምርጥ የቶተንሃም ደጋፊ እሆናለሁ " በማለት የተናገረው ካይ ሀቨርትዝ ሁላችንም ቶተንሀምን እንደግፋለን ጥሩ እንዲሆንላቸው እንመኛለን ሲል ከጨዋታው በኋላ ተናግሯል።

ግብ አስቆጣሪው ሊያንድሮ ትሮሳርድ በበኩሉ " ዛሬ ጥሩ አልተጫወትንም ነገርግን ዋናው ሶስት ነጥቡ ነው ቀጣይ ሳምንት በዋንጫ እንደምንደሰት ተስፋ አለኝ " ብሏል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
#PremiereLeague

በአሰልጣኝ ኤሪክ ቴንሀግ የሚመራው ማንችስተር ዩናይትድ በዘንድሮው የውድድር ዘመን ጥሩ ያልሆነ ጊዜን ማሳለፉ ቀጥሏል።

ማንችስተር ዩናይትድ በአንድ የውድድር አመት በርካታ ግቦች ሲቆጠሩበት ከሀምሳ ሶስት አመታት በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ መሆኑ ተገልጿል።

በተጨማሪም ቀያይ ሴጣኖቹ በአንድ የውድድር አመት በርካታ ጨዋታዎች ሲሸነፉ ከአርባ ስድስት አመታት በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ ነው።

በቀጣይ ማንችስተር ዩናይትድ በፕርሚየር ሊጉ ሁለት ቀሪ ጨዋታዎች የሚቀሩት ይሆናል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
" ካሴሚሮ ብቻ መወቀስ የለበትም " ቴንሀግ

የማንችስተር ዩናይትዱ ዋና አሰልጣኝ ኤሪክ ቴንሀግ ቡድናቸው ዛሬ ሰባት ወሳኝ ተጨዋቾቹን ቢያጣም ተፎካካሪ እንደነበር በሰጡት አስተያየት ገልጸዋል።

ካሴሚሮን ያስፈረምነው ሽንፈት ስለማይወድ ነው ያሉት አሰልጣኝ ኤሪክ ቴንሀግ እሱን ብቻ መውቀስ የለብንም የተጫወትነው እንደ ቡድን ነው በማለት ተናግረዋል።

" አርሰናል ከፕርሚየር ሊግ ምርጥ ቡድኖች አንዱ ነው ፣ ዛሬ ጨዋታው ተቀራራቢ ነበር ሰባት ወሳኝ ተጨዋቾች አጥተናል ነገርግን ተፎካካሪ ነበርን።" ቴንሀግ

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
" በእግርኳስ ሁሉም ይፈጠራል " አርቴታ

የመድፈኞቹ ዋና አሰልጣኝ ሚኬል አርቴታ ቡድናቸው ማክሰኞ የቶተንሀምን ማሸነፍ እንደሚጠብቅ ገልፀው በእግርኳስ ሁሉም ነገር እንደሚፈጠር ተናግረዋል።

" የህልማችን በር እስከ እሁድ ክፍት ሆኗል " ያሉት ሚኬል አርቴታ የመጨረሻ ሳምንት በደጋፊያችን ፊት ነው ቀኑን በጋራ የምንኖረው ውብ ቀን አድርገን እንቁጠረው ብለዋል።

" ማክሰኞ የቶተንሀም ማሸነፍ ያስፈልገናል እኛም ስራችንን እንሰራለን ይሆ እግርኳስ ነው ሁልጊዜ ሁሉም ነገር ይቻላል።"ብለዋል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
ማንችስተር ዩናይትድ የሴቶች ኤፌካፕ አሸንፈዋል !

የማንችስተር ዩናይትድ የሴቶች ቡድን በታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ የ ኤፌ ካፕ ዋንጫን ቶተንሀምን በመርታት ማሸነፍ ችለዋል።

በርካታ ታዳሚያን በዌ
ብሌይ በተከታተለው ጨዋታ ማንችስተር ዩናይት 4ለ0 በሆነ ውጤት አሸንፈዋል።

ለፍፃሜ መድረስ የቻሉት ቶተንሀም እና ዩናይትድ የ ኤፌ ካፕ ዋንጫን ከዚህ ቀደም አሸንፈው አያውቁም ነበር።

ይህን ጨዋታ በዌ
ብለይ ስታዲየም በርካታ ደጋፊዎች ሲታደሙት የጨዋታ መግቢያ ትኬቶች ሙሉ ተሽጠው ማለቃቸው ተዘግቧል።

@tikvahethsport @kidusyoftahe
ባየር ሊቨርኩሰን ባለመሸነፍ ጉዞው ቀጥሏል !

የጀርመን ቡንደስሊጋ ዋንጫ አሸናፊው ባየር ሊቨርኩሰን ከቦህም ጋር ያደረገውን የሰላሳ ሶስተኛ ሳምንት መርሐ ግብር 5ለ0 በሆነ ውጤት ማሸነፍ ችለዋል።

የባየር ሊቨርኩሰንን የማሸነፊያ ግቦች ፓትሪክ ሺክ ፣ ቦንፌስ ፣ አሚን አድሊ ፣ ግሪማልዶ እና ስታንሲች ከመረብ አሳርፈዋል።

በአሰልጣኝ ዣቢ አሎንሶ የሚመራው ባየር ሊቨርኩሰን በዘንድሮው የውድድር ዘመን ካደረጋቸው ሰላሳ ሶስት የቡንደስሊጋ ጨዋታዎች ሀያ ሰባቱን ሲያሸንፍ በስድስቱ አቻ ተለያይተዋል።

ባየር ሊቨርኩሰን በዘንድሮው የውድድር አመት ያደረጋቸውን ያለፉት #ሀምሳ ጨዋታዎች ሳይሸነፍ መጓዙን ቀጥሏል።

ባየር ሊቨርኩሰን በቀጣይ የመጨረሻ የሊግ ጨዋታውን ከኦግስበርግ ጋር የሚጫወቱ ይሆናል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
ፒኤስጂ ሽንፈት አስተናግዷል !

በፈረንሳይ ሊግ የሰላሳ ሶስተኛ ሳምንት መርሐ ግብር የሊጉ መሪ ፒኤስጂ ከቱሉስ ጋር ያደረገውን ጨዋታ 3 ለ 1 በሆነ ውጤት ተሸንፏል።

የፒኤስጂን ግብ ኪሊያን ምባፔ ከመረብ ሲያሳርፍ ለቱሉስ የማሸነፊያ ግቦችን ዳሊንጋ ፣  ግቦሆ እና ማግሪ ማስቆጠር ችለዋል።

ፈረንሳዊው የፊት መስመር ተጨዋች ኪሊያን ምባፔ በውድድር ዘመኑ ሀያ ሰባተኛ የሊግ ግቡን ማስቆጠር ችሏል።

በአመቱ መጨረሻ ፒኤስጂን የሚለቀው ኪሊያን ምባፔ በፓርክ ዲ ፕሪንስ ስታዲየም የፒኤስጂ የመጨረሻ ጨዋታውን አድርጓል።

የሊጉ ደረጃ ሰንጠረዥ ምን ይመስላል ?

1️⃣ ፒኤስጂ :- 70 ነጥብ

1️⃣0️⃣ ቱሉስ :- 43 ነጥብ

ቀጣይ ጨዋታ ምን ይመስላል ?

እሮብ - ኒስ ከ ፒኤስጂ

እሁድ - ቱሉስ ከ ብረስት

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
2024/05/13 05:32:54
Back to Top
HTML Embed Code: