Telegram Web Link
8+11=19 ይሆናል። ከምርኮ መጀመር ከ 605 ላይ19 ዓመት ሲቀነስ 586 ይሆናል፥ 605−19=586 ይሆናል። በዚህ ጊዜ ኢየሩሳሌምን ስለ መጠገን እና ስለ መሥራት ቃሉ ወደ ኤርሚያስ መጣ፦
ኤርምያስ 1፥3 በይሁዳም ንጉሥ በኢዮስያስ ልጅ በኢዮአቄም ዘመን፥ እስከ ይሁዳ ንጉሥ እስከ ኢዮስያስ ልጅ እስከ ሴዴቅያስ እስከ *"አሥራ አንደኛው ዓመት ፍጻሜ፥ ኢየሩሳሌም እስከ ተማረከችበት እስከ አምስተኛው ወር ድረስ *"የእግዚአብሔር ቃል መጣ"*።

ኢየሩሳሌምን መጠገንና መሥራት ቃሉ የመጣው ከተማይቱ በፈረሰችበት በ 586 ቅድመ-ልደት"BC" ነው። ኢየሩሳሌምን መጠገንና መሥራት ቃሉ ከመጣበት እስከ አለቃው መሢሕ ድረስ ሰባት ሱባዔ ይሆናል፥ ቅድሚያ ለምን 7 ሱባዔ እንደቀደመ እና እንደተቀመጠ የክርስትና ምሁራን አጥጋቢ መልስ የላቸውም። አንድ ሱባዔ 7 ዓመት ከሆነ 7 ሱባዔ 49 ዓመት ይሆናል። 7×7=49 ይሆናል። ከ 586 ቅድመ-ልደት"BC" 49 ዓመት ስንቆጥር 537 ይሆናል፥ 586-49= 537 ይመጣል።
በ 537 ቅድመ-ልደት"BC" እግዚአብሔር በኤርምያስም አፍ የተናገረው የእግዚአብሔር ቃል ይፈጸም ዘንድ እግዚአብሔር የፋርስን ንጉሥ ቂሮስን አስነሣ፦
ዕዝራ 1፥1 *"በኤርምያስም አፍ የተናገረው የእግዚአብሔር ቃል ይፈጸም ዘንድ በፋርስ ንጉሥ በቂሮስ በመጀመሪያው ዓመት እግዚአብሔር የፋርስን ንጉሥ የቂሮስን መንፈስ አስነሣ"*።

ይህ የፋርስ ንጉሥ ቂሮስ ከመወለዱ ከ 200 ዓመት በፊት ያህዌህ የሚቀባው መሢሕ እንደሆነ ተተንብዮለታል፦
ኢሳይያስ 45፥1 *"እግዚአብሔር፦ "ለመሢሑ לִמְשִׁיחוֹ֮ ለቂሮስ እንዲህ ይላል፦ "አሕዛብንም በፊቱ አስገዛ ዘንድ የነገሥታትንም ወገብ እፈታ ዘንድ፥ በሮቹም እንዳይዘጉ መዝጊያዎቹን በፊቱ እከፍት ዘንድ፥ ቀኝ እጁን ለያዝሁት"*።
"This is what the LORD says to his anointed, to Cyrus, whose right hand I take hold of to subdue nations before him and to strip kings of their armor, to open doors before him so that gates will not be shut: NIV

"መሺሆው" ִמְשִׁיחוֹ֮ ማለት "የእርሱ መሢሕ" ማለት ነው፥ ይህም የሚያሳየው አለቃው ቂሮስ የያህዌህ መሢሕ መሆኑን ነው። አለቃውም መሢሕም እርሱ ነው።

ነጥብ ሁለት
"ስድሳ ሁለት ሱባዔ"
ዳንኤል 9፥25 *ከዚያም በስድሳ ሁለት ሱባዔ እርስዋም በጭንቀት ዘመን ጎዳና እና ከቅጥር ጋር ትሠራለች"*። וְשָׁבֻעִים שִׁשִּׁים וּשְׁנַיִם, תָּשׁוּב וְנִבְנְתָה רְחוֹב וְחָרוּץ, וּבְצוֹק, הָעִתִּים.

"ከዚያም" የሚለው ቅድመ ተከተል የጊዜ ሳይሆን የንግግር ቅድመ ተከተል ነው። "የጭንቀ ዘመን" የተባለው ምርኮ የሚጀምርበት ቀን ነው፥ ይህ ቀን የመዓት ቀን የመከራና የጭንቀት ቀን ነው፥ በዚህ የጭንቀት ዘመን ከተማይቱ የሚያስጨንቁአት ሁሉ ተጨንቃ አገኙአት፦
ሶፎንያስ 1፥15 ያ ቀን የመዓት ቀን የመከራና የጭንቀት ቀን፥ የመፍረስና የመጥፋት ቀን፥ የጨለማና የጭጋግ ቀን፥ የደመናና የድቅድቅ ጨለማ ቀን።
ሰቆቃው ኤርምያስ 1፥1 አሌፍ። *"ሕዝብ ሞልቶባት የነበረች ከተማ ብቻዋን እንዴት ተቀመጠች"*!
ሰቆቃው ኤርምያስ 1፥3 ጋሜል። *"ይሁዳ ስለ መጨነቅና ስለ ባርነት ብዛት ተማረከች"*፤ በአሕዛብ መካከል ተቀመጠች ዕረፍትም አላገኘችም፤ *"የሚያስጨንቁአት ሁሉ ተጨንቃ አገኙአት"*።

"ይሁዳ ስለ መጨነቅና ስለ ባርነት ብዛት ተማረከች" የሚለው ኃይለ-ቃል ይሰመርበት። በ 605 ቅድመ-ልደት"BC" ከተማይቱ ተማረከች፥ የጭንቀቱ ዘመኗ ጀመረ። ከ 605 ጀምረን 62 ሱባዔ ስንቆጥር 171 ቅድመ-ልደት"BC" ይሆናል። ቅድሚያ 62 ሱባዔ 434 ዓመት ነው፥ 62×7=434 ይሆናል።
እንግዲህ ከምርኮ 605 ጀምሮ 434 ዓመት ስንቆጥር 171 ቅድመ-ልደት"BC" ነው። 605-434=171 ይሆናል። በዚህ ጊዜ የተገደለ መሢሕ አለ፦
ዳንኤል 9፥26 *"ከስድሳ ሁለት ጊዜ በኋላ መሢሕ ይገደላል"*፥ በእርሱም ዘንድ ምንም የለም።

ዳንኤል 9፥26 ላይ "ሰባት" የሚል ቃል የለም። የዕብራይስጡን ማየት ይቻላል። ስድሳ ሁለት ሱባዔ ሲያልቅ የተቀባው ሊቀ-ካህን ሣልሳዊ "አንያስ" ተገሏል፦
ዳንኤል 11፥22 የሚጐርፍም ሠራዊት ከፊቱ ይወሰዳል፥ እርሱ እና *"የቃል ኪዳኑ አለቃ ይሰበራሉ"*።

አንጥያኮስ ኤጴፋኔዎስ በ 171 ቅድመ-ልደት የተቀባው ሊቀ-ካህን ሣልሳዊ "አንያስን" አስገድሎታል። "ማሺአሕ" מָשִׁ֣יחַ ማለት "የተቀባ" ማለት ሲሆን ይህ ቃል 39 ጊዜ ብሉይ ኪዳን ላይ ለተለያየ ካህን፣ ንጉሥ እና ነቢይ አገልግሎት ላይ ውሏል፦
ዘሌዋውያን 4፥3 *የተቀባውም* הַמָּשִׁ֛יחַ ካህን በሕዝቡ ላይ በደል እንዲቈጠርባቸው ኃጢአት ቢሠራ፥ ስለ ሠራው ስለ ኃጢአቱ ነውር የሌለበት ወይፈን ለእግዚአብሔር ለኃጢአት መሥዋዕት ያቀርበዋል።

"ማሺአሕ" מָשִׁ֣יחַ የሚል ቃል በተገኘ ቁጥር ለወደፊት ከዳዊት ቤት ለሚመጣው ንጉሥና ነቢይ ነው ብሎ ማለት ቂልነት ነው። ኢንሻላህ ይቀጥላል......

በኡሥታዝ ወሒድ ዐቃቢ ኢሥላም

Follow us on:
https://fb.me/tiriyachen
https://www.tg-me.com/tiriyachen
https://tiriyachen.org
https://bit.ly/3eVixKv
https://www.tiktok.com/@tiriyachen

ወሠላሙ ዐለይኩም

ወሠላሙ ዐለይኩም
👍21
ሰባው ሱባዔ

ገቢር አንድ

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው።

ከእነሱም እርሱ ከመጽሐፉ ያይደለ ሲኾን ከመጽሐፉ መኾኑን እንድታስቡ በመጽሐፉ ምላሶቻቸውን የሚያጣምሙ ክፍሎች አሉ፡፡ እርሱ ከአላህ ዘንድ ያልኾነ ሲኾን «እርሱ ከአላህ ዘንድ ነውም» ይላሉ፡፡ እነርሱ የሚያውቁ ሲኾኑም በአላህ ላይ ውሸትን ይናገራሉ፡፡

وَإِنَّ مِنْهُمْ لَفَرِيقًا يَلْوُونَ أَلْسِنَتَهُم بِالْكِتَابِ لِتَحْسَبُوهُ مِنَ الْكِتَابِ وَمَا هُوَ مِنَ الْكِتَابِ وَيَقُولُونَ هُوَ مِنْ عِندِ اللَّهِ وَمَا هُوَ مِنْ عِندِ اللَّهِ وَيَقُولُونَ عَلَى اللَّهِ الْكَذِبَ وَهُمْ يَعْلَمُونَ

📜 ቁርኣን 3፥78
ነቢዩ ዳንኤል የኢየሩሳሌም መፍረስ የሚፈጸምበትን ሰባውን ዓመት፥ ያህዌህ በቃሉ ለነቢዩ ለኤርምያስ የተናገረውን የዓመቱን ቍጥር በመጽሐፍ አስተዋለ፦ ......

ሙሉውን ለማንበብ
https://tiriyachen.org/ሰባው-ሱባዔ/
1
ሰባው ሱባዔ

ገቢር ሁለት

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው።

ከእነሱም እርሱ ከመጽሐፉ ያይደለ ሲኾን ከመጽሐፉ መኾኑን እንድታስቡ በመጽሐፉ ምላሶቻቸውን የሚያጣምሙ ክፍሎች አሉ፡፡ እርሱ ከአላህ ዘንድ ያልኾነ ሲኾን «እርሱ ከአላህ ዘንድ ነውም» ይላሉ፡፡ እነርሱ የሚያውቁ ሲኾኑም በአላህ ላይ ውሸትን ይናገራሉ፡፡

وَإِنَّ مِنْهُمْ لَفَرِيقًا يَلْوُونَ أَلْسِنَتَهُم بِالْكِتَابِ لِتَحْسَبُوهُ مِنَ الْكِتَابِ وَمَا هُوَ مِنَ الْكِتَابِ وَيَقُولُونَ هُوَ مِنْ عِندِ اللَّهِ وَمَا هُوَ مِنْ عِندِ اللَّهِ وَيَقُولُونَ عَلَى اللَّهِ الْكَذِبَ وَهُمْ يَعْلَمُونَ
📜 ቁርኣን 3፥78

ነጥብ ሦስት
“አንድ ሱባዔ”

“እርሱም ከብዙ ሰዎች ጋር ጽኑ ቃል ኪዳን ለአንድ ሱባዔ ያደርጋል፤ በሱባዔውም እኵሌታ መሥዋዕቱንና ቍርባኑን ያስቀራል”።
📜 ዳንኤል 9፥27

“እርሱም” የሚለው ተውላጠ-ስም “የሚመጣው አለቃ” የሚለውን ተክቶ የመጣ ተውላጠ-ስም ነው፦ ........

ሙሉውን ያንብቡ 👇🏻👇🏻👇🏻
https://tiriyachen.org/ሰባው-ሱባዔ-2/
👍6
ቀሪን
በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡

"ተሳላቂዎችን ሁሉ እኛ በቅተንሃል"፡፡

إِنَّا كَفَيْنَٰكَ ٱلْمُسْتَهْزِءِينَ
📜ቁርኣን 15፥95

የአእምሮ ስንኩላን ከትልቅ እስለ ደቂቅ ያለ አንዳች ከልካይ የባልቴት የቡና ወሬ ሲነዙ ማየት ዐላዋቂነትን ከማሳበቅ ውጪ አንዳች የሚፈይዱት ነገር የለም። በኢሥላም ያሉ የመስኩ ሊሒቃን፦ “ውኃን ከጡሩ፥ ነገርን ከሥሩ” ይላሉና እኛም ከሥሩ ስለ ቀሪን የተነሳውን የወይዛዝርት የቡና ወሬ በትክክለኛ የአስተላለፍና የአስነዛዘር ሙግት እንሞግታለን። "ቀሪን" قَرِين የሚለው ቃል 8 ጊዜ በቁርኣን የተጠቀሰ ሲሆን "ጓደኛ" ማለት ነው፦

ከእነርሱ የሆነ ተናጋሪ ይላል፦ "እኔ ጓደኛ ነበረኝ"፡፡

قَالَ قَائِلٌ مِّنْهُمْ إِنِّي كَانَ لِي قَرِينٌ
📜ቁርኣን 37፥51

እዚህ አንቀጽ ላይ "ቀሪን" قَرِين የተባለበው ሰው ለሰው "ጓደኛ" በሚሆንበት ስሌት ነው። ስለዚህ "ቀሪን" ማለት "ሸይጧን" ማለት ሳይሆን "ጓደኛ" ማለት ብቻ ነው። ለምሳሌ ሥራችንን የሚመዘግቡ መልአክ "ቀሪን" قَرِين ተብለዋል፦ ........

ሙሉውን ለማንበብ 👇🏻
https://tiriyachen.org/ቀሪን/
👍2
ጀነት የሚገቡት እነማን ናቸው?

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡

“እነዚያ ያመኑ፣ እነዚያም ይሁዳውያን የኾኑ፣ ክርስቲያኖችም፣ ሳቢያኖችም ”በአላህ እና በመጨረሻው ቀን ያመነ መልካምንም ሥራ የሠራ ለእነርሱ በጌታቸው ዘንድ ምንዳቸው አላቸው”፡፡ በእነርሱም ላይ ፍርሃት የለባቸውም፤ እነርሱም አያዝኑም፡፡

إِنَّ الَّذِينَ آمَنُوا وَالَّذِينَ هَادُوا وَالنَّصَارَىٰ وَالصَّابِئِينَ مَنْ آمَنَ بِاللَّهِ وَالْيَوْمِ الْآخِرِ وَعَمِلَ صَالِحًا فَلَهُمْ أَجْرُهُمْ عِندَ رَبِّهِمْ وَلَا خَوْفٌ عَلَيْهِمْ وَلَا هُمْ يَحْزَنُونَ
📜ቁርኣን 2፥62

በጌታቸው ዘንድ ምንዳ ያላቸው ይሁዳውያን፣ ክርስቲያን እና ሳቢያን “መን” مَنْ በሚል አንጻራዊ ተውላጠ-ስም ተለይተዋል። እነዚህም በአላህ እና በመጨረሻው ቀን ያመኑና መልካምንም ሥራ የሠሩ ናቸው። “በአላህ እና በመጨረሻው ቀን ያመነ መልካምንም ሥራ የሠራ ለእነርሱ በጌታቸው ዘንድ ምንዳቸው አላቸው” የሚለው ሃይለ-ቃል ይሰመርበት። “በአላህ እና በመጨረሻው ቀን” ማመን የኢማን ማዕዘናትን ያቅፋል፥ በአላህ እና በመጨረሻው ቀን ማመን መካከል በመላእክቱም፣.....

ሙሉውን ለማንበብ 👇🏻👇🏻
https://tiriyachen.org/ጀነት-የሚገቡት-እነማን-ናቸው/
2
የአላህ ዙፋን

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፤

ሰማያትንና ምድርን በስድስት ቀኖች የፈጠረው ነው፤ ዐርሹም በውሃ ላይ ነበር።

وَهُوَ ٱلَّذِى خَلَقَ ٱلسَّمَٰوَٰتِ وَٱلْأَرْضَ فِى سِتَّةِ أَيَّامٍۢ وَكَانَ عَرْشُهُۥ عَلَى ٱلْمَآءِ لِيَبْلُوَكُمْ أَيُّكُمْ أَحْسَنُ عَمَلًۭا ۗ وَلَئِن قُلْتَ إِنَّكُم مَّبْعُوثُونَ مِنۢ بَعْدِ ٱلْمَوْتِ لَيَقُولَنَّ ٱلَّذِينَ كَفَرُوٓا۟ إِنْ هَٰذَآ إِلَّا سِحْرٌۭ مُّبِينٌۭ
📜 ቁርኣን 11፥7

መቼም ሚሽነሪዎች የኢስላም ተስተምህሮት ዶግ አመድ ቢሆንላቸው ደስታቸው እጥፍ ድርብ ነው፤ ሂስ የሙግት አንዱ ክፍል ቢሆንም የሚሽነሪዎች ሂስ ግን ማሸሞር፣ ማነወር እና ስላቅ ነው፤ ይህ ደግሞ ጡዘቱ ጣራ የነካና ዙሪያ ገባ ነው፤ ከእነርሱ ቅንነት የተሞላው መልስ መጠበቅ ማለት ከጅብ አፍ ላይ ስጋ እንደመጠበቅ ነው። እነርሱ የሚሰጡት ትችት እኛ ሙስሊሞችን የሚያፍረከርክ ሳይሆን ከእለት ወደ እለት የሚያጀግን ነው፤ ለማንኛውም የተነሳውን ትችት አብጠርጥረን እና አንጠርጥረን እንመልከት፦ “የአላህ ዙፋን በውሃ ላይ ነው፤ የሰይጣንም ዙፋን በውሃ ላይ ነው፤ ስለዚህ የሁለቱም ዙፋን አንድ ነው” በማለት ሊያምታቱ ይሞክራሉ።..............


ሙሉውን ለማንበብ 👇🏻
https://tiriyachen.org/የአላህ-ዙፋን/
ውሸት ይፈቀዳልን?

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ፥ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው።

ከጣዖታትም ርክሰት ተጠንቀቁ፡፡ ሐሰትንም ቃል ራቁ፡፡

فَٱجْتَنِبُوا۟ ٱلرِّجْسَ مِنَ ٱلْأَوْثَٰنِ وَٱجْتَنِبُوا۟ قَوْلَ ٱلزُّورِ
📜 ቁርኣን 22፥30


ከሥነ-ምግባር እሴት አንዱ ትክክለኛ ንግግር መናገር ነው፥ አንድ አማኝ ትክክለኛውንም ንግግር መናገር እና የሐሰትንም ቃል መራቅ አለበት፦

እላንተ ያመናችሁ ሆይ አላህን ፍሩ፤ ትክክለኛውንም ንግግር” ተናገሩ።

يَٰٓأَيُّهَا ٱلَّذِينَ ءَامَنُوا۟ ٱتَّقُوا۟ ٱللَّهَ وَقُولُوا۟ قَوْلًۭا سَدِيدًۭا
📜 ቁርኣን 33:70

ከጣዖታትም ርክሰት ተጠንቀቁ፡፡ ሐሰትንም ቃል ራቁ፡፡.......

ሙሉውን ያንብቡ👇🏻👇🏻👇🏻
https://tiriyachen.org/ውሸት-ይፈቀዳልን/
👍2
ሦስት ፀሐይ | ዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ | ጥሪያችን

🔗 https://youtu.be/u78iFMChPtE

👆  አዲስ ቪድዮ በዩትዩብ ቻነላችን ላይ


መልካም ቆይታ ከጥሪያችን ጋር
‐‐‐
Follow us on:
https://fb.me/tiriyachen
https://www.tg-me.com/tiriyachen
https://tiriyachen.org
https://bit.ly/3eVixKv
https://www.tiktok.com/@tiriyachen
👏3👍1
በህይወት ያለው ከሞተው አይበልጥም!!


በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ በጣም አዛኝ በሆነው
ምስጋና የዓለማት ጌታ ለሆነው ለአላህ የተገባ ነው፡፡ የአላህ ውዳሴና ሰላም፡ የሰላም አለቃና መምህር ለሆኑት ለነቢዩ ሙሐመድ ይሁን፡፡ ድልና የበላይነት ሐቅን ለማንገስና ሀሰትን ለማርከስ፡ በደልን አጥፎቶ ፍትህን ለማስፈን ዕውቀታቸውን፣ ንብረታቸውን፣ ጉልበታቸውን፣ ጊዜያቸውንና ህይወታቸውን መስዋእት በማድረግ ለሚታገሉት ይሁን፡፡
የማያጠግብ እንጀራ ባይበላ ይቅር! እንዲሉ ሆነና፡ እንኳን በአላህ አንድነት ላይ እምነቱን ላጸናው ሙስሊም ይቅርና ከሃይማኖት እሳቤ ገለልተኛ ሆኖ በንጹህ ህሊናው የሚያስብን ሰው ማሳመን የማችል የወረደ አስተሳሰብ ነው፡፡
እሱም፡- የመርየም ልጅ ዒሳ (ዐለይሂ-ሰላም) ሙስሊሞች እንደምትሉት ካልሞተና አላህ ወደራሱ ከወሰደው፡ በዛው ተቃራኒ ነቢዩ ሙሐመድ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) ከሞቱና ከተቀበሩ፡ በርግጥም ዒሳ በደረጃ ይበልጣቸዋል ማለት ነው!!፡፡ እንደገናም እሱ የአላህ ልጅ መሆን አለበት ማለት ነው! የሚል ነው፡፡ ለዚህ የተሳሳተ አስተሳሰብ እርምትን ለሚሻ ሰው በአላህ ፈቃድ መጠነኛ ምላሽን እንካችሁ ብያለሁ፡፡ ወማ ተውፊቂ ኢልላ ቢላህ (የመልካም ነገር ሁሉ ገጠመኝ ከአላህ እንጂ ከማንም አይደለም)፡፡

ሙሉውን ያንብቡ👇🏻👇🏻👇🏻
https://tiriyachen.org/በህይወት-ያለው-ከሞተው-አይበልጥም/
👍2
የኢሥላም መልእክት ላልደረሳቸው በሙሉ!!

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ በጣም አዛኝ በሆነው

ክብርና ምስጋና ለዓለማቱ ጌታ ለአላህ የተገባ ይሁን፡፡
📜 (አል-ፋቲሓ 2)

የአላህ ሰላምና ውዳሴ የሰው ዘር ታላቅ መሪ ለሆኑት ለነቢዩ ሙሐመድ
📜 (አል-አሕዛብ 56)

ለመላው የአላህ መልክተኞች
📜 (አል-ሷፍፋት 181)

የሐቅንም መንገድ በተከተለ ሁሉ ላይ ይሁን
📜 (ጣሀ 47)

ሙሉውን ያንብቡ👇🏻👇🏻👇🏻
https://tiriyachen.org/የኢሥላም-መልእክት-ላልደረሳቸው-በሙሉ/
ፊቅህ

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው።

5፥48 ወደ አንተም መጽሐፉን ከበፊቱ ያለውን መጽሐፍ አረጋጋጭና በእርሱ ላይ ተጠባባቂ ሲኾን በእውነት አወረድን፡፡ በመካከላቸውም *”አላህ ባወረደው ሕግ ፍረድ”*፡፡ እውነቱም ከመጣልህ በኋላ ዝንባሌዎቻቸውን አትከተል፡፡ *”ከእናንተ ለሁሉም ሕግን እና መንገድን አደረግን”*፡፡ وَأَنزَلْنَآ إِلَيْكَ ٱلْكِتَٰبَ بِٱلْحَقِّ مُصَدِّقًۭا لِّمَا بَيْنَ يَدَيْهِ مِنَ ٱلْكِتَٰبِ وَمُهَيْمِنًا عَلَيْهِ ۖ فَٱحْكُم بَيْنَهُم بِمَآ أَنزَلَ ٱللَّهُ ۖ وَلَا تَتَّبِعْ أَهْوَآءَهُمْ عَمَّا جَآءَكَ مِنَ ٱلْحَقِّ ۚ لِكُلٍّۢ جَعَلْنَا مِنكُمْ شِرْعَةًۭ وَمِنْهَاجًۭا

"ፊቅህ" فِقْه‎ የሚለው ቃል "ፈቂሀ" فَقِهَ‎ ማለትም "ተረዳ" ከሚል ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን "ጥልቅ መረዳት" ማለት ነው፦
6፥98 እርሱም ያ ከአንዲት ነፍስ ያስገኛችሁ ነው፡፡ በማሕፀን መርጊያና በጀርባ መቀመጫም አላችሁ፡፡ *"ለሚያወቁ" ሕዝቦች አንቀጾችን በእርግጥ ዘረዘርን"*፡፡ وَهُوَ الَّذِي أَنشَأَكُم مِّن نَّفْسٍ وَاحِدَةٍ فَمُسْتَقَرٌّ وَمُسْتَوْدَعٌ ۗ قَدْ فَصَّلْنَا الْآيَاتِ لِقَوْمٍ يَفْقَهُونَ

“ሚያወቁ” ተብሎ የተቀመጠው ቃል “የፍቀሁነ” يَفْقَهُونَ ሲሆን “ሚረዱ” ማለት ነው፥ ይህ ቋንቋዊ ፍቺው ነው። "ፊቅህ" فِقْه‎ የሚለው እሳቤ ሃይማኖታዊ ፍቺው ደግሞ የሥነ-ሕግ ጥናት”the study of law” ማለት ነው። ይህንን ሕግ የሚያጠና ምሁር በነጠላ "ፈቂህ" فَقِيه‎ ሲባል በብዜት "ፉቀሃእ" فُقَهَاء‎ ይባላል። አንድ ዐሊም የሚያጠናው ሕግ "ሸሪዓህ" ይባላል፥ "ሸሪዓህ" شَرِيعَة ማለት "ትክክለኛ ሕግ" ማለት ነው፦
45፥18 ከዚያም ከትእዛዝ *በትክክለኛይቱ ሕግ* ላይ አደረግንህ፡፡ ስለዚህ ተከተላት፡፡ የእነዚያንም የማያውቁትን ሕዝቦች ዝንባሌዎች አትከተል፡፡ ثُمَّ جَعَلْنَاكَ عَلَىٰ شَرِيعَةٍ مِّنَ الْأَمْرِ فَاتَّبِعْهَا وَلَا تَتَّبِعْ أَهْوَاءَ الَّذِينَ لَا يَعْلَمُون

"ትክክለኛይቱ ሕግ" ለሚለው ቃል የገባው "ሸሪዓህ" شَرِيعَة የሚል ነው፥ ይህም ቃል “ሺርዓህ” شِرْعَة ማለትም "ሕግ" ከሚል ቃል የመጣ ነው፦
5፥48 ወደ አንተም መጽሐፉን ከበፊቱ ያለውን መጽሐፍ አረጋጋጭና በእርሱ ላይ ተጠባባቂ ሲኾን በእውነት አወረድን፡፡ በመካከላቸውም *”አላህ ባወረደው ሕግ ፍረድ”*፡፡ እውነቱም ከመጣልህ በኋላ ዝንባሌዎቻቸውን አትከተል፡፡ *”ከእናንተ ለሁሉም ሕግን እና መንገድን አደረግን”*፡፡ وَأَنزَلْنَآ إِلَيْكَ ٱلْكِتَٰبَ بِٱلْحَقِّ مُصَدِّقًۭا لِّمَا بَيْنَ يَدَيْهِ مِنَ ٱلْكِتَٰبِ وَمُهَيْمِنًا عَلَيْهِ ۖ فَٱحْكُم بَيْنَهُم بِمَآ أَنزَلَ ٱللَّهُ ۖ وَلَا تَتَّبِعْ أَهْوَآءَهُمْ عَمَّا جَآءَكَ مِنَ ٱلْحَقِّ ۚ لِكُلٍّۢ جَعَلْنَا مِنكُمْ شِرْعَةًۭ وَمِنْهَاجًۭا

እዚህ አንቀጽ ላይ “ሕግ” ለሚለው ቃል የገባው “ሺርዓህ” شِرْعَة መሆኑ አንባቢ ልብ ይለዋል፥ “መንገድ” ተብሎ የተቀመጠው ቃል “ሚንሃጅ” مِنْهَاج ሲሆን “መንሃጅ” مَنْهَج ማለት ነው። አምላካችን አላህ"ﷻ" ለሁሉም መልእክተኞች በዘመናቸው ሸሪዓህ እና መንሃጅ ማድረጉን ያሳያል። “ፍረድ” ለሚለው ቃል የተጠቀመበት “ፈሕኩም” فَاحْكُمْ ሲሆን “ሑክም” ለሚለው የግስ መደብ ነው፥ “ሑክም” حُكْم የሚለው ቃል”ሐከመ” حَكَمَ ማለትም “ፈረደ” ከሚል ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን ፍርድ” ወይም “ሕግ” ማለት ነው። “አሕካም” أَحْكَام‎ ማለት ደግሞ የሑክም ብዙ ቁጥር ሲሆን "ሕግጋት" ማለት ነው። በኢሥላም አሕካም በአምስት ዋና ዋና ክፍል ይከፈላል፥ እነርሱም፦
1ኛ. “ፈርድ” فَرْد‎ ማለትም “የታዘዘ” ግዴታ ነው።
2ኛ. “ሙስተሐብ” مُسْتَحَبّ‎ ማለትም “የተወደደ” ሡናህ ነው።
3ኛ. “ሙባሕ” مُبَاح‌‌‎ ማለትም “የተፈቀደ” ሐላል ነው።
4ኛ. “መክሩህ” مَكْرُوه‎ ማለትም “የተጠላ” ድርጊት ነው።
5ኛ. “ሐራም” حَرَام ማለትም “የተከለከለ” ድርጊት ነው።

እነዚህ ሕግጋት ቁርኣን እና ሐዲስ ላይ በተቀመጠው መሠረት ብቻ ዒባዳህ ይፈጸማል። “ዒባዳህ” عِبَادَة ማለት “አምልኮ” ማለት ሲሆን ዒባዳህ አላህ ዘንድ ተቀባይነት የሚያገኝባቸው ሥስት ሸርጦች ኢማን፣ ኢኽላስ እና ኢቲባዕ ናቸው። “ኢቲባዕ” اِتِّبَاع የሚለው ቃል “አትበዐ” أَتْبَعَ ማለትም “ተከተለ” ከሚለው ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን “መከተል” ማለት ሲሆን ያለ ኢቲባዕ ማንኛውም ዒባዳህ ተቀባይነት የለውም። ኢቲባዕ ቁርኣን እና ሐዲስ ላይ በተቀመጠው ብቻ ዒባዳህን መፈጸም ነው፦
7፥3 *ከጌታችሁ ወደ እናንተ የተወረደውን "ተከተሉ"*። اتَّبِعُوا مَا أُنزِلَ إِلَيْكُم مِّن رَّبِّكُمْ
6፥106 *ከጌታህ ወደ አንተ የተወረደውን ተከተል* ፡፡ اتَّبِعْ مَا أُوحِيَ إِلَيْكَ مِن رَّبِّكَ

“ተከተሉ” የሚለው ቃል “ኢተቢዑ” اتَّبِعُوا ሲሆን “ኢቲባዕ” اِتِّبَاع ማለት እንግዲህ ከአላህ ወደ ነቢያችን”ﷺ” የተወረደውን ብቻ መከተል ነው፥ ወደ ነቢያችን”ﷺ” የተወረደው ደግሞ ቁርኣን እና ሰሒሕ ሐዲስ ነው። “ቢድዓህ” بِدْعَة ማለት ደግሞ “ኢብተደዐ” ٱبْتَدَعَ ማለትም “ፈጠረ” ከሚል ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን “ፈጠራ” ማለት ነው፥ ቢድዓህ የኢቲባዕ ተቃራኒ ነው። ቢድዓ ማለት ከአምስቱ አሕካም ውጪ አዲስ ፈጠራ ማለት ነው።

እነዚህ አምስቱ ሕግጋት የተዋቀረበት ውቅር ደግሞ አራት ናቸው፥ እነርሱም፦
1ኛ. “ቁርኣን” قُرْءَان የአምላካችን የአላህ"ﷻ" ንግግር ነው።
2ኛ. “ሡናህ” سُنَّة‎ የነቢያችን"ﷺ" ሐዲስ ነው።
3ኛ. “ቂያሥ” قِيَاس ዐሊሞች የሚያመዛዝኑበት “ማመጣጠን”Analogy” ነው።
4ኛ. “ኢጅማዕ” إِجْمَاع‎ የምሁራን ስምምነት “ሲኖዶስ”acadamic agreement” ነው።

አንድ ነገር ቁርኣን እና ሐዲስ ላይ ፈርድ ነው? ሙስተሐብ ነው? ሙባሕ ነው? መክሩህ ነው? ሐራም ነው? የሚለው ይታያል። እዚያ ላይ ከሌለ በቂያሥ ይታያል፥ ለምሳሌ "ቢራ" የሚለው ቃል ቁርኣን ላይ ባይኖርም ሐራም መሆኑ "ኸምር" በሚል ቂያሥ ይደረጋል። ቂያስ ማድረጉ በግል ደረጃ ከከበደ በኢጅማዕ በያን ይደረጋል።
ምን አለፋን “ፊቅህ” ሰፊ አርስት ነው፥ በውስጡ፦ ኢጅቲሀድ፣ ተቅሊድ፣ ተክሊፍ፣ ተክፊር፣ ፈትዋ፣ ዓዳህ፣ ኢሥትድላል፣ ኢሥቲሕሣን የመሳሰሉትን ከባባድ እሳቦት ይዟል። እነዚህን በግርድፉና በሌጣው እንያቸው፦

1. ኢጅቲሀድ
“ኢጅቲሀድ” اِجْتِهَاد‎ ማለት ቁርኣንን እና ሡናን ባማከለ ሁኔታ የሚደረግ “ፍለጋ” “ጥረት” ወይም “ግኝት” ኢጅቲሀድ ይባላል፥ ዐዋቂ ሆኖ የሚጥረው፣ የሚፈልገው፣ የሚያስሰው ሰው ደግሞ “ሙጅተሂድ” مُجْتَهِد ይባላል።
2. ተቅሊድ
‎ “ተቅሊድ” تَقْلِيد ማለት ዐላዋቂ የሆነ ሰው ከዐዋቂዎች የሚወስደው ነገር “ተቅሊድ” ይባላል፤ ይህ ሰው ደግሞ “ሙቀሊድ” مُقَلِّد ይባላል።

3. ተክሊፍ
“ተክሊፍ” تَكْلِيف‎ ማለት ቁርኣንን እና ሐዲስን መመሪያ አድርጎ የሚሠራ፥ በእነርሱ ትእዛዝ አዛዡንም ለይቶ ማወቅ ነው። ለምሳሌ ሶላት ስገድ ከተባለ ሰላት ትእዛዝ ነው ይተገብራል፥ ስለዚህ የታዘዘውን መተግበር እንጂ የራሱን ጥረት አያደርግም ሌላ ተጨማሬ ነገር ለማወቅ።

4. ተክፊር
“ተክፊር” تَكْفِير‎ ማለት ከእሥልምና ማስወጣት ሲሆን የተለያየ ሁጃ ደሊል ሊገኝበት ከቻለ አህሉል ዒልም የሚወስነው እርምጃ ነው። እርምጃውን የሚወስነው አካል “ሙከፊር” مكفر‌‎ ሲባል የካደው ሰው “ካፊር” كَافِر‎ በብዜት “ኩፋር” كُفَّار ይባላል። ድርጊቱ “ኩፍር” كُفْر‎ ይሰኛል።

5. ፈትዋ
“ፈትዋ” فَتْوَى‎ የሚለው ቃል “አፍታ” أَفْتَى ማለትም “አደረሰ” ወይም”ወሰነ” ከሚል ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን “መደበኛ ውሳኔ” ማለት ሲሆን ይህንን ብይን የሚሰጥ አካል “ሙፍቲ” مُفْتٍ‎ ይባላል።

6. ዓዳህ
“ዓዳህ” عَادَة የሚለው ቃል “ዓደ” عَادَ‎ ማለትም “ለመደ” “አወጋ” ከሚል ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን “ልምድ” “ባህል” “ወግ” ማለት ነው። “ዓዳት” عَادَات‎ ደግሞ የዓዳህ ብዙ ቁጥር ነው። በፊቅህ ነጥብ ውስጥ “ዓዳህ” የሚባል እሳቤ አለ። በአንተ እና በአላህ መካከል ያለው አምልኮ ውስጥ አዲስ ነገር ከጨመርን ቢድዓ ይባላል። በእኔ እና በአንተ መካከል ግን ምንም አዲስ ነገር ጥሩ ከሆነ ዓዳህ ነው።

7. ኢሥትድላል
“ደሊል” دَلِيل ማለት “ማስረጃ” ማለት ሲሆን ይህ ሂደት “ኢሥትድላል” اِسْتِدْلَال ይባላል። ቁርኣንን እና ሐዲስ ማስረጃ አርጎ ማስረዳት ኢሥትድላል ነው።

8. ኢሥቲሕሣን
“ኢሥቲሕሣን” ‏اِسْتِحْسَان‎ ማለት ደግሞ መዝሀቦችን መርጦ ሐሰን የሆኑትን ነገሮች በቂያሥ ወስዶ እና በጥሩ መልኩው በራሳቸው ማስቀመጥ ነው። የሚያስቀምጡ እነዚህ የመዝሀብ ሰዎች ናቸው። “መዝሀብ” مَذْهَب‎ ማለት በነጠላ ሲሆን በብዜት “መዛሂብ” مذاهب ሲሆን “የድርጊት መንገድ”school of thought” ማለት ነው። ልክ አንድ ጥጃ ከአራት ጡቶች መርጦ እንደሚጠባ ሁሉ ይህም ሰው አንዱን ወስዶ ይቀስማል፥ እነዚህ መዛሂብ፦
1. የኢማም አቡ ሃኒፋን ግንዛቤ የሚከተል “ሐነፊይ” حنفي‌‎ መዝሃብ ነው።
2. የኢማም ኢብኑ ኢድሪስ ሻፊዕ ግንዛቤ የሚከተል “ሻፊዕይ” شافعي‌‎ መዝሃብ ነው።
3.የኢማም ማሊክ ኢብኑ አነሥ ግንዛቤ የሚከተል “ማሊኪይ” مالكي‌‎ መዝሃብ ነው።
4. የኢማም አሕመድ ኢብኑ ሐንበል ግንዛቤ የሚከተል “ሐንበሊይ” حنبلي መዝሃብ ነው።

ይህንን የፊቂህ እሳቤ ደርዝና ፈርጅ ባለው መልኩ ለማስቀመጥ ሳይሆን በወፍ በረር ለቅምሻ ያክል መሰናዶ ነው። አምላካችን አላህ"ﷻ" እርሱ ባወረደው ሑክም የምንመራና የምፈርድ ያድርገን! አሚን።

ከኡሥታዝ ወሒድ ዐቃቢ ኢሥላም

የበለጠ ለማወቅ
Follow us on:
https://fb.me/tiriyachen
https://www.tg-me.com/tiriyachen
https://tiriyachen.org
https://bit.ly/3eVixKv
https://www.tiktok.com/@tiriyachen

ወሠላሙ ዐለይኩም
👍3
የመርየም ልጅ ዒሳ (ዐለይሂ-ሰላም)
"ከርሱ በሆነ ቃል"

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩህሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡

ክብርና ምስጋና ለዓለማቱ ጌታ ለአላህ የተገባ ይሁን፡፡
📜 (አል-ፋቲሓ 2)

ሰላምና ውዳሴ የሰው ዘር ታላቅ መሪ ለሆኑት ለነቢዩ ሙሐመድ
📜 (አል-አሕዛብ 56)

ለመላው የአላህ መልክተኞች
📜 (አል-ሷፍፋት 181)

የሐቅንም መንገድ በተከተለ ሁሉ ላይ ይሁን
📜 (ጣሀ 47)

1/ ከርሱ በሆነው ቃል፡-

"መላእክት ያሉትን (አስታዉስ) ፡- መርየም ሆይ አላህ ከርሱ በሆነዉ ቃል፣ ስሙ አልመሲሕ ዒሳ የመርየም ልጅ፣ በዚህ ዓለምና በመጨረሻዉም ዓለም የተከበረ፣ ከባለማሎችም በሆነ (ልጅ) ያበስረሻል"
📜 (ሱረቱ አሊ-ዒምራን 45)፡፡

በዚህ አንቀጽ ውስጥ ‹‹ከርሱ በሆነ ቃል›› የሚለውን በመምዘዝ፡ ወገኖቻችን:- ዒሳ (ዐለይሂ-ሰላም) የአላህ ቃል ነውና አምላክ መሆን አለበት ይሉናል፡፡ ለዚህ የተሳሳተ ግንዛቤ የምንሰጠው ምላሽ የሚከተለው ይሆናል፡-
ሀ/ አምላካችን አላህ ማንኛውንምን ነገር መፍጠር ከፈለገ፡ ‹‹ሁን›› በሚለው መለኮታዊ ቃሉ አማካኝነት መፍጠርና ማስገኘት ይችላል፡፡ ይህ ፍጥረትና ግኝት ግን የ ”ይሁን” ቃሉ ውጤት እንጂ: እራሱ ቃል ተብሎ አይጠራም፡፡ ምክንያቱም የተገኘው ‹‹ሁን›› በሚለው መለኮታዊ ቃል አማካኝነት በመሆኑ!!
አላህ በመለኮታዊ ቃሉ አማካኝነት አንድን ነገር ይፈጥራል፣ ያስገኛል፣ ይሰራል እንጂ፡ ይህ መለኮታዊ ቃል እራሱ የተፈለገውን ነገር ሁኖ አይፈጠርም፣ አይሰራም፣ አይገኝምም፡፡ የአላህ ቃል፡ የራሱ የአላህ አንድ መለኮታዊ ባሕሪ እንጂ: ፍጥረትና ግኝት አይደለምና፡፡ ይህንን ሀሳብ የሚገልጹ የተወሰኑ ቅዱስ ቁርኣናዊ አንቀጾችን እንመልከት፡-

ሙሉዉን ለማንበብ 👇🏻👇🏻
https://tiriyachen.org/የመርየም-ልጅ-ዒሳ-ዐለይሂ-ሰላም/
3👍1
የመርየም ልጅ ዒሳ (ዐለይሂ-ሰላም)
ከርሱ የሆነ መንፈስ
------------------------------
በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩህሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡

ክብርና ምስጋና ለዓለማቱ ጌታ ለአላህ የተገባ ይሁን፡፡ (አል-ፋቲሓ 2) ሰላምና ውዳሴ የሰው ዘር ታላቅ መሪ ለሆኑት ለነቢዩ ሙሐመድ (አል-አሕዛብ 56) ለመላው የአላህ መልክተኞች (አል-ሷፍፋት 181) የሐቅንም መንገድ በተከተለ ሁሉ ላይ ይሁን (ጣሀ 47)፡፡

🔹ከርሱ የኾነ መንፈስ፡-

"እናንተ የመጽሐፉ ሰዎች ሆይ! በሃይማኖታችሁ ወሰንን አትለፉ፤ በአላህም ላይ እውነትን እንጂ አትናገሩ፤ የመርየም ልጅ አልመሲሕ ዒሳ፣ የአላህ መልክተኛ፣ ወደ መርየም የጣላት (የሁን) ቃሉም ከርሱ የሆነ መንፈስም ብቻ ነው…"
📜 (ሱረቱ-ኒሳእ 4፡171)

ባለፈው ‹‹ከርሱ በሆነው ቃል›› የሚለውን አንስተን፡ በዚህ ዙሪያ የሚነሱ ብዥታዎችን በአላህ ፈቃድ ለማጥራት የተወሰነ ሙከራ ተደርጓል፡፡ ዛሬም የአላህ ፈቃዱ ከሆነ ‹‹ከርሱ የሆነ መንፈስ›› በሚለው ላይ መጠነኛ ቆይታ እናደርጋለን ኢንሻአላህ፡፡


ገብተው ሙሉውን ያንብቡ ይማሩበታል
https://tiriyachen.org/የመርየም-ልጅ-ዒሳ-ዐለይሂ-ሰላም-2/
👍3
የመላእክት ጋብቻ

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡

ኑሕንም ወደ ሕዝቦቹ በእርግጥ ላክነው፡፡ በውስጣቸውም ሺህ ዓመትን አምሳ ዓመት ሲቀር ተቀመጠ፡፡ እነርሱ በዳዮች ኾነውም የውኃው ማጥለቅለቅ ያዛቸው፡፡

وَلَقَدْ أَرْسَلْنَا نُوحًا إِلَىٰ قَوْمِهِ فَلَبِثَ فِيهِمْ أَلْفَ سَنَةٍ إِلَّا خَمْسِينَ عَامًا فَأَخَذَهُمُ الطُّوفَانُ وَهُمْ ظَالِمُونَ
📜 ቁርኣን 29፥14

አምላካችን አላህ”ﷻ” ኑሕ የሚባለውን መልእክተኛ የላከው፥ የኑሕ ሕዝቦች ወድንም፣ ሱዋዕንም፣ የጉሥንም፣ የዑቅንም ነስርንም የተባሉትን አማልክት ያመልኩ ስለነበር እና ያንን ሺርክ ትተው እርሱን ብቻ እንዲያመልኩ ጥሪ እንዲያደርግ ነው፦

ኑሕን ወደ ወገኖቹ በእርግጥ ላክነው፡፡ አላቸውም፡- «ወገኖቼ ሆይ! “አላህን አምልኩ፡፡ ለእናንተ ከእርሱ ሌላ ምንም አምላክ የላችሁም”፡፡ እኔ በእናንተ ላይ የከባድ ቀንን ቅጣት እፈራላችኋለሁ፡፡»

لَقَدْ أَرْسَلْنَا نُوحًا إِلَىٰ قَوْمِهِ فَقَالَ يَا قَوْمِ اعْبُدُوا اللَّهَ مَا لَكُم مِّنْ إِلَـٰهٍ غَيْرُهُ إِنِّي أَخَافُ عَلَيْكُمْ عَذَابَ يَوْمٍ عَظِيمٍ
📜 ቁርኣን 7፥59

አሉም «አምላኮቻችሁን አትተዉ፡፡ ወድንም፣ ሱዋዕንም፣ የጉሥንም፣ የዑቅንም ነስርንም አትተው፡፡

وَقَالُوا لَا تَذَرُنَّ آلِهَتَكُمْ وَلَا تَذَرُنَّ وَدًّا وَلَا سُوَاعًا وَلَا يَغُوثَ وَيَعُوقَ وَنَسْرًا
📜 ቁርኣን 71፥23

ሙሉውን ያንብቡ
https://tiriyachen.org/የመላእክት-ጋብቻ/
👍3
እንስሳት እና ነፍሳት

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ በጣም አዛኛ በሆነው፡፡

2፥26 *”አላህ ማንኛውንም ነገር ትንኝንም ኾነ ከበላይዋ የኾነንም ምሳሌ ለማድረግ አያፍርም”*፡፡ إِنَّ اللَّهَ لَا يَسْتَحْيِي أَن يَضْرِبَ مَثَلًا مَّا بَعُوضَةً فَمَا فَوْقَهَا

አምላካችን አላህ እኛም ለማስተማር የቤት እንስሳትን፣ የዱር እንስሳትን በራሪ ፍጥረትን፣ ነፍሳትን በቅዱስ ቃሉ አውስቷል። ከትንሿ ትንኝ ጀምሮ እስከ ትልቁ ዝሆን ድረስ ምሳሌ እያደረገ አውስቷል፦
2፥26 *አላህ ማንኛውንም ነገር “ትንኝንም” ኾነ ከበላይዋ የኾነንም ምሳሌ ለማድረግ አያፍርም*፡፡ إِنَّ اللَّهَ لَا يَسْتَحْيِي أَن يَضْرِبَ مَثَلًا مَّا بَعُوضَةً فَمَا فَوْقَهَا

ሀ. የቤት እንስሳት

1. ፈረስ
38፥32 አለም «እኔ ፀሐይ በግርዶ እስከ ተደበቀች ድረስ ከጌታዬ ማስታወስ ፋንታ *ፈረስን*! መውደድን መረጥኩ፡፡» فَقَالَ إِنِّي أَحْبَبْتُ حُبَّ الْخَيْرِ عَن ذِكْرِ رَبِّي حَتَّىٰ تَوَارَتْ بِالْحِجَابِ

2. አህያ
62፥5 የእነዚያ ተውራትን የተጫኑትና ከዚያም ያልተሸከሟት ያልሠሩባት ሰዎች ምሳሌ መጽሐፎችን እንደሚሸከም *አህያ* ብጤ ነው፡፡ የእነዚያ በአላህ አንቀጾች ያስተባበሉት ሕዝቦች ምሳሌ ከፋ፡፡ አላህም በዳዮችን ሕዝቦች አይመራም፡፡ مَثَلُ الَّذِينَ حُمِّلُوا التَّوْرَاةَ ثُمَّ لَمْ يَحْمِلُوهَا كَمَثَلِ الْحِمَارِ يَحْمِلُ أَسْفَارًا ۚ بِئْسَ مَثَلُ الْقَوْمِ الَّذِينَ كَذَّبُوا بِآيَاتِ اللَّهِ ۚ وَاللَّهُ لَا يَهْدِي الْقَوْمَ الظَّالِمِينَ

3. በቅሎ
16፥8 ፈረሶችንም፣ *በቅሎዎችንም*፣ አህዮችንም ልትቀመጡዋቸውና ልታጌጡባቸው ፈጠረላችሁ፡፡ የማታውቁትንም ድንቅ ነገር ይፈጥራል፡፡ وَالْخَيْلَ وَالْبِغَالَ وَالْحَمِيرَ لِتَرْكَبُوهَا وَزِينَةً ۚ وَيَخْلُقُ مَا لَا تَعْلَمُونَ

4. ላም
2፥69 «ለኛ ጌታህን ጠይቅልን፤ መልኳ ምን እንደኾነ ለኛ ይግለጽልን» አሉ፡፡ «እርሱ እርሷ መልኳ ደማቅ ተመልካቾችን የምታስደስት ዳለቻ *ላም* ናት ይላችኋል» አላቸው፡፡ قَالُوا ادْعُ لَنَا رَبَّكَ يُبَيِّن لَّنَا مَا لَوْنُهَا ۚ قَالَ إِنَّهُ يَقُولُ إِنَّهَا بَقَرَةٌ صَفْرَاءُ فَاقِعٌ لَّوْنُهَا تَسُرُّ النَّاظِرِينَ

5. ግመል
88፥17 ከሓዲዎች አይመለከቱምን? ወደ *ግመል* እንዴት እነደተፈጠረች! أَفَلَا يَنظُرُونَ إِلَى الْإِبِلِ كَيْفَ خُلِقَتْ

6. ከብት(በሬ)
5፥1 እናንተ ያመናችሁ ሆይ! በቃል ኪዳኖች ሙሉ፡፡ በእናንተ ላይ የሚነበበው ብቻ ሲቀር፡፡ የግመል፣ *የከብት*፣ የበግና የፍየል እንስሳዎች እናንተ በሐጅ ሥራ ላይ ኾናችሁ ማደንን የተፈቀደ ሳታደረጉ ለእናንተ ተፈቀዱ፡፡ አላህ የሚሻውን ይፈርዳል፡፡ يَا أَيُّهَا الَّذِينَ آمَنُوا أَوْفُوا بِالْعُقُودِ ۚ أُحِلَّتْ لَكُم بَهِيمَةُ الْأَنْعَامِ إِلَّا مَا يُتْلَىٰ عَلَيْكُمْ غَيْرَ مُحِلِّي الصَّيْدِ وَأَنتُمْ حُرُمٌ ۗ إِنَّ اللَّهَ يَحْكُمُ مَا يُرِيدُ

7. በግ
5፥1 እናንተ ያመናችሁ ሆይ! በቃል ኪዳኖች ሙሉ፡፡ በእናንተ ላይ የሚነበበው ብቻ ሲቀር፡፡ የግመል፣ የከብት፣ *የበግ* እና የፍየል እንስሳዎች እናንተ በሐጅ ሥራ ላይ ኾናችሁ ማደንን የተፈቀደ ሳታደረጉ ለእናንተ ተፈቀዱ፡፡ አላህ የሚሻውን ይፈርዳል፡፡ يَا أَيُّهَا الَّذِينَ آمَنُوا أَوْفُوا بِالْعُقُودِ ۚ أُحِلَّتْ لَكُم بَهِيمَةُ الْأَنْعَامِ إِلَّا مَا يُتْلَىٰ عَلَيْكُمْ غَيْرَ مُحِلِّي الصَّيْدِ وَأَنتُمْ حُرُمٌ ۗ إِنَّ اللَّهَ يَحْكُمُ مَا يُرِيدُ

8. ፍየል
5፥1 እናንተ ያመናችሁ ሆይ! በቃል ኪዳኖች ሙሉ፡፡ በእናንተ ላይ የሚነበበው ብቻ ሲቀር፡፡ የግመል፣ የከብት፣ የበግና *የፍየል* እንስሳዎች እናንተ በሐጅ ሥራ ላይ ኾናችሁ ማደንን የተፈቀደ ሳታደረጉ ለእናንተ ተፈቀዱ፡፡ አላህ የሚሻውን ይፈርዳል፡፡ يَا أَيُّهَا الَّذِينَ آمَنُوا أَوْفُوا بِالْعُقُودِ ۚ أُحِلَّتْ لَكُم بَهِيمَةُ الْأَنْعَامِ إِلَّا مَا يُتْلَىٰ عَلَيْكُمْ غَيْرَ مُحِلِّي الصَّيْدِ وَأَنتُمْ حُرُمٌ ۗ إِنَّ اللَّهَ يَحْكُمُ مَا يُرِيدُ

9. ውሻ
7፥176 በሻንም ኖሮ በእርሷ ከፍ ባደረግነው ነበር፡፡ እርሱ ግን ወደ ምድር ተዘነበለ፡፡ ፍላጎቱንም ተከተለ፡፡ ብጤውም ብታባርረው ምላሱን አውጥቶ የሚያለከልክ ወይም ብትተወው ምላሱን አውጥቶ የሚያለከልክ እንደ ኾነ *ውሻ* ነው፡፡ ይህ የእነዚያ በአንቀጾቻችን ያስተባበሉት ሕዝቦች ምሳሌ ነው፡፡ ያስተነትኑም ዘንድ ታሪኮችን ተርክላቸው፡፡ وَلَوْ شِئْنَا لَرَفَعْنَاهُ بِهَا وَلَـٰكِنَّهُ أَخْلَدَ إِلَى الْأَرْضِ وَاتَّبَعَ هَوَاهُ ۚ فَمَثَلُهُ كَمَثَلِ الْكَلْبِ إِن تَحْمِلْ عَلَيْهِ يَلْهَثْ أَوْ تَتْرُكْهُ يَلْهَث ۚ ذَّٰلِكَ مَثَلُ الْقَوْمِ الَّذِينَ كَذَّبُوا بِآيَاتِنَا ۚ فَاقْصُصِ الْقَصَصَ لَعَلَّهُمْ يَتَفَكَّرُونَ

ለ. የዱር እንስሳት

1. ዝሆን
105፥1 *በዝሆኑ* ባለቤቶች ጌታህ እንዴት እንደሠራ አላወቅህምን? أَلَمْ تَرَ كَيْفَ فَعَلَ رَبُّكَ بِأَصْحَابِ الْفِيلِ

2. አንበሳ
74፥51 *ከአንበሳ* የሸሹ፡፡ فَرَّتْ مِن قَسْوَرَةٍ

3. ተኩላ
12፥13 «እኔ እርሱን ዩሱፍን ይዛችሁ መሌዳችሁ በእርግጥ ያሳዝነኛል፡፡ እናንተም ከእርሱ ዘንጊዎች ስትሆኑ *ተኩላ* ይበላዋል ብዬ እፈራለሁ» አላቸው፡፡ قَالَ إِنِّي لَيَحْزُنُنِي أَن تَذْهَبُوا بِهِ وَأَخَافُ أَن يَأْكُلَهُ الذِّئْبُ وَأَنتُمْ عَنْهُ غَافِلُون

4. የሜዳ አህያ
74፥50 እነርሱ ልክ ደንባሪዎች *የሜዳ አህዮች* ይመስላሉ፡፡ كَأَنَّهُمْ حُمُرٌ مُّسْتَنفِرَةٌ

5. እባብ
7፥107 በትሩንም ጣለ፡፡ እርስዋም ወዲያውኑ ግልጽ *እባብ* ኾነች፡፡ فَأَلْقَىٰ عَصَاهُ فَإِذَا هِيَ ثُعْبَانٌ مُّبِينٌ

6. ዝንጀሮ
7፥166 ከእርሱም ከተከለከሉት ነገር በኮሩ ጊዜ ለእነሱ «ወረዶች *ዝንጀሮች* ኹኑ አልን፤» ኾኑም፡፡ فَلَمَّا عَتَوْا عَن مَّا نُهُوا عَنْهُ قُلْنَا لَهُمْ كُونُوا قِرَدَةً خَاسِئِينَ
👏1
7. አሳማ
16፥115 በእናንተ ላይ እርም ያደረገው በክትንና ደምን፣ *የአሳማንም* ስጋ፣ ያንንም በመታረድ ጊዜ በእርሱ ከአላህ ስም ሌላ የተነሳበትን ብቻ ነው፡፡ አመጸኛም ወሰን አላፊም ሳይኾን ለመብላት የተገደደ ሰው ይፈቀድለታል፡፡ አላህ መሓሪ አዛኝ ነውና፡፡ إِنَّمَا حَرَّمَ عَلَيْكُمُ الْمَيْتَةَ وَالدَّمَ وَلَحْمَ الْخِنزِيرِ وَمَا أُهِلَّ لِغَيْرِ اللَّهِ بِهِ ۖ فَمَنِ اضْطُرَّ غَيْرَ بَاغٍ وَلَا عَادٍ فَإِنَّ اللَّهَ غَفُورٌ رَّحِيمٌ

8. አሳ
37፥142 እርሱም ተወቃሽ ሲሆን *አሳው* ዋጠው፡፡ فَالْتَقَمَهُ الْحُوتُ وَهُوَ مُلِيمٌ

ሐ. በራሪ ፍጥረት

1. ሁድሁድ
27፥20 በራሪዎቹንም ተመለከተ፤ አለም *«ሁድሁድን* ለምን አላየውም! በእውነቱ ከራቁት ነበርን፡፡ وَتَفَقَّدَ الطَّيْرَ فَقَالَ مَا لِيَ لَا أَرَى الْهُدْهُدَ أَمْ كَانَ مِنَ الْغَائِبِينَ

2. ወፍ
3፥49 ወደ እስራኤልም ልጆች መልክተኛ ያደርገዋል፡፡ ይላልም፡- «እኔ ከጌታዬ ዘንድ በተዓምር ወደ እናንተ መጣሁ፡፡ እኔ ለናንተ ከጭቃ እንደ ወፍ ቅርፅ እፈጥራለሁ፡፡ በርሱም እተነፍስበታለሁ፡፡ በአላህም ፈቃድ *ወፍ* ይኾናል፡፡ በአላህም ፈቃድ ዕውር ኾኖ የተወለደን፣ ለምጸኛንም አድናለሁ፡፡ ሙታንንም አስነሳለሁ፡፡ የምትበሉትንና በቤታችሁ የምታደልቡትንም ሁሉ እነግራችኋለሁ፡፡ የምታምኑ እንደኾናችሁ ለእናንተ በዚህ ውስጥ በእርግጥ ተዓምር አለበት፡፡» وَرَسُولًا إِلَىٰ بَنِي إِسْرَائِيلَ أَنِّي قَدْ جِئْتُكُم بِآيَةٍ مِّن رَّبِّكُمْ ۖ أَنِّي أَخْلُقُ لَكُم مِّنَ الطِّينِ كَهَيْئَةِ الطَّيْرِ فَأَنفُخُ فِيهِ فَيَكُونُ طَيْرًا بِإِذْنِ اللَّهِ ۖ وَأُبْرِئُ الْأَكْمَهَ وَالْأَبْرَصَ وَأُحْيِي الْمَوْتَىٰ بِإِذْنِ اللَّهِ ۖ وَأُنَبِّئُكُم بِمَا تَأْكُلُونَ وَمَا تَدَّخِرُونَ فِي بُيُوتِكُمْ ۚ إِنَّ فِي ذَٰلِكَ لَآيَةً لَّكُمْ إِن كُنتُم مُّؤْمِنِينَ

3. ቁራ
5፥31 የወንድሙንም ሬሳ እንዴት እንደሚሸሽግ ያሳየው ዘንድ አላህ መሬትን የሚጭር *ቁራን* ላከለት፡፡ «ወይ እኔ የወንድሜን ሬሳ እሸሽግ ዘንድ እንደዚህ ቁራ ብጤ መኾን አቃተኝን» አለ፡፡ ከጸጸተኞችም ኾነ፡፡ فَبَعَثَ اللَّهُ غُرَابًا يَبْحَثُ فِي الْأَرْضِ لِيُرِيَهُ كَيْفَ يُوَارِي سَوْءَةَ أَخِيهِ ۚ قَالَ يَا وَيْلَتَىٰ أَعَجَزْتُ أَنْ أَكُونَ مِثْلَ هَـٰذَا الْغُرَابِ فَأُوَارِيَ سَوْءَةَ أَخِي ۖ فَأَصْبَحَ مِنَ النَّادِمِينَ

4. ቢራቢሮ
101፥4 ሰዎች እንደ ተበታተነ *ቢራቢሮ* በሚኾኑበት ቀን። يَوْمَ يَكُونُ النَّاسُ كَالْفَرَاشِ الْمَبْثُوث

5. ንብ
16፥68 ጌታህም ወደ *ንብ* እንዲህ ሲል አስታወቀ «ከተራራዎች፣ ከዛፍም፣ ሰዎች ከሚሠሩትም ቀፎ ቤቶችን ያዢ፡፡ وَأَوْحَىٰ رَبُّكَ إِلَى النَّحْلِ أَنِ اتَّخِذِي مِنَ الْجِبَالِ بُيُوتًا وَمِنَ الشَّجَرِ وَمِمَّا يَعْرِشُونَ

6. ዝንብ
22፥73 እናንተ ሰዎች ሆይ! አስደናቂ ምሳሌ ተገለጸላችሁ፡፡ ለእርሱም አድምጡት፡፡ እነዚያ ከአላህ ሌላ የምትግገዟቸው ጣዖታት *ዝንብን* ፈጽሞ አይፈጥሩም፡፡ እርሱን ለመፍጠር ቢሰበሰቡም እንኳን አይችሉም፡፡ አንዳችንም ነገር ዝንቡ ቢነጥቃቸው ከእርሱ አያስጥሉትም፡፡ ፈላጊውም ተፈላጊውም ደከሙ፡፡ يَا أَيُّهَا النَّاسُ ضُرِبَ مَثَلٌ فَاسْتَمِعُوا لَهُ ۚ إِنَّ الَّذِينَ تَدْعُونَ مِن دُونِ اللَّهِ لَن يَخْلُقُوا ذُبَابًا وَلَوِ اجْتَمَعُوا لَهُ ۖ وَإِن يَسْلُبْهُمُ الذُّبَابُ شَيْئًا لَّا يَسْتَنقِذُوهُ مِنْهُ ۚ ضَعُفَ الطَّالِبُ وَالْمَطْلُوبُ

7. አንበጣ
7፥133 ወዲያም የወሃን ማጥለቅለቅ *አንበጣንም* ነቀዝንም እንቁራሪቶችንም ደምንም የተለያዩ ተዓምራት ሲኾኑ በነሱ ላይ ላክን ኮሩም ተንኮለኞችም ሕዝቦች ነበሩ፡፡ فَأَرْسَلْنَا عَلَيْهِمُ الطُّوفَانَ وَالْجَرَادَ وَالْقُمَّلَ وَالضَّفَادِعَ وَالدَّمَ آيَاتٍ مُّفَصَّلَاتٍ فَاسْتَكْبَرُوا وَكَانُوا قَوْمًا مُّجْرِمِينَ

8. ትንኝ
2፥26 አላህ ማንኛውንም ነገር *ትንኝንም* ኾነ ከበላይዋ የኾነንም ምሳሌ ለማድረግ አያፍርም፡፡ إِنَّ اللَّهَ لَا يَسْتَحْيِي أَن يَضْرِبَ مَثَلًا مَّا بَعُوضَةً فَمَا فَوْقَهَا

መ. ነፍሳት

1. ነቀዝ
7፥133 ወዲያም የወሃን ማጥለቅለቅ አንበጣንም *ነቀዝንም* እንቁራሪቶችንም ደምንም የተለያዩ ተዓምራት ሲኾኑ በነሱ ላይ ላክን ኮሩም ተንኮለኞችም ሕዝቦች ነበሩ፡፡ فَأَرْسَلْنَا عَلَيْهِمُ الطُّوفَانَ وَالْجَرَادَ وَالْقُمَّلَ وَالضَّفَادِعَ وَالدَّمَ آيَاتٍ مُّفَصَّلَاتٍ فَاسْتَكْبَرُوا وَكَانُوا قَوْمًا مُّجْرِمِينَ

2. ሸረሪት
29፥41 የእነዚያ ከአላህ ሌላ ረዳቶችን ጣዖታትን የያዙ ሰዎች ምሳሌ ቤትን እንደ ሠራች *ሸረሪት* ብጤ ነው፡፡ ከቤቶችም ሁሉ በጣም ደካማው የሸረሪት ቤት ነው፡፡ ቢያውቁ ኖሮ አማልክት አድርገው አይግገዟቸውም ነበር፡፡ مَثَلُ الَّذِينَ اتَّخَذُوا مِن دُونِ اللَّهِ أَوْلِيَاءَ كَمَثَلِ الْعَنكَبُوتِ اتَّخَذَتْ بَيْتًا ۖ وَإِنَّ أَوْهَنَ الْبُيُوتِ لَبَيْتُ الْعَنكَبُوتِ ۖ لَوْ كَانُوا يَعْلَمُونَ

3. ጉንዳን
27፥18 በጉንዳንም ሸለቆ በመጡ ጊዜ አንዲት ጉንዳን «እናንተ *ጉንዳኖች* ሆይ! ወደ መኖሪያዎቻችሁ ግቡ፡፡ ሱለይማንና ሰራዊቱ እነርሱ የማያውቁ ሲኾኑ አይሰባብሩዋችሁ» አለች፡፡ حَتَّىٰ إِذَا أَتَوْا عَلَىٰ وَادِ النَّمْلِ قَالَتْ نَمْلَةٌ يَا أَيُّهَا النَّمْلُ ادْخُلُوا مَسَاكِنَكُمْ لَا يَحْطِمَنَّكُمْ سُلَيْمَانُ وَجُنُودُهُ وَهُمْ لَا يَشْعُرُونَ

4. እንቁራሪት
7፥133 ወዲያም የወሃን ማጥለቅለቅ አንበጣንም ነቀዝንም *እንቁራሪቶችንም* ደምንም የተለያዩ ተዓምራት ሲኾኑ በነሱ ላይ ላክን ኮሩም ተንኮለኞችም ሕዝቦች ነበሩ፡፡ فَأَرْسَلْنَا عَلَيْهِمُ الطُّوفَانَ وَالْجَرَادَ وَالْقُمَّلَ وَالضَّفَادِعَ وَالدَّمَ آيَاتٍ مُّفَصَّلَاتٍ فَاسْتَكْبَرُوا وَكَانُوا قَوْمًا مُّجْرِمِينَ

ኡሥታዝ ወሒድ ዐቃቢ ኢሥላም

ወሠላሙ ዐለይኩም
2
2025/07/09 09:33:14
Back to Top
HTML Embed Code: