Telegram Web Link
የቁርኣን አሰባሰብ
ክፍል አንድ

https://tiriyachen.org/የቁርኣን-አሰባሰብ/

--------------------------------------------
የቁርኣን አሰባሰብ
ክፍል ሁለት

https://tiriyachen.org/የቁርኣን-አሰባሰብ-2/
-----------------------------
ጥሪያችን በሁሉም ቦታ!
Follow us on:👇🏻
Telegram ፦ https://www.tg-me.com/tiriyachen
Website ፦ https://tiriyachen.org
Instagram ፦ https://bit.ly/3eVixKv
TikTok ፦ https://www.tiktok.com/@tiriyachen
ነሷራ

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፤

5፥14 ከእነዚያም እኛ *ክርስቲያኖች* ነን ካሉት የጠበቀ ቃል ኪዳናቸውን ያዝን፡፡ *በእርሱም ከታዘዙበት ነገር ፈንታን ተውት*፡፡ ስለዚህ እስከ ትንሣኤ ቀን ድረስ በመካከላቸው ጠብንና ጥላቻን ጣልንባቸው፡፡ አላህም ይሠሩት የነበሩትን ሁሉ በእርግጥ ፡፡ وَمِنَ الَّذِينَ قَالُوا إِنَّا نَصَارَىٰ أَخَذْنَا مِيثَاقَهُمْ فَنَسُوا حَظًّا مِّمَّا ذُكِّرُوا بِهِ فَأَغْرَيْنَا بَيْنَهُمُ ይነግራቸዋልالْعَدَاوَةَ وَالْبَغْضَاءَ إِلَىٰ يَوْمِ الْقِيَامَةِ ۚ وَسَوْفَ يُنَبِّئُهُمُ اللَّهُ بِمَا كَانُوا يَصْنَعُونَ

አምላካችን አላህ ለዒሳ ወንጌልን ሰጠው፤ በዚያ ወንጌል ውስጥ፦ “የኢንጅልም ባለቤቶች በውስጡ አላህ ባወረደው ሕግ ይፍረዱ” የሚል መመሪያ አለ፦
5፥46 በፈለጎቻቸውም ላይ የመርየምን ልጅ ዒሳን ከተውራት በስተፊቱ ያለውን አረጋጋጭ ሲሆን፣ ፤ *ኢንጂልንም በውስጡ ቀጥታና ብርሃን ያለበት በስተፊቱ ያለችውን አስከተልንተውራትንም የሚያረጋግጥ ለጥንቁቆችም መሪና ሲሆን ሰጠነው*። وَقَفَّيْنَا عَلَىٰٓ ءَاثَٰرِهِم بِعِيسَى ٱبْنِ مَرْيَمَ مُصَدِّقًۭا لِّمَا بَيْنَ يَدَيْهِ مِنَ ٱلتَّوْرَىٰةِ ۖ وَءَاتَيْنَٰهُ ገሣጭٱلْإِنجِيلَ فِيهِ هُدًۭى وَنُورٌۭ وَمُصَدِّقًۭا لِّمَا بَيْنَ يَدَيْهِ مِنَ ٱلتَّوْرَىٰةِ وَهُدًۭى وَمَوْعِظَةًۭ لِّلْمُتَّقِينَ
5፥47 የኢንጅልም ባለቤቶች በውስጡ *አላህ ባወረደው ሕግ ይፍረዱ*፤ وَلْيَحْكُمْ أَهْلُ ٱلْإِنجِيلِ بِمَآ أَنزَلَ ٱللَّهُ فِيهِ

“ቀፈይና” قَفَّيْنَا ማለትም “አስከተልን” እና “አተይናሁ” آتَيْنَاهُ ማለትም “ሰጠነው” የሚሉት ያለቁ አላፊ ግስ ናቸው፤ “ልየሕኩም” َلْيَحْكُمْ ማለትም “ይፍረዱ” የሚለው ትዕዛዛዊ ግስ መነሻ ላይ “ወ” و ማለትም “እና” የሚል አያያዥ መስተጻምር አለ፤ ያ ማለት “ይፍረዱ” የሚለው ትዕዛዛዊ ግስ “አስከተልን” እና “ሰጠነው” ከሚሉት ግስ ጋር ተያይዞ የመጣ መሆኑ “አልን” የሚል ሙስጠጢር ማለትም ህቡዕ ግስ‘’headen verb‘’ አላፊ ሆኖ መጥቷል፣ ስለዚህ ‘’የኢንጅልም ባለቤቶች በውስጡ አላህ ባወረደው ሕግ ይፍረዱ አልን‘’ የሚል ፍቺ ይኖረዋል። ተፍሲሩል ጀላለይን በዚህ መልኩ ነው የፈሰረው፤ ለናሙና ያክል ሌላ ተጨማሪ ጥቅስ ብንመለከት ነገሩን የበለጠ ግልጽ ያደርገዋል፦
19:12 የሕያ ሆይ! መጽሐፉን በጥብቅ *ያዝ*፣ ጥበብንም በሕጻንነቱ *ሰጠነዉ*። يَٰيَحْيَىٰ خُذِ ٱلْكِتَٰبَ بِقُوَّةٍۢ ۖ وَءَاتَيْنَٰهُ ٱلْحُكْمَ صَبِيًّۭا

“ሁዚ” خُذِ ማለትም “ያዝ” ትዕዛዛዊ ግስ ነው፤ “አተይናሁ” آتَيْنَاهُ ማለትም “ሰጠነው” የሚለው ቃል ደግሞ ያለቀ አላፊ ግስ ነዉ፣ “አተይናሁ” ከሚለው የሚለቅቃል በፊት “ወ” و ማለትም “እና” የሚል አያያዥ መስተጻምር አለ፤ ያ ማለት “ያዝ” የሚለው ግስ “ሰጠነው” ከሚለው ግስ ጋር ተያይዞ የመጣ መሆኑ “አልን” የሚል ሙስጠጢር አላፊ ሆኖ መጥቷል፣ ትዕዛዛዊስለዚህ ‘’መጽሐፉን በጥብቅ ያዝ አልነዉ‘‘’ የሚል ፍቺ እንደሚኖረው ሁሉ ከላይ ያለውንም በዚህ ሒሳብ እንረዳዋለን።

አምላካችን አላህ የኢንጅል ባለቤቶችን ከነበሩት ከዒሳ ቀዳማይ ጋር የከበደ ኪዳን አድርጓል፦
5፥14 ከእነዚያም እኛ *ክርስቲያኖች* ነን ካሉትጣልንባቸው የጠበቀ ቃል ኪዳናቸውን ያዝን፡፡ *በእርሱም ከታዘዙበት ነገር ፈንታን ተውት*፡፡ ስለዚህ እስከ ትንሣኤ ቀን ድረስ በመካከላቸው ጠብንና ጥላቻን ፡፡ አላህም ይሠሩት የነበሩትን ሁሉ በእርግጥ ይነግራቸዋል፡፡ وَمِنَ الَّذِينَ قَالُوا إِنَّا نَصَارَىٰ أَخَذْنَا مِيثَاقَهُمْ فَنَسُوا حَظًّا مِّمَّا ذُكِّرُواተብሎ بِهِ فَأَغْرَيْنَا بَيْنَهُمُ الْعَدَاوَةَ وَالْبَغْضَاءَ إِلَىٰ يَوْمِ الْقِيَامَةِ ۚ وَسَوْفَ يُنَبِّئُهُمُ اللَّهُ بِمَا كَانُوا يَصْنَعُونَ

“ክርስቲያኖች” የተቀመጠው ቃል “ነሷራ” نَصَارَىٰ ነው፤ “ነስራኒይ” نَصْرَانِيّ የሚለው ቃል በነጠላ ሲሆን በብዜት ደግሞ “ነሷራ” نَصَارَىٰ ነው፤ ይህም ቃል “ነሰረ” نَصَرَ ማለትም “ረዳ” ከሚል ግስ መደብ ወይም “ነስር” نَصْر ማለትም “እርዳታ” ከሚል ከስም መደብ የረባ ሲሆን ቋንቋዊው ፍቺው “ረዳቶች” ማለት ነው።
“ነሲር” نَصِير ወይም “ናሲር” نَاصِر ማለትም “እረዳት”፣ “መንሱር” مَنصُور ማለትም “የተረዳ”፣ “ሙንተሲር” مُّنتَصِر ማለትም “ተረጂ” የሚሉት ቃላት ልክ እንደ “ነሳራ” ቃል “ነሰረ” ከሚል ግስ መደብ ወይም “ነስር” ከሚል የስም መደብ የረቡ ናቸው፤ ይህ ስም በቁርኣን 15 ጊዜ ተውስቷል፤ እነዚህ የአላህ እና የመልእክተኛ የዒሳ እረዳቶች ሐዋርያት ናቸው፦
60፥14 እናንተ ያመናችሁ ሆይ! የመርየም ልጅ ዒሳ ለሐዋርያቶቹ «ወደ አላህ *ረዳቴ* ማነው?» እንዳለ ሐወርያቶቹም «እኛ የአላህ *ረዳቶች* ነን» እንዳሉትላይ የአላህ ረዳቶች ኹኑ፡፡ ከእስራኤልም ልጆች አንደኛዋ ጭፍራ አመነች፡፡ ሌላይቱም ጭፍራ ካደች፡፡ እነዚያን ያመኑትንም በጠላታቸው አበረታናቸው፤ አሸናፊዎችም ኾኑ፡፡ يَٰٓأَيُّهَا ٱلَّذِينَ ءَامَنُوا۟ كُونُوٓا۟ أَنصَارَ ٱللَّهِ كَمَا قَالَ عِيسَى ٱبْنُ مَرْيَمَ لِلْحَوَارِيِّـۧنَ مَنْ أَنصَارِىٓ إِلَى ٱللَّهِ ۖ قَالَ ٱلْحَوَارِيُّونَ نَحْنُ أَنصَارُ ٱللَّهِ ۖ فَـَٔامَنَت طَّآئِفَةٌۭ مِّنۢ بَنِىٓ إِسْرَٰٓءِيلَ وَكَفَرَت طَّآئِفَةٌۭ ۖ فَأَيَّدْنَا ٱلَّذِينَ ءَامَنُوا۟ عَلَىٰ عَدُوِّهِمْ فَأَصْبَحُوا۟ ظَٰهِرِينَ
3፥52 ዒሳ ከእነርሱ ክህደት በተሰማውም ጊዜ፡- «ወደ አላህ *ረዳቶቼ* እነማን ናቸው» አለ፤ ሐዋርያት፡- «እኛ የአላህ *ረዳቶች* ነን፤ በአላህ አምነናል፤ እኛም ትክክለኛ ታዛዦች መኾናችንን መስክር» አሉ፡፡ فَلَمَّآ أَحَسَّ عِيسَىٰ مِنْهُمُ ٱلْكُفْرَ قَالَ مَنْ أَنصَارِىٓ إِلَى ٱللَّهِ ۖ قَالَ ٱلْحَوَارِيُّونَ نَحْنُ أَنصَارُ ٱللَّهِ ءَامَنَّا بِٱللَّهِ وَٱشْهَدْ بِأَنَّا مُسْلِمُونَ

አላህ ከእነዚህ የእርሱ እና የመልእክተኛ እረዳቶች ጋር የከበደ ቃል ኪዳን አድርጓል፤ ይህምም ቃል ኪዳን “በእኔ እና በመልክተኛዬ እመኑ» በማለት አዟል፤ አነዚህ የዒሳ ሐዋርያትም ይህንን ቃል አምነው ሙስሊሞች መሆናቸውን አስመስክረዋል፦
5፥111 ወደ *ሐዋርያትም* «በእኔ እና በመልክተኛዬ እመኑ» *በማለት ባዘዝኩ* ጊዜ አስታውስ፡፡ *«አመንን፤ እኛ ሙስሊሞች መኾናችንን መስክር»* አሉ፡፡ وَإِذْ أَوْحَيْتُ إِلَى ٱلْحَوَارِيِّـۧنَ أَنْ ءَامِنُوا۟ بِى وَبِرَسُولِى قَالُوٓا۟ ءَامَنَّا وَٱشْهَدْ بِأَنَّنَا مُسْلِمُونَ
3:52 ዒሳ ከእነርሱ ክሕደት በተሰማዉም ጊዜ ፡-ወደ አላህ *ረዳቶቼ እነማን ናቸዉ? አለ፤ ሐዋሪያት ፡ -እኛ የአላህ ረዳቶች ነን፤ በአላህም አምነናል፤ እኛም ትክክለኛ ”ታዛዦች”* መሆናችንን፥ መስክር፥ አሉ። فَلَمَّآ أَحَسَّ عِيسَىٰትተው مِنْهُمُ ٱلْكُفْرَ قَالَ مَنْ أَنصَارِىٓ إِلَى ٱللَّهِ ۖ

ነገር ግን ከሐዋርያት ህልፈት በኃላ ያሉት ነስራኒይዎች በእርሱም ከታዘዙት ፈንታ በአላህ ላይ በመቅጠፍ “ሦስት ነው” በማለት ወሰን አልፈዋል፦
4፥171 እናንተ የመጽሐፉ ሰዎች ሆይ! በሃይማኖታችሁ ወሰንን አትለፉ፡፡ *በአላህም ላይ እውነትን እንጅ አትናገሩ፡፡……. ሦስት ነው* አትበሉም፡፡ ተከልከሉ፤ ለእናንተ የተሻለ ይኾናልና፡፡ አላህ አንድ አምላክ ብቻ ነው፡፡ يَٰٓأَهْلَ ٱلْكِتَٰبِ لَا تَغْلُوا۟ فِى دِينِكُمْ وَلَا تَقُولُوا۟ عَلَى ٱللَّهِ إِلَّا ٱلْحَقَّ ۚ إِنَّمَا ٱلْمَسِيحُ عِيسَى ٱبْنُ مَرْيَمَ رَسُولُ ٱللَّهِ وَكَلِمَتُهُۥٓ أَلْقَىٰهَآ إِلَىٰ مَرْيَمَ وَرُوحٌۭ مِّنْهُ ۖ فَـَٔامِنُوا۟ بِٱللَّهِ وَرُسُلِهِۦ ۖ وَلَا تَقُولُوا۟ ثَلَٰثَةٌ ۚ ٱنتَهُوا۟ خَيْرًۭا لَّكُمْ ۚ إِنَّمَا ٱللَّهُ إِلَٰهٌۭ وَٰحِدٌۭ ۖ سُبْحَٰنَهُۥٓ أَن يَكُونَ لَهُۥ وَلَدٌۭ ۘ لَّهُۥ مَا فِى ٱلسَّمَٰوَٰتِ وَمَا فِى ٱلْأَرْضِ ۗ وَكَفَىٰ بِٱللَّهِ وَكِيلًۭا

አላህ የኢየሱስን ቀዳማይ ተከታይ በእነዚያ ኢየሱስን በካዱት አይሁዳውያን ላይ ሲያበልጣቸው በተቃራኒው በሁለተኛው ክፍለ-ዘመን ያሉት ተከታዮቹ ግን አላህ ያልተናገረውን ምንኩስና የእርሱን ውዴታ ለመጠበቅ ፈጠሯት፦
3፥55 አላህም ባለ ጊዜ አስታውስ፡፡ ዒሳ ሆይ! እኔአድራጊ ወሳጂህ ወደ እኔም አንሺህ ነኝ፡፡ ከነዚያም ከካዱት ሰዎች አጥሪህ ነኝ *እነዚያንም የተከተሉህን እስከ ትንሣኤ ቀን ድረስ ከነዚያ ከካዱት በላይ ነኝ*፡፡ إِذْ قَالَ ٱللَّهُ يَٰعِيسَىٰٓ إِنِّى مُتَوَفِّيكَ وَرَافِعُكَ إِلَىَّ وَمُطَهِّرُكَ مِنَ ٱلَّذِينَ كَفَرُوا۟ وَجَاعِلُ ٱلَّذِينَ ٱتَّبَعُوكَ فَوْقَ ٱلَّذِينَ كَفَرُوٓا۟ إِلَىٰ يَوْمِ ٱلْقِيَٰمَةِ
57፥27 ከዚያም በዱካዎቻቸው ላይ መልክተኞቻችንን አስከታተልን፡፡ የመርየምን ልጅ ዒሳንም አስከተልን፡፡ ኢንጂልንም ሰጠነው፡፡ *በእነዚያም በተከተሉት ልቦች ውሰጥ መለዘብንና እዝነትን፣ አዲስ የፈጠሩዋትንም ምንኩስና አደረግን፡፡ በእነርሱ ምንኩስናን አልጻፍናትም፡፡ ግን የአላህን ውዴታ ለመፈለግ ሲሉ ፈጠሩዋት፡፡ ተገቢ አጠባበቋንም፤ አልጠበቋትም*፡፡ ከእነርሱም ለእነዚያ ላመኑት ምንዳቸውን ሰጠናቸው፡፡፡ ከእነርሱም ብዙዎቹ አመጸኞች ናቸው፡፡ ثُمَّ قَفَّيْنَا عَلَىٰٓ ءَاثَٰرِهِم بِرُسُلِنَا وَقَفَّيْنَا بِعِيسَى ٱبْنِ مَرْيَمَ وَءَاتَيْنَٰهُ ٱلْإِنجِيلَ وَجَعَلْنَا فِى قُلُوبِ ٱلَّذِينَ ٱتَّبَعُوهُ رَأْفَةًۭ وَرَحْمَةًۭ وَرَهْبَانِيَّةً ٱبْتَدَعُوهَا مَا كَتَبْنَٰهَا عَلَيْهِمْ إِلَّا ٱبْتِغَآءَ رِضْوَٰنِ ٱللَّهِ فَمَا رَعَوْهَا حَقَّ رِعَايَتِهَا ۖ فَـَٔاتَيْنَا ٱلَّذِينَ ءَامَنُوا۟ مِنْهُمْ أَجْرَهُمْ ۖ وَكَثِيرٌۭ مِّنْهُمْ فَٰسِقُونَ

ከዒሳ ተከታዮች ብዙዎቹ አመጸኞች ናቸው፤ ነገር ግን አላህ ከእነርሱም ለእነዚያ ላመኑት ምንዳቸውን ሰጣቸው፤ በእነርሱ ላይ በሚነበብላቸውም ጊዜ «በእርሱ አምነናል፡፡ እርሱ ከጌታችን የኾነ እውነት ነው፤ እኛ ከእርሱ በፊት ሙስሊሞች ነበርን» ይላሉ፦
28፥52 እነዚያ ከእርሱ በፊት መጽሐፍን የሰጠናቸው እነርሱ *በእርሱ ያምናሉ*፡፡ الَّذِينَ آتَيْنَاهُمُ الْكِتَابَ مِن قَبْلِهِ هُم بِهِ يُؤْمِنُونَ
28፥53 በእነርሱ ላይ በሚነበብላቸውም ጊዜ «በእርሱ አምነናል፡፡ እርሱ ከጌታችን የኾነ እውነት ነው፡፡ *እኛ ከእርሱ በፊት ሙስሊሞች ነበርን*» ይላሉ፡፡ وَإِذَا يُتْلَىٰ عَلَيْهِمْ قَالُوا آمَنَّا بِهِ إِنَّهُ الْحَقُّ مِن رَّبِّنَا إِنَّا كُنَّا مِن قَبْلِهِ مُسْلِمِينَ

ልብ አድርግ “እኛ ከእርሱ ከመጽሐፉ ማለትም ከቁርአን መውረድ በፊት ሙስሊም ነበርን” ማለታቸው ምክንያታዊ ነው፤ ሙስሊም” مُسْلِم ትርጉሙ “አቢድ” عَابِدُ ማለትም “አምላኪ” አሊያም “ቃኒት” قَانِتِ ማለትም “ታዛዥ” ማለት ነው። እንደሚታወቀው የመጽሐፉ ሰዎች ብዙዎቹ አመጸኞች ናቸው፤ አይሁዳውያን አላህ የተቆጣባቸው ሲሆኑ ክርስቲያኖች ደግሞ የተሳቱተት ናቸው፦
ጃምዒ አት-ተርሚዚ መጽሐፍ 47, ሐዲስ 3212
ዐዲይ ኢብኑ ሓቲም እንደተረከው ነብዩም”ﷺ” አሉ፦ አይሁዳውያን የተቆጣባቸው ናቸው፤ ክርስቲያኖች የተሳቱተት ናቸው። عَنْ عَدِيِّ بْنِ حَاتِمٍ، عَنِ النَّبِيِّ صلى الله عليه وسلم قَالَ ‏ “‏ الْيَهُودُ مَغْضُوبٌ عَلَيْهِمْ وَالنَّصَارَى ضُلاَّلٌ ‏”‏ ‏.‏

ነገር ግን ከአይሁዳውያን ጥቂት ያልተቆጣቸው፤ እንዲሁ ከክርስቲያኖች ጥቂት ያልተሳሳቱ ነበሩ፤ እኛም ከመንገዱ እንዳንስት የእነዚያን በእነርሱ ላይ በጎ የዋለላቸውን መንገድ ምራን ብለን እንቀራለን፦
1፥7 የእነዚያን በእነርሱ ላይ በጎ የዋልክላቸውን፣ በእነርሱ ላይ *”ያልተቆጣህባቸውን እና ያልተሳሳቱትንም ሰዎች መንገድ ምራን”*፤ በሉ። صِرَٰطَ ٱلَّذِينَ أَنْعَمْتَ عَلَيْهِمْ غَيْرِ ٱلْمَغْضُوبِ عَلَيْهِمْ وَلَا ٱلضَّآلِّينَ
ኢማም ቡኻርይ : መጽሐፍ 65, ሐዲስ 4475
አቢ ሁረይራህ”ረ.ዐ.” እንደተረከው የአላህ መልእክተኛ”ﷺ” አሉ፦ “ኢማሙ፦ “ያልተቆጣህባቸውን እና ያልተሳሳቱትንም ሰዎች መንገድ ምራን” ባለ ጊዜ አሚን በሉ፤ عَنْ أَبِي هُرَيْرَةَ ـ رضى الله عنه ـ أَنَّ رَسُولَ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم قَالَ ‏”‏ إِذَا قَالَ الإِمَامُአላህ ‏{‏غَيْرِ الْمَغْضُوبِ عَلَيْهِمْ وَلاَ الضَّالِّينَ‏}‏ فَقُولُوا آمِينَ‏.

“አሚን” آمين‌‎ ማለት ተስማምቻለው “ይሁን” “ይደረግ” ማለት ነው፤ አላህ ሆይ! ” ያልተቆጣህባቸውን እና ያልተሳሳቱትንም ሰዎች መንገድ ምራን፤ አሚን።

ከወሒድ ዐቃቢ ኢሥላም

የበለጠ ለማወቅ
ጥሪያችን Tiriyachen

ወሰላሙ አለይኩም
ሱረቱል ፋቲሓህ

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው።

15፥87 *ከሚደጋገሙ የኾኑን ሰባትን እና ታላቁንም ቁርኣን በእርግጥ ሰጠንህ*፡፡ وَلَقَدْ آتَيْنَاكَ سَبْعًا مِّنَ الْمَثَانِي وَالْقُرْآنَ الْعَظِيمَ

አምላካችን አላህ “ሙርሲል” مُرْسِل ማለትም “ላኪ” ነው፤ ነብያችን”ﷺ” ደግሞ “ረሱል” رِسَالَة ማለትም “መልክተኛው” ናቸው፤ እንዲሁ ቁርኣን የአላህ “ሪሳላ” رِسَالَ ማለትም “መልእክት” ነው።
የመልእክቱ “ሙአለፍ” مؤلف ማለትም “አመንጪ”author” አምላካችን አላህ ሲሆን፤ ነብያችን”ﷺ” ደግሞ የመልእክቱ “ሙራሲል” مراسل ማለት “አስተላላፊ”reporter” ናቸው፤ አምላካችን አላህ ለነብያችን”ﷺ”፦ “ቁል” قُلْ ማለትም “በል” በሚል ትዕዛዛዊ ግስ ያዛቸዋል፦
112፥1 *በል «እርሱ አላህ አንድ ነው*፡፡ قُلْ هُوَ اللَّهُ أَحَدٌ
13፥30 እንደዚሁ ከበፊትዋ ብዙ ሕዝቦች በእርግጥ ያለፉ ወደኾነችው ሕዝብ እነርሱ በአልረሕማን የሚክዱ ሲኾኑ ያንን *ወደ አንተ ያወረድነውን ቁርኣን በእነርሱ ላይ ታነብላቸው ዘንድ ላክንህ፡፡ «እርሱ አልረሕማን ጌታዬ ነው፡፡ ከእርሱ ሌላ አምላክ የለም፡፡ በእርሱ ላይ ተጠጋሁ፡፡ መመለሻዬም ወደ እርሱ ብቻ ነው» በላቸው*፡፡ كَذَٰلِكَ أَرْسَلْنَاكَ فِي أُمَّةٍ قَدْ خَلَتْ مِن قَبْلِهَا أُمَمٌ لِّتَتْلُوَ عَلَيْهِمُ الَّذِي أَوْحَيْنَا إِلَيْكَ وَهُمْ يَكْفُرُونَ بِالرَّحْمَـٰنِ ۚ قُلْ هُوَ رَبِّي لَا إِلَـٰهَ إِلَّا هُوَ عَلَيْهِ تَوَكَّلْتُ وَإِلَيْهِ مَتَابِ

“ወደ አንተ ያወረድነውን ቁርኣን በእነርሱ ላይ ታነብላቸው ዘንድ ላክንህ” የሚለው ሃይለ-ቃል ቁርኣንን አውራጅና ነብያችንን”ﷺ” ላኪው አላህ እራሱ “በል” ማለቱን እንረዳለን፤ በመቀጠል እዛው አንቀጽ ላይ “ቁል” قُلْ ብሎ መናገሩ በራሱ “በል” የሚለው ማንነት አላህ መሆኑን ቁልጭ አድርጎ ያሳያል፤ በተጨማሪም “በልን” ወደ ነብያችን”ﷺ” የሚጥለው እራሱ እንደሆነ ይናገራል፦
73፥5 *እኛ በአንተ ላይ ከባድ ቃልን እንጥላለንና*፡፡ إِنَّا سَنُلْقِي عَلَيْكَ قَوْلًا ثَقِيلًا

እዚህ አንቀጽ ላይ “ቃል” ለሚለው የተቀመው ቃላት “ቀውል” قَوْل ሲሆን “ቁል” قُلْ ከሚል ትዕዛዛዊ ግስ የመጣ ነው፤ ስለዚህ “በል” እያለ የሚያስነብባቸው እራሱ አላህ ነው፤ ሱረቱል ፋቲሓህ የሚደጋገሙ ሰባት አንቀጾች ናት፤ ምክንያቱም ሱረቱል ፋቲሓህ ሰባት አናቅጽ አላት፤ በተጨማሪም ነብያችን”ﷺ” ሱረቱል ፋቲሓህ የሚደጋገሙ ሰባት አንቀጾች ናት ብለው ነግረውናል፦
15፥87 *ከሚደጋገሙ የኾኑን ሰባትን እና ታላቁንም ቁርኣን በእርግጥ ሰጠንህ*፡፡ وَلَقَدْ آتَيْنَاكَ سَبْعًا مِّنَ الْمَثَانِي وَالْقُرْآنَ الْعَظِيمَ
ኢማም ቡኻርይ: መጽሐፍ 66, ሐዲስ 28
አቢ ሠዒድ ኢብኑ ሙዐላ እንደተረከው *ሶላት ላይ ሆኜ ነብዩ”ﷺ” ጠሩኝ፤ ነገር ጥሪያቸውን አልመለስኩላቸውም፤ በኃላ ላይ፦ “የአላህ መልእክተኛ ሆይ! ሶላት ላይ ነበርኩኝ” አልኩኝ፤ እሳቸውም፦ አላህ፦ “(መልእክተኛው) በጠራችሁ ጊዜ ለአላህ እና ለመልክተኛው ታዘዙ”8፥24 አላለምን? ከዚያም፦ “በቁርኣን ውስጥ ታላቂቱን ሱራህ ላስተምርህን? እርሷም፦ “ምስጋና ለአላህ ይገባው የዓለማት ጌታ ለኾነው የምትለዋ የሚደጋገሙ የሆኑ ሰባት ሱረቱል ፋቲሐህን እና ታላቁ ቁርኣንን ተሰጠኝ”*። عَنْ أَبِي سَعِيدِ بْنِ الْمُعَلَّى، قَالَ كُنْتُ أُصَلِّي فَدَعَانِي النَّبِيُّ صلى الله عليه وسلم فَلَمْ أُجِبْهُ قُلْتُ يَا رَسُولَ اللَّهِ إِنِّي كُنْتُ أُصَلِّي‏.‏ قَالَ ‏”‏ أَلَمْ يَقُلِ اللَّهُ ‏{‏اسْتَجِيبُوا لِلَّهِ وَلِلرَّسُولِ إِذَا دَعَاكُمْ‏}‏ ثُمَّ قَالَ أَلاَ أُعَلِّمُكَ أَعْظَمَ سُورَةٍ فِي الْقُرْآنِ قَبْلَ أَنْ تَخْرُجَ مِنَ الْمَسْجِدِ ‏”‌‏.‏ فَأَخَذَ بِيَدِي فَلَمَّا أَرَدْنَا أَنْ نَخْرُجَ قُلْتُ يَا رَسُولَ اللَّهِ إِنَّكَ قُلْتَ لأُعَلِّمَنَّكَ أَعْظَمَ سُورَةٍ مِنَ الْقُرْآنِ‏.‏ قَالَ ‏”‌‏{‏الْحَمْدُ لِلَّهِ رَبِّ الْعَالَمِينَ‏}‏ هِيَ السَّبْعُ الْمَثَانِي وَالْقُرْآنُ الْعَظِيمُ الَّذِي أُوتِيتُهُ ‏”‌‏.‏
ጃምዒ አት-ተርሚዚ መጽሐፍ 47, ሐዲስ 3415
አቢ ሁረይራህ”ረ.ዐ” እንደተረከው፦ “የአላህ መልእክተኛ”ﷺ” እንዲህ አሉ፦ *አል-ሐምዱሊሏህ የቁርኣን እናት፣ የመጽሐፉ እናት እና ሰባት የተደጋገሙ ናት*። عَنِ ابْنِ أَبِي ذِئْبٍ، عَنِ الْمَقْبُرِيِّ، عَنْ أَبِي هُرَيْرَةَ، قَالَ قَالَ رَسُولُ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم ‏ “‏ الْحَمْدُ لِلَّهِ أُمُّ الْقُرْآنِ وَأُمُّ الْكِتَابِ وَالسَّبْعُ الْمَثَانِي ‏”
ሱረቱል ፋቲሓህ ላይ ከሚሽነሪዎች የሚነሳው ጥያቄ “ቀጥተኛውን መንገድ ምራን“ የሚለው የአላህ ንግግር ከሆነ አላህ ማንን ነው ምራን የሚለው? የሚል ነው፤ መልሱ "ቀጥተኛውን መንገድ ምራን" እኛ እንድንል ለእኛ ያለው ነው፤ ይህንም "ቁል" قُلْ የሚል ትዕዛዛዊ ግስ "ሙስተቲር" ْمُسْتَتِر ማለትም "ህቡዕ-ግስ"headen verb" ሆኖ የመጣ ነው፦
1፥6 *ቀጥተኛውን መንገድ ምራን*፡፡ اهْدِنَا الصِّرَاطَ الْمُسْتَقِيمَ

"ኢህዲና" اهْدِنَا ማለትም "ምራን" ብዙ ቁጥር ሲሆን ይህ ባለቤት ግስ አማኞችን ያመለክታል፤ ተሳቢው ግስ ደግሞ መሪውን ያመለክታል፤ ስለዚህ "ቁሉ" قُلُوا የሚለው ሙስተቱር ሆኖ የመጣ ነው፤ ለምሳሌ በሱረቱል በቀራህ 2፥187 ላይ "ከተበ" كَتَبَ ማለትም "ጻፈ" የሚለውን ወደ ኢንግሊሽ ሲቀየር "He wrote" ነው፣ "He" ደግሞ ወደ ዐረቢኛ "ሁወ" هُوَ ማለትም "እርሱ" ነው፤ "ሁወ" هُوَ የሚለው "ከተበ" كَتَبَ ላይ ሚስተቲር ሆኖ የመጣ ነው፤ "ቁል" ወይም "ቁሉ" ተደብቀው በሙስተቲር የሚመጡበት ብዙ ቦታ ነው፦
11፥2 *አላህን እንጂ ሌላን አታምልኩ፤ እኔ ለእናንተ ከእርሱ የተላክሁ አስጠንቃቂ እና አብሳሪ ነኝ*፡፡ أَلَّا تَعْبُدُوا إِلَّا اللَّهَ ۚ إِنَّنِي لَكُم مِّنْهُ نَذِيرٌ وَبَشِيرٌ

እዚህ አንቀጽ ላይ "ቁል" የሚለው የለም፤ ያ ማለት "አስጠንቃቂ እና አብሳሪ ነኝ" የሚለው አላህ ነው ማለት ቂልነት ነው፤ ምክንያቱም "ሚንሁ" مِّنْهُ የሚል ሃይለ-ቃል አለ፤ "ሚን" مِّن ማለት "ከ" ሲሆን መስተዋድድ ነው፤ በሚን ላይ "ሁ" هُ ማለት "እርሱ" የሚል ተሳቢ አለ፤ "እርሱ" የተባለው ላኪ አላህ ነው "አስጠንቃቂ እና አብሳሪ ነኝ" የሚሉት ደግሞ የተላኩት ነብያችን"ﷺ" ናቸው፦
35፥24 *እኛ አብሳሪ እና አስጠንቃቂ አድርገን በእውነቱ ላክንህ*፡፡ إِنَّا أَرْسَلْنَاكَ بِالْحَقِّ بَشِيرًا وَنَذِيرًا
7፥188 *እኔ ለሚያምኑ ሕዝቦች አስጠንቃቂ እና አብሳሪ እንጂ ሌላ አይደለሁም» በላቸው*፡፡ قُل لَّا أَمْلِكُ لِنَفْسِي نَفْعًا وَلَا ضَرًّا إِلَّا مَا شَاءَ اللَّهُ ۚ وَلَوْ كُنتُ أَعْلَمُ الْغَيْبَ لَاسْتَكْثَرْتُ مِنَ الْخَيْرِ وَمَا مَسَّنِيَ السُّوءُ ۚ إِنْ أَنَا إِلَّا نَذِيرٌ وَبَشِيرٌ لِّقَوْمٍ يُؤْمِنُونَ
"በል" ሳይል በአንድ አንቀጽ ላይ በውስጠ ታዋቂነት "እኔም በእናንተ ላይ ጠባቂ አይደለሁም" ይልና፤ ሌላ አንቀጽ ላይ "እኔም በእናንተ ላይ ጠባቂ አይደለሁም በል" የሚል ይጠቀማል፦
6፥104 *እኔም በእናንተ ላይ ጠባቂ አይደለሁም*፡፡ وَمَا أَنَا عَلَيْكُم بِحَفِيظٍ
6፥66 *በላቸው፡- «በእናንተ ላይ ጠባቂ አይደለሁም፡፡»* قُل لَّسْتُ عَلَيْكُم بِوَكِيلٍ

"በል" ሳይል በአንድ አንቀጽ ላይ በውስጠ ታዋቂነት "እኔም የሙስሊሞች መጀመሪያ ነኝ" ይልና፤ ሌላ አንቀጽ ላይ "እኔም የሙስሊሞች መጀመሪያ ነኝ በል" የሚል ይጠቀማል፦
6፥163 *«ለእርሱ ተጋሪ የለውም፡፡ በዚህም በማጥራት ታዘዝኩ፡፡ እኔም የሙስሊሞች መጀመሪያ ነኝ»*፡፡ لَا شَرِيكَ لَهُ ۖ وَبِذَٰلِكَ أُمِرْتُ وَأَنَا أَوَّلُ الْمُسْلِمِينَ
39፥11 *በል* «እኔ አላህን ሃይማኖትን ለርሱ ያጠራሁ ኾኜ እንድግገዛው ታዘዝኩ፡፡ قُلْ إِنِّي أُمِرْتُ أَنْ أَعْبُدَ اللَّهَ مُخْلِصًا لَّهُ الدِّينَ
39፥12 *«የሙስሊሞችም መጀመሪያ እንድኾን ታዘዝኩ፡፡»* وَأُمِرْتُ لِأَنْ أَكُونَ أَوَّلَ الْمُسْلِمِينَ

ይህንን ከተረዳን ሱረቱል ፋቲሓህ ላይ "አንተን" ብለው በሚሉት ላይ "በል" ሳይል ሌላ አንቀጽ ላይ "አንተ በል" የሚል ይጠቀማል፦
3፥26 *በል*፡- «የንግስና ባለቤት የኾንክ አላህ ሆይ! ለምትሻው ሰው ንግሥናን ትሰጣለህ፡፡ ከምትሻውም ሰው ንግሥናን ትገፍፋለህ፡፡ የምትሻውንም ሰው ታልቃለህ፡፡ የምትሻውንም ሰው ታዋርዳለህ፡፡ መልካም ነገር ሁሉ በእጅህ በችሎታህ ነው፤ *"አንተ"* በነገሩ ሁሉ ላይ ቻይ ነህና፡፡ قُلِ اللَّهُمَّ مَالِكَ الْمُلْكِ تُؤْتِي الْمُلْكَ مَن تَشَاءُ وَتَنزِعُ الْمُلْكَ مِمَّن تَشَاءُ وَتُعِزُّ مَن تَشَاءُ وَتُذِلُّ مَن تَشَاءُ ۖ بِيَدِكَ الْخَيْرُ ۖ إِنَّكَ عَلَىٰ كُلِّ شَيْءٍ قَدِيرٌ

በተጨማሪም ነብያችን"ﷺ" በሐዲስ ላይ ሱረቱል ፋቲሓን የሚለው የአላህ ባሪያ ወደ አላህ መሆኑን በግልጽ እና በማያሻማ መልኩ ነግረውናል፦
ኢማም ሙስሊም መጽሐፍ 4 ሐዲስ 41
አቢ ሁረይራ"ረ.ዐ" እንደተረከው *ነብዩ"ﷺ" አሉ፦ "የቁርአን እናት ሳያነብ የሰገደ ሰው ሶላቱ ጎዶሎ ነው"* አንድ ሰው ለአቢ ሁረይራ፦ "ከአሰጋጁ በኋላ ብንሆንም እንኳን"? አለው፤ እርሱም አለ፦ "ለራስህ አንብብ ምክንያቱም ነብዩ"ﷺ" እንዲህ ሲሉ ሰምቻለሁና፦ *"ኃያሉና የተከበረው አላህ እንዲህ ብሏል፦ "ሶላትን በእኔ እና በባሪያዬ መካከል ለሁለት ከፍየዋለሁ እናም ባሪያዬየጠየቀውን ያገኛል*፤ ባሪያው፦ *"ምስጋና ለአላህ ይገባውየዓለማት ጌታ ለኾነው" ሲል አላህ፦ "ባሪያዬአመሰገነኝ" ይላል*፤ ባሪያው፦ *"እጅግ በጣም ርኅሩህ በጣም አዛኝ" ሲልደግሞ አላህ፦ "ባሪያዬአሞገሰኝ’ ይላል*፤ ባሪያው፦ *"የፍርዱ ቀን ባለቤት ለኾነው" ሲል አላህ፦ ባሪያዬ አላቀኝ" ይላል*፤ ባሪያው፦ *"አንተን ብቻ እንግገዛለን፤ አንተንም ብቻ እርዳታን እንለምናለን" በሚል ግዜ አላህ፦ "ይህ በእኔ እና
በባሪያዬ መካከል ነው እናም ባሪያዬ የጠየቀውን ያገኛል" ይላል*፤ ባሪያው፦ *"ቀጥተኛውን መንገድ ምራን የእነዚያን በእነርሱ ላይበጎ የዋልክላቸውን በነሱ ላይያልተቆጣህባቸውንና ያልተሳሳቱትንም ሰዎች መንገድ ምራን" በሚል ግዜ ደግሞ አላህ፦ "ይህ ለባሪያዬ ነው፤ እናም ባሪያዬየጠየቀውን ያገኛል" ይላል*፡፡ عَنْ أَبِي هُرَيْرَةَ، عَنِ النَّبِيِّ صلى الله عليه وسلم قَالَ ‏"‏ مَنْ صَلَّى صَلاَةً لَمْ يَقْرَأْ فِيهَا بِأُمِّ الْقُرْآنِ فَهْىَ خِدَاجٌ - ثَلاَثًا - غَيْرُ تَمَامٍ ‏"‏ ‏.‏ فَقِيلَ لأَبِي هُرَيْرَةَ إِنَّا نَكُونُ وَرَاءَ الإِمَامِ ‏.‏ فَقَالَ اقْرَأْ بِهَا فِي نَفْسِكَ فَإِنِّي سَمِعْتُ رَسُولَ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم يَقُولُ ‏"‏ قَالَ اللَّهُ تَعَالَى قَسَمْتُ الصَّلاَةَ بَيْنِي وَبَيْنَ عَبْدِي نِصْفَيْنِ وَلِعَبْدِي مَا سَأَلَ فَإِذَا قَالَ الْعَبْدُ ‏{‏ الْحَمْدُ لِلَّهِ رَبِّ الْعَالَمِينَ‏}‏ ‏.‏ قَالَ اللَّهُ تَعَالَى حَمِدَنِي عَبْدِي وَإِذَا قَالَ ‏{‏ الرَّحْمَنِ الرَّحِيمِ‏}‏ ‏.‏ قَالَ اللَّهُ تَعَالَى أَثْنَى عَلَىَّ عَبْدِي ‏.‏ وَإِذَا قَالَ ‏{‏ مَالِكِ يَوْمِ الدِّينِ‏}‏ ‏.‏ قَالَ مَجَّدَنِي عَبْدِي - وَقَالَ مَرَّةً فَوَّضَ إِلَىَّ عَبْدِي - فَإِذَا قَالَ ‏{‏ إِيَّاكَ نَعْبُدُ وَإِيَّاكَ نَسْتَعِينُ‏}‏ ‏.‏ قَالَ هَذَا بَيْنِي وَبَيْنَ عَبْدِي وَلِعَبْدِي مَا سَأَلَ ‏.‏ فَإِذَا قَالَ ‏{‏ اهْدِنَا الصِّرَاطَ الْمُسْتَقِيمَ * صِرَاطَ الَّذِينَ أَنْعَمْتَ عَلَيْهِمْ غَيْرِ الْمَغْضُوبِ عَلَيْهِمْ وَلاَ الضَّالِّينَ‏}‏ ‏.‏ قَالَ هَذَا لِعَبْدِي وَلِعَبْدِي مَا سَأَلَ ‏"‏ ‏.‏ قَالَ سُفْيَانُ حَدَّثَنِي بِهِ الْعَلاَءُ بْنُ عَبْدِ الرَّحْمَنِ بْنِ يَعْقُوبَ دَخَلْتُ عَلَيْهِ وَهُوَ مَرِيضٌ فِي بَيْتِهِ فَسَأَلْتُهُ أَنَا عَنْهُ ‏.‏

በዚህ መልኩ መረዳት ካልቻላችሁ አንድ ናሙና ከባይብል ላቅርብ፦ ዮሐንስ 20፥17 ኢየሱስም፦ ገና ወደ አባቴ አላረግሁምና አትንኪኝ፤ ነገር ግን ወደ ወንድሞቼ ሄደሽ፦ እኔ ወደ አባቴና ወደ አባታችሁ ወደ አምላኬና ወደ አምላካችሁ *ዓርጋለሁ ብለሽ ንገሪአቸው* አላት።

ወደ አምላኩ አራጊው ኢየሱስ ሆኖ ሳለ "ዓርጋለሁ ብለሽ ንገሪአቸው" ሲላት አራጊዋ መቅደላዊት ማርያም ሆና ነውን? አይ "ይላል" በይ ለማለት ተፈልጎ ነው ከተባለ "ይላል" የሚለውን የት አለ? በውስጠ-ታዋቂነት ይኖራል ከሆነ መልሱ እንግዲያውስ ሱረቱል ፋቲሐህንም በዚህ መልኩ መረዳት ይቻላል። ያለበለዚያ አራጊዋ መቅደላዊት ማርያም ትሆናለች።

ወሒድ ዐቃቢ ኢሥላም
ጥሪያችን በሁሉም ቦታ!
Follow us on:👇🏻
Telegram ፦ https://www.tg-me.com/tiriyachen
Website ፦ https://tiriyachen.org
Instagram ፦ https://bit.ly/3eVixKv
TikTok ፦ https://www.tiktok.com/@tiriyachen

ወሰላሙ አለይኩም
የቁርአን ሱራህ

ክፍል አንድ

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡

መግቢያ
“ሱራህ” سُورَة የሚለው ቃል ትርጉሙ “ምዕራፍ” ወይም “ክፍል” አሊያም “ደረጃ” ማለት ነው፤ ቁርአን ሱራህ እንዳለው አላህ በቁርአን 10 ጊዜ ያነሳዋል፣ ለናሙና ያክል ውስን ጥቅሶችን ብንመለከት፦
24:1 ይህች ያወረድናትና የደነገግናት “ሱራ” سُورَةٌ ናት፣
2:23 በባሪያችንም ላይ ካወረድነው በመጠራጠር ውስጥ ብትኾኑ ከብጤው አንዲትን “ምዕራፍ” بِسُورَةٍ አምጡ፡፡
10:38 በእውነትም «ቀጣጠፈው » ይላሉን «ይህ ከሆነ መሰሉን አንዲት “ሱራ” بِسُورَةٍ አምጡ፡፡
11፥13 ይልቁንም «ቀጣጠፈው» ይላሉን፡- «እውነተኞች እንደሆናችሁ ብጤው የሆኑን ዐስር የተቀጣጠፉ “ሱራዎች” سُوَرٍ አምጡ፡፡
9፥64 "መ*/ና*/ፍ*/ቃ*/ን"በልቦቻቸው ውስጥ ያለውን ነገር የምትነግራቸው “ሱራ” سُورَةٌ በእነርሱ ላይ መውረዷን ይፈራሉ፡፡

ቁርአን 114 ሱራዎች ሲኖሩት ለ 13 ዓመት 86 ሱራዎች የወረዱት በመካ ሲሆን ለ 10 ዓመት ደግሞ 28 ሱራዎች የወረዱት በመዲና ነው፣ አላህ ቁርአንን በሱራህ ከፋፍሎ ያወረደው ልብህ በማርጋት ለማንበብ እንዲመች ነው፦
17:106 ቁርአንንም በሰዎች ላይ ሆነህ ታነበው ዘንድ “ከፋፈልነው” ቀስ በቀስ ማውረድንም አወረድነው ።
25:32 እነዚያ የካዱትም፦ ቁርአን በርሱ ላይ ለምን በጠቅላላ አንድ ጊዜ አልተወረደም? አሉ፤ እንደዚሁ በእርሱ ልብህን ልናረጋ “ከፋፍለን” አወረድነው ፤ ቀስ በቀስ “መለያየትም” ለየነው።
3፥3 መጽሐፉን በአንተ ላይ “ከፋፍሎ” በእውነት አወረደ፡፡

አንድ ሱራህ ከሌላው ሱራህ የሚለየው በተስሚያህ ማለትም “በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ በጣም አዛኝ በሆነው” በሚል ቃል ነው፦
ሱነን አቢ ዳውድ መጽሐፍ 2, ቁጥር 398
ኢብኑ አባስ እንደተረከው የአላህ መልእክተኛም”ﷺ” አሉ፦ ሁለት ሱራዎች አይለያዩ በመካከላቸው “በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ በጣም አዛኝ በሆነው” የሚለው ቃል ወደ እርሳቸው ቢወርድላቸው እንጂ።
قَالَ كَانَ النَّبِيُّ صلى الله عليه وسلم لاَ يَعْرِفُ فَصْلَ السُّورَةِ حَتَّى تُنَزَّلَ عَلَيْهِ ‏{‏ بِسْمِ اللَّهِ الرَّحْمَنِ الرَّحِيمِ ‏}‏ ‏
96፥1 አንብብ በዚያ ሁሉን “በፈጠረው ጌታህ ስም”፡፡

እያንዳንዱ ሱራህ ሲጀምር በተስሚያህ ነው ከአንድ ሱራህ በስተቀር፤ ይህም ሱራህ ሱረቱ አት-ተውባህ ነው፤ 9ኛው ሱራህ ተስሚያህ ባይኖርም ሱረቱ አን-ነምል 27፥30 ላይ ይደግመዋል፤ ይህም ሱረቱ አት-ተውባህ የቁጣ ሱራህ ሆና ብትዘለልም የዘጠኝ ድምር የሆነችው ሱረቱ አን-ነምል ላይ ይገኛል፤ 2+7=9 ይሆናል፦
27፥30 «እርሱ ከሱለይማን ነው፡፡ እርሱም “በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩኅ በጣም አዛኝ በኾነው”፡፡

ኦሪት፣ መዝሙራት፣ የነቢያት መጽሐፍት ጸሐፊዎቻቸው ባልሆኑ ሰዎች ቢከፋፈሉም ባይብል ግን በምእራፍ የተከፋፈለው ከ 1244 AD እስከ 1248 AD እቴቨን ላንቶን በሚባል ሰው ነው፤ ከዚያም ባሻገር የመጽሐፍቱን ስም የዳቦ ስም አድርገው በሰው ስም የሰየሙት ነብያት ሳይሆኑ ታሪክ ጸሐፊዎች ናቸው፤ የቁርአን ሱራህ ስም ግን ከመለኮት በጂብሪል ወደ ነብያችን የተላለፈ ነው፤ ይህን ከነብያችን ንግግር ለናሙና ማቅረብ ይቻላል፦
ኢማም ሙስሊም መጽሐፍ 6, ሐዲስ 311
ነብዩም”ﷺ” አሉ፦ “”ከሱረቱል ከህፍ”” መጀመሪያ አስር አናቅፅ ያፈዘ ማንኛውም ከደጃል ይጠበቃል።
أَنَّ النَّبِيَّ صلى الله عليه وسلم قَالَ ‏ “‏ مَنْ حَفِظَ عَشْرَ آيَاتٍ مِنْ أَوَّلِ سُورَةِ الْكَهْفِ عُصِمَ مِنَ الدَّجَّالِ ‏”‏
ሱነን አቢ ዳውድ መጽሐፍ 21, ሐዲስ 33
ነብዩም”ﷺ” አሉ፦ “ሱረቱል ያሲንን” በሟቻችሁ ላይ ቅሩ።
قَالَ النَّبِيُّ صلى الله عليه وسلم ‏ “‏ اقْرَءُوا ‌‏ يس عَلَى مَوْتَاكُمْ ‏”

የቁርአን ሱራህ እያንዳንዱ ስም በውስጡ ይገኛል ከሶስት ሱራዎች በስተቀር፤ እነርሱም፦ ሱረቱል ኢኽላስ፣ ሱረቱል አንቢያ እና ሱረቱል ፋቲሃ ናቸው፤ እነዚህ ሱራዎች ውስጣቸው ባለው ትርጉም ተሰይመዋል፤ ሌላው 111 ሱራዎች ስማቸው በውስጣቸው ይገኛል፤ ዝርዝሩን ኢንሻላህ በክፍል ሁለት ይዤ እቀርባለው።

@ከወሒድ ዐቃቢ ኢሥላም

ጥሪያችን በሁሉም ቦታ!
Follow us on:👇🏻
Telegram ፦ https://www.tg-me.com/tiriyachen
Website ፦ https://tiriyachen.org
Instagram ፦ https://bit.ly/3eVixKv
TikTok ፦ https://www.tiktok.com/@tiriyachen

ወሰላሙ አለይኩም
የቁርአን ሱራህ

▪️ክፍል ሁለት

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡

የቁርአን ሱራህ እያንዳንዱ ስም በውስጡ ይገኛል ከሶስት ሱራዎች በስተቀር፤ እነርሱም፦ ሱረቱል ኢኽላስ፣ ሱረቱል አንቢያ እና ሱረቱል ፋቲሃ ናቸው፤ እነዚህ ሱራዎች ውስጣቸው ባለው ትርጉም ተሰይመዋል፤ ሌላው 111 ሱራዎች ስማቸው በውስጣቸው ይገኛል፤ ይህንን ዝርዝር እንመልከት፦

▪️“በቀራህ”
“በቀራህ” بَقَرَةٌ ማለት “ላም” ወይም “ጊደር” ማለት ሲሆን ሁለተኛው ሱራህ ነው፤ ይህም ስም በዚህ አንቀፅ ይገኛል፦
2፥68 «ለኛ ጌታህን ጠይቅልን፤ እርሷ ምን እንደኾነች ዕድሜዋን ያብራራልን» አሉ፡፡ «እርሱ እርሷ ያላረጀች ጥጃም ያልኾነች በዚህ መካከል ልከኛ የኾነች *ጊደር* بَقَرَةٌ ናት ይላችኋል፤

▪️“ዒምራን”
“አለ-ዒምራን” َءَالَ عِمْرَٰنَ ማለት “ኢያቄም” ማለት ሲሆን የማርያም አባት ስም ነው፤ *የዒምራንንም ቤተሰብ* ማለት ነው፤ ይህም ሶስተኛው ሱራህ ሲሆን ይህ ስም በዚህ አንቀፅ ይገኛል፦
3፥33 አላህ አደምን፣ ኑሕንም፣ የኢብራሂምንም ቤተሰብ፣ *የዒምራንንም ቤተሰብ* وَءَالَ عِمْرَٰنَ በዓለማት ላይ መረጠ፡፡

▪️“ኒሳእ”
“ኒሳእ” النِّسَاءَ ማለት “ሴቶች” ማለት ሲሆን አራተኛው ሱራህ ነው፤ ይህም ስም በዚህ አንቀፅ ይገኛል፦
4፥4 *ሴቶችንም* النِّسَاءَ መህሮቻቸውን በደስታ ስጡ፡፡ ለእናንተም ከእርሱ አንዳችን ነገር ነፍሶቻቸው ቢለግሱ መልካም ምስጉን ሲኾን ብሉት፡፡

▪️“ማኢዳህ”
“ማኢዳህ” مَائِدَةً ማለት “ማእድ” ወይም “ገበታ” ማለት ሲሆን አምስተኛው ሱራህ ነው፤ ይህም ስም በዚህ አንቀፅ ይገኛል፦
5፣112 ሐዋርያት፡- «የመርየም ልጅ ዒሳ ሆይ! ጌታህ በእኛ ላይ ከሰማይ *ማእድን* مَائِدَةً ሊያወርድልን ይችላልን» ባሉ ጊዜ አስታውስ፡፡ «ምእመናን እንደ ኾናችሁ አላህን ፍሩ» አላቸው፡፡

▪️“አንአም”
“አንአም” أَنْعَٰمٌۭ ማለት *”የቤት እንስሳ”* ማለት ሲሆን ስድስተኛው ሱራህ ነው፤ ይህም ስም በዚህ አንቀፅ ይገኛል፦
6፥138 በሐሳባቸውም ይህች እርም የኾነች *”ለማዳ እንስሳ”* أَنْعَٰمٌۭ እና አዝመራ ናት፡፡ የምንሻው ሰው እንጂ ሌላ አይበላትም፡፡

▪️“አዕራፍ”
“አዕራፍ” الْأَعْرَافِ ማለት *”ኮረብታ”* ማለት ሲሆን ሰባተኛው ሱራህ ነው፤ ይህም ስም በዚህ አንቀፅ ይገኛል፦
7፤46 በመካከላቸውም ግርዶሽ አልለ፡፡ *በአዕራፍም* الْأَعْرَافِ ላይ ሁሉንም በምልክታቸው የሚያውቁ ሰዎች አልሉ፡፡ የገነትንም ሰዎች ሰላም ለናንተ ይኹን በማለት ይጣራሉ፡፡ እነርሱም የሚከጅሉ ሲኾኑ ገና አልገቧትም፡፡

▪️“አንፋል”
“አንፋል” الْأَنفَالِ ማለት *”ምርኮ”* ማለት ሲሆን ስምንተኛው ሱራህ ነው፤ ይህም ስም በዚህ አንቀፅ ይገኛል፦
8:1 *ከምርኮ* الْأَنفَالِ ይጠይቁሃል፡፡ «የዘረፋ ገንዘቦች የአላህና የመልክተኛው ናቸው፡፡» ስለዚህ አላህን ፍሩ፡፡ በመካከላችሁ ያለችውንም ኹኔታ አሳምሩ፡፡ አማኞችም እንደኾናችሁ አላህንና መልክተኛውን ታዘዙ በላቸው፡፡

▪️“ተውባህ”
“ተውባህ” تَوْبَة ማለት *”ፀፀት”* ወይም “ንስሃ” ማለት ሲሆን ዘጠነኛው ሱራህ ነው፤ ይህም ስም በዚህ አንቀፅ ይገኛል፦
2፥102 ሌሎችም በኃጢአቶቻቸው የተናዘዙ መልካም ሥራንና ሌላን መጥፎ ሥራ የቀላቀሉ አልሉ፡፡ አላህ “ከእነሱ ጸጸታቸውን” يَتُوبَ عَلَيْهِمْ ሊቀበል ይከጀላል፡፡ አላህ መሓሪ አዛኝ ነውና፡፡

▪️ዩኑስ”
“ዩኑስ” يُونُسَ ማለት የአላህ ነብይ ሲሆን አስረኛው ሱራህ ነው፤ ይህም ስም በዚህ አንቀፅ ይገኛል፦
10:98 ያመነችና እምነትዋ የጠቀማት ከተማ ለምን አልኖረችም ግን *የዩኑስ* يُونُسَ ሕዝቦች ባመኑ ጊዜ በቅርቢቱ ሕይወት የውርደትን ቅጣት ከእነሱ ላይ አነሳንላቸው፡፡ እስከ ጊዜም ድረስ አጣቀምናቸው፡፡

▪️“ሁድ”
“ሁድ” هُودُ ማለት የአላህ ነብይ ሲሆን አስራ አንደኛው ሱራህ ነው፤ ይህም ስም በዚህ አንቀፅ ይገኛል፦
11:53 አሉ፡- «*ሁድ* هُودُ ሆይ! በአስረጅ አልመጣህልንም፡፡ እኛም ላንተ ንግግር ብለን አማልክቶቻችንን የምንተው አይደለንም፡፡ እኛም ለአንተ አማኞች አይደለንም፡፡

▪️“ዩሱፍ” ”
ዩሱፍ” يُوسُفُ ማለት የአላህ ነብይ ሲሆን አስራ ሁለተኛው ሱራህ ነው፤ ይህም ስም በዚህ አንቀፅ ይገኛል፦
12:4 *ዩሱፍ* يُوسُفُ ለአባቱ፡- «አባቴ ሆይ! እኔ ዐስራ አንድ ከዋክብትን ፀሐይንና ጨረቃንም በሕልሜ አየሁ፡፡ ለእኔ ሰጋጆች ሆነው አየኋቸው» ባለ ጊዜ አስታውስ፡፡

▪️“ረዕድ”
“ረዕድ” الرَّعْدُ ማለት *ነጎድጓድም* ማለት ሲሆን አስራ ሶስተኛው ሱራህ ነው፤ ይህም ስም በዚህ አንቀፅ ይገኛል፦
13 ፣13 *ነጎድጓድም* الرَّعْدُ አላህን በማመስገን ያጠራል፡፡ መላእክትም እርሱን ለመፍራት ያጠሩታል፡፡

▪️“ኢብራሂም”
“ኢብራሂም” إِبْرَاهِيمُ ማለት የአላህ ነብይ ሲሆን አስራ አራተኛው ሱራህ ነው፤ ይህም ስም በዚህ አንቀፅ ይገኛል፦
14፣35 *ኢብራሂምም* إِبْرَاهِيمُ ባለ ጊዜ አስታውስ «ጌታዬ ሆይ! ይህንን አገር (መካን) ጸጥተኛ አድርገው፡፡ እኔንም ልጆቼንም ጣዖታትን ከመገዛት አርቀን፡፡

▪️“ሂጅር”
“ሂጅር” الْحِجْرِ ማለት *የሸለቆ ስም* ሲሆን አስራ አምስተኛው ሱራህ ነው፤ ይህም ስም በዚህ አንቀፅ ይገኛል፦
15: 80 *የሒጅርም* الْحِجْرِ ሰዎች መልክተኞቹን በእርግጥ አስተባበሉ፡፡

▪️“ነሕል”
“ነሕል” النَّحْلِ ማለት *ንብ* ማለት ሲሆን አስራ ስድስተኛው ሱራህ ነው፤ ይህም ስም በዚህ አንቀፅ ይገኛል፦
16፣68 ጌታህም ወደ *ንብ* النَّحْلِ እንዲህ ሲል አስታወቀ «ከተራራዎች፣ ከዛፍም፣ ሰዎች ከሚሠሩትም ቀፎ ቤቶችን ያዢ፡፡

▪️“ኢስራእ”
“ኢስራእ” أَسْرَىٰ ማለት *ጉዞ* ማለት ሲሆን አስራ ሰባተኛው ሱራህ ነው፤ ይህም ስም በዚህ አንቀፅ ይገኛል፦
17፣1 ያ ባሪያውን ከተከበረው መስጊድ ወደዚያ ዙሪያውን ወደ ባረክነው ወደ ሩቁ መስጊድ በሌሊት ውስጥ “ያስኼደው” أَسْرَىٰ ጌታ ጥራት ይገባው፡፡ ከተዓምራቶቻችን ልናሳየው አስኼድነው፡፡ እነሆ እርሱ አላህ ሰሚው ተመልካቺው ነው፡፡

▪️“ከህፍ”
“ከህፍ” الْكَهْفِ ማለት *ዋሻ* ማለት ሲሆን አስራ ስምንተኛው ሱራህ ነው፤ ይህም ስም በዚህ አንቀፅ ይገኛል፦
18:9 *የዋሻው* الْكَهْفِ እና የሰሌዳው ባለቤቶች ከተዓምራቶቻችን ሲሆኑ ግሩም መሆናቸውን አሰብክን?

▪️“መርየም”
“መርየም” مَرْيَمَ ማለት “የኢሳ እናት” ስትሆን አስራ ዘጠነኛው ሱራህ ነው፤ ይህም ስም በዚህ አንቀፅ ይገኛል፦
19፣16 በመጽሐፉ ውስጥ *መርየምንም* ከቤተሰቧ ወደ ምሥራቃዊ ስፍራ በተለይች ጊዜ አውሳ፡፡

▪️“ጧሃ”
“ጧሃ” طه ማለት ከሃያ ዘጠኙ ሃርፎች አንዱ ሲሆን ሃያኛው ሱራህ ነው፤ ይህም ስም በዚህ አንቀፅ ይገኛል፦
20:1 ጠ.ሀ. *ጧሃ* طه

ኢንሻላህ ይቀጥላል….

✍🏻ከወሒድ ዐቃቢ ኢሥላም

የበለጠ ለማወቅ
ጥሪያችን Tiriyachen

ወሰላሙ አለይኩም
የቁርአን ሱራህ
ሁሉም ክፍሎች ተለቀዋል
👇🏻👇🏻👇🏻👇🏻👇🏻👇🏻

📍ክፍል አንድ https://www.facebook.com/share/p/1GQH3f1egH/
📍ክፍል ሁለት
https://www.facebook.com/share/p/151k5uyne2Y/
📍ክፍል ሶስት
https://www.facebook.com/share/p/16YTfdmx3q/
📍ክፍል አራት
https://www.facebook.com/share/p/1EjvP6LPcX/

📍የመጨረሻ ክፍል
https://www.facebook.com/share/p/15PYcuyUxF/
ሐጅ በባይብል

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡

22፥27 አልነውም፦ "በሰዎችም ውስጥ በሐጅ ትእዛዝ ጥራ!፡፡ وَأَذِّن فِي النَّاسِ بِالْحَجِّ يَأْتُوكَ رِجَالًا

"ሐጅ" حَجّ የሚለው ቃል "ሐጀ" حَجَّ ማለትም "ጎበኘ" ከሚል ሥርወ-ቃል የተገኘ ሲሆን "ጉብኝት" ማለት ነው፥ አምላካችን አሏህ ለኢብራሂም፦ "በሰዎችም ውስጥ በሐጅ ትእዛዝ ጥራ" አለው፦
22፥27 አልነውም፦ "በሰዎችም ውስጥ በሐጅ ትእዛዝ ጥራ!፡፡ وَأَذِّن فِي النَّاسِ بِالْحَجِّ يَأْتُوكَ رِجَالًا

በባይብል ደግሞ "ኸግ" חַג የሚለው ቃል "ኸገግ" חָגַג ማለትም "ጎበኘ" "ከበበ" ከሚል ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን "ጉብኝት" ማለት ነው፦
ዘጸአት 10፥9 "ሙሴም፦ "ለያህዌህ "ኸግ" ልናደርግ ስለሆነ ወጣቶቻችንን እና ሽማግሌዎቻችንን፣ ወንዶች እና ሴቶች ልጆቻችን፣ በጎቻችንን እና ከብቶቻችንን ይዘን እንሄዳለን" አለ። וַיֹּ֣אמֶר מֹשֶׁ֔ה בִּנְעָרֵ֥ינוּ וּבִזְקֵנֵ֖ינוּ נֵלֵ֑ךְ בְּבָנֵ֨ינוּ וּבִבְנֹותֵ֜נוּ בְּצֹאנֵ֤נוּ וּבִבְקָרֵ֙נוּ֙ נֵלֵ֔ךְ כִּ֥י חַג־יְהוָ֖ה לָֽנוּ׃
ዘጸአት 12፥14 ይህም ቀን መታሰቢያ ይሁናችሁ፥ ለያህዌህ "ኸግ" ታደርጉታላችሁ፤ ለልጅ ልጃችሁ ሥርዓት ሆኖ ለዘላለም ታደርጉታላችሁ። וְהָיָה֩ הַיֹּ֨ום הַזֶּ֤ה לָכֶם֙ לְזִכָּרֹ֔ון וְחַגֹּתֶ֥ם אֹתֹ֖ו חַ֣ג לַֽיהוָ֑ה לְדֹרֹ֣תֵיכֶ֔ם חֻקַּ֥ת עֹולָ֖ם תְּחָגֻּֽהוּ׃

በብዙ ትርጉም ላይ "በዓል"feast" ተብሎ የተቀመጠው ቃል በዕብራይስጡ "ጉብኝነት"pilgrim" ነው፥ "ኹግ" חוּג ማለት እራሱ "ኸገግ" חָגַג ማለትም "ከበበ" ከሚል ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን "ክበብ" ማለት ነው። ጥንት ለዘላለም የተሰጣቸው የጉብኝነት በዓል በመዞር ያረጉት ነበር፥ በአይሁዳውያን በዓመት ሦስት ጊዜ የዳስ በዓል፣ በዓለ ኃምሳ እና ፋሲካ ሊያከብሩ ሲሉ በወሩ ከ 15 እስከ 21 ለሥድስት ወይም ለሰባት ቀን ሲጎበኙ ይዞራሉ። "ሱካህ" סוכה ማለትም "ድንኳን" ማለት ሲሆን ድንኳኑን የሚዞሩት ዙረት "ሐካፋህ" ይባላል። "ሐካፋህ" הקפה ማለት "ዙረት" ማለት ሲሆን የሚዞሩት ሰባት ጊዜ ስለሆነ "ሐካፉት" הקפות ይሉታል፥ ይህም በሚንሃግ፣ በሚድራሽ እና በባቢሎን ታልሙድ ተዘግቧል። አሏህ ሐጅ ከሚያደርጉት ሑጃጆች ያድርገን! አሚን።

ከወሒድ ዐቃቢ ኢሥላም

ጥሪያችን በሁሉም ቦታ!
Follow us on:👇🏻
Telegram ፦ https://www.tg-me.com/tiriyachen
Website ፦ https://tiriyachen.org
Instagram ፦ https://bit.ly/3eVixKv
TikTok ፦ https://www.tiktok.com/@tiriyachen

ወሠላሙ ዐለይኩም
2025/07/05 16:40:14
Back to Top
HTML Embed Code: