ክርክር የለኝም፡፡ ከሁሉም በላይ ደግሞ ጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ (ዶ/ር) ለአቶ ኃይለ ማርያም ስለተደረገው አሸኛኘትና ስለተሰጠው ሽልማት በሐዋሳ በዚያው ሰሞን ባደረጉት ንግግር ውስጥ ያነሱትንና ያቀረቡትን ምክንያት በሚገባ እረዳለሁ፡፡ የአገራችን የለውጥ መንኮራኩር የሚጠይቀው ግራሶ እንዳለም አውቃለሁ፡፡

የኢትዮጵያ መንግሥት የመንግሥት ወይም የአገር መሪዎች ኒሻንና ሜዳሊያ የመስጠት የአገርን ባለውለታነት በክብር የመግለጽና የማረጋገጥ ትክል ሥልጣን (ሕገ መንግሥቱ ውስጥ ባይኖር እንኳን) እንዳላቸው አውቃለሁ፡፡ ጥያቄው ግን ኢትዮጵያን የመሰለች ከዚህ በላይ አንደተባለው፣ ‹‹… በዓለም ላይ የሚገኙ የሠለጠኑ መንግሥታት እንደሚያደርጉት ሁሉ) ሳይሆን፣ ለእነሱ ጭምር ትምህርት የሰጠች የተቋቋመ የሚያስቀና (Honour System) የነበራት አገር እንዴት አድርጋ ይህን ጎዶሎ ይዛ ትኑር? እንዴትስ ይህን ዝግጁነት የሚያመለክት ባለሥልጣንና ባለ አገር ትጣ? ይህ ጎዶሎ በገዛ ራሱ ምክንያት ካለው አሉታዊ ውጤትና ጉዳት ይልቅ፣ ዛሬ በዚህ ጊዜ የለውጥ ተቀናቃኞች ‹‹ሕገ መንግሥት ተጣሰ›› የሚል ዱላ ሆኖ ሲያገለግልም ዓይተናል፡፡

የዴሞክራሲው ለውጥ በደረሰበት ደረጃ ልክ ቆንጠጥና ጠበብ አድርገን በጥንቃቄ እንድንረማመድ መገደዳችን ሳያንስ፣ እንዲህ ያሉ ክፍተቶችን ዝም ብለን እያየን የለውጡ ተቀናቃኞች የጭቃ ጅራፍ እንዲሆኑ መፍቀድ የለብንም፡፡

የሕገ መንግሥቱ ድንጋጌዎች የሪፐብሊኩ ፕሬዚዳንት በሕግ መሠረት ኒሻኖችንና ሽልማቶችን ይሰጣል (አንቀጽ 71/5)፣ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ደግሞ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በሚያወጣው ሕግ ወይም በሚሰጠው ውሳኔ መሠረት ኒሻኖችንና ሽልማቶችን ለፕሬዚዳንቱ አቅርቦ ያሰጣል በማለት ይደነግጋሉ፡፡ ሁለቱም ድንጋጌዎች ውስጥ ‹‹ኒሻኖችና ሽልማቶች››ን በእንግሊዝኛው “Medals, Prizes and Gifts” ብሎ ውንብድብዱን ቢያወጣውም፣ የአገርን ባለውለታነት የማረጋገጥ የክብር ሥራ አስቀድሞ የወጣ ዝርዝር ሕግ የግድ ይፈልጋል፡፡ ኢትዮጵያ በዚህ ረገድ የውጭ ተሞክሮ መቅሰም ያለባት አገር አይደለችም፡፡ የዓለም ሙዚየሞች የሚያውቁት የተቋቋመ የባለውለታነት ዕዳ መመስከሪያ የሽልማትና የማዕረግ ሥርዓት የነበራት አገር ናት፡፡

አገር በየመስኩ አስተዋጽኦ ላደረጉላትና መስዋዕት ለሆኑላት ወይም ለከፈሉላት ባለውለታነቷን ማረጋገጥ ውለታቸውን ማወቅ፣ ማሰብ፣ ማስታወስና ለወደፊቱም እንዲበረታቱ ማድረግ ያለባት መሆኑ የአገር የውለታ ባለዕዳነት ከሚረጋገጥባቸው መንገዶች፣ ከመስዋዕትነቱና ከአስተዋጽኦው ጋር ተመጣጣኝ የሆነ የሜዳልያና የኒሻን ሽልማት መስጠት እንደሆነ የታወቀ ነው፡፡ ሲወርድ ሲወራረድ የመጣም የመንግሥት አሠራር ነበር፡፡ በዚህ በተያያዝነው የዴሞክራሲና የለውጥ ወቅት ጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይም ከአንድ ሁለት ጊዜ ተሰናባች የአገርና የመንግሥት መሪዎችን በሸኙበት ወቅት ተገልግለውበታል፡፡ ወይም የአገልግሎቱን አስፈላጊነት በተግባር አረጋግጠዋል፡፡ በሚያዝያ 2010 ዓ.ም እና በጥቅምት 2011 ዓ.ም. ጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ (ዶ/ር) የሚመሩት መንግሥት የአገርን የውለታ ባለዕዳነት ልወጣ ሲል ግን፣ አገር አስቀድሞ የተዘጋጀ በሕገ መንግሥቱ አንቀጽ 71(5) እና 74(11) መሠረት ስንዱ ሆኖ የሚጠብቅ፣ በተለይም የሲቪል የሜዳይና የኒሻን ሥርዓት አልነበራትም፡፡ ‹‹የሽልማት፣ የአድናቆትና የአክብሮት ሰርተፊኬት››፣ ‹‹የሻኒን አዋርድና ከፍተኛ የክብር ዲፕሎማ›› ‹‹የአገሪቱ ከፍተኛ የክቡር ዲፕሎማ›› ማለት ዓይነት ‹‹መቀባጠር››ም የመጣው ጉዳዩ የቢሻኝ ውሳኔ በመሆኑ ነው፡፡

የቢሻኝ ውሳኔ የሆነው መሸለሙ አይደለም፡፡ መሸለም የአገርና የመንግሥት ትክል (Inherent) ሥልጣኑ ነው፡፡ ዝርዝሩ ግን በሕግ መደንገግ አለበት፡፡ ከሁሉም በላይ፣ ከሌሎች መካከል በሕግ መደንገግ ያለበት የሽልማት ቅርፅ (በዝርዝር)፣ መጠንና አካል (ወርቅ፣ ወርቃማ፣ ወዘተ) አስቀድሞ በወጣ ሕግ ይወሰናል፡፡ ሜዳሊያና ኒሻን በትዕዛዝ የሚሠራ እንጂ የ‹‹አውርድልኝ›› ዕቃ አይደለም፡፡ መንግሥት ይህን ማስተካከልና ይህንን ጎዶሎ መሙላት አለበት፡፡

መንግሥት ይህን ማድረግ ያለበት ከ‹‹አውርድልኝ›› ዕቃ በዕውቅ የሚሠራ ዕቃ ይሻላል ተብሎ ብቻ አይደለም፡፡ በተሻላሚው ሰው አንገት ላይ በአደባባይ ሲጠለቁ የምናያቸው ሜዳይና ኒሻን መሳይ ቁሳቁሶች መጀመርያ የወንጀል ሕግ ጥበቃ የሚያገኙት (ከመንግሥት ፈቃድ ሳይሰጥ ሜዳይ፣ ኒሻን፣ ዓርማና ሪባን መሥራት፣ መጠቅምና አስመስሎ መሥራት ወንጀል) በሕግ ሲወሰን ነው፡፡ የሕገ መንግሥቱ አንቀጽ (የመንግሥትና የሃይማኖት መለያዎች ድንጋጌ) ተጣሰ የሚለው ስሞታም ሆነ ክስ የሥር የመሠረት መከላከያም የሜዳዩን ዓይነት፣ ቅርፅና አካል አስቀድሞ በሕግ በመወሰን ነው፡፡

ይህን ጎዶሎ ከመሙላት ጋር ሌላም መፈጸም ያለበት ሌላ ጉዳይ አለ፡፡ በተለያዩ  ዘመናት በየትግል ዘርፉ ባለውለታ ሆነው የተከበሩና የተሾሙ ኢትጵያውያን (የውጭ አገር ዜጎችም አሉ)፣ መንግሥት በተለዋወጠ ቁጥር ባለውለታነታቸው እንደ ቆሻሻ የሚደፋበትና የሚደመሰስበት ያልተጻፈ ባህልና ሕግ አንድ ሊባል ይገባል፡፡     

ከአዘጋጁ፡- ጽሑፉ የጸሐፊዋን አመለካከት ብቻ የሚያንፀባርቅ መሆኑን እንገልጻለን፡፡

The post አገር ባለውለታነቷን የምታረጋግጥበት ሥርዓታችንን እንፈትሽ! first appear on ሪፖርተር - Ethiopian Reporter - #1 Best and reliable news source in Ethiopia and is written by አንባቢ
የግብጽ ልኡክ ቡድን በተኩስ አቁም እና ታጋቾች ጉዳይ ለመነጋገር እስራኤል መግባቱ ተነገረ
جديد አል ዐይን ኒውስ (RSS)

የግብጽ የልኡክ ቡድን በትናንትናው እለት ከእስራኤል አቻው ጋር ተገናኝቶ የጋዛ ተኩስ አቁም ንግግር ስለሚጀመርበት ሁኔታ ተወያይቷል
አሜሪካ ለዩክሬን ተጨማሪ “ፓትሪዮት ሚሳኤል ስርአት” ልትልክ ነው
جديد አል ዐይን ኒውስ (RSS)

ዩክሬን የአሜሪካ ድጋፍ መዘግየት ሩሲያ ተጨማሪ የኬቭ መሬቶችን እንድትይዝ ያደርጋታል የሚል ስጋቷን ገልጻለች
ፍልስጤማውያን አትሌቶች በፓሪሱ ኦሎምፒክ እንዲሳተፉ ይጋበዛሉ - አለማቀፉ የኦሎምፒክ ኮሚቴ
جديد አል ዐይን ኒውስ (RSS)

አለማቀፉ የኦሎምፒክ ኮሚቴ በሩሲያ ላይ ያሳለፈውን ውሳኔ በእስራኤል ላይ አለመድገሙ ቅሬታ አስነስቶበታል
ሆላንዳዊው አርኔ ስሎት በሊቨርፑል የርገን ክሎፕን ለመተካት ተስማሙ
جديد አል ዐይን ኒውስ (RSS)

ፌኖርድ የ2022/23 የኢርዲቪዜ ዋንጫን እንዲያነሳ ያደረጉት ስሎት ወጣት ተጫዋቾችን በማብቃት ይታወቃሉ
የሀውቲ ታጣቂዎች በቀይ ባህር በነዳጅ ጫኝ መርከብ ላይ ጥቃት አደረሱ
جديد አል ዐይን ኒውስ (RSS)

የአሜሪካ ማሪን አድሚኒስትሬሽን የሀውቲ ታጣቂዎች ከባለፈው ህዳር ወር ጀምሮ በመርከቦች ላይ 50 ጥቃቶችን ሰንዝረዋል ብሏል
ሳንዶካን ደበበ የጠቅላይ ሚኒስትር ልዩ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ሆነው ተሾሙ
Addis Maleda (RSS)

ረቡዕ ጥቅምት 28 ቀን 2016 (አዲስ ማለዳ) ላለፈው አንድ ዓመት በፕላን እና ልማት ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ሆነው ሲሰሩ የቆዩትሳንዶካን ደበበ፤ የጠቅላይ ሚኒስትር ልዩ ጽህፈት ቤት ኃላፊ (chief of staff) ሆነው ተሾሙ።

ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ በሚኒስትር ዴኤታ ማዕረግ የልዩ ጽህፈት ቤታቸውን እንዲመሩ ሳንዶካንን የሾሟቸው፤ ከሦስት ሳምንት በፊት መሆኑን ለጉዳዩ ቅርበት ያላቸው ምንጮች ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ተናግረዋል።

ልዩ ጽህፈት ቤቱ በጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት ሥር ካሉ ስድስት መዋቅሮች አንዱ ነው። በጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት ሥር ያሉ ሌሎች መዋቅሮች የብሔራዊ ደህንነት ምክር ቤት፣ የቀዳማዊት እመቤት ጽህፈት ቤት፣ የፕሬስ ሴክሪተሪያት፣ የፖሊሲ እና የአፈጻጸም ክትትል ክፍል እንዲሁም የሪፐብሊኩ ጠባቂ ናቸው።

ሳንዶካን ልዩ ጽህፈት ቤቱን እንዲመሩ ከተሾሙ በኋላ ከጠቅላይ ሚኒስትር አብይ ጋር የመጀመሪያ የውጭ ጉዟቸውን ወደ ቻይና ማድረጋቸውንም ምንጮች ገልጸዋል። ሹመቱንም ሆነ የቻይናውን ጉዞ ሳንዶካን ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” አረጋግጠዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ ወደ ስልጣን እንደመጡ የልዩ ጽህፈት ቤታቸው ኃላፊ አድርገው በመጀመሪያ የሾሟቸው አሁን በካናዳ የኢትዮጵያ አምባሳደር የሆኑትን ፍጹም አረጋን ነው። እርሳቸውን በመተካት የጽህፈቱ ቤት ኃላፊ የሆኑት በአሁኑ ወቅት የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር የሆኑት ሽመልስ አብዲሳ ናቸው። ሽመልስ በሚያዝያ 2011 ለማ መገርሳን በመተካት የኦሮሚያ ክልልን እንዲመሩ ከመሾማቸው በፊት፤ በጠቅላይ ሚኒስትር ልዩ ጽህፈት ቤት በኃላፊነት ለሰባት ወራት ሰርተዋል።

ከግንቦት 2011 ጀምሮ ልዩ ጽህፈት ቤቱን ለስምንት ወራት በኃላፊነት ሲመሩ የቆዩት፤ በኢኖቬሽን እና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ የነበሩት ዶ/ር ሹመቴ ግዛው ሲሆን፤ ዶ/ር ሹመቴ ከልዩ ጽህፈት ቤት ኃላፊነታቸው ተነስተው የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር (ኢንሳን) በዋና ዳይሬክተርነት እንዲመሩ በጥር 2012 ሲሾሙ በምትካቸው በቦታው የተመደቡት መስፍን መላኩ ናቸው።

መስፍን በየካቲት 2015በኦሮሚያ ክልል በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የከተማ ክላስተር አስተባባሪ ሆነው ከተሾሙ በኋላ የኃላፊነት ቦታውን ተረክበው የነበሩት በጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት የውጭ ግንኙነት ፖሊሲ አማካሪነት ሲሰሩ የነበሩት መሐመድ ራፊ አባራያ መሆናቸውን ምንጮች ገልጸዋል። አዲሱ ተሿሚ ሳንዶካን ወደ ልዩ ጽህፈት ቤት ኃላፊነት ከመምጣታቸው በፊት፤ በተለያዩ የመንግስት ተቋማት ላለፉት 12 ዓመታት ሰርተዋል።

ሳንዶካን በፕላን እና ልማት ሚኒስቴር የነበራቸው ኃላፊነት፤ በአካባቢ ጥበቃ፣ የአየር ንብረት እና የስነ ህዝብ ጉዳዮች ላይ “ፖለቲካዊ አመራር” መስጠት መሆኑን በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው አስፍረዋል። ሳንዶካን በሚኒስቴሩ በነበራቸው ቆይታ የአየር ንብረትን በተመለከቱ ዓለም አቀፋዊ ስብሰባዎች ላይ ኢትዮጵያን በመወከል በተደጋጋሚ ተገኝተዋል።
ኢትዮጵያ በመላ አገሪቱ አንድ ሺሕ የሕዝብ መጸዳጃ ቤቶችን ልትገነባ ነው ተባለ
Addis Maleda (RSS)

ሐሙስ ጥቅምት 29 ቀን 2016 (አዲስ ማለዳ) ኢትዮጵያ በ23 ከተሞች የውሃ አያያዝና አቅርቦትን ለማሻሻል የ523 ሚሊዮን ዶላር ፕሮጀክት መጀመሯ የተገለጸ ሲሆን፤ ይህም ፕሮጀክት በመላ አገሪቱ 1 ሺሕ የሕዝብ መጸዳጃ ቤቶች መገንባትን እንደሚያካትት ተነግሯል፡፡

ለዚሁ ፕሮጀክት ማስፈጸሚያም የዓለም ባንክ የ460 ሚሊየን ዶላር ድጋፍ ያደረገ ሲሆን ቀሪውን 63 ሚሊየን ዶላር ደግሞ በሌሎች ለጋሽ ተቋማት ይሸፈናል ተብሏል።

ፕሮጀክቱ በሰሜኑ ጦርነት ጉዳት የደረሰባትን የመቀሌ ከተማ የሚያካትት መሆኑን አዲስ ማለዳ ከአለም አቀፍ ኮንስትራክሽን ሪቪዉ ያገኘችዉ መረጃ ያመላክታል፡፡

ኢትዮጵያ በከተማዋ የውሃ መሰረተ ልማቶችን ለማዳረስ እንዲሁም የኤሌክትሪክ ፓምፖች ለመግዛት 1 ሚሊየን ዶላር ወጪ ማድረጓም ተነግሯል፡፡

በፈረንጆቹ 2018 ግሎባል ዋተር ኢንተለጀንስ የተሰኘው ተቋም አደረኩት ባለው ጥናት መሰረት፤ በአገሪቱ ዘመናዊ መጸዳጃ የሚጠቀሙ የከተማ ነዋሪዎች 12 በመቶ ብቻ መሆናቸውን አመላክቷል።
በደቡብ ወሎ ዞን ያለው የጸጥታ ችግር በማዕድን ሐብት ልማት ላይ ከፍተኛ ተጽዕኖ ማሳደሩ
Addis Maleda (RSS)

ሐሙስ ጥቅምት 29 ቀን 2016 (አዲስ ማለዳ) በ2016 በ1ኛ ሩብ ዓመት በማዕድን ሐብት ልማት ለበርካታ ባለሐብቶች ፈቃድ ቢሰጥም፤ የጸጥታ ችግሩ ወደ ሥራ ለማስገባት ተጽዕኖ ማሳደሩን የደቡብ ወሎ ዞን ማዕድን ሐብት ልማት መምሪያ አስታውቋል፡፡

ሆኖም ግን 6 ሺሕ 532 ኪሎ ግራም ኦፓል ለውጭ ገበያ በማቅረብ ከ6 ሚሊየን ብር በላይ ገቢ መገኘቱን መምሪያው አመላክቷል፡፡

ደቡብ ወሎ የኦፓል፣ የድንጋይ ከሰል፣ የኦይል ሸል፣ የነዳጅ፣ የአምበር፣ የጃስፐር፣ የአጌት፣ የኦኒክስ፣ የቶርማሊን፣ የኳርቲዝ፣ የጅፕሰምና የሌሎች ከ30 በላይ የሚሆኑ ማዕድናት ባለቤት ስለመሆኑ ተረጋግጧል” ያሉት የዞኑ ማዕድን ሐብት ልማት መምሪያ ኃላፊ አህመድ አበባው፤ እነዚህንም የኢነርጂ፣ የጌጣጌጥና የኢንዱስትሪ ማዕድናት በሩብ ዓመቱ የመለየት ሥራ መከናወኑን አብራርተዋል፡፡

በዚህም ለ84 ባለሐብቶች አነስተኛ የማዕድን ሥራ ፈቃድ መሰጠቱን የተናገሩት የመምሪያው ኃላፊው፤ ከነዚህ ውስጥ 47 የሚሆኑት በሥራ ሂደት ላይ የሚገኙ ሲሆን፤ 19 በሚሆኑት ላይ ደግሞ በተለያዩ ጥፋቶች ምክንያት ፈቃዳቸው እንዲሰረዝ መደረጉን ተናግረዋል፡፡ አክለውም 42 ባህላዊ የማዕድን ሥራ ፈቃድ መሰጠቱ በመግለጽ፤ በዚህም ለ428 ነዋሪዎች የሥራ ዕድል ተፈጥሯል ብለዋል፡፡

12 ከፍተኛ ክሬቸር የምርት ፈቃድ መሰጠቱንም በመግለጽ፤ አራቱ በጥሩ ደረጃ ላይ እንደሚገኙና ቀሪዎቹ ደግሞ በተለያዩ ችግሮች ምክንያት ወደ ሥራ አለመግባታቸውን መግለጻቸውን አዲስ ማለዳ ከዞኑ ኮሙኒኬሽን መምሪያ ያገኘችው መረጃ ያመላክታል፡፡

የመምሪያው ኃላፊ በዚህ ሂደት በተፈጠረው የጸጥታ ችግር ምክንያት በዘርፉ የሚፈለገውን ያህል መሥራት አለመቻሉን የገለጹ ሲሆን፤ መሬትን ከሦስተኛ ወገን ነፃ አለማድረግ፣ የብድር አቅርቦት አለመመቻቸት፣ የኤሌትሪክ ኃይል አቅርቦት አለመኖር ሌሎች ያጋጠሙ ችግሮች መሆናቸውም አብራርተዋል፡፡

በተያያዘ ዜና በተያዘው የ2016 በጀት ዓመት የኦፓል ምርትን ለውጭ ገበያ በመላክ ሰባት ሚሊዮን 200 ሺሕ የአሜሪካን ዶላር ገቢ ለማግኘት ታቅዶ፤ በሩብ ዓመቱ 324 ሺሕ 428 ዶላር ገቢ መገኘቱን የአማራ ክልል ማዕድን ሀብት ልማት ቢሮ አስታውቋል፡፡

በሩብ ዓመቱ 10 ሺሕ 959 ኪሎ ግራም የኦፓል ምርት ለውጭ ገበያ በመላክ ገቢው መገኘቱን የገለጸው ቢሮው፤ ይህም የኦፓል ምርት እሴት የተጨመረበትንና ያልተጨመረበትን የሚያካትት መሆኑን አመላክቷል፡፡

በተጨማሪም በተያዘው በጀት 18 ሺሕ 156 ኪሎ ግራም የኦፓል ምርት ለውጭ ገበያ በመላክ፤ ሰባት ሚሊዮን 200 ሺሕ የአሜሪካን ዶላር ገቢ ለማግኘት ታቅዶ እየተሠራ እንደሚገኝ ገልጿል።
የተባበሩት አረብ ኢሚሬትስ አዲስ ሊገነባ ለታቀደው ብሔራዊ የአረጋዊያን ማዕከል ግንባታ ድጋፍ እንደምታደርግ አስታወቀች
Addis Maleda (RSS)

ሐሙስ ጥቅምት 29 ቀን 2016 (አዲስ ማለዳ) የዩናይትድ አረብ ኢሚሬትስ አምባሳደር ሙሐመድ ሳሬም አልረሺዲ ከሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር ከፍተኛ አመራሮች ጋር ተወያይተዋል።

በውይይቱም የሴቶችና ማህራዊ ጉዳይ ሚኒስትር ክብርት ዶ/ር ኤርጎጌ ተስፋዬ፤ ለአረጋውያን የሕክምና፣ የገቢ ማስገኛና ኹለገብ አገልግሎቶችን መስጠት የሚያስችል ማዕከል ለመገንባት እየተሰራ መሆኑን ለአምባሳደሩ አብራርተዋል።

ደረጃውን የጠበቀ የአረጋውያን ማዕከል ለመገንባት የዲዛይን ሥራው ሙሉ በሙሉ ተጠናቅቆ ተግባራዊ እንቅስቃሴ ተጀምሯል ያሉት ሚኒስትሯ፤ ለግንባታው የተባበሩት አረብ ኢሚሬትስ መንግሥት ድጋፍ እንዲያደርግላቸው ጠይቀዋል።

በኢትዮጵያ የተባበሩት አረብ ኢሚሬትስ አምባሳደር ሙሐመድ ሳሬም አልረሺዲ የኢትዮጵያ መንግሥት በብሔራዊ ደረጃ ለሚያስገነባው የአረጋውያን ማዕከል ግንባታ የበኩሉን ድጋፍ እንደሚያደርግ አረጋግጠዋል።

አረጋውያንን ጨምሮ በአስቸጋሪ ኹኔታ ውስጥ የሚገኙ የኅብረተሰብ ክፍሎችን ሕይወት ለመለወጥና ለማሻሻል እየተከናወኑ ያሉ ተግባራትንም አምባሳደሩ አድንቀዋል።

መንግሥት የአገር ባለውለታ የሆነት አረጋውያን መብት ለማስከበር፣ ማህበራዊ ደህንነታቸውን ለማስጠበቅ እና የልማቱ ተሳታፊና ተጠቃሚ ለማድረግ የሚረዳ ብሔራዊ የማህበራዊ ጥበቃ ፓሊሲና የማስፈጸሚያ ስትራቴጂ በመንደፍ በሥራ ላይ ማዋሉን የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታውቋል።
በኢትዮጵያ የማህበረሰብ አቀፍ የጤና መድህን አገልግሎት ተጠቃሚዎች ቁጥር ከ54 ሚሊዮን በላይ መድረሱ ተገለጸ
Addis Maleda (RSS)

ሐሙስ ጥቅምት 29 ቀን 2016 (አዲስ ማለዳ) የማህበረሰብ አቀፍ የጤና መድህን አገልግሎት ተጠቃሚዎች ቁጥር ከ54 ሚሊዮን በላይ መድረሱን የኢትዮጵያ የጤና መድህን አገልግሎት አስታውቋል፡፡

የኢትዮጵያ የጤና መድህን አገልግሎት የ2015 በጀት ዓመት አፈጻጸም ግምገማና ውይይት እየተካሄደ ነው።

የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ዶክተር ደረጀ ዱጉማ በዚሁ ወቅት፤ በጤናው ዘርፍ ውጤታማ የለውጥ ሥራ መከናወኑን የተናገሩ ሲሆን፤ በተለይም የጤና ተደራሽነትና ጥራትን ለማሻሻል የተለያዩ ሥራዎች ተከናውነዋል ብለዋል፡፡

አካታችና ፍትሃዊ የጤና አገልግሎት ተደራሽነትን ለማሳካት ከተቀረጹ ሪፎርሞች መካከል አንዱ የጤና መድህን ስርዓት መሆኑን ገልጸዋል።

የጤና መድህን ስርዓት በጤናው ዘርፍ ላይ ከፍተኛ ለውጥ እያስገኘ መሆኑንም አመላክተዋል።

የኢትዮጵያ ጤና መድህን አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ተስፋዬ ወርቁ በበኩላቸው፤ የጤና መድህን ስርዓት ዓላማ ዜጎች አስቀድመው በሚከፍሉት መዋጮ የጤና እክል በሚያጋጥማቸው ወቅት ያለምንም የክፍያ ስጋት የሕክምና አገልግሎት እንዲያገኙ ማስቻል መሆኑን አንስተዋል።

በዚህም የማህበረሰብ አቀፍ የጤና መድህን ተጠቃሚዎች ቁጥር ከ54 ሚሊዮን በላይ መድረሱን ተናግረዋል።

ከዚህም ውስጥ 10 ሚሊዮን የሚሆኑት የመክፈል አቅም የሌላቸውና ዓመታዊ መዋጯቸው በመንግሥት የተሸፈነላቸው መሆኑን ጠቁመዋል።

በየደረጃው የሚገኙ አመራሮች ስርዓቱ እንዲጠናከር የመምራትና የመደገፍ ሂደት ከጊዜ ወደ ጊዜ እያደገ መምጣቱንም ጨምረው መግለጻቸውን ኢዜአ ዘግቧል፡፡
ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ “ፍርድ ቤቱ የሰጠኝ ውሳኔ ገጽ ጎድሎታል” አለ
Addis Maleda (RSS)

ሐሙስ ጥቅምት 29 ቀን 2016 (አዲስ ማለዳ) ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ “የመከላከያ ሠራዊቱን ምስጢር ማውጣት” እና ሠራዊቱን መከፋፈል” በሚሉ ክሶች ነፃ መባሉን በመቃወም ዐቃቢ ሕግ የግባኝ መጠየቁን ተከትሎ ፍርድ ቤቱ የሰጠው ውሳኔው እና ቅሬታው ሲደርሰው የጎደሉ ገጾች እንዳሉት ገልጿል።

በዚህም “ጠቅላይ ፍርድ ቤት የአቃቤ ሕግን 16 ገጽ የይግባኝ ማመልከቻ ሲሰጠኝ፣ ከፍርድ ቤቱ ትእዛዝ ጋር በተያያዘ የእኔን ምላሽ የሚሹ ገጾች ጎድለውታል” ብሏል።

“ክስተቱ አጋጣሚ ነው ብዬ አላምንም” ያለው ተመስገን ለዛሬ ጥቅምት 29/ 2016 በዋለው ችሎት የመልስ ማሻሻያ እንዲፈቀድለት በማመልከቻ ጠይቋል።

ይህንን ተከትሎ ዐቃቢ ሕግ በጉዳዩ ላይ አስተያየት መስጠት እንደሚፈልግ በመናገሩ፣ የጋዜጠኛው ጠበቆች “እኛ ስህተት ሰርቷል ያልነው ፍርድ ቤቱን እንጂ ዐቃቢ ሕግን አይደለም። ስለዚህም ዐቃቢ ሕግ በማይመለከተው ጉዳይ አስተያየት ሊሰጥ አይገባም” ሲሉ መቃወማቸውን አዲስ ማለዳ ለማወቅ ችላለች።

በዚህም ምክንያት በ2 ዳኞች የተሰየመው ፍርድ ቤት በጉዳዩ ላይ ውሳኔ ለመስጠት አንድ ዳኛ ስለሚጎድል በሚል ለሕዳር 11/2016 ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል።

ዛሬ ጥቅምት 29/2016 ማለዳ የተካሄደውን ችሎት አስመልክቶ አስተያየቱን የሰጠው ጋዜጠኛው፤ “ፍርድ ቤቱ አቃቤ ሕግ ከብይን በኋላ እጠይቃለሁ ያለውን ይግባኝ ሳይጠይቅ መፍቀዱ፣ አስገራሚ ብቻ ሳይሆን ትልቅ የሕግ ጥሰትም ነው” ሲል ቅሬታውን ገልጿል።

“የመከላከያ ሠራዊቱን ምስጢር አውጥተሃል”፣ “ሠራዊቱ እንዲከፋፈል አድርገሃል” እንዲሁም “የተቋሙን ሥም አጥፍተሃል” በሚሉ ሦስት ክሶች ከግንቦት 18/2013 እስከ ህዳር 7/2014 ድረስ እስር ቤት የቆየው ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ፤ ክሱን ሲመለከት በነበረው የከፍተኛው ፍርድ ቤት የካቲት 29/2015 ባስተላለፈው ውሳኔ በሙሉ ድምጽ በነጻ መሰናበቱ ይታወሳል፡፡

ሆኖም ዐቃቢ ሕግ ክሱ ሳይቋጭ ጥቅምት 21/2015 ለጠቅላይ ፍርድ ቤት ይግባኝ ሰሚ ችሎት በብይኑ ላይ ያቀረበው ይግባኝ ፍርድ ቤቱ ተቀብሎ፤ “ያስቀርባል” ሲል በመወሰኑ ይግባኙ በቀረበ በዓመቱ ጥቅምት 5/2016 ጉዳዩን ያየው ፍርድ ቤቱ ለውሳኔ ለዛሬ ጥቅምት 29/2016 ቀጥሮ ነበር፡፡
“በጦርነት ባለመሳተፋችን ከሥራም ከደሞዝም ታግደናል” የትግራይ ክልል ፖሊሶች
Addis Maleda (RSS)

ሐሙስ ጥቅምት 29 ቀን 2016 (አዲስ ማለዳ) በፌደራል መንግሥቱና በህወሓት መካከል በተደረገው ጦርነት አልተሳተፋችሁም በሚል ከሰኔ 21/2013 በኋላ ከሥራም ከደሞዝም ታግደናል ሲሉ 240 የሚሆኑ የትግራይ ክልል ፖሊሶች ቅሬታቸውን ገለጹ፡፡

የፖሊስ አባላቱ “የፌደራል መንግሥቱ ትግራይ ክልልን ተቆጣጥሮ በነበረበት ወቅት በሞያችን ኅብረተሰቡን ስናገለግል ቆይተን፤ ህወሓት መቀሌ በገባ ግዜ ተለይተን ከሥራችን ታግደናል” ሲሉ መናገራቸውን አራዳ ኤፍኤም ዘግቧል፡፡

አባላቱ የተቋረጠው ሥራም ሆነ ደሞዝ እንዲመለስልን ለትግራይ ክልል ጊዜዊ አስተዳደርና ለክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን በተደጋጋሚ ጥያቄ ብናቀርብም ከቀጠሮ ያለፈ ምላሽ አላገኘንም ሲሉ ተናግረዋል፡፡

የኢትዮጵያ ህዝብ እምባ ጠባቂ የመቀሌ ቅርንጫፍ በበኩሉ፤ 240 የሚደርሱ የፖሊስ አባላት ያቀረቡት ቅሬታ ትክክል መሆኑን አረጋግጧል፡፡

የቅርንጫፉ ሀላፊ ፀጋየ እምባየ “ጊዜዊ አስተዳደሩም ሆነ የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽንን በአካልና በደብዳቤ ብንጠይቅም፤ በቂ ምላሽ ባለማግኘታችን የፌደራል እምባ ጠባቂ ጉዳዩን እንዲከታተል አስተላልፈናል” ብለዋል፡፡

ኢትዮጵያ ህዝብ እምባ ጠባቂ ተቋም በበኩሉ፤ “ቅሬታው በፌደራል ደረጃ እንዲፈታ ከቅርንጫፍ ቢሮው ጋር ተነጋግረናል፤ ነገር ግን መዝገባቸው ተሟልቶ ባለመቅረቡ የፌደራል ፖሊስ ኮሚሽንን መጠየቅ አልቻንም” የሚል ምላሽ መስጠቱን ሰጥቷል፡፡

ስለ ጉዳዩ የተጠየቁት የትግራይ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን የኮሚሽኑ አማካሪና ልዩ ፅሀፊ ኮማንደር መብርሀቱ በበኩላቸው፤ “ምላሽ የሚሰጡት የበላይ ሀላፊዎች ናቸው” በማለት መልስ ለመስጠት ፈቃደኛ ሳይሆኑ መቅረታቸውንም ዘገባው አመላክቷል፡፡
ኢትዮጵያ እና ሳዑዲ አረቢያ በነዳጅና ኢነርጂ መስኮች በጋራ ለመስራት ተስማሙ
Addis Maleda (RSS)

ሐሙስ ጥቅምት 29 ቀን 2016 (አዲስ ማለዳ) ኢትዮጵያ እና ሳዑዲ አረቢያ በነዳጅና ኢነርጂ መስኮች በጋራ ለመስራት የሚያስችል ስምምነት ተፈራርመዋል።

የትብብር ስምምነቱ በኢ.ፌ.ዲ.ሪ ገንዘብ ሚኒስትር አህመድ ሽዴ እና በሳዑዲ አረቢያዉ የኢነርጂ ሚኒስትር ልዑል አብዱልአዚዝ ቢን ሰልማን አል ሳዑድ መካከል ነው የተፈረመው።

ስምምነቱ በሪያድ እየተካሄደ በሚገኘው የሳዑዲ አፍሪካ ኢኮኖሚ ኮንፍረንስ ላይ የተፈረመ ሲሆን፤ በዚህም ኹለቱ አገሮች በነዳጅ አቅርቦት፣ በኢነርጂ ቴክኖሎጂ ሽግግር እና በኢነርጂ ኢንቨስትመንት መስኮች በትብብር ለመስራት የሚያስችል መሆኑን በሪያድ የኢትዮጵያ ኤምባሲ አስታውቋል።

ይህም የኢትዮጵያን ነዳጅ አቅርቦት ከማረጋገጥ አና በኢነርጂዉ መስክ ለሚደረገው የልማት እንቅስቃሴ የበለጠ መነሳሳት እንደሚሆን ታምኖበታል።
ኢራን ከእስራኤል ጋር ግንኙነት ያላትን መርከብ ሰራኞተች እንደምትለቅ ገለጸች
جديد አል ዐይን ኒውስ (RSS)

የኢራን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ከእስራኤል ጋር ግንኙነት አላት በሚል ተይዛ የነበረችው መርከብ ሰራተኞች ይለቀቃሉ ብሏል
አትሌት መዲና ኢሳ ከ20 አመት በታች የ5 ሺህ ሜትር የሩጫ ውድድር ክብረወሰን ሰበረች
جديد አል ዐይን ኒውስ (RSS)

አዲዳስ ባዘጋጀው “አዲዜሮ” አመታዊ ውድድር በወንዶቹ ዮሚፍ ቀጀልቻ ማሸነፍ ችሏል
ኢራቃዊቷ የቲክቶክ ተጽዕኖ ፈጣሪ ኦም ፋሀድ በጥይት ተገደለች
جديد አል ዐይን ኒውስ (RSS)

በቲክቶክ በምትለቃቸው ቪዲዮዎች ታዋቂነትን ያተረፈችው ኢራቃዊቷ ኦም ፋሀድ ባግዳድ ውስጥ በጥይት ግድያ ተፈጽሞባታል
የኦሎምፒክ ሻምፒዮኑ ሰለሞን ባረጋ በሻንጋይ ዳይመንድ ሊግ አሸነፈ
جديد አል ዐይን ኒውስ (RSS)

የ2024 ዋንዳ ዳይመንድ ሊግ ውድድር ለ6 ወራት የሚቆይ ሲሆን በአራት አህጉራት በ15 ከተሞች ይካሄዳል
የጋዛን ፍርስራሽ ለማጽዳት 14 አመታትን ሊፈጅ እንደሚችል ተመድ ገለጸ
جديد አል ዐይን ኒውስ (RSS)

እስራኤል ሀማስን ለማጥፋት በወሰደችው ወታደራዊ ዘመቻ 2.3 ሚሊዮን ህዝብ የሚኖርባትን ጠረፋማዋን ግዛት ወደ ፍርስራሽነት ቀይራታለች
ሳላህና ክሎፕ የተጋጩበት ምክንያት ምንድን ነው?
جديد አል ዐይን ኒውስ (RSS)

ሳላህ ዛሬ ስለጉዳዩ ማብራሪያ ከሰጠሁ “ነገሮች ይከራሉ” ብሏል
2024/04/28 18:46:01
Back to Top
HTML Embed Code: