የዘርፈ ብዙ ጉዳዮችና ቀዳማይ ልጅነት ትግበራ ዳይሬክቶሬት በ2017 ዓ.ም እቅድ አፈጻጸም እና በ2018 ዓ.ም እቅድ ዙሪያ ውይይት አካሄደ።
(ሰኔ 24/2017 ዓ.ም) በመርሀ ግብሩ የክፍለከተማ የዘርፈ ብዙና ልዩፍላጎት ቡድን መሪዎች እንዲሁም የስርአተ ጾታና ዘርፈ ብዙ ባለሙያዎችን ጨምሮ የዳይሬክቶሬቱ ባለሙያዎች የተሳተፉ ሲሆን በዘርፉ በ90 ቀናት የሚከናወኑ ተግባራት እቅድ ቀርቦ ውይይት ተካሂዷል።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የዘርፈ ብዙ ጉዳዮችና ቀዳማይ ልጅነት ትግበራ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ወይዘሮ በላይነሽ የሻው ስራ ክፍሉ በየሩብ አመቱ በዘርፉ የተከናወኑ ተግባራትን ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር በመሆን ሲገመግም መቆየቱን ገልጸው የዛሬው ውይይት በበጀት አመቱ የተከናወኑ ተግባራትን በመገምገም በ2018ዓ.ም የተሻለ ስራ ለመስራት እንዲቻል ታስቦ መዘጋጀቱን አስታውቀዋል።
ዳይሬክተሩዋ አያይዘውም በትምህርት ሴክተሩ በ90 ቀናት የተለያዩ ተግባራትን ለማከናወን እቅድ መዘጋጀቱን ገልጸው ከነዚህ ተግባራት መካከል በ2018 ሞዴል የሚሆኑ የቅድመ አንደኛ ደረጃ ተቋማትን መረጃ ከማደራጀት ጀምሮ ለህጻናቱ ምቹ የመማሪያ ቦታ እንዲሆኑ የማድረግ ፣ በየትምህርት ተቋማቱ የስርአተ ጾታ እና የጤና እንክብካቤ ክበባት ቢሮ እንዲኖር ፣ ለሴት ተማሪዎች የንጽህና መጠበቂ ክፍል ማዘጋጀትን ጨምሮ በእቅዱ የተቀመጡ ተግባራት ውጤታማ እንዲሆኑ የክፍለ ከተማ ቡድን መሪዎችና ባለሙያዎች በትኩረት መስራት እንደሚገባቸ አስገንዝበዋል።
(ሰኔ 24/2017 ዓ.ም) በመርሀ ግብሩ የክፍለከተማ የዘርፈ ብዙና ልዩፍላጎት ቡድን መሪዎች እንዲሁም የስርአተ ጾታና ዘርፈ ብዙ ባለሙያዎችን ጨምሮ የዳይሬክቶሬቱ ባለሙያዎች የተሳተፉ ሲሆን በዘርፉ በ90 ቀናት የሚከናወኑ ተግባራት እቅድ ቀርቦ ውይይት ተካሂዷል።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የዘርፈ ብዙ ጉዳዮችና ቀዳማይ ልጅነት ትግበራ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ወይዘሮ በላይነሽ የሻው ስራ ክፍሉ በየሩብ አመቱ በዘርፉ የተከናወኑ ተግባራትን ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር በመሆን ሲገመግም መቆየቱን ገልጸው የዛሬው ውይይት በበጀት አመቱ የተከናወኑ ተግባራትን በመገምገም በ2018ዓ.ም የተሻለ ስራ ለመስራት እንዲቻል ታስቦ መዘጋጀቱን አስታውቀዋል።
ዳይሬክተሩዋ አያይዘውም በትምህርት ሴክተሩ በ90 ቀናት የተለያዩ ተግባራትን ለማከናወን እቅድ መዘጋጀቱን ገልጸው ከነዚህ ተግባራት መካከል በ2018 ሞዴል የሚሆኑ የቅድመ አንደኛ ደረጃ ተቋማትን መረጃ ከማደራጀት ጀምሮ ለህጻናቱ ምቹ የመማሪያ ቦታ እንዲሆኑ የማድረግ ፣ በየትምህርት ተቋማቱ የስርአተ ጾታ እና የጤና እንክብካቤ ክበባት ቢሮ እንዲኖር ፣ ለሴት ተማሪዎች የንጽህና መጠበቂ ክፍል ማዘጋጀትን ጨምሮ በእቅዱ የተቀመጡ ተግባራት ውጤታማ እንዲሆኑ የክፍለ ከተማ ቡድን መሪዎችና ባለሙያዎች በትኩረት መስራት እንደሚገባቸ አስገንዝበዋል።
የውይይቱ ተሳታፊዎችም በቀረቡት የ2017 አፈጻጸም፣ በ2018 እቅድ እንዲሁም በ90 ቀናት በሚከናወኑ ተግባራት ዙሪያ የተለያዩ አስተያየቶችን እና ጥያቄዎችን አቅርበው ምላሽ ተሰቷል።
መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያውን ይጫኑ!
https://linktr.ee/aacaebc
መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያውን ይጫኑ!
https://linktr.ee/aacaebc
የ2017 የትምህርት ዘመን የ6ኛ ክፍል መልቀቂያ ከተማ አቀፍ ፈተና ውጤት ዛሬ ከሰዓት ይፋ ይሆናል፡፡
(ሰኔ 25/2017 ዓ.ም) የ2017 የትምህርት ዘመን የ6ኛ ክፍል መልቀቂያ ከተማ አቀፍ ፈተና ውጤት ዛሬ ከሰዓት የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የአጠቃላይ ካውንስል አባላት በማለፊያ ነጥቡ ላይ ውይይት ካደረጉ በሃላ ይፋ ይደረጋል።
የ2017 ዓ.ም የ6ኛ ክፍል መልቀቂያ ከተማ አቀፍ ፈተና በአጭር ጊዜ ታርሞ ይፋ መደረጉ ተማሪዎች ለቀጣዩ የትምህርት አመት ከወዲሁ በቂ ዝግጅት እንዲያደርጉ የሚያስችል ሲሆን የ2017 የትምህርት ዘመን የ6ኛ ክፍል ከተማ አቀፍ ፈተና ከሰኔ 10-12/2017 ዓ.ም ድረስ በከተማ አስተዳደሩ በሚገኙ 192 የመፈተኛ ጣቢያዎች ለተከታታይ ሶስት ቀናት መሰጠቱ ይታወሳል፡፡ ።
መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያውን ይጫኑ!
https://linktr.ee/aacaebc
(ሰኔ 25/2017 ዓ.ም) የ2017 የትምህርት ዘመን የ6ኛ ክፍል መልቀቂያ ከተማ አቀፍ ፈተና ውጤት ዛሬ ከሰዓት የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የአጠቃላይ ካውንስል አባላት በማለፊያ ነጥቡ ላይ ውይይት ካደረጉ በሃላ ይፋ ይደረጋል።
የ2017 ዓ.ም የ6ኛ ክፍል መልቀቂያ ከተማ አቀፍ ፈተና በአጭር ጊዜ ታርሞ ይፋ መደረጉ ተማሪዎች ለቀጣዩ የትምህርት አመት ከወዲሁ በቂ ዝግጅት እንዲያደርጉ የሚያስችል ሲሆን የ2017 የትምህርት ዘመን የ6ኛ ክፍል ከተማ አቀፍ ፈተና ከሰኔ 10-12/2017 ዓ.ም ድረስ በከተማ አስተዳደሩ በሚገኙ 192 የመፈተኛ ጣቢያዎች ለተከታታይ ሶስት ቀናት መሰጠቱ ይታወሳል፡፡ ።
መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያውን ይጫኑ!
https://linktr.ee/aacaebc
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የአጠቃላይ ካውንስል አባላት የ2017 የትምህርት ዘመን የ6ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና የማለፊያ ውጤት 50% እንዲሆን በዛሬው እለት ወስነዋል።
(ሰኔ 25/2017 ዓ.ም) የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ዶክተር ዘላለም ሙላቱ በአዲሱ ስርዓተ ትምህርት መሰረት በከተማ አስተዳደሩ የ6ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ከ2015 የትምህርት ዘመን ጀምሮ መሰጠቱን እንዲሁም በ2017 የትምህርት ዘመን ከባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት በመስራቱ የተመዘገበው ውጤት አበራታች መሆኑን ተናግረዋል።
ዶክተር ዘላለም አያይዘውም በ2017 ዓ.ም የሒሳብና እንግሊዘኛ ትምህርትን ለማሻሻል ተግባራዊ የተደረገው ስትራቴጂ በተማሪዎች ውጤት መረጋገጡን በተጨማሪም የከተማ አስተዳደሩ በትምህርት ዘርፉ ላይ ባደረገው ትኩረት ውጤቱ መመዝገቡን ተናግረው ፈተናውን በአጭር ጊዜ በማረም ውጤቱ ይፋ እንዲሆን ቀን ከሌት ሲሰሩ ለቆዩ የፈተና ክፍል ባለሙያዎችና ሂደቱን ሲደግፉ ለነበሩ አመራሮች ምስጋና አቅርበዋል።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ምክትል ቢሮ ኃላፊ አቶ ዲናኦል ጫላ በበኩላቸው በከተማ አስተዳደሩ በ2017 ዓ.ም 79,034 ተማሪዎች ፈተናውን መውሰዳቸውን ገልጸዋል፡፡
መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያውን ይጫኑ!
https://linktr.ee/aacaebc
(ሰኔ 25/2017 ዓ.ም) የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ዶክተር ዘላለም ሙላቱ በአዲሱ ስርዓተ ትምህርት መሰረት በከተማ አስተዳደሩ የ6ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ከ2015 የትምህርት ዘመን ጀምሮ መሰጠቱን እንዲሁም በ2017 የትምህርት ዘመን ከባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት በመስራቱ የተመዘገበው ውጤት አበራታች መሆኑን ተናግረዋል።
ዶክተር ዘላለም አያይዘውም በ2017 ዓ.ም የሒሳብና እንግሊዘኛ ትምህርትን ለማሻሻል ተግባራዊ የተደረገው ስትራቴጂ በተማሪዎች ውጤት መረጋገጡን በተጨማሪም የከተማ አስተዳደሩ በትምህርት ዘርፉ ላይ ባደረገው ትኩረት ውጤቱ መመዝገቡን ተናግረው ፈተናውን በአጭር ጊዜ በማረም ውጤቱ ይፋ እንዲሆን ቀን ከሌት ሲሰሩ ለቆዩ የፈተና ክፍል ባለሙያዎችና ሂደቱን ሲደግፉ ለነበሩ አመራሮች ምስጋና አቅርበዋል።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ምክትል ቢሮ ኃላፊ አቶ ዲናኦል ጫላ በበኩላቸው በከተማ አስተዳደሩ በ2017 ዓ.ም 79,034 ተማሪዎች ፈተናውን መውሰዳቸውን ገልጸዋል፡፡
መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያውን ይጫኑ!
https://linktr.ee/aacaebc
በአዲስ አበባ ከተማ የ2017 ዓ.ም የ6ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ከወሰዱ ተማሪዎች መካከል 95 % ያህሉ 50% እና ከዛ በላይ በማምጣት ወደ ቀጣዩ የክፍል ደረጃ መሸጋገራቸውን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ዶክተር ዘላለም ሙላቱ አስታወቁ።
(ሰኔ 25/2017 ዓ.ም) ኃላፊው በዛሬው እለት የ2017 ዓ.ም የ6ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ውጤትን በማስመልከት ለተለያዩ የመንግስትና የግል የመገናኛ ብዙኃን ጋዜጣዊ መግለጫ ሰተዋል።
በከተማ አስተዳደሩ የ6ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ውጤት በየአመቱ አበረታች ውጤት ማሳየት ላይ መሆኑን ኃላፊው በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫው ጠቁመው በ2017 ዓ.ም ፈተናውን ከወሰዱ 79,034 ተማሪዎች መካከል 75,085 ተማሪዎች ማለትም 95 በመቶ የሚሆኑ ተማሪዎች 50% እና በላይ አስመዝግበው ወደ ቀጣዩ የክፍል ደረጃ መሸጋገራቸውን አስታውቀዋል።
(ሰኔ 25/2017 ዓ.ም) ኃላፊው በዛሬው እለት የ2017 ዓ.ም የ6ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ውጤትን በማስመልከት ለተለያዩ የመንግስትና የግል የመገናኛ ብዙኃን ጋዜጣዊ መግለጫ ሰተዋል።
በከተማ አስተዳደሩ የ6ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ውጤት በየአመቱ አበረታች ውጤት ማሳየት ላይ መሆኑን ኃላፊው በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫው ጠቁመው በ2017 ዓ.ም ፈተናውን ከወሰዱ 79,034 ተማሪዎች መካከል 75,085 ተማሪዎች ማለትም 95 በመቶ የሚሆኑ ተማሪዎች 50% እና በላይ አስመዝግበው ወደ ቀጣዩ የክፍል ደረጃ መሸጋገራቸውን አስታውቀዋል።
ዶክተር ዘላለም አያይዘውም የ2017 ዓ.ም የ6ኛ ክፍል ፈተና ውጤታማ እንዲሆን ከተማ አስተዳደሩ ለትምህርት ሴክተሩ ትኩረት በመስጠት የትምህርት ቤት ምገባን ጨምሮ የደንብ ልብስ እና ሌሎች ተጨማሪ የትምህርት ግብአቶች ማቅረቡ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ማበርከቱን ገልጸው በየትምህርት ቤቱ የማጠናከሪያ ትምህርትን ጨምሮ ተማሪዎች በቴሌቪዥን የሚማሩበት አማራጭ መመቻቸቱ እና ባለድርሻ አካላት በቅንጅት መስራታቸው ለውጤቱ መገኘት ተጠቃሽ ምክንያቶች መሆናቸውን አመላክተዋል።
ዘንድሮው በከተማ ደረጃ ከፍተኛ ውጤት ካስመዘገቡ ተማሪዎች መካከል ከ1 እስከ 4 የሚሆኑት ከመንግስት ትምህርት ቤቶች መሆናቸው በግልና በመንግስት ትምህርት ቤቶች መካከል ያለዉን የውጤት ልዩነት እጅግ እየተቀራረበ መምጣቱን ኃላፊው በመግለጫቸው ጠቁመው መምህራንን ጨምሮ በየደረጃው የሚገኙ ባለድርሻ አካላት ተማሪዎቹ ውጤታማ እንዲሆኑ ላበረከቱት አስተዋጽኦ ምስጋና አቅርበዋል።
ተፈታኝ ተማሪዎች ከታች የተቀመጠውን ሊንክ በመጠቀም ከዛሬ ጀምሮ ውጤታቸውን ማየት እንደሚችሉ በጋዜጣዊ መግለጫው ተጠቁሟል።
LINK https://aa6.ministry.et/#/result
Telegram bot; @emacs_ministry_result_qmt_bot
መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያውን ይጫኑ!
https://linktr.ee/aacaebc
ዘንድሮው በከተማ ደረጃ ከፍተኛ ውጤት ካስመዘገቡ ተማሪዎች መካከል ከ1 እስከ 4 የሚሆኑት ከመንግስት ትምህርት ቤቶች መሆናቸው በግልና በመንግስት ትምህርት ቤቶች መካከል ያለዉን የውጤት ልዩነት እጅግ እየተቀራረበ መምጣቱን ኃላፊው በመግለጫቸው ጠቁመው መምህራንን ጨምሮ በየደረጃው የሚገኙ ባለድርሻ አካላት ተማሪዎቹ ውጤታማ እንዲሆኑ ላበረከቱት አስተዋጽኦ ምስጋና አቅርበዋል።
ተፈታኝ ተማሪዎች ከታች የተቀመጠውን ሊንክ በመጠቀም ከዛሬ ጀምሮ ውጤታቸውን ማየት እንደሚችሉ በጋዜጣዊ መግለጫው ተጠቁሟል።
LINK https://aa6.ministry.et/#/result
Telegram bot; @emacs_ministry_result_qmt_bot
መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያውን ይጫኑ!
https://linktr.ee/aacaebc