ተዉሂድ / ላኢላሃ ኢለላህ ማለት
* አላህን ብቻ መገዛት
* እሱን እንጂ አለመፍራት
* አምልኮ ለሱ ብቻ ማድረግ
* ከሱ ብቻ እንጂ አለመከጀል
* ወደሱ ብቻ እንጂ የድረስልን ጥሪ አለማሰማት
* በሱ እንጂ አለመመካት
* ለሱ ብቻ እንጅ ያለ መስገድ ያለ ማጎብደድ
* በስሙ ብቻ እንጂ ያለማረድ ያለመሰዋት
* በስሙ እንጂ ያለመማል
* ሥራን ለሱ ብቻ ጥርት አድርጎ መሥራት
* ከሱ አስበልጦ ሌላን አካል አለመውደድ
* ወደሱ ብቻ ተውባ ማድረግ
* ለሱ ብቻ እንጂ ስለት አለማድረግ
* በደነገገው ሕግ መዳኘት
* ባወረደው ቁርአን መሥራት
* በላከው መልዕክተኛ ማመን
#ይሄንን_የማያቁ_ብዙ_ወዳጆች_አሉን_እና_እናጋራቸው።
@yasin_nuru @yasin_nuru
* አላህን ብቻ መገዛት
* እሱን እንጂ አለመፍራት
* አምልኮ ለሱ ብቻ ማድረግ
* ከሱ ብቻ እንጂ አለመከጀል
* ወደሱ ብቻ እንጂ የድረስልን ጥሪ አለማሰማት
* በሱ እንጂ አለመመካት
* ለሱ ብቻ እንጅ ያለ መስገድ ያለ ማጎብደድ
* በስሙ ብቻ እንጂ ያለማረድ ያለመሰዋት
* በስሙ እንጂ ያለመማል
* ሥራን ለሱ ብቻ ጥርት አድርጎ መሥራት
* ከሱ አስበልጦ ሌላን አካል አለመውደድ
* ወደሱ ብቻ ተውባ ማድረግ
* ለሱ ብቻ እንጂ ስለት አለማድረግ
* በደነገገው ሕግ መዳኘት
* ባወረደው ቁርአን መሥራት
* በላከው መልዕክተኛ ማመን
#ይሄንን_የማያቁ_ብዙ_ወዳጆች_አሉን_እና_እናጋራቸው።
@yasin_nuru @yasin_nuru
👍162❤45👏7👌6
ዝሙት አደጋዎቹ እና መጠበቂያ መንገዶች
① ዝሙት የአላህን ቁጣ ያስከትላል።
② ዝሙት እጅግ ሰቅጣጭ ዱንያዊ ቅጣት የተወሰነበት ወንጀል ነው። አላህ እንዲህ ይላል:–
﴿الزَّانِيَةُ وَالزَّانِي فَاجْلِدُوا كُلَّ وَاحِدٍ مِنْهُمَا مِائَةَ جَلْدَةٍ وَلا تَأْخُذْكُمْ بِهِمَا رَأْفَةٌ فِي دِينِ اللهِ إِنْ كُنْتُمْ تُؤْمِنُونَ بِاللهِ وَالْيَوْمِ الآخِرِ وَلْيَشْهَدْ عَذَابَهُمَا طَائِفَةٌ مِنَ الْمُؤْمِنِينَ﴾
"ዝሙተኛይቱና ዝሙተኛው ከሁለቱ እያንዳንዳቸውን (ያላገቡ ከሆኑ) መቶ ግርፋትን ግረፉዋቸው፤ በእነርሱም በአላህ ፍርድ ርህራሄ አትያዛችሁ፡፡ በአላህና በመጨረሻው ቀን የምታምኑ እንደሆናችሁ (አትራሩ)፡፡ ቅጣታቸውንም ከምእምናን ጭፍሮች ይገኙበት፡፡" [አንኑር: 2]
የርህራሄ ተምሳሌት ከሆነችው ከእናትም በላይ አዛኝ የሆነው ጌታ ከባድ ቅጣት ከማስተላለፉም በላይ ቅጣቱን የሚፈፅሙት ርህራሄ እንዳይዛቸው ማሳሰቡ የወንጀሉን ከባድነት ነው አጉልቶ የሚያሳየን። በዚያ ላይ ቅጣቱ ለሌሎች መቀጣጫ ይሆን ዘንድ ከፊል ህዝብ እንዲመለከተው እያስታወሰ ነው።
ይሄ መቶ ግርፋት እንግዲህ ዝሙተኛው አግብቶ የማያውቅ ከሆነ ነው። አግብቶ የሚያውቅ ከሆነ ግን በድንጋይ ተወግሮ ነው የሚገደለው።
እነዚህ ዱንያዊ ቅጣቶች ናቸው። ጥፋቱን ፈፅሞ ሳይቶብት የሞተ ሰው የሚኖረው አኺራዊ ቅጣቱ ደግሞ የከፋ ነው የሚሆነው።
③ ዝሙት በቀብር (የበርዘኽ ህይወት) አስፈሪ ቅጣት ያለበት ጥፋት ነው። ነብዩ ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም እንዲህ ብለዋል:–
«رأيتُ الليلةَ رجلين أتياني فأخرَجاني، فانطلقتُ معهما فإذا أنا ببناءٍ على مثلِ التنُّورِ، أعلاه ضيِّقٌ وأسفله واسعٌ، يوقد تحتَه نارٌ، فيه رجالٌ ونساءٌ عراةٌ، فإذا أُوقدت النارُ ارتفعوا حتى يكادوا يخرجون، وإذا خمَدَت رجعوا، فقلتُ للرَّجُلينِ: من هؤلاء؟ قالا: هم الزناةُ»
"ዛሬ ሌሊት ሁለት ሰዎች ወደኔ መጥተው አየሁኝ። ይዘውኝ ወጡ። ከነሱ ጋር ተጓዝኩ። እንደ ምድጃ ባለ ግንብ ዘንድ ደረስኩ። ላዩ ጠባብ ታቹ ሰፊ ነው። ከስሩ እሳት ይቀጣጠላል። በውስጡ እርቃን የሆኑ ወንዶችና ሴቶች አሉ። እሳቱ ሲቀጣጠል ሊወጡ እስከሚቀርቡ ወደላይ ይወጣሉ። ሲከስም ይመለሳሉ። ‘እነማን ናቸው እነዚህ?’ ብየ ሁለቱን ሰዎች ስጠይቅ ‘ዝመተኞች ናቸው’ ይላሉ።" [ቡኻሪ: 7047]
④ ዝሙት በአኺራ ድርብርብ ቅጣት ከተዛተባቸው ሺርክና ሰው መግደል ጋር አብሮ የተጠቀሰ የወንጀል አይነቶች ነው። አላህ እንዲህ ይላል:–
(وَالَّذِينَ لَا يَدْعُونَ مَعَ اللَّهِ إِلَٰهًا آخَرَ وَلَا يَقْتُلُونَ النَّفْسَ الَّتِي حَرَّمَ اللَّهُ إِلَّا بِالْحَقِّ وَلَا يَزْنُونَ ۚ وَمَنْ يَفْعَلْ ذَٰلِكَ يَلْقَ أَثَامًا * يُضَاعَفْ لَهُ الْعَذَابُ يَوْمَ الْقِيَامَةِ وَيَخْلُدْ فِيهِ مُهَانًا)
"እነዚያም ከአላህ ጋር ሌላን አምላክ የማይገዙት፣ ያችንም አላህ እርም ያደረጋትን ነፍስ ያለ ሕግ የማይገድሉት፣ የማያመነዝሩትም ናቸው፡፡ ይህንንም የሚሠራ ሰው ቅጣትን ያገኛል፡፡ በትንሣኤ ቀን ቅጣቱ ለእርሱ ይደራረባል፡፡ በእርሱም ውስጥ የተዋረደ ኾኖ ይኖራል፡፡" [አልፉርቃን: 68–69]
ኢማሙ አሕመድ "ከግድያ ቀጥሎ ከዝሙት የከፋ ወንጀል አላውቅም" ይላሉ።
⑤ ዝሙት ከባድ ማስጠንቀቂያ የመጣበት የባለጌዎች መንገድ ነው። አላህ እንዲህ ይላል:–
﴿وَلا تَقْرَبُوا الزِّنَى إِنَّهُ كَانَ فَاحِشَةً وَسَاءَ سَبِيلاً﴾
"ዝሙትንም አትቅረቡ፡፡ እርሱ በእርግጥ ብልግና ነውና፡፡ መንገድነቱም ከፋ!" [ኢስራእ: 32]
⑥ ዝሙት ኢማንን የሚያራቁት አደገኛ ወንጀል ነው። ነብዩ ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም እንዲህ ብለዋል:–
«لا يزني الزاني حين يزني وهو مؤمنٌ»
"ዝሙት በሚፈፅመው ጊዜ ሙእሚን ሆኖ አይፈፅመውም።" [ቡኻሪና ሙስሊም]
ይሄ እጅግ እጅግ አስፈሪ ሐዲሥ ነው።
⑦ በዱንያም የአላህን ቁጣና ቅጣት ያስከትላል። ነብዩ ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም እንዲህ ብለዋል:–
إذا ظهر الزنا و الربا في قرية فقد أحلوا بأنفسهم عذاب الله
"ዝሙትና ወለድ በአንዲት መንደር ላይ ከተንሰራፋ በራሳቸው ላይ የአላህን ቅጣት አስወስነዋል።"
⑧ ዝሙት ሲበዛ በሐዲሥ እንደተገለፀው ቀድሞ የማይታወቅ በሽታና ወረርሺኝ ይመጣል። ለምሳሌ ኤድስን አስታውሱ።
…………
…ከዝሙት መራቂያ መንገዶች…
① በመጀመሪያ አንተ ቁርጠኛ ውሳኔ ላይ ድረስ። ከልብ ካለቀሱ እንባ አይገድም።
② እይታን መገደብ። "አይኖች ይዘሙታሉ። ዝሙታቸው ያልተፈቀደ እይታ ነው" ተብሏል በሐዲሥ።
③ ከአጅነቢ ጋር ከመቀላቀል፣ ከአጅነቢ ጋር ተገልሎ ከመቀመጥ መራቅ። አንድ ወንድ ከአንዲት ሴት ጋር ለብቻ መሆኑ ብልግና የመፈፀሙን እድል በጣም ከፍ ያደርገዋል።
"አንድ ወንድ ከአንዲት ሴት ጋር አይገለል። ይህ ሲሆን ሶስተኛቸው ሸይጧን ነውና" ተብሏል በሐዲሥ። ሰው በሌለበት የባልሽ ወንድም እንዲገባ አታድርጊ። "ዋርሳ (የባል ወንድም) ሞት ነው" ብለዋል ነብዩ ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለመወ።
④ ከመጥፎ ጓደኞች መራቅ
"እግሮች ይዘሙታሉ። ዝሙታቸው (ወዳልባሌ ቦታ) መሄድ ነው" ተብሏል በሐዲሥ።
⑤ አጅነቢ ከመጨበጥ መቆጠብ
"እጆች ይዘሙታሉ። ዝሙታቸው መንካት/ መጨበጥ ነው" ተብሏል በሐዲሥ።
⑥ ምላሳችንን ዝሙትን ከሚያስታወሱ ነገሮች ማራቅ። በሐዲሥ "ምላስም ይዘሙታል" እንደተባለ እናስታውስ።
⑦ እንደ ሙዚቃ፣ ፊልም፣ ልቦለድ፣ እርቃን ምስሎችና የብልግና ቪዲዮዎች በከባዱ ወደ ዝሙት የሚጣሩና የዝሙት ፍላጎትን የሚቀሰቅሱ ስራዎች ናቸው። አብዛኞቹ ዘፈኖች ስለ አጅነቢ ገላ፣ ከአጅነቢ ጋር ስለመጫወትና መዋል ነው የሚያወሩት። ዘፈን የዝሙት መሰላል፣ የንፍቅና መብቀያ ነው። አብዛኞቹ ፊልሞች የዝሙት ሙቀዲማዎች ይገኙባቸዋል።
⑧ አኺራን ማሰብ፣ ነገ ከአላህ ፊት መቆምና ከባድ ምርመራ እንዳለ ማሰብ። አላህ እንዲህ ይላል:–
(يَوْمَ تَشْهَدُ عَلَيْهِمْ أَلْسِنَتُهُمْ وَأَيْدِيهِمْ وَأَرْجُلُهُمْ بِمَا كَانُوا يَعْمَلُونَ)
"በእነሱ ላይ ምላሶቻቸው፣ እጆቻቸውና እግሮቻቸውም ይሠሩት በነበሩት ነገር በሚመሰክሩባቸው ቀን (ከባድ ቅጣት አላቸው)፡፡" [አንኑር: 24].
⑨ እራስን በሐላል ማብቃቃት (ማግባት)። ለቻለ ሰው እንደ ትዳር ከዝሙት መጥጠበቂያ ሰበብ የለም።
(10) ማግባት ያልሆነለት ደግሞ እስከዚያ ፆም ማብዛት። አመጋገብን ማስተካከል። እራስን ከቦዘኔነት አርቆ በስራ መጥመድ።
(11) ስለዝሙት አደገኝነት፣ ከዝሙት መራቅ አላህ ዘንድ ስላለው ደረጃ ማንበብ፣ ማድመጥ፣ ማስታወስ።
@yasin_nuru @yasin_nuru
① ዝሙት የአላህን ቁጣ ያስከትላል።
② ዝሙት እጅግ ሰቅጣጭ ዱንያዊ ቅጣት የተወሰነበት ወንጀል ነው። አላህ እንዲህ ይላል:–
﴿الزَّانِيَةُ وَالزَّانِي فَاجْلِدُوا كُلَّ وَاحِدٍ مِنْهُمَا مِائَةَ جَلْدَةٍ وَلا تَأْخُذْكُمْ بِهِمَا رَأْفَةٌ فِي دِينِ اللهِ إِنْ كُنْتُمْ تُؤْمِنُونَ بِاللهِ وَالْيَوْمِ الآخِرِ وَلْيَشْهَدْ عَذَابَهُمَا طَائِفَةٌ مِنَ الْمُؤْمِنِينَ﴾
"ዝሙተኛይቱና ዝሙተኛው ከሁለቱ እያንዳንዳቸውን (ያላገቡ ከሆኑ) መቶ ግርፋትን ግረፉዋቸው፤ በእነርሱም በአላህ ፍርድ ርህራሄ አትያዛችሁ፡፡ በአላህና በመጨረሻው ቀን የምታምኑ እንደሆናችሁ (አትራሩ)፡፡ ቅጣታቸውንም ከምእምናን ጭፍሮች ይገኙበት፡፡" [አንኑር: 2]
የርህራሄ ተምሳሌት ከሆነችው ከእናትም በላይ አዛኝ የሆነው ጌታ ከባድ ቅጣት ከማስተላለፉም በላይ ቅጣቱን የሚፈፅሙት ርህራሄ እንዳይዛቸው ማሳሰቡ የወንጀሉን ከባድነት ነው አጉልቶ የሚያሳየን። በዚያ ላይ ቅጣቱ ለሌሎች መቀጣጫ ይሆን ዘንድ ከፊል ህዝብ እንዲመለከተው እያስታወሰ ነው።
ይሄ መቶ ግርፋት እንግዲህ ዝሙተኛው አግብቶ የማያውቅ ከሆነ ነው። አግብቶ የሚያውቅ ከሆነ ግን በድንጋይ ተወግሮ ነው የሚገደለው።
እነዚህ ዱንያዊ ቅጣቶች ናቸው። ጥፋቱን ፈፅሞ ሳይቶብት የሞተ ሰው የሚኖረው አኺራዊ ቅጣቱ ደግሞ የከፋ ነው የሚሆነው።
③ ዝሙት በቀብር (የበርዘኽ ህይወት) አስፈሪ ቅጣት ያለበት ጥፋት ነው። ነብዩ ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም እንዲህ ብለዋል:–
«رأيتُ الليلةَ رجلين أتياني فأخرَجاني، فانطلقتُ معهما فإذا أنا ببناءٍ على مثلِ التنُّورِ، أعلاه ضيِّقٌ وأسفله واسعٌ، يوقد تحتَه نارٌ، فيه رجالٌ ونساءٌ عراةٌ، فإذا أُوقدت النارُ ارتفعوا حتى يكادوا يخرجون، وإذا خمَدَت رجعوا، فقلتُ للرَّجُلينِ: من هؤلاء؟ قالا: هم الزناةُ»
"ዛሬ ሌሊት ሁለት ሰዎች ወደኔ መጥተው አየሁኝ። ይዘውኝ ወጡ። ከነሱ ጋር ተጓዝኩ። እንደ ምድጃ ባለ ግንብ ዘንድ ደረስኩ። ላዩ ጠባብ ታቹ ሰፊ ነው። ከስሩ እሳት ይቀጣጠላል። በውስጡ እርቃን የሆኑ ወንዶችና ሴቶች አሉ። እሳቱ ሲቀጣጠል ሊወጡ እስከሚቀርቡ ወደላይ ይወጣሉ። ሲከስም ይመለሳሉ። ‘እነማን ናቸው እነዚህ?’ ብየ ሁለቱን ሰዎች ስጠይቅ ‘ዝመተኞች ናቸው’ ይላሉ።" [ቡኻሪ: 7047]
④ ዝሙት በአኺራ ድርብርብ ቅጣት ከተዛተባቸው ሺርክና ሰው መግደል ጋር አብሮ የተጠቀሰ የወንጀል አይነቶች ነው። አላህ እንዲህ ይላል:–
(وَالَّذِينَ لَا يَدْعُونَ مَعَ اللَّهِ إِلَٰهًا آخَرَ وَلَا يَقْتُلُونَ النَّفْسَ الَّتِي حَرَّمَ اللَّهُ إِلَّا بِالْحَقِّ وَلَا يَزْنُونَ ۚ وَمَنْ يَفْعَلْ ذَٰلِكَ يَلْقَ أَثَامًا * يُضَاعَفْ لَهُ الْعَذَابُ يَوْمَ الْقِيَامَةِ وَيَخْلُدْ فِيهِ مُهَانًا)
"እነዚያም ከአላህ ጋር ሌላን አምላክ የማይገዙት፣ ያችንም አላህ እርም ያደረጋትን ነፍስ ያለ ሕግ የማይገድሉት፣ የማያመነዝሩትም ናቸው፡፡ ይህንንም የሚሠራ ሰው ቅጣትን ያገኛል፡፡ በትንሣኤ ቀን ቅጣቱ ለእርሱ ይደራረባል፡፡ በእርሱም ውስጥ የተዋረደ ኾኖ ይኖራል፡፡" [አልፉርቃን: 68–69]
ኢማሙ አሕመድ "ከግድያ ቀጥሎ ከዝሙት የከፋ ወንጀል አላውቅም" ይላሉ።
⑤ ዝሙት ከባድ ማስጠንቀቂያ የመጣበት የባለጌዎች መንገድ ነው። አላህ እንዲህ ይላል:–
﴿وَلا تَقْرَبُوا الزِّنَى إِنَّهُ كَانَ فَاحِشَةً وَسَاءَ سَبِيلاً﴾
"ዝሙትንም አትቅረቡ፡፡ እርሱ በእርግጥ ብልግና ነውና፡፡ መንገድነቱም ከፋ!" [ኢስራእ: 32]
⑥ ዝሙት ኢማንን የሚያራቁት አደገኛ ወንጀል ነው። ነብዩ ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም እንዲህ ብለዋል:–
«لا يزني الزاني حين يزني وهو مؤمنٌ»
"ዝሙት በሚፈፅመው ጊዜ ሙእሚን ሆኖ አይፈፅመውም።" [ቡኻሪና ሙስሊም]
ይሄ እጅግ እጅግ አስፈሪ ሐዲሥ ነው።
⑦ በዱንያም የአላህን ቁጣና ቅጣት ያስከትላል። ነብዩ ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም እንዲህ ብለዋል:–
إذا ظهر الزنا و الربا في قرية فقد أحلوا بأنفسهم عذاب الله
"ዝሙትና ወለድ በአንዲት መንደር ላይ ከተንሰራፋ በራሳቸው ላይ የአላህን ቅጣት አስወስነዋል።"
⑧ ዝሙት ሲበዛ በሐዲሥ እንደተገለፀው ቀድሞ የማይታወቅ በሽታና ወረርሺኝ ይመጣል። ለምሳሌ ኤድስን አስታውሱ።
…………
…ከዝሙት መራቂያ መንገዶች…
① በመጀመሪያ አንተ ቁርጠኛ ውሳኔ ላይ ድረስ። ከልብ ካለቀሱ እንባ አይገድም።
② እይታን መገደብ። "አይኖች ይዘሙታሉ። ዝሙታቸው ያልተፈቀደ እይታ ነው" ተብሏል በሐዲሥ።
③ ከአጅነቢ ጋር ከመቀላቀል፣ ከአጅነቢ ጋር ተገልሎ ከመቀመጥ መራቅ። አንድ ወንድ ከአንዲት ሴት ጋር ለብቻ መሆኑ ብልግና የመፈፀሙን እድል በጣም ከፍ ያደርገዋል።
"አንድ ወንድ ከአንዲት ሴት ጋር አይገለል። ይህ ሲሆን ሶስተኛቸው ሸይጧን ነውና" ተብሏል በሐዲሥ። ሰው በሌለበት የባልሽ ወንድም እንዲገባ አታድርጊ። "ዋርሳ (የባል ወንድም) ሞት ነው" ብለዋል ነብዩ ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለመወ።
④ ከመጥፎ ጓደኞች መራቅ
"እግሮች ይዘሙታሉ። ዝሙታቸው (ወዳልባሌ ቦታ) መሄድ ነው" ተብሏል በሐዲሥ።
⑤ አጅነቢ ከመጨበጥ መቆጠብ
"እጆች ይዘሙታሉ። ዝሙታቸው መንካት/ መጨበጥ ነው" ተብሏል በሐዲሥ።
⑥ ምላሳችንን ዝሙትን ከሚያስታወሱ ነገሮች ማራቅ። በሐዲሥ "ምላስም ይዘሙታል" እንደተባለ እናስታውስ።
⑦ እንደ ሙዚቃ፣ ፊልም፣ ልቦለድ፣ እርቃን ምስሎችና የብልግና ቪዲዮዎች በከባዱ ወደ ዝሙት የሚጣሩና የዝሙት ፍላጎትን የሚቀሰቅሱ ስራዎች ናቸው። አብዛኞቹ ዘፈኖች ስለ አጅነቢ ገላ፣ ከአጅነቢ ጋር ስለመጫወትና መዋል ነው የሚያወሩት። ዘፈን የዝሙት መሰላል፣ የንፍቅና መብቀያ ነው። አብዛኞቹ ፊልሞች የዝሙት ሙቀዲማዎች ይገኙባቸዋል።
⑧ አኺራን ማሰብ፣ ነገ ከአላህ ፊት መቆምና ከባድ ምርመራ እንዳለ ማሰብ። አላህ እንዲህ ይላል:–
(يَوْمَ تَشْهَدُ عَلَيْهِمْ أَلْسِنَتُهُمْ وَأَيْدِيهِمْ وَأَرْجُلُهُمْ بِمَا كَانُوا يَعْمَلُونَ)
"በእነሱ ላይ ምላሶቻቸው፣ እጆቻቸውና እግሮቻቸውም ይሠሩት በነበሩት ነገር በሚመሰክሩባቸው ቀን (ከባድ ቅጣት አላቸው)፡፡" [አንኑር: 24].
⑨ እራስን በሐላል ማብቃቃት (ማግባት)። ለቻለ ሰው እንደ ትዳር ከዝሙት መጥጠበቂያ ሰበብ የለም።
(10) ማግባት ያልሆነለት ደግሞ እስከዚያ ፆም ማብዛት። አመጋገብን ማስተካከል። እራስን ከቦዘኔነት አርቆ በስራ መጥመድ።
(11) ስለዝሙት አደገኝነት፣ ከዝሙት መራቅ አላህ ዘንድ ስላለው ደረጃ ማንበብ፣ ማድመጥ፣ ማስታወስ።
@yasin_nuru @yasin_nuru
❤96👍82💯10👏6🥰1
እነሆ! የጋዛ ጦርነት እንዲቆም ስምምነት ላይ ተደርሷል።
ቢረፍድም አል-ሐምዱ ሊላህ !
" የሆነው ሁሉ ያሳዝናል፤ አላህ ይበቀልላቸው፤ የሞቱትን ከሸሂዶች ይመድባቸው፤ በደላቸውን ያውጣላቸው፤ የድል ጥግን ያቀዳጃቸው።
@yasin_nuru @yasin_nuru
ቢረፍድም አል-ሐምዱ ሊላህ !
" የሆነው ሁሉ ያሳዝናል፤ አላህ ይበቀልላቸው፤ የሞቱትን ከሸሂዶች ይመድባቸው፤ በደላቸውን ያውጣላቸው፤ የድል ጥግን ያቀዳጃቸው።
@yasin_nuru @yasin_nuru
❤239👍68🥰24😢13🤔1
¶ሼር በማድረግ የአጅሩ ተካፋይ ይሁኑ ¶
…………………………………………
ለምን አትሰግድም ወንድሜ?
ለምን አትሰግጂም እህቴ? በዱንያ_ላይ፦
1• እስካልሰግድክ ድረስ ከእድሜህ ላይ በረካ ይነሳል ...
2• እስካልሰገድክ ድረሰ ከፊትህ ላይ ኑር ይገፈፋል...
3• እስካልሰገድክ ድረስ ምትሰራው ስራ ሁሉ ተቀባይነት የለውም.
4• እስካልሰገድክ ድረስ ዱዓህ ተሰሚነት አያገኝም.
5• እሰካልሰገድክ ድረስ ሌሎች ሚያደርጉልህ ዱዓም አይጠቅምህም.
ስትሞት፦
1• እስካልሰገድክ ድረስ እማትረባና የተዋረድክ ሆነህ ትሞታለህ.
2• እስካልሰገድክ ድረስ እንደተራብክ ትሞታለህ.
3• እስካልሰገድክ ድረስ እንደተጠማህ ትሞታለህ. የባህርን ውሃ እንዳለ ብትጠጣ ጥምህን አይቆትጥልህም.
ቀብር_ውስጥ፦
1• እስካልሰገድክ ድረስ ጎንና ጎንህ እስኪተላልፈ ድረስ ቀብርህን አሏህ ያጠብብሃል.
2• እስካልሰገድክ ድረስ ቀብርህ ውስጥ እሳት ተቀጣጥሎብህ ነጋ ጠባ ትሰቃያለህ.
3• እስካልሰገድክ ድረስ በቀን አምስት ጊዜ ከእባብ ጋር ቀጠሮ ይኖርሃል !
የፈጅርን ሰላት ባለመስገድህ ሲያሰቃይህ ዙሁር ይደረሳል፤
የዙሁርን ሰላት ባለመሰገድህ ሲያሰቃይህ አስር ይደርሳል ፤
እንደዚህ እያለ ስቃይህ ይቀጥላል (አንድ ጊዜ ምትመታው እሰከ 70 ክንደ ያህለ መሬት ውስጥ ያሰምጠሃል)..
የቂያማለት፦
1• እስካልሰገድክ ድረስ ወደ ጀሃነም እሳት . በፊትህ እየተጎተትክ ትወሰዳለህ .
2• እሰካልሰገድክ ድረስ አሏህ ፊት ቆመህ ስትተሳሰብ አሏህ (ሱ,ወ) በቁጣ አይን ይመለከትህና ፊትህ ላይ ያለ ስጋ ይነሳል.
3• እስካልሰገድክ ድረስ ከአሏህ (ሱ.ወ) ጋር የምትተሳሰበው ሂሳብ የከፋ ይሆንና ወደ ጀሃነም እሳት እንደትወረወር ይደረጋል .
ወንድሜ አሁንም አትሰግድም ??
እህቴ አሁንም አትሰግጂም ??
ያአሏህ ይህንን ፁሁፍ ላዘጋጀውም ላነበብነውም ወንጀላችንን ማረን…
በሂወት ያሉና የሌሉትንም ወንድምና እህቶቻችንንም ወንጀል ማርልን……..
በግፍ በእስር በጦርነት ላይ እየተሰቃዩ ያሉ ወንድሞቻችንን እህቶቻችችንን ጠብቅልን!!!
ለአሏህ ብለን ሼር እናረገው አናውቅም በዚህች ሰበብ ወንድሞቻችንና እህቶቻችን ሂዳያ ያገኙና እኛም በጭንቁ የቂያማ ቀን ይጠቅመን ይሆናል፡፡
@yasin_nuru @yasin_nuru
…………………………………………
ለምን አትሰግድም ወንድሜ?
ለምን አትሰግጂም እህቴ? በዱንያ_ላይ፦
1• እስካልሰግድክ ድረስ ከእድሜህ ላይ በረካ ይነሳል ...
2• እስካልሰገድክ ድረሰ ከፊትህ ላይ ኑር ይገፈፋል...
3• እስካልሰገድክ ድረስ ምትሰራው ስራ ሁሉ ተቀባይነት የለውም.
4• እስካልሰገድክ ድረስ ዱዓህ ተሰሚነት አያገኝም.
5• እሰካልሰገድክ ድረስ ሌሎች ሚያደርጉልህ ዱዓም አይጠቅምህም.
ስትሞት፦
1• እስካልሰገድክ ድረስ እማትረባና የተዋረድክ ሆነህ ትሞታለህ.
2• እስካልሰገድክ ድረስ እንደተራብክ ትሞታለህ.
3• እስካልሰገድክ ድረስ እንደተጠማህ ትሞታለህ. የባህርን ውሃ እንዳለ ብትጠጣ ጥምህን አይቆትጥልህም.
ቀብር_ውስጥ፦
1• እስካልሰገድክ ድረስ ጎንና ጎንህ እስኪተላልፈ ድረስ ቀብርህን አሏህ ያጠብብሃል.
2• እስካልሰገድክ ድረስ ቀብርህ ውስጥ እሳት ተቀጣጥሎብህ ነጋ ጠባ ትሰቃያለህ.
3• እስካልሰገድክ ድረስ በቀን አምስት ጊዜ ከእባብ ጋር ቀጠሮ ይኖርሃል !
የፈጅርን ሰላት ባለመስገድህ ሲያሰቃይህ ዙሁር ይደረሳል፤
የዙሁርን ሰላት ባለመሰገድህ ሲያሰቃይህ አስር ይደርሳል ፤
እንደዚህ እያለ ስቃይህ ይቀጥላል (አንድ ጊዜ ምትመታው እሰከ 70 ክንደ ያህለ መሬት ውስጥ ያሰምጠሃል)..
የቂያማለት፦
1• እስካልሰገድክ ድረስ ወደ ጀሃነም እሳት . በፊትህ እየተጎተትክ ትወሰዳለህ .
2• እሰካልሰገድክ ድረስ አሏህ ፊት ቆመህ ስትተሳሰብ አሏህ (ሱ,ወ) በቁጣ አይን ይመለከትህና ፊትህ ላይ ያለ ስጋ ይነሳል.
3• እስካልሰገድክ ድረስ ከአሏህ (ሱ.ወ) ጋር የምትተሳሰበው ሂሳብ የከፋ ይሆንና ወደ ጀሃነም እሳት እንደትወረወር ይደረጋል .
ወንድሜ አሁንም አትሰግድም ??
እህቴ አሁንም አትሰግጂም ??
ያአሏህ ይህንን ፁሁፍ ላዘጋጀውም ላነበብነውም ወንጀላችንን ማረን…
በሂወት ያሉና የሌሉትንም ወንድምና እህቶቻችንንም ወንጀል ማርልን……..
በግፍ በእስር በጦርነት ላይ እየተሰቃዩ ያሉ ወንድሞቻችንን እህቶቻችችንን ጠብቅልን!!!
ለአሏህ ብለን ሼር እናረገው አናውቅም በዚህች ሰበብ ወንድሞቻችንና እህቶቻችን ሂዳያ ያገኙና እኛም በጭንቁ የቂያማ ቀን ይጠቅመን ይሆናል፡፡
@yasin_nuru @yasin_nuru
❤97👍84😢9🤔8🕊6🥰2
ከእስልምና አንድ የሚያስደስተኝ ነገር ምን እንደሆነ ታቃላችሁ...
የትም ይሁን አንድ ሙስሊም ሲበደል በየትኛውም ሃገር ያለ ሙስሊም ለተበደለው ወገን የሚያሳየው ድጋፍ አንድነት🥰 #ከጀሰዲን_ዋሂድ
እናንተ ከእስልምና የሚያስደስታችሁ አንድ ነገር ምንድነው?
ሰሉ አለ ረሱል🥰🥰
የትም ይሁን አንድ ሙስሊም ሲበደል በየትኛውም ሃገር ያለ ሙስሊም ለተበደለው ወገን የሚያሳየው ድጋፍ አንድነት🥰 #ከጀሰዲን_ዋሂድ
እናንተ ከእስልምና የሚያስደስታችሁ አንድ ነገር ምንድነው?
ሰሉ አለ ረሱል🥰🥰
❤163👍38😍16🥰2
አንዳንድ አረብ ሃገር ያላችሁ እህቶቻችን...
Mነኝ የሳኡዲዋ ቀበጥ
መዲና ነኝ የማዳም ቅመም
Imu ነኝ ባይተዋር ነው ልቤ😁
M ነኝ ወለዮዋ
ሳዓዳ ብቸኛዋ
ሰአዳ ነኝ የማዳም ሽቅርቅር😂
ፋጤ ነኝ የሪያዷ ቅመም😂
ሌላ የምታቁት ስም ካለ ቀጥሉበት ኮሜንት ላይ😂😂
ማነው ቆይ እነዚህን ስሞች የሚያወጣላችሁ😁😁
Mነኝ የሳኡዲዋ ቀበጥ
መዲና ነኝ የማዳም ቅመም
Imu ነኝ ባይተዋር ነው ልቤ😁
M ነኝ ወለዮዋ
ሳዓዳ ብቸኛዋ
ሰአዳ ነኝ የማዳም ሽቅርቅር😂
ፋጤ ነኝ የሪያዷ ቅመም😂
ሌላ የምታቁት ስም ካለ ቀጥሉበት ኮሜንት ላይ😂😂
ማነው ቆይ እነዚህን ስሞች የሚያወጣላችሁ😁😁
😁133🤣58👍22👏14🤗10❤8
👍121❤19🔥11
*መቼ ነው* እውነተኛ ሙስሊሞች የምንሆነው?
*መቼ ነው* አላህ በፈጠራቸው ነግሮች የምንማረከው?
*መቼ ነው* አሏህ ለምን እንደፈጠርን የምንረዳው?
*መቼ ነው* አሏህ እንደሚፈልገው መኖር የምንጀምረው?
*መቼ ነው* ስለ ሀይማኖታችን በሙሉ ልብ እምንናገረው?
*መቼ ነው* እማይጠቅም ንግግር ከመናገር የምንቆጠበው?
*መቼ ነው* ሀዲስና ቁርአን ስንሰማ የምንደነግጠው?
*መቼ ነው* ለመልካም ስራ ሰበብ የምንሆነው?
*መቼ ነው* በሰላታችን የምንጠቀመው?
*መቼ ነው* ዱአችን ተሰሚነት የሚያገኝው?
*መቼ ነው* ዲናችንን የምንረዳው?
*መቼ ነው* ውሎና አዳራችን በሱና የሚሆነው?
*መቼ ነው* ሙሉ በሙሉ በአሏህ ላይ የምንመካው?
*መቼ ነው* የዱንያን ትልቅነት ከልባችን የምናወጣው?
*መቼ ነው* ቤታችን ውስጥ ያለው የተበላሸ ሂዎት የሚስተካከለው?
*መቼ ነው* ቤታችን ውስጥ ቁርአንና ሀዲስ የሚቀራው የሚወራው?
*መቼ ነው* ውሽት እምናቆመው?
*መቼ ነው* የአሏህን ውሳኔ መቃውም እምናቆመው?
*መቼ ነው* እኔ እኔ ማለት ትተን ውንደሜ እህቴ ማለት እምንጀምረው?
*መቼ ነው* ለሰዎች ከአላህ ውጪ ጌታ እንደሌለ እምንናገረው?
*መቼ ነው* በኛ ዘመን በዲናችን የበላይነት ምናገኝው?
*መቼ ነው* የኢስላም ዘቦች የምንሆነው?
*መቼ ነው* ኢስላምን የምናስተዋውቀው?
*መቼ ነው* ለድሃ እምናዝነው?.
*መቼ ነው* ትዳራችን ስላም ሚያገኝው?
*መቼ ነው* የጋብቻን ጥቅም ተገንዝበት ለትዳር የምንቻኮለው?
*መቼ ነው* ዱአቶቻችን ለገጠሩ የሚጨነቁት?
*መቼ ነው* ከሀሜት; ስውን ከመበድል; ክማስቀየምና ከማማት እምንላቀቀው?
*መቼ ነው* ወላጆቻችንን እምናስደስተውና እምንታዝዝው?
*መቼ ነው* ያልተጣራ ውሬ ካማውራት እምንቆጠበው?
*መቼ ነው* ለአሏህ ብለን እምንዋደደው?
*መቼ ነው* አሏህ በወሰነልን ነገር ደስተኞች የምንሆነው?
*መቼ ነው* የሌሊት ሰላትንና ዚክርን የምንላመደው?
*መቼ ነው* የበድለንን ይቅር የመንለው?
*መቼ ነው* ከራስ ወዳድነት እምንላቀቀው?
*መቼ ነው* ከሞት ቡኃላ ላለው ሂወት ስንቅ እምናዘጋጀው?
*መቼ ነው* ኡለማዎቻችንን እምናከብረው?
*መቼ ነው* ለእውቅት ጊዜ የምንሰጠው?
*መቼ ነው* ባወቅነው የምንሰራው?
*መቼ ነው* የ ምንሞትበትን ቀንም ይሁን ስፍራ እንደማናውቅ ተገንዝበን በተጠንቀቅ የምንቆመው?
*መቼ እረ መቼ ነው* ኢስላምን የምንኖረው?
*መቼ ነው* ለእነዚህ ተግባራዊ መልስ የምንመልሰው?
አሏህ ያግራልን
አሚን
አቡ ፋሩቅ
@yasin_nuru @yasin_nuru
*መቼ ነው* አላህ በፈጠራቸው ነግሮች የምንማረከው?
*መቼ ነው* አሏህ ለምን እንደፈጠርን የምንረዳው?
*መቼ ነው* አሏህ እንደሚፈልገው መኖር የምንጀምረው?
*መቼ ነው* ስለ ሀይማኖታችን በሙሉ ልብ እምንናገረው?
*መቼ ነው* እማይጠቅም ንግግር ከመናገር የምንቆጠበው?
*መቼ ነው* ሀዲስና ቁርአን ስንሰማ የምንደነግጠው?
*መቼ ነው* ለመልካም ስራ ሰበብ የምንሆነው?
*መቼ ነው* በሰላታችን የምንጠቀመው?
*መቼ ነው* ዱአችን ተሰሚነት የሚያገኝው?
*መቼ ነው* ዲናችንን የምንረዳው?
*መቼ ነው* ውሎና አዳራችን በሱና የሚሆነው?
*መቼ ነው* ሙሉ በሙሉ በአሏህ ላይ የምንመካው?
*መቼ ነው* የዱንያን ትልቅነት ከልባችን የምናወጣው?
*መቼ ነው* ቤታችን ውስጥ ያለው የተበላሸ ሂዎት የሚስተካከለው?
*መቼ ነው* ቤታችን ውስጥ ቁርአንና ሀዲስ የሚቀራው የሚወራው?
*መቼ ነው* ውሽት እምናቆመው?
*መቼ ነው* የአሏህን ውሳኔ መቃውም እምናቆመው?
*መቼ ነው* እኔ እኔ ማለት ትተን ውንደሜ እህቴ ማለት እምንጀምረው?
*መቼ ነው* ለሰዎች ከአላህ ውጪ ጌታ እንደሌለ እምንናገረው?
*መቼ ነው* በኛ ዘመን በዲናችን የበላይነት ምናገኝው?
*መቼ ነው* የኢስላም ዘቦች የምንሆነው?
*መቼ ነው* ኢስላምን የምናስተዋውቀው?
*መቼ ነው* ለድሃ እምናዝነው?.
*መቼ ነው* ትዳራችን ስላም ሚያገኝው?
*መቼ ነው* የጋብቻን ጥቅም ተገንዝበት ለትዳር የምንቻኮለው?
*መቼ ነው* ዱአቶቻችን ለገጠሩ የሚጨነቁት?
*መቼ ነው* ከሀሜት; ስውን ከመበድል; ክማስቀየምና ከማማት እምንላቀቀው?
*መቼ ነው* ወላጆቻችንን እምናስደስተውና እምንታዝዝው?
*መቼ ነው* ያልተጣራ ውሬ ካማውራት እምንቆጠበው?
*መቼ ነው* ለአሏህ ብለን እምንዋደደው?
*መቼ ነው* አሏህ በወሰነልን ነገር ደስተኞች የምንሆነው?
*መቼ ነው* የሌሊት ሰላትንና ዚክርን የምንላመደው?
*መቼ ነው* የበድለንን ይቅር የመንለው?
*መቼ ነው* ከራስ ወዳድነት እምንላቀቀው?
*መቼ ነው* ከሞት ቡኃላ ላለው ሂወት ስንቅ እምናዘጋጀው?
*መቼ ነው* ኡለማዎቻችንን እምናከብረው?
*መቼ ነው* ለእውቅት ጊዜ የምንሰጠው?
*መቼ ነው* ባወቅነው የምንሰራው?
*መቼ ነው* የ ምንሞትበትን ቀንም ይሁን ስፍራ እንደማናውቅ ተገንዝበን በተጠንቀቅ የምንቆመው?
*መቼ እረ መቼ ነው* ኢስላምን የምንኖረው?
*መቼ ነው* ለእነዚህ ተግባራዊ መልስ የምንመልሰው?
አሏህ ያግራልን
አሚን
አቡ ፋሩቅ
@yasin_nuru @yasin_nuru
❤108👍80🙏28💔18👏7🔥6
አሜሪካ ቲክቶክን ዘጋች።
' ቲክቶክ ' የተባለው የአጫጭር ቪድዮ ማጋሪያ እስከ ዛሬ እሁድ ድረስ እንዲሸጥ ካልሆነ ግን እንዲታገድ የወጣው ህግ ተግባራዊ ሆኗል።
በዚህም ቲክቶክ በመላ አሜሪካ ውስጥ ከዛሬ ጀምሮ እንዳይሰራ ተደርጓል።
መተግበሪያው ገና እግዱ ተግባራዊ የሚሆንበት ሰዓት ሳይደርስ ቀደም ብሎ (ከሰዓታት በፊት) ነው የዘጋው።
እኛም ጋር ከጥቅሙ ጉዳቱ አመዝኗል ትውልዱን እያበላሸ ነው።
@yasin_nuru @yasin_nuru
' ቲክቶክ ' የተባለው የአጫጭር ቪድዮ ማጋሪያ እስከ ዛሬ እሁድ ድረስ እንዲሸጥ ካልሆነ ግን እንዲታገድ የወጣው ህግ ተግባራዊ ሆኗል።
በዚህም ቲክቶክ በመላ አሜሪካ ውስጥ ከዛሬ ጀምሮ እንዳይሰራ ተደርጓል።
መተግበሪያው ገና እግዱ ተግባራዊ የሚሆንበት ሰዓት ሳይደርስ ቀደም ብሎ (ከሰዓታት በፊት) ነው የዘጋው።
እኛም ጋር ከጥቅሙ ጉዳቱ አመዝኗል ትውልዱን እያበላሸ ነው።
@yasin_nuru @yasin_nuru
👍273❤20👏15💯14🔥4
በረመዳን የማትረሱት የልጅነት ትዝታ ምንድነው?😍❤
Ezedin
እናንተስ?
እኔ ፆም ምንድነው ሲሉኝ ሾርባ መጠጣት ነው ያልኩት መቼም አይረሳኝም🥺😁😁 ወላህ አሁን ድረስ የሚያበሸቀኝ አንድ ሰው አለ እረፍ በሉልኝ😂
Ezedin
እናንተስ?
😁127👍21🥰19❤13🤣13
🔰 ሙርተድ(ከእስልምና የወጣ ይገደላል??ለምን ይገደላል?🔰
አላሁ ሱብሀነሁ ወተዓላ ሰዎችንና ጂኖችን የፈጠረበት ዐላማ እሱን ብቻ እንዲያመልኩ ነው።
አላህ እንዲህ ይላል👇
وَمَا خَلَقْتُ الْجِنَّ وَالْإِنسَ إِلَّا لِيَعْبُدُونِ
(📗ሱረቱ አል-ዛሪያት - 56)
ጋኔንንና ሰውንም ሊግገዙኝ እንጅ ለሌላ አልፈጠርኳቸውም፡፡
በእስልምና አንድ ሙስሊም ያልሆነ ግለሰብን አስገድዶ ወደ እስልምና ማስገባት የሚባል ነገር የለም።
አላህ እንዲህ ይላል👇
በሃይማኖት ማስገደድ የለም፡፡ ቅኑ መንገድ ከጠማማው በእርግጥ ተገለጠ፡፡ "(📘ሱራ በቀራ፥ 2:256)
➤ ተገዶ እስልምና መቀበሉ ራሱ ትርጉም የለውም። ጥቅም የለውም። ምክንያቱም እስልምናን የተቀበለው በውጩ እንጂ ልቡ ላይ ሌላ እምነት ካለው ሙናፊቅ ይሆናል። በጣም ትልቅ ቅጣት ይጠብቀዋል።
አላህ እንዲህ ይላል👇.
إِنَّ الْمُنَافِقِينَ فِي الدَّرْكِ الْأَسْفَلِ مِنَ النَّارِ وَلَن تَجِدَ لَهُمْ نَصِيرًا
*መናፍቃን በእርግጥ ከእሳት በታችኛው አዘቅት ውስጥ ናቸው፡፡ ለእነርሱም ረዳትን አታገኝላቸውም*፡፡
📚 አልኒሳእ 4፥145
➤ አላህ የሚፈልገው ጥርት ያለን አመልኮ እንጂ ሳይፈልጉ በግድ የሚፈፅሙትን አይደለም።
👇ማስረጃ
«وَمَا أُمِرُوا إِلَّا لِيَعْبُدُوا اللَّهَ مُخْلِصِينَ لَهُ الدِّينَ حُنَفَاءَ وَيُقِيمُوا الصَّلَاةَ وَيُؤْتُوا الزَّكَاةَ ۚ وَذَٰلِكَ دِينُ الْقَيِّمَةِ»
«አላህን፣ ኃይማኖትን ለርሱ ብቻ አጥሪዎች ቀጥተኞች ኾነው ሊግገዙት፣ ሶላትንም አስተካክለው ሊሰግዱ፣ ዘካንም ሊሰጡ እንጅ ያልታዘዙ ሲኾኑ (ተለያዩ)። ይህም የቀጥተኛዪቱ (ኃይማኖት) ድንጋጌ ነው።»
📚 [አል-በዪይናህ: 5]
ተገደው አላህን የሚያመልኩ ሰዎች አምልኳቸው ጥራት ስለሌለው ጥቅም የለውም። ስለዚህ በእስልምና ሌላን ሰው አስገድዶ ወደ እስልምና ማስገባት የሚባል ነገር የለም ጥቅምም የለውም።
➤ በእስልምና ሌላን ሰው ወደ እስልምና አስገድዶ ማስገባት እንደሌለ ካየን
ሙስሊም ያልሆኑ ግለሰቦች ያስገድዳል ብለው የሚያነሱትን ሀዲስ እንመልከትና መልስ እንስጥበት
ሀዲሱ👇👇👇👇
عنْ اِبْنِ عَبَّاسٍ رَضِيَ اَللَّهُ عَنْهُمَا قَالَ: قَالَ رَسُولُ اَللَّهِ - صلى الله عليه وسلم -{ مَنْ بَدَّلَ دِينَهُ فَاقْتُلُوهُ }
ኢብኑ ዐባስ እንዳስተላለፉት ነቢዩ ሰላሏሁ ዓለይሂ ወሰለም እንዲህ ብለዋል" ሀይማኖቱን የቀየረን ግደሉት"
➤➤ በመጀመሪያ ሰዎች በአላህ የማምንና የመካድ ምረጫ ተሰጥቷቸዋል። ነፃ ፈቃድ ተሰጥተዋል።
አላህ እንዲህ ይላል👇
وقلِ الْحَقُّ مِن رَّبِّكُمْ ۖ فَمَن شَاءَ فَلْيُؤْمِن وَمَن شَاءَ فَلْيَكْفُرْ ۚ إِنَّا أَعْتَدْنَا لِلظَّالِمِينَ نَارًا أَحَاطَ بِهِمْ سُرَادِقُهَا ۚ وَإِن يَسْتَغِيثُوا يُغَاثُوا بِمَاءٍ كَالْمُهْلِ يَشْوِي الْوُجُوهَ ۚ بِئْسَ الشَّرَابُ وَسَاءَتْ مُرْتَفَقًا
ሱረቱ አል ከህፍ፥ - 29 ]
«እውነቱም ከጌታችሁ ነው፡፡ የሻም ሰው ይመን፤ የሻም ሰው ይካድ» በላቸው፡፡ እኛ ለበደለኞች አጥሯ በእነሱ የከበበ የኾነችውን እሳት አዘጋጅተናል፡፡ (ከጥም) እርዳታንም ቢፈልጉ እንደ ዘይት ዝቃጭ ባለ ፊቶችን በሚጠብስ ውሃ ይረዳሉ፡፡ መጠጡ ከፋ! መደገፊያይቱም ምንኛ አስከፋች!
☝️ አላህ እዚህ አንቀፅ ላይ ሰዎች የማመንና የመካድ ነፃ ፈቃድ እንዳላቸው ከጠቀሰ በኃላ እነዚያ የካዱ ሰዎች ቅጣት እንደሚያገኙ ይጠቅስልናል።
ይህ ማለት ሰዎች የማመንና የመካድ ምርጫ እንዳላቸው፣ የመካድ መብት ግን እንደሌላቸው እንረዳለን። የመካድ መብት ቢኖራቸው በክህደታቸው ባልተቀጡ ነበር።
ይህንን ካየን ከእስልምና የወጣ ሰው ለምን ይገደላል። የመካድ ምርጫ ካለው ለምን ይገደላል ለሚለው መልሱ👇👇
➤➤1. በእስልምና حد ሐድ ( የወንጀል መቅጫ ህግ፣ውሳኔ) የሚባል ነገር አለ። ይህም አንድ ሙስሊም ለሚተገብራቸው ወንጀሎች የተቀመጠ ቅጣት ነው።
ለምሳሌ "حد الزاني " አግብቶ ዝሙት የሰራ ቅጣት(መግደል)፣حد السرقة የስርቆት ህግ(እጁን መቁረጥ), حد القتل የግድያ ቅጣት(መገደል) ወዘተ የሚባሉ ህግጋቶች አሉ። እነዚህን ወንጀሎች የተዳፈረ ከላይ የተጠቀሰውን ቅጣት ያገኛል ምክንያቱም ከላይ እንደተጠቀሰው ሰዎች የመካድ፣ወንጀል የመስራት ምርጫ እንጂ መብት ስለሌላቸው ይቀጣሉ ይጠየቃሉ። ለምሳሌ አግብቶ ዝሙት የሰራ ሰው ዝሙት የሚባል ወንጀል ስለሰራ ይገደላል። ዝሙት መስራት መብቱ ነው አይባልም ልክንደዚሁ አንድ ሙስሊም ከከፈረ ከዝሙት የባሰ የተለቀ ኩፍር(አምላክን መካድ) የሚባል ትልቅ ወንጀል ስለሰራ ይገደላል። አምላኩን መካድ መብቱ ነው አይባልም።
ሰዎች በፈጠሯቸው በተለያዩ ሀገሮች ህግ ላይ ራሱ " ሀገሩን የካደ ሰው ይገደላል" የሚል ህግ አላቸው። ሀገርን መካድ መብቱ ነው እንደማይባለው ሁሉ አምላክን መካድም መብቱ አይደለም።
ሀገርን የካደ ሰው ከተገደለ ሀገርን የፈጠረ አምላክን ሲክድ ይገደል ቢባል ምኑ ነው ሚገርመው።
በአጭሩ ከእስልምና የወጣ ሰው የሚገደለው አምላኩን ስለካደ ክህደት ስለፈፀመ ይገደላል እንጂ አስገድደን እንዲሰልም አይደለም።
➤➤2. ሙርተድ የሚገደልበት ሁለተኛው ምክንያት ለሙስሊሞች ፊትና ስለሚሆን ነው። ከድሮ ጀምሮ "ከእስልምና ወጥቻለሁ፣መስሊም ነበርኩ ወዘተ እያሉ እስልምና ላይ እየቀጠፉ የእስልምና ስም እንደሚያጠፉት ለሙስሊሞች ፊትና ስለሚሆኑ ሙስሊሞችን ከንደዚህ አይነት ፈታኝ ከሆኑ ሰዎች ነፃ ለማድረግ(ሰዎች በነሱ ቅጥፈት እንዳይፈተኑ) ተብሎ ይገደላሉ።
አላህ እንዲህ ይላል
ۚ وَالْفِتْنَةُ أَكْبَرُ مِنَ الْقَتْلِ ۗ وَلَا يَزَالُونَ يُقَاتِلُونَكُمْ حَتَّىٰ يَرُدُّوكُمْ عَن دِينِكُمْ إِنِ اسْتَطَاعُوا ۚ وَمَن يَرْتَدِدْ مِنكُمْ عَن دِينِهِ فَيَمُتْ وَهُوَ كَافِرٌ فَأُولَٰئِكَ حَبِطَتْ أَعْمَالُهُمْ فِي الدُّنْيَا وَالْآخِرَةِ ۖ وَأُولَٰئِك أَصْحابُ النَّارِ ۖ هُمْ فِيهَا خَالِدون
ፈተናም (ማጋራት) ከመግደል ይበልጥ ከባድ ነው፡፡ (ከሐዲዎች) ቢችሉ ከሃይማኖታችሁ እስከሚመልሳችሁ ድረስ የሚዋጉዋችሁ ከመሆን አይቦዝኑም፡፡ ከእናንተ ውስጥም ከሃይማኖቱ የሚመለስና እርሱም ከሐዲ ሆኖ የሚሞት ሰው እነዚያ (በጎ) ሥራቸው በቅርቢቱም በመጨረሻይቱም አገር ተበላሸች፡፡ እነዚያ የእሳት ጓዶች ናቸው፡፡ እነርሱ በርሷ ውስጥ ዘውታሪዎች ናቸው፡፡»(📚አልበቀራህ 2:217)
ይቀጥላል......👇 ሙሉውን አንብቡት👇👇👇👇👇👇
https://www.tg-me.com/iwnetlehullu1/376
አላሁ ሱብሀነሁ ወተዓላ ሰዎችንና ጂኖችን የፈጠረበት ዐላማ እሱን ብቻ እንዲያመልኩ ነው።
አላህ እንዲህ ይላል👇
وَمَا خَلَقْتُ الْجِنَّ وَالْإِنسَ إِلَّا لِيَعْبُدُونِ
(📗ሱረቱ አል-ዛሪያት - 56)
ጋኔንንና ሰውንም ሊግገዙኝ እንጅ ለሌላ አልፈጠርኳቸውም፡፡
በእስልምና አንድ ሙስሊም ያልሆነ ግለሰብን አስገድዶ ወደ እስልምና ማስገባት የሚባል ነገር የለም።
አላህ እንዲህ ይላል👇
በሃይማኖት ማስገደድ የለም፡፡ ቅኑ መንገድ ከጠማማው በእርግጥ ተገለጠ፡፡ "(📘ሱራ በቀራ፥ 2:256)
➤ ተገዶ እስልምና መቀበሉ ራሱ ትርጉም የለውም። ጥቅም የለውም። ምክንያቱም እስልምናን የተቀበለው በውጩ እንጂ ልቡ ላይ ሌላ እምነት ካለው ሙናፊቅ ይሆናል። በጣም ትልቅ ቅጣት ይጠብቀዋል።
አላህ እንዲህ ይላል👇.
إِنَّ الْمُنَافِقِينَ فِي الدَّرْكِ الْأَسْفَلِ مِنَ النَّارِ وَلَن تَجِدَ لَهُمْ نَصِيرًا
*መናፍቃን በእርግጥ ከእሳት በታችኛው አዘቅት ውስጥ ናቸው፡፡ ለእነርሱም ረዳትን አታገኝላቸውም*፡፡
📚 አልኒሳእ 4፥145
➤ አላህ የሚፈልገው ጥርት ያለን አመልኮ እንጂ ሳይፈልጉ በግድ የሚፈፅሙትን አይደለም።
👇ማስረጃ
«وَمَا أُمِرُوا إِلَّا لِيَعْبُدُوا اللَّهَ مُخْلِصِينَ لَهُ الدِّينَ حُنَفَاءَ وَيُقِيمُوا الصَّلَاةَ وَيُؤْتُوا الزَّكَاةَ ۚ وَذَٰلِكَ دِينُ الْقَيِّمَةِ»
«አላህን፣ ኃይማኖትን ለርሱ ብቻ አጥሪዎች ቀጥተኞች ኾነው ሊግገዙት፣ ሶላትንም አስተካክለው ሊሰግዱ፣ ዘካንም ሊሰጡ እንጅ ያልታዘዙ ሲኾኑ (ተለያዩ)። ይህም የቀጥተኛዪቱ (ኃይማኖት) ድንጋጌ ነው።»
📚 [አል-በዪይናህ: 5]
ተገደው አላህን የሚያመልኩ ሰዎች አምልኳቸው ጥራት ስለሌለው ጥቅም የለውም። ስለዚህ በእስልምና ሌላን ሰው አስገድዶ ወደ እስልምና ማስገባት የሚባል ነገር የለም ጥቅምም የለውም።
➤ በእስልምና ሌላን ሰው ወደ እስልምና አስገድዶ ማስገባት እንደሌለ ካየን
ሙስሊም ያልሆኑ ግለሰቦች ያስገድዳል ብለው የሚያነሱትን ሀዲስ እንመልከትና መልስ እንስጥበት
ሀዲሱ👇👇👇👇
عنْ اِبْنِ عَبَّاسٍ رَضِيَ اَللَّهُ عَنْهُمَا قَالَ: قَالَ رَسُولُ اَللَّهِ - صلى الله عليه وسلم -{ مَنْ بَدَّلَ دِينَهُ فَاقْتُلُوهُ }
ኢብኑ ዐባስ እንዳስተላለፉት ነቢዩ ሰላሏሁ ዓለይሂ ወሰለም እንዲህ ብለዋል" ሀይማኖቱን የቀየረን ግደሉት"
➤➤ በመጀመሪያ ሰዎች በአላህ የማምንና የመካድ ምረጫ ተሰጥቷቸዋል። ነፃ ፈቃድ ተሰጥተዋል።
አላህ እንዲህ ይላል👇
وقلِ الْحَقُّ مِن رَّبِّكُمْ ۖ فَمَن شَاءَ فَلْيُؤْمِن وَمَن شَاءَ فَلْيَكْفُرْ ۚ إِنَّا أَعْتَدْنَا لِلظَّالِمِينَ نَارًا أَحَاطَ بِهِمْ سُرَادِقُهَا ۚ وَإِن يَسْتَغِيثُوا يُغَاثُوا بِمَاءٍ كَالْمُهْلِ يَشْوِي الْوُجُوهَ ۚ بِئْسَ الشَّرَابُ وَسَاءَتْ مُرْتَفَقًا
ሱረቱ አል ከህፍ፥ - 29 ]
«እውነቱም ከጌታችሁ ነው፡፡ የሻም ሰው ይመን፤ የሻም ሰው ይካድ» በላቸው፡፡ እኛ ለበደለኞች አጥሯ በእነሱ የከበበ የኾነችውን እሳት አዘጋጅተናል፡፡ (ከጥም) እርዳታንም ቢፈልጉ እንደ ዘይት ዝቃጭ ባለ ፊቶችን በሚጠብስ ውሃ ይረዳሉ፡፡ መጠጡ ከፋ! መደገፊያይቱም ምንኛ አስከፋች!
☝️ አላህ እዚህ አንቀፅ ላይ ሰዎች የማመንና የመካድ ነፃ ፈቃድ እንዳላቸው ከጠቀሰ በኃላ እነዚያ የካዱ ሰዎች ቅጣት እንደሚያገኙ ይጠቅስልናል።
ይህ ማለት ሰዎች የማመንና የመካድ ምርጫ እንዳላቸው፣ የመካድ መብት ግን እንደሌላቸው እንረዳለን። የመካድ መብት ቢኖራቸው በክህደታቸው ባልተቀጡ ነበር።
ይህንን ካየን ከእስልምና የወጣ ሰው ለምን ይገደላል። የመካድ ምርጫ ካለው ለምን ይገደላል ለሚለው መልሱ👇👇
➤➤1. በእስልምና حد ሐድ ( የወንጀል መቅጫ ህግ፣ውሳኔ) የሚባል ነገር አለ። ይህም አንድ ሙስሊም ለሚተገብራቸው ወንጀሎች የተቀመጠ ቅጣት ነው።
ለምሳሌ "حد الزاني " አግብቶ ዝሙት የሰራ ቅጣት(መግደል)፣حد السرقة የስርቆት ህግ(እጁን መቁረጥ), حد القتل የግድያ ቅጣት(መገደል) ወዘተ የሚባሉ ህግጋቶች አሉ። እነዚህን ወንጀሎች የተዳፈረ ከላይ የተጠቀሰውን ቅጣት ያገኛል ምክንያቱም ከላይ እንደተጠቀሰው ሰዎች የመካድ፣ወንጀል የመስራት ምርጫ እንጂ መብት ስለሌላቸው ይቀጣሉ ይጠየቃሉ። ለምሳሌ አግብቶ ዝሙት የሰራ ሰው ዝሙት የሚባል ወንጀል ስለሰራ ይገደላል። ዝሙት መስራት መብቱ ነው አይባልም ልክንደዚሁ አንድ ሙስሊም ከከፈረ ከዝሙት የባሰ የተለቀ ኩፍር(አምላክን መካድ) የሚባል ትልቅ ወንጀል ስለሰራ ይገደላል። አምላኩን መካድ መብቱ ነው አይባልም።
ሰዎች በፈጠሯቸው በተለያዩ ሀገሮች ህግ ላይ ራሱ " ሀገሩን የካደ ሰው ይገደላል" የሚል ህግ አላቸው። ሀገርን መካድ መብቱ ነው እንደማይባለው ሁሉ አምላክን መካድም መብቱ አይደለም።
ሀገርን የካደ ሰው ከተገደለ ሀገርን የፈጠረ አምላክን ሲክድ ይገደል ቢባል ምኑ ነው ሚገርመው።
በአጭሩ ከእስልምና የወጣ ሰው የሚገደለው አምላኩን ስለካደ ክህደት ስለፈፀመ ይገደላል እንጂ አስገድደን እንዲሰልም አይደለም።
➤➤2. ሙርተድ የሚገደልበት ሁለተኛው ምክንያት ለሙስሊሞች ፊትና ስለሚሆን ነው። ከድሮ ጀምሮ "ከእስልምና ወጥቻለሁ፣መስሊም ነበርኩ ወዘተ እያሉ እስልምና ላይ እየቀጠፉ የእስልምና ስም እንደሚያጠፉት ለሙስሊሞች ፊትና ስለሚሆኑ ሙስሊሞችን ከንደዚህ አይነት ፈታኝ ከሆኑ ሰዎች ነፃ ለማድረግ(ሰዎች በነሱ ቅጥፈት እንዳይፈተኑ) ተብሎ ይገደላሉ።
አላህ እንዲህ ይላል
ۚ وَالْفِتْنَةُ أَكْبَرُ مِنَ الْقَتْلِ ۗ وَلَا يَزَالُونَ يُقَاتِلُونَكُمْ حَتَّىٰ يَرُدُّوكُمْ عَن دِينِكُمْ إِنِ اسْتَطَاعُوا ۚ وَمَن يَرْتَدِدْ مِنكُمْ عَن دِينِهِ فَيَمُتْ وَهُوَ كَافِرٌ فَأُولَٰئِكَ حَبِطَتْ أَعْمَالُهُمْ فِي الدُّنْيَا وَالْآخِرَةِ ۖ وَأُولَٰئِك أَصْحابُ النَّارِ ۖ هُمْ فِيهَا خَالِدون
ፈተናም (ማጋራት) ከመግደል ይበልጥ ከባድ ነው፡፡ (ከሐዲዎች) ቢችሉ ከሃይማኖታችሁ እስከሚመልሳችሁ ድረስ የሚዋጉዋችሁ ከመሆን አይቦዝኑም፡፡ ከእናንተ ውስጥም ከሃይማኖቱ የሚመለስና እርሱም ከሐዲ ሆኖ የሚሞት ሰው እነዚያ (በጎ) ሥራቸው በቅርቢቱም በመጨረሻይቱም አገር ተበላሸች፡፡ እነዚያ የእሳት ጓዶች ናቸው፡፡ እነርሱ በርሷ ውስጥ ዘውታሪዎች ናቸው፡፡»(📚አልበቀራህ 2:217)
ይቀጥላል......👇 ሙሉውን አንብቡት👇👇👇👇👇👇
https://www.tg-me.com/iwnetlehullu1/376
👍99❤🔥4❤3👏3🎉3👌3🤔2🏆2🕊1
ጀግንነትን ከታላቁ መሪ እንማር!
የበረሐው አንበሳ ኡመር ሙክታር ከጣልያኑ መርማሪ ጋር የነበራቸው ቆይታ…
መርማሪ፦የጣልያን ጠላት ሆነህ ተዋግተሀል?
ኡመር ፦አዎን
መርማሪ፦የሊብያን ህዝብ ጣልያንን እንዲዋጉ አሳምፀሀል?
ኡመር፦አዎን
መርማሪ፦የወንጀልህን ቅጣት ታውቀዋለህ?
ኡመር፦አዎን
መርማሪ፦የምትናገረውን ነገር ታምንልኛለህ?
ኡመር፦በሚገባ
መርማሪ፦ከመቼ ጀምረህ ነው ጣልያንን መዋጋት የጀመርከው?
ኡመር ፦ከ20 አመት ይሆነኛል!
መርማሪ፦በሰራሀው ነገር ተፀፅተሀል?!
ኡመር ፦በጭራሽ!
መርማሪ፦ስቅላት እንደሚጠብቅህ ታውቃለህን?!
ኡመር፦አዎን
የፍርድ ቤት ዳኛው፦መጨረሻህ በዚህ መልኩ ስለሆነ በጣም አዝናለሁ
ኡመር፦እንዲያውም ህይወቴን የምቋጭበት ምርጥ መንገድ ብዬ የማስበው በዚህ መንገድ ስጨርሰው ነው
ዳኛ፦ኡመርን በሂወት ለማጎጎት እየሞከረ…ለሙጃሂዶቹ ከዚህ ድርጊት እንዲቆጠቡ አድርግ እኛ በነፃ እንለቅሀልን…
ኡመር፦በጣም በግርምት ካዩት በኃላ…እንዲህ በማለት ታዎቂ ንግግራቸውን ተናገሩ " በሁሉም ሰላቶቼ ውስጥ ለ ላኢላሀኢለሏህ ሙሀመዱ ረሱሉላህ የምትመሰክር ጣቴ ባጢል ነገር አትፅፍም"
@yasin_nuru @yasin_nuru
የበረሐው አንበሳ ኡመር ሙክታር ከጣልያኑ መርማሪ ጋር የነበራቸው ቆይታ…
መርማሪ፦የጣልያን ጠላት ሆነህ ተዋግተሀል?
ኡመር ፦አዎን
መርማሪ፦የሊብያን ህዝብ ጣልያንን እንዲዋጉ አሳምፀሀል?
ኡመር፦አዎን
መርማሪ፦የወንጀልህን ቅጣት ታውቀዋለህ?
ኡመር፦አዎን
መርማሪ፦የምትናገረውን ነገር ታምንልኛለህ?
ኡመር፦በሚገባ
መርማሪ፦ከመቼ ጀምረህ ነው ጣልያንን መዋጋት የጀመርከው?
ኡመር ፦ከ20 አመት ይሆነኛል!
መርማሪ፦በሰራሀው ነገር ተፀፅተሀል?!
ኡመር ፦በጭራሽ!
መርማሪ፦ስቅላት እንደሚጠብቅህ ታውቃለህን?!
ኡመር፦አዎን
የፍርድ ቤት ዳኛው፦መጨረሻህ በዚህ መልኩ ስለሆነ በጣም አዝናለሁ
ኡመር፦እንዲያውም ህይወቴን የምቋጭበት ምርጥ መንገድ ብዬ የማስበው በዚህ መንገድ ስጨርሰው ነው
ዳኛ፦ኡመርን በሂወት ለማጎጎት እየሞከረ…ለሙጃሂዶቹ ከዚህ ድርጊት እንዲቆጠቡ አድርግ እኛ በነፃ እንለቅሀልን…
ኡመር፦በጣም በግርምት ካዩት በኃላ…እንዲህ በማለት ታዎቂ ንግግራቸውን ተናገሩ " በሁሉም ሰላቶቼ ውስጥ ለ ላኢላሀኢለሏህ ሙሀመዱ ረሱሉላህ የምትመሰክር ጣቴ ባጢል ነገር አትፅፍም"
@yasin_nuru @yasin_nuru
👍222❤58🥰14👌9😎5👏3
ያሸህረል ቁርአን አህለን 🕋
ያ ሸህረል ወህዳ አህለን🕌
ያ ሸህረል ተውባ አህለን🌙💚
የአንድነት የህብር ቀለም፣❤️
የከፍታ የፍካት ዓለም፣😍
አዲስ ንጋት የሩህ መስከረም፣🥳
ረመዳን አገናኘን በፍቅር ዳግም፤ 🥰
39 days😳 away from Ramadan!
39 ቀን ቀረው😳
اللهم بلغنا رمضان
@yasin_nuru @yasin_nuru
ያ ሸህረል ወህዳ አህለን🕌
ያ ሸህረል ተውባ አህለን🌙💚
የአንድነት የህብር ቀለም፣❤️
የከፍታ የፍካት ዓለም፣😍
አዲስ ንጋት የሩህ መስከረም፣🥳
ረመዳን አገናኘን በፍቅር ዳግም፤ 🥰
39 days😳 away from Ramadan!
39 ቀን ቀረው😳
اللهم بلغنا رمضان
@yasin_nuru @yasin_nuru
👍113❤38🥰24🕊5
#እንድታውቁት
" የሀጅ ጉዞ ምዝገባ ጥር 15 ይጀምራል የሀጅ ጉዞ ዋጋ አሁን ባለው 625,000 (ስድስት መቶ ሃያ አምስት ሺ) ብር ነው " - ጠቅላይ ምክር ቤቱ
የ1446ኛው የሀጅ እና ዑምራ ጉዞ ምዝገባ ከጥር 15 ቀን 2017 ጀምሮ እስከ የካቲት 21 ብቻ እንደሚከናወን የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ገልጿል።
ምዝገባው ጥር 15/2017 በሁሉም የክልል እና የከተማ አስተዳደር የምዝገባ ጣቢያዎች ይጀመራል።
የሳውዲ ሀጅ ሚኒስቴር ባስቀመጠው አሰራር መሰረት ያለው የምዝገባ ጊዜ አጭር በመሆኑ ሁጃጆች (ተጓዦች) በወቅቱ ቅድመ ዝግጅታቸውን እንዲያጠናቅቁ ጥሪ ቀርቧል።
የዘንድሮ የሀጅ እና ዑምራ የጉዞ ዋጋ 625 ሺህ ብር መሆኑ ተገልጿል።
ምክር ቤቱ " የጉዞው ዋጋ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ጋር ተያይዞ የታየው የዶላር ጭማሪና በአየር መንገዶች ላይ ያለው የትኬት ዋጋ መናር ዋጋው ከፍ እንዲል አድርጎታል " ብሏል።
" የሀጅ ዋሃ ከዶላር አንፃር የ4,921 ዶላር ቅናሽ እንዲደረግበት ቢደረግም በብር ግን ጭማሪ አሳይቷል " ሲል ገልጿል።
ጠቅላይ ምክር-ቤቱ የአገልግሎት ዋጋን በመቀነስ በዕቅድ የተያዙ ፕሮጀክቶችን በማጠፍና በሳውዲ የሚቀርበውን አገልግሎት ተመጣጣኝ እንዲሆን በማድረግ 108 ሺህ ብር ቅናሽ እንዲኖረው ማድረጉን አሳውቋል።
የዶላር ዋጋ ከፍ በማለቱ ግን ብሩ መጨመሩ ተገልጿል።
ባለፈው ዓመት ለአንድ ሀጅ ዋጋ አጠቃላይ ብር 329,000 እንደነበር ይወሳል።
@yasin_nuru @yasin_nuru
" የሀጅ ጉዞ ምዝገባ ጥር 15 ይጀምራል የሀጅ ጉዞ ዋጋ አሁን ባለው 625,000 (ስድስት መቶ ሃያ አምስት ሺ) ብር ነው " - ጠቅላይ ምክር ቤቱ
የ1446ኛው የሀጅ እና ዑምራ ጉዞ ምዝገባ ከጥር 15 ቀን 2017 ጀምሮ እስከ የካቲት 21 ብቻ እንደሚከናወን የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ገልጿል።
ምዝገባው ጥር 15/2017 በሁሉም የክልል እና የከተማ አስተዳደር የምዝገባ ጣቢያዎች ይጀመራል።
የሳውዲ ሀጅ ሚኒስቴር ባስቀመጠው አሰራር መሰረት ያለው የምዝገባ ጊዜ አጭር በመሆኑ ሁጃጆች (ተጓዦች) በወቅቱ ቅድመ ዝግጅታቸውን እንዲያጠናቅቁ ጥሪ ቀርቧል።
የዘንድሮ የሀጅ እና ዑምራ የጉዞ ዋጋ 625 ሺህ ብር መሆኑ ተገልጿል።
ምክር ቤቱ " የጉዞው ዋጋ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ጋር ተያይዞ የታየው የዶላር ጭማሪና በአየር መንገዶች ላይ ያለው የትኬት ዋጋ መናር ዋጋው ከፍ እንዲል አድርጎታል " ብሏል።
" የሀጅ ዋሃ ከዶላር አንፃር የ4,921 ዶላር ቅናሽ እንዲደረግበት ቢደረግም በብር ግን ጭማሪ አሳይቷል " ሲል ገልጿል።
ጠቅላይ ምክር-ቤቱ የአገልግሎት ዋጋን በመቀነስ በዕቅድ የተያዙ ፕሮጀክቶችን በማጠፍና በሳውዲ የሚቀርበውን አገልግሎት ተመጣጣኝ እንዲሆን በማድረግ 108 ሺህ ብር ቅናሽ እንዲኖረው ማድረጉን አሳውቋል።
የዶላር ዋጋ ከፍ በማለቱ ግን ብሩ መጨመሩ ተገልጿል።
ባለፈው ዓመት ለአንድ ሀጅ ዋጋ አጠቃላይ ብር 329,000 እንደነበር ይወሳል።
@yasin_nuru @yasin_nuru
👍55❤11🤔6😱5
ለፈገግታ😁😁
ሙስሊም ወንድ ታክሲ ውስጥ ሂጃብ የለበሰችን ሴት ሲያይ👀😂
ሙስሊም መሆኑን ለማሳወቅ #በአላህ ፍቃድ ወራጅ አለ😁😁😁😂😂
እስቲ ጨምሩበት😂
@yasin_nuru @yasin_nuru
ሙስሊም ወንድ ታክሲ ውስጥ ሂጃብ የለበሰችን ሴት ሲያይ👀😂
ሙስሊም መሆኑን ለማሳወቅ #በአላህ ፍቃድ ወራጅ አለ😁😁😁😂😂
እስቲ ጨምሩበት😂
@yasin_nuru @yasin_nuru
😁251🤣94👍59🤔8👏7❤3
//ማነው ድሀ ጨዋ አይደለም ያለህ?//
♨አንድ ሀብታም ሰውዬ ወደ አንዲት ሊስትሮ ወደ ምትሳራ ብላቴና ሄደው ጫማ ማስጠረግ ጀመረ
🌻በመጀመሪያ ቀን በንቀት አይኑ እያየ አስጠርጎ ሄደ
🌻በሁለተኛ ቀንም ተመሳሳይ ፈት አሳይቶ ሄደ
🌻ሦስተኛ ቀን ልጅቷ ጫማውን እየጠረገች በስህተት ትንሽ ቀለም ካልሲ ላይ አደረገች በዚህ የተናደደው ሰውዬ በጣም ተሳድቦ ይቅርታ እያለችው ጥሏት ሄደ
ከትንሽ ደቂቃ ቡኋላ ተመልሶ መጣ ለካ ስልኩን ጥሎ ሂዶ ነበረ ከዛም ከትህትና ስልክ ጠፍቶብኝ ነው እዚህ ጥዬ ይሆን እንዴ ብሎ ይጠይቃል
ልጅቷ አዎ ስልኩ እዚህ አለ መጥቼ ልሰጥህ ፈልጌ ነበረ ግን የት እንደሄክ አላወኩም ትላለች
ሰውዬውም በልጅቷ ታማኝነት ተገርሞ ሀምሳ ብር ከኪሱ አውጥቶ ይሰጣታል
ልጅቷም እባክህ ጌታዬ አምስት ብር ጨምረህ ስጠኝ ትላለች
ሰውዬውም ያለ ምንም መቅመማት አውጥቶ ሰጣት
ልጅቷም ሀምሳ ብሩን መልሳ ሰጠች ምነው ላንቺ እኮ ነው ለታማኝነትሽ ብዬ ነው ይላታል
የታማኝነት ዋጋ ስንት ነው ትላለች
ሰውዬውም እኔ'ጃ ብሎ መለሰ
ልጅቷም አንተም ታማኝ ለመሆን ሞክር መርዳት ካለብህ ሰው መጀመሪያውኑ እርዳ አምስት ብሩ የሰራውት ብር ነው እኔ ታማኝነትን አልሸጥም ብላ ጥላው ሄደች
ሌላ ቀን መጥቶ ልጅቷን ቤት ብዙ ጫማዎች አሉኝ እቤት እንሂድ ብሏት ይዟት ሄደ
ከዛም እሷ ስራ እየሰራች እሱ ቤት ጥሏት ይሄደል። ቤት ውስጥ ጠረጴዛ ላይ ብዙ ብር አስቀምጦ እመጣለሁ ብሎ ይሄደል
ልጅቷም ብሩን ከጠረጼዛ አንስታ ጥሩ ቦታ ላይ አስቀመጠች
ሰውዬው ከሄደበት ቦታ መጥቶ ብሩን ጠረጴዛ ላይ ተመለከተ ብሩ እዛ አልነበረም ሰውዬውም ልጅቷን ጠርቶ እናንተ ድሆች መቼም ብር አይታችሁ ማለፍ አትችሉም አይደለም ባለፈው ታማኝ ነኝ ብለሽ ነበረ እኮ ብሎ ሰደባት
ልጅቷም አትሳሳት እኔ የድሀ ልጅ ድሀ ነኝ ድሀ የሆነ ሁሉ ሌባ ባለጌ አይደለም ሀብታም የሆነ ሁሉ ደግሞ ጨዋ አይደለም ስለዚህ ሰውን ሰው በመሆኑ ብቻ ቅረብ😡
አንድ ሰው መሆን የሚችለው ራሱን ብቻ ነው
አንድ ሰው ብዙ ሰው መሆን አይችልም
ስለዚህ በአንድ ሰው ስህተት ብዙ ሰዎችን አትሳደብ ስለ ሁሉም ነገር አመሰግናለሁ።
ብሩን እዚህ መጥፎ ቦታ ላይ አይቼ እዛ ጥሩ ቦታ አስቀምጨልሀለው ብላ ጥለው ሊትሄድ ስትል ሰውዬው መጥቶ ተንበርክኮ ይቅርታ ጠየቀ
ከዛም አብራው እንድትኖር ተማፀነ
ሰውን በልብሱ ወይንም በአቋሙ አይታችሁ አትፍረዱ ልብና ልብስ የተላያዩ ነገሮች ናቸዉ
ልብ የፈጣሪ ስጦታ ሲሆን ልብስ በብር የሚገዛ እቃ ነው ስለዚህ የፈጣሪን ስጦታ በብር ከሚገዛው እቃ ጋር አታወደድሩ
ቅንነት ለራስ ነው
ቅንነት መልሶ ይከፍላል
@yasin_nuru @yasin_nuru
♨አንድ ሀብታም ሰውዬ ወደ አንዲት ሊስትሮ ወደ ምትሳራ ብላቴና ሄደው ጫማ ማስጠረግ ጀመረ
🌻በመጀመሪያ ቀን በንቀት አይኑ እያየ አስጠርጎ ሄደ
🌻በሁለተኛ ቀንም ተመሳሳይ ፈት አሳይቶ ሄደ
🌻ሦስተኛ ቀን ልጅቷ ጫማውን እየጠረገች በስህተት ትንሽ ቀለም ካልሲ ላይ አደረገች በዚህ የተናደደው ሰውዬ በጣም ተሳድቦ ይቅርታ እያለችው ጥሏት ሄደ
ከትንሽ ደቂቃ ቡኋላ ተመልሶ መጣ ለካ ስልኩን ጥሎ ሂዶ ነበረ ከዛም ከትህትና ስልክ ጠፍቶብኝ ነው እዚህ ጥዬ ይሆን እንዴ ብሎ ይጠይቃል
ልጅቷ አዎ ስልኩ እዚህ አለ መጥቼ ልሰጥህ ፈልጌ ነበረ ግን የት እንደሄክ አላወኩም ትላለች
ሰውዬውም በልጅቷ ታማኝነት ተገርሞ ሀምሳ ብር ከኪሱ አውጥቶ ይሰጣታል
ልጅቷም እባክህ ጌታዬ አምስት ብር ጨምረህ ስጠኝ ትላለች
ሰውዬውም ያለ ምንም መቅመማት አውጥቶ ሰጣት
ልጅቷም ሀምሳ ብሩን መልሳ ሰጠች ምነው ላንቺ እኮ ነው ለታማኝነትሽ ብዬ ነው ይላታል
የታማኝነት ዋጋ ስንት ነው ትላለች
ሰውዬውም እኔ'ጃ ብሎ መለሰ
ልጅቷም አንተም ታማኝ ለመሆን ሞክር መርዳት ካለብህ ሰው መጀመሪያውኑ እርዳ አምስት ብሩ የሰራውት ብር ነው እኔ ታማኝነትን አልሸጥም ብላ ጥላው ሄደች
ሌላ ቀን መጥቶ ልጅቷን ቤት ብዙ ጫማዎች አሉኝ እቤት እንሂድ ብሏት ይዟት ሄደ
ከዛም እሷ ስራ እየሰራች እሱ ቤት ጥሏት ይሄደል። ቤት ውስጥ ጠረጴዛ ላይ ብዙ ብር አስቀምጦ እመጣለሁ ብሎ ይሄደል
ልጅቷም ብሩን ከጠረጼዛ አንስታ ጥሩ ቦታ ላይ አስቀመጠች
ሰውዬው ከሄደበት ቦታ መጥቶ ብሩን ጠረጴዛ ላይ ተመለከተ ብሩ እዛ አልነበረም ሰውዬውም ልጅቷን ጠርቶ እናንተ ድሆች መቼም ብር አይታችሁ ማለፍ አትችሉም አይደለም ባለፈው ታማኝ ነኝ ብለሽ ነበረ እኮ ብሎ ሰደባት
ልጅቷም አትሳሳት እኔ የድሀ ልጅ ድሀ ነኝ ድሀ የሆነ ሁሉ ሌባ ባለጌ አይደለም ሀብታም የሆነ ሁሉ ደግሞ ጨዋ አይደለም ስለዚህ ሰውን ሰው በመሆኑ ብቻ ቅረብ😡
አንድ ሰው መሆን የሚችለው ራሱን ብቻ ነው
አንድ ሰው ብዙ ሰው መሆን አይችልም
ስለዚህ በአንድ ሰው ስህተት ብዙ ሰዎችን አትሳደብ ስለ ሁሉም ነገር አመሰግናለሁ።
ብሩን እዚህ መጥፎ ቦታ ላይ አይቼ እዛ ጥሩ ቦታ አስቀምጨልሀለው ብላ ጥለው ሊትሄድ ስትል ሰውዬው መጥቶ ተንበርክኮ ይቅርታ ጠየቀ
ከዛም አብራው እንድትኖር ተማፀነ
ሰውን በልብሱ ወይንም በአቋሙ አይታችሁ አትፍረዱ ልብና ልብስ የተላያዩ ነገሮች ናቸዉ
ልብ የፈጣሪ ስጦታ ሲሆን ልብስ በብር የሚገዛ እቃ ነው ስለዚህ የፈጣሪን ስጦታ በብር ከሚገዛው እቃ ጋር አታወደድሩ
ቅንነት ለራስ ነው
ቅንነት መልሶ ይከፍላል
@yasin_nuru @yasin_nuru
👍169🥰24❤22💯14👏8
ቲክቶክ ላይ ዩትዩብ ላይ አንዳንድ ወንድሞች
አንድ ሰው የተሳሳተ መንገድ ላይ ሆኖ ስታዩት
እሱን ለማተካከል ከፈለጋችሁ አደብ ባለው መልኩ ለብቻው ምከሩት።
እኛ ወንጀላችን አጠገባችን ሰው የማያስቀርብ ሆኖ ሳለ ሌላ ሰውን ግን አጥረግርገን የምንሰድብበት፤ተውበት እንዲያረግ ሳይሆን በወንጀሉ እንዲገፋ በሚያረግ በቁጣ የምንናገራቸው እኛ ማን ሆነን ነው?
ስንመክር በአደብ ለብቻ ይሁን አልመለስም ካሉ እንግዲህ ምንም ማረግ አንችልም በማስገደድ አይሆንም። ነብዩ ሙሳ እንኳ ፊርዓውንን እንኳ እንዴት ነው አናግር የተባሉት እኔ ጌታ ነኝ ያለውን።
ስለዚህ እኛ ከሙሳ በልጠን ነው በአደባባይ ክብራቸውን ዝቅ እያደረግን የምንናገረው🤔 በግድ እንዲ ካልሆናቹ የምንለው? ከልባችሁ ዱዓ አድርጉላቸው
የባሳ ለመበላሸታቸው ሰበብ አትሁኑ ዱአ አድርጉላቸው በየኮሜንቱም እየገባችሁ መጥፎ ነገር የምትፅፉ አላህ እንዲመልሳቸው ዱዓ አድርጉላቸው። ይሄን ማድረግ #ካልቻላችሁ_ዝም_በሉ።
ቲክቶክ ላይ ከእስልምናችሁ ጋር የማይሄድ ነገር የምትሰሩ ይቅርባችሁ ሞት ቢመጣ ዋጋ ያስከፍላቹሃል። የእስልምና እምነት ተከታይ ስለሆናችሁ የእስልምና ወገኖቻችሁ የናንተን ቪድዮ ሲያዩ ይረበሻሉ እና እንተም የዚች አለም ነገር ሳያሳስባችሁ ወደ እስልምናችሁ ተመለሱ አላህ አያሳፍራችሁም የምትፈልጉትን ይሰጣቹሃል ተመለሱ ወደ አላህ።
አላህ ሁላችንንም ወደ እሱ ይመልሰን።
@yasin_nuru @yasin_nuru
አንድ ሰው የተሳሳተ መንገድ ላይ ሆኖ ስታዩት
እሱን ለማተካከል ከፈለጋችሁ አደብ ባለው መልኩ ለብቻው ምከሩት።
እኛ ወንጀላችን አጠገባችን ሰው የማያስቀርብ ሆኖ ሳለ ሌላ ሰውን ግን አጥረግርገን የምንሰድብበት፤ተውበት እንዲያረግ ሳይሆን በወንጀሉ እንዲገፋ በሚያረግ በቁጣ የምንናገራቸው እኛ ማን ሆነን ነው?
ስንመክር በአደብ ለብቻ ይሁን አልመለስም ካሉ እንግዲህ ምንም ማረግ አንችልም በማስገደድ አይሆንም። ነብዩ ሙሳ እንኳ ፊርዓውንን እንኳ እንዴት ነው አናግር የተባሉት እኔ ጌታ ነኝ ያለውን።
ስለዚህ እኛ ከሙሳ በልጠን ነው በአደባባይ ክብራቸውን ዝቅ እያደረግን የምንናገረው🤔 በግድ እንዲ ካልሆናቹ የምንለው? ከልባችሁ ዱዓ አድርጉላቸው
የባሳ ለመበላሸታቸው ሰበብ አትሁኑ ዱአ አድርጉላቸው በየኮሜንቱም እየገባችሁ መጥፎ ነገር የምትፅፉ አላህ እንዲመልሳቸው ዱዓ አድርጉላቸው። ይሄን ማድረግ #ካልቻላችሁ_ዝም_በሉ።
ቲክቶክ ላይ ከእስልምናችሁ ጋር የማይሄድ ነገር የምትሰሩ ይቅርባችሁ ሞት ቢመጣ ዋጋ ያስከፍላቹሃል። የእስልምና እምነት ተከታይ ስለሆናችሁ የእስልምና ወገኖቻችሁ የናንተን ቪድዮ ሲያዩ ይረበሻሉ እና እንተም የዚች አለም ነገር ሳያሳስባችሁ ወደ እስልምናችሁ ተመለሱ አላህ አያሳፍራችሁም የምትፈልጉትን ይሰጣቹሃል ተመለሱ ወደ አላህ።
አላህ ሁላችንንም ወደ እሱ ይመልሰን።
@yasin_nuru @yasin_nuru
❤105👍43👏15💯7🕊4
ፈጣሪህን ብቻ አታስቀይም እንጂ ... ሰዉኮ ብታዝለዉም እግሬ ለምን ተንጠለጠለ... የሚል ፍጡር ነዉ🥺🥺
ትክክል ነው?
የኡመር(ረ.ዐ) እና የአህያው ታሪክ ትዝ አለኝ
@yasin_nuru @yasin_nuru
👍110❤36💯15