ኢራን በኳታር እና በኢራቅ በሚገኙ የአሜሪካ የጦር ሰፈሮች ላይ የሚሳኤል ጥቃት ሰነዘረች
ኢራን ቅዳሜ እለት በኒውክሌር ጣቢያዎቿ ላይ ለተፈፀመባት ጥቃት የአፀፋ ምላሽ ለመስጠት በኳታር እና ኢራቅ በሚገኙ የአሜሪካ አየር ሰፈሮች ሚሳኤሎችን መተኮሷን የመንግስት ሚዲያ ዘግቧል።
ኳታር በአሜሪካ ቁጥጥር ስር በሚገኘው የአል ኡዴይድ ጦር ሰፈር ላይ የደረሰውን ጥቃት አረጋግጣ ድርጊቱን "ጥሰት" በማለት በቀጥታ ምላሽ የመስጠት መብቷ የተጠበቀ መሆኑን ተናግራለች። ኳታር ለጊዜው የአየር ክልሏን የዘጋች ሲሆን የአሜሪካ እና የዩናይትድ ኪንግደም ዜጎችም ደህንነቱ በተጠበቀ ስፍራ እንዲጠለሉ ተነግሯቸዋል።
ፔንታጎን አል ኡዴይድ ከኢራን በተተኮሱ የአጭር እና መካከለኛ ርቀት ባለስቲክ ሚሳኤሎች መጠቃቱን አረጋግጧል። አንድ የመከላከያ ባለስልጣን በጥቃቱ እስካሁን የአሜሪካን ጉዳት የደረሰበትን ሪፖርት አለመኖሩን ተናግረዋል። የመከላከያ ባለስልጣናት አሁንም ሁኔታውን እየተከታተሉ መሆኑን እና መረጃ በሚገኝበት ጊዜ ተጨማሪ መረጃ እንደሚሰጡ ተናግረዋል።
በስምኦን ደረጄ
#ዳጉ_ጆርናል
ኢራን ቅዳሜ እለት በኒውክሌር ጣቢያዎቿ ላይ ለተፈፀመባት ጥቃት የአፀፋ ምላሽ ለመስጠት በኳታር እና ኢራቅ በሚገኙ የአሜሪካ አየር ሰፈሮች ሚሳኤሎችን መተኮሷን የመንግስት ሚዲያ ዘግቧል።
ኳታር በአሜሪካ ቁጥጥር ስር በሚገኘው የአል ኡዴይድ ጦር ሰፈር ላይ የደረሰውን ጥቃት አረጋግጣ ድርጊቱን "ጥሰት" በማለት በቀጥታ ምላሽ የመስጠት መብቷ የተጠበቀ መሆኑን ተናግራለች። ኳታር ለጊዜው የአየር ክልሏን የዘጋች ሲሆን የአሜሪካ እና የዩናይትድ ኪንግደም ዜጎችም ደህንነቱ በተጠበቀ ስፍራ እንዲጠለሉ ተነግሯቸዋል።
ፔንታጎን አል ኡዴይድ ከኢራን በተተኮሱ የአጭር እና መካከለኛ ርቀት ባለስቲክ ሚሳኤሎች መጠቃቱን አረጋግጧል። አንድ የመከላከያ ባለስልጣን በጥቃቱ እስካሁን የአሜሪካን ጉዳት የደረሰበትን ሪፖርት አለመኖሩን ተናግረዋል። የመከላከያ ባለስልጣናት አሁንም ሁኔታውን እየተከታተሉ መሆኑን እና መረጃ በሚገኝበት ጊዜ ተጨማሪ መረጃ እንደሚሰጡ ተናግረዋል።
በስምኦን ደረጄ
#ዳጉ_ጆርናል
ዲሞክራቲክ ኮንጎ የኮባልት የውጪ ንግድ እገዳን በ3 ወራት አራዘመች
የዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ መንግስት የኮባልት ኤክስፖርት ጊዜያዊ እገዳን ለተጨማሪ ሶስት ወራት አራዝሟል፣ ለዚህም የሰጠው ምክንያት በአለም ገበያ ላይ ያለውን የምርቱን የተትረፈረፈ አቅርቦት በመጥቀስ ነው። የስትራቴጂክ ማዕድን ንጥረነገሮች ገበያ ቁጥጥር ባለስልጣን በሰጠው መግለጫ “የእገዳው መራዘም ያስፈለገው በገበያው ላይ ያለው ከፍተኛ የአክሲዮን መጠን በመቀጠሉ ነው” ብሏል።
ኤጀንሲው የተራዘመው እገዳ ከማብቃቱ በፊት ሁኔታውን ለመገምገም እና አዲስ ውሳኔ ለመስጠት ማቀዱን ይህም እርምጃው እንዲስተካከል፣ እንዲራዘም ወይም እንዲነሳ ሊያደርግ እንደሚችልም ገልጿል። እ.ኤ.አ. በፌብሩዋሪ 22 ላይ የተጣለው የመጀመሪያው የአራት ወራት እገዳ አለም አቀፍ የኮባልት ዋጋን ለማረጋጋት፣ በማዕድኑ አቅርቦት ሰንሰለት ውስጥ ግልፅነትን ለመጨመር እና የሀገር ውስጥ ማጣሪያ እና እሴት ጨምሮ የመላክ ሂደትን ለማበረታታት ያለመ ነበር።
ዲሞክራቲክ ኮንጎ ከ 70 በመቶ በላይ የሚሆነውን የዓለም ኮባልት የምታመርት ሲሆን ይህው ውድ ሀብት የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪ ባትሪዎች እና ሌሎች ከፍተኛ የቴክኖሎጂ መተግበሪያዎችን ለማቅረብ ወሳኝ አካል እንደሆነ መረጃዎች ያሳያሉ።
በስምኦን ደረጄ
#ዳጉ_ጆርናል
የዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ መንግስት የኮባልት ኤክስፖርት ጊዜያዊ እገዳን ለተጨማሪ ሶስት ወራት አራዝሟል፣ ለዚህም የሰጠው ምክንያት በአለም ገበያ ላይ ያለውን የምርቱን የተትረፈረፈ አቅርቦት በመጥቀስ ነው። የስትራቴጂክ ማዕድን ንጥረነገሮች ገበያ ቁጥጥር ባለስልጣን በሰጠው መግለጫ “የእገዳው መራዘም ያስፈለገው በገበያው ላይ ያለው ከፍተኛ የአክሲዮን መጠን በመቀጠሉ ነው” ብሏል።
ኤጀንሲው የተራዘመው እገዳ ከማብቃቱ በፊት ሁኔታውን ለመገምገም እና አዲስ ውሳኔ ለመስጠት ማቀዱን ይህም እርምጃው እንዲስተካከል፣ እንዲራዘም ወይም እንዲነሳ ሊያደርግ እንደሚችልም ገልጿል። እ.ኤ.አ. በፌብሩዋሪ 22 ላይ የተጣለው የመጀመሪያው የአራት ወራት እገዳ አለም አቀፍ የኮባልት ዋጋን ለማረጋጋት፣ በማዕድኑ አቅርቦት ሰንሰለት ውስጥ ግልፅነትን ለመጨመር እና የሀገር ውስጥ ማጣሪያ እና እሴት ጨምሮ የመላክ ሂደትን ለማበረታታት ያለመ ነበር።
ዲሞክራቲክ ኮንጎ ከ 70 በመቶ በላይ የሚሆነውን የዓለም ኮባልት የምታመርት ሲሆን ይህው ውድ ሀብት የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪ ባትሪዎች እና ሌሎች ከፍተኛ የቴክኖሎጂ መተግበሪያዎችን ለማቅረብ ወሳኝ አካል እንደሆነ መረጃዎች ያሳያሉ።
በስምኦን ደረጄ
#ዳጉ_ጆርናል
በእስራኤል ኢራን ውጥረት ዙሪያ ትንታኔውን
ከጋዜጠኛ ሚሊዮን ሙሴ እና ስምኦን ደረጄ ይመልከቱ
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
https://youtu.be/SUqCVs3MXf4?si=f2OYdsn7uOPosB31
#ዳጉ_ጆርናል
ከጋዜጠኛ ሚሊዮን ሙሴ እና ስምኦን ደረጄ ይመልከቱ
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
https://youtu.be/SUqCVs3MXf4?si=f2OYdsn7uOPosB31
#ዳጉ_ጆርናል
Forwarded from ዳጉ ጆርናል-ስፖርት (Beⓒk)
በዋልታ ቴሌቪዥን የስፖርት ጋዜጠኝነት የምናዉቀዉ አብዱ መሐመድም ስለ ድሬዳዋ እና ስሁል ሽረ የጨዋታ ማጭበር በፌስቡክ ገጹ ላይ የጻፈዉን ዳጉ ጆርናል ስፖርት እንደሚከተለዉ ያቀርበዋል።
"300ሺ ኢንቨስት አድርገው 27 ሚሊዮን ብር በአንድ ቀን ሰርተው ያደሩ" ሰዎች አሉ ይለናል ጋዜጠኛዉ
"ይህን ኳስ የሞከረው አጥቂ መስሎህ ሙከራውን ብታደንቅ አይፈረድብህም:: እውነታው ግን የስሑል ሽረ ተከላካይ ራሱ ላይ ለማስቆጠር ነው ይህን የመሰለ ግሩም ሙከራ ያደረገው:: ግብ ጠባቂው ሚስኪን ነገሩ አልገባው ተዋደቀኮ😂 የጉድ ሃገር!
ዮኒ"almost የአጥቂ ኳስ ነው የሞከረው.... explain ለማድረግ የሚያስቸግር ይመስለኛል" የማርክ Markos Elias ሳቅ...
300ሺ ኢንቨስት አድርገው 27 ሚሊዮን ብር በአንድ ቀን ሰርተው ያደሩ ታታሪ ባለሙያዎችን የያዘ ውብ እግር ኳስ ነውኮ ያለን 😂😂😂" ሲል ትዝብቱን አስፍሯል።
#ዳጉ_ጆርናል_ጆርናል
"300ሺ ኢንቨስት አድርገው 27 ሚሊዮን ብር በአንድ ቀን ሰርተው ያደሩ" ሰዎች አሉ ይለናል ጋዜጠኛዉ
"ይህን ኳስ የሞከረው አጥቂ መስሎህ ሙከራውን ብታደንቅ አይፈረድብህም:: እውነታው ግን የስሑል ሽረ ተከላካይ ራሱ ላይ ለማስቆጠር ነው ይህን የመሰለ ግሩም ሙከራ ያደረገው:: ግብ ጠባቂው ሚስኪን ነገሩ አልገባው ተዋደቀኮ😂 የጉድ ሃገር!
ዮኒ"almost የአጥቂ ኳስ ነው የሞከረው.... explain ለማድረግ የሚያስቸግር ይመስለኛል" የማርክ Markos Elias ሳቅ...
300ሺ ኢንቨስት አድርገው 27 ሚሊዮን ብር በአንድ ቀን ሰርተው ያደሩ ታታሪ ባለሙያዎችን የያዘ ውብ እግር ኳስ ነውኮ ያለን 😂😂😂" ሲል ትዝብቱን አስፍሯል።
#ዳጉ_ጆርናል_ጆርናል
የኮሎምቢያ ጦር 57 ወታደሮቹ በኮኬን ምርት በሚታወቀዉ አካባቢ በሲቪሎች መታገታቸዉን አስታወቀ
በደቡብ ምዕራብ ተራራማ አካባቢ ከ50 በላይ ወታደሮች በሲቪሎች መያዛቸውን የኮሎምቢያ ጦር አስታዉቋል።ቅዳሜ እለት በኤል ታምቦ ውስጥ በተደረገ ኦፕሬሽን የወታደሮቹ ቡድን በቁጥጥር ስር የዋለው ሚካይ ካንየን ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ሲሆን ፣ የኮኬይን ምርት ቁልፍ ቀጠና እና በሀገሪቱ የፀጥታ ችግር ባለበት ስፍራ መሆኑ ታዉቋል፡፡
እሁድ እለት፣ ሌላ የወታደር ቡድን እዚያው ክልል ወደምትገኘው ኤል ፕላቴዶ ከተማ ሲያመሩ ቢያንስ በ200 ነዋሪዎች ተከበዋልል።ሁለቱም አፈናዎች በድምሩ አራት መኮንኖች እና 53 ፕሮፌሽናል ወታደሮች መታገታቸዉን ጦሩ አስታዉቋል፡፡
በደቡብ ምዕራብ ወታደራዊ እንቅስቃሴዎችን የሚመራው ጄኔራል ፌዴሪኮ አልቤርቶ ሜጂያ ማህበረሰቡን "ሰርገው የገቡ" አማፂያን "ጠለፋ" መሆኑን በቪዲዮ ላይ አክለዋል።የኮሎምቢያ ጦር በክልሉ ውስጥ ያሉ ሲቪሎች በ 2016 ከመንግስት ጋር የሰላም ስምምነት አካል ለመሆን ፈቃደኛ ያልሆነው የኮሎምቢያ አብዮታዊ ጦር ሃይሎች ዋና ተቃዋሚ ቡድን ከማዕከላዊ ጄኔራል ስታፍ ትዕዛዝ እንደሚቀበሉ አረጋግጠዋል ።
በስምኦን ደረጄ
#ዳጉ_ጆርናል
በደቡብ ምዕራብ ተራራማ አካባቢ ከ50 በላይ ወታደሮች በሲቪሎች መያዛቸውን የኮሎምቢያ ጦር አስታዉቋል።ቅዳሜ እለት በኤል ታምቦ ውስጥ በተደረገ ኦፕሬሽን የወታደሮቹ ቡድን በቁጥጥር ስር የዋለው ሚካይ ካንየን ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ሲሆን ፣ የኮኬይን ምርት ቁልፍ ቀጠና እና በሀገሪቱ የፀጥታ ችግር ባለበት ስፍራ መሆኑ ታዉቋል፡፡
እሁድ እለት፣ ሌላ የወታደር ቡድን እዚያው ክልል ወደምትገኘው ኤል ፕላቴዶ ከተማ ሲያመሩ ቢያንስ በ200 ነዋሪዎች ተከበዋልል።ሁለቱም አፈናዎች በድምሩ አራት መኮንኖች እና 53 ፕሮፌሽናል ወታደሮች መታገታቸዉን ጦሩ አስታዉቋል፡፡
በደቡብ ምዕራብ ወታደራዊ እንቅስቃሴዎችን የሚመራው ጄኔራል ፌዴሪኮ አልቤርቶ ሜጂያ ማህበረሰቡን "ሰርገው የገቡ" አማፂያን "ጠለፋ" መሆኑን በቪዲዮ ላይ አክለዋል።የኮሎምቢያ ጦር በክልሉ ውስጥ ያሉ ሲቪሎች በ 2016 ከመንግስት ጋር የሰላም ስምምነት አካል ለመሆን ፈቃደኛ ያልሆነው የኮሎምቢያ አብዮታዊ ጦር ሃይሎች ዋና ተቃዋሚ ቡድን ከማዕከላዊ ጄኔራል ስታፍ ትዕዛዝ እንደሚቀበሉ አረጋግጠዋል ።
በስምኦን ደረጄ
#ዳጉ_ጆርናል
በተለያዩ ግለሰቦች የተዘረፉ ከ 10 ሚሊየን ብር በላይ የሚያወጡ የመጠጥ ውሃማስተላለፊያ ትቦዎች በቁጥጥር ስር ዋለ
በምስራቅ ሀረርጌ ዞን ግራዋ ወረዳ የግራዋ ወረዳ አስተዳደር ውሀ ማዕድን እና ኢነርጂ ፅህፈት ቤት ንብረት የሆኑ ከ10 ሚሊየን ብር በላይ የሚያወጡ እና በተለያዩ ግለሰቦች የተዘረፉ የመጠጥ ውሀ ማስተላለፊያ ቱቦዎች በቁጥጥር ስር በማዋል ለመንግስት ገቢ ማስመለሱን የግራዋ ወረዳ አቃቤ ህግ ፅህፈት ቤት ገልጿል።
ብስራት ሬዲዮ ከግራዋ ወረዳ አቃቤ ህግ ፅህፈት ቤት ባገኘዉ መረጃ መሰረት ንብረትነቱ የግራዋ ወረዳ የውሀ ማዕድን እና ኢነርጂ ፅህፈት ቤት የሆኑ እና ለገጠር ቀበሌዎች የንፁህ መጠጥ ውሀ ለማዳረስ በተዘረጋው እቅድ መሠረት የተከማቹ የመጠጥ ውሀ ቱቦዎች በተለያዩ ግለሰቦች የመዘረፋቸው ሪፖርቱ ለፖሊስ እና አቃቤ ህግ በደረሰው መረጃ መሠረት በተደረገ ድንገተኛ ፍተሻ ከ10 ሚሊየን ብር በላይ የሚያወጡ የውሀ ቱቦዎች ከተለያዩ ጎለሰብ መኖሪያ ቤቶች ተሰባስበው በንብረት አስተዳደር መመሪያ መሠረት ለግምጃ ቤት ገቢ እንዲሆኑ መደረጉን ፅህፈት ቤቱ ገልጿል።
ከተለያዩ ግለሰቦች እጅ የተገኙት በርካታ የውሀ ቱቦዎች 10 ሚሊየን 662 ሺህ 380 ብር እንደሚያወጣ የገለፀው ፅህፈት ቤቱ የመጠጥ ውሀ ቱቦዎች ዘረፋ ላይ የተሰማሩ ግለሰቦች ላይ በማስረጃ የተጠናከረ ምርመራ በማድረግ በቅርብ ቀን ለፍትህ ለማቅረብ እየተሰራ እንደሚገኝ የግራዋ ወረዳ አቃቤ ህግ ፅህፈት ቤት መግለጫ አመላክቷል።
በሰመኃር አለባቸዉ
#ዳጉ_ጆርናል
በምስራቅ ሀረርጌ ዞን ግራዋ ወረዳ የግራዋ ወረዳ አስተዳደር ውሀ ማዕድን እና ኢነርጂ ፅህፈት ቤት ንብረት የሆኑ ከ10 ሚሊየን ብር በላይ የሚያወጡ እና በተለያዩ ግለሰቦች የተዘረፉ የመጠጥ ውሀ ማስተላለፊያ ቱቦዎች በቁጥጥር ስር በማዋል ለመንግስት ገቢ ማስመለሱን የግራዋ ወረዳ አቃቤ ህግ ፅህፈት ቤት ገልጿል።
ብስራት ሬዲዮ ከግራዋ ወረዳ አቃቤ ህግ ፅህፈት ቤት ባገኘዉ መረጃ መሰረት ንብረትነቱ የግራዋ ወረዳ የውሀ ማዕድን እና ኢነርጂ ፅህፈት ቤት የሆኑ እና ለገጠር ቀበሌዎች የንፁህ መጠጥ ውሀ ለማዳረስ በተዘረጋው እቅድ መሠረት የተከማቹ የመጠጥ ውሀ ቱቦዎች በተለያዩ ግለሰቦች የመዘረፋቸው ሪፖርቱ ለፖሊስ እና አቃቤ ህግ በደረሰው መረጃ መሠረት በተደረገ ድንገተኛ ፍተሻ ከ10 ሚሊየን ብር በላይ የሚያወጡ የውሀ ቱቦዎች ከተለያዩ ጎለሰብ መኖሪያ ቤቶች ተሰባስበው በንብረት አስተዳደር መመሪያ መሠረት ለግምጃ ቤት ገቢ እንዲሆኑ መደረጉን ፅህፈት ቤቱ ገልጿል።
ከተለያዩ ግለሰቦች እጅ የተገኙት በርካታ የውሀ ቱቦዎች 10 ሚሊየን 662 ሺህ 380 ብር እንደሚያወጣ የገለፀው ፅህፈት ቤቱ የመጠጥ ውሀ ቱቦዎች ዘረፋ ላይ የተሰማሩ ግለሰቦች ላይ በማስረጃ የተጠናከረ ምርመራ በማድረግ በቅርብ ቀን ለፍትህ ለማቅረብ እየተሰራ እንደሚገኝ የግራዋ ወረዳ አቃቤ ህግ ፅህፈት ቤት መግለጫ አመላክቷል።
በሰመኃር አለባቸዉ
#ዳጉ_ጆርናል
እስራኤል የኢራንን ስጋትነት በማስወገዳችን በትራምፕ የተኩስ አቁም ሀሳብ ተስማምተናል አለች
የእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስትር ፅህፈት ቤት በትራምፕ የተኩስ አቁም ስምምነት ላይ መግለጫ አውጥቷል። ኔታንያሁ ተቀብለውታል ሲል ይፋ አድርጓል። የእስራኤል መንግስት በኢራን ላይ ያደረሰውን ጥቃት “ዓላማውን” በማሳካቱ የተኩስ አቁም ሃሳብን ተቀብያለሁ ብሏል።
በመግለጫው መሰረት እስራኤል የኢራንን “ሁለት ፈጣን የህልውና ስጋት” የሆኑትን ከኒውክሌር ጦር መሳሪያ እና ባለስቲክ ሚሳኤሎች አስወግዳለች። በተጨማሪም እስራኤል "በወታደራዊ አመራር ላይ ከፍተኛ ጉዳት አድርሳለች፣ እንዲሁም በደርዘን የሚቆጠሩ የኢራን መንግስት ኢላማዎችን አውድማለች" ብሏል። መግለጫው በመቀጠል የእስራኤል ሃይሎች በመጨረሻው ቀን በቴህራን እምብርት የመንግስት ኢላማዎችን ክፉኛ በመምታት በመቶዎች የሚቆጠሩ የባሲጅ ኦፕሬተሮችን በማስወገድ የኢራን መንግስት ተቃውሞዎችን ለማፈን ብዙ ጊዜ የሚጠቀመው ሚሊሻ እና "ሌላ ከፍተኛ የኒውክሌር ሳይንቲስትን ያስወግዳል" ብሏል።
"እስራኤል ፕሬዝዳንት ትራምፕን እና አሜሪካን በመከላከያ ላደረጉት ድጋፍ እና የኢራንን የኒውክሌር ስጋትን ለማስወገድ ላሳዩት ተሳትፎ ምስጋና አቅርበዋል" ሲል መግለጫው አክሎ ገልጿል።የኢራን መንግስት ሚዲያ እንደዘገበው ኢራን የተኩስ አቁም ስምምነት ተግባራዊ ከመሆኑ በፊት የመጨረሻ ዙር ሚሳኤሎችን ወደ እስራኤል ተኩሳለች። በጥቃቱ ቢያንስ አራት ሰዎችን ተገድለዋል። የኢራን መንግስት ቲቪም በእስራኤል ላይ ኢራን ከፈፀመችው የጥቃት ማዕበል በኋላ የተኩስ አቁም ስምምነት ተጥሏል ሲል ዘግቧል።
በስምኦን ደረጄ
#ዳጉ_ጆርናል
የእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስትር ፅህፈት ቤት በትራምፕ የተኩስ አቁም ስምምነት ላይ መግለጫ አውጥቷል። ኔታንያሁ ተቀብለውታል ሲል ይፋ አድርጓል። የእስራኤል መንግስት በኢራን ላይ ያደረሰውን ጥቃት “ዓላማውን” በማሳካቱ የተኩስ አቁም ሃሳብን ተቀብያለሁ ብሏል።
በመግለጫው መሰረት እስራኤል የኢራንን “ሁለት ፈጣን የህልውና ስጋት” የሆኑትን ከኒውክሌር ጦር መሳሪያ እና ባለስቲክ ሚሳኤሎች አስወግዳለች። በተጨማሪም እስራኤል "በወታደራዊ አመራር ላይ ከፍተኛ ጉዳት አድርሳለች፣ እንዲሁም በደርዘን የሚቆጠሩ የኢራን መንግስት ኢላማዎችን አውድማለች" ብሏል። መግለጫው በመቀጠል የእስራኤል ሃይሎች በመጨረሻው ቀን በቴህራን እምብርት የመንግስት ኢላማዎችን ክፉኛ በመምታት በመቶዎች የሚቆጠሩ የባሲጅ ኦፕሬተሮችን በማስወገድ የኢራን መንግስት ተቃውሞዎችን ለማፈን ብዙ ጊዜ የሚጠቀመው ሚሊሻ እና "ሌላ ከፍተኛ የኒውክሌር ሳይንቲስትን ያስወግዳል" ብሏል።
"እስራኤል ፕሬዝዳንት ትራምፕን እና አሜሪካን በመከላከያ ላደረጉት ድጋፍ እና የኢራንን የኒውክሌር ስጋትን ለማስወገድ ላሳዩት ተሳትፎ ምስጋና አቅርበዋል" ሲል መግለጫው አክሎ ገልጿል።የኢራን መንግስት ሚዲያ እንደዘገበው ኢራን የተኩስ አቁም ስምምነት ተግባራዊ ከመሆኑ በፊት የመጨረሻ ዙር ሚሳኤሎችን ወደ እስራኤል ተኩሳለች። በጥቃቱ ቢያንስ አራት ሰዎችን ተገድለዋል። የኢራን መንግስት ቲቪም በእስራኤል ላይ ኢራን ከፈፀመችው የጥቃት ማዕበል በኋላ የተኩስ አቁም ስምምነት ተጥሏል ሲል ዘግቧል።
በስምኦን ደረጄ
#ዳጉ_ጆርናል
ከሌላ ወንድ ጋር እጮኝነት ጀምራለች በሚል የገዛ እጮኛውን በጩቤ ወግቶ የገደለው ግለሰብ በእስራት ተቀጣ
በኮንሶ ዞን ከነ ወረዳ ፋሻ ቀበሌ ልዩ ስሙ ኮቶላ ወንዝ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ግንቦት 3 ቀን 2017 ዓ.ም የወንጀል ድርጊቱን ፈጽሟል፡፡
ኩሻቦ ኩራዎ የተባለው ግለሰብ የገዛ እጮኛው የሆነችውን መምህርት ተዋበች ኩሲያን የተባለችውን እንስት ከሌላ ወንድ ጋር እጮኝነት ጀምራለች በሚል ጥርጣሬ በአሰቃቂ ሁኔታ በጩቤ ደጋግሞ ወግቶ መግደሉን ተከትሎ በቁጥጥር ስር ውሏል።
ፖሊስም በተከሳሹ ላይ የምርመራ መዝገብ በማጣራት ለኮንሶ ዞን ፍትህ መምሪያ የላከ ሲሆን የምርመራ መዝገብ የደረሰው የኮንሶ ዞን ዐቃቤ ህግም በተከሳሽ ላይ ክስ መስርቶ ለኮንሶ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት ይልካል።
የኮንሶ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤትም ከዐቃቤ ህግ የደረሰው ክስ ሲመረምር ከቆየ በኃላ ሰኔ 13 ቀን 2017 ዓ.ም በዋለው ችሎት ተከሳሽ ኩሻቦ ኩራዎ በፈፀመው የግድያ ወንጀል ጥፋተኛ ነው በማለት ተከሳሽን ያርማል ሌሎችም ያስተምራል በማለት በ25 ዓመት ፅኑ እስራት እንዲቀጣ ወስኗል።
ተከሳሹ ወንጀሉን የፈጸመው ማለዳ ሰው በደንብ በማይንቀሳቀስበት ብሎም በአሳቻ ሰዓትና ስፍራ በመሆኑና የወንጀሉ አፈፃፀም አሰቃቂ በመሆኑ ምክንያት ቅጣቱን እንዳከበደው ብስራት ከኮንሶ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት ያገኘው መረጃ ያሳያል።
በሰብል አበበ
#ዳጉ_ጆርናል
በኮንሶ ዞን ከነ ወረዳ ፋሻ ቀበሌ ልዩ ስሙ ኮቶላ ወንዝ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ግንቦት 3 ቀን 2017 ዓ.ም የወንጀል ድርጊቱን ፈጽሟል፡፡
ኩሻቦ ኩራዎ የተባለው ግለሰብ የገዛ እጮኛው የሆነችውን መምህርት ተዋበች ኩሲያን የተባለችውን እንስት ከሌላ ወንድ ጋር እጮኝነት ጀምራለች በሚል ጥርጣሬ በአሰቃቂ ሁኔታ በጩቤ ደጋግሞ ወግቶ መግደሉን ተከትሎ በቁጥጥር ስር ውሏል።
ፖሊስም በተከሳሹ ላይ የምርመራ መዝገብ በማጣራት ለኮንሶ ዞን ፍትህ መምሪያ የላከ ሲሆን የምርመራ መዝገብ የደረሰው የኮንሶ ዞን ዐቃቤ ህግም በተከሳሽ ላይ ክስ መስርቶ ለኮንሶ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት ይልካል።
የኮንሶ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤትም ከዐቃቤ ህግ የደረሰው ክስ ሲመረምር ከቆየ በኃላ ሰኔ 13 ቀን 2017 ዓ.ም በዋለው ችሎት ተከሳሽ ኩሻቦ ኩራዎ በፈፀመው የግድያ ወንጀል ጥፋተኛ ነው በማለት ተከሳሽን ያርማል ሌሎችም ያስተምራል በማለት በ25 ዓመት ፅኑ እስራት እንዲቀጣ ወስኗል።
ተከሳሹ ወንጀሉን የፈጸመው ማለዳ ሰው በደንብ በማይንቀሳቀስበት ብሎም በአሳቻ ሰዓትና ስፍራ በመሆኑና የወንጀሉ አፈፃፀም አሰቃቂ በመሆኑ ምክንያት ቅጣቱን እንዳከበደው ብስራት ከኮንሶ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት ያገኘው መረጃ ያሳያል።
በሰብል አበበ
#ዳጉ_ጆርናል
ታሪፍ ላይ ተመጣጣኝ ማሻሻያ ካልተደረገ የፈሳሽ ጭነት ማጓጓዣ ባለንብረቶች ከገበያ ዉጪ ለመሆን እንገደዳለን አሉ
የኢትዮጵያ የፈሳሽ ጭነት ማጓጓዣ ባለንብረቶች ማህበር ባደረገዉ ስብሰባ የማህበሩ አባላት እራሳቸውን ማስተዳደር የማይችሉበት ደረጃ ላይ መድረሳቸውንና ታሪፍ ላይ ተመጣጣኝ ማሻሻያ ካልተደረገ ከገበያ ዉጪ ለመሆን እንደሚገደዱ ብስራት ሬዲዮ ሰምቷል ።
የማህበሩ ፕሬዝዳንት አቶ ፀጋ አሳመረ ለብስራት ሬዲዮ እንደተናገሩት ከሆነ የታሪፍ ጭማሪ የጎማ ፣የነዳጅና የገበያ ሁኔታ ታይቶ በዓመት አንድ ጊዜ የሚከናወን ሲሆን እንደየሁኔታው ደግሞ በየስድስት ወሩ ጭማሪ እንዲደረግ የሚጠይቅ መመሪያ መኖሩን ገልፀዋል ። ለእነዚህ የፈሳሽ ጭነት ማጓጓዣዎች የታሪፍ ጭማሪ ከተደረገ ሀምሌ ወር ሲመጣ ሁለት ዓመት እንደሚያስቆጥር የማህበሩ ፕሬዝዳንት ተናግረዋል ።
ከማህበሩ አባላት ፣ከኢትዮጵያ ነዳጅ ቁጥጥርና ድርጅት ባለስልጣን ፣ከትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር እና ከንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር ሁለት ሁለት አባላት በመወከል ስምንት ሰዎች ጊዜያዊ የዋጋ ግሽበትን የሚመለከት ጥናት አድርገዉ ለነዳጅ ቁጥጥር ባለስልጣንና ለንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር ሚኒስትር ደኤታ የቀረበ ሲሆን የታሪፍ ጭማሪ እንደሚደረግ ቢገለፅም እስካሁን ምንም አይነት ጭማሪ አለመደረጉ ተነግሯል ።
ከዶላር ጭማሪ ጋር ተያይዞ የሚደረጉ ግብይቶች በሙሉ ጭማሪ ያሳዩ ሲሆን አምና 40ሺህ ብር የነበረዉ ጎማ ዘንድሮ 75ሺህ ብር ነዉ። የዘይት ፣የመለዋወጫ እና የሹፌሮችም ደሞዝ በዚህ መልኩ መጨመሩ ተገልጿል ። ባለፉት ዓመታት የተመዘገበዉን የኢኮኖሚ እድገት ተከትሎ የነዳጅ ስርጭት ፍላጎት ለሟሟላት ከጊዜ ወደ ጊዜ በዘርፉ ላይ የሚሰማሩ ተሽከርካሪዎች ቁጥር እያደገ በአሁኑ ሰዓት ከ4700 በላይ ቦቴ ተሽከርካሪዎች በ59 የነዳጅ ኩባንያዎች ዉስጥ አገልግሎት እየሰጡ ይገኛሉ።
ዘርፉ ለሀገሪቱ ኢኮኖሚ ከፍተኛ ድርሻ ያለዉ ቢሆንም በዘርፉ የተሰማሩ ባለንብረቶች ጠንካራ አደረጃጀት የሌላቸው በመሆኑ ከመንግሥት ጋር በሚደረግ የታሪፍ ዝግጅት ፣ድርድሮችና ኢንዱስትሪውን አስመልክቶ በሚወጡ ህጎች ላይ የበኩላቸዉን ድርሻ ለማበርከትና እንደ የአስፈላጊነቱ የፖሊሲ ምክረ ሀሳብ ለማቅረብ የሚቻልበትን ሁኔታ ለመፍጠር ማህበሩ በአዲስ መልክ ተቋቁሞ ስራ ከጀመረ ሁለት ዓመታት ማሰቆጠሩን አቶ ፀጋ ተናግረዋል ።
በመባ ወርቅነህ
#ዳጉ_ጆርናል
የኢትዮጵያ የፈሳሽ ጭነት ማጓጓዣ ባለንብረቶች ማህበር ባደረገዉ ስብሰባ የማህበሩ አባላት እራሳቸውን ማስተዳደር የማይችሉበት ደረጃ ላይ መድረሳቸውንና ታሪፍ ላይ ተመጣጣኝ ማሻሻያ ካልተደረገ ከገበያ ዉጪ ለመሆን እንደሚገደዱ ብስራት ሬዲዮ ሰምቷል ።
የማህበሩ ፕሬዝዳንት አቶ ፀጋ አሳመረ ለብስራት ሬዲዮ እንደተናገሩት ከሆነ የታሪፍ ጭማሪ የጎማ ፣የነዳጅና የገበያ ሁኔታ ታይቶ በዓመት አንድ ጊዜ የሚከናወን ሲሆን እንደየሁኔታው ደግሞ በየስድስት ወሩ ጭማሪ እንዲደረግ የሚጠይቅ መመሪያ መኖሩን ገልፀዋል ። ለእነዚህ የፈሳሽ ጭነት ማጓጓዣዎች የታሪፍ ጭማሪ ከተደረገ ሀምሌ ወር ሲመጣ ሁለት ዓመት እንደሚያስቆጥር የማህበሩ ፕሬዝዳንት ተናግረዋል ።
ከማህበሩ አባላት ፣ከኢትዮጵያ ነዳጅ ቁጥጥርና ድርጅት ባለስልጣን ፣ከትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር እና ከንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር ሁለት ሁለት አባላት በመወከል ስምንት ሰዎች ጊዜያዊ የዋጋ ግሽበትን የሚመለከት ጥናት አድርገዉ ለነዳጅ ቁጥጥር ባለስልጣንና ለንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር ሚኒስትር ደኤታ የቀረበ ሲሆን የታሪፍ ጭማሪ እንደሚደረግ ቢገለፅም እስካሁን ምንም አይነት ጭማሪ አለመደረጉ ተነግሯል ።
ከዶላር ጭማሪ ጋር ተያይዞ የሚደረጉ ግብይቶች በሙሉ ጭማሪ ያሳዩ ሲሆን አምና 40ሺህ ብር የነበረዉ ጎማ ዘንድሮ 75ሺህ ብር ነዉ። የዘይት ፣የመለዋወጫ እና የሹፌሮችም ደሞዝ በዚህ መልኩ መጨመሩ ተገልጿል ። ባለፉት ዓመታት የተመዘገበዉን የኢኮኖሚ እድገት ተከትሎ የነዳጅ ስርጭት ፍላጎት ለሟሟላት ከጊዜ ወደ ጊዜ በዘርፉ ላይ የሚሰማሩ ተሽከርካሪዎች ቁጥር እያደገ በአሁኑ ሰዓት ከ4700 በላይ ቦቴ ተሽከርካሪዎች በ59 የነዳጅ ኩባንያዎች ዉስጥ አገልግሎት እየሰጡ ይገኛሉ።
ዘርፉ ለሀገሪቱ ኢኮኖሚ ከፍተኛ ድርሻ ያለዉ ቢሆንም በዘርፉ የተሰማሩ ባለንብረቶች ጠንካራ አደረጃጀት የሌላቸው በመሆኑ ከመንግሥት ጋር በሚደረግ የታሪፍ ዝግጅት ፣ድርድሮችና ኢንዱስትሪውን አስመልክቶ በሚወጡ ህጎች ላይ የበኩላቸዉን ድርሻ ለማበርከትና እንደ የአስፈላጊነቱ የፖሊሲ ምክረ ሀሳብ ለማቅረብ የሚቻልበትን ሁኔታ ለመፍጠር ማህበሩ በአዲስ መልክ ተቋቁሞ ስራ ከጀመረ ሁለት ዓመታት ማሰቆጠሩን አቶ ፀጋ ተናግረዋል ።
በመባ ወርቅነህ
#ዳጉ_ጆርናል
በአዲስ አበባ በመኖሪያ ግቢ በተሰራ የፍሳሽ ማጠራቀሚያ ታንከር ዉስጥ እድሜዉ 7 ዓመት የሆነ ታዳጊ ህይወቱ አለፈ
ትላንትና ሰኔ 16 ቀን 2017 ዓ.ም ከሰዓት በኋላ በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ-ከተማ ወረዳ 14 ጋርመንት አካባቢ በመኖሪያ ግቢ ውስጥ በተሰራው የፍሳሽ ማጠራቀሚያ ታንከር ዉስጥ እድሜዉ 7 ዓመት የሆነ ታዳጊ ህይወቱ ማለፉን የእሳትና አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን አስታውቋል።
ታዳጊዉ ህይወቱ ያለፈበት ምክንያት የፍሳሽ ማጠራቀሚያ ታንከር ምንም ዓይነት ከለላ ያልተደረገለትና የታንከሩ ክዳንም ክፍቱን የነበረ መሆኑን የኮሚሽኑ የህዝብ ግንኙነት ባለሙያ አቶ ንጋቱ ማሞ ለብስራት ሬድዮ ተናግረዋል ።
በጋራና በተለያዩ መኖሪያ ቤቶች ቅጥር ጊቢ ዉስጥና አካባቢ የታዳጊዎች ጨዋታና እንቅስቃሴ የሚኖር በመሆኑ አካባቢው ምቹ መደረግ እንዳለባቸው ኮሚሽኑ አሳስቧል።
በመሰል ቦታዎች እና ቅጥር ጊቢ ውስጥ የሚገኙ የፍሳሽ ማጠራቀሚያ ታንከሮች ላይ በቂ ከለላና ክዳን በማድረግ ቸልተኝነትን በማስወገድ ሊያጋጥሙ የሚችሉ አደጋዎችን አስቀድሞ መከላከል ይገባል።
ከዚህ ቀደምም በቂርቆስ ክፍለ-ከተማ መስቀል ፍላወር አካባቢ በመኖሪያ አፓርታማ ቅጥር ጊቢ ዉስጥ እና በአዲስ ከተማ ክፍለ-ከተማ አዲሱ ሚካኤል አካባቢ ባለ ኮንደሚኒየም ጊቢ ዉስጥ ክዳንና መከለያ ባልተደረገበት የፍስሽ ማጠራቀሚያ ታንከር ዉስጥ ሁለት ታዳጊዎች ገብተዉ ህይወታቸዉ ማለፉ ይታወሳል።
በትግስት ላቀው
#ዳጉ_ጆርናል
ትላንትና ሰኔ 16 ቀን 2017 ዓ.ም ከሰዓት በኋላ በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ-ከተማ ወረዳ 14 ጋርመንት አካባቢ በመኖሪያ ግቢ ውስጥ በተሰራው የፍሳሽ ማጠራቀሚያ ታንከር ዉስጥ እድሜዉ 7 ዓመት የሆነ ታዳጊ ህይወቱ ማለፉን የእሳትና አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን አስታውቋል።
ታዳጊዉ ህይወቱ ያለፈበት ምክንያት የፍሳሽ ማጠራቀሚያ ታንከር ምንም ዓይነት ከለላ ያልተደረገለትና የታንከሩ ክዳንም ክፍቱን የነበረ መሆኑን የኮሚሽኑ የህዝብ ግንኙነት ባለሙያ አቶ ንጋቱ ማሞ ለብስራት ሬድዮ ተናግረዋል ።
በጋራና በተለያዩ መኖሪያ ቤቶች ቅጥር ጊቢ ዉስጥና አካባቢ የታዳጊዎች ጨዋታና እንቅስቃሴ የሚኖር በመሆኑ አካባቢው ምቹ መደረግ እንዳለባቸው ኮሚሽኑ አሳስቧል።
በመሰል ቦታዎች እና ቅጥር ጊቢ ውስጥ የሚገኙ የፍሳሽ ማጠራቀሚያ ታንከሮች ላይ በቂ ከለላና ክዳን በማድረግ ቸልተኝነትን በማስወገድ ሊያጋጥሙ የሚችሉ አደጋዎችን አስቀድሞ መከላከል ይገባል።
ከዚህ ቀደምም በቂርቆስ ክፍለ-ከተማ መስቀል ፍላወር አካባቢ በመኖሪያ አፓርታማ ቅጥር ጊቢ ዉስጥ እና በአዲስ ከተማ ክፍለ-ከተማ አዲሱ ሚካኤል አካባቢ ባለ ኮንደሚኒየም ጊቢ ዉስጥ ክዳንና መከለያ ባልተደረገበት የፍስሽ ማጠራቀሚያ ታንከር ዉስጥ ሁለት ታዳጊዎች ገብተዉ ህይወታቸዉ ማለፉ ይታወሳል።
በትግስት ላቀው
#ዳጉ_ጆርናል
የወራቤ ዩኒቨርሲቲ ከ90 በመቶ በላይ ተማሪዎችን በመውጫ ፈተና ማለፋቸዉን አስታወቀ
ወራቤ ዩኒቨርሲቲ በ2017 ዓ.ም የመውጫ ፈተና ካስፈተናቸው ተማሪዎች 90 ከመቶ ማሳለፋቸዉን የወራቤ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት የሆኑት ዶክተር ቶፊቅ ጀማል ለብስራት ሬዲዮ ተናግረዋል።
ከዚህ በፊት የመውጫ ፈተና ሲጀመር ፈተናው ያለፉ ተማሪዎች በ2015 62 በመቶ፣ በ2016 ደግሞ 84 በመቶ የነበረ ሲሆን የዘንድሮው ዓመት ጥሩ መሻሻል የታየበት መሆኑን ገልጸዋል። አክለው በፈተና ሰዓት ላይ የአሌክትሪክ መቋረጥ አጋጥሞ የነበረ መሆኑን በመግለጽ ይህ ባይፈጠፍ ኖሮ ከዚህ በላይ ከፍ ማለት ይችል እንደነበረም አንስተዋል።
በዚህም በመጀመሪያ እና ሁለተኛ ዲግሪ ትምህርታቸውን ሲከታተሉ ከነበሩት የሚጠበቅባቸውን ውጤት ያስመዘገቡ ተማሪዎች ዲግሪ አጽድቋል።በተጨማሪም በቀጣይ የትምህርት ዘመን የቱሪዝም እና የሆቴል ማኔጅመንት ትምህርት ክፍል እንዲከፈት ስርዓተ-ትምህርት ጸድቋል።
ወራቤ የቱሪስት መዳረሻ መሆን የምትችል ከተማ በመሆኗ የዲፓርተመንቱ መካተት አስፈላጊ መሆኑ እና በየደረጃው ተከልሶ የተገመገመ የአምስት ትምህርት ክፍሎች ስርዓተ ትምህርትም በሴኔቱ መጽደቁ ተጠቁሟል።ወራቤ ዩኒቨርሲቲ ከመማር ማስተማር ባለፈ የተለያዩ የአካባቢውን ማህበረሰብ የሚረዱ ስራዎች እያከናወነ ይገኛል።
በዚህም ለአርሶ አደሩ የሚጠቅሙ የዘር ማሻሸያዎችን በምርምር ማቅረብ እንዲሁም ቅዳሜ እና እሁድ የዩኒቨርሲቲ መምህራን በየአካባቢው ባሉ ትምህርት ቤቶች በመሄድ የማጠናከሪያ ትምህርት እንዲሰጡ እንደሚደረግ የወራቤ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ዶክተር ቶፊቅ ጀማል ጨምረው ለብስራት ሬዲዮ ተናግረዋል።
በኤደን ሽመልስ
#ዳጉ_ጆርናል
ወራቤ ዩኒቨርሲቲ በ2017 ዓ.ም የመውጫ ፈተና ካስፈተናቸው ተማሪዎች 90 ከመቶ ማሳለፋቸዉን የወራቤ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት የሆኑት ዶክተር ቶፊቅ ጀማል ለብስራት ሬዲዮ ተናግረዋል።
ከዚህ በፊት የመውጫ ፈተና ሲጀመር ፈተናው ያለፉ ተማሪዎች በ2015 62 በመቶ፣ በ2016 ደግሞ 84 በመቶ የነበረ ሲሆን የዘንድሮው ዓመት ጥሩ መሻሻል የታየበት መሆኑን ገልጸዋል። አክለው በፈተና ሰዓት ላይ የአሌክትሪክ መቋረጥ አጋጥሞ የነበረ መሆኑን በመግለጽ ይህ ባይፈጠፍ ኖሮ ከዚህ በላይ ከፍ ማለት ይችል እንደነበረም አንስተዋል።
በዚህም በመጀመሪያ እና ሁለተኛ ዲግሪ ትምህርታቸውን ሲከታተሉ ከነበሩት የሚጠበቅባቸውን ውጤት ያስመዘገቡ ተማሪዎች ዲግሪ አጽድቋል።በተጨማሪም በቀጣይ የትምህርት ዘመን የቱሪዝም እና የሆቴል ማኔጅመንት ትምህርት ክፍል እንዲከፈት ስርዓተ-ትምህርት ጸድቋል።
ወራቤ የቱሪስት መዳረሻ መሆን የምትችል ከተማ በመሆኗ የዲፓርተመንቱ መካተት አስፈላጊ መሆኑ እና በየደረጃው ተከልሶ የተገመገመ የአምስት ትምህርት ክፍሎች ስርዓተ ትምህርትም በሴኔቱ መጽደቁ ተጠቁሟል።ወራቤ ዩኒቨርሲቲ ከመማር ማስተማር ባለፈ የተለያዩ የአካባቢውን ማህበረሰብ የሚረዱ ስራዎች እያከናወነ ይገኛል።
በዚህም ለአርሶ አደሩ የሚጠቅሙ የዘር ማሻሸያዎችን በምርምር ማቅረብ እንዲሁም ቅዳሜ እና እሁድ የዩኒቨርሲቲ መምህራን በየአካባቢው ባሉ ትምህርት ቤቶች በመሄድ የማጠናከሪያ ትምህርት እንዲሰጡ እንደሚደረግ የወራቤ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ዶክተር ቶፊቅ ጀማል ጨምረው ለብስራት ሬዲዮ ተናግረዋል።
በኤደን ሽመልስ
#ዳጉ_ጆርናል
በኦሮሚያ ክልል በአንድ ሳምንት ውስጥ በደረሰ የትራፊክ አደጋ የ10 ሰዎች ህይወት አለፈ
በኦሮሚያ ክልል ከሰኔ 9 እስከ ሰኔ 15 ቀን 2017 ዓ.ም ድረስ ባሉት ቀናቶች በደረሱ የትራፊክ አደጋዎች የ10 ሰዎች ህይወት ሲያልፍ ፣በ15 ሰዎች ላይ ከባድ እና በ8 ሰዎች ላይ ቀላል አካል ጉዳት ደርሷል፡፡የሞት አደጋዎቹ በተለያዩ ዞኖች እና ከተሞች የተከሰቱ ናቸው።
በአንድ ሳምንት ውስጥ በደረሰው አደጋ ከ6 ዓመት እስከ 44 ዓመት የእድሜ ክልል ላይ የሚገኙ ሰዎች ህይወታቸው ማለፉን የኦሮሚያ ክልል የትራፊክ ቁጥጥር ክፍል ባለሙያ የሆኑት ኢንስፔክተር መሰለ አበራ ለብስራት ሬዲዮና ቴሌቪዥን ተናግረዋል፡፡
አደጋዎቹ የተከሰቱት በቀኑ እና በለሊቱ ክፍለ ጊዜ ሲሆን አደጋውን ያደረሱት ወንድ አሽከርካሪዎች ናቸው። የሞት አደጋዎች የደረሱት በጭነት፣በቤት ተሽከርካሪ፣ በህዝብ ማመላለሻ እና በባለ ሦስት እግር (ባጃጅ) የተከሰቱ መሆናቸው ተገልጿል፡፡
የአደጋዎቹ መንስኤዎቹ ከፍጥነት ወሰን በላይ ማሽከርከር እና ለእግረኛ ቅድሚያ አለመስጠት እና ያለ መንጃ ፍቃድ ማሽከርከር መሆኑን ኢንስፔክተር መሰለ አበራ ለብስራት ሬዲዮና ቴሌቪዥን ተናግረዋል፡፡
በሳምራዊት ስዩም
#ዳጉ_ጆርናል
በኦሮሚያ ክልል ከሰኔ 9 እስከ ሰኔ 15 ቀን 2017 ዓ.ም ድረስ ባሉት ቀናቶች በደረሱ የትራፊክ አደጋዎች የ10 ሰዎች ህይወት ሲያልፍ ፣በ15 ሰዎች ላይ ከባድ እና በ8 ሰዎች ላይ ቀላል አካል ጉዳት ደርሷል፡፡የሞት አደጋዎቹ በተለያዩ ዞኖች እና ከተሞች የተከሰቱ ናቸው።
በአንድ ሳምንት ውስጥ በደረሰው አደጋ ከ6 ዓመት እስከ 44 ዓመት የእድሜ ክልል ላይ የሚገኙ ሰዎች ህይወታቸው ማለፉን የኦሮሚያ ክልል የትራፊክ ቁጥጥር ክፍል ባለሙያ የሆኑት ኢንስፔክተር መሰለ አበራ ለብስራት ሬዲዮና ቴሌቪዥን ተናግረዋል፡፡
አደጋዎቹ የተከሰቱት በቀኑ እና በለሊቱ ክፍለ ጊዜ ሲሆን አደጋውን ያደረሱት ወንድ አሽከርካሪዎች ናቸው። የሞት አደጋዎች የደረሱት በጭነት፣በቤት ተሽከርካሪ፣ በህዝብ ማመላለሻ እና በባለ ሦስት እግር (ባጃጅ) የተከሰቱ መሆናቸው ተገልጿል፡፡
የአደጋዎቹ መንስኤዎቹ ከፍጥነት ወሰን በላይ ማሽከርከር እና ለእግረኛ ቅድሚያ አለመስጠት እና ያለ መንጃ ፍቃድ ማሽከርከር መሆኑን ኢንስፔክተር መሰለ አበራ ለብስራት ሬዲዮና ቴሌቪዥን ተናግረዋል፡፡
በሳምራዊት ስዩም
#ዳጉ_ጆርናል
በህገወጥ መንገድ ሲዘዋወር የነበረ ከ8ሺህ ሊትር በላይ ናፍጣ ተያዘ
በወላይታ ዞን ዳሞት ሶሬ ወረዳ ፖሊስ ባደረገው ድንገተኛ ፍተሻ በሕገወጥ መንገድ ሲዘዋወር የነበረ 8ሺ ሊትር በላይ በቁጥር በ34 የዉሃ መያዣ ታንከር የተከማቸ ናፍጣ በቁጥጥር ሥር ማድረጉን የወረዳው ፖሊሲ አስታውቋል::
አንድ ህገ ወጥና የተጨብረበረ የንግድ ደረሰኝ የያዘ የሰሌዳ ቁጥር ET-86230 ኮድ 3 የሆነ ሲኖትራክ የጭነት መኪና ከወላይታ ሶዶ ወደ ዳውሮ ዞን ሲሄድ ድንገተኛ ፍተሻ መደረጉ ተገልጿል።
በተደረገው ድንገተኛ ፍተሻ ከንጋቱ 12:00 አከባቢ ሕጋዊ ያልሆነውን የናፍጣ ግዥ ሰነድ ሕጋዊ በማስመሰልና የተለያዩ የተጨብረበሩ ሰነዶችን በመያዝ ለማለፍ ሲሞክር ሊያዝ ችሏል።
በህገወጥ መንገድ ናፍጣ የተጫነበት ሲኖትራክ የጭነት ተሽከርካሪ በወረዳው በዶጌ ማሽዶ ቀበሌ ለፍተሻ በወጡት ፖሊስ አባላት ክትትል ቁጥጥር ሥር መዋሉንየደቡብ ኢትዮጵያ ፖሊስ ኮሚሽን ህዝብ ግንኙነት እና ገጽታ ግንባታ ዳይሬክተር ምክትል ኮማንደር አሸናፊ ኃይሌ ለብስራት ሬዲዮ ተናግረዋል።
በሳምራዊት ስዩም
#ዳጉ_ጆርናል
በወላይታ ዞን ዳሞት ሶሬ ወረዳ ፖሊስ ባደረገው ድንገተኛ ፍተሻ በሕገወጥ መንገድ ሲዘዋወር የነበረ 8ሺ ሊትር በላይ በቁጥር በ34 የዉሃ መያዣ ታንከር የተከማቸ ናፍጣ በቁጥጥር ሥር ማድረጉን የወረዳው ፖሊሲ አስታውቋል::
አንድ ህገ ወጥና የተጨብረበረ የንግድ ደረሰኝ የያዘ የሰሌዳ ቁጥር ET-86230 ኮድ 3 የሆነ ሲኖትራክ የጭነት መኪና ከወላይታ ሶዶ ወደ ዳውሮ ዞን ሲሄድ ድንገተኛ ፍተሻ መደረጉ ተገልጿል።
በተደረገው ድንገተኛ ፍተሻ ከንጋቱ 12:00 አከባቢ ሕጋዊ ያልሆነውን የናፍጣ ግዥ ሰነድ ሕጋዊ በማስመሰልና የተለያዩ የተጨብረበሩ ሰነዶችን በመያዝ ለማለፍ ሲሞክር ሊያዝ ችሏል።
በህገወጥ መንገድ ናፍጣ የተጫነበት ሲኖትራክ የጭነት ተሽከርካሪ በወረዳው በዶጌ ማሽዶ ቀበሌ ለፍተሻ በወጡት ፖሊስ አባላት ክትትል ቁጥጥር ሥር መዋሉንየደቡብ ኢትዮጵያ ፖሊስ ኮሚሽን ህዝብ ግንኙነት እና ገጽታ ግንባታ ዳይሬክተር ምክትል ኮማንደር አሸናፊ ኃይሌ ለብስራት ሬዲዮ ተናግረዋል።
በሳምራዊት ስዩም
#ዳጉ_ጆርናል
እስራኤል እና አሜሪካ በኢራን ላይ የነበራቸውን የጦርነት አላማ ማሳካት አልቻሉም ተባለ
በቴህራን የመካከለኛው ምስራቅ ስትራቴጂክ ጥናት ማዕከል ተመራማሪ የሆኑት አባስ አስላኒ እንዳሉት እስራኤል በጋዛ እና ሊባኖስ የተኩስ አቁም ስምምነቶችን ለማድረግ በምትወስንበት ጊዜ ጥሩ ታሪክ ስለሌላት ኢራን ወደ ተኩስ አቁም እየተቃረበች ያለችው በጥንቃቄ ነው።
"ለዚያም ነው ቴህራን ጠንቃቃ የምትሆነው እና ባለሥልጣናቱ በይፋ ለማረጋገጥ በፍጥነት ወደፊቱ አልወጡም ። በጊዜ ሂደት ምንም ጥሰት ከሌለ ኢራን የተኩስ አቁም ስምምነትን የምታከብር ይመስለኛል" ሲሉ ለአልጀዚራ ተናግረዋል።አስላኒ ይህ በኢራን እና በእስራኤል እና በአጋሯ ዩናይትድ ስቴትስ መካከል የተደረገ ጦርነት መሆኑን ገልፀው ሁለቱ አጋሮች ግባቸውን የኢራን የኒውክሌር መርሃ ግብር ማፍረስ እና በኢራን ውስጥ "የአገዛዝ ለውጥ" በማምጣት ያልተሳካ ጦርነት ነው ብለዋል ።
"በኢራን የኒውክሌር መሥሪያ ቤቶች ላይ ጉዳት መድረሱን አይተናል፣ ነገር ግን የሀገሪቱ የኒውክሌር መርሃ ግብር በእነዚያ መገልገያዎች እና መሳሪያዎች ላይ ብቻ አይደለም፣ ኢራን የኒውክሌር ቁሳቁሶቿን ወደ አስተማማኝ ቦታ አዛውራለች፣ እውቀቷም ያልተነካ ነው "በማለት እስራኤል እንደመታችው የኢራን የሚሳኤል አቅምም አልጠፋም ሲሉ ተደምጠዋል። አስላኒ የኒውክሌር ድርድር በቀጠለበት ወቅት ዩናይትድ ስቴትስ እና እስራኤል ኢራንን ስላጠቁ "ትርጉም ያለው" ከአሜሪካ ጋር የሚደረገው ድርድር በአጭር ጊዜ ውስጥ ሊከናወን አይችልም ብለዋል።
ሁሉም ሀገራት በግጭቱ ድል እንደተጎናጸፉ እየተናገሩ ይገኛል፡፡ሁለቱም ወገኖች የተኩስ አቁምን የሚያከብሩበት ምክንያት አላቸው።እስራኤል ኦፕሬሽን Rising Lion ብላ የሰየመችውን የዘመቻውን ስኬት በተመለከተ ስትናገር የኢራንን ኒውክሌር እና ወታደራዊ አቅም በእጅጉ ጎድቷል፣ ከፍተኛ የጦር ባለስልጣናትን እና ሳይንቲስቶችን ገድሏል ትላለች።
ከዚህ በተጨማሪም በርካታ የአሜሪካ ፕሬዚዳንቶች ለማድረግ ፈቃደኛ ያልነበሩትን ጥቃት እንዲፈጽሙ ትራምፕን ማሳመን ችላለች።የተኩስ አቁም ስምምነቱ ለሁለት ዓመታት ያህል ከቆየ ጦርነት በኋላ በተዳከሙት እስራኤላውያን ላይ የሚደርሰውን ጫና ከፍተኛ ነዉ፡፡ ለኢራን፣ በአስር ሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎች በተፈናቀሉበት የማያቋርጥ የቦምብ ጥቃት ውስጥ ለነበረው ህዝብ እፎይታ ነው። አሁን ላይ የወደሙትን አንዳንድ የመሠረተ ልማት አውታሮችን ጨምሮ፣ ከባድ የኢኮኖሚ ቀውስ ውስጥ የሚጥላት ሲሆን በዓለም አቀፍ ደረጃ ከፍተኛ ማዕቀብ የተጣለባት በመሆኑ ረጅም መንገድ ይጠብቃታል፡፡
በስምኦን ደረጄ
#ዳጉ_ጆርናል
በቴህራን የመካከለኛው ምስራቅ ስትራቴጂክ ጥናት ማዕከል ተመራማሪ የሆኑት አባስ አስላኒ እንዳሉት እስራኤል በጋዛ እና ሊባኖስ የተኩስ አቁም ስምምነቶችን ለማድረግ በምትወስንበት ጊዜ ጥሩ ታሪክ ስለሌላት ኢራን ወደ ተኩስ አቁም እየተቃረበች ያለችው በጥንቃቄ ነው።
"ለዚያም ነው ቴህራን ጠንቃቃ የምትሆነው እና ባለሥልጣናቱ በይፋ ለማረጋገጥ በፍጥነት ወደፊቱ አልወጡም ። በጊዜ ሂደት ምንም ጥሰት ከሌለ ኢራን የተኩስ አቁም ስምምነትን የምታከብር ይመስለኛል" ሲሉ ለአልጀዚራ ተናግረዋል።አስላኒ ይህ በኢራን እና በእስራኤል እና በአጋሯ ዩናይትድ ስቴትስ መካከል የተደረገ ጦርነት መሆኑን ገልፀው ሁለቱ አጋሮች ግባቸውን የኢራን የኒውክሌር መርሃ ግብር ማፍረስ እና በኢራን ውስጥ "የአገዛዝ ለውጥ" በማምጣት ያልተሳካ ጦርነት ነው ብለዋል ።
"በኢራን የኒውክሌር መሥሪያ ቤቶች ላይ ጉዳት መድረሱን አይተናል፣ ነገር ግን የሀገሪቱ የኒውክሌር መርሃ ግብር በእነዚያ መገልገያዎች እና መሳሪያዎች ላይ ብቻ አይደለም፣ ኢራን የኒውክሌር ቁሳቁሶቿን ወደ አስተማማኝ ቦታ አዛውራለች፣ እውቀቷም ያልተነካ ነው "በማለት እስራኤል እንደመታችው የኢራን የሚሳኤል አቅምም አልጠፋም ሲሉ ተደምጠዋል። አስላኒ የኒውክሌር ድርድር በቀጠለበት ወቅት ዩናይትድ ስቴትስ እና እስራኤል ኢራንን ስላጠቁ "ትርጉም ያለው" ከአሜሪካ ጋር የሚደረገው ድርድር በአጭር ጊዜ ውስጥ ሊከናወን አይችልም ብለዋል።
ሁሉም ሀገራት በግጭቱ ድል እንደተጎናጸፉ እየተናገሩ ይገኛል፡፡ሁለቱም ወገኖች የተኩስ አቁምን የሚያከብሩበት ምክንያት አላቸው።እስራኤል ኦፕሬሽን Rising Lion ብላ የሰየመችውን የዘመቻውን ስኬት በተመለከተ ስትናገር የኢራንን ኒውክሌር እና ወታደራዊ አቅም በእጅጉ ጎድቷል፣ ከፍተኛ የጦር ባለስልጣናትን እና ሳይንቲስቶችን ገድሏል ትላለች።
ከዚህ በተጨማሪም በርካታ የአሜሪካ ፕሬዚዳንቶች ለማድረግ ፈቃደኛ ያልነበሩትን ጥቃት እንዲፈጽሙ ትራምፕን ማሳመን ችላለች።የተኩስ አቁም ስምምነቱ ለሁለት ዓመታት ያህል ከቆየ ጦርነት በኋላ በተዳከሙት እስራኤላውያን ላይ የሚደርሰውን ጫና ከፍተኛ ነዉ፡፡ ለኢራን፣ በአስር ሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎች በተፈናቀሉበት የማያቋርጥ የቦምብ ጥቃት ውስጥ ለነበረው ህዝብ እፎይታ ነው። አሁን ላይ የወደሙትን አንዳንድ የመሠረተ ልማት አውታሮችን ጨምሮ፣ ከባድ የኢኮኖሚ ቀውስ ውስጥ የሚጥላት ሲሆን በዓለም አቀፍ ደረጃ ከፍተኛ ማዕቀብ የተጣለባት በመሆኑ ረጅም መንገድ ይጠብቃታል፡፡
በስምኦን ደረጄ
#ዳጉ_ጆርናል
የህዝብና የመንግስትን ጥቅም መሰረት አድርገው ከተፈፀሙ ወንጀሎች ከ53 ሚሊዮን ብር በላይ ተመላሽ ማደረጉን የጉራጌ ዞን ፍትህ መምርያ አስታወቀ
የጉራጌ ዞን ፍትህ መምርያ ሊጠናቀቅ የሳምንታት እድሜ በቀረው የ2017 በጀት ዓመት ላይ የህዝብና የመንግስትን ጥቅም በማስመልከት ከተፈፀሙ ወንጀሎች ከፍተኛ ሀብት በተሳካ ሁኔታ ተመላሽ ማድረጉን አስታዉቋል፡፡
የፍትህ መምርያው የህዝብና የመንግስትን ጥቅም መሰረት አድርገው በተፈፀሙ ወንጀሎች ከወረዳ እስከ ፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት ባደረገው የፍታብሄር ክስ ክርክር 15 ሚሊየን 354 ሺ 497 ብር ገቢ ማድረግ የቻለ ሲሆን በድርድር ደግሞ 38 ሚሊየን 551 ሺህ 400 ብር በድምሩ 53 ሚሊየን 905 ሺህ 897 ብር ገቢ ለማድረግ መቻሉን የጉራጌ ዞን ፍትህ መምርያ ኃላፊ የሆኑት አቶ ኤልያስ ሰብለጋ ለብስራት ሬድዮ ተናግረዋል።
ኃላፊው አክለው በሙስና ነክ ወንጀሎች፣ ከሙስና ጋር በማጣመር በቀረቡ የፍታብሄር ክሶች አፈፃፀምም፤ በክስ 950 ሺ 265 ብር ፣ በምርመራ ሂደት ደግሞ 13 ሚሊዮን 646 ሺ 31 ብር በድምሩ 14 ሚሊየን 596 ሺ 297 ብር ገቢ ማድረግ ተችሏል ብለዋል።
ከዚህ በተጨማሪ በታክስና ኢኮኖሚ ነክ ወንጀሎች ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር በመቀናጀት በህገወጥ መንገድ ሲጓጓዙ የነበሩ ከ6.9 ሚሊዮን ብር በላይ ግምታዊ ዋጋ ያላቸው ንብረቶች ለመንግስት ገቢ ተደርገዋል ሲሉ የገለፁት አቶ ኤልያስ ውዝፍ የታክስ ዕዳ ከነበረባቸው ታክስ ከፋዮች ከገቢዎች መምሪያ ጋር በመቀናጀት በድርድር ከ8.1 ሚሊዮን ብር በላይ ገቢ ማድረግ መቻሉንም ጨምረው ለብስራት ተናግረዋል።
በሰብል አበበ
#ዳጉ_ጆርናል
የጉራጌ ዞን ፍትህ መምርያ ሊጠናቀቅ የሳምንታት እድሜ በቀረው የ2017 በጀት ዓመት ላይ የህዝብና የመንግስትን ጥቅም በማስመልከት ከተፈፀሙ ወንጀሎች ከፍተኛ ሀብት በተሳካ ሁኔታ ተመላሽ ማድረጉን አስታዉቋል፡፡
የፍትህ መምርያው የህዝብና የመንግስትን ጥቅም መሰረት አድርገው በተፈፀሙ ወንጀሎች ከወረዳ እስከ ፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት ባደረገው የፍታብሄር ክስ ክርክር 15 ሚሊየን 354 ሺ 497 ብር ገቢ ማድረግ የቻለ ሲሆን በድርድር ደግሞ 38 ሚሊየን 551 ሺህ 400 ብር በድምሩ 53 ሚሊየን 905 ሺህ 897 ብር ገቢ ለማድረግ መቻሉን የጉራጌ ዞን ፍትህ መምርያ ኃላፊ የሆኑት አቶ ኤልያስ ሰብለጋ ለብስራት ሬድዮ ተናግረዋል።
ኃላፊው አክለው በሙስና ነክ ወንጀሎች፣ ከሙስና ጋር በማጣመር በቀረቡ የፍታብሄር ክሶች አፈፃፀምም፤ በክስ 950 ሺ 265 ብር ፣ በምርመራ ሂደት ደግሞ 13 ሚሊዮን 646 ሺ 31 ብር በድምሩ 14 ሚሊየን 596 ሺ 297 ብር ገቢ ማድረግ ተችሏል ብለዋል።
ከዚህ በተጨማሪ በታክስና ኢኮኖሚ ነክ ወንጀሎች ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር በመቀናጀት በህገወጥ መንገድ ሲጓጓዙ የነበሩ ከ6.9 ሚሊዮን ብር በላይ ግምታዊ ዋጋ ያላቸው ንብረቶች ለመንግስት ገቢ ተደርገዋል ሲሉ የገለፁት አቶ ኤልያስ ውዝፍ የታክስ ዕዳ ከነበረባቸው ታክስ ከፋዮች ከገቢዎች መምሪያ ጋር በመቀናጀት በድርድር ከ8.1 ሚሊዮን ብር በላይ ገቢ ማድረግ መቻሉንም ጨምረው ለብስራት ተናግረዋል።
በሰብል አበበ
#ዳጉ_ጆርናል
የአዲስ አበባ የ8ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ውጤት ይፋ ሆነ
በአዲስ አበባ የ2017 የትምህርት ዘመን የ8ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ከወሰዱ ተማሪዎች መካከል 89 በመቶ ወደ ቀጣይ ክፍል ማለፋቸውን የአዲስ አበባ ትምህርት ቢሮ ገለፀ።
የትምህርት ቢሮ ኃላፊ ዶ/ር ዘላላሞ ሙላቱ ዛሬ ከሰዓት በሰጡት መግለጫ ዘንድሮ ከተፈተኑ 70 ሺህ 525 ተማሪዎች መካከል 62 ሺህ 639 ተማሪዎች ወደ 9ኛ ክፍል ተዛውረዋል ብለዋል።
እንደከተማ ከፍተኛ ውጤት ካስመዘገቡ 20 ተማሪዎች 13ቱ ከአዳሪ ትምህርት ቤት ሲሆኑ 3ቱ ከልዩ ልዩ ትምህርት ቤቶች መሆናቸውንም ጠቁመዋል።
ተፈተኝ ተማሪዎች በትምህርት ቢሮው የማህበራዊ ሚዲያ ውስጥ በሚገኘው ሊንክ ገብተው ውጤታቸውን መየት እንደሚችሉም በመግለጫው ተገልጿል።
የዘንድሮ የ8ኛ ክፍል ከፍተኛው ውጤት 97.3 ሆኖ ተመዝግቧል።
#ዳጉ_ጆርናል
በአዲስ አበባ የ2017 የትምህርት ዘመን የ8ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ከወሰዱ ተማሪዎች መካከል 89 በመቶ ወደ ቀጣይ ክፍል ማለፋቸውን የአዲስ አበባ ትምህርት ቢሮ ገለፀ።
የትምህርት ቢሮ ኃላፊ ዶ/ር ዘላላሞ ሙላቱ ዛሬ ከሰዓት በሰጡት መግለጫ ዘንድሮ ከተፈተኑ 70 ሺህ 525 ተማሪዎች መካከል 62 ሺህ 639 ተማሪዎች ወደ 9ኛ ክፍል ተዛውረዋል ብለዋል።
እንደከተማ ከፍተኛ ውጤት ካስመዘገቡ 20 ተማሪዎች 13ቱ ከአዳሪ ትምህርት ቤት ሲሆኑ 3ቱ ከልዩ ልዩ ትምህርት ቤቶች መሆናቸውንም ጠቁመዋል።
ተፈተኝ ተማሪዎች በትምህርት ቢሮው የማህበራዊ ሚዲያ ውስጥ በሚገኘው ሊንክ ገብተው ውጤታቸውን መየት እንደሚችሉም በመግለጫው ተገልጿል።
የዘንድሮ የ8ኛ ክፍል ከፍተኛው ውጤት 97.3 ሆኖ ተመዝግቧል።
#ዳጉ_ጆርናል
ኢራን የተኩስ አቁም ስምምነቱን በመጣሷ ከባድ ምላሽ ይጠብቃታል ስትል እስራኤል ዛተች
የእስራኤል መከላከያ ሚንስትር ኢዝራኤል ካትስ ባወጡት የእስራኤል መከላከያ ሰራዊት "ኢራን የተኩስ አቁምን በመጣሷ በቴህራን እምብርት ላይ ባሉ የአገዛዙ ኢላማዎች ላይ ከፍተኛ ጥቃት በመሰንዘር በሀይል ምላሽ እንዲሰጥ" ትዕዛዝ ሰጥተዋል፡፡
የኢራን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጥቃት የሚያቆመዉ እስራኤል ተመሳሳይ እርምጃ ከወሰደብ ብቻ እንደሆነ ቀደም ብሎ ተናግሯል።የእስራኤል ጦር ከኢራን የተወነጨፉ ሚሳኤሎችን ለይቻለሁ ሲል በዛሬዉ እለት አስታዉቋል፡፡የአየር መከላከያ ዘዴዎች ስጋቱን ለመጥለፍ እየሰሩ ሲሆን ሰዎች ወደ መጠለያ ገብተው እንዲቆዩ እየነገራቸው ይገኛል፡፡
የእስራኤል መከላከያ ሃይል (አይዲኤፍ) ዋና አዛዥ ወታደራዊው ኃይላችን ለኢራን ድርጊት "ከባድ ጥሰት" በማለት "የኃይል ምላሽ ይሰጣል" ብለዋል፡፡ኢያል ዛሚር እንደተናገሩት "በኢራን መንግስት የተካሄደውን የተኩስ አቁም ከፍተኛ ጥሰት ተከትሎ በኃይል ምላሽ እንሰጣለን" ሲሉ በኤክስ ገጻቸዉ ላይ ባወጡት መግለጫ ገልጸዋል፡፡
የኢራን መንግስት ሚዲያ ከተኩስ አቁም በኋላ በእስራኤል ላይ ሚሳኤል ተኮሰች የሚለውን ውንጀላ አስተባብሏል።የኢራን ታጣቂ ሃይሎች ለጠላት ጭካኔ አሳፋሪ እና አርአያነት ያለው ምላሽ መስጠቷን የገለጸችዉ ኢራን ትላንት ምሽት በኳታር በሚገኘው የአሜሪካ ጦር ሰፈር ላይ በደረሰው ጥቃት እና ጎህ ሲቀድ እስራኤል በሚሳኤል መመታቷን አስታዉቃለች፡፡የኢራን ከፍተኛ ብሄራዊ ደህንነት ምክር ቤት ቴህራን በግዛቷ ላይ ለደረሰው ጥቃት ተመጣጣኝ እና በጊዜ ምላሽ ሰጥታለች ያለ ሲሆን "ጠላትን በግዳጅ እንዲጸጸት እና ሽንፈትን እንዲቀበል አድርጓል" ብሏል።
በስምኦን ደረጄ
#ዳጉ_ጆርናል
የእስራኤል መከላከያ ሚንስትር ኢዝራኤል ካትስ ባወጡት የእስራኤል መከላከያ ሰራዊት "ኢራን የተኩስ አቁምን በመጣሷ በቴህራን እምብርት ላይ ባሉ የአገዛዙ ኢላማዎች ላይ ከፍተኛ ጥቃት በመሰንዘር በሀይል ምላሽ እንዲሰጥ" ትዕዛዝ ሰጥተዋል፡፡
የኢራን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጥቃት የሚያቆመዉ እስራኤል ተመሳሳይ እርምጃ ከወሰደብ ብቻ እንደሆነ ቀደም ብሎ ተናግሯል።የእስራኤል ጦር ከኢራን የተወነጨፉ ሚሳኤሎችን ለይቻለሁ ሲል በዛሬዉ እለት አስታዉቋል፡፡የአየር መከላከያ ዘዴዎች ስጋቱን ለመጥለፍ እየሰሩ ሲሆን ሰዎች ወደ መጠለያ ገብተው እንዲቆዩ እየነገራቸው ይገኛል፡፡
የእስራኤል መከላከያ ሃይል (አይዲኤፍ) ዋና አዛዥ ወታደራዊው ኃይላችን ለኢራን ድርጊት "ከባድ ጥሰት" በማለት "የኃይል ምላሽ ይሰጣል" ብለዋል፡፡ኢያል ዛሚር እንደተናገሩት "በኢራን መንግስት የተካሄደውን የተኩስ አቁም ከፍተኛ ጥሰት ተከትሎ በኃይል ምላሽ እንሰጣለን" ሲሉ በኤክስ ገጻቸዉ ላይ ባወጡት መግለጫ ገልጸዋል፡፡
የኢራን መንግስት ሚዲያ ከተኩስ አቁም በኋላ በእስራኤል ላይ ሚሳኤል ተኮሰች የሚለውን ውንጀላ አስተባብሏል።የኢራን ታጣቂ ሃይሎች ለጠላት ጭካኔ አሳፋሪ እና አርአያነት ያለው ምላሽ መስጠቷን የገለጸችዉ ኢራን ትላንት ምሽት በኳታር በሚገኘው የአሜሪካ ጦር ሰፈር ላይ በደረሰው ጥቃት እና ጎህ ሲቀድ እስራኤል በሚሳኤል መመታቷን አስታዉቃለች፡፡የኢራን ከፍተኛ ብሄራዊ ደህንነት ምክር ቤት ቴህራን በግዛቷ ላይ ለደረሰው ጥቃት ተመጣጣኝ እና በጊዜ ምላሽ ሰጥታለች ያለ ሲሆን "ጠላትን በግዳጅ እንዲጸጸት እና ሽንፈትን እንዲቀበል አድርጓል" ብሏል።
በስምኦን ደረጄ
#ዳጉ_ጆርናል