ሰቨን ቢራ የ2025 ሞንዴ ሰሌክሽን ዓለም አቀፍ የጥራት ተሸላሚ ሆነ
የ2025 ሞንዴ ሰሌክሽን ዩናይትድ ቢቬሬጅ አክሲዮን ማህበር በሰቨን የቢራ ምርት ጥራት የወርቅ ተሸላሚ መሆኑን አስታውቋል። ተቋሙ ሽልማቱን በማስመልከት በሰጠው መግለጫ አለማቀፋዊ እውቅናን ያገኘንበት እንዲሁም የስራችንን ወጤት ያየንበት በመሆኑ ሽልማቱ ከሜዳሊያም በላይ ነው ሲል አስታውቋል። ሽልማቱ ዩናይትድ ቢቬሬጅ ለጥራት፣ ለደንበኞቹ ፍላጎት፣ እንዲሁም ታዓማኒነት እንደሚሰራ ምስክር መሆን የሚችል ሽልማት ነውም ተብሏል።
ኩባንያው " የተባበሩት ቢቬሬጅ አክስዮን ማህበር ለጥራት፣ ወጥነት ላለው ምርት እንዲሁም የደንበኞቹን እምነት ለመጠበቅ ዘወትር የሚተጋ በመሆኑ በሞንዴ ሰሌክሽን እውቅና ማግኘት መቻሉ ትልቅ ክብር ነው" ያለ ሲሆን "ይህ ሽልማት የመላው ቡድናችንን ትጋት እና ጥረት የሚያረጋግጥ ሲሆን ጥራትን ያስቀደመ የስኬት ማማ ላይ እንደሚቀመጥ ማሳያ ነው" ሲልም አክሏል።
ሞንዴ ሰሌክሽን የጥራት ሽልማት ብቻ አይደለም በዓለም አቀፍ ደረጃ እውቅና ያለው ማህተም ነው። ተጠቃሚዎች ከፍተኛውን ዓለም አቀፍ የጥራት ደረጃዎችን የሚያሟላ ምርት እንደመረጡ የሚያረጋግጥ የጥራት ምልክት ነው። ሞንዴ ሰሌክሽን ከሌሎች የሽልማት ዘርፎች ለየት ባለ መልኩ የራሱን መመሪያዎች በማዘጋጀት በተደራጀ መልኩ አለም ዓቀፍ በሆኑ እና የረጅም ጊዜ ልምድ ባላቸው ገለልተኛ ዳኞች አሸናፊው የሚለይበት መሆኑ ልዩ ያደርገዋል።
የሞንዴ ሰሌክሽን ከሽልማትነት ባለፈ ከፍተኛ የጥራት መመዘኛዎች በማሟላት የተመረጡ ምርቶች ቡድን አንድ አካል መሆን መቻልም ነው። ይህም ተጠቃሚዎች በገለልተኛ አካል የተገመገመ እና በጥራቱ የላቀ ምርት በቀላሉ ለማግኘት ያስችላቸዋል ተብሏል። ይህ ስኬት ከተጠቃሚዎች እምነት ባሻገር ዩናይትድ ቢቬሬጅ አክሲዮን ማህበርም በዓለም አቀፍም ሆነ በሀገር ውስጥ ያለውን ገበያ ያጠናክራል በተጨማሪም ለአዳዲስ ስራዎች ፤ ተደራሽነቶች ፤ አጋርነቶች እንዲሁም ስኬቶች መንገድ ይከፍታል ተብሎለታል።
ሰቨን ቢራ ይኽን ሽልማት ማሸነፉ ዩናይትድ ቤቬሬጅ ለተዓማኒነቱ እና ለምርት ጥራቱ ተግቶ እንደሚሰራ ማረጋገጫ ነውም ተብሏል።
በሚሊዮን ሙሴ
#ዳጉ_ጆርናል
የ2025 ሞንዴ ሰሌክሽን ዩናይትድ ቢቬሬጅ አክሲዮን ማህበር በሰቨን የቢራ ምርት ጥራት የወርቅ ተሸላሚ መሆኑን አስታውቋል። ተቋሙ ሽልማቱን በማስመልከት በሰጠው መግለጫ አለማቀፋዊ እውቅናን ያገኘንበት እንዲሁም የስራችንን ወጤት ያየንበት በመሆኑ ሽልማቱ ከሜዳሊያም በላይ ነው ሲል አስታውቋል። ሽልማቱ ዩናይትድ ቢቬሬጅ ለጥራት፣ ለደንበኞቹ ፍላጎት፣ እንዲሁም ታዓማኒነት እንደሚሰራ ምስክር መሆን የሚችል ሽልማት ነውም ተብሏል።
ኩባንያው " የተባበሩት ቢቬሬጅ አክስዮን ማህበር ለጥራት፣ ወጥነት ላለው ምርት እንዲሁም የደንበኞቹን እምነት ለመጠበቅ ዘወትር የሚተጋ በመሆኑ በሞንዴ ሰሌክሽን እውቅና ማግኘት መቻሉ ትልቅ ክብር ነው" ያለ ሲሆን "ይህ ሽልማት የመላው ቡድናችንን ትጋት እና ጥረት የሚያረጋግጥ ሲሆን ጥራትን ያስቀደመ የስኬት ማማ ላይ እንደሚቀመጥ ማሳያ ነው" ሲልም አክሏል።
ሞንዴ ሰሌክሽን የጥራት ሽልማት ብቻ አይደለም በዓለም አቀፍ ደረጃ እውቅና ያለው ማህተም ነው። ተጠቃሚዎች ከፍተኛውን ዓለም አቀፍ የጥራት ደረጃዎችን የሚያሟላ ምርት እንደመረጡ የሚያረጋግጥ የጥራት ምልክት ነው። ሞንዴ ሰሌክሽን ከሌሎች የሽልማት ዘርፎች ለየት ባለ መልኩ የራሱን መመሪያዎች በማዘጋጀት በተደራጀ መልኩ አለም ዓቀፍ በሆኑ እና የረጅም ጊዜ ልምድ ባላቸው ገለልተኛ ዳኞች አሸናፊው የሚለይበት መሆኑ ልዩ ያደርገዋል።
የሞንዴ ሰሌክሽን ከሽልማትነት ባለፈ ከፍተኛ የጥራት መመዘኛዎች በማሟላት የተመረጡ ምርቶች ቡድን አንድ አካል መሆን መቻልም ነው። ይህም ተጠቃሚዎች በገለልተኛ አካል የተገመገመ እና በጥራቱ የላቀ ምርት በቀላሉ ለማግኘት ያስችላቸዋል ተብሏል። ይህ ስኬት ከተጠቃሚዎች እምነት ባሻገር ዩናይትድ ቢቬሬጅ አክሲዮን ማህበርም በዓለም አቀፍም ሆነ በሀገር ውስጥ ያለውን ገበያ ያጠናክራል በተጨማሪም ለአዳዲስ ስራዎች ፤ ተደራሽነቶች ፤ አጋርነቶች እንዲሁም ስኬቶች መንገድ ይከፍታል ተብሎለታል።
ሰቨን ቢራ ይኽን ሽልማት ማሸነፉ ዩናይትድ ቤቬሬጅ ለተዓማኒነቱ እና ለምርት ጥራቱ ተግቶ እንደሚሰራ ማረጋገጫ ነውም ተብሏል።
በሚሊዮን ሙሴ
#ዳጉ_ጆርናል
“እኔ በሕይወት እያለሁ መምህራን መኪና ኖሯቸው ከማየት በላይ የሚያስደስተኝ ነገር የለም” ጠ/ሚ ዐቢይ አሕመድ
ከመላው ኢትዮጵያ ከተውጣጡ የመምህራን ተወካዮች ጋር ውይይት ያደረጉት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ
"እኔ በሕይወት እያለሁ መምህራን መኪና ኖሯቸው፣ መኪናቸውን በሚያስተምሩበት ትምህርት ቤታቸው በር ላይ አቁመው ሲያስተምሩ ከማየት በላይ ለኔ ደስታ የለም" ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ውስጥ ውስጡን እየተሠሩ ያሉት ሥራዎች ሲሳኩ የመምህራን ጥያቄዎች ምላሽ ያገኛሉ ብለዋል።
የመምህራን ጥያቄ በደመወዝ ጭማሪ ብቻ የማይመለስ መሆኑን አንስተው፣ የደመወዝ ጭማሪው ላይ ብቻ ትኩረት ከተደረገ ያለችው ተበልታ ታልቃለች ብሏል።
#ዳጉ_ጆርናል
ከመላው ኢትዮጵያ ከተውጣጡ የመምህራን ተወካዮች ጋር ውይይት ያደረጉት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ
"እኔ በሕይወት እያለሁ መምህራን መኪና ኖሯቸው፣ መኪናቸውን በሚያስተምሩበት ትምህርት ቤታቸው በር ላይ አቁመው ሲያስተምሩ ከማየት በላይ ለኔ ደስታ የለም" ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ውስጥ ውስጡን እየተሠሩ ያሉት ሥራዎች ሲሳኩ የመምህራን ጥያቄዎች ምላሽ ያገኛሉ ብለዋል።
የመምህራን ጥያቄ በደመወዝ ጭማሪ ብቻ የማይመለስ መሆኑን አንስተው፣ የደመወዝ ጭማሪው ላይ ብቻ ትኩረት ከተደረገ ያለችው ተበልታ ታልቃለች ብሏል።
#ዳጉ_ጆርናል
በእስራኤል አራን ውጥረት ዙሪያ ትንታኔውን
ከጋዜጠኛ ሚሊዮን ሙሴ እና ስምኦን ደረጄ ይመልከቱ👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
https://youtu.be/i_3CSgNtWNM?si=xoJAepcbq2XeEI86
#ዳጉ_ጆርናል
ከጋዜጠኛ ሚሊዮን ሙሴ እና ስምኦን ደረጄ ይመልከቱ👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
https://youtu.be/i_3CSgNtWNM?si=xoJAepcbq2XeEI86
#ዳጉ_ጆርናል
የቀነኒሳ በቀለ የመጀመሪያ ልጅ መጽሐፍ አሳተመች
የቀነኒሳ በቀለ የመጀመሪያ ልጅ መጽሐፍ አሳተመች። ኤልናታ ቀነኒሳ በቀለ ያሳተመችው የግጥም መጽሐፍ በውስጡ 17 ግጥሞች ያሉት ሲሆን ከመስከረም ጀምሮ በተለያዩ ትምህርት ቤቶች ለሽያጭ ይቀርባል:: መጽሐፉ ትኩረቱን ሰላም ላይ ያደረገ እንደሆነ ለፋስት መረጃ የደረሰው መረጃ ያመለክታል።
መፅሐፉ በ350 ብር ቀርቧል።
Via ፋስት መረጃ
#ዳጉ_ጆርናል
የቀነኒሳ በቀለ የመጀመሪያ ልጅ መጽሐፍ አሳተመች። ኤልናታ ቀነኒሳ በቀለ ያሳተመችው የግጥም መጽሐፍ በውስጡ 17 ግጥሞች ያሉት ሲሆን ከመስከረም ጀምሮ በተለያዩ ትምህርት ቤቶች ለሽያጭ ይቀርባል:: መጽሐፉ ትኩረቱን ሰላም ላይ ያደረገ እንደሆነ ለፋስት መረጃ የደረሰው መረጃ ያመለክታል።
መፅሐፉ በ350 ብር ቀርቧል።
Via ፋስት መረጃ
#ዳጉ_ጆርናል
ኢራን በፈፀመችው የአፀፋ የሚሳኤል ጥቃት ቢያንስ አስር የእስራኤል ዜጎችን ገደለች
ኢራን በሀይፋ እና ቴል አቪቭ አቅራቢያ ባሉ የእስራኤል ኢላማዎች ላይ ሚሳኤሎችን በመተኮስ ቢያንስ 10 ሰዎች መገደላቸውን የህክምና ባለሙያዎችና ሚዲያዎች ዘግበዋል። ጥቃቶቹ የተፈፀሙት የእስራኤል ሃይሎች በመላው ኢራን የሲቪል እና የኢነርጂ መሠረተ ልማቶችን በቦምብ ከመቱ በኋላ ቴህራን በሚገኘው ሻህራን የነዳጅ ተቋም ላይ የእሳት ቃጠሎ ሙድረሱን ተከትሎ ነው።
ኢራን በእስራኤል ላይ ባደረሰችው የሚሳኤል ጥቃት 10 ሰዎች መሞታቸውን ባለሥልጣናቱ አረጋግጠዋል። ከቴል አቪቭ በስተደቡብ በምትገኘው ባት ያም ከተማ ስድስት ሰዎች መገደላቸውን ፖሊስ ገልጿል፤ ከነዚህም መካከል 2 ህጻናትን ጨምሮ። ሰባት ሰዎች የጠፉ ሲሆን የአደጋ ጊዜ አገልግሎቶች በፈራረሱ ህንፃዎች ላይ ፍለጋ እያደረጉ ይገኛል።በሰሜናዊ አረብ ከተማ ታምራ በተፈፀመ የኢራን የሚሳኤል ጥቃት አራት ሰዎች መሞታቸውን የአደጋ ጊዜ አገልግሎት እና የአካባቢው ሆስፒታል ገልጸዋል።
የእስራኤል ፕሬዝዳንት አይዛክ ሄርዞግ ሀገሪቱ በማዕከላዊ እና በሰሜናዊ ክልሎቿ ኢራን ባደረሰችው ጥቃት ከምሽት ስንነቃ "በጣም አሳዛኝ እና አስቸጋሪ ጠዋት" አሳልፈናክ ሲሉ ኤክስ ለጥፈዋል። "ወንጀለኛው የኢራን ጥቃት" ገድሏል እና አቁስሏል ብለዋል። አይሁዶች እና አረቦች፣ የእስራኤል ዜጎች እና አዲስ ስደተኞች ፣ሕጻናት እና አረጋውያን ሴቶች እንዲሁም ወንዶች ጨምሮ ተጎድተዋል ሲሉ አክለዋል። "በቤተሰባቸው ላይ ከባድ ሀዘን የደረሰባቸውን ለደረሰው አሰቃቂ ጉዳት አዝኛለሁ፤ የተጎዱትን ማገገም እና የጠፉትን እንዲያገኙ እጸልያለሁ ፤አብረን እናዝናለን,ዴ አብረን እናሸንፋለን" ሲሉ ፕሬዝዳንቱ ተደምጠዋል።
በስምኦን ደረጄ
#ዳጉ_ጆርናል
ኢራን በሀይፋ እና ቴል አቪቭ አቅራቢያ ባሉ የእስራኤል ኢላማዎች ላይ ሚሳኤሎችን በመተኮስ ቢያንስ 10 ሰዎች መገደላቸውን የህክምና ባለሙያዎችና ሚዲያዎች ዘግበዋል። ጥቃቶቹ የተፈፀሙት የእስራኤል ሃይሎች በመላው ኢራን የሲቪል እና የኢነርጂ መሠረተ ልማቶችን በቦምብ ከመቱ በኋላ ቴህራን በሚገኘው ሻህራን የነዳጅ ተቋም ላይ የእሳት ቃጠሎ ሙድረሱን ተከትሎ ነው።
ኢራን በእስራኤል ላይ ባደረሰችው የሚሳኤል ጥቃት 10 ሰዎች መሞታቸውን ባለሥልጣናቱ አረጋግጠዋል። ከቴል አቪቭ በስተደቡብ በምትገኘው ባት ያም ከተማ ስድስት ሰዎች መገደላቸውን ፖሊስ ገልጿል፤ ከነዚህም መካከል 2 ህጻናትን ጨምሮ። ሰባት ሰዎች የጠፉ ሲሆን የአደጋ ጊዜ አገልግሎቶች በፈራረሱ ህንፃዎች ላይ ፍለጋ እያደረጉ ይገኛል።በሰሜናዊ አረብ ከተማ ታምራ በተፈፀመ የኢራን የሚሳኤል ጥቃት አራት ሰዎች መሞታቸውን የአደጋ ጊዜ አገልግሎት እና የአካባቢው ሆስፒታል ገልጸዋል።
የእስራኤል ፕሬዝዳንት አይዛክ ሄርዞግ ሀገሪቱ በማዕከላዊ እና በሰሜናዊ ክልሎቿ ኢራን ባደረሰችው ጥቃት ከምሽት ስንነቃ "በጣም አሳዛኝ እና አስቸጋሪ ጠዋት" አሳልፈናክ ሲሉ ኤክስ ለጥፈዋል። "ወንጀለኛው የኢራን ጥቃት" ገድሏል እና አቁስሏል ብለዋል። አይሁዶች እና አረቦች፣ የእስራኤል ዜጎች እና አዲስ ስደተኞች ፣ሕጻናት እና አረጋውያን ሴቶች እንዲሁም ወንዶች ጨምሮ ተጎድተዋል ሲሉ አክለዋል። "በቤተሰባቸው ላይ ከባድ ሀዘን የደረሰባቸውን ለደረሰው አሰቃቂ ጉዳት አዝኛለሁ፤ የተጎዱትን ማገገም እና የጠፉትን እንዲያገኙ እጸልያለሁ ፤አብረን እናዝናለን,ዴ አብረን እናሸንፋለን" ሲሉ ፕሬዝዳንቱ ተደምጠዋል።
በስምኦን ደረጄ
#ዳጉ_ጆርናል
ዳጉ-ጆርናል/Dagu-Journal
የአንጋፋው ጋዜጠኛ የደረጄ ኃይሌ 60ኛ ዓመት የልደት በዓል ዛሬ በድምቀት ይከበራል ከፍተኛ የሆነ ተወዳጅነትን ያተረፈው ጋዜጠኛ ደረጄ ኃይሌ የሕይወቱን እና የሙያ ክህሎቱን ረጅም ጉዞ ለማስቃኘት ለማመስገን እንዲሁም 60ኛ ዓመት የልደት በዓሉን በአርትስ ቴሌቪዥን እና በወዳጆቹ አስተባባሪነት ዛሬ ታላቅ ፕሮግራም ተዘጋጅቷል፡፡ በዚህ ፕሮግራም ላይ በርካታ የስነጥበብ አፍቃሪያን ቤተሰቦቹ ወዳጆቹ የአርትስ…
ጋዜጠኛ ደረጀ ኃይሌ የመኖሪያ ቤት ስጦታ ተበረከተለት
በትናንትናው እለት የ60ኛ ዓመት የልደት በዓሉን እያከበረ የሚገኘው አንጋፋው ጋዜጠኛ ደረጀ ኃይሌ ከጃምቦ ሪልስቴት የመኖሪያ ቤት ስጦታ ተበርክቶለታል።
በተጨማሪም ጋዜጠኛ ደረጀ ኃይሌ የጃምቦ ሪልስቴት የብራንድ አምባሳደር መሆኑ ይፋ ሆኗል።
የአንጋፋው ጋዜጠኛ ደረጀ ኃይሌ የሙያ ባልደረቦቹና ወዳጆቹ እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በተገኙበት የልደት በዓሉ ተከብሯል።
Via አርትስ ቴሌቪዥን
#ዳጉ_ጆርናል
በትናንትናው እለት የ60ኛ ዓመት የልደት በዓሉን እያከበረ የሚገኘው አንጋፋው ጋዜጠኛ ደረጀ ኃይሌ ከጃምቦ ሪልስቴት የመኖሪያ ቤት ስጦታ ተበርክቶለታል።
በተጨማሪም ጋዜጠኛ ደረጀ ኃይሌ የጃምቦ ሪልስቴት የብራንድ አምባሳደር መሆኑ ይፋ ሆኗል።
የአንጋፋው ጋዜጠኛ ደረጀ ኃይሌ የሙያ ባልደረቦቹና ወዳጆቹ እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በተገኙበት የልደት በዓሉ ተከብሯል።
Via አርትስ ቴሌቪዥን
#ዳጉ_ጆርናል
በደራሲ ሚስጥረ አደራው የተፃፈው "እኔ" የተሰኘው መፅሐፍ ሰኔ 7 ቀን 2017 ዓ.ም ተመርቆ ለንባብ በቃ
ከዚህ ቀደም የተለያዩ ሃሳቦቿንና ስራዎቿን በተለይም የትርጉም ስራዎችን በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያ አማራጮቿ በማቅረብ የምትታወቀው ሚስጥረ አደራው የመጀመሪያ ስራዋ የሆነውን "እኔ" የተሰኘ መፅሃፍ ለንባብ አብቅታለች።
ሚስጥረ በብዙዎች ዘንድ የፐርሺያውን ገጣሚ የሩሚን ስራዎች ወደ አማርኛ በመቅዳትና በማቅረብ በስፋት የምትታወቅ ሲሆን አሁን የተለያዩ ታሪኮችን የያዘ መፅሃፍ ነው ይዛ የመጣችው።
"እኔ" የተሰኘው መፅሐፍ፤ ፀሐፊዋ በተለያዩ ጊዜዎች ማህበራዊና መሰል ጉዳዮች የሚፈጥሯቸውን ሸክሞችና ጭቆናዎች በማጠየቅ የራስን ነፃነት ለመፈለግ የሚደረግን በጥያቄና መልስ የተሞላን የህይወት ትግልን የምታሳይበት ነው።
በዋልያ መፅሃፍት በተካሄደው የምረቃ ስነ ስርዓት ላይም ጋዜጠኛ የኋላሸት ዘሪሁን፣ አርታኢና ተርጓሚ ቴዎድሮስ አጥላው፣ አርቲስት አዳነች ወልደ ገብርኤል፣ ደራሲ ዘቢብ መልኬ፣ የስነ ልቦና እና የጤና ባለሙያ ሰላማዊት ሞሲሳን ጨምሮ ተጋባዥ እንግዶች ዲስኩርና ስለ መፅሃፉ ምልከታቸውን ተናግረዋል።
ደራሲዋ ሚስጥረ አደራው በ Health Informatics ዲግሪ እንዲሁም በ Health Information Data analytics የማስተርስ ዲግሪዋን በመያዝ በህክምና ዘርፍ ውስጥ በመስራት ላይ ትገኛለች።ከዛሬ ጀምሮ ለንባብ የበቃው "እኔ" መፅሃፍ 179 ገፆች አሉት።
#ዳጉ_ጆርናል
ከዚህ ቀደም የተለያዩ ሃሳቦቿንና ስራዎቿን በተለይም የትርጉም ስራዎችን በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያ አማራጮቿ በማቅረብ የምትታወቀው ሚስጥረ አደራው የመጀመሪያ ስራዋ የሆነውን "እኔ" የተሰኘ መፅሃፍ ለንባብ አብቅታለች።
ሚስጥረ በብዙዎች ዘንድ የፐርሺያውን ገጣሚ የሩሚን ስራዎች ወደ አማርኛ በመቅዳትና በማቅረብ በስፋት የምትታወቅ ሲሆን አሁን የተለያዩ ታሪኮችን የያዘ መፅሃፍ ነው ይዛ የመጣችው።
"እኔ" የተሰኘው መፅሐፍ፤ ፀሐፊዋ በተለያዩ ጊዜዎች ማህበራዊና መሰል ጉዳዮች የሚፈጥሯቸውን ሸክሞችና ጭቆናዎች በማጠየቅ የራስን ነፃነት ለመፈለግ የሚደረግን በጥያቄና መልስ የተሞላን የህይወት ትግልን የምታሳይበት ነው።
በዋልያ መፅሃፍት በተካሄደው የምረቃ ስነ ስርዓት ላይም ጋዜጠኛ የኋላሸት ዘሪሁን፣ አርታኢና ተርጓሚ ቴዎድሮስ አጥላው፣ አርቲስት አዳነች ወልደ ገብርኤል፣ ደራሲ ዘቢብ መልኬ፣ የስነ ልቦና እና የጤና ባለሙያ ሰላማዊት ሞሲሳን ጨምሮ ተጋባዥ እንግዶች ዲስኩርና ስለ መፅሃፉ ምልከታቸውን ተናግረዋል።
ደራሲዋ ሚስጥረ አደራው በ Health Informatics ዲግሪ እንዲሁም በ Health Information Data analytics የማስተርስ ዲግሪዋን በመያዝ በህክምና ዘርፍ ውስጥ በመስራት ላይ ትገኛለች።ከዛሬ ጀምሮ ለንባብ የበቃው "እኔ" መፅሃፍ 179 ገፆች አሉት።
#ዳጉ_ጆርናል
Forwarded from ዳጉ ጆርናል-ስፖርት (Beⓒk)
መኸዲ ታሬሚ በእስራኤል እና ኢራን ጦርነት የተነሳ ለክለቦች የአለም ዋንጫ ኢንተር ሚላንን መቀላቀል አልቻለም
የኢንተር ሚላኑ ኢራናዊ አጥቂ መኸዲ ታሬሚ በእስራኤል እና ኢራን ጦርነት ለክለቦች የአለም ዋንጫ ኢንተርን መቀላቀል አልቻለም ተብሏል።
ታሬሚ ማክሰኞ እለት ኢራን ደቡብ ኮሪያን አስተናግዳ 3 ለ 0 ባሸነፈችበት ጨዋታ የሀገሩን መለያ አለብሶ ግብም አስቆጥሮ ነበር።
ታድያ ቅዳሜ እለት በሎሳንጀለስ የሚገኘዉን የኢንተር ሚላንን ቡድን እንዲቀላቀል ፕሮግራም ተይዞለት የነበረ ቢሆንም ከኢራን የሚነሱ በረራዎች ለደህንነት ሲባል በመቋረጣቸው ከኢራን መዉጣት አልቻለም ተብሏል።
እስራኤል በኢራን ላይ ጥቃት የከፈተችው ሀሙስ እለት ሲሆን ከሀሙስ ጀምሮ የኢራን የአየር ክልል ዝግ ሆኗል ተብሏል።
እስራኤል እና ኢራን ከቃላት መወራወር ወደ ሮኬት መወራወር ከዚህ ቀደም በቅርቡ በአንድ አጋጣሚ ገብተዉ የነበረ ቢሆንም የሮኬት ተኩሱን አቁመዉት ነበር። ሆኖም እስራኤል የተጠናከረ ጥቃት ከከፈተች በኋላ ኢራንም ሮኬት በቴላቪቭ ላይ ስታዘንብ አድራለች።
በሁለቱ ሀገራት ጦርነት በሰዉ ህይወት እና በንብረት ላይ ከፍተኛ ጉዳት እየደረሰ መሆኑን እየተመለከትን ነዉ።
በበረከት ሞገስ
ለስፖርታዊ መረጃዎችን ይፋዊ የዳጉ ጆርናል ስፖርት ቻናል https://www.tg-me.com/Dagujournalsport ን ይቀላቀሉ
#ዳጉ_ጆርናል_ስፖርት
የኢንተር ሚላኑ ኢራናዊ አጥቂ መኸዲ ታሬሚ በእስራኤል እና ኢራን ጦርነት ለክለቦች የአለም ዋንጫ ኢንተርን መቀላቀል አልቻለም ተብሏል።
ታሬሚ ማክሰኞ እለት ኢራን ደቡብ ኮሪያን አስተናግዳ 3 ለ 0 ባሸነፈችበት ጨዋታ የሀገሩን መለያ አለብሶ ግብም አስቆጥሮ ነበር።
ታድያ ቅዳሜ እለት በሎሳንጀለስ የሚገኘዉን የኢንተር ሚላንን ቡድን እንዲቀላቀል ፕሮግራም ተይዞለት የነበረ ቢሆንም ከኢራን የሚነሱ በረራዎች ለደህንነት ሲባል በመቋረጣቸው ከኢራን መዉጣት አልቻለም ተብሏል።
እስራኤል በኢራን ላይ ጥቃት የከፈተችው ሀሙስ እለት ሲሆን ከሀሙስ ጀምሮ የኢራን የአየር ክልል ዝግ ሆኗል ተብሏል።
እስራኤል እና ኢራን ከቃላት መወራወር ወደ ሮኬት መወራወር ከዚህ ቀደም በቅርቡ በአንድ አጋጣሚ ገብተዉ የነበረ ቢሆንም የሮኬት ተኩሱን አቁመዉት ነበር። ሆኖም እስራኤል የተጠናከረ ጥቃት ከከፈተች በኋላ ኢራንም ሮኬት በቴላቪቭ ላይ ስታዘንብ አድራለች።
በሁለቱ ሀገራት ጦርነት በሰዉ ህይወት እና በንብረት ላይ ከፍተኛ ጉዳት እየደረሰ መሆኑን እየተመለከትን ነዉ።
በበረከት ሞገስ
ለስፖርታዊ መረጃዎችን ይፋዊ የዳጉ ጆርናል ስፖርት ቻናል https://www.tg-me.com/Dagujournalsport ን ይቀላቀሉ
#ዳጉ_ጆርናል_ስፖርት
Forwarded from ዳጉ ጆርናል-ስፖርት (....)
የኦክላንድ ሲቲ እና ባየር ሙኒክ የደረጃ ልዩነት..
- አንዳንድ የኦክላንድ ሲቲ ተጫዋቾች በመደበኛ ስራቸው የተነሳ ሙሉ ቡድኑ ወደ አሜሪካ አልተጓዘም። የቡድኑ አባላት የድርጅት ሥራ አስኪያጅ፣ መምህር፣ ፀጉር አስተካካይ፣ የሪል ስቴት ተወካይ እና ሌሎችም ከተለያዩ ሙያዎች የተውጣጡ ናቸው።
☑️ የኦክላንድ ሲቲ ከፍተኛ ተከፋይ ተጫዋች የሃሪ ኬንን ሳምንታዊ ደሞዝ ለማግኘት ለ 107 አመታት መጫወት ይኖርበታል!
☑️ 💵 የኦክላንድ ሲቲ አማተር ተጫዋቾች በሳምንት 90 ዶላር የሚከፈል ደሞዝ አላቸው! 🇳🇿
☑️ 💵 የባየር ሙኒኩ ተጫዋች ሃሪ ኬን በሳምንት 503,484 ዶላር ያገኛል! 🇩🇪
☑️ 🇳🇿 ኦፕታ ደረጃ ከሰጣቸው ከ13,000 በላይ የሀገር ውስጥ የእግር ኳስ ቡድኖች 5,074 ደረጃ ላይ ኦክላንድ ሲቲ ተቀመጧል።
☑️ 🇪🇸 በስፔን እግር ኳስ እርከን 6ኛ ደረጃ ላይ የሚጫወተው ካስቴላ ሲኤፍ ከነሱ ደረጃ በላይ ተቀምጧል ይህም የኦክላንድ ሲቲ ደረጃ ያሳያል።
ለስፖርታዊ መረጃዎችን ይፋዊ የዳጉ ጆርናል ስፖርት ቻናል https://www.tg-me.com/Dagujournalsport ን ይቀላቀሉ
#ዳጉ_ጆርናል_ስፖርት
- አንዳንድ የኦክላንድ ሲቲ ተጫዋቾች በመደበኛ ስራቸው የተነሳ ሙሉ ቡድኑ ወደ አሜሪካ አልተጓዘም። የቡድኑ አባላት የድርጅት ሥራ አስኪያጅ፣ መምህር፣ ፀጉር አስተካካይ፣ የሪል ስቴት ተወካይ እና ሌሎችም ከተለያዩ ሙያዎች የተውጣጡ ናቸው።
☑️ የኦክላንድ ሲቲ ከፍተኛ ተከፋይ ተጫዋች የሃሪ ኬንን ሳምንታዊ ደሞዝ ለማግኘት ለ 107 አመታት መጫወት ይኖርበታል!
☑️ 💵 የኦክላንድ ሲቲ አማተር ተጫዋቾች በሳምንት 90 ዶላር የሚከፈል ደሞዝ አላቸው! 🇳🇿
☑️ 💵 የባየር ሙኒኩ ተጫዋች ሃሪ ኬን በሳምንት 503,484 ዶላር ያገኛል! 🇩🇪
☑️ 🇳🇿 ኦፕታ ደረጃ ከሰጣቸው ከ13,000 በላይ የሀገር ውስጥ የእግር ኳስ ቡድኖች 5,074 ደረጃ ላይ ኦክላንድ ሲቲ ተቀመጧል።
☑️ 🇪🇸 በስፔን እግር ኳስ እርከን 6ኛ ደረጃ ላይ የሚጫወተው ካስቴላ ሲኤፍ ከነሱ ደረጃ በላይ ተቀምጧል ይህም የኦክላንድ ሲቲ ደረጃ ያሳያል።
ለስፖርታዊ መረጃዎችን ይፋዊ የዳጉ ጆርናል ስፖርት ቻናል https://www.tg-me.com/Dagujournalsport ን ይቀላቀሉ
#ዳጉ_ጆርናል_ስፖርት