ከፍቼ አዲስአበባ የሚሰሩ ተሽከርካሪዎች በነዳጅ እጦት ምክንያት ስራ ለማቆም ተገደናል ሲሉ ቅሬታቸውን አቀረቡ
ከፍቼ አዲስ አበባ የህዝብ ማመላለሻ ትራንስፖርት የሚሰጡ ተሽከርካሪዎች በነዳጅ እጦት ምክንያት አገልግሎት ሊያቆሙ በመገደዳቸው ተገልጋዮች ለእንግልት መዳረጋቸውን ለብስራት ሬዲዮ ተናግረዋል።
በዚህም የትራንስፖርት ተጠቃሚው ማህበረሰብ ለእንግልት መዳረጉን ቅሬታ አቅራቢዎቹ ተናግረዋል። አሽከርካሪዎች በበኩላቸው ትላንት ነዳጅ ለመቅዳት ቢሞክሩም ማደያ ላይ አልቋል የሚል ምላሽ ተሰጥቷቸው በዚህም መንቀሳቀስ አለመቻላቸውን ገልጸዋል። የተወሰኑ አሽከርካሪዎች ከህገወጥ የነዳጅ ቸርቻሪዎች ላይ አንድ ሊትር ናፍጣ በሁለት መቶ ብር ገዝተው ወደ ስራ መሰማራታቸው ብስራት ሰምቷል።
የሰሜን ሸዋ ዞን ንግድ ፅ/ቤት ሀላፊ አቶ ደረጀ ሰማ እንደገለጹት የነዳጅ እጥረቱ በዋነኛነት በሀምሌ ወር ይጨምራል በሚል ስጋት አንዳንድ ማደያዎች ከህግ ውጪ ነዳጅን ለተሽከርካሪዎች በጄሪካን በመሸጥ እንዲሁም ትስስር ላላቸው ነጋዴዎች በመሸጥ የነዳጅ እጥረቱ እንዲከሰት አድርገዋል ። ለዚህም በዋነኛነት፣ አንዳንድ የአስተዳደር ፣ የፀጥታ አካላት የንግዱ ማህበረሰብ እና የትላልቅ ማሽነሪ ተሽከርካሪ ባለቤቶች ከማደያዎች ጋር ያላቸው የጥቅም ትስስር ለነዳጅ እጥረቱ በር መክፈቱን ገልጸዋል።
በተጨማሪም በዞኑ ካሉት አስራ አንድ ማደያዎች መካከል በገብረ ጉራቻ፣ ሙከጡሪ ፣ጫንጮ አሌልቱ መናሃሪያዎች ላይ ቅጣት መጣሉን በመጥቀስ በተለይ የሙከጡሪ ማደያ ተደጋጋሚ የህግ ጥሰት በመፈፀሙ አስተማሪ ቅጣት እንደሚጠብቀው ነግረውናል።
በነዳጅ እጥረት ምክንያት በትራንስፖርት ዋጋ ላይ ጭማሪ ያደረጉ ህገወጥ አሽከርካሪዎች ላይ አስተማሪ ቅጣት በመስጠት ከማደያ ጣቢያ ያለውን ነዳጅ በተገቢው በማካፈል የትንራንስፖርቱን ፍሰት ማስተካከል መቻሉን ብስራት ሬዲዮ ሰምቷል።በሀገወጥ የነዳጅ ግብይት የተሰማሩ ስድስት ነጋዴዎችም ያጠራቀሙት ነዳጅ ውርስ ሆኖ ለተጠቃሚዎች እንደሚከፋፈል ተነግሯል።
በኤደን ሽመልስ
#ዳጉ_ጆርናል
ከፍቼ አዲስ አበባ የህዝብ ማመላለሻ ትራንስፖርት የሚሰጡ ተሽከርካሪዎች በነዳጅ እጦት ምክንያት አገልግሎት ሊያቆሙ በመገደዳቸው ተገልጋዮች ለእንግልት መዳረጋቸውን ለብስራት ሬዲዮ ተናግረዋል።
በዚህም የትራንስፖርት ተጠቃሚው ማህበረሰብ ለእንግልት መዳረጉን ቅሬታ አቅራቢዎቹ ተናግረዋል። አሽከርካሪዎች በበኩላቸው ትላንት ነዳጅ ለመቅዳት ቢሞክሩም ማደያ ላይ አልቋል የሚል ምላሽ ተሰጥቷቸው በዚህም መንቀሳቀስ አለመቻላቸውን ገልጸዋል። የተወሰኑ አሽከርካሪዎች ከህገወጥ የነዳጅ ቸርቻሪዎች ላይ አንድ ሊትር ናፍጣ በሁለት መቶ ብር ገዝተው ወደ ስራ መሰማራታቸው ብስራት ሰምቷል።
የሰሜን ሸዋ ዞን ንግድ ፅ/ቤት ሀላፊ አቶ ደረጀ ሰማ እንደገለጹት የነዳጅ እጥረቱ በዋነኛነት በሀምሌ ወር ይጨምራል በሚል ስጋት አንዳንድ ማደያዎች ከህግ ውጪ ነዳጅን ለተሽከርካሪዎች በጄሪካን በመሸጥ እንዲሁም ትስስር ላላቸው ነጋዴዎች በመሸጥ የነዳጅ እጥረቱ እንዲከሰት አድርገዋል ። ለዚህም በዋነኛነት፣ አንዳንድ የአስተዳደር ፣ የፀጥታ አካላት የንግዱ ማህበረሰብ እና የትላልቅ ማሽነሪ ተሽከርካሪ ባለቤቶች ከማደያዎች ጋር ያላቸው የጥቅም ትስስር ለነዳጅ እጥረቱ በር መክፈቱን ገልጸዋል።
በተጨማሪም በዞኑ ካሉት አስራ አንድ ማደያዎች መካከል በገብረ ጉራቻ፣ ሙከጡሪ ፣ጫንጮ አሌልቱ መናሃሪያዎች ላይ ቅጣት መጣሉን በመጥቀስ በተለይ የሙከጡሪ ማደያ ተደጋጋሚ የህግ ጥሰት በመፈፀሙ አስተማሪ ቅጣት እንደሚጠብቀው ነግረውናል።
በነዳጅ እጥረት ምክንያት በትራንስፖርት ዋጋ ላይ ጭማሪ ያደረጉ ህገወጥ አሽከርካሪዎች ላይ አስተማሪ ቅጣት በመስጠት ከማደያ ጣቢያ ያለውን ነዳጅ በተገቢው በማካፈል የትንራንስፖርቱን ፍሰት ማስተካከል መቻሉን ብስራት ሬዲዮ ሰምቷል።በሀገወጥ የነዳጅ ግብይት የተሰማሩ ስድስት ነጋዴዎችም ያጠራቀሙት ነዳጅ ውርስ ሆኖ ለተጠቃሚዎች እንደሚከፋፈል ተነግሯል።
በኤደን ሽመልስ
#ዳጉ_ጆርናል
አዳማ ከተማ ከፕሪሚየር ሊጉ ወረደ
በ36ኛ ሳምንት የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር አዳማ ከተማ በሀዋሳ ከተማ ተሸንፎ ከፕሪሚየር ሊጉ ወርዷል፡፡
ዛሬ 9፡00 ላይ የተደረገው የሁለቱ ክለቦች ጨዋታ በሀዋሳ ከተማ 2 ለ 1 አሸናፊነት ተጠናቋል፡፡
የሀዋሳ ከተማን ግቦች አቤኔዘር ዮሐንስ እና በረከት ሳሙኤል ሲያስቆጥሩ፥ አዳማ ከተማን ከሽንፈት ያልታደገችውን ግብ ቢኒያም አይተን ከመረብ አሳርፏል፡፡
ውጤቱን ተከትሎ በ39 ነጥብ 16ኛ ደረጃ ላይ የተቀመጠው አዳማ ከተማ፥ ስሑል ሽረ እና ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርሲቲን ተከትሎ ወደ ከፍተኛ ሊግ መውረዱ ተረጋግጧል፡፡
በሊጉ የመሰንበት እድሉን በራሱ ለመወሰን አንድ ነጥብ ብቻ የሚፈልገው ፋሲል ከነማ ምሽት 12 ሰዓት ላይ ሲዳማ ቡናን ይገጥማል፡፡
#ዳጉ_ጆርናል
በ36ኛ ሳምንት የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር አዳማ ከተማ በሀዋሳ ከተማ ተሸንፎ ከፕሪሚየር ሊጉ ወርዷል፡፡
ዛሬ 9፡00 ላይ የተደረገው የሁለቱ ክለቦች ጨዋታ በሀዋሳ ከተማ 2 ለ 1 አሸናፊነት ተጠናቋል፡፡
የሀዋሳ ከተማን ግቦች አቤኔዘር ዮሐንስ እና በረከት ሳሙኤል ሲያስቆጥሩ፥ አዳማ ከተማን ከሽንፈት ያልታደገችውን ግብ ቢኒያም አይተን ከመረብ አሳርፏል፡፡
ውጤቱን ተከትሎ በ39 ነጥብ 16ኛ ደረጃ ላይ የተቀመጠው አዳማ ከተማ፥ ስሑል ሽረ እና ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርሲቲን ተከትሎ ወደ ከፍተኛ ሊግ መውረዱ ተረጋግጧል፡፡
በሊጉ የመሰንበት እድሉን በራሱ ለመወሰን አንድ ነጥብ ብቻ የሚፈልገው ፋሲል ከነማ ምሽት 12 ሰዓት ላይ ሲዳማ ቡናን ይገጥማል፡፡
#ዳጉ_ጆርናል
የቱሉቦሎ - ኬላ አስፋልት መንገድ ፕሮጀክት ተጠናቀቀ
የኦሮሚያ እና የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልሎችን የሚያገናኘው የቱሉቦሎ - ኬላ አስፋልት መንገድ ፕሮጀክት ግንባታው ሙሉ በሙሉ መጠናቀቁን ተከትሎ ደረጃውን የጠበቀ አገልግሎት በመስጠት ላይ ይገኛል።
የመንገድ ፕሮጀክቱ 80 ኪሎሜትር የሸፈነ ሲኾን፥ በአስፋልት ኮንክሪት ደረጃ ነው የተገነባው። የመንገድ ግንባታውን የቻይናው ዓለም-አቀፍ የሥራ ተቋራጭ ሁናን ሁንዳ ሮድ ኤንድ ብሪጅ ኮርፖሬሽን አከናውኖታል።
ሀገር በቀሉ የተባበሩት የምህንድስና አማካሪዎች የግንባታውን ጥራት በመቆጣጠር እና በማማከር በኩል ተሳትፏል። ለፕሮጀክቱ የዋለው 1 ነጥብ 3 ቢሊዮን ብር ወጪ ሙሉ በሙሉ በፌደራል መንግስት ተሸፍኗል።
በመንገድ ፕሮጀክቱ ሦስት ድልድዮችን ጨምሮ አነስተኛ፣ ከፍተኛ ፍሳሽ ማስተላለፊያዎች፣ ቱቦዎች እና ከልቨርቶች ግንባታም ተካትቷል። መንገዱ በገጠር የመንገድ ትከሻን ጨምሮ 10 ሜትር፣ በወረዳ 20 ሜትር እንዲሁም በቀበሌ 15 ሜትር የጎን ስፋት አለው።
የመንገዱ መጠናቀቅ የአዲስ አበባ-ቡታጅራ -ሆሳዕና እና የአዲስ አበባ - ወልቂጤ - ጅማ መስመር ያሉትን አውራ መንገዶች ያገናኛል፡፡ ይህም ከዚህ ቀደም ይደረግ የነበረውን ዙሪያ ጥምጥም ጉዞ በማስቀረት የጉዞ ጊዜን ያሳጥራል።
የተቀላጠፈ የትራንስፖርት እንቅስቃሴ እንዲኖር በማስቻል፣ የማኅበራዊ ተቋማት ተደራሽነትን በማስፋት እንዲሁም የገበያ ትስስሩን በማጠናከር የመንገዱ መገንባት ከፍተኛ አስተዋጽዖ ያበረክታል።
የቱሉቦሎ፣ ሀርቡጩሉሌ፣ ኮምበል፣ አጨበር፣ ቀሽት እና ኬላን ጨምሮ ሌሎች በርካታ አካባቢዎችን በቅርበት ያገናኛል።
#ዳጉ_ጆርናል
የኦሮሚያ እና የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልሎችን የሚያገናኘው የቱሉቦሎ - ኬላ አስፋልት መንገድ ፕሮጀክት ግንባታው ሙሉ በሙሉ መጠናቀቁን ተከትሎ ደረጃውን የጠበቀ አገልግሎት በመስጠት ላይ ይገኛል።
የመንገድ ፕሮጀክቱ 80 ኪሎሜትር የሸፈነ ሲኾን፥ በአስፋልት ኮንክሪት ደረጃ ነው የተገነባው። የመንገድ ግንባታውን የቻይናው ዓለም-አቀፍ የሥራ ተቋራጭ ሁናን ሁንዳ ሮድ ኤንድ ብሪጅ ኮርፖሬሽን አከናውኖታል።
ሀገር በቀሉ የተባበሩት የምህንድስና አማካሪዎች የግንባታውን ጥራት በመቆጣጠር እና በማማከር በኩል ተሳትፏል። ለፕሮጀክቱ የዋለው 1 ነጥብ 3 ቢሊዮን ብር ወጪ ሙሉ በሙሉ በፌደራል መንግስት ተሸፍኗል።
በመንገድ ፕሮጀክቱ ሦስት ድልድዮችን ጨምሮ አነስተኛ፣ ከፍተኛ ፍሳሽ ማስተላለፊያዎች፣ ቱቦዎች እና ከልቨርቶች ግንባታም ተካትቷል። መንገዱ በገጠር የመንገድ ትከሻን ጨምሮ 10 ሜትር፣ በወረዳ 20 ሜትር እንዲሁም በቀበሌ 15 ሜትር የጎን ስፋት አለው።
የመንገዱ መጠናቀቅ የአዲስ አበባ-ቡታጅራ -ሆሳዕና እና የአዲስ አበባ - ወልቂጤ - ጅማ መስመር ያሉትን አውራ መንገዶች ያገናኛል፡፡ ይህም ከዚህ ቀደም ይደረግ የነበረውን ዙሪያ ጥምጥም ጉዞ በማስቀረት የጉዞ ጊዜን ያሳጥራል።
የተቀላጠፈ የትራንስፖርት እንቅስቃሴ እንዲኖር በማስቻል፣ የማኅበራዊ ተቋማት ተደራሽነትን በማስፋት እንዲሁም የገበያ ትስስሩን በማጠናከር የመንገዱ መገንባት ከፍተኛ አስተዋጽዖ ያበረክታል።
የቱሉቦሎ፣ ሀርቡጩሉሌ፣ ኮምበል፣ አጨበር፣ ቀሽት እና ኬላን ጨምሮ ሌሎች በርካታ አካባቢዎችን በቅርበት ያገናኛል።
#ዳጉ_ጆርናል
አርኤስኤፍ ከግብፅ ጋር ያለውን ግንኙነት ለማስተካከል የውይይት ጥሪ አቀረበ
የሱዳን ፓራሚሊተሪ ፈጣን ድጋፍ ሰጭ ሃይል መሪ መሀመድ ሀምዳን ዳጋሎ ከግብፅ ጋር ያሉ አለመግባባቶችን በውይይት መፍታት እንደሚፈልጉ ገልፀዋል። ዳጋሎ በሰፊው በዳርፉር ክልል ለወታደሮቹ ባደረገው ንግግር ከጎረቤት የግብፅ ሃይል ጋር ያለውን ውጥረት አስመልክቶ ተናግረዋል። ቀደም ሲል ግብፅን ለሱዳን ጦር ኃይሎች ወታደራዊ ዕርዳታ ታቀርባለች በሚል የሰላ ትችት ሰንዝረዉ እንደነበርም ይታወቃል።
"ግብፅንና ሌሎች ጎረቤቶቻችንን እናከብራለን እናም ማንኛውም ችግር በውይይት እና በውይይት ሊፈታ ይችላል" ሲሉ ሄሜቲ በንግግራቸዉ የተደመጡ ሲሆን አርኤስኤፍ በአቅራቢያ ካሉ አገሮች ጋር ያለውን ግንኙነት ለማበላሸት በመሞከር ስማቸው ያልተጠቀሱ “ወንጀለኞችን” ከሰዋል።በሱዳን፣ በሊቢያ እና በግብፅ መካከል የሚገኘውን የኦዋይናት የድንበር ትሪያንግልን በቅርቡ የያዘው አርኤስኤፍ ቀጣናውን ከሽብርተኝነት፣ በኮንትሮባንድ እና በህገ ወጥ የሰዎች ዝውውር ለመከላከል እንሰራለንም ሲሉ ዳጋሎ ተናግረዋል።
አክለውም "ፈጣን ድጋፍ ሰጭ ሃይሎች ከጎረቤት ሀገር ጋር ምንም ችግር የለባቸውም" ብለዋል።የአርኤስኤፍ እና የሱዳን ጦር ኃይላቸውን ለማዋሃድ ባወጡት እቅድ ምክንያት የገዢነት አጋርነታቸው ከፈራረሰ በኋላ ከሁለት አመት በላይ ሲዋጉ ቆይተዋል። ግጭቱም ከፍተኛ ሰብዓዊ ቀውስ ፈጥሮ ሚሊዮኖችን አፈናቅሏል።ዳጋሎ በንግግራቸው በዳርፉር የእርዳታ አቅርቦትን ለማመቻቸት ቃል የገቡ ሲሆን ከሚያዝያ 15 ቀን 2023 ጀምሮ ለወታደሮቻቸው ዕዳ መልሰው እንደሚከፍሉም ተናግረዋል።
በሠራዊቱ ላይ የሚያደርሰውን ጥቃት በማደስ እና የተቀሩትን ሃይሎች እንደሚያሸንፉ ቃል የገቡት ጀነራሉ ከጦር ኃይሉ ጋር ለተባበሩ ሌሎች የታጠቁ አንጃ መሪዎችም የእርቅ ጥሩ አቅርበዋል። የሱዳን ነፃ አውጪ ንቅናቄ እና የፍትህ እና የእኩልነት ንቅናቄ መሪዎችን በመጥቀስ "ከሚኒ (አርኮ ሚናዊ) እና ከጅብሪል (ኢብራሂም) ጋር ምንም ችግር የለንም ዛሬ ወደ እኛ ቢመጡ እንኳን ደህና መጣችሁ ብለን እንቀበላቸው አለን ሲሉም ተደምጠዋል።
በሚሊዮን ሙሴ
#ዳጉ_ጆርናል
የሱዳን ፓራሚሊተሪ ፈጣን ድጋፍ ሰጭ ሃይል መሪ መሀመድ ሀምዳን ዳጋሎ ከግብፅ ጋር ያሉ አለመግባባቶችን በውይይት መፍታት እንደሚፈልጉ ገልፀዋል። ዳጋሎ በሰፊው በዳርፉር ክልል ለወታደሮቹ ባደረገው ንግግር ከጎረቤት የግብፅ ሃይል ጋር ያለውን ውጥረት አስመልክቶ ተናግረዋል። ቀደም ሲል ግብፅን ለሱዳን ጦር ኃይሎች ወታደራዊ ዕርዳታ ታቀርባለች በሚል የሰላ ትችት ሰንዝረዉ እንደነበርም ይታወቃል።
"ግብፅንና ሌሎች ጎረቤቶቻችንን እናከብራለን እናም ማንኛውም ችግር በውይይት እና በውይይት ሊፈታ ይችላል" ሲሉ ሄሜቲ በንግግራቸዉ የተደመጡ ሲሆን አርኤስኤፍ በአቅራቢያ ካሉ አገሮች ጋር ያለውን ግንኙነት ለማበላሸት በመሞከር ስማቸው ያልተጠቀሱ “ወንጀለኞችን” ከሰዋል።በሱዳን፣ በሊቢያ እና በግብፅ መካከል የሚገኘውን የኦዋይናት የድንበር ትሪያንግልን በቅርቡ የያዘው አርኤስኤፍ ቀጣናውን ከሽብርተኝነት፣ በኮንትሮባንድ እና በህገ ወጥ የሰዎች ዝውውር ለመከላከል እንሰራለንም ሲሉ ዳጋሎ ተናግረዋል።
አክለውም "ፈጣን ድጋፍ ሰጭ ሃይሎች ከጎረቤት ሀገር ጋር ምንም ችግር የለባቸውም" ብለዋል።የአርኤስኤፍ እና የሱዳን ጦር ኃይላቸውን ለማዋሃድ ባወጡት እቅድ ምክንያት የገዢነት አጋርነታቸው ከፈራረሰ በኋላ ከሁለት አመት በላይ ሲዋጉ ቆይተዋል። ግጭቱም ከፍተኛ ሰብዓዊ ቀውስ ፈጥሮ ሚሊዮኖችን አፈናቅሏል።ዳጋሎ በንግግራቸው በዳርፉር የእርዳታ አቅርቦትን ለማመቻቸት ቃል የገቡ ሲሆን ከሚያዝያ 15 ቀን 2023 ጀምሮ ለወታደሮቻቸው ዕዳ መልሰው እንደሚከፍሉም ተናግረዋል።
በሠራዊቱ ላይ የሚያደርሰውን ጥቃት በማደስ እና የተቀሩትን ሃይሎች እንደሚያሸንፉ ቃል የገቡት ጀነራሉ ከጦር ኃይሉ ጋር ለተባበሩ ሌሎች የታጠቁ አንጃ መሪዎችም የእርቅ ጥሩ አቅርበዋል። የሱዳን ነፃ አውጪ ንቅናቄ እና የፍትህ እና የእኩልነት ንቅናቄ መሪዎችን በመጥቀስ "ከሚኒ (አርኮ ሚናዊ) እና ከጅብሪል (ኢብራሂም) ጋር ምንም ችግር የለንም ዛሬ ወደ እኛ ቢመጡ እንኳን ደህና መጣችሁ ብለን እንቀበላቸው አለን ሲሉም ተደምጠዋል።
በሚሊዮን ሙሴ
#ዳጉ_ጆርናል
በመቱ ከተማ ወድቆ ያገኙትን ከ173 ሺህ ብር በላይ ለፖሊስ ያስረከቡ ጓደኛማቾች ምስጋና ተቸራቸው
በኢሊባቡር ዞን መቱ ከተማ ነዋሪ የሆኑ ሁለት ጎረቤታም ሴቶች ወደ ገበያ ሲያመሩ መሬት ላይ የወደቀ ጥቁር ፌስታል አይተው ገንዘብ መሆኑን ሲገነዘቡ ለፖሊስ ማስረከባቸውን የመቱ ከተማ ፖሊስ መምሪያ ገልጿል ።
የመቱ ከተማ ፖሊስ ዋና መምርያ የኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ፅ/ቤት ኃላፊ ረዳት ኢንስፔክተር አሸብር ጌታሁን ለብስራት ሬዲዮ እንደተናገሩት ወይዘሮ የሺህ ሀረግ ይርጉ እና ወይዘሮ አገርቱ ዴቢሳ የተባሉ የመቱ ከተማ አባ አሳያ ቀበሌ ማርያም ሰፈር ነዋሪ ናቸው።
ሰኔ 16 ቀን 2017 ዓ.ም የሰኞ ገበያ ዕቃ ለመግዛት በመውበት ይህ አጋጣሚ ተከስቷል። ጎረቤታሞቹ የግል ጥቅም እና ፍላጎት ሳያሸንፋቸው በቀጥታ በጥቁር ፌስታል የተጠቀለለውን 173 ሺህ ብር ከሀምሳ ሳንቲም ለመቱ ከተማ ፖሊስ አስረክበዋል።
ሁለቱ ሴቶች በታማኝነት ብሩን እንዳስረከቡ የብሩ ባለቤት አቶ ሰሚር ሙሰማ የተባሉና በመቱ ከተማ አባ አሳያ ቀበሌ ማርያም ሰፈር ነዋሪ የዳቦ መጋገርያ ቤት ባለቤት ከሰዓታት ቆይታ በኋላ በመምጣት ሁለቱ ሴቶች መሬት ላይ ወድቆ ያገኙት ብር የራሰቸው መሆኑን ያመለክታሉ።
ፖሊስም ሁለቱ ሴቶች ያገኙት ብር የአቶ ሰሚር ስለመሆኑ ባደረገው ማጣራት ዱቄት ገዝተው ለመመልስ ወደ ሱቅ መደብር መጓዛቸውን ከዚያም ከቤት ይዘውት የወጡትን ብር ሲያፈላልጉ መገኘቱን በመስማታቸው ወዲያው ወደ ፖሊስ ፅ/ቤት መቅረባቸውን ባቀረቡት ማስረጃ ማረጋገጡን ገልፀዋል።
ብሩ ምንም ሳይጎድል እንዲያገኙ ላደረጉላቸው ሁለት ሴቶች ትልቅ ምስጋና አቅርበው ለዚህ ታማኝነት ተግባር ወሮታ ከፋይነኝ ሲሉ መግለጻቸውን ረዳት ኢንስፔክተር አሽብር ጌታሁን ለብስራት ሬዲዮ ገልፀዋል።
በኤደን ሽመልስ
#ዳጉ_ጆርናል
በኢሊባቡር ዞን መቱ ከተማ ነዋሪ የሆኑ ሁለት ጎረቤታም ሴቶች ወደ ገበያ ሲያመሩ መሬት ላይ የወደቀ ጥቁር ፌስታል አይተው ገንዘብ መሆኑን ሲገነዘቡ ለፖሊስ ማስረከባቸውን የመቱ ከተማ ፖሊስ መምሪያ ገልጿል ።
የመቱ ከተማ ፖሊስ ዋና መምርያ የኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ፅ/ቤት ኃላፊ ረዳት ኢንስፔክተር አሸብር ጌታሁን ለብስራት ሬዲዮ እንደተናገሩት ወይዘሮ የሺህ ሀረግ ይርጉ እና ወይዘሮ አገርቱ ዴቢሳ የተባሉ የመቱ ከተማ አባ አሳያ ቀበሌ ማርያም ሰፈር ነዋሪ ናቸው።
ሰኔ 16 ቀን 2017 ዓ.ም የሰኞ ገበያ ዕቃ ለመግዛት በመውበት ይህ አጋጣሚ ተከስቷል። ጎረቤታሞቹ የግል ጥቅም እና ፍላጎት ሳያሸንፋቸው በቀጥታ በጥቁር ፌስታል የተጠቀለለውን 173 ሺህ ብር ከሀምሳ ሳንቲም ለመቱ ከተማ ፖሊስ አስረክበዋል።
ሁለቱ ሴቶች በታማኝነት ብሩን እንዳስረከቡ የብሩ ባለቤት አቶ ሰሚር ሙሰማ የተባሉና በመቱ ከተማ አባ አሳያ ቀበሌ ማርያም ሰፈር ነዋሪ የዳቦ መጋገርያ ቤት ባለቤት ከሰዓታት ቆይታ በኋላ በመምጣት ሁለቱ ሴቶች መሬት ላይ ወድቆ ያገኙት ብር የራሰቸው መሆኑን ያመለክታሉ።
ፖሊስም ሁለቱ ሴቶች ያገኙት ብር የአቶ ሰሚር ስለመሆኑ ባደረገው ማጣራት ዱቄት ገዝተው ለመመልስ ወደ ሱቅ መደብር መጓዛቸውን ከዚያም ከቤት ይዘውት የወጡትን ብር ሲያፈላልጉ መገኘቱን በመስማታቸው ወዲያው ወደ ፖሊስ ፅ/ቤት መቅረባቸውን ባቀረቡት ማስረጃ ማረጋገጡን ገልፀዋል።
ብሩ ምንም ሳይጎድል እንዲያገኙ ላደረጉላቸው ሁለት ሴቶች ትልቅ ምስጋና አቅርበው ለዚህ ታማኝነት ተግባር ወሮታ ከፋይነኝ ሲሉ መግለጻቸውን ረዳት ኢንስፔክተር አሽብር ጌታሁን ለብስራት ሬዲዮ ገልፀዋል።
በኤደን ሽመልስ
#ዳጉ_ጆርናል
የድሬዳዋ ምድር ባቡር ግቢን የቱሪስት መዳረሻ ስፍራ ለማድረግ እየተሰራ ነዉ ተባለ
የድሬዳዋ የምድር ባቡር ተርሚናል እድሳት ከኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን በተመደበለት በጀት ጥገና ተደርጎለት ከሁለት ወራት በፊት መጠናቀቁን የድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር ባህልና ቱሪዝም ፅህፈት ቤት አስታዉቋል ።
ቅርሱ እድሳት የተከናወነለት ታሪካዊ ይዘቱን ሳይለቅ ሲሆን ሙሉ ለሙሉ ዉድመት ደርሶባቸዉ ለነበሩ መስኮቶችም ተመሳሳይ ቁሳቁሶችን በመጠቀም ወደነበረበት የመመለስ ስራ መከናወኑም ተገልጿል ።
በድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር ባህልና ቱሪዝም ፅህፈት ቤት የቅርስ ዘርፍ አስተባባሪ አቶ አብረሃም ያረጋል ለብስራት ሬዲዮ እንደተናገሩት የድሬዳዋ ምድር ባቡር ምድረ ግቢን የቱሪስት መዳረሻ ስፍራ ለማድረግ በኢትዮጵያ ቅርስ ጥናትና ጥበቃ ባለስልጣን በተመደበ በጀት በአማካሪ ድርጅት የሰነድ ዝግጅት ለማካሄድ በጨረታ ላይ የሚገኝ ሲሆን ሂደቱ በቅርቡ ተጠናቆ የሰነድ ዝግጅት ይከናወናል ።
በምድር ባቡር ግቢ ውስጥ የሚገኝ የባቡር ፉርጎን ጥቅም ላይ በማዋል የከተማዋን ባህል የሚገልፁ እና ለህብረተሰቡ አገልግሎት መስጠት የሚችሉ እንደ ፈጣን ምግብ ያሉ አገልግሎቶችን ለማቅረብ ፕሮጀክት በመቅረፅ ከቱሪዝም ሚኒስቴር ጋር የዲዛይን ስራ እንደሚከናወን ተገልጿል ። ይህም የኮሪደር ልማቱን ባማከለ መልኩ የሚከናወን መሆኑን የገለፁት አስተባባሪዉ ይህንን የባቡር ፉርጎ በመጠቀም የሚሰጠዉን አገልግሎት በድሬዳዋ ከተማ ለገሀር አደባባይ አከባቢ ለመገንባት መታቀዱን አክለዋል ።
በመባ ወርቅነህ
#ዳጉ_ጆርናል
የድሬዳዋ የምድር ባቡር ተርሚናል እድሳት ከኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን በተመደበለት በጀት ጥገና ተደርጎለት ከሁለት ወራት በፊት መጠናቀቁን የድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር ባህልና ቱሪዝም ፅህፈት ቤት አስታዉቋል ።
ቅርሱ እድሳት የተከናወነለት ታሪካዊ ይዘቱን ሳይለቅ ሲሆን ሙሉ ለሙሉ ዉድመት ደርሶባቸዉ ለነበሩ መስኮቶችም ተመሳሳይ ቁሳቁሶችን በመጠቀም ወደነበረበት የመመለስ ስራ መከናወኑም ተገልጿል ።
በድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር ባህልና ቱሪዝም ፅህፈት ቤት የቅርስ ዘርፍ አስተባባሪ አቶ አብረሃም ያረጋል ለብስራት ሬዲዮ እንደተናገሩት የድሬዳዋ ምድር ባቡር ምድረ ግቢን የቱሪስት መዳረሻ ስፍራ ለማድረግ በኢትዮጵያ ቅርስ ጥናትና ጥበቃ ባለስልጣን በተመደበ በጀት በአማካሪ ድርጅት የሰነድ ዝግጅት ለማካሄድ በጨረታ ላይ የሚገኝ ሲሆን ሂደቱ በቅርቡ ተጠናቆ የሰነድ ዝግጅት ይከናወናል ።
በምድር ባቡር ግቢ ውስጥ የሚገኝ የባቡር ፉርጎን ጥቅም ላይ በማዋል የከተማዋን ባህል የሚገልፁ እና ለህብረተሰቡ አገልግሎት መስጠት የሚችሉ እንደ ፈጣን ምግብ ያሉ አገልግሎቶችን ለማቅረብ ፕሮጀክት በመቅረፅ ከቱሪዝም ሚኒስቴር ጋር የዲዛይን ስራ እንደሚከናወን ተገልጿል ። ይህም የኮሪደር ልማቱን ባማከለ መልኩ የሚከናወን መሆኑን የገለፁት አስተባባሪዉ ይህንን የባቡር ፉርጎ በመጠቀም የሚሰጠዉን አገልግሎት በድሬዳዋ ከተማ ለገሀር አደባባይ አከባቢ ለመገንባት መታቀዱን አክለዋል ።
በመባ ወርቅነህ
#ዳጉ_ጆርናል
እስራኤል በጋዛ በፈፀመችው ጥቃት ቢያንስ 43 ፍልስጤማውያንን ተገደሉ
በጋዛ በተስፋፋው ረሃብ ውስጥ ቢያንስ 43 አጥብቀው የምግብ እርዳታ የሚሹ ፍልስጤማውያን በማእከላዊ የጋዋ ግዛት አካባቢ በተፈጸመ ጥቃት ተገድለዋል ሲል የአልጀዚራ የእውነታ ማረጋገጫ ክፍል ሳናድ ዘግቧል።
እንደ ዘገባው ከሆነ ተጎጂዎቹ የተገደሉት ከዋዲ ጋዛ በስተደቡብ በሚገኘው የሳላህ አል-ዲን ጎዳና ላይ ምግብ በመጠባበቅ ላይ በነበሩበት ወቅት ነው።
በሳናድ የተገኘ የምስል ቅጅ የተጎጂዎች አስከሬን በጋዛ ናስር ሜዲካል ኮምፕሌክስ እና በአል-አውዳ ሆስፒታል ተከማችቶ ያሳያል። በእስራኤል እና በአሜሪካ የሚደገፈው የጋዛ የሰብዓዊ ፋውንዴሽን እ.ኤ.አ ግንቦት 27 ቀን እርዳታ ማከፋፈሉን ከጀመረ ወዲህ እስራኤል የእርዳታ ማዕከላት አቅራቢያ ፍልስጤማውያን ላይ ባደረሰችው ጥቃት ከ400 በላይ ሰዎችን ሲገደሉ 1,000 የሚያህሉ ቆስለዋልም ተብሏል።
በሚሊዮን ሙሴ
#ዳጉ_ጆርናል
በጋዛ በተስፋፋው ረሃብ ውስጥ ቢያንስ 43 አጥብቀው የምግብ እርዳታ የሚሹ ፍልስጤማውያን በማእከላዊ የጋዋ ግዛት አካባቢ በተፈጸመ ጥቃት ተገድለዋል ሲል የአልጀዚራ የእውነታ ማረጋገጫ ክፍል ሳናድ ዘግቧል።
እንደ ዘገባው ከሆነ ተጎጂዎቹ የተገደሉት ከዋዲ ጋዛ በስተደቡብ በሚገኘው የሳላህ አል-ዲን ጎዳና ላይ ምግብ በመጠባበቅ ላይ በነበሩበት ወቅት ነው።
በሳናድ የተገኘ የምስል ቅጅ የተጎጂዎች አስከሬን በጋዛ ናስር ሜዲካል ኮምፕሌክስ እና በአል-አውዳ ሆስፒታል ተከማችቶ ያሳያል። በእስራኤል እና በአሜሪካ የሚደገፈው የጋዛ የሰብዓዊ ፋውንዴሽን እ.ኤ.አ ግንቦት 27 ቀን እርዳታ ማከፋፈሉን ከጀመረ ወዲህ እስራኤል የእርዳታ ማዕከላት አቅራቢያ ፍልስጤማውያን ላይ ባደረሰችው ጥቃት ከ400 በላይ ሰዎችን ሲገደሉ 1,000 የሚያህሉ ቆስለዋልም ተብሏል።
በሚሊዮን ሙሴ
#ዳጉ_ጆርናል
በኢትዮጵያ ህገወጥ የእንስሳት ዝውውርን ማስቆም አልተቻለም ተባለ
ኢትዮጵያ የዱር እንስሳትና የእፅዋት ሀብት ያላት ሀገር ብትሆንም ይህ ሀብቷ ግን በበርካታ ችግሮች ውስጥ እንደሚገኝ የኢትዮጵያ የዱር እንስሳት ጥበቃ ባለስልጣን አስታውቋል።በባለስልጣኑ የዱር እንስሳት ህገወጥ ዝውውር ቁጥጥር ከፍተኛ ባለሙያ የሆኑት አቶ ዳንኤል ጳውሎስ ለብስራት ሬድዮ እንደተናገሩት የዱር እንስሳትና የእፅዋት ሀብትን ለመጠበቅ በመጠለያና ፓርኮች አካባቢ የቁጥጥር ስራን የሚሰሩ ሰራተኞች ጥቃት እንዳይፈፀም የሚያስችል ስራን ያከናውናሉ።
ነገር ግን በእነዚህ ስፍራዎች ከህገወጥ ሰፈራ አንስቶ ህገወጥ የአደን ተግባራት ጭምር ይስተዋላሉ። እነዚህ ሁሉ በተፈጥሮ ሀብቱ ላይ ከተደቀኑ ችግሮች መካከል ተጠቃሽ ናቸው ያሉት አቶ ዳንኤል የዱር እንስሳት ከነ ህይወታቸው ጭምር እየተያዙ በህገወጥ መልኩ ከአንድ አካባቢ ወደ ሌላ እንደዚሁም ከሀገር አልፈው ወደ ውጪ የሚዘዋወሩበት ሁኔታ መኖሩን ገልፀዋል።እንስሳቱ ለምግብነት፣ለጌጣጌጥ መስሪያነትና ለሌሎች አላማዎች በሚል በህገወጥ መልኩ እንደሚዘዋወሩ አቶ ዳንኤል ጨምረው ለጣቢያችን ተናግረዋል።
የዱር እንስሳትን ሀብት በአግባቡ በመጠቀም ተገቢውን ኢኮኖሚያዊ ጥቅም ለማግኘት የቁጥጥር ስራዎች መጠናከር እንደሚገባቸው ተገልጿል።ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ በህገ ወጥ የዱር እንስሳት ውጤቶቻቸው ዝውውር እና ቁጥጥር ዙሪያ ለሚመለከታቸው አካላት ስልጠና መስጠቱን አስታውቋል።ለአምስት ቀናት በቆየው ስልጠና የዱር እንስሳት ውጤቶቻቸው ዝውውርን ለመከላከል የሚያስችሉ ሰነዶች የቀረቡ ሲሆን ሰልጣኞች ከህገወጦች የሚያዙ የዱር እንስሳት ውጤቶችን መለየት የሚያስችል የተግባር ላይ ስልጠና እንዲያገኙ ተደርጓል።
በተጨማሪም በቦሌ አለም አቀፍ ኤርፖርት ላይ የሚገኙትን የአነፍናፊ ውሾች የፍተሻ ተግባር የሚያከናውኑበትን ሁኔታ መጎብኘት ችለዋል።
ቅድስት ደጀኔ
#ዳጉ_ጆርናል
ኢትዮጵያ የዱር እንስሳትና የእፅዋት ሀብት ያላት ሀገር ብትሆንም ይህ ሀብቷ ግን በበርካታ ችግሮች ውስጥ እንደሚገኝ የኢትዮጵያ የዱር እንስሳት ጥበቃ ባለስልጣን አስታውቋል።በባለስልጣኑ የዱር እንስሳት ህገወጥ ዝውውር ቁጥጥር ከፍተኛ ባለሙያ የሆኑት አቶ ዳንኤል ጳውሎስ ለብስራት ሬድዮ እንደተናገሩት የዱር እንስሳትና የእፅዋት ሀብትን ለመጠበቅ በመጠለያና ፓርኮች አካባቢ የቁጥጥር ስራን የሚሰሩ ሰራተኞች ጥቃት እንዳይፈፀም የሚያስችል ስራን ያከናውናሉ።
ነገር ግን በእነዚህ ስፍራዎች ከህገወጥ ሰፈራ አንስቶ ህገወጥ የአደን ተግባራት ጭምር ይስተዋላሉ። እነዚህ ሁሉ በተፈጥሮ ሀብቱ ላይ ከተደቀኑ ችግሮች መካከል ተጠቃሽ ናቸው ያሉት አቶ ዳንኤል የዱር እንስሳት ከነ ህይወታቸው ጭምር እየተያዙ በህገወጥ መልኩ ከአንድ አካባቢ ወደ ሌላ እንደዚሁም ከሀገር አልፈው ወደ ውጪ የሚዘዋወሩበት ሁኔታ መኖሩን ገልፀዋል።እንስሳቱ ለምግብነት፣ለጌጣጌጥ መስሪያነትና ለሌሎች አላማዎች በሚል በህገወጥ መልኩ እንደሚዘዋወሩ አቶ ዳንኤል ጨምረው ለጣቢያችን ተናግረዋል።
የዱር እንስሳትን ሀብት በአግባቡ በመጠቀም ተገቢውን ኢኮኖሚያዊ ጥቅም ለማግኘት የቁጥጥር ስራዎች መጠናከር እንደሚገባቸው ተገልጿል።ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ በህገ ወጥ የዱር እንስሳት ውጤቶቻቸው ዝውውር እና ቁጥጥር ዙሪያ ለሚመለከታቸው አካላት ስልጠና መስጠቱን አስታውቋል።ለአምስት ቀናት በቆየው ስልጠና የዱር እንስሳት ውጤቶቻቸው ዝውውርን ለመከላከል የሚያስችሉ ሰነዶች የቀረቡ ሲሆን ሰልጣኞች ከህገወጦች የሚያዙ የዱር እንስሳት ውጤቶችን መለየት የሚያስችል የተግባር ላይ ስልጠና እንዲያገኙ ተደርጓል።
በተጨማሪም በቦሌ አለም አቀፍ ኤርፖርት ላይ የሚገኙትን የአነፍናፊ ውሾች የፍተሻ ተግባር የሚያከናውኑበትን ሁኔታ መጎብኘት ችለዋል።
ቅድስት ደጀኔ
#ዳጉ_ጆርናል
በአሜሪካ የጦር ሰፈር ላይ የተፈጸመዉ ጥቃት ከኳታር ጋር ምንም ግንኙነት የለውም ስትል ኢራን ተናገረች
የኢራን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ሰኞ በአሜሪካ በሚመራው አል ኡዴይድ ወታደራዊ ጦር ሰፈር ላይ የተፈጸመው ጥቃት ከኳታር ጋር ምንም ግንኙነት እንደሌለው ተናግረዋል ።መሰረቱ በኳታር ነው፣ ያሉት ባካይ ግን የኢራን ድርጊት "ራስን የመከላከል ተግባር" ነው ብሏል።"ኢራን የኳታርን ግዛት እና ሌሎች ጎረቤት ሀገራትን በተመለከተ ለመልካም ጉርብትና ፖሊሲዋ ሙሉ በሙሉ ቁርጠኛ ነች" ሲሉ ባካይ በኤክስ ላይ አጋርተዋል።
የአሜሪካ እና እስራኤላውያን የወንጀል ጥቃቶች በኢራን ላይ የተሳሳቱ ፖሊሲዎች በእኛ እና በቀጠናው ወንድማማች አገሮች መካከል መለያየት እንዳይፈጥሩ ወስነናል ያሉት የኢራን ምክትል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ኳታር በአካባቢው ያለውን መባባስ ለመከላከል ስላደረገችዉ ምስጋናቸውን ገልጿል።የኢራን ምክትል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማጂድ ታክት-ራቫንቺ እና የኳታር የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር መሐመድ ቢን አብዱላዚዝ አል-ኩላይፊን ለአገራቸው ስላደረገችዉ "ገንቢ ሚና" አመስግነዋል::
ታክት ራቫንቺ ኢራን "በመልካም ጉርብትና እና ከፍተኛ ጥቅም ላይ የተመሰረተ የሁለቱን ሀገራት ግንኙነት ለመቀጠል እና ለማጠናከር ቆርጣለች" ሲሉ ተናግረዋል።ኢራን በኳታር አል ኡዴይድ በሚገኘው የአሜሪካ ጦር ሰፈር ላይ በኒውክሌር ተቋሞቿ ላይ ላደረሰችው ጥቃት አጸፋ የተኩስ ሚሳኤሎችን መተኮሷ ይታወሳል። በምላሹ ኳታር ድርጊቱን አጥብቆ በማውገዝ የኢራን አምባሳደርን አስጠርታለች፡፡
በስምኦን ደረጄ
#ዳጉ_ጆርናል
የኢራን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ሰኞ በአሜሪካ በሚመራው አል ኡዴይድ ወታደራዊ ጦር ሰፈር ላይ የተፈጸመው ጥቃት ከኳታር ጋር ምንም ግንኙነት እንደሌለው ተናግረዋል ።መሰረቱ በኳታር ነው፣ ያሉት ባካይ ግን የኢራን ድርጊት "ራስን የመከላከል ተግባር" ነው ብሏል።"ኢራን የኳታርን ግዛት እና ሌሎች ጎረቤት ሀገራትን በተመለከተ ለመልካም ጉርብትና ፖሊሲዋ ሙሉ በሙሉ ቁርጠኛ ነች" ሲሉ ባካይ በኤክስ ላይ አጋርተዋል።
የአሜሪካ እና እስራኤላውያን የወንጀል ጥቃቶች በኢራን ላይ የተሳሳቱ ፖሊሲዎች በእኛ እና በቀጠናው ወንድማማች አገሮች መካከል መለያየት እንዳይፈጥሩ ወስነናል ያሉት የኢራን ምክትል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ኳታር በአካባቢው ያለውን መባባስ ለመከላከል ስላደረገችዉ ምስጋናቸውን ገልጿል።የኢራን ምክትል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማጂድ ታክት-ራቫንቺ እና የኳታር የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር መሐመድ ቢን አብዱላዚዝ አል-ኩላይፊን ለአገራቸው ስላደረገችዉ "ገንቢ ሚና" አመስግነዋል::
ታክት ራቫንቺ ኢራን "በመልካም ጉርብትና እና ከፍተኛ ጥቅም ላይ የተመሰረተ የሁለቱን ሀገራት ግንኙነት ለመቀጠል እና ለማጠናከር ቆርጣለች" ሲሉ ተናግረዋል።ኢራን በኳታር አል ኡዴይድ በሚገኘው የአሜሪካ ጦር ሰፈር ላይ በኒውክሌር ተቋሞቿ ላይ ላደረሰችው ጥቃት አጸፋ የተኩስ ሚሳኤሎችን መተኮሷ ይታወሳል። በምላሹ ኳታር ድርጊቱን አጥብቆ በማውገዝ የኢራን አምባሳደርን አስጠርታለች፡፡
በስምኦን ደረጄ
#ዳጉ_ጆርናል
ትራምፕ የኢራን የኒውክሌር መርሃ ግብር አልጠፋም በሚል ሾልኮ የወጣውን የደህንነት መረጃ ውድቅ አደረጉ
ዶናልድ ትራምፕ አሜሪካ በኢራን ላይ ባደረሰችው ጥቃት ዙሪያ ሾልኮ ስለወጣው መረጃ ምላሽ ሰጥተዋል። የግል ንብረታቸው በሆነው ትሩዝ ሶሻል ላይ ባጋሩት መረጃ፣ ትራምፕ የአሜሪካን ሚዲያ እና ዘገባዎቻቸውን ነቅፈዋል። የሐሰት ዜና ሲ ኤን ኤን እና ከወደቀው ኒውዮርክ ታይምስ ጋር ተጣምረው አጋርተዋል ብለዋል። በኢራን ውስጥ ያሉ እጅግ በጣም አስፈላጊ ወታደራዊ መሳሪያዎች ታሪካዊ በሆነው ጥቃት ሙሉ በሙሉ ተደምስሷል ሲሉ ተደምጠዋል።
የትራምፕ አስተዳደር አሜሪካ በኢራን ላይ ያደረሰችው ጥቃት የኒውክሌር ፕሮግራሟን አላወደመውም የሚለውን ዘገባ ውድቅ ማድረጉን ቀጥሏል።
በስምኦን ደረጄ
#ዳጉ_ጆርናል
ዶናልድ ትራምፕ አሜሪካ በኢራን ላይ ባደረሰችው ጥቃት ዙሪያ ሾልኮ ስለወጣው መረጃ ምላሽ ሰጥተዋል። የግል ንብረታቸው በሆነው ትሩዝ ሶሻል ላይ ባጋሩት መረጃ፣ ትራምፕ የአሜሪካን ሚዲያ እና ዘገባዎቻቸውን ነቅፈዋል። የሐሰት ዜና ሲ ኤን ኤን እና ከወደቀው ኒውዮርክ ታይምስ ጋር ተጣምረው አጋርተዋል ብለዋል። በኢራን ውስጥ ያሉ እጅግ በጣም አስፈላጊ ወታደራዊ መሳሪያዎች ታሪካዊ በሆነው ጥቃት ሙሉ በሙሉ ተደምስሷል ሲሉ ተደምጠዋል።
የትራምፕ አስተዳደር አሜሪካ በኢራን ላይ ያደረሰችው ጥቃት የኒውክሌር ፕሮግራሟን አላወደመውም የሚለውን ዘገባ ውድቅ ማድረጉን ቀጥሏል።
በስምኦን ደረጄ
#ዳጉ_ጆርናል
የአሜሪካ ጥቃት የኢራንን የኒውክሌር መርሃ ግብር አለማጥፋቱን የስለላ ሪፖርት አመላከት
(ዝርዝሩን በስምኦን ደረጄ)
ዩናይትድ ስቴትስ በኢራን የኒውክሌር መሥሪያ ቤቶች ላይ የፈጸመችው ጥቃት የሀገሪቱን የኒውክሌር መርሃ ግብር አላጠፋም እናም ምናልባትም በወራት ውስጥ ዳግም እንዲመለስ ያደርገዋል ሲል ፔንታጎን ጥቃቱን በተመለከተ አስቀድሞ ባደረገው የመረጃ ግምገማ ገልጿል። የኢራን አብዮታዊ ሪፐብሊክ የበለፀገ የዩራኒየም ክምችት በቅዳሜው የቦምብ ጥቃቶች አልተወገደም ሲሉ የመከላከያ መረጃ ኤጀንሲ ግምገማን የሚያውቁ ምንጮች ለሲቢኤስ ተናግረዋል። ዋይት ሀውስ እንዳለው ግን "የተሳሳተ" ግምገማ በዝቅተኛ ደረጃ የተሰራ የስለላ ግኝት ነው በማለት አጣጥሏል።
ፕሬዝደንት ዶናልድ ትራምፕ በኢራን የሚገኙትን የኒውክሌር ቦታዎች ሙሉ በሙሉ ወድመዋል ሲሉ ሚዲያዎች "በታሪክ ውስጥ ስኬታማ ከሆኑ ወታደራዊ ጥቃቶች መካከል አንዱን ለማዋረድ እየሞከሩ ነው" ሲሉ ከሰዋል።ዩናይትድ ስቴትስ 18 ሜትር (60 ጫማ) ኮንክሪት ወይም 61 ሜትር (200 ጫማ) መሬት ውስጥ ዘልቆ መግባት በሚችሉ "በቤንከር ባስተር" ቦምቦች በኢራን ውስጥ ሶስት የኒውክሌር ተቋማትን ፎርዶ፣ ናታንዝ እና ኢስፋሃንን መታለች። ነገር ግን የፔንታጎን የስለላ ግምገማን የሚያውቁ ምንጮች የኢራን የኒውክሌር ስፍራ በአብዛኛው "ያልተበላሹ" እና ተጽእኖው ከመሬት በላይ ባሉ ሕንፃዎች ላይ ብቻ የተገደበ ነው ይላሉ።
ወደ ሁለት የኒውክሌር መስሪያ ቤቶች የሚገቡት መግቢያዎች ተዘግተዋል፣ አንዳንድ መሠረተ ልማቶች ወድመዋል ወይም ተበላሽተዋል፣ ነገር ግን አብዛኛው ከመሬት በታች ያሉ ህንጻዎች ከፍንዳታው አደጋ አምልጠዋል። ማንነታቸው ያልታወቁ ምንጮቹ ለአሜሪካ ሚዲያ እንደተናገሩት ጥቃቱ ኢራንን ወደ ኋላ የመለሰው “ከጥቂት ወራት በላይ ነው” ተብሎ ተገምቷል እናም ማንኛውም የኒውክሌር ፕሮግራሟን እንደገና መጀመር እና ለመጠገን ምን ያህል ጊዜ እንደሚወስድ ላይ የተመሠረተ ሊሆን ይችላል ። የኢራን የበለጸገው የዩራኒየም ክምችት ከጥቃቱ በፊት መንቀሳቀሱንም ምንጮች ለሲቢኤስ አረጋግጠዋል።
የዩናይትድ ስቴትስ 14,000 ኪሎ ግራም የሚመዝነው ግዙፍ የኦርዳንስ ቦምብ የኢራንን የመሬት ውስጥ ማበልፀጊያ ተቋማትን ሊያወድም የሚችል ብቸኛው መሳሪያ እንደሆነ ይታሰብ ነበር። ቴህራን የኒውክሌር መርሃ ግብሯ ለሰላማዊ ዓላማ ነው ስትል ሁልጊዜም ትደመጣለች።የቅዳሜውን የአሜሪካን ጥቃት ተከትሎ በነበሩት የመጀመሪያ ሰአታት ውስጥ የጋራ ጦር ሃላፊዎች ሊቀመንበር ጄኔራል ዳን ኬን ለጋዜጠኞች እንደተናገሩት በተቋማቱ ላይ የደረሰውን ጉዳት ለመገምገም ጊዜ ይፈልጋል ብለዋል። ነገር ግን "ሦስቱም ቦታዎች በጣም ከባድ ጉዳት እና ውድመት ደርሶባቸዋል" ሲሉ አክለዋል።የሳተላይት ምስሎች በፎርዶ ኑክሌር ቦታዎች ላይ በሚገኙ ሁለት የመግቢያ ስፍራዎች ዙሪያ ስድስት አዲስ ጉድጓዶች፣ እንዲሁም ግራጫ ብናኝ እና ፍርስራሾችን ያሳያሉ። ድረ-ገጾቹ ከመሬት በታች ምን ያህል ጉዳት እንደደረሰባቸው ግን በምስሎቹ ላክ ግልጽ አይደለም።
የኢራን የመንግስት ብሮድካስት ምክትል የፖለቲካ ዳይሬክተር ሀሰን አቤዲኒ በአሜሪካ ኢላማ የተደረጉት ሶስት ቦታዎች ጥቃቱ ከመፈፀሙ ከተወሰነ ጊዜ በፊት ተወስደዋል ብለዋል እናም ኢራን ቁሳቁሶቹ ቀድሞውኑ ስላሸሸችው ትልቅ ጉዳት አላጋጠማትም ብለዋል ። በሌላ በኩል የአሜሪካ ባለስልጣናት ተልዕኮውን የተሳካ ነው ሲሉ የእስራኤል ባለስልጣናትም አድንቀዋል። የመከላከያ ሚኒስትር ፔት ሄግሰት ማክሰኞ በሰጡት መግለጫ "ሁሉንም አይቻለሁ የእኛ የቦምብ ጥቃት ኢራን የኒውክሌር ጦር መሳሪያ የመፍጠር አቅምን ያጠፋ ነበር" ብለዋል ። "ቦምቦቹ አውዳሚ አልነበሩም የሚል ሰው ፕሬዚዳንቱን እና የተሳካውን ተልዕኮ ለማዳከም እየሞከረ ነው" ሲሉ ሄግዝ ተደምጠዋል።
የዩናይትድ ስቴትስ ኮንግረስማን የዴሞክራቲክ የምክር ቤቱ የውጭ ጉዳይ ኮሚቴ አባል ብራድ ሼርማን ለቢቢሲ እንደተናገሩት የትራምፕ አስተዳደር ድልን ለማወጅ ግልፅ ያልሆኑ ቃላትን እየተጠቀመ ነው ብለዋል። የቦምብ ጥቃት ተልዕኮው ምን እንዳከናወነ እስካሁን ግልፅ አይደለም። አስተዳደሩ በፈፀመው ጥቃት ዘጠኝ የኒውክሌር ጦር መሣሪያዎችን ለመፍጠር በቂ ስለሆነው የኢራን ዩራኒየም ስለማጥፋቱ አልተናገረም ብለዋል። ሸርማን አክለው "የኢራን የኒውክሌር ፕሮግራሙን አጥፋን ሲሉ፣ ሴንትሪፉጁስ ተደምስሷል እና ወደፊት ዩራኒየም የመፍጠር አቅሙ ወይም ክምችቱን እየደመሰሰ መሆኑን እንኳን አይናገሩም" ሲሉ ተደምጠዋል። የምክትል ፕሬዝዳንት ቫንስ መግለጫን ጨምሮ ሁሉም ምልክቶች የሚያመለክቱት ክምችቱን ያገኘን አይመስለንም ብለዋል ። ጥቃቱ ከመድረሱ ቀናት በፊት የጭነት መኪናዎች ወደ አንዱ መገልገያ ሲሄዱ የሚያሳዩ ምስሎች የሉም ሲሉ ጠቁመዋል።
ጠቅላይ ሚንስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ ማክሰኞ እንዳሉት ከኢራን ጋር ያለው ጦርነት በሰኔ ወር ከጀመረ ወዲህ እስራኤል የኢራንን የኒውክሌር ፍላጎት በመገደብ እንዲሁም የሚሳኤል ጦር መሳሪያዎቿን በማውደም ውጤታማ ሆናለች ብለዋል። ኔታንያሁ በጽህፈት ቤታቸው ባወጡት የቪዲዮ መግለጫ ላይ “በእኛ ላይ የነበሩትን ሁለት ፈጣን የህልውና ስጋቶች አስወግደናል፤ በኒውክሌር መጥፋት ስጋት እና 20,000 የባላስቲክ ሚሳኤሎች ተወግደዋል ብለዋል። የሳውዲ የዜና አውታር አልሃዳት ስማቸው ያልተገለጸ የእስራኤልን ምንጭ ጠቅሶ እንደዘገበው እስራኤል አብዛኛው የኢራን የበለጸገ ዩራኒየም በፍርስራሹ ውስጥ የተቀበረ መሆኑን ታውቃለች ብሏል። አሜሪካ 18 የስለላ ኤጀንሲዎች አሏት፤ አንዳንድ ጊዜ በተልዕኳቸው እና በአካባቢው ባላቸው እውቀት ላይ ተመስርተው የሚጋጩ ዘገባዎችን ያዘጋጃሉ። ለምሳሌ የአሜሪካ የስለላ ማህበረሰብ በኮቪድ-19 አመጣጥ ላይ አሁንም ስምምነት ላይ አልደረሰም። ወደፊት የስለላ ሪፖርቶች በተቋማቱ ላይ የተለያየ ጉዳት ደረጃን የሚያሳዩ ተጨማሪ መረጃዎችን ሊያካትቱ ይችላሉ።
የሳይንስ እና የአለም አቀፍ ደህንነት ተቋም ፕሬዝዳንት እና የምስጢር የኒውክሌር ጦር መሳሪያ ልማት ኤክስፐርት ዴቪድ አልብራይት ኢራን በአሜሪካ ጥቃት የደረሰባት ጉዳት ማለት የኒውክሌር መርሃ ግብሯን ወደነበረበት ለመመለስ ከፍተኛ ጊዜ፣ኢንቨስትመንት እና ጉልበት ይጠይቃል ብለዋል። አልብራይት በኤክስ ላይ በለጠፉት ጽሁፍ ኢራን “በዩናይትድ ስቴትስ እና በእስራኤል ከፍተኛ ክትትል ላይ ናት” ሲሉ አክለው ተናግረዋል፣ እናም እንደገና ለመገንባት ከሞከሩ ለተጨማሪ ጥቃቶች ይጋልጣሉ። ሰኞ እለት ኢራን በሺዎች የሚቆጠሩ የአሜሪካ ወታደሮች መገኛ በሆነው ኳታር በሚገኘው አል-ኡዲድ አየር ሰፈር ላይ የሚሳኤል ጥቃትን በአሜሪካ ላይ የአፀፋ እርምጃ ወስዳለች። ያ ጥቃቱ በአብዛኛው የተጠለፈ ሲሆን ምንም አይነት ጉዳት አልደረሰም። ኢራን ከወሰደችበት አፀፋ በኋላ፣ በፕሬዚዳንት ትራምፕ እና በኳታር ሸምጋዮች የተኩስ አቁም ስምምነት በኢራን እና በእስራኤል መካከል ተደርሷል።
በስምኦን ደረጄ
#ዳጉ_ጆርናል
(ዝርዝሩን በስምኦን ደረጄ)
ዩናይትድ ስቴትስ በኢራን የኒውክሌር መሥሪያ ቤቶች ላይ የፈጸመችው ጥቃት የሀገሪቱን የኒውክሌር መርሃ ግብር አላጠፋም እናም ምናልባትም በወራት ውስጥ ዳግም እንዲመለስ ያደርገዋል ሲል ፔንታጎን ጥቃቱን በተመለከተ አስቀድሞ ባደረገው የመረጃ ግምገማ ገልጿል። የኢራን አብዮታዊ ሪፐብሊክ የበለፀገ የዩራኒየም ክምችት በቅዳሜው የቦምብ ጥቃቶች አልተወገደም ሲሉ የመከላከያ መረጃ ኤጀንሲ ግምገማን የሚያውቁ ምንጮች ለሲቢኤስ ተናግረዋል። ዋይት ሀውስ እንዳለው ግን "የተሳሳተ" ግምገማ በዝቅተኛ ደረጃ የተሰራ የስለላ ግኝት ነው በማለት አጣጥሏል።
ፕሬዝደንት ዶናልድ ትራምፕ በኢራን የሚገኙትን የኒውክሌር ቦታዎች ሙሉ በሙሉ ወድመዋል ሲሉ ሚዲያዎች "በታሪክ ውስጥ ስኬታማ ከሆኑ ወታደራዊ ጥቃቶች መካከል አንዱን ለማዋረድ እየሞከሩ ነው" ሲሉ ከሰዋል።ዩናይትድ ስቴትስ 18 ሜትር (60 ጫማ) ኮንክሪት ወይም 61 ሜትር (200 ጫማ) መሬት ውስጥ ዘልቆ መግባት በሚችሉ "በቤንከር ባስተር" ቦምቦች በኢራን ውስጥ ሶስት የኒውክሌር ተቋማትን ፎርዶ፣ ናታንዝ እና ኢስፋሃንን መታለች። ነገር ግን የፔንታጎን የስለላ ግምገማን የሚያውቁ ምንጮች የኢራን የኒውክሌር ስፍራ በአብዛኛው "ያልተበላሹ" እና ተጽእኖው ከመሬት በላይ ባሉ ሕንፃዎች ላይ ብቻ የተገደበ ነው ይላሉ።
ወደ ሁለት የኒውክሌር መስሪያ ቤቶች የሚገቡት መግቢያዎች ተዘግተዋል፣ አንዳንድ መሠረተ ልማቶች ወድመዋል ወይም ተበላሽተዋል፣ ነገር ግን አብዛኛው ከመሬት በታች ያሉ ህንጻዎች ከፍንዳታው አደጋ አምልጠዋል። ማንነታቸው ያልታወቁ ምንጮቹ ለአሜሪካ ሚዲያ እንደተናገሩት ጥቃቱ ኢራንን ወደ ኋላ የመለሰው “ከጥቂት ወራት በላይ ነው” ተብሎ ተገምቷል እናም ማንኛውም የኒውክሌር ፕሮግራሟን እንደገና መጀመር እና ለመጠገን ምን ያህል ጊዜ እንደሚወስድ ላይ የተመሠረተ ሊሆን ይችላል ። የኢራን የበለጸገው የዩራኒየም ክምችት ከጥቃቱ በፊት መንቀሳቀሱንም ምንጮች ለሲቢኤስ አረጋግጠዋል።
የዩናይትድ ስቴትስ 14,000 ኪሎ ግራም የሚመዝነው ግዙፍ የኦርዳንስ ቦምብ የኢራንን የመሬት ውስጥ ማበልፀጊያ ተቋማትን ሊያወድም የሚችል ብቸኛው መሳሪያ እንደሆነ ይታሰብ ነበር። ቴህራን የኒውክሌር መርሃ ግብሯ ለሰላማዊ ዓላማ ነው ስትል ሁልጊዜም ትደመጣለች።የቅዳሜውን የአሜሪካን ጥቃት ተከትሎ በነበሩት የመጀመሪያ ሰአታት ውስጥ የጋራ ጦር ሃላፊዎች ሊቀመንበር ጄኔራል ዳን ኬን ለጋዜጠኞች እንደተናገሩት በተቋማቱ ላይ የደረሰውን ጉዳት ለመገምገም ጊዜ ይፈልጋል ብለዋል። ነገር ግን "ሦስቱም ቦታዎች በጣም ከባድ ጉዳት እና ውድመት ደርሶባቸዋል" ሲሉ አክለዋል።የሳተላይት ምስሎች በፎርዶ ኑክሌር ቦታዎች ላይ በሚገኙ ሁለት የመግቢያ ስፍራዎች ዙሪያ ስድስት አዲስ ጉድጓዶች፣ እንዲሁም ግራጫ ብናኝ እና ፍርስራሾችን ያሳያሉ። ድረ-ገጾቹ ከመሬት በታች ምን ያህል ጉዳት እንደደረሰባቸው ግን በምስሎቹ ላክ ግልጽ አይደለም።
የኢራን የመንግስት ብሮድካስት ምክትል የፖለቲካ ዳይሬክተር ሀሰን አቤዲኒ በአሜሪካ ኢላማ የተደረጉት ሶስት ቦታዎች ጥቃቱ ከመፈፀሙ ከተወሰነ ጊዜ በፊት ተወስደዋል ብለዋል እናም ኢራን ቁሳቁሶቹ ቀድሞውኑ ስላሸሸችው ትልቅ ጉዳት አላጋጠማትም ብለዋል ። በሌላ በኩል የአሜሪካ ባለስልጣናት ተልዕኮውን የተሳካ ነው ሲሉ የእስራኤል ባለስልጣናትም አድንቀዋል። የመከላከያ ሚኒስትር ፔት ሄግሰት ማክሰኞ በሰጡት መግለጫ "ሁሉንም አይቻለሁ የእኛ የቦምብ ጥቃት ኢራን የኒውክሌር ጦር መሳሪያ የመፍጠር አቅምን ያጠፋ ነበር" ብለዋል ። "ቦምቦቹ አውዳሚ አልነበሩም የሚል ሰው ፕሬዚዳንቱን እና የተሳካውን ተልዕኮ ለማዳከም እየሞከረ ነው" ሲሉ ሄግዝ ተደምጠዋል።
የዩናይትድ ስቴትስ ኮንግረስማን የዴሞክራቲክ የምክር ቤቱ የውጭ ጉዳይ ኮሚቴ አባል ብራድ ሼርማን ለቢቢሲ እንደተናገሩት የትራምፕ አስተዳደር ድልን ለማወጅ ግልፅ ያልሆኑ ቃላትን እየተጠቀመ ነው ብለዋል። የቦምብ ጥቃት ተልዕኮው ምን እንዳከናወነ እስካሁን ግልፅ አይደለም። አስተዳደሩ በፈፀመው ጥቃት ዘጠኝ የኒውክሌር ጦር መሣሪያዎችን ለመፍጠር በቂ ስለሆነው የኢራን ዩራኒየም ስለማጥፋቱ አልተናገረም ብለዋል። ሸርማን አክለው "የኢራን የኒውክሌር ፕሮግራሙን አጥፋን ሲሉ፣ ሴንትሪፉጁስ ተደምስሷል እና ወደፊት ዩራኒየም የመፍጠር አቅሙ ወይም ክምችቱን እየደመሰሰ መሆኑን እንኳን አይናገሩም" ሲሉ ተደምጠዋል። የምክትል ፕሬዝዳንት ቫንስ መግለጫን ጨምሮ ሁሉም ምልክቶች የሚያመለክቱት ክምችቱን ያገኘን አይመስለንም ብለዋል ። ጥቃቱ ከመድረሱ ቀናት በፊት የጭነት መኪናዎች ወደ አንዱ መገልገያ ሲሄዱ የሚያሳዩ ምስሎች የሉም ሲሉ ጠቁመዋል።
ጠቅላይ ሚንስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ ማክሰኞ እንዳሉት ከኢራን ጋር ያለው ጦርነት በሰኔ ወር ከጀመረ ወዲህ እስራኤል የኢራንን የኒውክሌር ፍላጎት በመገደብ እንዲሁም የሚሳኤል ጦር መሳሪያዎቿን በማውደም ውጤታማ ሆናለች ብለዋል። ኔታንያሁ በጽህፈት ቤታቸው ባወጡት የቪዲዮ መግለጫ ላይ “በእኛ ላይ የነበሩትን ሁለት ፈጣን የህልውና ስጋቶች አስወግደናል፤ በኒውክሌር መጥፋት ስጋት እና 20,000 የባላስቲክ ሚሳኤሎች ተወግደዋል ብለዋል። የሳውዲ የዜና አውታር አልሃዳት ስማቸው ያልተገለጸ የእስራኤልን ምንጭ ጠቅሶ እንደዘገበው እስራኤል አብዛኛው የኢራን የበለጸገ ዩራኒየም በፍርስራሹ ውስጥ የተቀበረ መሆኑን ታውቃለች ብሏል። አሜሪካ 18 የስለላ ኤጀንሲዎች አሏት፤ አንዳንድ ጊዜ በተልዕኳቸው እና በአካባቢው ባላቸው እውቀት ላይ ተመስርተው የሚጋጩ ዘገባዎችን ያዘጋጃሉ። ለምሳሌ የአሜሪካ የስለላ ማህበረሰብ በኮቪድ-19 አመጣጥ ላይ አሁንም ስምምነት ላይ አልደረሰም። ወደፊት የስለላ ሪፖርቶች በተቋማቱ ላይ የተለያየ ጉዳት ደረጃን የሚያሳዩ ተጨማሪ መረጃዎችን ሊያካትቱ ይችላሉ።
የሳይንስ እና የአለም አቀፍ ደህንነት ተቋም ፕሬዝዳንት እና የምስጢር የኒውክሌር ጦር መሳሪያ ልማት ኤክስፐርት ዴቪድ አልብራይት ኢራን በአሜሪካ ጥቃት የደረሰባት ጉዳት ማለት የኒውክሌር መርሃ ግብሯን ወደነበረበት ለመመለስ ከፍተኛ ጊዜ፣ኢንቨስትመንት እና ጉልበት ይጠይቃል ብለዋል። አልብራይት በኤክስ ላይ በለጠፉት ጽሁፍ ኢራን “በዩናይትድ ስቴትስ እና በእስራኤል ከፍተኛ ክትትል ላይ ናት” ሲሉ አክለው ተናግረዋል፣ እናም እንደገና ለመገንባት ከሞከሩ ለተጨማሪ ጥቃቶች ይጋልጣሉ። ሰኞ እለት ኢራን በሺዎች የሚቆጠሩ የአሜሪካ ወታደሮች መገኛ በሆነው ኳታር በሚገኘው አል-ኡዲድ አየር ሰፈር ላይ የሚሳኤል ጥቃትን በአሜሪካ ላይ የአፀፋ እርምጃ ወስዳለች። ያ ጥቃቱ በአብዛኛው የተጠለፈ ሲሆን ምንም አይነት ጉዳት አልደረሰም። ኢራን ከወሰደችበት አፀፋ በኋላ፣ በፕሬዚዳንት ትራምፕ እና በኳታር ሸምጋዮች የተኩስ አቁም ስምምነት በኢራን እና በእስራኤል መካከል ተደርሷል።
በስምኦን ደረጄ
#ዳጉ_ጆርናል