Telegram Web Link
<<+>>   #የሰኔ_መዓልት <<+>>

=>ቀደምት #ኢትዮዽያውያን ሰው ወሬ ሲያበዛባቸው "#ምነው_የሰኔ_መዓልትን_ሆንክብኝ!" ሲሉ ይተርቡ ነበር:: "አሳጥርልኝ! ወሬህ ረዘመብኝ!" ለማለት ነው::

+ለዚህ መነሻ የሆነው ደግሞ ከ13ቱ ወራት መዓልቱ (ቀኑ) ቶሎ የማይመሽበት ወር ሰኔ መሆኑ ነው:: በእርግጥ ንግግራችን አጭርና ግልጽ ቢሆን ሁሌም መልካም ነው:: ሰው እስኪሰለቸን ድረስ ማውራቱ የሚገባ: የሚመችም አይደለምና::

+"ሺ ዓመት አላወራ! በናትህ (ሽ) ትንሽ ላውራ?" እያሉ መንዛዛቱም ቢሆን አይመከርም::

<< እኔም ወደ ጉዳዬ ልግባ >>

+ከዓመቱ 13 ወራት የሰኔ መዓልቱ ለምን ረዘመ ብንል:- መልሱ አጭር ነው:: "#ይህ_የእግዚአብሔር_ጥበብና_ሥራ_ነው::"
ሳይንሱ ሺህ መንስኤን ሊደረድር ይችላል:: ለእኛ ግን አበው እንዳስተማሩን ሰኔ #የሥራና_የጾም ወር ነው::

+ትጋትን የሚወድ አምላክ ይህንን ወቅት ለጾም ለሥራና: ለበጐ ተግባር አርዝሞልናል:: በእርግጥ ጥቂት ሠርተን ብዙ ለምንተኛ ለዚህ ዘመን ሰዎች ይህ ሊጸንብን ይችል ይሆናል:: ግን ምንም እንኩዋ ሁሉ ወራት ለሥራ ቢሠሩም ወርሃ ሰኔ #ለገበሬና #ለክርስቲያን ትልቁን ሥራ የሚጀምሩበት ወቅት ነው::

+በሰኔ ያልተጋ #ገበሬ ዓመቱን ሙሉ መከረኛ ነው:: ከነ ተረቱም "#ሰነፍ_ገበሬ_ይሞታል_በሰኔ" ይባላል::

+#ክርስቲያንም ከበዓለ ሃምሳ ማግስት #በዓለ ዸራቅሊጦስን ተደግፎ ሰኔን ሊተጋባት ግድ ይላል:: በመከራ ዘመን የሚመሰል #ክረምት ሳይመጣ በወርሃ ሰኔ ሊተጋ ግድ ይለዋል:: ሽሽቱ በክረምትና በሰንበት እንዳይሆንም ይጸልያል:: (ማቴ.24:20)

+#እግዚአብሔር ሁሉን በሁሉ የሠራ: ያዘጋጀና የፈጸመ ጌታ ነው:: ምንም እንዳይጐድልብንም አድርጐናል:: በተለይ #የኢ/ኦ/ተ_ቤተ_ክርረስቲያን ሁሉ ነገሯ በሥርዓት ነው:: ለሁም ነገር ትርጉምና ሸጋ የሆኑ ሐተታዎች አሏት::

+ስለዚህም የዘመን ቀመሯን መሠረት አድርጋ #ወርሃ_ሰኔ መዓልቱ 15: ሌሊቱ 9 ነው ትላለች:: ብርሃኑ ሲበዛም እንዲህ ትለናለች::

¤ብርሃን #ጌታ_ነው:: (ዮሐ. 9:5)
¤ብርሃን #ድንግል_ማርያም_ናት:: (ራዕይ. 12:1)
¤ብርሃን #ቅዱሳን_ናቸው:: (ማቴ. 5:14)

+ቀጥሎም መጽሐፍ እንዲህ ይለናል:-
"#አምጣነ_ብክሙ_ብርሃን: #እመኑ_በብርሃን: #ከመ_ትኩኑ_ዉሉደ_ብርሃን: #ዘእንበለ_ይርከብክሙ_ጽልመት" (ጨለማ ሳያገኛችሁ: ብርሃንም ሳለላችሁ: የብርሃን ልጆች ትሆኑ ዘንድ: በብርሃን እመኑ) (ዮሐ. 12:36)

=>አምላከ ብርሃን: ወላዴ ሕይወት አምላካችን: ቸር ብርሃኑን ይላክልን:: ተረፈ ዘመኑንም የሰላምና የበረከት ያድርግልን::

<< ወስብሐት ለእግዚአብሔር >>

" ፍቅር ያጌብረኒ ከመ እንግር ዜናሆሙ ለቅዱሳን"::/የቅዱሳንን ዜና(ታሪክ) እንድመሰክር ፍቅር ያስገድደኛል::  አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ /መጽሐፈ ምሥጢር/

(re)  Dn  Yordanos Abebe


🔗https://www.tg-me.com/zikirekdusn
▶️
https://www.youtube.com/@ZikereKedusan
✞✞✞ በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን ፡፡ ✞✞✞

እንኳን አደረሳችሁ

❖ ሰኔ 1 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት

+"+ ቅዱስ_ዮሴፍ_ጻድቅ +"+

=>ቤተ_ክርስቲያን
በዚህ ስም ብዙ ቅዱሳን አሏት:: በተለይ ደግሞ እስራኤል
የተባለ የቅዱስ_ያዕቆብ
ልጅ ቅዱስ ዮሴፍ ከሁሉም ቅድሚያውን ይይዛል::
ታላቁ ቅዱስ_መጽሐፍ
ላይ በስፋት ታሪካቸው ከተጻፈላቸው ቅዱሳን አንዱ ነው::

+ስለዚህ ቅዱስ ዝርዝር መረጃን
ለማግኘት ኦሪት_ዘፍጥረትን
ከምዕራፍ 39 እስከ 50 ድረስ ማንበብ ይኖርብናል::
ከዚህ በተረፈም በዜና ቤተ ክርስቲያን ስለ ቅዱሱ ብዙ
ተብሏል::

+መጽሐፍ ቅዱስ ሲጀምር ስለ ቅዱስ ሰው አዳም
ይነግረናል:: ቀጥሎም ስለ ቅዱሳኑ
ሴት
ሔኖክ
ኖኅ
ሴም
አብርሃም
ይስሐቅና
ያዕቆብ
ነግሮን ቅዱስ_ዮሴፍ
ላይ ይደርሳል::

+ቅዱስ ዮሴፍ ያዕቆብ (እስራኤል) ከሚወዳት
ሚስቱ ራሔል
ከወለዳቸው 2 የስስት ልጆቹ አንዱ ነው:: ቅዱሱ ምንም
እናቱ ብትሞተበትም በአባቱና በፈጣሪው ፊት ሞገስ
ነበረው::
ምክንያቱም ቅን: ታዛዥና የፍቅር ሰው ነበርና::

+እንዲያ አምርረው ለሚጠሉት ወንድሞቹ እንኳን ክፋትን
አያስብም ነበር:: ይልቁኑ ለእነሱ ምሳ (ስንቅ) ይዞ
ሊፈልጋቸው
በበርሃ ይንከራተት ነበር እንጂ::
+መንገድ ላይ ቢርበው አለቀሰ እንጂ ስንቃቸውን
አልበላባቸውም:: የአባቶቹ አምላክ ግን ድንጋዩን ዳቦ
አድርጐ
መግቦታል:: 10ሩ ወንድሞቹ ግን ስለ በጐነቱ ፈንታ
ሊገድሉት ተማከሩ:: ከፈጣሪው አግኝቶ በነገራቸው ሕልም
"ሊነግሥብን
ነው" ብለው ቀንተውበታልና::
+በፍጻሜው ግን በይሁዳ መካሪነት ለዐረብ ነጋድያን
ሸጠውታል:: በዚህም ለምሥጢረ ሥጋዌ (ለጌታ መሸጥና
ሕማማት) ምሳሌ
ለመሆን በቅቷል:: ወንድሞቹ ለክፋት ቢሸጡትም ቅሉ
ውስጡ ፈቃደ እግዚአብሔር ነበረበትና በባርነት
በተሸጠበት በዺጥፋራ
ቤት ፈጣሪው ሞገስ ሆነው::
+ወጣትነቱን በፍቅረ እግዚአብሔር ሸብ አድርጐ አስሮ
ነበርና የዺጥፋራ ሚስት የዝሙት ጥያቄ
አላንበረከከውም:: "ማንም
አያየንም" ስትለውም "እፎ እገብር ኃጢአተ በቅድመ
እግዚአብሔር" (ማንም ባያይስ እንዴት በፈጣሪየ ፊት
ኃጢአትን
አሠራለሁ?) በማለት ከበደል አምልጧል:: ስለዚህ
ፈንታም የእሥር ቅጣት አግኝቶታል::
+ጌታ ከእርሱ ጋር ቢሆን በእሥር ቤትም ሞገስን አገኘና
አለቅነትን ተሾመ:: "ኢኀደረ ዮሴፍ ዘእንበለ ሲመት"
እንዲል
መጽሐፍ:: ከዚያም የንጉሡን (የፈርዖንን) ባለሟሎች
ሕልም ተረጐመ:: ቀጥሎም ንጉሡን በሕልም ትርጓሜ
አስደመመ::
ፈርዖንም ቅዱሱን በግዛቱ (ግብጽ) ላይ ሾመው::
+ቅዱስ ዮሴፍ በምድረ ግብጽ ነግሦ ሕዝቡን ከረሃብ
ታደገ:: ለቅዱስ አባቱ ለእሥራኤልና ክፉ ለዋሉበት
ወንድሞቹም መጋቢ
ሆናቸው:: አስኔት (አሰኔት) የምትባል ሴት አግብቶም
ኤፍሬምና ምናሴ የተባሉ ልጆችን አፍርቷል::
+በመንገዱ ሁሉ እግዚአብሔርን አስደስቶ: ከአባቱ
ዘንድም ምርቃትና በረከትን ተቀብሎ በ110 ዓመቱ
በዚህች ቀን በመልካም
ሽምግልና ዐርፏል:: ወገኖቹም በክብርና በእንባ
ቀብረውታል:: "አጽሜን አፍልሱ" ብሎ በተናገረው ትንቢት
መሠረትም ልጆቹ
(እነ ቅዱስ ሙሴ) ከግብጽ ባርነት ሲወጡ አጽሙን ወደ
ከነዓን አፍልሠዋል::

+" ቅዱስ ለውንትዮስ ሰማዕት "+

=>ቅዱሱ የተወለደው በ3ኛው መቶ ክ/ዘመን አካባቢ
ሲሆን ሃገሩ ጠራብሎስ ትባላለች:: በወቅቱ በወታደርነት
ነገሥታቱን
ያገለግል ነበር:: ድንግል: ደም ግባት የሞላለት ወጣት ስለ
ነበር በሰዎች ፊት ሞገስ ነበረው::

+እርሱ ግን ምን ወታደር ቢሆን ጾምና ጸሎትን ያዘወትር
ነበር:: በተለይ ደግሞ የዳዊትን መዝሙር እየመላለሰ
ይጸልየው:
ይወደው ነበር:: ንግግሩ ሁሉ በመንፈስ ቅዱስ ጨውነት
የታሸ ነውና ብዙ ጉዋደኞቹን ከክህደት ወደ ሃይማኖት:
ከክፋት ወደ
ደግነት መልሷል::

+የመከራ ዘመን በደረሰ ጊዜም በገሃድ ስመ ክርስቶስን
ይሰብክ ነበር:: ክፉ ሰዎች ከሰውት በመኮንኑ ፊት በቀረበ
ጊዜም
አልፈራም:: ወታደሮቹ መሬት ላይ ጥለው እየደበደቡት:
ደሙ እንደ ጐርፍ እየተቀዳ እርሱ ግን ይዘምር ነበር::

+በመጨረሻም ስለ ክርስቶስ ፍቅር አንገቱን ተሰይፏል::
ቅዱስ ለውንትዮስ እጅግ ተአምረኛ ሰማዕት ነውና
በእምነት
እንጥራው:: ቤተ ክርስቲያንም ዛሬ የቅዱሱን ተአምራት
ታስባለች:: ቅዳሴ ቤቱም የተከበረው በዚሁ ዕለት ነው::

=>አምላከ ቅዱሳን ወርኀ ሰኔን የፍሬ: የበረከት: የንስሃና
የጽድቅ አድርጐ ይስጠን:: ከሰማዕቱ ጽናትን: ጸጋ በረከትን
ይክፈለን::

=>ሰኔ 1 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት=
1.ቅዱስ ዮሴፍ ጻድቅ (የያዕቆብ ልጅ)
2.እናታችን አስኔት (የቅ/ ዮሴፍ ሚስት)
3.ቅዱስ ለውንትዮስ ክቡር ሰማዕት
4.ቅዱስ ቢፋሞን ሰማዕት
5.ቅዱስ ቆዝሞስ ሰማዕት

❖ወርኃዊ በዓላት
1፡ ልደታ ለማርያም
2፡ ቅዱስ በርተሎሜዎስ ሐዋርያ
3፡ ቅዱስ ሚልኪ ቁልዝማዊ
4፡ ቅዱስ ራጉኤል ሊቀ መላእክት
5፡ ቅዱሳን ኢያቄም ወሐና

=>+"+ እንዲህም አላቸው:- "ወደ ግብጽ የሸጣችሁኝ እኔ
ወንድማችሁ ዮሴፍ ነኝ:: አሁንም ወደዚህ ስለ ሸጣችሁኝ
አትዘኑ:: አትቆርቆሩም:: እግዚአብሔር ሕይወትን ለማዳን
ከእናንተ በፊት ሰዶኛልና . . . እግዚአብሔርም በምድር
ላይ
ቅሬታን አስቀርላችሁ ዘንድ: በታላቅ መድኃኒትም
አድናችሁ ዘንድ ከእናንተ በፊት ላከኝ::" +"+ (ዘፍ.
45:4-8)

<<< ወስብሐት ለእግዚአብሔር >>>

https://www.tg-me.com/zikirekdusn
ዝክረ ቅዱሳን ማኅበረ ቅዱስ ዳዊት - ዘብሔረ ጎንደር (ዲ/ዮርዳኖስ አበበ):
#Feasts of #Senne_1

✞✞✞On this day we commemorate Saint Joseph the Righteous✞✞✞

✞✞✞In the name of the Father, the Son and the Holy Spirit, one God. Amen!✞✞✞

✞✞✞ Saint Joseph the Righteous✞✞✞
=>The Church has many saints that are called by this name. However, Joseph, the son of the one called Israel, Jacob, takes precedence from all. He was one of the saints whose lives were written down in the great Holy Bible.

✞And we must read Genesis from Chapter 39 to 50 to get a detailed story of the Saint. Beyond that, in the Accounts of the Church much has been said about him.

✞The Bible when it begins tells us about Adam. And then it speaks about the saints
*Seth
*Enoch
*Noah
*Shem
*Abraham
*Isaac
*Jacob
*And then it reaches Saint Joseph.

✞St. Joseph was one of the 2 dear children of Jacob (Israel) whom he had from his beloved wife Rachel. Though the Saint lost his mother, he grew up in favor before his father and his Creator. And that was because he was sincere, obedient, and loving.

✞And he did not think ill of his brothers who hated him bitterly. Rather he wandered in the desert looking for them while carrying [their] ration (their lunch).

✞And on the road, when he became hungry, instead of eating from their lunch, he wept and the God of his fathers fed him by transforming rock to bread. Nonetheless, his 10 brothers in return of his kindness, conspired to kill him. And the reason was because they were jealous of him thinking that he was going to rule over them basing the dream that he had dreamt, which was from God, and told them about.

✞And finally by the council of Judah they sold him to Arab merchants. And by this, he became a typology for Christ, Who was sold by Judas and also for His passion. Even though his brothers sold the Saint, there was the Will of God in their act. Hence, where he was sold as a slave, in the house of Potiphar, God gave him favor.

✞And there, because he girdled his youth with the love of God, he did not bow down to the requests of adultery by the wife of Potiphar. And when she said, “No one will see us”, he replied, “Though no one sees us, how can I do this great wickedness, and sin before God?” and escaped from transgression. And in turn, he was imprisoned.

✞And since God was with him, he gained favor in prison and was chosen as a leader [in charge of the other prisoners]. As it is said in a text “Joseph did not go a night without being appointed”. Thereafter, he interpreted the dreams of the servants of the King. And later, he amazed the Pharaoh himself by interpreting his dream. And the Pharaoh appointed him over his land (Egypt).

✞St. Joseph, while he ruled in the land of Egypt, saved the people from starvation. And he provided food to his holy father, Israel, and his brothers as well, who were previously cruel to him. And he bore Ephraim and Manasseh after marrying a woman named Asenath.
   
✞At 110 years, after delighting God in all his ways, and after receiving blessing from his father, he passed away on this day in a good old age. And his kinsfolk buried him with great lamentation and honor. And according to his prophecy by which he said “Translocate my body”, his children (Moses and others), when they were freed from bondage in Egypt, translated his relics to Canaan. 

✞✞✞Saint Leontius (Laventius)✞✞✞
=>The Saint was born around the 3rd century and he was from Tarablos /Ṭarābulus in Arabic/ (Tripoli, Lebanon). At the time, he used to serve the rulers as a soldiers. And because he was a virgin and a handsome youth, he had favor before the people.

✞And though he was a soldier, he usually fasted and prayed. Particularly, he frequently prayed the Psalms of David and loved it. And because all his speech was sweetened by the Holy Spirit, he converted many of his friends from blasphemy to the Faith and from cruelty to kindness.
✞And when the Era of Persecution was at hand, he preached the name of Christ in public. And when wicked people accused him and he was brought before the governor, he was not fearful. Rather, he chanted while the soldiers threw him down, beat him, and his blood flowed on the ground.

✞And finally, he was beheaded for the love of Christ. Let us call upon St. Leontius (Laventius) in faith as he is a wonder working Saint. The Church commemorates today the miracle he performed. And it was also on this day that the consecration of his church took place.

✞✞✞May the God of the Saints give us the Month of Senne for blessing, repentance, to do righteousness and bear fruit. And may He grant us from the diligence, grace, and blessing of the martyr. 

✞✞✞Annual feasts celebrated on the 1st of Senne
1. St. Joseph the Righteous (Jacob’s son)
2. Our Mother Asenath (St. Joseph’s wife)
3. St. Leontius (Laventius)
4. St. Abe-Fam (Bifam or Phoebammon) the Martyr
5. St. Cosmas (Qozman) El-Tahawy the Martyr

✞✞✞Monthly Feasts
1. Nativity of the Virgin Mary, our Lady
2. Sts. Joachim and Anna
3. St. Bartholomew the Apostle
4. St. (Mar) Melki of Kuelzem (Full of Virtues)
5. St. Raguel the Archangel

✞✞✞“And he said, I am Joseph your brother, whom ye sold into Egypt. Now therefore be not grieved, nor angry with yourselves, that ye sold me hither: for God did send me before you to preserve life. . .And God sent me before you to preserve you a posterity in the earth, and to save your lives by a great deliverance.”✞✞✞
Gen. 45:4-8

✞✞✞ Salutations to God ✞✞✞

(Translated by Mhr. Esuendale Shemeles with the permission of Dn. Yordanos Abebe)
እንኳን አደረሳችሁ

💠"መንግሥተ ሰማያት ቀርባለችና ንስሐ ግቡ::"💠    /ማቴ ፫:፫/

🔶ዝክረ ቅዱሳንን ተማሩ ብለን እንለምናችኋለን!!

        እናስተውል!!

🔸1,ጥሩ ክርስትና ፈጥኖ የሚገኝ አይደለም፡፡ ትእግስትን ይጠይቃል፡፡
🔸2,ሰይጣን እኛን ኃጢአት በማሠራት አይረካም፡፡ የሚፈልገው ተስፋ ማስቆረጥ ነው፡፡
🔸3, በእምነት የሚደረግ የትኛውም ጸሎት መፍትሔ አለው፡፡
🔸4,የበጎ ለውጥ እናት ዓላማና ቁርጥ ውሳኔ ናቸው

4 ነገሮችን በደንብ እንያዝ!!!

    🔻1,ዓላማ
    🔻2, እምነት
    🔻3,ጥረት
    🔻4,ጥንቃቄ

ዝክረ ቅዱሳን ማኅበረ ቅዱስ ዳዊት ጉባኤ ዘጎንደር

🌿ፍቅር ያጌብረኒ ከመ እንግር ዜናሆሙ ለቅዱሳን! (የቅዱሳንን ታሪክ እንድመሰክር ፍቅር ያስገድደኛል)
🌿አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ (መጽሐፈ ምሥጢር)

🔗
https://www.tg-me.com/zikirekdusn
▶️
https://www.youtube.com/@ZikereKedusan
Audio
🕊መንግሥተ ሰማያት ቀርባለችና ንስኅ ግቡ🕊 (ማቴ ፫:፫)

ርዕስ፦📝

"" አገልግሎቴ ቅዱሳንን ደስ የሚያሰኝ ይሆን ዘንድ ጸልዩ! "" (ሮሜ. ፲፭ : ፴፩)

"ቅድስት አመተ ክርስቶስ"

📅(ግንቦት 28 - 2016)

🎤 በመምህር ዲ/ዮርዳኖስ አበበ

ዝክረ ቅዱሳን ማኅበረ ቅዱስ ዳዊት

🌿ፍቅር ያጌብረኒ ከመ እንግር ዜናሆሙ ለቅዱሳን! (የቅዱሳንን ዜና እንድመሰክር ፍቅር ያስገድደኛል)

🌿አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ (መጽሐፈ ምሥጢር)

🔗https://www.tg-me.com/zikirekdusn
▶️
https://www.youtube.com/@ZikereKedusan
††† እንኩዋን ለበዓለ ዸራቅሊጦስ (መንፈስ ቅዱስ) በሰላም አደረሳችሁ †††

††† በዓለ ጰራቅሊጦስ (መንፈሰ ጽቅድ) †††

=>ከዚሕ በፊት እንደተመለከትነው የጌታችን ዓበይት በዓላቱ 2 ጊዜ (ማለትም
ጥንተ በዓልና የቀመር በዓል ተብለው) ይከበራሉ:: ዛሬም ከ➊➒➐➏ ዓመታት
በፊት አምላካችን መንፈስ ቅዱስ በቅዱሳን ሐዋርያት ላይ መውረዱን
እናስባለን::

††† ይህስ እንደ ምን ነው ቢሉ:-

+ቸር አምላክ ወልድ ኢየሱስ ክርስቶስ ለእኛ ሲል
*ከልዑል ማዕርጉ ወርዶ:
*በማሕጸነ ድንግል ተጸንሶ:
*በኅቱም ድንግልና ተወልዶ:
*ከኃጢአት በቀር በግዕዘ ሕጻናት አድጐ:
*በ30 ዘመኑ ተጠምቆ:
*ቅድስት ሕግ ወንጌልን አስተምሮ:
*በፈቃዱ ሙቶ:
*በባሕርይ ስልጣኑ ተነስቶ:
*በአርባኛው ቀን ያርጋል::

+ታዲያ ደቀ መዛሙርቱን የቅዱስ መንፈሱን ጸጋ ተስፋ እንዲያደርጉ ነግሯቸው
ነበርና በተነሳ በ50ኛው ቀን: በዐረገ በ10 ቀን ተስፋውን ፈጸመላቸው::

+እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ዶሮ ጫጩቶቿን በክንፎቿ እንድትይዝ
በአንድ ላይ ሰብስባ ለክብረ መንፈስ ቅዱስ አብቅታቸዋለች:: 120ው ቤተሰብ
ከጌታችን እናት ጋር ሲጸልዩ መንፈስ ቅዱስ በአውሎ ንፋስ አርአያ ወርዶ
በአምሳለ እሳት አደረባቸው::

+ቅዱሳን ሐዋርያት ፈሪዎች የነበሩ ደፋሮች: አሮጌ ሕሊና የነበራቸው
ሐዲሶች ሆኑ:: በአዕምሮ ጐለመሱ: ቁዋንቁዋ ተናገሩ: ምሥጢርም
ተረጐሙ:: በቅጽበትም ብሉይ ከሐዲስ በልቡናቸው ውስጥ ተሞላ::

+ሐዋርያቱ ቅዱስ መንፈስን ተቀብለው ዓለምን በወንጌል ዕርፈ መስቀል
አርሰዋል:: አልጫውን ዓለም ጨው ሆነው አጣፍጠዋል:: ሳይሳሱም
አንገታቸውን ለሰይፍ ሰጥተዋል::
"ኪያሁ መንፈሰ ነሢኦሙ ለለአሐዱ:
ሐዋርያት ለሰቢክ አሕጉራተ ዓለም ዖዱ:
ሰማዕትኒ ለሕማም ነገዱ::" እንዳለ ደራሲ::

በዚህ ቀን 2 ነገሮች በትኩረት ይነገራሉ:-

1."የመንፈስ ቅዱስ የባሕርይ አምላክነት:-"

እርሱ ከአብ የሠረጸ: ቅድመ ዓለም የነበረ: በባሕርይ ስልጣኑ ከአብና ከወልድ ጋር እኩል የሆነ: የራሱ ፍጹም አካል ያለው ፍጹም አምላካችን ነውና::

2."ቅድስት ቤተ ክርስቲያን:-"

አብ ያሰባት: ወልድ በደሙ የቀደሳት: መንፈስ ቅዱስ በጸጋው ያጸናት
የክርስቲያኖች አማናዊት አንድነት: አንድም ቤት ናትና:: ዛሬ በጉባዔ ተመስርታለች::

የመንፈስ ቅዱስ ቸርነቱ፤ ምሕረቱ፤ ጸጋው ይደርብን፡፡

ወስብሐት ለእግዚአብሔር ልዑል!

https://www.tg-me.com/zikirekdusn
✞✞✞On this day we commemorate the Descent of the Holy Spirit (the Feast of Pentecost)✞✞✞

✞✞✞In the name of the Father, the Son and the Holy Spirit, one God. Amen!✞✞✞

✞✞✞The Feast of Pentecost-The Descent of the Holy Spirit ✞✞✞
=>As we have seen on previous days (on Ginbot 8/May 16), the Feasts of our Lord are celebrated twice a year (i.e. the Actual Dates “Tinte Beal” and the Movable Feasts “Yeqemer Beal”). Today also we commemorate that 1,980 years ago (from 2014 E.C) took place the Descent (Dorea) of the Holy Spirit upon the Apostles. 

✞✞✞If asked how that came to be, it was as follows.
✞After the Good God, the Son - Jesus Christ, for us
*Came [to this world] by humbling Himself
*Was conceived in the womb of the Virgin
*Was born of the Virgin
*Grew up like children but without sin
*Was baptized at age of 30 years
*Taught the Gospel, the holy commandment[s]
*Died by His will
*Arose from the dead by His authority
*And ascended on the 40th day of His resurrection;

✞As He had assured His disciples of the coming of His Holy Spirit, He fulfilled the promise on the 50th day of His resurrection and the 10th day of His ascension.

✞And our Lady the Virgin St. Mary gathering together the Apostles, as a mother hen would hold its chicks within its wings, enabled them to receive honor from the Holy Spirit. And while the 120 Disciples (called “The Kin of Christ”) prayed with our Lord’s Mother, the Holy Spirit descended in the manner of a rushing mighty wind and in the likeness of fire and dwelt in them [by grace].

✞Then, the Holy Apostles who were previously fearful became brave, and their timeworn conscience was renewed. They also became illuminated, spoke [different] languages, and explained mysteries. And in an instant their hearts were filled with the Old and New Testaments.

✞And after the Apostles received the Holy Spirit, they tilled the world with the Gospel. And as salts they sweetened the flavorless world. And they gave their necks, without hesitation, to the sword [for the sake of Christ’s name].

As the author has said,
“They received each [gifts] from the Holy Spirit
And to preach to the nations of the world the Apostles went
And as witnesses [they] travelled for torment”

✞Hence, on this day, 2 things are given emphasis in the discourses.
1. The Divinity of the Holy Spirit.
*That He is perfect God, Who proceeds from the Father, has existed before the world, is equal in authority with the Father and the Son, and has His own Hypostasis.
2. The Church
*That It is a true communion of Christians which was thought by the Father, sanctified by the blood of the Son and preserved by the gift[s] of the Holy Spirit. It is also the [consecrated] building or house of worship. And that on this day, it was established as a community – an ecclesia.

=>May the God of the Saints grant us His sinful servants from the grace of His Holy Spirit.

✞✞✞“And when the day of Pentecost was fully come, they were all with one accord in one place. And suddenly there came a sound from heaven as of a rushing mighty wind, and it filled all the house where they were sitting. And there appeared unto them cloven tongues like as of fire, and it sat upon each of them. And they were all filled with the Holy Ghost (Holy Spirit), and began to speak with other tongues, as the Spirit gave them utterance.”✞✞✞
Acts 2:1-4

✞✞✞Salutations to God✞✞✞
Audio
"" ስንክሳር - ሰኔ ፩/1 ""

"በዓለ ጰራቅሊጦስ (መንፈስ ቅዱስ)"

"ወበዓለ ቅዱሳን ለውንትዮስ ወዮሴፍ ጻድቅ"

(ግንቦት 30 - 2017)

https://www.tg-me.com/zikirekdusn
እንኳን አደረሰነ!

☞ሠረቀ ወርኀ ሰኔ ቡሩክ፤ በሰላመ እግዚአብሔር፤ አሜን፡፡
ወአመ ፩፦

በዓለ ርደተ መንፈስ ቅዱስ፥ ጰራቅሊጦስ
ወተዝካረ በዓላ ለድንግል (እግዝእትነ ማርያም)

ወበዓለ ቅዱሳን አበው፦

✿አበዊነ ሐዋርያት (፲ቱ ወ፪ቱ)
✿ንጹሐን አርድእት (፸ ወ፪ቱ)
✿ቅዱሳት አንስት (፴ ወ፮ቱ)
✿ዮሴፍ ጻድቅ፥ መኮንነ ግብጽ (ወልደ ያዕቆብ እስራኤል)
✿አስኔት ብእሲቱ (ዘእምቤተ ፈርዖን)
✿ኤፍሬም ወምናሴ (ውሉዱ)
✿ለውንትዮስ ክቡር ሰማዕት (ገባሬ መንክራት)
✿ቢፋሞን ሰማዕት መስተጋድል
✿ሰማዕታት ቢጽ (ዘእምሃገረ ጣሃ)
✿ወሰማዕታት (ዘሃገረ እስክንድርያ)
✿ቶማስ ክቡር ሊቀ ጳጳሳት
✿ቆዝሞስ ሰማዕት
✿ጽርሐ ጽዮን ቅድስት

❖ወስብሐት ለእግዚአብሔር፤
ኪያነኒ ይምሐረነ በጸሎቶሙ።
ወበረከቶሙ ይብጽሐነ፤ ለዓለመ ዓለም አሜን፡፡

https://www.tg-me.com/zikirekdusn
2025/07/13 22:23:16
Back to Top
HTML Embed Code: