Telegram Web Link
እንኳን አደረሰነ!

☞ወርኀ ሰኔ ቡሩክ፤ ወአመ ፮፦

ተዝካረ በዓለ ርደተ መንፈስ ቅዱስ፥ ጰራቅሊጦስ
ወተዝካረ ጻማ ንግደታ ለእግዝእትነ ማርያም ድንግል (ደብረ ቁስቋም)
ቅድስት ጾመ ሐዋርያት (ንጹሐን)

ወበዓለ ቅዱሳን አበው፦

✿አበዊነ ሐዋርያት (፲ቱ ወ፪ቱ)
✿ቴዎድሮስ ጻድቅ መነኮስ (ወሰማዕት)
✿፬ቱ መኳንንተ እስና (አውሳብዮስ፥ ወታማን፥ ወሐርዋግ፥ ወባኮስ)
✿ሰማዕታት ዘሃገረ መርዩጥ
✿ወ፵ ሰማዕታት (ካልዓን)
✿እንድርያስ ወአርሶንያ (ወላድያኒሁ ለአቡነ ሳሙኤል ዘወገግ)
✿ገብረ ክርስቶስ መነኮስ
✿ጽርሐ ጽዮን ቅድስት

❖ወስብሐት ለእግዚአብሔር፤
ኪያነኒ ይምሐረነ በጸሎቶሙ።
ወበረከቶሙ ይብጽሐነ፤ ለዓለመ ዓለም አሜን፡፡

https://www.tg-me.com/zikirekdusn
††† እንኳን ለታላቁ ሊቅ ቅዱስ ያዕቆብ ዘሥሩግ ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ፣ አደረሰን። †††

††† በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን! †††

††† ቅዱስ ያዕቆብ ዘሥሩግ †††

††† በቤተ ክርስቲያን ታሪክ በደራሲነታቸው : በወንጌል አገልግሎታቸውና በቅድስናቸው ከተመሠከረላቸው ዐበይት ሊቃውንት አንዱ ቅዱስ ያዕቆብ ዘሥሩግ ነው::

ሊቁ የተወለደው መጋቢት 27 ቀን በ433 ዓ/ም ሲሆን ሃገሩ ሶርያ ነው:: ወላጆቹ ክርስቲያኖች ለዚያውም አባቱ ሊቀ ካህናት ነበር:: ቅዱስ ያዕቆብ ገና በልጅነቱ ጀምሮ ጸጋ እግዚአብሔር የጠራው ነውና በብዙ ነገሩ የተለየ ነበር::

አንድ ቀን በዕለተ ሰንበት : ገና በ3 ዓመቱ : እናቱ አቅፋ ወደ ቤተ መቅደስ ወሰደችው:: ምዕመናን ቅዱስ ሥጋውንና ክቡር ደሙን ሲቀበሉ ሕጻኑ ያዕቆብም ይቆርብ ዘንድ ቀረበ:: ሊቀ ዻዻሱ ደሙን በዕርፈ መስቀል ሊያቀብለው ሲል መልአኩ መጥቶ "በጽዋው ጋተው" አለው:: የጌታን ደም በጽዋ ቢጠጣ ምስጢር ተገለጸለትና "አንሰ እፈርሕ ሠለስተ ግብራተ - እኔስ 3 ነገሮች ያስፈሩኛል" ሲል አሰምቶ ተናገረ::

††† ዻዻሱና ሕዝቡ ወደ ሕጻኑ ያዕቆብ ቀርበው "ምን ምን?" አሉት:: እርሱም:-
1.ነፍሴ ከሥጋየ ስትለይ::
2.ቅድመ እግዚአብሔር ለፍርድ ስቀርብ::
3.ከፈጣሪየ የፍርድ ቃል ሲወጣ" አላቸው::
ያን ጊዜ ሕዝቡና ሊቀ ዻዻሳቱ "እግዚአብሔር በዚሕ ሕጻን አድሮ ዘለፈን" እያሉ ለንስሃ በቅተዋል::

ቅዱስ ያዕቆብ 7 ዓመት ሲሞላው ይማር ብለው ወደ ጉባዔ አስገቡት:: በ5 ዓመታት ብሉይ ከሐዲስ ጠንቅቆ በ12 ዓመቱ ሊቅ ሆኗል:: በዚህ ወቅት የነበሩ ታላላቅ ሊቃነ ዻዻሳት ወደ እርሱ ተሰበብስበው "እንግዳ ድርሰት ድረስልን:: አዲስ ምሥጢር ንገረን" አሉት:: እርሱ ግን ሲቻለው ስለ ትሕትና "አልችልም" አላቸው::

"እንግዲያውስ ትንቢተ ሕዝቅኤልን ተርጉምልን" ቢሉት ባጭር ታጥቆ አመሥጥሮላቸው ተደስተዋል:: ፈጣሪንም አመስግነዋል::

ቅዱስ ያዕቆብ ከዚህ በኋላ ወደ ገዳም ገብቶ ትሕርምተ አበውን : ዕጸበ ገዳምን : ሕይወተ ቅዱሳንን በተግባር ተምሯል:: በድንግልናው ጸንቶ : ጾምና ጸሎትን እያዘወተረ ኑሯል:: በፈቃደ እግዚአብሔር የሥሩግ (በኤፍራጥስና ጤግሮስ ወንዞች መካከል የምትገኝ የሶርያ ግዛት ናት) ኤዺስ ቆዾስ ሆኖ ተሹሟል::

††† በዘመኑም:-
1.የ451ን የኬልቄዶን ጉባኤ አውግዟል::
2.ብዙ መናፍቃንን ተከራክሮ ምላሽ አሳጥቷል::
3.በወንጌል አገልግሎት መልካም እረኝነቱን አሳይቷል::
4.ዛሬ የምንገለገልበትን መጽሐፈ ቅዳሴውን ጨምሮ በርካታ መንፈሳዊ ድርሰቶችን ደርሷል::

በመጨረሻም ከብዙ የተጋድሎና የቅድስና ዓመታት በኋላ በተወለደ በ72 ዓመቱ በ505 ዓ/ም በዚሕች ቀን አርፏል:: አንዳንድ ምንጮች ደግሞ ሰኔ 27 ቀን እንዳረፈ ይናገራሉ:: ቅዱስ ያዕቆብ ዘሥሩግ ለቤተ ክርስቲያን የቁርጥ ቀን ተወዳጅ ልጇ ነውና በእጅጉ ታከብረዋለች::

††† አምላከ ቅዱሳን ከታላቁ ሊቅ በረከት ይክፈለን::

††† ሰኔ 7 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት
1.ቅዱስ ያዕቆብ ዘሥሩግ
2.ቅዱስ : ቡሩክና አሸናፊ አባ አበስኪሮን (ታላቅ ሰማዕትና ባለ ብዙ ተአምራት ነው)
3."16,000" ሰማዕታት (በአንድ ቀን የተገደሉ)
4.የእመቤታችን ቤተ ክርስቲያን የተከፈተበት በዓል (ከ1ሺ ዓመታት በፊት ምስር (CAIRO) ውስጥ)

††† ወርሐዊ በዓላት
1.ሥሉስ ቅዱስ (አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ)
2.አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ
3.አባ ሲኖዳ (የባሕታውያን አለቃ)
4.አባ ዳንኤል ዘገዳመ ሲሐት
5.አባ ባውላ ገዳማዊ
6.ቅዱስ አትናቴዎስ ሐዋርያዊ
7.ቅዱስ አግናጥዮስ (ለአንበሳ የተሰጠ)

††† "ይሕንን እዘዝና አስተምር :: በቃልና በኑሮ : በፍቅርም : በእምነትም : በንጽህናም ለሚያምኑቱ ምሳሌ ሁን እንጂ ማንም ታናሽነትህን አይናቀው:: እስክመጣ ድረስ ለማንበብና ለመምከር : ለማስተማርም ተጠንቀቅ::" †††
(1ጢሞ. 4:11)

††† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †††
#Feasts of #Senne_7

✞✞✞On this day we commemorate the Departure of the Great Scholar Saint Jacob of Serugh✞✞✞

✞✞✞In the name of the Father, the Son and the Holy Spirit, one God. Amen!✞✞✞

✞✞✞Saint Jacob of Serugh✞✞✞
=>St. Jacob of Serugh is one of the major scholars about whose authorship, ministry of the Gospel, and holiness Church History attests. 

✞The Scholar was born in Syria on Megabit 27 (April 5) in the year 433 E.C. His parents were Christians and on top of that his father was an Archpriest. And as St. Jacob was called by the Grace of God from his childhood, he was unique in many aspects.

✞One day, on a Sunday, while he was just three years old, his mother carried him to Church. And when the faithful partook of the Holy Body and Blood, the child Jacob also went to partake from the Holy Eucharist. And when the Archbishop was about to give him from the Holy Blood with a cross-spoon, an angel appeared and said, “Make him drink from the chalice”. And when the Saint sipped the Holy Blood of the Lord from the chalice, mystery was revealed to him and he said aloud, “Three things frighten me.” 

✞Then the Bishop and the people came closer to the child, Jacob, and asked, “What and what?” And the Saint answered to them saying,
1. “When my soul departs from my body.
2. When I am brought before God for judgment.
3. And when a verdict comes forth from my Creator.”

✞And at that moment, the people and the Archbishop said, “God has rebuked us by indwelling in this child” and were able to repent.

✞And when St. Jacob became seven years old, his parents placed him in school. And within 5 years, he completed his learning, and was well versed in the Old and New Testaments. And he became a scholar at the age of 12. And great archbishops of the time went to him and asked, “Write for us a new homily and tell us a new mystery.” However, he replied, “I cannot”, though he was able, for the sake of humility. 

✞And when they requested saying, “Then exegete for us the Book of Ezekiel”, he readily expounded it for them and they were joyous and praised the Creator.
 
✞After this, St. Jacob entered a monastery and learned practically the teachings of the elders, the struggles of monasticism, and the lives of the saints. And he lived preserved in his virginity making fasting and prayer his daily habits. And by the will of God, he was ordained as the Episcopos of Serugh (a region of Syria in between the Euphrates and Tigris rivers).

✞And in his day, he
1. Denounced the Council of Chalcedon of 451 A.D.
2. Argued with and silenced many heretics.
3. Showed that he was a good shepherd through his ministry of the Gospel.
4. Wrote many spiritual works including his anaphora (The Anaphora of St. Jacob of Serugh) which we use until today.

✞Finally, he passed away on this day at the age of 72 in the year 505 E.C after many years of strife and holiness. Some sources say that he passed away on Senne 27 (July 4). As St. Jacob of Serugh was the son of the Church in Her time of need, She honors him highly.   

✞✞✞May the God of the Saints grant us from the blessing of the Great Scholar.

✞✞✞Annual feasts celebrated on the 7th of Senne
1. St. Jacob of Serugh
2. The Blessed and Victorious St. Abba Abaskhiroun (A great martyr who has performed numerous miracles)
3. 16,000 Martyr (Killed in a day)
4. The Feast of the Re-opening of Our Lady’s Church (A thousand years ago in Cairo)

✞✞✞ Monthly Feasts
1. The Holy Trinity (The Father, the Son and the Holy Spirit)
2. Abba Giorgis of Gascha
3. Abba Shenouda (Shenoute) (The Archimandrite)
4. Abba Daniel of the Monastery of Scete
5. Abba Paula the Monastic
6. St. Athanasius the Apostolic
7. St. Ignatius of Antioch (martyred by being given to lions)

✞✞✞“These things command and teach. Let no man despise thy youth; but be thou an example of the believers, in word, in conversation, in charity, in spirit, in faith, in purity. Till I come, give attendance to reading, to exhortation, to doctrine.”✞✞✞
1Tim. 4:11-13

✞✞✞ Salutations to God ✞✞✞
አቤቱ አምላካችንና መድኃኒታችን #ኢየሱስ_ክርስቶስ ሆይ! በፊትህ ራሳቸውን ዝቅ ዝቅ ስላደረጉ ሰዎች እንለምንሃለን . . .

ልጆቻቸውን አሳድግ::
¤ጐልማሶቻቸውን አጐልምስ::
¤ሽማግሎቻቸውን ደግፍ::
¤የተንቀጠቀጡትን አጽና::
¤ሴቶቻቸውን ጠብቅ::
¤ልጆቻቸውንም አደራ አስጠብቅ::

¤የተራቡትን አጥግብ::
የተጠሙትንም አርካ::
¤ለተራቆቱት አልብስ::
የተጨነቁትንም አሳርፍ::
¤የተከዙትን ደስ አሰኝ::
ያዘኑትንም አስደስት::

¤የታመሙትን አድን::
¤ድውያኑንም ፈውስ::
¤የዕውራኖቻቸውንም ዐይን አብራ::
¤የማይሰሙትንም ጀሮ አሰማ::
¤እሥሮቻቸውንም ፍታ::
¤የተማረኩትንም አድን::

ሥጋቸውን አንጻ::
ነፍሳቸውን አክብር::
ወደ ቤታቸውም በሚገቡበት ጊዜ አቤቱ አንተ መርተህ ከዚያ አድርሳቸው::

<< አቤቱ! ለዘለዓለሙ ጠብቃቸው:: ከፍ ከፍም አድርጋቸው:: >>

(#ቅዱስ_ያዕቆብ_ዘሥሩግ)

<<< ከቅዱሱ ሊቅ : ከበዓሉም በረከትን አምላኩ ይክፈለን:: >>>
ፍቅር ያጌብረኒ ከመ እንግር ዜናሆሙ ለቅዱሳን"::/የቅዱሳንን ዜና(ታሪክ) እንድመሰክር ፍቅር ያስገድደኛል:: አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ /መጽሐፈ ምሥጢር/
https://www.tg-me.com/zikirekdusn
🕊መንግሥተ ሰማያት ቀርባለችና ንስኅ ግቡ🕊
(ማቴ ፫:፫)

በአማን ተንሥአ መድኃኒነ!
🌿ብፁዕ አባ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ዘኤለ ገዳማተ እምኀበ እግዚኡ ይነሣእ እሴተ ቦአ ሀገረ ደብረ ሊባኖስ በፍሥሐ ወበሰላም።

ሰአል ለነ ጊዮርጊስ ኀበ እግዚአብሔር ወጸሊ በእንቲአነ ሐረድዎ ወገመድዎ ወዘረዉ ሥጋሁ ከመ ሐመድ ወወሰድዎ ኀበ ሰብአ ነገሥት ረገጸ ምድረ አንሥአ ሙታነ አባ ጊዮርጊስ በሰላም ዐደወ መንግሥተ ክብር ወረሰ።

🌿ወልደ እግዚአብሔር አምላክነ ወመድኃኒነ ዕቀብ  ሕይወተነ እም ገሀነመ እሳት ወእምኵሉ መንሱት በእንተ ቅዱስ ስምከ ወበእንተ ማርያም እምከ ወበእንተ ቅዱስ መስቀል ወበእንተ ዮሐንስ ወንጌላዊ ወበእንተ ዮሐንስ መጥምቅከ ወበእንተ ኵሎሙ ቅዱሳን ወሀባ ሰላመ ለሀገሪትነ ኢትዮጵያ ወለቅድስት ቤተክርስቲያን።

ሰላም ለክሙ ጻድቃን ወሰማዕት እለ አዕረፍክሙ በዛቲ ዕለት መዋዕያነ ዓለም አንትሙ በብዙኅ ትዕግሥት። ሰአሉ ቅድመ ፈጣሪ በኩሉ ሰዓት እንበለ ንስሐ ኪያነ ኢይንሣእ ሞት።

🌿አንቅሐኒ በጽባሕ ክሥተኒ ዕዝንየ በዘአጸምእ አምላኪየ አምላኪየ እገይሥ ኀቤከ ዘይሰማዕ ግበር ሊተ ምሕረተከ በጽባሕ"

ነቢያት ወሐዋርያት፥ ጻድቃን ወሰማዕት፤ ደናግል ወመነኮሳት፥ አዕሩግ ወሕጻናት፤ ገዳማውያን ወሊቃውንት፤ ሰአሉ ለነ ኲልክሙ፥ ቅድመ መንበሩ ለጸባኦት።

🌿እግዝእትየ ፍትሕኒ እማዕሠሩ ለሰይጣን፤
እሙ ለመድኅን ወለተ ብርሃን።

ዝክረ ቅዱሳን ማኅበረ ቅዱስ ዳዊት ጉባኤ ዘጎንደር

🌿ፍቅር ያጌብረኒ ከመ እንግር ዜናሆሙ ለቅዱሳን! (የቅዱሳንን ታሪክ እንድመሰክር ፍቅር ያስገድደኛል)
🌿አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ (መጽሐፈ ምሥጢር)

🔗https://www.tg-me.com/zikirekdusn
▶️https://www.youtube.com/@ZikereKedusan
እንኳን አደረሰነ!

☞ወርኀ ሰኔ ቡሩክ፤ ወአመ ፯፦

ተዝካረ በዓለ ርደተ መንፈስ ቅዱስ፥ ጰራቅሊጦስ
ወተዝካረ በዓለ ሥሉስ ቅዱስ (አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ)
ተርኅወታ ወቅዳሴሃ ለቤተ ክርስቲያን ዘእግዝእትነ ማርያም ድንግል (በሃገረ ምስር)
ቅድስት ጾመ ሐዋርያት (ንጹሐን)

ወበዓለ ቅዱሳን አበው፦

✿አበዊነ ሐዋርያት (፲ቱ ወ፪ቱ)
✿ቡሩክ ወመዋዒ ሰማዕት አባ አበስኪሮን (ዘሃገረ ቀሊን)
✿ማኅበራኒሁ ሰማዕታት
✿ያዕቆብ ጻድቅ ኤጲስ ቆጶስ (ዘሥሩግ)
✿፼ ወ፷፻ ሰማዕታት (እለ ኮነኖሙ አርማንዮስ)
✿ጽርሐ ጽዮን ቅድስት

❖ወስብሐት ለእግዚአብሔር፤
ኪያነኒ ይምሐረነ በጸሎቶሙ።
ወበረከቶሙ ይብጽሐነ፤ ለዓለመ ዓለም አሜን፡፡

https://www.tg-me.com/zikirekdusn
ቅዳሴ ቤታ ለድንግል በሃገረ ምስር፤
ወአባ አበስኪሮን ኃያል ገባሬ መንክር፤
ቅዱስ ያዕቆብ ዘሥሩግ ብእሲ ማዕምር፤
ወሰማዕታት ሔራን ፍቁራነ እግዚአብሔር!
††† እንኳን ለእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ዓመታዊ በዓል በሰላም አደረሳችሁ፣ አደረሰን። †††

††† በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን! †††

††† በዓሉ ከሰላሳ ሦስቱ ዓበይት የእመቤታችን በዓላት አንዱ ሲሆን በዚሕች ቀን ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከድንግል እናቱ እግር ሥር ጠበል አፍልቋል::

††† ጥንተ ነገሩስ እንደ ምን ነው ቢሉ:-
ድንግል ማርያም አምላክ ልጇን አዝላ ስደት ወጥታ ምድረ ግብጽ ትደርሳለች:: በወቅቱ ከደረሱባት ችግሮች አንዱ ደግሞ ረሃብና ጽሙ ነበር:: እንኳን ለስደተኛ በቤቱ ላለም ረሃብና ጥም እንዴት እንደሚከብድ የደረሰበት ያውቀዋል::

††† ለዛም ነው ሊቁ በቅዳሴው:-
"አዘክሪ ድንግል ረሃበ ወጽምዐ : ምንዳቤ ወኀዘነ : ወኩሎ ዐጸባ ዘበጽሐኪ ምስሌሁ" ያለው::

ታዲያ አንድ ቀን የበርሃው ፀሐይ አቃጥሏቸው ባረፉበት ድንግል እመቤታችን ውኃ ልመና ወጣች:: ብዙ ለመነች : ግን ጥርኝ እንኳ የሚሠጣት አጥታ በሐዘን ተመለሰች:: ስትመለስ ግን ይባስ ብሎ የልጇን ጫማ ሽፍቶች ወስደውት ደረሰች::

ያን ጊዜ ልጇን ታቅፋ "ውኃ ሳላገኝልሕ : ጫማሕንም አሰረቅኩብህ" ብላ ምርር ብላ አልቅሳለች::
"በከየት ወትቤ ማርያም ማዕነቅ::
እምሰብአ ሃገር አልቦ ዘየአምራ ለጽድቅ::
ሰአልክዎሙ ማየ ኢወሀሐቡኒ በሕቅ::
ወአሕጎልኩ ለወልድየ አሳእኖ ዘወርቅ::" እንዳለ ደራሲ::

ይሕንን የተመለከተ ልጇ የቆመችበትን መሬት ቢባርከው ሕይወትነት ያለው ማይ (ጠበል) ፈለቀ:: ጌታችን : እመቤታችን: ዮሴፍና ሰሎሜ ከውኃው ጠጥተዋል::

ሲሔዱ ግን ለእንግዶች ጣፋጭ (መድኃኒት) : ለአካባቢው ሰዎች ግን መራራ ሁኗል::
"ከመ ኢይስተይዋ ሰብአ ሐገር ለይእቲ ማይ አምረራ::
ወለርኁቃንሰ ፈውሰ ወጥዕምተ ገብራ::" እንዳለ መጽሐፍ:: (ሰቆቃወ ድንግል)

ከመቶዎች ዓመታት በኋላም ጌታ ጠበል ያፈለቀበት : ድንግል እመቤታችን የቆመችበት ቦታ ላይ በእመ ብርሃን ስም ቤተ ክርስቲያን ታንጿል:: ቅዳሴ ቤቱም ተከብሯል:: ጠበሉም ሲባርክና ሲፈውስ ይኖራል::

††† የጠበል በዓል †††

†††ዳግመኛ ዕለቱ የጠበል በዓል ተብሎም ይታሠባል:: ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ስለ ጠበል ፈዋሽነት ሁሌ ብታስተምርም በዚህ ቀን ግን ልዩ ትኩረቷ ታደርገዋለች::

እግዚአብሔር በምክንያትም አለምክንያትም መፈወስ ይችላል:: ያለ ምክንያት በቃሉና በወዳጆቹ ቃል አድሮ "ዳን" ይላል:: ወይም ደግሞ በምክንያት በእመት (እምነት) : በጠበል : ቅዱስ ቃሉን በመስማት : በመስቀሉና በመጻሕፍት በመባረክ (በመታሸት) : በቅዱሳን አካል (በልብሳቸው : በበትራቸው : በጥላቸው በአጽማቸው . . .) ይፈውሳል::

እርሱ እግዚአብሔር ነውና በወደደውና በመረጠው አድሮ ያድናል ( ይፈውሳል):: (2ነገ. 5:10, ሐዋ. 3:6, 5:15, 19:11)

††† ዛሬ ግን የጠበል ፈዋሽነት በጉልህ ይነገራል:: (ዮሐ. 5:1, 9:7)

††† አምላከ ቅዱሳን ከደዌ ሥጋ : ከደዌ ነፍስ በምሕረቱ ይሠውረን:: ከድንግል እመቤታችን በረከትም ያሳትፈን::

††† ሰኔ 8 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት
1.የእመቤታችን ድንግል ማርያም ቅዳሴ ቤት
2.የቅዱስ ውኃ (ጠበል) መታሠቢያ
3.ቅድስት ትምዳ እናታችን
4.ቅዱስ አውሎጊስ
5.አባ አትካሮን

††† ወርኀዊ በዓላት
1.ቅዱስ ሙሴ ሊቀ ነቢያት
2.ኪሩቤል (አርባዕቱ እንስሳ)
3.አባ ብሶይ (ቢሾይ)
4.አቡነ ኪሮስ
5.አባ ሳሙኤል ዘደብረ ቀልሞን
6.ቅዱስ ማትያስ ሐዋርያ (ከአሥራ ሁለቱ ሐዋርያት)

††† "ለእግዚአብሔር ክብርን ስጡ::
ግርማው በእሥራኤል ላይ: ኃይሉም በደመናት ላይ ነው::
እግዚአብሔር በቅዱሳኑ ላይ ድንቅ ነው::
የእሥራኤል አምላክ እርሱ ኃይልን: ብርታትንም ለሕዝቡ ይሰጣል::
እግዚአብሔርም ይመስገን:::" †††
(መዝ. ፷፯፥፴፬)

††† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †††
2025/07/05 20:18:13
Back to Top
HTML Embed Code: