Telegram Web Link
✞✞✞The Ascension of our Lord✞✞✞
=>Our Holy Church celebrates the Ascension 2 times a year. One is “Tinte Beal” - the date on which the actual ascension took place and the other is called “Yeqemer Beal” – one which is calculated - a movable feast. “Tinte Beal” indicates the exact/actual date on which our Lord ascended.

✞The Holy Savior, Jesus Christ, to Whom is glory, after He saved the world in His wisdom (passion and death), He taught the Apostles for 40 days the Book of Covenant and the Teachings of the Hidden Things (The Mystagogia).

✞And on the 40th day, He took the 120 Disciples to Bethany. There, He ordained them to the rank of Archbishops, ordered them not to get out of Jerusalem, instructed them to wait for the hope of the Holy Spirit, and ascended with His incarnate body to His heavenly throne while blessing them.

✞The heavens, earth, the clouds, the winds, lightening, the angels and all of creation praised at that moment. And our Lord, so that the Jews and the heretics will not say His ascension was an illusion, and to also indicate His resurrection was true ascended on the 40th day.

✞And since ‘where the head is all the body parts are present’, He made His ascension in public. As it was said, “The Lord ascended to make known the ascension of the saints, the pure.”

✞✞✞”God is gone up with a shout, the Lord with the sound of a trumpet. Sing praises to God, sing praises: sing praises unto our King, sing praises.” ✞✞✞
Psalm 46 (47):5-6

✞✞✞"And he led them out as far as to Bethany, and he lifted up his hands, and blessed them. And it came to pass, while he blessed them, he was parted from them, and carried up into heaven. And they worshipped him, and returned to Jerusalem with great joy: And were continually in the temple, praising and blessing God. Amen."✞✞✞
Luke 24:50-53
ስለ ምሥጢራተ ቅድሳት

ከኢትዮዽያ #ኦርቶዶክስ_ተዋሕዶ ምዕመናን አብዛኛው #ከቅዱስ_ሥጋውና_ክቡር_ደሙ የራቀ መሆኑን ሳስብ በጣም አዝናለሁ!

ግን ለምን ???

ለምን ብዙዎቻችን #ሕይወት_መድኃኒት ከሆነው ማዕድ ተለየን ???

ከቅዱስ ሥጋው ሳይበሉ: ከክቡር ደሙ ሳይጠጡ መዳን ይኖር ይሆን ???

በሰማያዊው ዙፋን #በዘለዓለም_አምላክ_በክርስቶስ ፊትስ በቂ መልስ ይኖረን ይሆን ???

ሁልጊዜ ባልረባ ምክንያት ሕይወት ከሆነው #ማዕደ_ክርስቶስ እስከ መቼ እንርቃለን ???

+እርሱ ግን አሰምቶ ይጠራናል:: "ኑ! ሥጋየን ብሉ: ደሜንም ጠጡ" ይለናል:: "ሥጋየን የሚበላ: ደሜንም የሚጠጣ የዘለዓለም ሕይወት አለው:: እኔም በእርሱ አድሬበት እኖራለሁ" ይለናል:: (ዮሐ. 6:56)

+ሌላ መንገድ አለ እንዳይመስለን ደግሞ "የሰውን ልጅ (የክርስቶስን) ሥጋውን ካልበላችሁ: ደሙንም ካልጠጣችሁ በራሳችሁ ሕይወት የላችሁም" (ዮሐ. 6:53) የሚል ተግሣጽን ልኮልናል::

+ቤተ ክርስቲያን እኛን ወደ #ምስጢረ_ቁርባን ለማድረስ ከእነዚህ የተረፈ ነገር አልጫነችብንምኮ!

¤በሃይማኖት መኖር (መመላለስ)
¤ከክርስቶስ (ከጌታችን) ጋር ለመኖር ቁርጥ ውሳኔ
¤በመምሕረ ንስሃ ሥር መጠለል
¤በንስሃ ሕይወት መመላለስና
¤ቀዋሚ የሕይወት መሥመር (ጋብቻ ወይ ምናኔ) መያዝን ትሻለች እንጂ መቼ ሌላ ቀንበር ጫነችብን!

+እናም የመንፈስ ወንድሞቼና እህቶቼ . . .
¤የራቅን እንቅረብ!
¤የቀረብንም እንበርታ!
¤የበረታንም እንጽና!
¤የጸናንም ደካሞቹን እንርዳ! (ይህ በጌታ ዘንድ ዋጋው ትልቅ ነውና!)

#የምሕረት_ጌታ #ለምሥጢራተ_ቅድሳት የምንበቃበትን የምሕረት ዘመን ያምጣልን::

☞ግን እናስብበት!!!

<<< ወስብሐት ለእግዚአብሔር >>>

Re. Dn Yordanos Abebe


https://www.tg-me.com/zikirekdusn
Audio
"" ከአራዊት ጋር ነበረ ! "" (ማር. ፩:፲፫)

"ዜናሁ ለአቡነ ዓቢየ እግዚእ ክቡር"

(ግንቦት 19 - 2017)
እንኳን አደረሰነ!

☞ወርኀ ግንቦት ቡሩክ፤ አመ ፳ወ፩፦

በዓል ዐቢይ ወክቡር - ዕለተ ዕርገቱ ለአምላክነ ኢየሱስ ክርስቶስ (በዓለ ዕርገት ስቡሕ)
በዓለ አስተርእዮታ ለእግዝእትነ ማርያም ድንግል፥ ወላዲተ አምላክ
ቅድስት ደብረ ምጥማቅ (ሐመረ ብርሃን)

✞ወበዓለ ቅዱሳን አበው፦

✿ሐዋርያት አበዊነ (መምህራን ክቡራን)
✿፸ወ፪ቱ አርድእት ወቅዱሳት አንስት
✿ቢታንያ ቅድስት (መካነ ዕርገቱ ለመድኅን)
✿ዐቢይ ወክቡር መርትያኖስ ዘአቴና (ኃያል ወመስተጋድል)
✿አሮን ሶርያዊ መስተጋድል (ገባሬ ተአምር ወመንክር)
✿ዞዊ ወፎጢና (አንስት ንጹሐት)
✿አሞጽ ነቢይ ወመርዶላ
✿ንጉሥነ ሐፄ ዘርዓ ያዕቆብ

❖ወስብሐት ለእግዚአብሔር፤
ኪያነኒ ይምሐረነ በጸሎቶሙ።
ወበረከቶሙ ይብጽሐነ፤ ለዓለመ ዓለም አሜን፡፡

https://www.tg-me.com/zikirekdusn
✞✞✞ በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ
አምላክ ፡፡ አሜን ፡፡ ✞✞✞

ግንቦት 22 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት

+"+ ቅዱስ እንድራኒቆስ +"+

=>ቅዱስ ወብጹእ እንድራኒቆስ ሐዋርያ ትውልዱ ነገዱ
ከቤተ እሥራኤል ሲሆን ከ72ቱ አርድእት አንዱ ነው::
ጌታችን በመዋዕለ
ስብከቱ 120 ቤተሰቦቹን ሲመርጥ እርሱን ከአርድእት ጋር
ደምሮ አስተምሮታል::

+ሰብዐው አርድእት በጌታችን ተልከው አጋንንት
ሲገዙላቸው ከእነርሱ አንዱ ቅዱስ እንድራኒቆስ ነበር::
ይሕ የተፈጸመ ገና
መድኃኔ ዓለም ከመሰቀሉ በፊት ነው:: (ሉቃ. 10:1-20)

+ቅዱሱ ከጌታችን ዕርገት በኋላ ከሐዋርያት ጋር ለ10
ቀናት በሱባኤ ሰንብቶ የመንፈስ ቅዱስን ሐብት
ተቀብሏል:: እንደ
ባልንጀሮቹም ወደ ዓለም ወጥቶ የወንጌል የምሥራችን
ሰብኳል:: በተለይ ከቅዱስ ዻውሎስ ጋር ለበርካታ ዓመታት
አምላኩን
አገልግሏል:: ቅዱስ ዻውሎስም በቆረንቶስ እያለ ቅዱስ
እንድራኒቆስ በሮም ያስተምር ነበር:: ለዛም ነው በሮሜ
መልዕክቱ
16:7 ላይ "እንድራኒቆስን ሰላም በሉ" ያለው::

+ቅዱስ ዻውሎስ በሰማዕትነት ካረፈ በኋላ ከቅዱስ
ዮልዮስ ጋር ሆነው የአህዛብን ልቡና በወንጌል
አብርተዋል:: እጅግ ብዙ
መከራ ደርሶባቸዋል:: ከእግዚአብሔር በተሰጣቸው
ትዕግስት ድል ነሥተዋል:: በዚሕም በርካታ የጣኦት
ቤቶችን አፍርሰው
አብያተ ክርስታያናትን አንጸዋል::
በአሕዛብም ፊት ድንቅ ድንቅ ተአምራትን አሳይተዋል::

+ቅዱስ እንድራኒቆስ ብዙ መከራን ቢቀበልም አንገቱን
ይቆረጥ ዘንድ የጌታ ፈቃዱ አልነበረምና ጥቂት ታሞ
በዚሕች ቀን
አርፏል:: ባልንጀራው (ሐዋርያው) ቅዱስ ዮልዮስ በክብር
ገንዞ ቀብሮታል::

+"+ ቅዱስ ያዕቆብ +"+

=>ዳግመኛ በዚሕ ቀን ጻድቅና ተአማኒ (ታማኝ) የተባለ
የምሥራቅ ሰው ቅዱስ ያዕቆብ መታሠቢያ ይደረግለታል::

+ቅዱስ ያዕቆብ ቁስጥንጥንያ አካባቢ በርሃ ውስጥ ይኖር
የነበረ አባት ነው:: ከቅድሰና ሕይወቱ ባሻገር በደፋርነቱ
(ጥብዐቱ) ይታወቃል:: በ340ዎቹ ዓ/ም ታናሹ
ቆስጠንጢኖስ አርዮሳዊ በሆነ ጊዜ ይሔ አባት በይፋ
ገስጾታል:: በዚህም
ምክንያት መከራ ተቀብሏል: ታስሯል: ተገርፏል::
እግዚአብሔርም መናፍቁን ንጉሥ ለጦርነት በወጣበት
ቀስፎታል::

❖የአባቶቻችን አምላክ ልዑለ ባሕርይ ክርስቶስ ጸጋ
ክብራቸውን ያድለን::

❖ግንቦት 22 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት=
1.ቅዱስ እንድራኒቆስ ሐዋርያ (ከ72ቱ አርድእት)
2.ቅዱስ ያዕቆብ ምሥራቃዊ (ለክርስቶስ የታመነ)

❖ወርኃዊ በዓላት
1፡ ቅዱስ ዑራኤል ሊቀ መላእክት
2፡ ቅዱስ ደቅስዮስ
3፡ ቅዱስ ዮልዮስ ሰማዕት
4፡ ቅዱስ ሉቃስ ወንጌላዊ
5፡ አባ እንጦንስ አበ መነኮሳት
6፡ አባ ጳውሊ የዋህ

++"+ ስለ እናንተ ብዙ ለደከመች ለማርያ ሰላምታ
አቅርቡልኝ:: በሐዋርያት መካከል ስመ ጥሩዎች ለሆኑ:
ደግሞም
ክርስቶስን በማመን ለቀደሙኝ: አብረውኝም ለታሰሩ
ለዘመዶቼ ለአንድራኒቆንና ለዮልያን (እንድራኒቆስና
ዮልዮስ) ሰላምታ
አቅርቡልኝ:: +"+ (ሮሜ. 16:6)

<<< ወስብሐት ለእግዚአብሔር >>>

https://www.tg-me.com/zikirekdusn
#Feasts of #Ginbot_22

✞✞✞On this day we commemorate Saint Andronicus, one of the 72 Disciples✞✞✞

✞✞✞In the name of the Father, the Son and the Holy Spirit, one God. Amen!✞✞✞

✞✞✞ Saint Andronicus✞✞✞
=> The Blessed and Holy Andronicus the Apostle was one of the 72 Disciples whose lineage was of the House of Israel. During the ministry of our Lord, while He chose His 120 Disciples (The 120 Families), He included him with the 72.

✞ St. Andronicus was one of the Seventy-Disciples that our Lord sent and to whom the demons were subject. (Luke 10:1-20)

✞ After the Ascension of our Lord, the Saint remained in prayer for ten days with the Apostles. Then, he received the gifts of the Holy Spirit. And like his colleagues, Andronicus preached the Gospel by going out to the world. He served his Creator for many years, particularly with St. Paul. And while St. Paul was in Corinth, St. Andronicus taught in Rome. And that is why the Apostle said in his Epistle to the Romans (16:7), “Salute Andronicus.”

✞ And after St. Paul passed away as a martyr, together with St. Junia, they illuminated the hearts of the gentiles with the Gospel. And they encountered many trials which they were victorious over by forbearance, which was given to them by God. Hence, they destroyed temples and erected churches. And they have also performed many miracles before the unbelievers.

✞ Though St. Andronicus endured many trials, it was not the will of the Lord that he be beheaded. Thus, after a bit of illness, he departed on this day. And his friend, the Apostle St. Junia, honorably shrouded and buried him.

✞Saint Jacob✞✞✞
=>Also on this day, St. Jacob of the East/Orient, the righteous and faithful, is commemorated.

✞ St. Jacob was a father that lived in a desert near Constantinople. This father is known beyond his holy life for his courage. In the 340s, when Constantine the Younger became an Arian, this father rebuked him publicly. And because of this, he endured trials. He was imprisoned and lashed. And God smote the heretical Emperor [for it] where he went for battle.

✞✞✞ May the God of our fathers, Christ, Who is Divine, grant us from their honor.

✞✞✞ Annual feasts celebrated on the 22nd of Ginbot
1. St. Andronicus the Apostle (One of the 72 Disciples)
2. St. Jacob the Eastern/Oriental (One who was faithful to Christ)

✞✞✞ Monthly Feasts
1. St. Uriel Archangel
2. St. Luke the Evangelist
3. St. Dekesius (Devotee of our Lady)
4. Abba Anthony (The Father of the Monks)
5. Abba Paul the Simple

✞✞✞ “Greet Mary, who bestowed much labour on us. Salute Andronicus and Junia, my kinsmen, and my fellowprisoners, who are of note among the apostles, who also were in Christ before me.”✞✞✞
Rom. 16:6-7

✞✞✞ Salutations to God ✞✞✞

(Translated by Mhr. Esuendale Shemeles with the permission of Dn. Yordanos Abebe)
🕊መንግሥተ ሰማያት ቀርባለችና ንስኅ ግቡ🕊
(ማቴ ፫:፫)

በአማን ተንሥአ መድኃኒነ!
🌿ብፁዕ አባ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ዘኤለ ገዳማተ እምኀበ እግዚኡ ይነሣእ እሴተ ቦአ ሀገረ ደብረ ሊባኖስ በፍሥሐ ወበሰላም።

ሰአል ለነ ጊዮርጊስ ኀበ እግዚአብሔር ወጸሊ በእንቲአነ ሐረድዎ ወገመድዎ ወዘረዉ ሥጋሁ ከመ ሐመድ ወወሰድዎ ኀበ ሰብአ ነገሥት ረገጸ ምድረ አንሥአ ሙታነ አባ ጊዮርጊስ በሰላም ዐደወ መንግሥተ ክብር ወረሰ።

🌿ወልደ እግዚአብሔር አምላክነ ወመድኃኒነ ዕቀብ  ሕይወተነ እም ገሀነመ እሳት ወእምኵሉ መንሱት በእንተ ቅዱስ ስምከ ወበእንተ ማርያም እምከ ወበእንተ ቅዱስ መስቀል ወበእንተ ዮሐንስ ወንጌላዊ ወበእንተ ዮሐንስ መጥምቅከ ወበእንተ ኵሎሙ ቅዱሳን ወሀባ ሰላመ ለሀገሪትነ ኢትዮጵያ ወለቅድስት ቤተክርስቲያን።

ሰላም ለክሙ ጻድቃን ወሰማዕት እለ አዕረፍክሙ በዛቲ ዕለት መዋዕያነ ዓለም አንትሙ በብዙኅ ትዕግሥት። ሰአሉ ቅድመ ፈጣሪ በኩሉ ሰዓት እንበለ ንስሐ ኪያነ ኢይንሣእ ሞት።

🌿አንቅሐኒ በጽባሕ ክሥተኒ ዕዝንየ በዘአጸምእ አምላኪየ አምላኪየ እገይሥ ኀቤከ ዘይሰማዕ ግበር ሊተ ምሕረተከ በጽባሕ"

ነቢያት ወሐዋርያት፥ ጻድቃን ወሰማዕት፤ ደናግል ወመነኮሳት፥ አዕሩግ ወሕጻናት፤ ገዳማውያን ወሊቃውንት፤ ሰአሉ ለነ ኲልክሙ፥ ቅድመ መንበሩ ለጸባኦት።

🌿እግዝእትየ ፍትሕኒ እማዕሠሩ ለሰይጣን፤
እሙ ለመድኅን ወለተ ብርሃን።

ዝክረ ቅዱሳን ማኅበረ ቅዱስ ዳዊት ጉባኤ ዘጎንደር

🌿ፍቅር ያጌብረኒ ከመ እንግር ዜናሆሙ ለቅዱሳን! (የቅዱሳንን ታሪክ እንድመሰክር ፍቅር ያስገድደኛል)
🌿አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ (መጽሐፈ ምሥጢር)

🔗https://www.tg-me.com/zikirekdusn
▶️https://www.youtube.com/@ZikereKedusan
💠"መንግሥተ ሰማያት ቀርባለችና ንስሐ ግቡ::"💠 /ማቴ ፫:፫/)

"" ፊትህን አሳየኝ? "" (መኃ. ፪:፲፬)

"በዓለ ቅድስት ደብረ ምጥማቅ"

(ግንቦት 21 - 2014)

በመምህር ዲ/ዮርዳኖስ አበበ

ዝክረ ቅዱሳን ማኅበረ ቅዱስ ዳዊት ጉባኤ ዘጎንደር።
" ፍቅር ያጌብረኒ ከመ እንግር ዜናሆሙ ለቅዱሳን"::/የቅዱሳንን ዜና(ታሪክ) እንድመሰክር ፍቅር ያስገድደኛል:: አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ /መጽሐፈ ምሥጢር/
https://www.tg-me.com/zikirekdusn
እንኳን አደረሰነ!

☞ወርኀ ግንቦት ቡሩክ፤ አመ ፳ወ፪፦

በዓለ አስተርእዮታ ለእግዝእትነ ማርያም ድንግል፥ ወላዲተ አምላክ
ቅድስት ደብረ ምጥማቅ (ሐመረ ብርሃን)

✞ወበዓለ ቅዱሳን አበው፦

✿ሐዋርያ ክቡር እንድራኒቆስ (፩ እም፸ወ፪ቱ አርድእት)
✿ያዕቆብ ምሥራቃዊ (ተአማኒ በክርስቶስ እግዚእነ)

❖ወስብሐት ለእግዚአብሔር፤
ኪያነኒ ይምሐረነ በጸሎቶሙ።
ወበረከቶሙ ይብጽሐነ፤ ለዓለመ ዓለም አሜን፡፡

https://www.tg-me.com/zikirekdusn
2025/07/12 14:27:07
Back to Top
HTML Embed Code: