TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
" ህልምን ለማሳካት ቆራጥ መሆን ያስፈልጋል " - ከሶስተኛ ልጃችው ጋር ለ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና የተቀመጡት የ52 አመቱ አባት
ዛሬ ከሶስተኛ ልጃቸው ጋር የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና እየወሰዱ ያሉት የ52 አመቱ አባት አቶ ግዛው መኮነንን ነዋሪነታቸው በምዕራብ ጎንደር ዞን በአዳኝ ሀገር ጫቆ ወረዳ ነው።
ከሚኖሩበት ነጋዴ ባህር ከተማ ህዝብ ተሰብስቦ " መልካም እድል " ብሎ መርቆ ወደ ጎንደር ዮንቨርስቲ ከልጃቸው ጋር ሸኝቷቸዋል።
አቶ ግዛው መኮነን የ5 ልጆች አባት ሲሆኑ የ52 አመት የእድሜ ባለጸጋ ናቸው።
" በ1979 ዓ.ም የ6ተኛ ክፍል ተማሪ ነበርኩ ያውም ጎበዝ አንድ አንደኛ የምወጣ ተሸላሚ ተማሪ ነበርኩ ግን በወቅቱ አስገዳጅ በሆነ ምክንያት ትምህርቴን አቋረጥኩ " ይላሉ ከቲክቫህ ኢትዮጵያ ጋር በነበራቸው ቆይታ።
አቶ ግዛው " ትምህርቴን እንዳቋርጥ ያስገደዱኝ ወላጆቼ ናቸው በወቅቱ ደርግ በግዳጅ ለውትድርና ወጣቱን ይመለምል ነበር ያኔ ወላጆቼ ወደ በርሃ እንድገባ አስገደዱኝ ማለትም 1979 ዓ.ም ከአራት አመት የበርሃ ቆይታ በኃላ ወደ ትውልድ ከተማየ ስመለስ በ1983 ዓ.ም ማለት ነው ጏደኞቼ የ11ኛ ክፍል ተማሪ ሆነው አገኘኃቸው " ብለዋል።
" በዚህ ልዩነትማ ትምህርት አልጀምርም አንዴ ኃላ ቀርቻለሁ ብየ ሚስት አገባሁ ከዛም በተከታታይ 5 ልጆችን ወለድኩ ልጆቼን ለማሳደግም በግብርና ኃላም በንግድ ስራ ተሰማራሁ 5ተኛ ልጄን ከወለድኩ በኃላ የዛሬ 6 አመት ማለት ነው በማታው ትምህርት ክፍል ካቆምኩበት 6ተኛ ክፍል ቀጠልኩ በርትቼ በማጥናትም ለዛሬ ፈተና ደርሻለሁ " ሲሉ ገልጸዋል።
አቶ ግዛው ያኔ አብረዋቸው የተማሩ ጏደኞቻቸው እስከ ፕሮፌሰርነት ማዕረግ የደረሱ እንዳሉና በሚኖሩበት አካባቢም ፖሊስና መምህር ሆነው ህዝብን ሲያገለግሉ ሲመለከቱ ይቆጩ እንደነበር ይናገራሉ።
እሳቸው እንደሚሉት በግብርና ስራ ልጅን የማሳደግ ኃላፊነት ይዘው ህይወታቸውን ቢገፉም ጎን ለጎን የትምህርያቸው ጉዳይ ያንገበግባቸው ነበር።
የአቶ ግዛው የመጀመሪያ ልጃቸው በንግድ የተሰማራ ሲሆን ሁለተኛ ልጃቸው የግብርና ኤክስቴንሽን ሰራተኛ ናት ሶስተኛ ልጃቸው ዛሬ ከእርሳቸው ጋር በጎንደር ዩንቨርስቲ ሀገር አቀፍ ፈተናውን እየወሰደ ነው ፤ አራተኛና አምስተኛ ልጆቻቸው ተማሪዎች ናቸው።
" ህልም ለማሳካት ቆራጥ መሆን ያስፈልጋል " የሚሉት አቶ ግዛው ፈተናውን ለመውሰድ በቂ ቅድመ ዝግጅት ማድረጋቸውን እና ከልጃቸው ጋር እስከ እኩለ ሌሊት አብረው ሲያጠኑና ሲረዳዱ መክረማቸውን ተናገረዋል።
ለዩንቨርስቲ መግቢያ የሚያበቃ ውጤት ለማምጣት መዘጋጀታቸውን ውጤቱ ቢመጣም ዩኒቨርሲቲ ለመግባት መዘጋጀታቸውን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልፀዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
ባሕር ዳር
#TikvahEthiopiaFamilyBahirdar
@tikvahethiopia
ዛሬ ከሶስተኛ ልጃቸው ጋር የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና እየወሰዱ ያሉት የ52 አመቱ አባት አቶ ግዛው መኮነንን ነዋሪነታቸው በምዕራብ ጎንደር ዞን በአዳኝ ሀገር ጫቆ ወረዳ ነው።
ከሚኖሩበት ነጋዴ ባህር ከተማ ህዝብ ተሰብስቦ " መልካም እድል " ብሎ መርቆ ወደ ጎንደር ዮንቨርስቲ ከልጃቸው ጋር ሸኝቷቸዋል።
አቶ ግዛው መኮነን የ5 ልጆች አባት ሲሆኑ የ52 አመት የእድሜ ባለጸጋ ናቸው።
" በ1979 ዓ.ም የ6ተኛ ክፍል ተማሪ ነበርኩ ያውም ጎበዝ አንድ አንደኛ የምወጣ ተሸላሚ ተማሪ ነበርኩ ግን በወቅቱ አስገዳጅ በሆነ ምክንያት ትምህርቴን አቋረጥኩ " ይላሉ ከቲክቫህ ኢትዮጵያ ጋር በነበራቸው ቆይታ።
አቶ ግዛው " ትምህርቴን እንዳቋርጥ ያስገደዱኝ ወላጆቼ ናቸው በወቅቱ ደርግ በግዳጅ ለውትድርና ወጣቱን ይመለምል ነበር ያኔ ወላጆቼ ወደ በርሃ እንድገባ አስገደዱኝ ማለትም 1979 ዓ.ም ከአራት አመት የበርሃ ቆይታ በኃላ ወደ ትውልድ ከተማየ ስመለስ በ1983 ዓ.ም ማለት ነው ጏደኞቼ የ11ኛ ክፍል ተማሪ ሆነው አገኘኃቸው " ብለዋል።
" በዚህ ልዩነትማ ትምህርት አልጀምርም አንዴ ኃላ ቀርቻለሁ ብየ ሚስት አገባሁ ከዛም በተከታታይ 5 ልጆችን ወለድኩ ልጆቼን ለማሳደግም በግብርና ኃላም በንግድ ስራ ተሰማራሁ 5ተኛ ልጄን ከወለድኩ በኃላ የዛሬ 6 አመት ማለት ነው በማታው ትምህርት ክፍል ካቆምኩበት 6ተኛ ክፍል ቀጠልኩ በርትቼ በማጥናትም ለዛሬ ፈተና ደርሻለሁ " ሲሉ ገልጸዋል።
አቶ ግዛው ያኔ አብረዋቸው የተማሩ ጏደኞቻቸው እስከ ፕሮፌሰርነት ማዕረግ የደረሱ እንዳሉና በሚኖሩበት አካባቢም ፖሊስና መምህር ሆነው ህዝብን ሲያገለግሉ ሲመለከቱ ይቆጩ እንደነበር ይናገራሉ።
እሳቸው እንደሚሉት በግብርና ስራ ልጅን የማሳደግ ኃላፊነት ይዘው ህይወታቸውን ቢገፉም ጎን ለጎን የትምህርያቸው ጉዳይ ያንገበግባቸው ነበር።
የአቶ ግዛው የመጀመሪያ ልጃቸው በንግድ የተሰማራ ሲሆን ሁለተኛ ልጃቸው የግብርና ኤክስቴንሽን ሰራተኛ ናት ሶስተኛ ልጃቸው ዛሬ ከእርሳቸው ጋር በጎንደር ዩንቨርስቲ ሀገር አቀፍ ፈተናውን እየወሰደ ነው ፤ አራተኛና አምስተኛ ልጆቻቸው ተማሪዎች ናቸው።
" ህልም ለማሳካት ቆራጥ መሆን ያስፈልጋል " የሚሉት አቶ ግዛው ፈተናውን ለመውሰድ በቂ ቅድመ ዝግጅት ማድረጋቸውን እና ከልጃቸው ጋር እስከ እኩለ ሌሊት አብረው ሲያጠኑና ሲረዳዱ መክረማቸውን ተናገረዋል።
ለዩንቨርስቲ መግቢያ የሚያበቃ ውጤት ለማምጣት መዘጋጀታቸውን ውጤቱ ቢመጣም ዩኒቨርሲቲ ለመግባት መዘጋጀታቸውን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልፀዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
ባሕር ዳር
#TikvahEthiopiaFamilyBahirdar
@tikvahethiopia
❤1.68K👏377😭53🤔34🙏34🥰19🕊17😡15😢12💔3
#AddisAbaba
" በዘንድሮ የግብር ማሳወቂያ እና መክፈያ ወቅት በገቢዎች ቢሮ 256 ቢሊየን ብር ለመሰብሰብ ታቅዷል " - ገቢዎች ቢሮ
ከሐምሌ 1/2017 ዓ/ም ጀምሮ እስከ ጥቅምት 30/2018 ዓ/ም ድረስ የ2017 ዓ/ም የግብር ማሳወቂያ ወቅት ነው።
በዛሬው ዕለት የደረጃ "ሐ" ግብር ከፋይ ደንበኞች ግብራቸውን ማሳወቅ የጀመሩ ሲሆን እስከ ሐምሌ 30/2017 ዓም ድረስ ግብር ግብራቸውን እያሳወቁ ይቆያሉ።
ከዚህ ቀደም ከነበረው አሰራር ለየት ባለ መልኩ በየደረጃው ያሉ ግብር ከፋዮች በወጣላቸው መርሃ ግብር መሰረት ግብራቸውን እንዲከፍሉ እንደሚደረግ የቢሮው የኮምዩኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ ሰውነት አየለ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።
አቶ ሰውነት " ከዚህ ቀደም የደረጃ 'ለ' ግብር ከፋዮች ከሃምሌ 1 እስከ ጳጉሜ 5 ነበር የሚከፍሉት ዘንድሮ ይህ አሰራር ተቀይሮ ሃምሌን ለዝግጅት እንዲጠቀሙት እና ግብራቸውን ከ ነሐሴ 1 እስከ ጳጉሜ 5 ድረስ እንዲከፍሉ ተወስኗል አከፋፈላቸውም በስም ቅደም ተከተል ይሆናል " ብለዋል።
ዳይሬክተሩ በስም ቅደም ተከተል እንዲከፍሉ መደረጉ ግብር ከፋዩ ላይ መጨናነቆች እንዳይኖሩ እና ለብልሹ አሰራሮች እንዳይዳረጉ ያግዛል ነው ያሉት።
አቶ ሰውነት አየለ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በዝርዝር በሰጡት ሃሳብ ምን አሉ ?
" የደረጃ 'ለ' ግብር ከፋይ ደንበኞች በነሐሴ ወር የመጀመሪያው ሳምንት ላይ የስም ዝርዝራቸው ከ A-D ያሉ ግብር ከፋዮች የሚስተናገዱበት ፕሮግራም ወጥቷል፣ በዚህም መሰረት ግብር ከፋዩን በአራት ሳምንት በመከፋፈል አመታዊ ግብራቸውን እንዲያሳውቁ እና እንዲከፍሉ ይደረጋል።
የደረጃ 'ሀ' ግብር ከፋዮችን በሚመለከትም ከዚህ ቀደም ከሐምሌ 1 እስከ ጥቅምት 30 የአመታዊ ግብራቸውን የመክፈያ እና የማሳወቂያ ጊዜያቸው ነበር።
እነዚህ ግብር ከፋዮችም ሐምሌ እና ነሃሴን ለዝግጅት ተጠቅመው መስከረም እና ጥቅምትን ግብራቸውን የሚከፍሉበት ፕሮግራም ወጥቷል።
ቢሮው በተለያዩ ጊዜያት ከንግዱ ማህበረሰብ ጋር ባደረጋቸው ውይይቶች ወቅት የተነሱ የተለያዩ ችግሮች ነበሩ እነዚህን የተጠቀሱ ችግሮችን ለመቅረፍ የሚያስችሉ በጥናት የተለዩ 24 አይነት አዳዲስ አሰራሮችን ዘርግተናል ከዛሬ ጀምሮ ተግባራዊ ይደረጋል።
ለምሳሌ የኦዲት ጥራት ጋር ላይ ከአሰራር ጋር በተያያዘ ባሉ ክፍተቶች ምክንያት ሁለት ኦዲተሮች አንድ አይነት ፋይል ተመልክተው ውሳኔ ሲወስኑ ግን ሁለት አይነት ውሳኔ የሚወስኑበት አሰራር ነበር ይህንን ለማስቀረት የሚያስችል የአሰራር ስርአት ተዘርግቷል።
ከሂሳብ መዝገብ ጋር በተገናኘም የሂሳም መዝገብ መያዝ ያለባቸው ግብር ከፋዮች መዝገቡን ባለመያዛቸው በቁርጥ ግብር ሲስተናገዱ ነበር።
አፈጻጸም ላይ በነበረ ክፍተት ምክንያት በተለይም የደረጃ 'ሀ' እና 'ለ' ግብር ከፋዮች ያለ ሂሳብ መዝገብ ሲስተናገዱ የቆዩ ቢሆንም ከአሁኑ የ2017 ዓ/ም የግብር ማሳወቂያ ወቅት ጀምሮ ያለ ሂሳብ መዝገብ አይሰራም።
ሂሳብ መዝገብ ሳይዙ የሚመጡ ከሆነ ግን የሚወሰነው ውሳኔ አስተማሪ የሚሆን ይሆናል።
የግብር አሰባሰብ ስርአቱም ከእጅ ንክኪ በጸዳ መንገድ እንዲሆን በማሰብ የደረጃ 'ሐ' ግብር ከፋዮች በET-TAX በተሰኘ በተቋሙ በለማ መተግበሪያ እቤታቸው ተቀምጠው ግብራቸውን የሚያውቁበት እና የሚከፍሉበት ሁኔታ ተፈጥሯል።
በSMS በሚደርሳቸው መረጃም በTelebirr እና CBE Birr ግብራቸውን መክፈል ይችላሉ።
የደረጃ 'ሀ' እና የደረጃ 'ለ' ግብር ከፋዮችም በተመሳሳይ E-TAX በተሰኘ መተግበሪያ እንዲከፍሉ እያደረግን ያለንበት ሁኔታ አለ ነገር ግን ሁሉም ወደዚህ አሰራር ስርአት ገና አልገቡም።
ከፍተኛ ግብር ከፋዮች 100 ፕርሰንት ወደዚህ አሰራር ስርአት ገብተዋል ቀሪዎቹ በየቅርንጫፉ እቅድ ተይዞ አብዛኛው ግብር ከፋይ ወደዚህ አሰራር እንዲገባ እየተሰራ ነው።
የኦዲት ጥራትን የሚያረጋግጥ የስራ ክፍል ተደራጅቷል ኦዲተሩ የወሰነው ውሳኔ ምን ያህል ጥራት አለው የሚለውን ያረጋግጣል ከፍተኛ ልዩነት ከተፈጠረም ግብር ከፋዩ እንዲከፈል ይደረጋል፣ ይህንን የወሰነው አካልም ተጠያቂ ይሆናል።
የግብር ከፋዩን ሂሳብ መዝግብ የሚያዘጋጁ ባለሞያዎች በሚመለከት ከዚህ ቀደም ከግብር ከፋዩ ጋር በመደራደር ከፍተኛ የሆነ ግብር የመሰወር ስራ የሚሰሩበት እና የተሳሳቱ ሰነዶችን የሚያቀርቡበት ሁኔታ ነበር።
በዚህ ጊዜ ግብር ከፋዩን ኦዲት አድርገን ገንዘቡን ብናስከፍልም የሂሳብ ባለሞያዎቹ ተጠያቂ የምናደርግበት አሰራር አልነበረም አሁን የሂሳብ ባለሞያዎቹም ተጠያቂ የሚሆኑበትን አሰራር ዘርግተናል።
ኦንላይን ግብይትንም ለመቆጣጠር እና ግብር እንዲከፍሉ ለማድረግ የሚቻልበት የአሰራር ስረዓት ለመዘርጋት እየተሰራ ነው።
ከማዕከል ሁሉንም ቅርንጫፎች ለመቆጣጠር የሚያስችል ካሜራ አስገጥመናል።
በዘንድሮ የግብር ማሳወቂያ እና መክፈያ ወቅት በገቢዎች ቢሮ 256 ቢሊየን ብር ለመሰብሰብ ታቅዷል " ብለዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAddisAbaba
@tikvahethiopia
" በዘንድሮ የግብር ማሳወቂያ እና መክፈያ ወቅት በገቢዎች ቢሮ 256 ቢሊየን ብር ለመሰብሰብ ታቅዷል " - ገቢዎች ቢሮ
ከሐምሌ 1/2017 ዓ/ም ጀምሮ እስከ ጥቅምት 30/2018 ዓ/ም ድረስ የ2017 ዓ/ም የግብር ማሳወቂያ ወቅት ነው።
በዛሬው ዕለት የደረጃ "ሐ" ግብር ከፋይ ደንበኞች ግብራቸውን ማሳወቅ የጀመሩ ሲሆን እስከ ሐምሌ 30/2017 ዓም ድረስ ግብር ግብራቸውን እያሳወቁ ይቆያሉ።
ከዚህ ቀደም ከነበረው አሰራር ለየት ባለ መልኩ በየደረጃው ያሉ ግብር ከፋዮች በወጣላቸው መርሃ ግብር መሰረት ግብራቸውን እንዲከፍሉ እንደሚደረግ የቢሮው የኮምዩኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ ሰውነት አየለ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።
አቶ ሰውነት " ከዚህ ቀደም የደረጃ 'ለ' ግብር ከፋዮች ከሃምሌ 1 እስከ ጳጉሜ 5 ነበር የሚከፍሉት ዘንድሮ ይህ አሰራር ተቀይሮ ሃምሌን ለዝግጅት እንዲጠቀሙት እና ግብራቸውን ከ ነሐሴ 1 እስከ ጳጉሜ 5 ድረስ እንዲከፍሉ ተወስኗል አከፋፈላቸውም በስም ቅደም ተከተል ይሆናል " ብለዋል።
ዳይሬክተሩ በስም ቅደም ተከተል እንዲከፍሉ መደረጉ ግብር ከፋዩ ላይ መጨናነቆች እንዳይኖሩ እና ለብልሹ አሰራሮች እንዳይዳረጉ ያግዛል ነው ያሉት።
አቶ ሰውነት አየለ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በዝርዝር በሰጡት ሃሳብ ምን አሉ ?
" የደረጃ 'ለ' ግብር ከፋይ ደንበኞች በነሐሴ ወር የመጀመሪያው ሳምንት ላይ የስም ዝርዝራቸው ከ A-D ያሉ ግብር ከፋዮች የሚስተናገዱበት ፕሮግራም ወጥቷል፣ በዚህም መሰረት ግብር ከፋዩን በአራት ሳምንት በመከፋፈል አመታዊ ግብራቸውን እንዲያሳውቁ እና እንዲከፍሉ ይደረጋል።
የደረጃ 'ሀ' ግብር ከፋዮችን በሚመለከትም ከዚህ ቀደም ከሐምሌ 1 እስከ ጥቅምት 30 የአመታዊ ግብራቸውን የመክፈያ እና የማሳወቂያ ጊዜያቸው ነበር።
እነዚህ ግብር ከፋዮችም ሐምሌ እና ነሃሴን ለዝግጅት ተጠቅመው መስከረም እና ጥቅምትን ግብራቸውን የሚከፍሉበት ፕሮግራም ወጥቷል።
ቢሮው በተለያዩ ጊዜያት ከንግዱ ማህበረሰብ ጋር ባደረጋቸው ውይይቶች ወቅት የተነሱ የተለያዩ ችግሮች ነበሩ እነዚህን የተጠቀሱ ችግሮችን ለመቅረፍ የሚያስችሉ በጥናት የተለዩ 24 አይነት አዳዲስ አሰራሮችን ዘርግተናል ከዛሬ ጀምሮ ተግባራዊ ይደረጋል።
ለምሳሌ የኦዲት ጥራት ጋር ላይ ከአሰራር ጋር በተያያዘ ባሉ ክፍተቶች ምክንያት ሁለት ኦዲተሮች አንድ አይነት ፋይል ተመልክተው ውሳኔ ሲወስኑ ግን ሁለት አይነት ውሳኔ የሚወስኑበት አሰራር ነበር ይህንን ለማስቀረት የሚያስችል የአሰራር ስርአት ተዘርግቷል።
ከሂሳብ መዝገብ ጋር በተገናኘም የሂሳም መዝገብ መያዝ ያለባቸው ግብር ከፋዮች መዝገቡን ባለመያዛቸው በቁርጥ ግብር ሲስተናገዱ ነበር።
አፈጻጸም ላይ በነበረ ክፍተት ምክንያት በተለይም የደረጃ 'ሀ' እና 'ለ' ግብር ከፋዮች ያለ ሂሳብ መዝገብ ሲስተናገዱ የቆዩ ቢሆንም ከአሁኑ የ2017 ዓ/ም የግብር ማሳወቂያ ወቅት ጀምሮ ያለ ሂሳብ መዝገብ አይሰራም።
ሂሳብ መዝገብ ሳይዙ የሚመጡ ከሆነ ግን የሚወሰነው ውሳኔ አስተማሪ የሚሆን ይሆናል።
የግብር አሰባሰብ ስርአቱም ከእጅ ንክኪ በጸዳ መንገድ እንዲሆን በማሰብ የደረጃ 'ሐ' ግብር ከፋዮች በET-TAX በተሰኘ በተቋሙ በለማ መተግበሪያ እቤታቸው ተቀምጠው ግብራቸውን የሚያውቁበት እና የሚከፍሉበት ሁኔታ ተፈጥሯል።
በSMS በሚደርሳቸው መረጃም በTelebirr እና CBE Birr ግብራቸውን መክፈል ይችላሉ።
የደረጃ 'ሀ' እና የደረጃ 'ለ' ግብር ከፋዮችም በተመሳሳይ E-TAX በተሰኘ መተግበሪያ እንዲከፍሉ እያደረግን ያለንበት ሁኔታ አለ ነገር ግን ሁሉም ወደዚህ አሰራር ስርአት ገና አልገቡም።
ከፍተኛ ግብር ከፋዮች 100 ፕርሰንት ወደዚህ አሰራር ስርአት ገብተዋል ቀሪዎቹ በየቅርንጫፉ እቅድ ተይዞ አብዛኛው ግብር ከፋይ ወደዚህ አሰራር እንዲገባ እየተሰራ ነው።
የኦዲት ጥራትን የሚያረጋግጥ የስራ ክፍል ተደራጅቷል ኦዲተሩ የወሰነው ውሳኔ ምን ያህል ጥራት አለው የሚለውን ያረጋግጣል ከፍተኛ ልዩነት ከተፈጠረም ግብር ከፋዩ እንዲከፈል ይደረጋል፣ ይህንን የወሰነው አካልም ተጠያቂ ይሆናል።
የግብር ከፋዩን ሂሳብ መዝግብ የሚያዘጋጁ ባለሞያዎች በሚመለከት ከዚህ ቀደም ከግብር ከፋዩ ጋር በመደራደር ከፍተኛ የሆነ ግብር የመሰወር ስራ የሚሰሩበት እና የተሳሳቱ ሰነዶችን የሚያቀርቡበት ሁኔታ ነበር።
በዚህ ጊዜ ግብር ከፋዩን ኦዲት አድርገን ገንዘቡን ብናስከፍልም የሂሳብ ባለሞያዎቹ ተጠያቂ የምናደርግበት አሰራር አልነበረም አሁን የሂሳብ ባለሞያዎቹም ተጠያቂ የሚሆኑበትን አሰራር ዘርግተናል።
ኦንላይን ግብይትንም ለመቆጣጠር እና ግብር እንዲከፍሉ ለማድረግ የሚቻልበት የአሰራር ስረዓት ለመዘርጋት እየተሰራ ነው።
ከማዕከል ሁሉንም ቅርንጫፎች ለመቆጣጠር የሚያስችል ካሜራ አስገጥመናል።
በዘንድሮ የግብር ማሳወቂያ እና መክፈያ ወቅት በገቢዎች ቢሮ 256 ቢሊየን ብር ለመሰብሰብ ታቅዷል " ብለዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAddisAbaba
@tikvahethiopia
❤936😡472😭86😱42🤔22🙏22🕊20😢10👏8💔7🥰6
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#AddisAbaba
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ቢሮ የ2017 ዓ/ም የግብር ዘመን ግብር አወሳሰንና አሰባሰብ አሰራር ይፋ አድርጓል።
አዲሱ መመሪያ የሂሳብ መዝገብና የሂሳብ መግለጫ መሰረት በማድረግ የማሳወቅ፣ የመክፈል እና ሰነዶችን የመያዝ ግዴታ ተፈጻሚ የማይደረግባቸው ግብር ከፋዮችን በሚመለከት።
እንዲሁም የሂሳብ መዝገብና የሂሳብ መግለጫ መሰረት በማድረግ የማሳወቅ፣ የመከፈል እና ሰነዶችን የመያዝ ግዴታን ያልተወጡ ግብር ከፋዮችን በተመለከተ መደረግ ስላለበት ዝርዝር ሃሳብ የያዘ ደብዳቤ በቢሮው የታክስ ጉዳዮች ዘርፍ ምክትል ቢሮ ሃላፊ ወ/ሮ ወርቅነሽ ሰቦቃ ተፈርሞ ለሁሉም ለግብር ከፋዮች ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ተልኳል።
ደብዳቤው "የተወሰኑ ግብር ከፋዬች በህጉ የተጣለባቸውን ግዴታ ለመወጣት የተሰማሩበትን የስራ ዘርፍ ባለው የተለየ ባህሪ ምክንያት መቸገራቸውን በተለያየ ጊዜ በመጥቀስ አቤቱታ ያቀረቡ" መሆኑን ገልጿል።
ይሁን እንጂ የግብር ሕጉ ለየትኛውም የንግድ ዘርፍ በተለየ መልኩ የሂሳብ መዝገብና የሂሳብ መግለጫ መሰረት በማድረግ የማሳወቅ የመከፈል እና ሰነዶችን የመያዝ ግዴታን ቀሪ አለማድረጉንም አሳውቋል።
ይህንኑ ግዴታ አለመወጣትም አስተዳደራዊ ቅጣት የሚያስከትል መሆኑ እንደተጠበቀ ሆኖ የተለየ ባህሪ ያላቸው የተወሰኑ የሥራ ዘርፎች የግብር ህጉን ድንጋጌዎች በአስከበረ አግባብ የገቢ አሰበሰቡን እና የአገልግሎት አሰጣቱን ፍታሀዊነት ማዕከል ያደረገ የአሰራር ሥርዓት ለ2017 የግብር ማሳወቂያ ጊዜ ሂሳብ መዝገብ የማቅረብ ግዴታን ተፈጻሚነት በቅጣት ብቻ በማለፍ ማዘግየት አስፈላጊ መሆኑ ታምኖበታል ብሏል።
ስለሆነም የደረጃ "ሀ" እና የደረጃ "ለ" ግብር ከፋዬች የሂሳብ መዝገብና የሂሳብ መግለጫ መሰረት በማድረግ የማሳወቅ፣ የመከፈል እና ሰነዶችን የመያዝ ግዴታን ከዚህ በታች የተዘረዘሩ ግብር ከፋዬች በማይወጡበት ጊዜ ለደረጃ «ሐ» ግብር ከፋዬች የወጣውን ገቢ ግብር ደንብ ቁጥር 410/2009 የትርፍ ሕዳግ እና በግምት ግብር አወሳሰን መመሪያ ቁጥር 138/2010 በቁርጥ የወጪ ሰንጠረዥ መጠቀም ዘርፉ ግዴታውን በገቢ ግብር ሕጉ መሰረት እንዳይወጣ ከተማውም ማግኘት የሚገባውን ገቢ እንዳይሰበስብ ምክንያት ስለሚሆን ይህንኑ ክፍተት ለመዝጋት በገቢ ግብር አዋጁ ቁጥር 979/2008 አንቀጽ 80 መሰረት ግብር በግምት በሚሰላበት ጊዜ፦
ከግብር ከፋዮች ግንዛቤ የተለየ ድጋፍ የሚፈልጉ እና ሥራቸውም ከመንግስት ጋር በተገባ ውል ብቻ የሚያከናውኑ በማህበር የተደራጁ :-
- የትምህርት ቤቶችና የምገባ ማዕከላት መጋቢ እናቶች
- በከተማ ጽዳትና ውበት ደረቅ ቆሻሻ እና ገጸ-ምድር ማስዋብ ላይ የተሰማሩ
- ከንግድ ቢሮ ትስስር የተፈጠረላቸው የሸገር ዳቦን የሚሸጡ ማህበራት
ከመንግስት ተቋማት ጋር ያላቸውን ውልና በበጀት ዓመቱ ከአሰራቸው የመንግስት ተቋም ዓመቱን ሙሉ የተከፈላቸውን ክፍያ የሚገልጽ መረጃ ሲያመጡ መረጃን መሰረት አድርጎ በሠንጠረዥ "ሐ" መሠረት ግብሩን በማስላት ገቢው ተወስኖ እንዲሰበሰብ።
በተጨማሪም የሸገር ዳቦን የሚሸጡ በተጓዳኝ የሚከናውኑ የንግድ ስራዎች መኖራቸው በመስክ ምልከታ ተረጋግጦ በየዘርፉ የቀን ገቢ ግምት እንዲገመትላቸው ተደርጎ ግብሩ ተወስኖ እንዲሰበሰብ።
የንግድ ሥራ ፍቃድ ሳይኖራቸው በሞያ ፍቃድ ብቻ አገልግሎት የሚሰጡ ጠበቆች ፣የኢንሹራንስ ወኪሎች ፣ኢንሹራንስ ጉዳት ገማች ግለሰቦች በሚመለከት:-
➡️ ከግብር አመቱ አጠቃላይ እንደ ገቢ 35 በመቶ እንደ ወጪ 65 በመቶ ግብር የሚከፈልበት ገቢ ሆኖ በሠንጠረዥ "ሐ" መሠረት ግብሩን በማስላት ተወስኖ ገቢው እንዲሰበሰብ።
➡️ የንግድ ሥራ ያልሆነ ገቢ ያላቸው የመኖሪያ ቤት አከራዮች ከግብር አመቱ አጠቃላይ ገቢ 35 በመቶ እንደ ወጪ 65 በመቶ ግብር የሚከፈልበት ገቢ ሆኖ በሠንጠረዥ "ሐ" መሠረት ግብሩን በማስላት ተወስኖ ገቢው እንዲሰበሰብ።
➡️ በግል ኮድ 02 እና በንግድ ኮድ 03 ተሸከርካሪ የኪራይ አገልግሎት የሚሰጡ አጠቃላይ የኪራይ ገቢ ላይ በሠንጠረዥ "ሐ" መሠረት በመረጃ የሚወሰን በመሆኑ ግብሩን በማስላት ተወስኖ ገቢው እንዲሰበሰብ።
➡️ በህግ ደረሰኝ የመጠቀም ግዴታ ተፈጻሚ የማይደረግባቸው የከተማ ውስጥ የትራንስፖርት አገልግሎት ሰጭዎች /በቴክኖሎጂ ስምሪት የሚሰጣቸውን የሜትር ታከሲዎች ጨምሮ/ የገቢ ግብር ደንብ ቁጥር 410/2009 ሠንጠረዥ "ሐ" መሠረት ግብሩን በማስላት ተወስኖ ገቢው እንዲሰበሰብ መወሰኑን ይገልጻል።
(ተጨማሪውን ከተያያዘው ደብዳቤ ይመልከቱ)
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAddisAbaba
@tikvahethiopia
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ቢሮ የ2017 ዓ/ም የግብር ዘመን ግብር አወሳሰንና አሰባሰብ አሰራር ይፋ አድርጓል።
አዲሱ መመሪያ የሂሳብ መዝገብና የሂሳብ መግለጫ መሰረት በማድረግ የማሳወቅ፣ የመክፈል እና ሰነዶችን የመያዝ ግዴታ ተፈጻሚ የማይደረግባቸው ግብር ከፋዮችን በሚመለከት።
እንዲሁም የሂሳብ መዝገብና የሂሳብ መግለጫ መሰረት በማድረግ የማሳወቅ፣ የመከፈል እና ሰነዶችን የመያዝ ግዴታን ያልተወጡ ግብር ከፋዮችን በተመለከተ መደረግ ስላለበት ዝርዝር ሃሳብ የያዘ ደብዳቤ በቢሮው የታክስ ጉዳዮች ዘርፍ ምክትል ቢሮ ሃላፊ ወ/ሮ ወርቅነሽ ሰቦቃ ተፈርሞ ለሁሉም ለግብር ከፋዮች ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ተልኳል።
ደብዳቤው "የተወሰኑ ግብር ከፋዬች በህጉ የተጣለባቸውን ግዴታ ለመወጣት የተሰማሩበትን የስራ ዘርፍ ባለው የተለየ ባህሪ ምክንያት መቸገራቸውን በተለያየ ጊዜ በመጥቀስ አቤቱታ ያቀረቡ" መሆኑን ገልጿል።
ይሁን እንጂ የግብር ሕጉ ለየትኛውም የንግድ ዘርፍ በተለየ መልኩ የሂሳብ መዝገብና የሂሳብ መግለጫ መሰረት በማድረግ የማሳወቅ የመከፈል እና ሰነዶችን የመያዝ ግዴታን ቀሪ አለማድረጉንም አሳውቋል።
ይህንኑ ግዴታ አለመወጣትም አስተዳደራዊ ቅጣት የሚያስከትል መሆኑ እንደተጠበቀ ሆኖ የተለየ ባህሪ ያላቸው የተወሰኑ የሥራ ዘርፎች የግብር ህጉን ድንጋጌዎች በአስከበረ አግባብ የገቢ አሰበሰቡን እና የአገልግሎት አሰጣቱን ፍታሀዊነት ማዕከል ያደረገ የአሰራር ሥርዓት ለ2017 የግብር ማሳወቂያ ጊዜ ሂሳብ መዝገብ የማቅረብ ግዴታን ተፈጻሚነት በቅጣት ብቻ በማለፍ ማዘግየት አስፈላጊ መሆኑ ታምኖበታል ብሏል።
ስለሆነም የደረጃ "ሀ" እና የደረጃ "ለ" ግብር ከፋዬች የሂሳብ መዝገብና የሂሳብ መግለጫ መሰረት በማድረግ የማሳወቅ፣ የመከፈል እና ሰነዶችን የመያዝ ግዴታን ከዚህ በታች የተዘረዘሩ ግብር ከፋዬች በማይወጡበት ጊዜ ለደረጃ «ሐ» ግብር ከፋዬች የወጣውን ገቢ ግብር ደንብ ቁጥር 410/2009 የትርፍ ሕዳግ እና በግምት ግብር አወሳሰን መመሪያ ቁጥር 138/2010 በቁርጥ የወጪ ሰንጠረዥ መጠቀም ዘርፉ ግዴታውን በገቢ ግብር ሕጉ መሰረት እንዳይወጣ ከተማውም ማግኘት የሚገባውን ገቢ እንዳይሰበስብ ምክንያት ስለሚሆን ይህንኑ ክፍተት ለመዝጋት በገቢ ግብር አዋጁ ቁጥር 979/2008 አንቀጽ 80 መሰረት ግብር በግምት በሚሰላበት ጊዜ፦
ከግብር ከፋዮች ግንዛቤ የተለየ ድጋፍ የሚፈልጉ እና ሥራቸውም ከመንግስት ጋር በተገባ ውል ብቻ የሚያከናውኑ በማህበር የተደራጁ :-
- የትምህርት ቤቶችና የምገባ ማዕከላት መጋቢ እናቶች
- በከተማ ጽዳትና ውበት ደረቅ ቆሻሻ እና ገጸ-ምድር ማስዋብ ላይ የተሰማሩ
- ከንግድ ቢሮ ትስስር የተፈጠረላቸው የሸገር ዳቦን የሚሸጡ ማህበራት
ከመንግስት ተቋማት ጋር ያላቸውን ውልና በበጀት ዓመቱ ከአሰራቸው የመንግስት ተቋም ዓመቱን ሙሉ የተከፈላቸውን ክፍያ የሚገልጽ መረጃ ሲያመጡ መረጃን መሰረት አድርጎ በሠንጠረዥ "ሐ" መሠረት ግብሩን በማስላት ገቢው ተወስኖ እንዲሰበሰብ።
በተጨማሪም የሸገር ዳቦን የሚሸጡ በተጓዳኝ የሚከናውኑ የንግድ ስራዎች መኖራቸው በመስክ ምልከታ ተረጋግጦ በየዘርፉ የቀን ገቢ ግምት እንዲገመትላቸው ተደርጎ ግብሩ ተወስኖ እንዲሰበሰብ።
የንግድ ሥራ ፍቃድ ሳይኖራቸው በሞያ ፍቃድ ብቻ አገልግሎት የሚሰጡ ጠበቆች ፣የኢንሹራንስ ወኪሎች ፣ኢንሹራንስ ጉዳት ገማች ግለሰቦች በሚመለከት:-
➡️ ከግብር አመቱ አጠቃላይ እንደ ገቢ 35 በመቶ እንደ ወጪ 65 በመቶ ግብር የሚከፈልበት ገቢ ሆኖ በሠንጠረዥ "ሐ" መሠረት ግብሩን በማስላት ተወስኖ ገቢው እንዲሰበሰብ።
➡️ የንግድ ሥራ ያልሆነ ገቢ ያላቸው የመኖሪያ ቤት አከራዮች ከግብር አመቱ አጠቃላይ ገቢ 35 በመቶ እንደ ወጪ 65 በመቶ ግብር የሚከፈልበት ገቢ ሆኖ በሠንጠረዥ "ሐ" መሠረት ግብሩን በማስላት ተወስኖ ገቢው እንዲሰበሰብ።
➡️ በግል ኮድ 02 እና በንግድ ኮድ 03 ተሸከርካሪ የኪራይ አገልግሎት የሚሰጡ አጠቃላይ የኪራይ ገቢ ላይ በሠንጠረዥ "ሐ" መሠረት በመረጃ የሚወሰን በመሆኑ ግብሩን በማስላት ተወስኖ ገቢው እንዲሰበሰብ።
➡️ በህግ ደረሰኝ የመጠቀም ግዴታ ተፈጻሚ የማይደረግባቸው የከተማ ውስጥ የትራንስፖርት አገልግሎት ሰጭዎች /በቴክኖሎጂ ስምሪት የሚሰጣቸውን የሜትር ታከሲዎች ጨምሮ/ የገቢ ግብር ደንብ ቁጥር 410/2009 ሠንጠረዥ "ሐ" መሠረት ግብሩን በማስላት ተወስኖ ገቢው እንዲሰበሰብ መወሰኑን ይገልጻል።
(ተጨማሪውን ከተያያዘው ደብዳቤ ይመልከቱ)
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAddisAbaba
@tikvahethiopia
1❤1.3K😡175🤔35🙏35🥰25🕊23😭22😢21😱18👏13
#AAiT
Announcement of Professional Training Programs
Python Programming + Data Analytics and Visualization
By: Addis Ababa University,
College of Technology and Built Environment,
School of Electrical & Computer Engineering
Registration Deadline: July 24, 2025
Training Starts on: July 26, 2025
Online Registration Link: https://forms.gle/M1DPS1zFP4K9QT4V6
Telephone: +251-913-574525/ +251-940-182870
Email: [email protected]
For more information: https://forms.gle/M1DPS1zFP4K9QT4V6
Telegram Channel: https://www.tg-me.com/TrainingAAiT
Announcement of Professional Training Programs
Python Programming + Data Analytics and Visualization
By: Addis Ababa University,
College of Technology and Built Environment,
School of Electrical & Computer Engineering
Registration Deadline: July 24, 2025
Training Starts on: July 26, 2025
Online Registration Link: https://forms.gle/M1DPS1zFP4K9QT4V6
Telephone: +251-913-574525/ +251-940-182870
Email: [email protected]
For more information: https://forms.gle/M1DPS1zFP4K9QT4V6
Telegram Channel: https://www.tg-me.com/TrainingAAiT
❤158🙏7🤔5👏2🕊2
#Axum
የአክሱም ከተማ ፖሊስ በከተማው ክንደያ በተባለ ቀበሌ ሁለት ተጠርጣሪዎች አደገኛ ኬሚካል በመጠቀም የወርቅ ማጣራት ተግባር ሲያከናውኑ በቁጥጥር ስር እንዳዋላቸው አሳውቋል።
ፖሊስ ከህብረተሰብ በደረሰው ጥቆማ የፍ/ቤት የፍተሻ ትእዛዝ በመያዝ የተለያዩ የፍትህ አካላት ፣ የአገር ሽማግሌዎችና የጤና ባለሙያዎች በማሳተፍ ነው ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ስር ያዋላቸው፡፡
የከተማዋ አቃቤ ህግ የህበረተሰብ የጤና ጠንቅ የሆነውን አደገኛ ኬሚካል በመጠቀም ህገወጥ ተግባር ሲፈፅሙ የተገኙት ተጠርጣሪዎቹ በአጭር ጊዜ አስተማሪ ቅጣት እንዲያገኙ ከባለ ድርሻ አካላት በመሆን ይሰራል ብሏል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
መቐለ
Photo credit - Tigrai Television
@tikvahethiopia
የአክሱም ከተማ ፖሊስ በከተማው ክንደያ በተባለ ቀበሌ ሁለት ተጠርጣሪዎች አደገኛ ኬሚካል በመጠቀም የወርቅ ማጣራት ተግባር ሲያከናውኑ በቁጥጥር ስር እንዳዋላቸው አሳውቋል።
ፖሊስ ከህብረተሰብ በደረሰው ጥቆማ የፍ/ቤት የፍተሻ ትእዛዝ በመያዝ የተለያዩ የፍትህ አካላት ፣ የአገር ሽማግሌዎችና የጤና ባለሙያዎች በማሳተፍ ነው ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ስር ያዋላቸው፡፡
የከተማዋ አቃቤ ህግ የህበረተሰብ የጤና ጠንቅ የሆነውን አደገኛ ኬሚካል በመጠቀም ህገወጥ ተግባር ሲፈፅሙ የተገኙት ተጠርጣሪዎቹ በአጭር ጊዜ አስተማሪ ቅጣት እንዲያገኙ ከባለ ድርሻ አካላት በመሆን ይሰራል ብሏል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
መቐለ
Photo credit - Tigrai Television
@tikvahethiopia
❤384👏46🤔18🙏11😡11🕊6😭6
TIKVAH-ETHIOPIA
የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት " ስጋት ላይ ጥሎናል " ያሉት አዲስ መመሪያ ምን ይዟል ? የኢትዮጵያ ትምህርትና ስልጠና ባለስልጣን፣ የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማትን አሰራር ስርዓት ለማስያዝ በሚል ዳግም ምዝገባ በማካሔድ ላይ መሆኑን ከዚህ ቀደም በሰጣቸው መግለጫዎች አስታውቋል፡፡ በዚህ ሒደት 85 የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በአዲሱ መስፈርት መሰረት ዳግም ለመመዝገብ ፈቃደኛ ስላልሆኑ እንደሚዘጉም…
" መንግስት የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማትን የመዝጋትም ሆነ የማዳከም ፍላጎት የለውም " - የትምህርትና ስልጠና ባለስልጣን
የትምህርትና ስልጠና ባለስልጣን፣ በግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተዋናዮች በዳግመ ምዝገባው ዙርያ ላቀረቡት ቅሬታ ምላሽ ሰጥቷል፡፡
የባለስልጣን መስሪያ ቤቱ ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ ውብሸት ታደለ፣ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃለመጠይቅ፣ መንግስት ተቋማቱን የማጥፋት እቅድ አለው እየተባለ ለሚቀርበው ቅሬታ በሰጡት አስተያየት፣ " ይሔ አስተያየት ስህተት ነው፣ እነዚህን ተቋማት የማዳከም አላማ የለም " ብለዋል፡፡
" ይልቁንም መንግስት እነዚህን ተቋማት የማጠናከር አላማና ፍላጎት ነው ያለው፣ የዳግመ ምዝገባና ምዘና ሒደቱ ትኩረትም ይህን እውን ማድረግ ነው " ሲሉ ገልፀዋል፡፡
የዳግመ ምዝገባና ምልከታ ሒደቱ በአዲስ አበባ መጠናቀቁን ተናግረው፣ በቀጣይ የትኞቹ ተቋማት ይቀጥላሉ፣ የትኞቹ አይቀጥሉም የሚለውን ለመግለፅ ሪፖርት በመዘጋጀት ላይ መሆኑን አብራርተዋል፡፡
የአዲስ አበባው የዳግመ ምዝገባና ምዘና ስራ በመጠናቀቁ፣ በቅርቡ በክልሎች ይህንን ስራ ለመጀመር ቅድመ ዝግጅት እየተደረገ መሆኑንም አስታውቀዋል፡፡
ምክትል ዋና ዳይሬክተሩ አቶ ውብሸት ታደለ በዝርዝር ምን አሉ ?
" አሁን እየተከናወነ ባለው ዳግመ ምዝገባና ምዘነና ሒደት የተፈለገው፣ የትምህርት ተቋማቱ መሰረታዊ በሆነ መንገድ ራሳቸውን እንዲያድሱ ነው፡፡
ባለቤትነታቸው እንኳ የማይታወቅና አጠራጣሪ የሆኑ ተቋማት አሉ፡፡ እነዚህን ችግሮች የማጥራት ስራ ነው እየተሰራ ያነው፡፡መዝጋት የምትፈልገውን ተቋም ይህን ያህል ጊዜ ማቆየት አያስፈልግም፡፡ በፖሊሲ አቅጣጫ አስቀምጠህ ከገበያ እንዲወጡ ማድረግ ይቻላል፡፡ ግን እሱ አይደለም አላማችን፡፡
የእኛ አላማ፣ ትናንሽ ቢዝነሶች ሆነው የጀመሩት ተቋማት ወደ አንድ ተደራጅተውና ተጠናክረው እንዲመጡ ነው፡፡ ካልቻሉ ደግሞ ከገበያው መውጣት አለባቸው፡፡
ክቡር ሚኒስትሩ (ፕሮፌሰር ብረሀኑ ነጋ) ከዚህ በፊት የተናገሩት ነገርም (50 ተቋማት ይበቃሉ ማለታቸው ይታወሳል) ከዚህ የተለየ አይደለም፡፡ ጠንከር ጠንከር ያላችሁ ተቋማት ሁኑ፡፡ ጥቂት ተቋማት ይበቃሉ፡፡ ይህ ሁሉ ተቋም አለ ማለት፣ በከፍተኛ ትምህርት ዘርፍ የተለየ ለውጥ ይመጣል ማለት አይደለም ነው ያሉት፡፡ ጥራት ያለው ትምህርት የሚሰጥ ተቋም ያስፈልጋል ነው ያሉት፡፡ የእኛም አላማ ይኸው ነው፡፡
ከዚህ በፊት ወጣ የተባለው፣ ' አብዛኞቹ ተቋማት መስፈርቱን አያሟሉም ተብለዋል ' የተባለው ዘገባ ስህተት ነው፡፡ ሚድያዎችን ለመተባበር ብለን የሰጠናቸውን መረጃ አዛብተው ዘገቡት፡፡ ከዛም፣ ሁሉም የግል ትምህርት ተቋማት መስፈርቱን አያሟሉም ተባለ ተብሎ ተስተጋባ፡፡ ይህ ስህተት ነው፡፡
በወቅቱ ያልነው፣ አብዛኞቹ ተቋማት ለዳግመ ምዝገባ የሚሆን የተሟላ ሰነድ አላቀረቡም ነው፡፡ ሰነድ አስገቡ ስንላቻው ስለነበር ማለት ነው፡፡ ሰነድ አላሟሉም ማለትና ያስገቡትን ሰነድ ገምግሞ መስፈርቱን አላሟሉም ማለት የተለያዩ ነገሮች ናቸው፡፡
ቀደም ሲል ሒደቱ በጣም ቀላል ነበር ኮሌጅ ለመክፈት፣ ትንሽ ገንዘብ ካለህ አንድ ሁለት ክፍል ተከራይተህ መክፈት ነበር፡፡ በዚህ መሰሉ ሒደት መቀጠል አይቻልም አሁን፡፡ ይህን ቀላል አካሔድ የለመዱ ተቋማት መቀጠል አይችሉም፡፡ የተቀመጠውን መስፈርት አሟልተው በትንሹ ኮሌጅ የሚያስብል ስራ ሰርተው ነው ይህንን ቢዝነስ መጀመርና ማስኬድ ያለባቸው፡፡
አሁን በትምህርትና ስልጠና ባለስልጣን በተቀመጠው መስፈርት መሰረት እንደ ኮሌጅ መቀጠል እችላለሁ የሚሉት ተቋማት ናቸው የተመዘገቡት፡፡ ከተመዘገቡት መካከል ደግሞ፣ አሁን ግምገማ ተደርጎ፣ ሰነዶቻቸው ተፈትሸው፣ የመስክ ምልከታም ተደርጎ፣ በትክክል መስፈርቱን ያሟላሉ የሚባሉትን ውጤት እንገልፃለን፡፡
አሁን ባለው ሁኔታ የአዲስ አበባን ተቋማት ምዝገባና ምልከታ ሙሉ በሙሉ አጠናቀናል፡፡ ውጤቱን ለመግለፅ ሪፖርቱን በማዘጋጀት ላይ ነው ያለነው፡፡ ጎን ለጎን ደግሞ በክልሎች ይህንን ስራ ለመጀመር ቅድመ ዘግጅት እያደረግን ነው፡፡ ስራው በአዲሱ የበጀት አመት የሚጀመር ይሆናል፡፡
እስካሁን ከዘርፉ የወጡ ተቋማትን በተመለከተ የተለያየ አሀዝ ይቀርባል፡፡ ለምሳሌ መጀመሪያ ላይ 84 ተቋማት ሳይመዘገቡ ቀሩ፡፡ በኋላ ላይ ግን ዘግይተው የመጡ አሉ፡፡ ከነሱ ውስጥ በቂ ምክንያት ያቀረቡትን መዝግበን እየገመገምን ነው፡፡ በሌላ በኩል ደግሞ ተመዝግበው ከነበሩት ውስጥ ለመውጣት ሒደት ላይ ያሉ አሉ፣ ጎንለጎን ማለት ነው፡፡ ይህ የእነሱ ገባ ወጣ ማለት፣ ከዘርፉ የወጡ ተቋማት ብዛት በየጊዜው እንዲለያይ አድርጎታል፡፡ እንደዛም ሆኖ፣ አሁን የምዝገባና የግምገማ ሒደት ላይ ስለሆንን ትክክለኛ ቁጥሩን ማስቀመጥ ቢያስቸግርም ቢያንስ 80 የግል ትምህርት ተቋማት፣ ስራቸውን አቋርጠው ከዘርፉ ተሰናብተዋል፡፡
የዳግመ ምዝገባው መመሪያ ላይ በቂ ውይይት አልተደረገበትም፣ ከዘርፉ ተዋናዮች ግብአት አልተወሰደም የሚለውም ጉዳይ ትክክል አይደለም፡፡ ከተቋማቱ ባለቤቶች በሁለት መንገድ ግብአት ተቀብለናል፡፡ አንደኛው፣ ከውይይት መድረክ የተገኘው ሲሆን፣ ሁለተኛው ደግሞ በፅሑፍ የተቀበልነው ነው፡፡ በዚህ መንገድ በአዲስ አበባ በሀይሌ ግራንድ ሆቴል ከተደረገ ውይይትና በፅሑፍ ከቀረቡልን ሀሳቦች ግብአት ወስደናል፡፡አስፈላጊ የሆኑትንና ያስኬዳሉ የምንላቸውን ሀሳቦች በግብአትነት ተጠቅመንባቸዋል፡፡
ለምሳሌ ፦ ከእነሱ ተቀብለን ካካተትናቸው ሀሳቦች አንዱ፣ በመውጫ ፈተና ቢያንስ 25 በመቶ ያላሳለፈ ተቋም መቀጠል የለበትም የሚለው መስፈርት መቼ ተግባራዊ መሆን ይጀምር የሚለው ላይ የእነሱን ሀሳብ ተቀብለን የእፎይታ ጊዜ እንዲሰጥ አድርገናል፡፡
ይህ መስፈርት መተግበር የሚጀምረው፣ መመሪያው በወጣበት ጊዜ ትምህርት በጀመሩ ተማሪዎች ላይ እንጂ፣ በነባር ተማሪዎች ላይ መሆን የለበትም የሚለው ሀሳብ ከነሱ የመጣ ነው፡፡ ይህ ሀሳባቸው አሳማኝ በመሆኑ ተቀበልነው፡፡ አሁን ለትግበራው ሁለት አመት ገደማ አላቸው፡፡ በ 2019 ዓ.ም ገደማ ነው መተግበር የሚጀምረው ይህ መመሪያ፡፡ ሌሎችም የተቀበልናቸው ሀሳቦች አሉ፡ " ብለዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
የትምህርትና ስልጠና ባለስልጣን፣ በግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተዋናዮች በዳግመ ምዝገባው ዙርያ ላቀረቡት ቅሬታ ምላሽ ሰጥቷል፡፡
የባለስልጣን መስሪያ ቤቱ ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ ውብሸት ታደለ፣ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃለመጠይቅ፣ መንግስት ተቋማቱን የማጥፋት እቅድ አለው እየተባለ ለሚቀርበው ቅሬታ በሰጡት አስተያየት፣ " ይሔ አስተያየት ስህተት ነው፣ እነዚህን ተቋማት የማዳከም አላማ የለም " ብለዋል፡፡
" ይልቁንም መንግስት እነዚህን ተቋማት የማጠናከር አላማና ፍላጎት ነው ያለው፣ የዳግመ ምዝገባና ምዘና ሒደቱ ትኩረትም ይህን እውን ማድረግ ነው " ሲሉ ገልፀዋል፡፡
የዳግመ ምዝገባና ምልከታ ሒደቱ በአዲስ አበባ መጠናቀቁን ተናግረው፣ በቀጣይ የትኞቹ ተቋማት ይቀጥላሉ፣ የትኞቹ አይቀጥሉም የሚለውን ለመግለፅ ሪፖርት በመዘጋጀት ላይ መሆኑን አብራርተዋል፡፡
የአዲስ አበባው የዳግመ ምዝገባና ምዘና ስራ በመጠናቀቁ፣ በቅርቡ በክልሎች ይህንን ስራ ለመጀመር ቅድመ ዝግጅት እየተደረገ መሆኑንም አስታውቀዋል፡፡
ምክትል ዋና ዳይሬክተሩ አቶ ውብሸት ታደለ በዝርዝር ምን አሉ ?
" አሁን እየተከናወነ ባለው ዳግመ ምዝገባና ምዘነና ሒደት የተፈለገው፣ የትምህርት ተቋማቱ መሰረታዊ በሆነ መንገድ ራሳቸውን እንዲያድሱ ነው፡፡
ባለቤትነታቸው እንኳ የማይታወቅና አጠራጣሪ የሆኑ ተቋማት አሉ፡፡ እነዚህን ችግሮች የማጥራት ስራ ነው እየተሰራ ያነው፡፡መዝጋት የምትፈልገውን ተቋም ይህን ያህል ጊዜ ማቆየት አያስፈልግም፡፡ በፖሊሲ አቅጣጫ አስቀምጠህ ከገበያ እንዲወጡ ማድረግ ይቻላል፡፡ ግን እሱ አይደለም አላማችን፡፡
የእኛ አላማ፣ ትናንሽ ቢዝነሶች ሆነው የጀመሩት ተቋማት ወደ አንድ ተደራጅተውና ተጠናክረው እንዲመጡ ነው፡፡ ካልቻሉ ደግሞ ከገበያው መውጣት አለባቸው፡፡
ክቡር ሚኒስትሩ (ፕሮፌሰር ብረሀኑ ነጋ) ከዚህ በፊት የተናገሩት ነገርም (50 ተቋማት ይበቃሉ ማለታቸው ይታወሳል) ከዚህ የተለየ አይደለም፡፡ ጠንከር ጠንከር ያላችሁ ተቋማት ሁኑ፡፡ ጥቂት ተቋማት ይበቃሉ፡፡ ይህ ሁሉ ተቋም አለ ማለት፣ በከፍተኛ ትምህርት ዘርፍ የተለየ ለውጥ ይመጣል ማለት አይደለም ነው ያሉት፡፡ ጥራት ያለው ትምህርት የሚሰጥ ተቋም ያስፈልጋል ነው ያሉት፡፡ የእኛም አላማ ይኸው ነው፡፡
ከዚህ በፊት ወጣ የተባለው፣ ' አብዛኞቹ ተቋማት መስፈርቱን አያሟሉም ተብለዋል ' የተባለው ዘገባ ስህተት ነው፡፡ ሚድያዎችን ለመተባበር ብለን የሰጠናቸውን መረጃ አዛብተው ዘገቡት፡፡ ከዛም፣ ሁሉም የግል ትምህርት ተቋማት መስፈርቱን አያሟሉም ተባለ ተብሎ ተስተጋባ፡፡ ይህ ስህተት ነው፡፡
በወቅቱ ያልነው፣ አብዛኞቹ ተቋማት ለዳግመ ምዝገባ የሚሆን የተሟላ ሰነድ አላቀረቡም ነው፡፡ ሰነድ አስገቡ ስንላቻው ስለነበር ማለት ነው፡፡ ሰነድ አላሟሉም ማለትና ያስገቡትን ሰነድ ገምግሞ መስፈርቱን አላሟሉም ማለት የተለያዩ ነገሮች ናቸው፡፡
ቀደም ሲል ሒደቱ በጣም ቀላል ነበር ኮሌጅ ለመክፈት፣ ትንሽ ገንዘብ ካለህ አንድ ሁለት ክፍል ተከራይተህ መክፈት ነበር፡፡ በዚህ መሰሉ ሒደት መቀጠል አይቻልም አሁን፡፡ ይህን ቀላል አካሔድ የለመዱ ተቋማት መቀጠል አይችሉም፡፡ የተቀመጠውን መስፈርት አሟልተው በትንሹ ኮሌጅ የሚያስብል ስራ ሰርተው ነው ይህንን ቢዝነስ መጀመርና ማስኬድ ያለባቸው፡፡
አሁን በትምህርትና ስልጠና ባለስልጣን በተቀመጠው መስፈርት መሰረት እንደ ኮሌጅ መቀጠል እችላለሁ የሚሉት ተቋማት ናቸው የተመዘገቡት፡፡ ከተመዘገቡት መካከል ደግሞ፣ አሁን ግምገማ ተደርጎ፣ ሰነዶቻቸው ተፈትሸው፣ የመስክ ምልከታም ተደርጎ፣ በትክክል መስፈርቱን ያሟላሉ የሚባሉትን ውጤት እንገልፃለን፡፡
አሁን ባለው ሁኔታ የአዲስ አበባን ተቋማት ምዝገባና ምልከታ ሙሉ በሙሉ አጠናቀናል፡፡ ውጤቱን ለመግለፅ ሪፖርቱን በማዘጋጀት ላይ ነው ያለነው፡፡ ጎን ለጎን ደግሞ በክልሎች ይህንን ስራ ለመጀመር ቅድመ ዘግጅት እያደረግን ነው፡፡ ስራው በአዲሱ የበጀት አመት የሚጀመር ይሆናል፡፡
እስካሁን ከዘርፉ የወጡ ተቋማትን በተመለከተ የተለያየ አሀዝ ይቀርባል፡፡ ለምሳሌ መጀመሪያ ላይ 84 ተቋማት ሳይመዘገቡ ቀሩ፡፡ በኋላ ላይ ግን ዘግይተው የመጡ አሉ፡፡ ከነሱ ውስጥ በቂ ምክንያት ያቀረቡትን መዝግበን እየገመገምን ነው፡፡ በሌላ በኩል ደግሞ ተመዝግበው ከነበሩት ውስጥ ለመውጣት ሒደት ላይ ያሉ አሉ፣ ጎንለጎን ማለት ነው፡፡ ይህ የእነሱ ገባ ወጣ ማለት፣ ከዘርፉ የወጡ ተቋማት ብዛት በየጊዜው እንዲለያይ አድርጎታል፡፡ እንደዛም ሆኖ፣ አሁን የምዝገባና የግምገማ ሒደት ላይ ስለሆንን ትክክለኛ ቁጥሩን ማስቀመጥ ቢያስቸግርም ቢያንስ 80 የግል ትምህርት ተቋማት፣ ስራቸውን አቋርጠው ከዘርፉ ተሰናብተዋል፡፡
የዳግመ ምዝገባው መመሪያ ላይ በቂ ውይይት አልተደረገበትም፣ ከዘርፉ ተዋናዮች ግብአት አልተወሰደም የሚለውም ጉዳይ ትክክል አይደለም፡፡ ከተቋማቱ ባለቤቶች በሁለት መንገድ ግብአት ተቀብለናል፡፡ አንደኛው፣ ከውይይት መድረክ የተገኘው ሲሆን፣ ሁለተኛው ደግሞ በፅሑፍ የተቀበልነው ነው፡፡ በዚህ መንገድ በአዲስ አበባ በሀይሌ ግራንድ ሆቴል ከተደረገ ውይይትና በፅሑፍ ከቀረቡልን ሀሳቦች ግብአት ወስደናል፡፡አስፈላጊ የሆኑትንና ያስኬዳሉ የምንላቸውን ሀሳቦች በግብአትነት ተጠቅመንባቸዋል፡፡
ለምሳሌ ፦ ከእነሱ ተቀብለን ካካተትናቸው ሀሳቦች አንዱ፣ በመውጫ ፈተና ቢያንስ 25 በመቶ ያላሳለፈ ተቋም መቀጠል የለበትም የሚለው መስፈርት መቼ ተግባራዊ መሆን ይጀምር የሚለው ላይ የእነሱን ሀሳብ ተቀብለን የእፎይታ ጊዜ እንዲሰጥ አድርገናል፡፡
ይህ መስፈርት መተግበር የሚጀምረው፣ መመሪያው በወጣበት ጊዜ ትምህርት በጀመሩ ተማሪዎች ላይ እንጂ፣ በነባር ተማሪዎች ላይ መሆን የለበትም የሚለው ሀሳብ ከነሱ የመጣ ነው፡፡ ይህ ሀሳባቸው አሳማኝ በመሆኑ ተቀበልነው፡፡ አሁን ለትግበራው ሁለት አመት ገደማ አላቸው፡፡ በ 2019 ዓ.ም ገደማ ነው መተግበር የሚጀምረው ይህ መመሪያ፡፡ ሌሎችም የተቀበልናቸው ሀሳቦች አሉ፡ " ብለዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
❤840😡111🙏30🤔24😭18🕊16🥰9😢6😱4
#SafaricomEthiopia
⚡️ በዕለታዊ የዳታ ጥቅሎች ዘና ፈታ እንበል! 🥳
በልዩ ልዩ አማራጮች የቀረበልንን የሳፋሪኮም የኢንተርኔት ጥቅል የM-PESA Appን በመጠቀም አሁኑኑ እንግዛ! በፈጣን ዳታ እንንበሽበሽ!
#1wedefit
#Furtheraheadtogether
⚡️ በዕለታዊ የዳታ ጥቅሎች ዘና ፈታ እንበል! 🥳
በልዩ ልዩ አማራጮች የቀረበልንን የሳፋሪኮም የኢንተርኔት ጥቅል የM-PESA Appን በመጠቀም አሁኑኑ እንግዛ! በፈጣን ዳታ እንንበሽበሽ!
#1wedefit
#Furtheraheadtogether
❤102😡18🥰6😭5🙏2
TIKVAH-ETHIOPIA
" ትምህርት ቤቶች ባቀረቡት የዋጋ ጭማሪ ፕሮፖዛል ላይከወላጆች ጋር መግባባት ላይ መድረስ ካልተቻለ ባለሥልጣኑ ውሳኔ የሚሰጥ ይሆናል " - የአዲስ አበባ ትምህርት ቢሮ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሥር የሚገኙ 1,227 የግል ትምህርት ቤቶች በ2018 ዓ.ም. የትምህርት ዘመን እስከ 65 በመቶ ድረስ የትምህርት ቤት ክፍያ ጭማሪ እንዲያደርጉ እንደተፈቀደለቸው መዘገቡ ይታወሳል። ጭማሪውን ተከትሎ የአዲስ…
#AddisAbaba
የትምህርት ቤት ክፍያ !
20 በመቶ ትምህርት ቤቶች በ2018 የትምህርት ዘመን አገልግሎት ክፍያ ጭማሪ ላይ ከወላጆች ጋር አለመስማማታቸውን የአዲስ አበባ ትምህርት ቢሮ አሳውቋል።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ካቢኔ በቅርቡ ባጸደቀው የግል ትምህርት አገልግሎት ክፍያ አሰራር ስርአት ደንብ ቁጥር 194/2017 መሰረት በ2018 የትምህርት ዘመን አገልግሎት ክፍያ ላይ ከ ተማሪ ወላጅና አሳዳጊዎች ጋር ካልተስማሙ መንግስታዊ ካልሆኑ የትምህርት ተቋማት ጋር ውይይት መካሄዱን የከተማው ትምህርት ቢሮ አሳውቋል።
በውይይት መርሃ ግብሩ ፦
- የትምህርት ቢሮ ሃላፊ ዘላለም ሙላቱ (ዶ/ር) ፣
- የትምህርት እና ሥልጠና ባለሥልጣን ከፍተኛ አመራሮች
- የግል ትምህርት ቤቶች አሰሪዎች ማህበር ፣
- የግል ትምህርት ቤት ባለቤቶች እና የተማሪ ወላጅ ኮሚቴ ተወካዮች እንደ ተሳተፉ ቢሮው በማህበራዊ ትስስር ገጹ ገልጿል።
ውይይቱ የተካሄደው በጭማሪው ላይ መስማማት ላይ ያልደረሱ ትምህርት ቤቶች ደንቡ በሚያስቀምጠው መሰረት ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ ውሳኔ ያሳለፈ በመሆኑ በዚህ ጉዳይ ላይ የጋራ አስተሳሰብ ለመያዝ እንዲቻል መሆኑን ተገልጿል።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ዶክተር ዘላለም ሙላቱ "በደንቡ መሰረት 80 ፐርሰንት ያህል ትምህርት ቤቶች ከወላጆችና አሳዳጊዎች ጋር በመስማማት የአገልግሎት ክፍያ መጨመራቸው የሚበረታታ ተግባር ነው" ብለዋል።
እንደ ትምህርት ቢሮ ሃላፊው ገለጻ 20 በመቶ የሚሆኑ ትምህርት ቤቶች ከክፍያ ጭማሪ ጋር በተያያዘ ከወላጆች እና አሳዳጊዎች መስማማት ላይ አለመድረሳቸውን አመላክቷል።
የትምህርትና ስልጠናና ቁጥጥር ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር አቶ ኢዘዲን ሙስባህ "በደንቡ ላይ በመግባባት ወደ ስራ መገባቱን በዚህም መሰረት በርካታ ትምህርት ቤቶች ከወላጆች ጋር በመስማማት መጨመራቸውን ፣ መመሪያውን መሰረት በማድረግም ባለስልጣኑ በተቀሩትና መስማማት ባልቻሉት ላይ ውሳኔ መስጠቱን" አሳውቀዋል ።
ባለሥልጣኑ ምን ውሳኔ እንዳሳለፈ በዝርዝር ባይገለጽም የወላጆችን የመክፈል አቅም እና የትምህርት ተቋማቱን የግብአት አቅርቦት ታሳቢ አድርጎ ተግባራዊ የሆነ መሆኑን ስለመናገራቸው ትምህርት ቢሮው አሳውቋል።
#AddisAbabaEducationBureau
@tikvahethiopia
የትምህርት ቤት ክፍያ !
20 በመቶ ትምህርት ቤቶች በ2018 የትምህርት ዘመን አገልግሎት ክፍያ ጭማሪ ላይ ከወላጆች ጋር አለመስማማታቸውን የአዲስ አበባ ትምህርት ቢሮ አሳውቋል።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ካቢኔ በቅርቡ ባጸደቀው የግል ትምህርት አገልግሎት ክፍያ አሰራር ስርአት ደንብ ቁጥር 194/2017 መሰረት በ2018 የትምህርት ዘመን አገልግሎት ክፍያ ላይ ከ ተማሪ ወላጅና አሳዳጊዎች ጋር ካልተስማሙ መንግስታዊ ካልሆኑ የትምህርት ተቋማት ጋር ውይይት መካሄዱን የከተማው ትምህርት ቢሮ አሳውቋል።
በውይይት መርሃ ግብሩ ፦
- የትምህርት ቢሮ ሃላፊ ዘላለም ሙላቱ (ዶ/ር) ፣
- የትምህርት እና ሥልጠና ባለሥልጣን ከፍተኛ አመራሮች
- የግል ትምህርት ቤቶች አሰሪዎች ማህበር ፣
- የግል ትምህርት ቤት ባለቤቶች እና የተማሪ ወላጅ ኮሚቴ ተወካዮች እንደ ተሳተፉ ቢሮው በማህበራዊ ትስስር ገጹ ገልጿል።
ውይይቱ የተካሄደው በጭማሪው ላይ መስማማት ላይ ያልደረሱ ትምህርት ቤቶች ደንቡ በሚያስቀምጠው መሰረት ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ ውሳኔ ያሳለፈ በመሆኑ በዚህ ጉዳይ ላይ የጋራ አስተሳሰብ ለመያዝ እንዲቻል መሆኑን ተገልጿል።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ዶክተር ዘላለም ሙላቱ "በደንቡ መሰረት 80 ፐርሰንት ያህል ትምህርት ቤቶች ከወላጆችና አሳዳጊዎች ጋር በመስማማት የአገልግሎት ክፍያ መጨመራቸው የሚበረታታ ተግባር ነው" ብለዋል።
እንደ ትምህርት ቢሮ ሃላፊው ገለጻ 20 በመቶ የሚሆኑ ትምህርት ቤቶች ከክፍያ ጭማሪ ጋር በተያያዘ ከወላጆች እና አሳዳጊዎች መስማማት ላይ አለመድረሳቸውን አመላክቷል።
የትምህርትና ስልጠናና ቁጥጥር ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር አቶ ኢዘዲን ሙስባህ "በደንቡ ላይ በመግባባት ወደ ስራ መገባቱን በዚህም መሰረት በርካታ ትምህርት ቤቶች ከወላጆች ጋር በመስማማት መጨመራቸውን ፣ መመሪያውን መሰረት በማድረግም ባለስልጣኑ በተቀሩትና መስማማት ባልቻሉት ላይ ውሳኔ መስጠቱን" አሳውቀዋል ።
ባለሥልጣኑ ምን ውሳኔ እንዳሳለፈ በዝርዝር ባይገለጽም የወላጆችን የመክፈል አቅም እና የትምህርት ተቋማቱን የግብአት አቅርቦት ታሳቢ አድርጎ ተግባራዊ የሆነ መሆኑን ስለመናገራቸው ትምህርት ቢሮው አሳውቋል።
#AddisAbabaEducationBureau
@tikvahethiopia
❤375😭55😡40🕊10🤔7😢6😱3
" በወረዳዎቹ በቂ የጸጥታ ኃይል የለም። ጥቂት የጸጥታ ኃይሎችም ታጣቅዎቹ ጥቃት ካደረሱና ዝርፊያ ከፈጸሙ በኋላ ይመጡና ወዲያው ይመለሳሉ " - ፓርቲው
ቦሮ ዴሞክራቲክ ፓርቲ ፣ " የ'ሸኔ' ታጣቂዎች በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል በተለይ በመተከልና ካማሺ ዞኖች እያደረሱት ያለው ጥቃት ቀጥሏል " ሲል ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጿል።
ፓርቲው ሰሞኑንም በወንበራ ወረዳ ጥቃት መድረሱን ገልጾ፣ " የክልሉ መንግስት ለጉዳዩ በቂ ትኩረት በመስጠት በቂ የጸጥታ ኃይል በመላክና በአከባቢው የመከላከያ ካምፕ በማቋቋም የህዝቡን ሰላምና ደህንነት እንዲያስጠብቅ " ጠይቋል።
" በካማሺ ዞን አንዳንድ ወረዳዎች፣ በመተከል ዞን በቡለን፣ ድባጢና ወምበራ ወረዳዎች ታጣቂዎቹ የሚያደርሱት ጥቃት ተጠናክሮ ቀጥሏል " ያለው ፓርቲው፣ " ታጣቅዎቹ ንጹሐንን እና የጸጥታ አካላትን ይገድላሉ፣ የግልና የመንግስት ሀብት፣ ንብረት፤ የመንግስት ተቋማትን ይዘርፋሉ፤ ያወድማሉ " ሲልም ከሷል።
" ባለፈው ወር ቡለን ከተማ፣ ድባጢ ወረዳ በርበር ከተማ ሁለት ጊዜ ጥቃት ያደረሱ ሲሆን፣ በቡለን ከተማ በአንድ ሌሊት ብቻ የአረፋ በዓል በማክበር ላይ የነበሩ 11 የክልሉ ልዩ ኃይል አባላትን ከመግደል ባለፈ በርካታ ንጽሐንን፣ የሀገር ሽማግሌዎችን፣ የሃይማኖት አባቶችንና የጸጥታ አካላት ገድለዋል፤ ንጽሐንን አግተዋል " ብሏል።
ታጣቂዎቹን ተቋማትን " ዘርፈዋል፤ አውድመዋል " ሲል የከሰሰው ፓርቲው፣ " ሰሞኑን በወምበራ ወረዳ ወግዲና ሌሎች ቀበሌዎች ተመሳሳይ ጥቃቶችን ፈጽመዋል። ይህ ታጣቂ ቡድን በድባጢ ወረዳ ከ60% በላይ፣ በቡለን ወረዳ ከ30% በላይ ቀበሌዎችን በራሱ ቁጥጥር ስር በማደርግ ሰሞኑን ደግሞ በወንበራ ወረዳ በወግዲ ቀበሌ ግዛቱን ለማስፋፋት እየጣረ ይገኛል " ሲል ጠቁሟል።
ፓርቲው፣ " የሸኔ ታጣቂዎች በየወረዳዎቹ በሚኖሩ በሁሉም ብሔር ብሔረሰቦች ላይ ነው ጥቃት የሚያደርሱት " ብሎ፣ " በዚህ ምክንያት ነዋሪዎቹ ከፍተኛ ስጋት ውስጥ ይገኛሉ። በርካቶችም ተፈናቅለው ወደ አጎራባች ከተሞችና ወረዳዎች እየሄዱ ይገኛሉ " ብሏል።
" ታጣቂዎቹ በወረዳዎቹ ይህንን ሁሉ ጥቃት ሲፈጽሙና ወረዳዎች ‘ካቅማችን በላይ ነው’ እያሉ ለክልሉ መንግስት ሲያሳውቁ የክልሉ መንግስት ግን ለምን በቂ ትኩረት መስጠት እንዳልፈለገና ህዝቡን መከላከል ለምን እንዳልቻለ ለእኛ እንቆቅልሽ ሆኗል " ነው ያለው።
ፓርቲው ለቲክቫህ ኢትዮጵያ፣ " ህዝቡም በተደጋጋሚ ለክልሉ መንግስት የይድረሱልኝ ጥሪ ቢያቀርብም ሰሚ አላገኘም። በወረዳዎች በቂ የጸጥታ ኃይል የለም። ጥቂት የጸጥታ ኃይሎችም ታጣቅዎቹ ጥቃት ካደረሱና ዝርፊያ ከፈጸሙ በኋላ ይመጡና ወዲያውኑ ወይንም በነጋታው ይመለሳሉ " ሲል ነው የገለጸው።
" ህዝቡ ከፍተኛ ስጋት ላይ ይገኛል። ከሁሉም በላይ ይህ ሁሉ ጥቃትና በደል በህዝቡ ሲደርስ ክስተቱ በየትኛውም የመንግስት ሚዲያ አለመዘገቡና ሽፋን አለማግኘቱ ህዝቡን አሳዝኗል " በማለትም ወቅሷል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
ቦሮ ዴሞክራቲክ ፓርቲ ፣ " የ'ሸኔ' ታጣቂዎች በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል በተለይ በመተከልና ካማሺ ዞኖች እያደረሱት ያለው ጥቃት ቀጥሏል " ሲል ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጿል።
ፓርቲው ሰሞኑንም በወንበራ ወረዳ ጥቃት መድረሱን ገልጾ፣ " የክልሉ መንግስት ለጉዳዩ በቂ ትኩረት በመስጠት በቂ የጸጥታ ኃይል በመላክና በአከባቢው የመከላከያ ካምፕ በማቋቋም የህዝቡን ሰላምና ደህንነት እንዲያስጠብቅ " ጠይቋል።
" በካማሺ ዞን አንዳንድ ወረዳዎች፣ በመተከል ዞን በቡለን፣ ድባጢና ወምበራ ወረዳዎች ታጣቂዎቹ የሚያደርሱት ጥቃት ተጠናክሮ ቀጥሏል " ያለው ፓርቲው፣ " ታጣቅዎቹ ንጹሐንን እና የጸጥታ አካላትን ይገድላሉ፣ የግልና የመንግስት ሀብት፣ ንብረት፤ የመንግስት ተቋማትን ይዘርፋሉ፤ ያወድማሉ " ሲልም ከሷል።
" ባለፈው ወር ቡለን ከተማ፣ ድባጢ ወረዳ በርበር ከተማ ሁለት ጊዜ ጥቃት ያደረሱ ሲሆን፣ በቡለን ከተማ በአንድ ሌሊት ብቻ የአረፋ በዓል በማክበር ላይ የነበሩ 11 የክልሉ ልዩ ኃይል አባላትን ከመግደል ባለፈ በርካታ ንጽሐንን፣ የሀገር ሽማግሌዎችን፣ የሃይማኖት አባቶችንና የጸጥታ አካላት ገድለዋል፤ ንጽሐንን አግተዋል " ብሏል።
ታጣቂዎቹን ተቋማትን " ዘርፈዋል፤ አውድመዋል " ሲል የከሰሰው ፓርቲው፣ " ሰሞኑን በወምበራ ወረዳ ወግዲና ሌሎች ቀበሌዎች ተመሳሳይ ጥቃቶችን ፈጽመዋል። ይህ ታጣቂ ቡድን በድባጢ ወረዳ ከ60% በላይ፣ በቡለን ወረዳ ከ30% በላይ ቀበሌዎችን በራሱ ቁጥጥር ስር በማደርግ ሰሞኑን ደግሞ በወንበራ ወረዳ በወግዲ ቀበሌ ግዛቱን ለማስፋፋት እየጣረ ይገኛል " ሲል ጠቁሟል።
ፓርቲው፣ " የሸኔ ታጣቂዎች በየወረዳዎቹ በሚኖሩ በሁሉም ብሔር ብሔረሰቦች ላይ ነው ጥቃት የሚያደርሱት " ብሎ፣ " በዚህ ምክንያት ነዋሪዎቹ ከፍተኛ ስጋት ውስጥ ይገኛሉ። በርካቶችም ተፈናቅለው ወደ አጎራባች ከተሞችና ወረዳዎች እየሄዱ ይገኛሉ " ብሏል።
" ታጣቂዎቹ በወረዳዎቹ ይህንን ሁሉ ጥቃት ሲፈጽሙና ወረዳዎች ‘ካቅማችን በላይ ነው’ እያሉ ለክልሉ መንግስት ሲያሳውቁ የክልሉ መንግስት ግን ለምን በቂ ትኩረት መስጠት እንዳልፈለገና ህዝቡን መከላከል ለምን እንዳልቻለ ለእኛ እንቆቅልሽ ሆኗል " ነው ያለው።
ፓርቲው ለቲክቫህ ኢትዮጵያ፣ " ህዝቡም በተደጋጋሚ ለክልሉ መንግስት የይድረሱልኝ ጥሪ ቢያቀርብም ሰሚ አላገኘም። በወረዳዎች በቂ የጸጥታ ኃይል የለም። ጥቂት የጸጥታ ኃይሎችም ታጣቅዎቹ ጥቃት ካደረሱና ዝርፊያ ከፈጸሙ በኋላ ይመጡና ወዲያውኑ ወይንም በነጋታው ይመለሳሉ " ሲል ነው የገለጸው።
" ህዝቡ ከፍተኛ ስጋት ላይ ይገኛል። ከሁሉም በላይ ይህ ሁሉ ጥቃትና በደል በህዝቡ ሲደርስ ክስተቱ በየትኛውም የመንግስት ሚዲያ አለመዘገቡና ሽፋን አለማግኘቱ ህዝቡን አሳዝኗል " በማለትም ወቅሷል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
❤402😡49😭34🙏15🕊12😢7💔7🤔5😱5👏2
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#Sidama
ለሀዋሳ ከተማ አስተዳደር አዲስ ፖሊስ አዛዥ ተሹሟል።
የምስራቅ ሲዳማ ዞን ፖሊስ አዛዥ የነበሩት ምክትል ኮሚሽነር ግርማ ማቴዎስ የሀዋሳ ከተማ ፖሊስ አዛዥ ሆነዉ ተሹመዋል።
በፀጥታ ዘርፉ ዉስጥ ሪፎርም ዉስጥ እንደሆነ በሚነገረው የሲዳማ ክልል ፖሊስ ተቋም ዛሬ በሀዋሳ ከተማ ከንቲባ አቶ መኩሪያ መርሻዬ በተፃፈ ደብዳቤ የምስራቃዊ ሲዳማ ዞን ፖሊስ አዛዥ የነበሩት ምክትል ኮሚሽነር ግርማ ማቴዎስ ከዛሬ ሐምሌ 2/2017ዓ/ም ጀምሮ የሀዋሳ ከተማ ፖሊስ አዛዥ ሆነዉ ተሹመዋል።
የሀዋሳ ከተማ ፖሊስ አዛዥ የነበሩት ኮማንደር መልካሙ አየለ በምን ምክንያት እንደተነሱ እስካሁን የተገለፀ ነገር የለም።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
ሀዋሳ
#TikvahEthiopiaFamilyHawassa
@tikvahethiopia
ለሀዋሳ ከተማ አስተዳደር አዲስ ፖሊስ አዛዥ ተሹሟል።
የምስራቅ ሲዳማ ዞን ፖሊስ አዛዥ የነበሩት ምክትል ኮሚሽነር ግርማ ማቴዎስ የሀዋሳ ከተማ ፖሊስ አዛዥ ሆነዉ ተሹመዋል።
በፀጥታ ዘርፉ ዉስጥ ሪፎርም ዉስጥ እንደሆነ በሚነገረው የሲዳማ ክልል ፖሊስ ተቋም ዛሬ በሀዋሳ ከተማ ከንቲባ አቶ መኩሪያ መርሻዬ በተፃፈ ደብዳቤ የምስራቃዊ ሲዳማ ዞን ፖሊስ አዛዥ የነበሩት ምክትል ኮሚሽነር ግርማ ማቴዎስ ከዛሬ ሐምሌ 2/2017ዓ/ም ጀምሮ የሀዋሳ ከተማ ፖሊስ አዛዥ ሆነዉ ተሹመዋል።
የሀዋሳ ከተማ ፖሊስ አዛዥ የነበሩት ኮማንደር መልካሙ አየለ በምን ምክንያት እንደተነሱ እስካሁን የተገለፀ ነገር የለም።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
ሀዋሳ
#TikvahEthiopiaFamilyHawassa
@tikvahethiopia
❤447🕊29😢22💔18🤔14🙏13😡11😭10😱7🥰5👏2