Calling all #Ethiopian Innovators!
The second round of the Immunisation Innovation Accelerator is now open - offering up to $100,000 in grants to solutions that improve #vaccine access.
📅 Application deadline: July 27
🔗 https://www.stc-accelerator.org/
#ChildHealth #InnovationInAction #HealthInnovation #Ethiopia
The second round of the Immunisation Innovation Accelerator is now open - offering up to $100,000 in grants to solutions that improve #vaccine access.
📅 Application deadline: July 27
🔗 https://www.stc-accelerator.org/
#ChildHealth #InnovationInAction #HealthInnovation #Ethiopia
❤82🙏6😱5🤔2😢2🥰1👏1
ንብ ኢንተርናሽናል ባንክ ንብተራ ኦንላይን መተግበሪያን ይፋ አደረገ !
ንብ ኢንተርናሽናል ባንክ አዲስ ይፋ ባደረገው የሦስት ዓመት ስትራቴጂ ዕቅድና የአምስት ዓመት ፍኖተ ካርታ ውስጥ ካቀዳቸው ዋና ዋና ተግባራት መካከል አንዱ የሆነውን ንብተራ ኦንላይን መተግበሪያ የማብሰሪያ መርሐ ግብር አካሄደ፡፡
ይህ ለደንበኞች የተሟላ፣ ምቹ፣ ቀላልና ቀልጣፋ አገልግሎት መስጠት የሚያስችለው ንብተራ ኦንላይን ሱፐር አፕ መተግበሪያ ከሐምሌ 05 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ ሥራ ላይ እንዲውል ተደርጓል፡፡
መተግበርያው ደንበኞች ከባንክ አገልግልት በተጨማሪ ግብይቶችንና ክፍያዎችን በቀላሉ የእጅ ስልካቸውን ብቻ በመጠቀም መፈጸም እንደሚያስችላቸው በዚሁ የማብሰሪያ መርሃ ግብር ላይ ተገልጻል፡፡
በመርሐ ግብሩ ላይ ተገኝተው መልዕክት ያስተላለፉት የባንኩ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ሔኖክ ከበደ ባስተላለፉት መልዕክት ባንኩ ለደንበኞቹ ዘመኑ የሚፈልገውን ቴክኖሎጂ በመጠቀም በውጤት የታጀበ አገልግልት ለመስጠት ጥረቱን አጠናክሮ እንደሚቀጥል የገለጹ ሲሆን አዲሱ የሦስት ዓመት ስትራቴጂክ ዕቅድም ከባለድርሻ አካላትና ከመላው ደንበኞቹ ጋር በመሆን የላቀ ውጤት የሚመዘገብበት ይሆናል ብለዋል፡፡
በመጨረሻም ይህ በውስጥ አቅም በልጽጎ ወደ ተግባር የገባው ንብተራ ኦንላይን መተግበሪያና አዲሱ የሶስት አመት ስትራቴጂክ ዕቅድ በአጭር ጊዜ ውስጥ በማበልፀግና ወደ ሥራ እንዲገባ ላደረጉ የባንኩ ሠራተኞችና የሥራ ኃላፊዎች ምሰጋና ያቀረቡት የባንኩ ሥራ አስፈጻሚ ቦርድ ሊ/መንበር አቶ ሺሰማ ሸዋነካ አዲሱ የስትራቴጂክ ዕቅድ ላይ ሁሉም ባለድርሻ አካላት ምክክር አድርገውበትና ጸድቆ ወደ ሥራ መግባቱን አመልክተዋል፡፡
በይፋዊ የንብተራ ኦንላይን መተግበሪያ መርሃ ግብሩ ላይ የባንኩ ሥራ አስፈጻሚ ቦርድ አባላት፣ ደንበኞች፣ የባንኩ የስራ ኃላፊዎችና ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል፡፡
ለበለጠ መረጃ፡- https://www.nibbanksc.com/wp-content/uploads/2025/07/Press-release-NIB-Tera.pdf
ይሠሯል ከልብ፣ እንደ ንብ!
#Nib #DigitalBanking #Nibinternationalbank #nibbank #nibtera #nibsuperapp
Facebook / Instagram / linkedin / X / Youtube / Tiktok / Website
ንብ ኢንተርናሽናል ባንክ አዲስ ይፋ ባደረገው የሦስት ዓመት ስትራቴጂ ዕቅድና የአምስት ዓመት ፍኖተ ካርታ ውስጥ ካቀዳቸው ዋና ዋና ተግባራት መካከል አንዱ የሆነውን ንብተራ ኦንላይን መተግበሪያ የማብሰሪያ መርሐ ግብር አካሄደ፡፡
ይህ ለደንበኞች የተሟላ፣ ምቹ፣ ቀላልና ቀልጣፋ አገልግሎት መስጠት የሚያስችለው ንብተራ ኦንላይን ሱፐር አፕ መተግበሪያ ከሐምሌ 05 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ ሥራ ላይ እንዲውል ተደርጓል፡፡
መተግበርያው ደንበኞች ከባንክ አገልግልት በተጨማሪ ግብይቶችንና ክፍያዎችን በቀላሉ የእጅ ስልካቸውን ብቻ በመጠቀም መፈጸም እንደሚያስችላቸው በዚሁ የማብሰሪያ መርሃ ግብር ላይ ተገልጻል፡፡
በመርሐ ግብሩ ላይ ተገኝተው መልዕክት ያስተላለፉት የባንኩ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ሔኖክ ከበደ ባስተላለፉት መልዕክት ባንኩ ለደንበኞቹ ዘመኑ የሚፈልገውን ቴክኖሎጂ በመጠቀም በውጤት የታጀበ አገልግልት ለመስጠት ጥረቱን አጠናክሮ እንደሚቀጥል የገለጹ ሲሆን አዲሱ የሦስት ዓመት ስትራቴጂክ ዕቅድም ከባለድርሻ አካላትና ከመላው ደንበኞቹ ጋር በመሆን የላቀ ውጤት የሚመዘገብበት ይሆናል ብለዋል፡፡
በመጨረሻም ይህ በውስጥ አቅም በልጽጎ ወደ ተግባር የገባው ንብተራ ኦንላይን መተግበሪያና አዲሱ የሶስት አመት ስትራቴጂክ ዕቅድ በአጭር ጊዜ ውስጥ በማበልፀግና ወደ ሥራ እንዲገባ ላደረጉ የባንኩ ሠራተኞችና የሥራ ኃላፊዎች ምሰጋና ያቀረቡት የባንኩ ሥራ አስፈጻሚ ቦርድ ሊ/መንበር አቶ ሺሰማ ሸዋነካ አዲሱ የስትራቴጂክ ዕቅድ ላይ ሁሉም ባለድርሻ አካላት ምክክር አድርገውበትና ጸድቆ ወደ ሥራ መግባቱን አመልክተዋል፡፡
በይፋዊ የንብተራ ኦንላይን መተግበሪያ መርሃ ግብሩ ላይ የባንኩ ሥራ አስፈጻሚ ቦርድ አባላት፣ ደንበኞች፣ የባንኩ የስራ ኃላፊዎችና ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል፡፡
ለበለጠ መረጃ፡- https://www.nibbanksc.com/wp-content/uploads/2025/07/Press-release-NIB-Tera.pdf
ይሠሯል ከልብ፣ እንደ ንብ!
#Nib #DigitalBanking #Nibinternationalbank #nibbank #nibtera #nibsuperapp
Facebook / Instagram / linkedin / X / Youtube / Tiktok / Website
❤325👏35😡15🥰4😢4😭3
TIKVAH-ETHIOPIA
" ሦስት 5Lሚኒባሶች ናቸው የተወሰዱት ፤ ሦስት ሆነው ነበር ያደሩት አንዱ ጥበቃ አብሮ ጠፍቷል " - ባለንብረቶቹ ትላንት (ረቡዕ ለሐሙስ) ከሌሊቱ 9 ሰዓት ገደማ ፓርክ ከተደረጉበት ሦስት 5L ሚኒባሶች እንደተወሰዱባቸው ለቲክቫህ ኢትዮጵያ የገለጹ ባለንብረቶች ተሽከርካሪዎቹን ያየ ሁሉ እንዲጠቁማቸው በአጽንኦት ተማጽነዋል። ባለንብረቶቹ " ሦስት 5L ሚኒባሶች ናቸው የተወሰዱት፤ ሦስት ሆነው ነበር ያደሩት…
" አንዱ መኪና ተገኝቷል " - ባለንብረቶች
ከቀናት በፊት ለሊት 9 ሰዓት ላይ አዲስ አበባ ቃሊቶ ቶታል ኮንዶሚየም ግቢ ውስጥ የቆሙ ሶስት 5L ሚኒባስ ተሽከርካሪዎች በአንድ ጊዜ እንደተወሰዱ፣ አንደኛው እንደተገኘ ሌሎቹን ያየ ሰው እንዲቆጥማቸው ባለንበረቶቹ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰቦች አሳውቀው ነበር።
መልዕክቱ በቲክቫህ ኢትዮጵያ ከወጣ በኋላ አንዱ መኪና ማለትም ኦሮ ኮድ 03 34021 ጀሞ 2 አካባቢ መገኘቱን ገልጸዋል።
" መረጃዉን አይቶ ለደወለልን ግለሰብ እንዲሁም ለአቃቂ ቃሊቲ ፖሊስ አባላት ምስጋናችንን አድርሱልን " ብለዋል።
አሁን ላይ ተሽከርካሪውን በእጃቸው ለማድረግ ከፖሊስ እየጠበቁ መሆናቸውን አመልክተው " ተሽከርካሪዎቹን ይወስዳሉ ተብለው የተጠረጠሩት አልተያዙም ክትትል እየተደረገ ነው " ሲሉ ጠቁመዋል።
አሁንም ቀሪ አንዱን ተሽከርካሪ ኦሮ ኮድ 03 41867 ያየ እንዲጠቁማቸው ተማጽነዋል።
ከዚህ ቀደም ባለንብረቶቹ በጥበቃና ቀጣሪ ኤጀንሲው ላይ ጥርጣሬ እንዳላቸው ገልጸው የነበረ ሲሆን በዚህ ላይ ገና ፖሊስ ምርመራ እያደረገ መሆኑን አስረድተዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamliyAA
@tikvahethiopia
ከቀናት በፊት ለሊት 9 ሰዓት ላይ አዲስ አበባ ቃሊቶ ቶታል ኮንዶሚየም ግቢ ውስጥ የቆሙ ሶስት 5L ሚኒባስ ተሽከርካሪዎች በአንድ ጊዜ እንደተወሰዱ፣ አንደኛው እንደተገኘ ሌሎቹን ያየ ሰው እንዲቆጥማቸው ባለንበረቶቹ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰቦች አሳውቀው ነበር።
መልዕክቱ በቲክቫህ ኢትዮጵያ ከወጣ በኋላ አንዱ መኪና ማለትም ኦሮ ኮድ 03 34021 ጀሞ 2 አካባቢ መገኘቱን ገልጸዋል።
" መረጃዉን አይቶ ለደወለልን ግለሰብ እንዲሁም ለአቃቂ ቃሊቲ ፖሊስ አባላት ምስጋናችንን አድርሱልን " ብለዋል።
አሁን ላይ ተሽከርካሪውን በእጃቸው ለማድረግ ከፖሊስ እየጠበቁ መሆናቸውን አመልክተው " ተሽከርካሪዎቹን ይወስዳሉ ተብለው የተጠረጠሩት አልተያዙም ክትትል እየተደረገ ነው " ሲሉ ጠቁመዋል።
አሁንም ቀሪ አንዱን ተሽከርካሪ ኦሮ ኮድ 03 41867 ያየ እንዲጠቁማቸው ተማጽነዋል።
ከዚህ ቀደም ባለንብረቶቹ በጥበቃና ቀጣሪ ኤጀንሲው ላይ ጥርጣሬ እንዳላቸው ገልጸው የነበረ ሲሆን በዚህ ላይ ገና ፖሊስ ምርመራ እያደረገ መሆኑን አስረድተዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamliyAA
@tikvahethiopia
❤540🙏76🕊14🥰10😡9👏7😢4🤔3😭3
#AddisAbaba
በመዲናዋ የተመረጡ የመንግሥት ተቋማት እስከ እሁድ ግማሽ ቀን ድረስ አገልግሎት ሊሰጡ ነው።
በአዲስ አበባ ከተማ በተመረጡ የከተማ አስተዳደሩ ተቋማት ላይ መደበኛ የሥራ ቀናት መራዘሙን የከተማው ፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሀብት ልማት ቢሮ አስታውቋል።
ቢሮው እንዳሳወቀው፥ አገልግሎት ፈላጊዎች በተመረጡ ተቋማት ከሰኞ እስከ ቅዳሜ ከጠዋቱ 2፡30 እስከ 11፡30 እና እሁድ እስከ ቀኑ 6፡30 ድረስ አገልግሎት ማግኘት እንደሚችሉ ነው የገለጸው።
አገልግሎቱም ከማዕከል መስሪያ ቤቶች ጀምሮ ክ/ከተማ እና ወረዳዎች ድረስ የሚዘልቅ መሆኑን አስታውቋል።
በተጠቀሱት ቀናት አገልግሎት የሚሰጡ ከማዕከል እስከ ወረዳ ያሉ ተቋማት የትኞቹ ናቸው ?
- ንግድ ቢሮ፣
- ገቢዎች ቢሮ፣
- መሬት ልማት አስተዳደር ቢሮ፣
- መሬት ይዞታ ምዝገባና መረጃ ኤጀንሲ፣
- ግንባታ ፍቃድ ቁጥጥር ባለስልጣን፣
- ህብረት ስራ እና የፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሀብት ልማት ቢሮ እና ቅርንጫፍ ፅ/ቤቶች ላይ በተጠቀሰው መሰረት አገልግሎት የሚሰጥ መሆኑን አሳውቋል።
@TikvahethMagazine @tikvahethiopia
በመዲናዋ የተመረጡ የመንግሥት ተቋማት እስከ እሁድ ግማሽ ቀን ድረስ አገልግሎት ሊሰጡ ነው።
በአዲስ አበባ ከተማ በተመረጡ የከተማ አስተዳደሩ ተቋማት ላይ መደበኛ የሥራ ቀናት መራዘሙን የከተማው ፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሀብት ልማት ቢሮ አስታውቋል።
ቢሮው እንዳሳወቀው፥ አገልግሎት ፈላጊዎች በተመረጡ ተቋማት ከሰኞ እስከ ቅዳሜ ከጠዋቱ 2፡30 እስከ 11፡30 እና እሁድ እስከ ቀኑ 6፡30 ድረስ አገልግሎት ማግኘት እንደሚችሉ ነው የገለጸው።
አገልግሎቱም ከማዕከል መስሪያ ቤቶች ጀምሮ ክ/ከተማ እና ወረዳዎች ድረስ የሚዘልቅ መሆኑን አስታውቋል።
በተጠቀሱት ቀናት አገልግሎት የሚሰጡ ከማዕከል እስከ ወረዳ ያሉ ተቋማት የትኞቹ ናቸው ?
- ንግድ ቢሮ፣
- ገቢዎች ቢሮ፣
- መሬት ልማት አስተዳደር ቢሮ፣
- መሬት ይዞታ ምዝገባና መረጃ ኤጀንሲ፣
- ግንባታ ፍቃድ ቁጥጥር ባለስልጣን፣
- ህብረት ስራ እና የፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሀብት ልማት ቢሮ እና ቅርንጫፍ ፅ/ቤቶች ላይ በተጠቀሰው መሰረት አገልግሎት የሚሰጥ መሆኑን አሳውቋል።
@TikvahethMagazine @tikvahethiopia
😡1.31K❤1.15K👏272😭116🤔41💔31🙏27🕊23😱22🥰14
" የታርጋ ቁጥሩ ኮድ3-48279 አ.አ የሆነ ተሽከርካሪ ተሰርቆብናል " - ድርጅቱ
ሮሜል ጀነራል ትሬዲንግ የተሰኘ ድርጅት ጃፓን ሰራሽ 5L የ2002 ሞዴል ታርጋ ቁጥሩ ኮድ 3-48279 አ.አ የሆነ ሚኒባስ መኪና መሰረቁን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጿል።
መኪናው ሀምሌ 5 ቀን 2017 ዓ.ም ከቀኑ 9 ሰዓት አካባቢ አዲስ አበባ ከኡራኤል ወደ ወሎ ሰፈር በሚወስደው አዲሱ አስፓልት ላይ ' ሰላም አደባባይ ' ከመድረሱ በፊት ባለው ቦታ ከቆመበት በሌቦች እንደተሰረቀ አመልክቷል።
ድርጅቱ ይህንን በዕለቱ ለቂርቆስ ክፍለ ከተማ ፖሊስ መምሪያ እንዳመለከተ ገልጿል።
" የመኪናው ልዩ ምልክት ዕቃ ለመጫን እንዲመች ከገቢና ቀጥሎ ያለው ወንበር ብቻ ያለው ሲሆን ሌላው የተፈታ ነው " ብሏል።
" መኪናችን ያለበትን ለጠቆመ ወይም ለያዘ ወረታ እንከፍላለን " ያለው ድርጅቱ " ለጥቆማ ስልክ ቁጥሮቻችን +251930078032 ፣ 0913324134 እና +251115620212 ናቸው " ሲል አመልክቷል።
@tikvahethiopia
ሮሜል ጀነራል ትሬዲንግ የተሰኘ ድርጅት ጃፓን ሰራሽ 5L የ2002 ሞዴል ታርጋ ቁጥሩ ኮድ 3-48279 አ.አ የሆነ ሚኒባስ መኪና መሰረቁን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጿል።
መኪናው ሀምሌ 5 ቀን 2017 ዓ.ም ከቀኑ 9 ሰዓት አካባቢ አዲስ አበባ ከኡራኤል ወደ ወሎ ሰፈር በሚወስደው አዲሱ አስፓልት ላይ ' ሰላም አደባባይ ' ከመድረሱ በፊት ባለው ቦታ ከቆመበት በሌቦች እንደተሰረቀ አመልክቷል።
ድርጅቱ ይህንን በዕለቱ ለቂርቆስ ክፍለ ከተማ ፖሊስ መምሪያ እንዳመለከተ ገልጿል።
" የመኪናው ልዩ ምልክት ዕቃ ለመጫን እንዲመች ከገቢና ቀጥሎ ያለው ወንበር ብቻ ያለው ሲሆን ሌላው የተፈታ ነው " ብሏል።
" መኪናችን ያለበትን ለጠቆመ ወይም ለያዘ ወረታ እንከፍላለን " ያለው ድርጅቱ " ለጥቆማ ስልክ ቁጥሮቻችን +251930078032 ፣ 0913324134 እና +251115620212 ናቸው " ሲል አመልክቷል።
@tikvahethiopia
❤363🤔60😢35🕊23😱18🥰3👏2
የቀድሞው የናይጄሪያ ፕሬዝደንት ሞሐመዱ ቡሃሪ ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ።
የ82 ዓመቱ ቡሃሪ በብሪታኒያ ዋና ከተማ ለንደን በሚገኝ ክሊኒክ ውስጥ ከዚህ ዓለም በሞት እንደተለዩ የቀድሞ ቃል አቀባያቸው ገርባ ጋሹ ገልጸዋል።
ሁለት የፕሬዝዳንታዊ የሥልጣን ዘመን ያገለገሉት ቡኻሪ ሥልጣን ያስረከቡት እኤአ በ2023 ነበር።
በናይጄሪያ ታሪክ ቡሃሪ በምርጫ በሥልጣን ላይ የሚገኝ ፕሬዝደንት ያሸነፉ የመጀመሪያው የተቃዋሚ ፓርቲ ዕጩ ነበሩ። እኤአ 2015 ሥልጣን የያዙት የቀድሞውን ፕሬዝደንት ጉድላክ ጆናታን በምርጫ አሸንፈው ነው።
ይሁንና ናይጄሪያን የመሩባቸው ዓመታት በጤና ዕክል ምክንያት አሉባልታ በብዛት ይናፈስባቸው ነበር።
ቡሃሪ ራሳቸውን ዴሞክራሲያዊ አድርገው ከመቀየራቸው በፊት በ1980ዎቹ ጠንካራ አምባገነን ሆነው ናይጄሪያን መርተዋል።
ቡሃሪ ከሦስት ያልተሳካ ሙከራ በኋላ ጉድላክ ጆናታንን አሸንፈው ፕሬዝዳንት ሲሆኑ በናይጄሪያ ፖለቲካ የለውጥ ዕድል ተፈጠረ ተብሎ ተስፋ ተሰንቆ ነበር።
ይሁንና በስልጣን ዘመናቸው በናይጄሪያ የበረታውን ሙስና እና የመረጋጋት እጦት መቅረፍ ተስኗቸዋል። የሥልጣን ዘመናቸው ኢኮኖሚያዊ ችግሮች እና የጤና ዕክል የበረታባቸው ነበሩ። መንግሥታቸው በተቃዋሚዎች ላይ በወሰዳቸው ርምጃዎች ከፍተኛ ትችት ይሰነዘርባቸው ነበር።
በሰሜናዊ እና ደቡባዊ ናይጄሪያ ከፍተኛ ፉክክር ባለባት ሀገር ቡሃሪ የትውልድ አካባቢያቸውን ሰዎች እና ዘመድ አዝማዶቻቸውን ለከፍተኛ የመንግሥት ሥልጣን በመሾም አለመተማመን እና ጥርጣሬ እንዲነግስ አድርገዋል እየተባሉ ይተቻሉ።
Credit - DW
@tikvahethiopia
የ82 ዓመቱ ቡሃሪ በብሪታኒያ ዋና ከተማ ለንደን በሚገኝ ክሊኒክ ውስጥ ከዚህ ዓለም በሞት እንደተለዩ የቀድሞ ቃል አቀባያቸው ገርባ ጋሹ ገልጸዋል።
ሁለት የፕሬዝዳንታዊ የሥልጣን ዘመን ያገለገሉት ቡኻሪ ሥልጣን ያስረከቡት እኤአ በ2023 ነበር።
በናይጄሪያ ታሪክ ቡሃሪ በምርጫ በሥልጣን ላይ የሚገኝ ፕሬዝደንት ያሸነፉ የመጀመሪያው የተቃዋሚ ፓርቲ ዕጩ ነበሩ። እኤአ 2015 ሥልጣን የያዙት የቀድሞውን ፕሬዝደንት ጉድላክ ጆናታን በምርጫ አሸንፈው ነው።
ይሁንና ናይጄሪያን የመሩባቸው ዓመታት በጤና ዕክል ምክንያት አሉባልታ በብዛት ይናፈስባቸው ነበር።
ቡሃሪ ራሳቸውን ዴሞክራሲያዊ አድርገው ከመቀየራቸው በፊት በ1980ዎቹ ጠንካራ አምባገነን ሆነው ናይጄሪያን መርተዋል።
ቡሃሪ ከሦስት ያልተሳካ ሙከራ በኋላ ጉድላክ ጆናታንን አሸንፈው ፕሬዝዳንት ሲሆኑ በናይጄሪያ ፖለቲካ የለውጥ ዕድል ተፈጠረ ተብሎ ተስፋ ተሰንቆ ነበር።
ይሁንና በስልጣን ዘመናቸው በናይጄሪያ የበረታውን ሙስና እና የመረጋጋት እጦት መቅረፍ ተስኗቸዋል። የሥልጣን ዘመናቸው ኢኮኖሚያዊ ችግሮች እና የጤና ዕክል የበረታባቸው ነበሩ። መንግሥታቸው በተቃዋሚዎች ላይ በወሰዳቸው ርምጃዎች ከፍተኛ ትችት ይሰነዘርባቸው ነበር።
በሰሜናዊ እና ደቡባዊ ናይጄሪያ ከፍተኛ ፉክክር ባለባት ሀገር ቡሃሪ የትውልድ አካባቢያቸውን ሰዎች እና ዘመድ አዝማዶቻቸውን ለከፍተኛ የመንግሥት ሥልጣን በመሾም አለመተማመን እና ጥርጣሬ እንዲነግስ አድርገዋል እየተባሉ ይተቻሉ።
Credit - DW
@tikvahethiopia
❤406😭151😢28🕊16💔14👏8🤔8🙏8😡4
TIKVAH-ETHIOPIA
ጥያቄያችን ካልተመለሰ ወደ ቤት አንገባም ያሉ ነዋሪዎች ! " መንግስት መጥቶ ጥያቄያችንን ካለመለሰልን ወደ ቤት ላለመመለስ ወስነን ሜዳ ላይ ተሰብስበናል " - ነዋሪዎች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ " ሰሚ እስክናገኝ ወደ ቤታችን አንመለስም ! " በሲዳማ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት በሰሜናዊ ሲዳማ ዞን ሀዋሳ ዙሪያ ወረዳ የዶሬ ባፋኖ አከባቢ ነዋሪዎች " በአዲስ የመዋቅር ጥናት እና ልማታዊ ጉዳዮች ዙሪያ የወረዳዉ…
" ሸዉደዉናል 5ዐ ሰዉ መርጣችሁ ስጡን ብለዉ ካስነሱን በኋላ የተወከሉትን ስብሰባ ጠርተዉ አስፈራርተዋል " - ነዋሪዎች
➡️ " የኛ ጥያቄ የወረዳውን የተወሰኑ ቀበሌያት ወደ ሀዋሳ ከተማ ክፍለ ከተማነት ለማጠቃለል መወሰኑ ተገቢነት የለዉም የሚል ነው ! "
የሲዳማ ክልል ሰሜናዊ ሲዳማ ዞን ሀዋሳ ዙሪያ ወረዳ የዶሬ ባፋኖ አከባቢ ነዋሪዎች ለሀዋሳ ከተማ አስተዳደር አዲስ ተዋቀረ በተባለው የክፍለ ከተማ አደረጃጀት ከሀዋሳ ዙሪያ ወረዳ 5 ቀበሌያትን ብቻ ነጥሎ መወሰዱን በመግለፅ ቅሬታ እንዳደረባቸው ለቲክቫህ ኢትዮጵየ ገልጸው ነበር።
ነዋሪዎቹ የተመረጡት ቀበሌያት ምርታማና የተሻለ የኢኮኖሚ አቅም ያላቸዉ በመሆኑ የወረዳዉን የመልማት አቅም ያዳክመዋል፤ ከዚህ ቀደም የተገባልንም ቃል ተግባራዊ አልተደረገም ሲሉ አደባባይ በመዉጣት " ጥያቄያችን እስኪመለስ ወደ ቤታችን አንመለስም " ማለታቸው አይዘነጋን።
" በዕለቱ ሕዝቡ ከሜዳ ላይ አልነሳ በማለቱ ምሽት ከ2 ሰዓት በኋላ የዞንና የወረዳ አመራሮች መጥተዉ 'ለነገ 50 ተወካዮችን መርጣችሁ ዉይይት እናድርግ' ብለዉ ሕዝቡ እንዲበተን ካደረጉ በኋላ በማግስቱ የተመረጡትን ተወካዮች ሰብስበዉ አስፈራርተዋቸው ስብሰባዉን ረግጠዉ ወጥተዋል " ሲሉ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።
" አመራሮች ሸዉደዉናል 50 ሰዎችን መርጣችሁ ወክሉና እናንተ ወደ ቤት ተመለሱ እነሱ ነገ ከኛ ጋር ይወያዩ ብለው በሽማግሌዎች በኩል ሕዝቡ እንዲበተን ካደረጉ በኋላ በማግስቱ የተወከሉትን ሰዎች ' እናንተ ናችሁ ሕዝቡን የሚታሳምፁት ' ብለዉ በማስፈራራት ስብሰባዉን ጭምር ረግጠዉ ወጥተዋል " ሲሉ ገልፀዋል።
ዶሬ ባፋናና አከባቢዉ ያሉ ሌሎች ቀበሌዎች ከዚህ ቀደም በሀዋሳ ከተማ ስር ከመካለል ጋር ተያይዞ አንድ ላይ ዉሳኔው ያለ ልዩነት ተግባራዊ እንደሚደረግ እየተነገራቸዉ የቆየ ቢሆንም አሁን ላይ በወረዳው የተሻለ አቅም ያላቸው የተባሉ 5 ቀበሌያትን ብቻ ነጥሎ ' በሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ሀዋሳ ላንጋኖ ክፍለ ከተማ ' በሚል ሊደራጅ እንደሆነ መነገሩ ሕዝቡን ማስቆጣቱን ነዋሪዎቹ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አስረድተዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ በጉዳዩ ዙሪያ ተጨማሪ መረጃ ለማግኘት ያደረገዉ ሙከራ የወረዳዉ አስተዳዳሪ ፈቃደኛ ባለመሆናቸው ሳይሳካ ቀርቷል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
ሀዋሳ
#TikvahEthiopiaFamliyHawassa
@tikvahethiopia
➡️ " የኛ ጥያቄ የወረዳውን የተወሰኑ ቀበሌያት ወደ ሀዋሳ ከተማ ክፍለ ከተማነት ለማጠቃለል መወሰኑ ተገቢነት የለዉም የሚል ነው ! "
የሲዳማ ክልል ሰሜናዊ ሲዳማ ዞን ሀዋሳ ዙሪያ ወረዳ የዶሬ ባፋኖ አከባቢ ነዋሪዎች ለሀዋሳ ከተማ አስተዳደር አዲስ ተዋቀረ በተባለው የክፍለ ከተማ አደረጃጀት ከሀዋሳ ዙሪያ ወረዳ 5 ቀበሌያትን ብቻ ነጥሎ መወሰዱን በመግለፅ ቅሬታ እንዳደረባቸው ለቲክቫህ ኢትዮጵየ ገልጸው ነበር።
ነዋሪዎቹ የተመረጡት ቀበሌያት ምርታማና የተሻለ የኢኮኖሚ አቅም ያላቸዉ በመሆኑ የወረዳዉን የመልማት አቅም ያዳክመዋል፤ ከዚህ ቀደም የተገባልንም ቃል ተግባራዊ አልተደረገም ሲሉ አደባባይ በመዉጣት " ጥያቄያችን እስኪመለስ ወደ ቤታችን አንመለስም " ማለታቸው አይዘነጋን።
" በዕለቱ ሕዝቡ ከሜዳ ላይ አልነሳ በማለቱ ምሽት ከ2 ሰዓት በኋላ የዞንና የወረዳ አመራሮች መጥተዉ 'ለነገ 50 ተወካዮችን መርጣችሁ ዉይይት እናድርግ' ብለዉ ሕዝቡ እንዲበተን ካደረጉ በኋላ በማግስቱ የተመረጡትን ተወካዮች ሰብስበዉ አስፈራርተዋቸው ስብሰባዉን ረግጠዉ ወጥተዋል " ሲሉ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።
" አመራሮች ሸዉደዉናል 50 ሰዎችን መርጣችሁ ወክሉና እናንተ ወደ ቤት ተመለሱ እነሱ ነገ ከኛ ጋር ይወያዩ ብለው በሽማግሌዎች በኩል ሕዝቡ እንዲበተን ካደረጉ በኋላ በማግስቱ የተወከሉትን ሰዎች ' እናንተ ናችሁ ሕዝቡን የሚታሳምፁት ' ብለዉ በማስፈራራት ስብሰባዉን ጭምር ረግጠዉ ወጥተዋል " ሲሉ ገልፀዋል።
ዶሬ ባፋናና አከባቢዉ ያሉ ሌሎች ቀበሌዎች ከዚህ ቀደም በሀዋሳ ከተማ ስር ከመካለል ጋር ተያይዞ አንድ ላይ ዉሳኔው ያለ ልዩነት ተግባራዊ እንደሚደረግ እየተነገራቸዉ የቆየ ቢሆንም አሁን ላይ በወረዳው የተሻለ አቅም ያላቸው የተባሉ 5 ቀበሌያትን ብቻ ነጥሎ ' በሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ሀዋሳ ላንጋኖ ክፍለ ከተማ ' በሚል ሊደራጅ እንደሆነ መነገሩ ሕዝቡን ማስቆጣቱን ነዋሪዎቹ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አስረድተዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ በጉዳዩ ዙሪያ ተጨማሪ መረጃ ለማግኘት ያደረገዉ ሙከራ የወረዳዉ አስተዳዳሪ ፈቃደኛ ባለመሆናቸው ሳይሳካ ቀርቷል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
ሀዋሳ
#TikvahEthiopiaFamliyHawassa
@tikvahethiopia
❤504😢57🕊26😡24🤔16😭14💔9🥰8👏8😱6
#ATTENTION🚨
ከፍተኛ ጥንቃቄ የሚያስፈልገው መልዕክት !
በኢትዮጵያ በርካታ አካባቢዎች ለአብነትም አዋሽ ወንዝን ተከትሎ የሚኖሩ ከመካከለኛው የሀገሪቱ ክፍል ከኦሮሚያ ክልል ከደቡብ ምዕራብ ሸዋ ዞን ወረዳዎች ጀምሮ እስከ ታችኛው አዋሽ አካባቢዎች በተለይም ፦
- በአፋር ክልል በአዋሽ ወንዝ ዳር የሚገኙ ወረዳዎች፣
- በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ዳሰች ወረዳ ሆሞራቴ ከተማን ጨምሮ፣
- በጋምቤላ ክልል ጋምቤላ ከተማ እና ሌሎች በባሮ ወንዝ ተጋላጭ ሊሆኑ የሚችሉት ወረዳዎች፣
- በዋቤ ሸበሌ ወንዝ ሊጠቁ የሚችሉ የሶማሌ ክልል ወረዳዎች፣
- በአማራ ክልል በጣና ሀይቅ አቅራቢያ የሚገኙ አንዳንድ የክልሉ አካባቢዎች በዚህ የክረምት ወቅት ለጎርፍ አደጋ ተጋላጭ እና የተጎጂ ይሆናሉ ተብሎ ተለይቷል፡፡
በተጨማሪም የክረምት ወቅት ዝናብ ተጠቃሚ የአገሪቱ አከባቢዎችና ከተሞች በሙሉ ከባድ ዝናብ በሚኖርበት ወቅት በየትኛዉም ጊዜ በቅፅበታዊ ጎርፍ አደጋ ሊጠቁ የሚችሉ ሲሆን በአንዳንድ አካባቢዎች ባልታሰቡ ክስተቶች እና ትናንሽ ወንዞች ምክንያት የጎርፍ አደጋ ሊከሰት ይችላል፡፡
የ2017 ክረምት ወቅት የኢትዮጵያ ሚቲዎሮሎጂ ኢንስቲትዩት እና ዓለም አቀፍ ትንበያዎች እንደሚያመለክቱት በእነዚህ ክልሎች እና ሌሎችም ከመደበኛ በላይ የሆነ ዝናብ የሚጠበቅ ነዉ፡፡
የጎርፍ አደጋ ስጋት ተጋላጭ የሆኑ አካባቢዎች የትኞቹ ናቸው ?
➡️ በተፋሰስና ወንዝ ዳርቻ (አዋሽ ፣ ዋቤ ሸበሌ፣ ተከዜ፣ ባሮ፣ ኦሞ፣ የከተሞች ወንዞች፣ ወ.ዘ.ተ….)፣
➡️ በግድቦች ማስተንፈሻ አካባቢዎች (ተንዳሆና ቀሰም፣ ግልገል ጊቤ ፣ ተከዜ፣ ገናሌ፣ ዳዋ ፣ ፊንጫ፣ ቆቃ ወ.ዘ.ተ...)፣
➡️ የክረምት ዝናብ ተጠቃሚ የሆነ አከባቢዎችና ከተሞች ሙሉ በሙሉ ከባድ ዝናብ በሚኖርበት ወቅት በየትኛዉም ጊዜ ቅፅበታዊ ጎርፍ ሊጠቁ ይችላሉ።
ማህበረሰቡ፣ የሚመለከታቸው ተቋማት እና የአስተዳደር መዋቅሮች አስፈላጊውን ጥንቃቄና በክትትል ላይ ተመሰረተ እርምጃዎች እንዲወስዱ የኢትዮጵያ አደጋ ሥጋት ሥራ አመራር ኮሚሽን አሳስቧል።
(ዝርዝር መረጀዎች ከላይ ተያይዟል)
⚠️ መልዕክቱን ለሌሎች ያጋሩ!
#EDRMC
#TikvahEthiopiaFamliyAA
@tikvahethiopia
ከፍተኛ ጥንቃቄ የሚያስፈልገው መልዕክት !
በኢትዮጵያ በርካታ አካባቢዎች ለአብነትም አዋሽ ወንዝን ተከትሎ የሚኖሩ ከመካከለኛው የሀገሪቱ ክፍል ከኦሮሚያ ክልል ከደቡብ ምዕራብ ሸዋ ዞን ወረዳዎች ጀምሮ እስከ ታችኛው አዋሽ አካባቢዎች በተለይም ፦
- በአፋር ክልል በአዋሽ ወንዝ ዳር የሚገኙ ወረዳዎች፣
- በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ዳሰች ወረዳ ሆሞራቴ ከተማን ጨምሮ፣
- በጋምቤላ ክልል ጋምቤላ ከተማ እና ሌሎች በባሮ ወንዝ ተጋላጭ ሊሆኑ የሚችሉት ወረዳዎች፣
- በዋቤ ሸበሌ ወንዝ ሊጠቁ የሚችሉ የሶማሌ ክልል ወረዳዎች፣
- በአማራ ክልል በጣና ሀይቅ አቅራቢያ የሚገኙ አንዳንድ የክልሉ አካባቢዎች በዚህ የክረምት ወቅት ለጎርፍ አደጋ ተጋላጭ እና የተጎጂ ይሆናሉ ተብሎ ተለይቷል፡፡
በተጨማሪም የክረምት ወቅት ዝናብ ተጠቃሚ የአገሪቱ አከባቢዎችና ከተሞች በሙሉ ከባድ ዝናብ በሚኖርበት ወቅት በየትኛዉም ጊዜ በቅፅበታዊ ጎርፍ አደጋ ሊጠቁ የሚችሉ ሲሆን በአንዳንድ አካባቢዎች ባልታሰቡ ክስተቶች እና ትናንሽ ወንዞች ምክንያት የጎርፍ አደጋ ሊከሰት ይችላል፡፡
የ2017 ክረምት ወቅት የኢትዮጵያ ሚቲዎሮሎጂ ኢንስቲትዩት እና ዓለም አቀፍ ትንበያዎች እንደሚያመለክቱት በእነዚህ ክልሎች እና ሌሎችም ከመደበኛ በላይ የሆነ ዝናብ የሚጠበቅ ነዉ፡፡
የጎርፍ አደጋ ስጋት ተጋላጭ የሆኑ አካባቢዎች የትኞቹ ናቸው ?
➡️ በተፋሰስና ወንዝ ዳርቻ (አዋሽ ፣ ዋቤ ሸበሌ፣ ተከዜ፣ ባሮ፣ ኦሞ፣ የከተሞች ወንዞች፣ ወ.ዘ.ተ….)፣
➡️ በግድቦች ማስተንፈሻ አካባቢዎች (ተንዳሆና ቀሰም፣ ግልገል ጊቤ ፣ ተከዜ፣ ገናሌ፣ ዳዋ ፣ ፊንጫ፣ ቆቃ ወ.ዘ.ተ...)፣
➡️ የክረምት ዝናብ ተጠቃሚ የሆነ አከባቢዎችና ከተሞች ሙሉ በሙሉ ከባድ ዝናብ በሚኖርበት ወቅት በየትኛዉም ጊዜ ቅፅበታዊ ጎርፍ ሊጠቁ ይችላሉ።
ማህበረሰቡ፣ የሚመለከታቸው ተቋማት እና የአስተዳደር መዋቅሮች አስፈላጊውን ጥንቃቄና በክትትል ላይ ተመሰረተ እርምጃዎች እንዲወስዱ የኢትዮጵያ አደጋ ሥጋት ሥራ አመራር ኮሚሽን አሳስቧል።
(ዝርዝር መረጀዎች ከላይ ተያይዟል)
#EDRMC
#TikvahEthiopiaFamliyAA
@tikvahethiopia
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
❤1.28K🙏247🕊53😭34😢29👏21🥰17😡10🤔7😱3
#AAiT
Announcement of Professional Training Programs
Python Programming + Data Analytics and Visualization
By: Addis Ababa University,
College of Technology and Built Environment,
School of Electrical & Computer Engineering
Registration Deadline: July 24, 2025
Training Starts on: July 26, 2025
Online Registration Link: https://forms.gle/M1DPS1zFP4K9QT4V6
Telephone: +251-913-574525/ +251-940-182870
Email: [email protected]
For more information: https://forms.gle/M1DPS1zFP4K9QT4V6
Telegram Channel: https://www.tg-me.com/TrainingAAiT
Announcement of Professional Training Programs
Python Programming + Data Analytics and Visualization
By: Addis Ababa University,
College of Technology and Built Environment,
School of Electrical & Computer Engineering
Registration Deadline: July 24, 2025
Training Starts on: July 26, 2025
Online Registration Link: https://forms.gle/M1DPS1zFP4K9QT4V6
Telephone: +251-913-574525/ +251-940-182870
Email: [email protected]
For more information: https://forms.gle/M1DPS1zFP4K9QT4V6
Telegram Channel: https://www.tg-me.com/TrainingAAiT
❤86😭3🥰1🙏1
🤙🏽ከሳፋሪኮም ወደ የቴሌ የሚያስደውሉ የድምፅ ጥቅሎች በመጠቀም ከ07 ➡️ 09 መስመር በእጥፍ ጉርሻ በሽ በሽ ብለን እንደዋወል! ከሳፋሪኮም ጋር በአብሮነት አንድ ወደፊት⚡️
#SafaricomEthiopia
#1Wedefit
#Furtheraheadtogether
#SafaricomEthiopia
#1Wedefit
#Furtheraheadtogether
❤45🙏7😡3😭2🕊1
ዓባይ ባንክ የተመሰረተበትን 15ኛ ዓመት በይፋ ማክበር ጀመረ
-------------------------------------------
ዓባይ ባንክ አ.ማ የኢትዮጵያ የግል ባንክ ዘርፍ በመቀላቀል የተሟላ የባንክ አገልግሎት ለመስጠት የተመሰረተበትን 15ኛ ዓመት የምስረታ በዓል በይፋ ማክበር ጀመረ፡፡
ባንኩ የተመሰረተበትን 15ኛ ዓመት የምስረታ በዓል በይፋ ማክበር መጀመሩን አስመልክቶ በሀያት ሪጀንሲ ሆቴል በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ የዓባይ ባንክ ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ የኋላ ገሠሠ እንደገለጹት፣ ባንኩ በተመሰረተ አጭር ጊዜ ውስጥ በሁሉም የሥራ አፈፃፀም መለኪያዎች እጅግ ከፍተኛ ውጤት ማስመዝገቡን እና ለተገኘው ሁለንተናዊ የሥራ ስኬት የባንኩ ደንበኞች፣ የሥራ አመራር ቦርድ አባላት፣ ባለአክሲዮኖች፣ የሥራ አመራር አባላት፣ ሠራተኞች እና የተለያዩ ባለድርሻ አካላት የነበራቸው ሚና ከፍተኛ እንደነበረ አውስተዋል፡፡ የምስረታ በዓሉ በአጠቃላይ ለደንበኞች እና ለመላ የባንኩ ቤተሰቦች መሆኑን የጠቆሙት ዋና ሥራ አስፈጻሚው፣ ብሩህ አጀማመራችንን የሚዘክር እና የከፍታ መዳረሻችንን የሚያመላክትም ይሆናል ብልዋል፡፡
ባንኩ በ823 መስራች ባለአክሲዮኖች በብር 125 ነጥብ 8 ሚሊዮን የተከፈለ ካፒታል ሥራ የጀመረ ሲሆን፣ በአሁኑ ወቅት ከፍተኛ እድገት በማስመዝገብ የባለአክሲዮኖችን ቁጥሩ 4 ሺህ 500 እንዲሁም የተከፈለ ካፒታሉን ብር 7 ቢሊዮን ማድረስ መቻሉ በጋዜጣዊ መግለጫው ላይ ተገልጿል፡፡
ዓባይ - የታላቅነት ምንጭ!
-------------------------------------------
ዓባይ ባንክ አ.ማ የኢትዮጵያ የግል ባንክ ዘርፍ በመቀላቀል የተሟላ የባንክ አገልግሎት ለመስጠት የተመሰረተበትን 15ኛ ዓመት የምስረታ በዓል በይፋ ማክበር ጀመረ፡፡
ባንኩ የተመሰረተበትን 15ኛ ዓመት የምስረታ በዓል በይፋ ማክበር መጀመሩን አስመልክቶ በሀያት ሪጀንሲ ሆቴል በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ የዓባይ ባንክ ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ የኋላ ገሠሠ እንደገለጹት፣ ባንኩ በተመሰረተ አጭር ጊዜ ውስጥ በሁሉም የሥራ አፈፃፀም መለኪያዎች እጅግ ከፍተኛ ውጤት ማስመዝገቡን እና ለተገኘው ሁለንተናዊ የሥራ ስኬት የባንኩ ደንበኞች፣ የሥራ አመራር ቦርድ አባላት፣ ባለአክሲዮኖች፣ የሥራ አመራር አባላት፣ ሠራተኞች እና የተለያዩ ባለድርሻ አካላት የነበራቸው ሚና ከፍተኛ እንደነበረ አውስተዋል፡፡ የምስረታ በዓሉ በአጠቃላይ ለደንበኞች እና ለመላ የባንኩ ቤተሰቦች መሆኑን የጠቆሙት ዋና ሥራ አስፈጻሚው፣ ብሩህ አጀማመራችንን የሚዘክር እና የከፍታ መዳረሻችንን የሚያመላክትም ይሆናል ብልዋል፡፡
ባንኩ በ823 መስራች ባለአክሲዮኖች በብር 125 ነጥብ 8 ሚሊዮን የተከፈለ ካፒታል ሥራ የጀመረ ሲሆን፣ በአሁኑ ወቅት ከፍተኛ እድገት በማስመዝገብ የባለአክሲዮኖችን ቁጥሩ 4 ሺህ 500 እንዲሁም የተከፈለ ካፒታሉን ብር 7 ቢሊዮን ማድረስ መቻሉ በጋዜጣዊ መግለጫው ላይ ተገልጿል፡፡
ዓባይ - የታላቅነት ምንጭ!
❤197🕊11🤔7😭4🥰1😢1