Telegram Web Link
በወላይታ ዞን ሰርጉን አቋርጦ ቀዶ ህክምና የሰራው ሐኪም አድናቆት እየተቸረው ይገኛል

ዶ/ር ብሩክ ወይሻ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል፣ በወላይታ ዞን፣ በበሌ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል የቀዶ ጥገና ስፔሻሊስት ነው።

ወጣቱ ሐኪም ታዲያ የራሱን የሰርግ ዝግጅት አቋርጦ ወጥቶ ታካሚን ቀዶ ጥገና በማድረግ ሕይወት የማዳኑ ጉዳይ የአካባቢው ነዋሪዎች መነጋገሪያ ሆኗል።

የሰርጉ ዝግጅት ከነበረበት ከ40 በላይ ኪሎ ሜትር በላይ ወደ ሆስፒታሉ ተጉዞ ቀዶ ጥገና በማድረግ የሰው ሕይወት ማዳን መቻሉን ዶ/ር ብሩክ ለኢቢሲ ተናግሯል።

ወጣቱ ሐኪም የተሟላ የቀዶ ጥገና ሕክምና ገና በቅርቡ በጀመረው ሆስፒታል የመጀመሪያው ስፔሻሊስት ቅጥር ሲሆን፤ በሆስፒታሉ ሥራ ከጀመረም ገና ሶስት ሳምንቱ ነው።

በቀዶ ጥገና የታከመው በሽታ ከጨጓራ ሕመም ጋር ተያይዞ የሚከሰትና ሕይወትን አደጋ ላይ የሚጥል ሲሆን፤ ታካሚው በሰዓቱ ሕክምና ባይደረግለት ኖሮ ሕይወቱ ሊያልፍ ይችል እንደነበርም ነው የተገለፀው።

ቀዶ ጥገና የሕክምና ባለሙያዎች የቡድን ሥራ ነው ያለው ዶ/ር ብሩክ፤ በአጠቃላይ በቀዶ ጥገናው ለተሳተፈው የሕክምና ቡድን ምስጋና አቅርቧል ።

የቀዶ ጥገና ሕክምናው የተደረገለት የ40 ዓመት ታካሚ በጥሩ ጤንነት ላይ እንደሚገኝ የገለፀው ዶ/ር ብሩክ፤ ከዚህ የሚበልጥ ደስታ የለም ብሏል።

በሙያዬ የፈፀምኩትን ቃለ-መሃላ እና የገባሁትን ቃል-ኪዳን መቼም ቢሆን አላጥፍም፤ ለሙያው የሚገባውን ክብር እሰጣለሁ ብሏል ወጣቱ ሐኪም ብሩክ ወይሻ።(Via ETV)

  T.me/ethio_mereja
        ኢትዮ-መረጃ
ጤና ባለሙያዎች!!

የደሞዝ እና ጥቅማ ጥቅም ጥያቄ በማንሳት ለመንግሥት የሰላሳ ቀናት የቅድሚያ ማስጠንቀቂያ ጊዜ ሰጥተው የነበሩት የጤና ባለሙያዎች ምላሽ ባለማግኘታቸው ከፊል የሥራ ማቆም አድማ መምታታቸውን ለቢቢሲ ተናገሩ።

ባለሙያዎች ከጥቂት "የተመረጡ የሕክምና ክፍሎች" ውጪ ያሉ ክፍሎች ከዛሬ ግንቦት 5/2017 ዓ.ም. ጀምሮ ሥራ ማቆማቸውን ገልፀዋል።

ቢቢሲ ያነጋገራቸው አምስት በተለያዩ የአገሪቱ አካባቢዎች የሚገኙ ባለሙያዎች ከድንገተኛ፣ ከማዋለጃ፣ ከፅኑ ሕሙማን እንዲሁም ከድንገተኛ ቀዶ ሕክምና ክፍሎች ውጪ ያሉ የሕክምና ተቋማት ክፍሎች አገልግሎቶች ማቋረጣቸውን ተናግረዋል።

በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች የሚገኙ የጤና ባለሙያዎች ዛሬ ማክሰኞ ግንቦት 5 ቀን 2017 ዓ.ም. በመላ ሀገሪቱ የተጀመረውን የከፊል የስራ ማቆም አድማ ለማካሄድ ሲሞክሩ ከመንግሥት አካላት ማስፈራሪያና ጫና እንደደረሰባቸውም አስታውቀዋል።

በአዲስ አበባ ከተማ በዛሬው ዕለት ተጠርቷል የተባለውን የህክምና ባለሙያዎች አድማ በዋና ዋና የመንግስት ሆስፒታሎች ማለትም በዳግማዊ #ምኒልክ ሪፈራል ሆስፒታል፣ #በዘውዲቱ መታሰቢያ ሆስፒታል እና #በየካቲት12 ሜዲካል ኮሌጅ ሆስፒታል ጠዋት ላይ የከፊል የስራ ማቆም መካሄዱን ለመታዘብ ተችሏል።

  T.me/ethio_mereja
        ኢትዮ-መረጃ
ሕወሓት ከፖለቲካ ፓርቲነት ተሠረዘ

ሕዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ሕወሓት) ከፖለቲካ ፓርቲነት መሠረዙን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ አስታወቀ፡፡

ሕዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ህወሓት) ከፖለቲካ ፓርቲነት መሠረዙን አስመልክቶ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ያወጣው መግለጫ ሙሉ ቃል ቀጥሎ ቀርቧል፡-


  T.me/ethio_mereja
        ኢትዮ-መረጃ
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
#ቴምር ሪልስቴት
‼️7ሳይቶችን ስርተን አስረክበናል አሁን ላይ ደግሞ መሀል ፒያሳ ለሽያጭ ያወጣነው ሱቅ

‼️ፒያሳ ሱቅ ሽያጭ 
👉3.9ሚሊዮን 20ካሬ ቅድመ ክፍያ900,000ብር 4ተኛ እና 5ተኛ
👉4.2ሚሊዮን 20ካሬ ቅድመ ክፍያ 1.2ሚሊዮን 3ተኛ
👉4.8ሚሊዮን 20ካሬ ቅድመ ክፍያ 1.5ሚሊዮን 2ተኛ
👉5.5ሚሊዮን 20ካሬ ቅድመ ክፍያ 2ሚሊዮን 1ኛ
👉 7ሚሊዮን 20ካሬ ቅድመ ክፍያ 2.8ሚሊዮን ግራውንድ በውስጥ በኩል
👉10ሚሊዮን 20ካሬ ቅድመ ክፍያ 4ሚሊዮን ግራውንድ በውጪ
ለበለጠ መረጃ ይደውሉ
       👇👇👇👇👇👇
     +251939770177
     +251996856273
https://www.tg-me.com/TemerRealEstateSalesConsultant
WhatsApp. https://wa.me/251939770177
Telegram :@KalTemerRealEstate
"ሁሉን የሚያግባባ ነገር ፈልጉና ችግሮችን በሰላማዊ ውይይት ፍቱ" - ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ የርክበ ካህናት ምልዓተ ጉባኤ በዛሬው ዕለት በጽርሐ መንበረ ፓትርያርክ ተጀምሯል።

የርክበ ካህናት ምልዓተ ጉባኤ መጀመሩን አስመልክቶ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት መልዕክት አስተላልፈዋል።

በመልዕክታቸውም "ኢትዮጵያን ወደ ተሻለ ልማትና ዕድገት እናሻግራለን ብላችሁ እየደከማችሁ ያላችሁ ወገኖቻችን እባካችሁ መለስ ብላችሁ እናታችሁ የተንገላታችበትን እዩና በቃ በሉ" ብለዋል።

"ሁሉን የሚያግባባ ነገር ፈልጉና ችግሮችን በሰላማዊ ውይይት ፍቱ" ያሉ ሲሆን፤ "በዚህ ኣማራጭ እናት ሀገር እፎይታ እንድታገኝ ኣድርጉ፤ ይህንም ለውድ እናት የሚደረግ ካሣ ኣድርጋችሁ ውሰዱት፤ የቤተ ክርስቲያናችን ወቅታዊ መልእክትና ጥሪም ይህ ነው" ብለዋል።

ከሰላም እጦት የተነሣ በእጅጉ እየተጎዳ ያለውን ሕዝባችን ሰላምና ፍትሕ እንዲያገኝ በጸሎትም በትምህርትም፣ በምክርም መስራት እንደሚገባ አሳስበዋል።

"የኢትዮጵያ ህዝብ ለእንግልት እየተዳረገ ያለውም የሌሎች እጅ ባይለየውም በዋናነት በገዛ ልጆቹ ነው" ያሉት ፓትርያርኩ፤ "እናት በገዛ ልጆቿ ስትንገላታ ማየት እጅግ ኣሳዛኝ ነገር ነው፤ እንደዚህ ያለው ነገር በደንብ ያልታሰበበት ኣካሄድ በብስለትና በንስሓ ማስተካከል አሸናፊነትን እንጂ ተሸናፊነትን አያሳይምና እንዲታሰብበት እንመክራለን" ብለዋል።

  T.me/ethio_mereja
        ኢትዮ-መረጃ
ክርስቲያኖ ሮናልዶ ከዓለም ከፍተኛው ተከፋይ ስፖርተኛ ሆነ

የእግር ኳሱ ኮከብ ክርስቲያኖ ሮናልዶ በ2025 ከ275 ሚሊዮን ዶላር በላይ ገቢ በማግኘት የዓለም ከፍተኛው ተከፋይ ስፖርተኛ መሆን ችሏል።

ለሳዑዲዉ ክለብ አልናስር እየተጫወተ የሚገኘው ሮናልዶ ከስፖንሰር ሺፕ እና ከደሞዝ ጥቅማጥቅሞች ያገኘው ገቢ ከዓለም ቀዳሚው ስፖርተኛ አድርጎታል።

ክርስቲያኖ ሮናልዶ የዓለም ከፍተኛው ተከፋይ ስፖርተኛ ሲሆን ይህ ለ3ኛ ተከታታይ ዓመታት መሆን ፎርብስ ዘግቧል።

የቅርጫት ኳሱ ኮከብ ስቴፈን ከሪ በ 156 ሚሊዮን ዶላር ሁለተኛ ደረጃን ሲይዝ፤ ብሪታንያዊው ቦክሰኛ ታይሰን ፉሪ በ146 ሚሊዮን ሶስተኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል፡፡

ሌላኛው የእግር ኳስ ኮከብ ሊዮኔል ሜሲ 135 ሚሊዮን ዶላር ገቢ በማግኘት 5ኛ ደረጃ ላይ መቀመጥ ችሏል፡፡ እንዲሁም ሌላኛው የእግር ኳስ ተጫዋቾች ካሪም ቤንዜማ 104 ሚሊዮን ዶላር ገቢ በማግኘት 8ኛ ደረጃ ላይ የተቀመጠ ተጫዋች ሆኗል።

  T.me/ethio_mereja
        ኢትዮ-መረጃ
#ከቴምር ሪልስቴት
🎯🎯7ሳይቶችን ስርተን አስረክበናል አሁን ላይ ደግሞ መሀል ሣር ቤት አፓርትመንት እና ሱቅ ፒያሳ ለሽያጭ ያወጣነው 

👉2መኝታ 84ካሬ 5,392,800ብር ሙሉ ክፍያ
👉2መኝታ 94ካሬ 6,034,800ብር ሙሉ ክፍያ
👉3መኝታ 106ካሬ 6,869,400ብርሙሉክፍያ
👉3መኝታ 125ካሬ 8,025,000ብር ሙሉ ክፍያ

‼️ፒያሳ ሱቅ ሽያጭ 
👉3.9ሚሊዮን 20ካሬ ቅድመ ክፍያ900,000ብር 4ተኛ እና 5ተኛ
👉4.2ሚሊዮን 20ካሬ ቅድመ ክፍያ 1.2ሚሊዮን 3ተኛ
👉4.8ሚሊዮን 20ካሬ ቅድመ ክፍያ 1.5ሚሊዮን 2ተኛ
👉5.5ሚሊዮን 20ካሬ ቅድመ ክፍያ 2ሚሊዮን 1ኛ
👉 7ሚሊዮን 20ካሬ ቅድመ ክፍያ 2.8ሚሊዮን ግራውንድ በውስጥ በኩል
👉10ሚሊዮን 20ካሬ ቅድመ ክፍያ 4ሚሊዮን ግራውንድ በውጪ
ለበለጠ መረጃ ይደውሉ
       👇👇👇👇👇👇
     +251939770177
     +251996856273
https://www.tg-me.com/TemerRealEstateSalesConsultant
WhatsApp. https://wa.me/251939770177
2025/06/30 06:14:16
Back to Top
HTML Embed Code: