Telegram Web Link
ኦስትሪያ እና ኢትዮጵያ በከፍተኛ ትምህርቱ ዘርፍ በትብብር ለመሥራት የሚያስችላቸውን ውይይት አካሄዱ።
-------------------------------------------

(ሰኔ 18/2017 ዓ.ም) የከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ኮራ ጡሹኔ በኦስትሪያ ምክትል የፋይናንስ ሚኒስትር ‘H.E. Andreas REICHHARDT’ የተመራ ከፍተኛ የልዑካን ቡድንን በጽ/ቤታቸው ተቀብለው አነጋግረዋል።

በዚሁ ወቅት ክቡር ሚኒስትር ዴኤታው በኢትዮጵያ የከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ የትምህርት ጥራትና ብቃትን ለማረጋገጥ እየተተገበሩ ያሉ ሪፎርሞችን ለልዑካን ቡድኑ አብራርተውላቸዋል።

በተለይም የከፍተኛ ትምህርት ተቋማትን በተልዕኮና ትኩረት መስክ በመለየት በርካታ ሥራዎች እየተሰሩ መሆኑን አንስተው በዘርፉ የበለጠ ውጤታማ ለመሆን በትብብር የሚሰሩ ተግባራት መኖራቸውንም አብራርተዋል።

የኦስትሪያ ምክትል የፋይናን ሚኒስትር H.E. Andreas REICHHARDT በበኩላቸው ኦስትሪያና ኢትዮጵያ በትምህርት ዘርፍ የቆየ ትብብር እንደነበራቸው አንስተው ይህንን ትብብር የበለጠ አጠናክረው መቀጠል እንደሚፈልጉ ገልጸዋል። ሙሉ መረጃውን ለማግኘት ይህንን ሊንክ ይጫኑ፤ https://www.facebook.com/share/p/16e9wjFp2b/
የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ቁልፍ የሪፎርም ስራዎች አተገባበርና አፈጻጸም ላይ ያተኮረ ጉባኤ ተካሄደ።

ሰኔ 20/2017 ዓ.ም) "አካዳሚያዊ ውይይት ለአካዳሚክ ልህቀት" በሚል መሪ ቃል በተዘጋጀው ጉባኤ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የአካዳሚክ ምክትል ፕሬዘዳንቶችና የአካዳሚክ ፕሮግራም ሀላፊዎች በቁልፍ የሪፎርም ተግባራት አፈጻጸምና አሁን ላይ ያሉበትን ደረጃ በተመለከተ ልምዳቸውን አጋርተዋል።

በትኩረትና ተልኮ መስክ ልየታ (differentiation) ፤ በሥርዓተ ትምህርት ክለሳ( Curriculum revision)፤በሠራተኞችና ተማሪዎች የሙያ እድገት (Staff and students career development)፤ በቁልፍ የአፈጻጸም አመላካች መነሻና ኢላማ ልየታ ፤ KPI baseline and target identification),፣ የአፈጻጸም ኮንትራት ውል (Performance contracting implementation ) እንዲሁም በብሄራዊ ፈተናዎች አስተዳደርና አፈጻጸም ላይ የተሻለ ተሞክሮ ያላቸው ተቋማት ልምድ ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል።

በቀረቡት ተሞክሮዎች ላይ ሀሳባቸውን ያካፈሉት በትምህርት ሚኒስቴር የአካዳሚክ ጉዳዬች መሪ ስራ አስፈጻሚ ዶ/ር ኤባ ሜጄና አንዳንድ ተቋማት የሄዱበትን እርቀት አበረታተዋል።

ይሁን እንጂ በተወሠኑ ተቋማት ያለው ወጥነትና ቁርጠኝነት በሚፈለገው ልክ ባለመሆኑ ተቋማቱንም ይሁን የተቋማቱን ስራ ሀላፊዎች ጥንቃቄ ሊደረግ እንደሚገባ አስገንዝበዋል። ሙሉ መረጃውን ለማግኘት ይህንን ሊንክ ይጫኑ፣ https://web.facebook.com/share/p/16pXWpbSTh/
ሚኒስቴሩ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ምዕራብ ኦሞ ዞን ጀሙ ከተማ የሚያስገነባው ሞዴል ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ግንባታ ተጀመረ።
---------------------------------------------------
(ሰኔ 22/2017 ዓ.ም) የትምህርት ቤቱን ግንባታ የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ፣ አማካሪ ሚኒስትር ዴኤታው ፕሮፌሰር ክንደያ ገ/ህይወት እንዲሁም የክልሉ ከፍተኛ አመራሮች በተገኙበት ተጀምሯል።

የትምህርት ሚኒስትሩ በዚሁ ወቅት ባስተላለፉት መልዕክት ይህ ትምህርት ቤት በአርብቶ አደር አካባቢ የሚገነባ መሆኑን በመጥቀስ እያንዳዱ የኢትዮጵያ ልጅ እኩል የትምህር እድል እንዲያገኝ እየተሠራ ይገኛል ብለዋል።

ሁሉም ዜጎች አኩል እድል አግኝተው የሚማሩበት እና የበቁ፣ ተወዳዳሪ የሆኑ ልጆችን ለማፍራት በሁሉም ቦታ ትኩረት ሰጥቶ መሥራት ይጠበቃልም ብለዋል።

በምክትል ርዕሰ መስተደድር ማዕረግ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪና የክልሉ ትምህርት ቢሮ ኃላፊ አቶ አለማው ዘውዴ በበኩላቸው የዚህ ትምህርት ቤት ግንባታ ትምህርት ሚኒስቴር ትምህርትን በፍትሃዊነት ለሁሉም ዜጎች ተደራሽ ለማድረግ የሚያደርገውን ጥረት ማሳያ መሆኑን ተናግረዋል። ሙሉ መረጃውን ለማግኘት ይህንን ሊንክ ይጫኑ፣
https://www.facebook.com/share/p/16pG3QJgKT/
የትምህርት ሚኒስትሩ የ12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ፈተናን በቦንጋ ዩኒቨርሲቲ ተገኝተው አስጀመሩ።
--------------------------------------

(ሰኔ 23/2017 ዓ.ም) የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ፣ የሚኒስቴሩ አማካሪ ሚኒስትር ዴኤታ ፕሮፌሰር ክንደያ ገ/ህይወት እንዲሁም የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ዶ/ር ኢ/ር ነጋሽ ከሾጌ የ2017 ትምህርት ዘመን የኢትዮጵያ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ (12ኛ ክፍል) ፈተናን በቦንጋ ዩኒቨርሲቲ ተገኝተው አስጀምረዋል።

በዚሁ ጊዜ የትምህርት ሚኒስትሩ ባስተላለፉት መልዕክት ጠንክሮ ያጠና ተማሪ የተሻለ ውጤት ማምጣት እንደሚችል በማንሳት ተማሪዎች ተረጋግተው ፈተናቸውን እንዲወስዱ አበረታተዋል።

የመጀመሪያ ዙር የተፈጥሮ ሳይንስ ፈተና በዛሬው እለት በሁሉም የመፈተኛ ጣቢያዎች መሰጠት ተጀምሯል።

ዘንድሮ በወረቀትና በበየነ መረብ ከ608 ሺ በላይ ተማሪዎች ፈተናቸውን ይወስዳሉ ተብሎ ይጠበቃል።

የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ (12ኛ ክፍል) ፈተና ከሰኔ 23 እስከ ሃምሌ 08/2017ዓ.ም እንደሚሰጥ ይታወቃል
ዩኒቨርሲቲዎች የተሠጣቸውን ተልዕኮ በሚገባ ለይተው ሊሰሩ እንደሚገባ ተጠቆመ፤

የትምህርት ሚኒስቴር ከፍተኛ አመራሮች ከቦንጋ ዩኒቨርስቲ ማህበረሰብ አባላት ጋር ተወያይተዋል።
-------------------------------------------

(ሰኔ 24/2017 ዓ.ም) የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ዩኒቨርሲቲዎች አንድ ጊዜ ከተከፈቱ ተጠያቂነት የለም ማለት አይደለም፦ በተሠጠው ተልዕኮ መሠረት ካልሰሩ የተጠያቂነት ሥርዓት ሊዘረጋ ይገባል ብለዋል።

በተለይም ዩኒቨርሲቲዎች በእውነትና እውቀት ለሀገር የሚጠቅም ውይይት የሚደረግባቸው፣ ብቃት ያላቸው የሰው ሃይል ማፍራት የሚችሉ ትክክለኛ ዩኒቨርሳል የሆነ አቋም ሊኖራቸው ይገባል ለዚህም ትኩረት ተሠጥቶ እየተሠራ ይገኛል ብለዋል።

የትምህርት ሚኒስቴር አማካሪ ሚኒስት ዴኤታ ፕሮፌሰር ክንደያ ገ/ህይወት በበኩላቸው ዩኒቨርሲቲዎች አለም አቀፍ እውቀት የሚገበይባቸው ተቋማት በመሆናቸው ተቋማዊ አሰራርን መዘርጋት ተገቢ ነው ለዚህም የዩኒቨርስቲ አመራር ምደባ በእውቀትና በአለም አቀፍ ውድድሮች ሊሆን ይገባል ያሉ ሲሆን

እንደ ሀገር የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ በሚሰራው ሥራ የድርሻቸውን ሊወጡ ይገባል ብለዋል። ሙሉ መረጃውን ለማግኘት ይህንን ሊንክ ይጫኑ፤
https://www.facebook.com/share/p/19QmuzJJF7/
የበይነ መረብ ፈተና ተማሪዎች በራስ መተማመንን አዳብረው ፈተና እንዲሰሩ እድል እንደሚሰጥ ተጠቆመ፡
ከ299ሺ የሚበልጡ የማህበራዊ ሳይንስ ተማሪዎች የ2017 ዓ.ም. የ12ኛ ክፍል አገር አቀፍ ፈተና በመውሰድ ላይ ናቸው፡፡
-------------------//-----------------------------
የትምህርት ሚኒስትር ደኤታ ክብርት ወ/ሮ አየለች እሸቴ በአዲስ አበባ  በበይነ መረብ የሚፈተኑ የማህበራዊ  ሳይንስ ተማሪዎችን ተዘዋውረው በተመለከቱበት ወቅት እንደገለጹት የበይነ-መረብ ፈተና ተማሪዎች በራሳቸው ተማምነው ባወቁትና በተዘጋጁበት አግባብ ፈተና መስራት እንዲችሉ እድል የሚሰጥ መሆኑን ገልጸዋል።

የበይነ መረብ ፈተና ተማሪዎች በአቅረቢያቸው ሆነው ከቤታቸው እየተመላለሱ እንዲፈተኑ  እድል እንደሚፈጥር የጠቆሙት ክብርት ሚኒስትር ደኤታዋ በፈተና ጣቢያዎች ባደረጉት ምልከታም ፈተናው በተሻለ ሁኔታ እየተካሄደና ተማሪዎችም በተረጋጋ መንፈስ ፈተናውን እየወሰዱ መሆናቸውን ለመታዘብ መቻላቸውን ተናግረዋል፡፡

አክለውም የተፈጥሮ ሳይንስ ፈተና ተጠናቆ የማህበራዊ ሳይንስ ፈተና መጀመሩን የገለጹት ወ/ሮ አየለች በቀጣይ ያሉ ፈተናዎችንም ተማሪዎች ተረጋግተው እንዲፈተኑና መልካም እድልም እንዲገጥማቸው ምኞታቸውን ገልጸዋል፡፡

የአገር አቀፍ ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር እሸቱ ከበደ / ዶ/ር/ በበኩላቸው ከዛሬ ጀምሮ እስከ ሐምሌ 8/ 2017 ዓ.ም በሚሰጠው የማህበራዊ ሳይንስ ፈተና ከ299 ሺህ በላይ ተማሪዎች ፈተናውን በወረቀትና በበይነ መረብ እንደሚወስዱ ገልጸዋል፡፡

በአጠቃላይ በአገር አቀፍ ደረጃ እየተሰጠ ባለው የ2017 የሁለተኛ ደረጃ መልቀቂያ ፈተና 608ሺ በላይ ተማሪዎች በመላ አገሪቱ ፈተናውን ለመውሰድ መመዝገባቸውንም ዋና ይሬክተሩ አስታውሰዋል፡፡
2025/07/08 17:53:44

❌Photos not found?❌Click here to update cache.


Back to Top
HTML Embed Code: