#ትግራይ፦ በታራሚዎች እና በተጠርጣሪዎች የሰብአዊ መብቶች ሁኔታ ላይ ከባለድርሻ አካላት ጋር የተካሄደ የውይይት መድረክ
...
የታራሚዎችንና የተጠርጣሪዎችን ሰብአዊ መብቶች ለማረጋገጥ ሁሉም ባለድርሻ አካላት በቅንጅት ሊሠሩ ይገባል
የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) በትግራይ ክልል ከሰኔ 25 እስከ ሐምሌ 2 ቀን እና በመጋቢት ወር 2016 ዓ.ም. እንዲሁም በኅዳር ወር 2017 ዓ.ም. በ5 ማረሚያ ቤቶች እና 18 ፖሊስ ጣቢያዎች ባከናወነው የሰብአዊ መብቶች ክትትል ግኝቶች ላይ የካቲት 3 እና 4 ቀን 2017 ዓ.ም. በመቐለ ከተማ 2 ዙር የውይይት መድረኮችን አካሂዷል። በውይይት መድረኮቹ የክልሉ ማረሚያ ቤቶች አስተዳደር ኮሚሽን፣ የማረሚያ ቤቶችና ፖሊስ ኮሚሽን ኃላፊዎች፣ የዞን ፖሊስ አዛዦችና መርማሪዎች፣ የክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት እና ፍትሕ ቢሮ ተወካዮች ተገኝተዋል።
በውይይት መድረኩ ክትትል በተደረገባቸው ማረሚያ ቤቶች ትምህርትና ስልጠና ተጠናክሮ መሰጠት መጀመሩ፤ ፍርደኝነትን፣ ዕድሜንና የቅጣት መጠንን መሠረት ያደረገ ለይቶ የመያዝ ሁኔታ መኖሩ፤ ከመደበኛ የወንጀል ሕግ ሂደት ውጪ ታስረው የቆዩ ሰዎች እንዲለቀቁ ለማድረግ አስፈላጊውን ደንብ እና የአፈጻጸም መመሪያ ለማውጣት ሥራ መጀመሩ እንዲሁም ነጻ የሕግ ድጋፍ አገልግሎት መጀመሩ በመልካም ጎን የተጠቀሱ ናቸው።
🔗 https://ehrc.org/?p=31447
#Ethiopia🇪🇹 #HumanRightsForAll
በነጻ የስልክ መስመራችን 7307 ላይ በመደወል የሰብአዊ መብቶች ጥሰት አቤቱታ ማቅረብ ወይም ጥቆማ መስጠት ይችላሉ።
...
የታራሚዎችንና የተጠርጣሪዎችን ሰብአዊ መብቶች ለማረጋገጥ ሁሉም ባለድርሻ አካላት በቅንጅት ሊሠሩ ይገባል
የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) በትግራይ ክልል ከሰኔ 25 እስከ ሐምሌ 2 ቀን እና በመጋቢት ወር 2016 ዓ.ም. እንዲሁም በኅዳር ወር 2017 ዓ.ም. በ5 ማረሚያ ቤቶች እና 18 ፖሊስ ጣቢያዎች ባከናወነው የሰብአዊ መብቶች ክትትል ግኝቶች ላይ የካቲት 3 እና 4 ቀን 2017 ዓ.ም. በመቐለ ከተማ 2 ዙር የውይይት መድረኮችን አካሂዷል። በውይይት መድረኮቹ የክልሉ ማረሚያ ቤቶች አስተዳደር ኮሚሽን፣ የማረሚያ ቤቶችና ፖሊስ ኮሚሽን ኃላፊዎች፣ የዞን ፖሊስ አዛዦችና መርማሪዎች፣ የክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት እና ፍትሕ ቢሮ ተወካዮች ተገኝተዋል።
በውይይት መድረኩ ክትትል በተደረገባቸው ማረሚያ ቤቶች ትምህርትና ስልጠና ተጠናክሮ መሰጠት መጀመሩ፤ ፍርደኝነትን፣ ዕድሜንና የቅጣት መጠንን መሠረት ያደረገ ለይቶ የመያዝ ሁኔታ መኖሩ፤ ከመደበኛ የወንጀል ሕግ ሂደት ውጪ ታስረው የቆዩ ሰዎች እንዲለቀቁ ለማድረግ አስፈላጊውን ደንብ እና የአፈጻጸም መመሪያ ለማውጣት ሥራ መጀመሩ እንዲሁም ነጻ የሕግ ድጋፍ አገልግሎት መጀመሩ በመልካም ጎን የተጠቀሱ ናቸው።
🔗 https://ehrc.org/?p=31447
#Ethiopia🇪🇹 #HumanRightsForAll
በነጻ የስልክ መስመራችን 7307 ላይ በመደወል የሰብአዊ መብቶች ጥሰት አቤቱታ ማቅረብ ወይም ጥቆማ መስጠት ይችላሉ።
👍1
Stakeholder Dialogue on Humanitarian Demining and Mine Victim Assistance (Zimbabwe, Harare)
...
Ensuring the rights and inclusion of landmine survivors requires a holistic, rights-based approach that integrates victim assistance into a broader disability and development framework
The Ethiopian Human Rights Commission (EHRC) Commissioner for Women, Children, Older Persons and Disability Rights Rigbe Gebrehawaria, who is also the Expert Member of the Working Group on the Rights of Older Persons and Persons with Disabilities in Africa took part in Zimbabwe’s National Stakeholder Dialogue on Humanitarian Demining and Mine Victim Assistance, held from February 18-20, 2025, in Harare.
🔗 https://ehrc.org/?p=31460
#Ethiopia🇪🇹 #HumanRightsForAll
በነጻ የስልክ መስመራችን 7307 ላይ በመደወል የሰብአዊ መብቶች ጥሰት አቤቱታ ማቅረብ ወይም ጥቆማ መስጠት ይችላሉ።
...
Ensuring the rights and inclusion of landmine survivors requires a holistic, rights-based approach that integrates victim assistance into a broader disability and development framework
The Ethiopian Human Rights Commission (EHRC) Commissioner for Women, Children, Older Persons and Disability Rights Rigbe Gebrehawaria, who is also the Expert Member of the Working Group on the Rights of Older Persons and Persons with Disabilities in Africa took part in Zimbabwe’s National Stakeholder Dialogue on Humanitarian Demining and Mine Victim Assistance, held from February 18-20, 2025, in Harare.
🔗 https://ehrc.org/?p=31460
#Ethiopia🇪🇹 #HumanRightsForAll
በነጻ የስልክ መስመራችን 7307 ላይ በመደወል የሰብአዊ መብቶች ጥሰት አቤቱታ ማቅረብ ወይም ጥቆማ መስጠት ይችላሉ።
❤2👍1🔥1
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
የሳምንቱ #HumanRights Concept: የሀገር ውስጥ ተፈናቃዮች ዘላቂ መፍትሔ የማግኘት መብት
...
በአፍሪካ የሀገር ውስጥ ተፈናቃዮች ጥበቃ እና ድጋፍን አስመልክቶ የተደረገ የአፍሪካ ኅብረት ስምምነት (የካምፓላ ስምምነት)፣ አንቀጽ 11 (1)፣ (2)
ተዋዋይ ሀገራት በዘላቂነት እና ደኅንነትንና ክብርን በጠበቀ መልኩ በፈቃደኝነት ላይ የተመሠረተ የመመለስ፣ ከአካባቢ ማኅበረሰብ ጋር ተዋሕዶ የመኖር ወይም ወደ ሌላ ቦታ የማስፈር መፍትሔዎችን ለማመቻቸት አጥጋቢ የሆኑ ሁኔታዎች በማበረታታትና በመፍጠር ለመፈናቀል ችግር ዘላቂ መፍትሔዎችን ማፈላለግ አለባቸው፡፡
የሀገር ውስጥ ተፈናቃዮች የመመለስ፣ ከአካባቢ ማኅበረሰብ ጋር ተዋሕዶ የመኖር ወይም ወደ ሌላ ቦታ የመስፈር አማራጮችን ነጻ ሆነውና በመረጃ ተደግፈው መምረጥ እንዲችሉ ተዋዋይ ሀገራት በእነዚህና ሌሎች አማራጮች ዙሪያ ሊያማክሯቸው እና ዘላቂ መፍትሔዎችን በመፈለግ ሂደት መሳተፍ እንዲችሉ ሁኔታዎችን ሊያመቻቹላቸው ይገባል፡፡
🔗 https://ehrc.org/?p=31473
#Ethiopia🇪🇹 #KeepWordSafe #ጤናማቃላት
በነጻ የስልክ መስመራችን 7307 ላይ በመደወል የሰብአዊ መብቶች ጥሰት አቤቱታ ማቅረብ ወይም ጥቆማ መስጠት ይችላሉ።
...
በአፍሪካ የሀገር ውስጥ ተፈናቃዮች ጥበቃ እና ድጋፍን አስመልክቶ የተደረገ የአፍሪካ ኅብረት ስምምነት (የካምፓላ ስምምነት)፣ አንቀጽ 11 (1)፣ (2)
ተዋዋይ ሀገራት በዘላቂነት እና ደኅንነትንና ክብርን በጠበቀ መልኩ በፈቃደኝነት ላይ የተመሠረተ የመመለስ፣ ከአካባቢ ማኅበረሰብ ጋር ተዋሕዶ የመኖር ወይም ወደ ሌላ ቦታ የማስፈር መፍትሔዎችን ለማመቻቸት አጥጋቢ የሆኑ ሁኔታዎች በማበረታታትና በመፍጠር ለመፈናቀል ችግር ዘላቂ መፍትሔዎችን ማፈላለግ አለባቸው፡፡
የሀገር ውስጥ ተፈናቃዮች የመመለስ፣ ከአካባቢ ማኅበረሰብ ጋር ተዋሕዶ የመኖር ወይም ወደ ሌላ ቦታ የመስፈር አማራጮችን ነጻ ሆነውና በመረጃ ተደግፈው መምረጥ እንዲችሉ ተዋዋይ ሀገራት በእነዚህና ሌሎች አማራጮች ዙሪያ ሊያማክሯቸው እና ዘላቂ መፍትሔዎችን በመፈለግ ሂደት መሳተፍ እንዲችሉ ሁኔታዎችን ሊያመቻቹላቸው ይገባል፡፡
🔗 https://ehrc.org/?p=31473
#Ethiopia🇪🇹 #KeepWordSafe #ጤናማቃላት
በነጻ የስልክ መስመራችን 7307 ላይ በመደወል የሰብአዊ መብቶች ጥሰት አቤቱታ ማቅረብ ወይም ጥቆማ መስጠት ይችላሉ።
❤2👍1
#ቤኒሻንጉል፦ የታራሚዎች ሰብአዊ መብቶች አያያዝን አስመልክቶ ከባለድርሻ አካላት ጋር የተደረገ ውይይት
...
በማረሚያ ቤቶች ያሉ ችግሮችን በዘላቂነት ለመቅረፍና የታራሚዎችን የሰብአዊ መብቶች አያያዝ ለማሻሻል የሁሉንም ባለድርሻ አካላት ርብርብና የተቀናጀ ሥራ ይጠይቃል
የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) በ2016 ዓ.ም. የበጀት ዓመት አራተኛው ሩብ ዓመት እንዲሁም በ2017 ዓ.ም. በጀት ዓመት አንደኛው እና ሁለተኛው ሩብ ዓመት በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ባሉ ሁሉም ማረሚያ ቤቶች በታራሚዎች እና በቀጠሮ እስረኞች ሰብአዊ መብቶች አያያዝ ላይ ባከናወናቸው የክትትል ሥራዎች የተለዩ ግኝቶች ላይ የካቲት 14 ቀን 2017 ዓ.ም. ከባለድርሻ አካላት ጋር በባምባሲ ከተማ ውይይት አድርጓል።
በውይይቱም የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ማረሚያ ቤቶች ኮሚሽን ኮሚሽነር፣ የክልሉ ምክር ቤት የሰላም፣ ፍትሕና ዴሞክራሲ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ፤ የፍትሕ ቢሮ ተወካዮች፣ የአሶሳ፣ የካማሺ እና የመተከል ዞን ማረሚያ ቤቶች ኃላፊዎች እንዲሁም ሌሎች ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል።
🔗 https://ehrc.org/?p=31536
#Ethiopia🇪🇹 #HumanRightsForAll
በነጻ የስልክ መስመራችን 7307 ላይ በመደወል የሰብአዊ መብቶች ጥሰት አቤቱታ ማቅረብ ወይም ጥቆማ መስጠት ይችላሉ።
...
በማረሚያ ቤቶች ያሉ ችግሮችን በዘላቂነት ለመቅረፍና የታራሚዎችን የሰብአዊ መብቶች አያያዝ ለማሻሻል የሁሉንም ባለድርሻ አካላት ርብርብና የተቀናጀ ሥራ ይጠይቃል
የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) በ2016 ዓ.ም. የበጀት ዓመት አራተኛው ሩብ ዓመት እንዲሁም በ2017 ዓ.ም. በጀት ዓመት አንደኛው እና ሁለተኛው ሩብ ዓመት በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ባሉ ሁሉም ማረሚያ ቤቶች በታራሚዎች እና በቀጠሮ እስረኞች ሰብአዊ መብቶች አያያዝ ላይ ባከናወናቸው የክትትል ሥራዎች የተለዩ ግኝቶች ላይ የካቲት 14 ቀን 2017 ዓ.ም. ከባለድርሻ አካላት ጋር በባምባሲ ከተማ ውይይት አድርጓል።
በውይይቱም የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ማረሚያ ቤቶች ኮሚሽን ኮሚሽነር፣ የክልሉ ምክር ቤት የሰላም፣ ፍትሕና ዴሞክራሲ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ፤ የፍትሕ ቢሮ ተወካዮች፣ የአሶሳ፣ የካማሺ እና የመተከል ዞን ማረሚያ ቤቶች ኃላፊዎች እንዲሁም ሌሎች ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል።
🔗 https://ehrc.org/?p=31536
#Ethiopia🇪🇹 #HumanRightsForAll
በነጻ የስልክ መስመራችን 7307 ላይ በመደወል የሰብአዊ መብቶች ጥሰት አቤቱታ ማቅረብ ወይም ጥቆማ መስጠት ይችላሉ።
👍1
በሰብአዊ መብቶች ላይ ከሚሠሩ የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ጋር የተካሄደ ውይይት
...
ኢሰመኮ በሰብአዊ መብቶች ላይ ከሚሠሩ የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ጋር በትብብርና በቅንጅት መሥራቱን አጠናክሮ ይቀጥላል
የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ትኩረታቸውን በሰብአዊ መብቶች ላይ አድርገው ከሚንቀሳቀሱ ሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ጋር በአጋርነት የሚሠራበትን “የኢሰመኮ-ሲቪል ማኅበራት የትብብር መድረክ” አጠናክሮ ለማስቀጠል ያለመ ውይይት የካቲት 20 ቀን 2017 ዓ.ም. በዋና መሥሪያ ቤቱ አካሂዷል። በውይይት መድረኩ በሴቶች እና በሕፃናት፣ በአካል ጉዳተኞች እና በአረጋውያን፣ በነጻ የሕግ ድጋፍ አገልግሎት፣ በመገናኛ ብዙኃን እና በሌሎች የሰብአዊ መብቶች ጉዳዮች ላይ የሚሠሩ የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ኃላፊዎች እና ተወካዮች ተገኝተዋል።
መድረኩ የኢሰመኮ ዋና ኮሚሽነር ብርሃኑ አዴሎን ከድርጅቶቹ ተወካዮች እና ኃላፊዎች ጋር ያስተዋወቀ ሲሆን ኢሰመኮ ከሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ጋር ሊኖረው የሚገባውን የትብብር ሥራ በተደራጀ እና ሥርዓት ባለው መልኩ ለመምራት ባዘጋጀው የስትራቴጂክ አጋርነት መምሪያ (Strategic Partnership Guideline) መሠረት ሲሠራባቸው የቆዩ ዘርፎችን በተመለከተ ማብራሪያ ቀርቧል።
🔗 https://ehrc.org/?p=31555
#Ethiopia🇪🇹 #HumanRightsForAll
በነጻ የስልክ መስመራችን 7307 ላይ በመደወል የሰብአዊ መብቶች ጥሰት አቤቱታ ማቅረብ ወይም ጥቆማ መስጠት ይችላሉ።
...
ኢሰመኮ በሰብአዊ መብቶች ላይ ከሚሠሩ የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ጋር በትብብርና በቅንጅት መሥራቱን አጠናክሮ ይቀጥላል
የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ትኩረታቸውን በሰብአዊ መብቶች ላይ አድርገው ከሚንቀሳቀሱ ሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ጋር በአጋርነት የሚሠራበትን “የኢሰመኮ-ሲቪል ማኅበራት የትብብር መድረክ” አጠናክሮ ለማስቀጠል ያለመ ውይይት የካቲት 20 ቀን 2017 ዓ.ም. በዋና መሥሪያ ቤቱ አካሂዷል። በውይይት መድረኩ በሴቶች እና በሕፃናት፣ በአካል ጉዳተኞች እና በአረጋውያን፣ በነጻ የሕግ ድጋፍ አገልግሎት፣ በመገናኛ ብዙኃን እና በሌሎች የሰብአዊ መብቶች ጉዳዮች ላይ የሚሠሩ የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ኃላፊዎች እና ተወካዮች ተገኝተዋል።
መድረኩ የኢሰመኮ ዋና ኮሚሽነር ብርሃኑ አዴሎን ከድርጅቶቹ ተወካዮች እና ኃላፊዎች ጋር ያስተዋወቀ ሲሆን ኢሰመኮ ከሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ጋር ሊኖረው የሚገባውን የትብብር ሥራ በተደራጀ እና ሥርዓት ባለው መልኩ ለመምራት ባዘጋጀው የስትራቴጂክ አጋርነት መምሪያ (Strategic Partnership Guideline) መሠረት ሲሠራባቸው የቆዩ ዘርፎችን በተመለከተ ማብራሪያ ቀርቧል።
🔗 https://ehrc.org/?p=31555
#Ethiopia🇪🇹 #HumanRightsForAll
በነጻ የስልክ መስመራችን 7307 ላይ በመደወል የሰብአዊ መብቶች ጥሰት አቤቱታ ማቅረብ ወይም ጥቆማ መስጠት ይችላሉ።
👏1
የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ላይ የተጣለው እገዳ መነሳቱን በተመለከተ
...
ኢሰመኮ ከሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ባለሥልጣን እና ከታገዱት የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ጋር ተደጋጋሚ ውይይቶችን በማድረግ ለጉዳዩ መፍትሔ ለማስገኘት ሢሠራ ቆይቷል
የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ባለሥልጣን በኅዳር ወር 2017 ዓ.ም. የመብቶች እና ዴሞክራሲ ዕድገት ማዕከል፣ የሕግ ባለሙያዎች ለሰብአዊ መብቶች እና ስብስብ ለሰብአዊ መብቶች በኢትዮጵያ የተባሉ 3 በሰብአዊ መብቶች ዙሪያ የሚሠሩ የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ላይ ጥሎት የነበረውን እገዳ ካነሳ በኋላ በታኅሣሥ ወር 2017 ዓ.ም. የመብቶች እና ዴሞክራሲ ዕድገት ማዕከል እና የሕግ ባለሙያዎች ለሰብአዊ መብቶችን በድጋሚ እንዲሁም የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ጉባኤ እና የኢትዮጵያ የሰብአዊ መብቶች ተሟጋቾች ማእከልን ማገዱ ይታወሳል።
ኢሰመኮ ታኅሣሥ 18 ቀን 2017 ዓ.ም. ባወጣው ጋዜጣዊ መግለጫ በሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ላይ የሚተላለፉ እገዳዎች በሲቪል ምኅዳሩ እና በማኅበር የመደራጀት መብቶች ላይ አሉታዊ ተጽዕኖ እንዳይፈጥሩ ጥንቃቄ ሊደረግ እንደሚገባ አሳስቧል። በተጨማሪም ኢሰመኮ በድርጅቶቹ እገዳ ላይ ሰፊ የሰብአዊ መብቶች ምርመራ ያከናወነ ሲሆን የደረሰባቸውን ግኝቶች እና ምክረ ሐሳቦች ለሚመለከታቸው አካላት አጋርቷል።
🔗 https://ehrc.org/?p=31567
#Ethiopia🇪🇹 #HumanRightsForAll
በነጻ የስልክ መስመራችን 7307 ላይ በመደወል የሰብአዊ ጥሰት አቤቱታ ማቅረብ ወይም ጥቆማ መስጠት ይችላሉ።
...
ኢሰመኮ ከሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ባለሥልጣን እና ከታገዱት የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ጋር ተደጋጋሚ ውይይቶችን በማድረግ ለጉዳዩ መፍትሔ ለማስገኘት ሢሠራ ቆይቷል
የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ባለሥልጣን በኅዳር ወር 2017 ዓ.ም. የመብቶች እና ዴሞክራሲ ዕድገት ማዕከል፣ የሕግ ባለሙያዎች ለሰብአዊ መብቶች እና ስብስብ ለሰብአዊ መብቶች በኢትዮጵያ የተባሉ 3 በሰብአዊ መብቶች ዙሪያ የሚሠሩ የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ላይ ጥሎት የነበረውን እገዳ ካነሳ በኋላ በታኅሣሥ ወር 2017 ዓ.ም. የመብቶች እና ዴሞክራሲ ዕድገት ማዕከል እና የሕግ ባለሙያዎች ለሰብአዊ መብቶችን በድጋሚ እንዲሁም የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ጉባኤ እና የኢትዮጵያ የሰብአዊ መብቶች ተሟጋቾች ማእከልን ማገዱ ይታወሳል።
ኢሰመኮ ታኅሣሥ 18 ቀን 2017 ዓ.ም. ባወጣው ጋዜጣዊ መግለጫ በሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ላይ የሚተላለፉ እገዳዎች በሲቪል ምኅዳሩ እና በማኅበር የመደራጀት መብቶች ላይ አሉታዊ ተጽዕኖ እንዳይፈጥሩ ጥንቃቄ ሊደረግ እንደሚገባ አሳስቧል። በተጨማሪም ኢሰመኮ በድርጅቶቹ እገዳ ላይ ሰፊ የሰብአዊ መብቶች ምርመራ ያከናወነ ሲሆን የደረሰባቸውን ግኝቶች እና ምክረ ሐሳቦች ለሚመለከታቸው አካላት አጋርቷል።
🔗 https://ehrc.org/?p=31567
#Ethiopia🇪🇹 #HumanRightsForAll
በነጻ የስልክ መስመራችን 7307 ላይ በመደወል የሰብአዊ ጥሰት አቤቱታ ማቅረብ ወይም ጥቆማ መስጠት ይችላሉ።
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
የሳምንቱ #HumanRights Concept: የሴቶች የእኩልነት መብት
...
በሴቶች ላይ የሚደረግ ማንኛውንም አድሎአዊ ልዩነት ለማስወገድ የተደረገ ዓለም አቀፍ ስምምነት፣ አንቀጽ 3
አባል ሀገራት በሁሉም መስክ በተለይም በፖለቲካዊ፣ ማኅበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና ባህላዊ መስኮች የሴቶችን ሁለንተናዊ እድገት ለማረጋገጥና ከፍ ለማድረግ እንዲሁም ሴቶች ከወንዶች እኩል በሰብአዊ መብቶቻቸው እና መሠረታዊ ነጻነቶቻቸው መጠቀም እንዲችሉ ሕግ ማውጣትን ጨምሮ አግባብነት ያላቸውን እርምጃዎች ሁሉ መውሰድ አለባቸው።
የኢትዮጵያ ሕገ መንግሥት፣ አንቀጽ 35(3)
ሴቶች በበታችነትና በልዩነት በመታየታቸው የደረሰባቸውን የታሪክ ቅርስ ከግምት ውስጥ በማስገባት ይህ ቅርስ እንዲታረምላቸው፤ በተጨማሪ የድጋፍ እርምጃዎች ተጠቃሚ የመሆን መብት አላቸው። በዚህ በኩል የሚወሰዱት እርምጃዎች ዓላማ በፖለቲካዊ፣ በማኅበራዊና በኢኮኖሚያዊ መስኮች እንዲሁም በመንግሥት እና በግል ተቋሞች ውስጥ ሴቶች ከወንዶች ጋር በእኩልነት ተወዳዳሪና ተሳታፊ እንዲሆኑ ለማድረግ እንዲቻል ልዩ ትኩረት ለመስጠት ነው።
🔗 https://ehrc.org/?p=31576
#Ethiopia🇪🇹 #IWD2025 #ForAllWomenAndGirls #InternationalWomensDay #RingTheBellForGenderEquality #KeepWordSafe #ጤናማቃላት
በነጻ የስልክ መስመራችን 7307 ላይ በመደወል የሰብአዊ መብቶች ጥሰት አቤቱታ ማቅረብ ወይም ጥቆማ መስጠት ይችላሉ።
...
በሴቶች ላይ የሚደረግ ማንኛውንም አድሎአዊ ልዩነት ለማስወገድ የተደረገ ዓለም አቀፍ ስምምነት፣ አንቀጽ 3
አባል ሀገራት በሁሉም መስክ በተለይም በፖለቲካዊ፣ ማኅበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና ባህላዊ መስኮች የሴቶችን ሁለንተናዊ እድገት ለማረጋገጥና ከፍ ለማድረግ እንዲሁም ሴቶች ከወንዶች እኩል በሰብአዊ መብቶቻቸው እና መሠረታዊ ነጻነቶቻቸው መጠቀም እንዲችሉ ሕግ ማውጣትን ጨምሮ አግባብነት ያላቸውን እርምጃዎች ሁሉ መውሰድ አለባቸው።
የኢትዮጵያ ሕገ መንግሥት፣ አንቀጽ 35(3)
ሴቶች በበታችነትና በልዩነት በመታየታቸው የደረሰባቸውን የታሪክ ቅርስ ከግምት ውስጥ በማስገባት ይህ ቅርስ እንዲታረምላቸው፤ በተጨማሪ የድጋፍ እርምጃዎች ተጠቃሚ የመሆን መብት አላቸው። በዚህ በኩል የሚወሰዱት እርምጃዎች ዓላማ በፖለቲካዊ፣ በማኅበራዊና በኢኮኖሚያዊ መስኮች እንዲሁም በመንግሥት እና በግል ተቋሞች ውስጥ ሴቶች ከወንዶች ጋር በእኩልነት ተወዳዳሪና ተሳታፊ እንዲሆኑ ለማድረግ እንዲቻል ልዩ ትኩረት ለመስጠት ነው።
🔗 https://ehrc.org/?p=31576
#Ethiopia🇪🇹 #IWD2025 #ForAllWomenAndGirls #InternationalWomensDay #RingTheBellForGenderEquality #KeepWordSafe #ጤናማቃላት
በነጻ የስልክ መስመራችን 7307 ላይ በመደወል የሰብአዊ መብቶች ጥሰት አቤቱታ ማቅረብ ወይም ጥቆማ መስጠት ይችላሉ።
❤1👍1👎1
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
የሳምንቱ #HumanRights Concept: የሕፃናት በቂ የኑሮ ደረጃ የማግኘት መብት እና ትምህርት
...
የሕፃናት መብቶች ስምምነት፣ አንቀጽ 27(3)
ወላጆች እና ለሕፃኑ ኃላፊነት ያለባቸው ሌሎች አካላት የሕፃኑን ለእድገቱ ተስማሚ የሆነ በቂ የኑሮ ደረጃ የማግኘት መብት እንዲያሟሉ ለማገዝ፣ አባል ሀገራት እንደየሀገራዊ ሁኔታቸው እና ዐቅማቸው ተገቢውን እርምጃ ይወስዳሉ። አስፈላጊ በሆነ ጊዜም በምገባ፣ በአልባሳት እና በመጠለያ ረገድ ቁሳዊ ድጋፍ ያደርጋሉ፤ የድጋፍ መርኃ ግብሮችንም ያዘጋጃሉ።
የአፍሪካ የሕፃናት መብቶችና ደኅንነት ቻርተር፣ አንቀጽ 11(3)(መ)
አባል ሀገራት የሕፃናትን የመማር መብት ሙሉ በሙሉ እውን ለማድረግ ሁሉንም ተገቢ እርምጃዎች ይወስዳሉ። በተለይም በትምህርት ቤት ተገኝቶ ትምህርትን በቋሚነት መከታተልን ለማበረታታት እንዲሁም የተማሪዎችን ትምህርት የማቋረጥ ምጣኔ ለመቀነስ እርምጃዎችን መውሰድ አለባቸው።
🔗 https://ehrc.org/?p=31650
#Ethiopia🇪🇹 #ForEveryChild #KeepWordSafe #ጤናማቃላት
በነጻ የስልክ መስመራችን 7307 ላይ በመደወል የሰብአዊ መብቶች ጥሰት አቤቱታ ማቅረብ ወይም ጥቆማ መስጠት ይችላሉ።
...
የሕፃናት መብቶች ስምምነት፣ አንቀጽ 27(3)
ወላጆች እና ለሕፃኑ ኃላፊነት ያለባቸው ሌሎች አካላት የሕፃኑን ለእድገቱ ተስማሚ የሆነ በቂ የኑሮ ደረጃ የማግኘት መብት እንዲያሟሉ ለማገዝ፣ አባል ሀገራት እንደየሀገራዊ ሁኔታቸው እና ዐቅማቸው ተገቢውን እርምጃ ይወስዳሉ። አስፈላጊ በሆነ ጊዜም በምገባ፣ በአልባሳት እና በመጠለያ ረገድ ቁሳዊ ድጋፍ ያደርጋሉ፤ የድጋፍ መርኃ ግብሮችንም ያዘጋጃሉ።
የአፍሪካ የሕፃናት መብቶችና ደኅንነት ቻርተር፣ አንቀጽ 11(3)(መ)
አባል ሀገራት የሕፃናትን የመማር መብት ሙሉ በሙሉ እውን ለማድረግ ሁሉንም ተገቢ እርምጃዎች ይወስዳሉ። በተለይም በትምህርት ቤት ተገኝቶ ትምህርትን በቋሚነት መከታተልን ለማበረታታት እንዲሁም የተማሪዎችን ትምህርት የማቋረጥ ምጣኔ ለመቀነስ እርምጃዎችን መውሰድ አለባቸው።
🔗 https://ehrc.org/?p=31650
#Ethiopia🇪🇹 #ForEveryChild #KeepWordSafe #ጤናማቃላት
በነጻ የስልክ መስመራችን 7307 ላይ በመደወል የሰብአዊ መብቶች ጥሰት አቤቱታ ማቅረብ ወይም ጥቆማ መስጠት ይችላሉ።
❤2
#ትግራይ፦ ፖለቲካዊ አለመግባባቶች በሰብአዊ መብቶች ላይ ተጨማሪ ጉዳት እንዳያደርሱ አፋጣኝ ሰላማዊ መፍትሔዎችን መውሰድ ያስፈልጋል
...
ኢሰመኮ ከመደበኛ የክትትልና ምርመራ ሥራው ጎን ለጎን ባለድርሻ አካላትን በማነጋገር ችግሩ የሰብአዊ መብቶች ጥበቃን በሚያረጋግጥ መልኩ በውይይት እንዲፈታ ጥረት ያደርጋል
የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) በትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ውስጥ እና ውጪ በሚገኙ እና የህዝባዊ ወያኔ ሓርነት ትግራይ (ህወሓት) መሪዎች መሆናቸውን በሚገልጹ አካላት መካከል ከተከሰተው አለመግባባት ጋር ተያይዞ በክልሉ ለወራት የዘለቀውና ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ አሳሳቢነቱ እየጨመረ የመጣው ውጥረት በክልሉ አጠቃላይ ሰላም እና የሰብአዊ መብቶች ሁኔታ ላይ ያለውን አንድምታ እየተከታተለ ይገኛል።
በተለይም የክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዚደንት መጋቢት 1 ቀን 2017 ዓ.ም. በከፍተኛ ወታደራዊ አዛዦች ላይ ጊዜያዊ እገዳ ማስተላለፋቸውን እንዲሁም የህወሓት ተወካይ መሆናቸውን የሚገልጹት አካላት በተለያዩ የክልሉ አካባቢዎች የጊዜያዊ አስተዳደሩን የመንግሥት ተቋማት ለመቆጣጠር እንቅስቃሴ ማድረጋቸውን ተከትሎ ከክልሉ ነዋሪዎች ዕለታዊ እንቅስቃሴ ባሻገር በሰዎች ሰብአዊ መብቶች ላይ አደጋ እና ሥጋት ፈጥረዋል።
🔗 https://ehrc.org/?p=31769
#Ethiopia🇪🇹 #HumanRightsForAll
በነጻ የስልክ መስመራችን 7307 ላይ በመደወል የሰብአዊ መብቶች ጥሰት አቤቱታ ማቅረብ ወይም ጥቆማ መስጠት ይችላሉ።
...
ኢሰመኮ ከመደበኛ የክትትልና ምርመራ ሥራው ጎን ለጎን ባለድርሻ አካላትን በማነጋገር ችግሩ የሰብአዊ መብቶች ጥበቃን በሚያረጋግጥ መልኩ በውይይት እንዲፈታ ጥረት ያደርጋል
የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) በትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ውስጥ እና ውጪ በሚገኙ እና የህዝባዊ ወያኔ ሓርነት ትግራይ (ህወሓት) መሪዎች መሆናቸውን በሚገልጹ አካላት መካከል ከተከሰተው አለመግባባት ጋር ተያይዞ በክልሉ ለወራት የዘለቀውና ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ አሳሳቢነቱ እየጨመረ የመጣው ውጥረት በክልሉ አጠቃላይ ሰላም እና የሰብአዊ መብቶች ሁኔታ ላይ ያለውን አንድምታ እየተከታተለ ይገኛል።
በተለይም የክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዚደንት መጋቢት 1 ቀን 2017 ዓ.ም. በከፍተኛ ወታደራዊ አዛዦች ላይ ጊዜያዊ እገዳ ማስተላለፋቸውን እንዲሁም የህወሓት ተወካይ መሆናቸውን የሚገልጹት አካላት በተለያዩ የክልሉ አካባቢዎች የጊዜያዊ አስተዳደሩን የመንግሥት ተቋማት ለመቆጣጠር እንቅስቃሴ ማድረጋቸውን ተከትሎ ከክልሉ ነዋሪዎች ዕለታዊ እንቅስቃሴ ባሻገር በሰዎች ሰብአዊ መብቶች ላይ አደጋ እና ሥጋት ፈጥረዋል።
🔗 https://ehrc.org/?p=31769
#Ethiopia🇪🇹 #HumanRightsForAll
በነጻ የስልክ መስመራችን 7307 ላይ በመደወል የሰብአዊ መብቶች ጥሰት አቤቱታ ማቅረብ ወይም ጥቆማ መስጠት ይችላሉ።
❤1
ለ5ኛው ሀገር አቀፍ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች የሰብአዊ መብቶች ምስለ ችሎት ውድድር ተሳታፊዎች የተሰጠ የማስጀመሪያ ስልጠና
...
ውድድሩ ተማሪዎች ስለ ሰብአዊ መብቶች ዕውቀትና ክህሎታቸውን እንዲያዳብሩ የሚረዳ ነው
የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ለ5ኛ ጊዜ ለሚያካሂደው ሀገር አቀፍ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች የሰብአዊ መብቶች ምስለ ችሎት ውድድር የማስጀመሪያ ስልጠና የካቲት 22 ቀን 2017 ዓ.ም. በ12 ክልሎች እና በ2 የከተማ አስተዳደሮች ሰጥቷል፡፡ የስልጠናው ዓላማ የውድድሩን አጠቃላይ ገጽታ ማስገንዘብ እና በዚህ ዓመት ለውድድር የተመረጠውን የሰብአዊ መብቶች ርዕሰ ጉዳይ ለተወዳዳሪ ተማሪዎች እና አሰልጣኝ መምህራን ማስተዋወቅ ነው።
በዚህ ስልጠና ከአዲስ አበባ፣ አዳማ፣ ደሴ፣ ዲላ፣ ድሬዳዋ፣ ግልገል በለስ፣ ሐረር፣ ጅግጅጋ፣ ለኩ፣ መቐለ፣ ሜጢ፣ ሚዛን፣ ሰመራ እና ወልቂጤ ከተሞች ከ105 የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች የተወከሉ ተወዳዳሪ ተማሪዎች፣ የክልል ትምህርት ቢሮ አስተባባሪዎች፣ አሰልጣኝ መምህራን፣ ርዕሳነ መምህራን እና የተማሪ ወላጆች ተሳትፈዋል።
🔗 https://ehrc.org/?p=31799
#Ethiopia🇪🇹 #HumanRightsForAll
በነጻ የስልክ መስመራችን 7307 ላይ በመደወል የሰብአዊ መብቶች ጥሰት አቤቱታ ማቅረብ ወይም ጥቆማ መስጠት ይችላሉ።
...
ውድድሩ ተማሪዎች ስለ ሰብአዊ መብቶች ዕውቀትና ክህሎታቸውን እንዲያዳብሩ የሚረዳ ነው
የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ለ5ኛ ጊዜ ለሚያካሂደው ሀገር አቀፍ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች የሰብአዊ መብቶች ምስለ ችሎት ውድድር የማስጀመሪያ ስልጠና የካቲት 22 ቀን 2017 ዓ.ም. በ12 ክልሎች እና በ2 የከተማ አስተዳደሮች ሰጥቷል፡፡ የስልጠናው ዓላማ የውድድሩን አጠቃላይ ገጽታ ማስገንዘብ እና በዚህ ዓመት ለውድድር የተመረጠውን የሰብአዊ መብቶች ርዕሰ ጉዳይ ለተወዳዳሪ ተማሪዎች እና አሰልጣኝ መምህራን ማስተዋወቅ ነው።
በዚህ ስልጠና ከአዲስ አበባ፣ አዳማ፣ ደሴ፣ ዲላ፣ ድሬዳዋ፣ ግልገል በለስ፣ ሐረር፣ ጅግጅጋ፣ ለኩ፣ መቐለ፣ ሜጢ፣ ሚዛን፣ ሰመራ እና ወልቂጤ ከተሞች ከ105 የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች የተወከሉ ተወዳዳሪ ተማሪዎች፣ የክልል ትምህርት ቢሮ አስተባባሪዎች፣ አሰልጣኝ መምህራን፣ ርዕሳነ መምህራን እና የተማሪ ወላጆች ተሳትፈዋል።
🔗 https://ehrc.org/?p=31799
#Ethiopia🇪🇹 #HumanRightsForAll
በነጻ የስልክ መስመራችን 7307 ላይ በመደወል የሰብአዊ መብቶች ጥሰት አቤቱታ ማቅረብ ወይም ጥቆማ መስጠት ይችላሉ።
👍3
በኢሰመኮ የቅብብሎሽና ቅንጅት ማእቀፍ ዳሰሳ ጥናት ላይ የተደረገ ውይይት
...
የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) የሰብአዊ መብቶች ጥሰት ለደረሰባቸው ተጎጂዎች ተጓዳኝ ድጋፍ ለመስጠት እስካሁን እየተገበረ በሚገኘው የቅብብሎሽና ቅንጅት ማእቀፍ ላይ የተሠራውን የዳሰሳ ጥናት መነሻ በማድረግ ከባለድርሻ አካላት ጋር የካቲት 28 ቀን 2017 ዓ.ም. ውይይት አካሂዷል። የውይይቱ ዓላማ በሥራ ላይ ያለውን የቅብብሎሽ አሠራር በተሻለ መልኩ ለማደራጀት እና ለማጠናከር በዳሰሳ ጥናቱ ግኝቶች ላይ እንዲሁም ኢሰመኮ ወደፊት ለሚተገብረው መደበኛ የቅብብሎሽ ሥርዓት ከባለድርሻ አካላት ግብአት ማሰባሰብ ነው።
በውይይቱ ለተጎጂዎች ድጋፍ የሚሰጡ ከ35 በላይ የሚሆኑ መንግሥታዊና መንግሥታዊ ያልሆኑ አካላትን ጨምሮ በሴቶች፣ በሕፃናት፣ በአካል ጉዳተኞች እና በሌሎች ዘርፎች ላይ የሚንቀሳቀሱ ተቋማት ተሳትፈዋል።
በውይይት መድረኩም በዳሰሳ ጥናቱ የተለዩ ቁልፍ ግኝቶች የቀረቡ ሲሆን ኢሰመኮ ተጎጂዎችን ከሕግ፣ ከሥነ ልቦና፣ ከመጠለያ፣ ከማኅበራዊ ወዘተ. ድጋፍ ሰጪ ድርጅቶች ጋር ማገናኘት መቻሉ፤ ተጎጂዎች በተቻለ መጠን ለዳግም ጥቃት ተጋላጭ እንዳይሆኑ፤ ሰብአዊ መብቶች እንዲጠበቁ ከማድረግ አንጻር መልካም ሥራ ማከናወን መቻሉ ተጠቃሽ ናቸው። እንዲሁም የሰብአዊ መብቶች ጥሰቶችን በተቀናጀ እና በፍጥነት ምላሽ ለመስጠት ኢሰመኮ ከመቼውም ጊዜ በላይ የተጠናከረ መደበኛ የቅብብሎሽ ሥርዓት (Referral System) መዘርጋቱ በይበልጥ አስፈላጊ መሆኑ ተመላክቷል።
🔗 https://ehrc.org/?p=31843
#Ethiopia🇪🇹 #HumanRightsForAll
በነጻ የስልክ መስመራችን 7307 ላይ በመደወል የሰብአዊ መብቶች ጥሰት አቤቱታ ማቅረብ ወይም ጥቆማ መስጠት ይችላሉ።
...
የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) የሰብአዊ መብቶች ጥሰት ለደረሰባቸው ተጎጂዎች ተጓዳኝ ድጋፍ ለመስጠት እስካሁን እየተገበረ በሚገኘው የቅብብሎሽና ቅንጅት ማእቀፍ ላይ የተሠራውን የዳሰሳ ጥናት መነሻ በማድረግ ከባለድርሻ አካላት ጋር የካቲት 28 ቀን 2017 ዓ.ም. ውይይት አካሂዷል። የውይይቱ ዓላማ በሥራ ላይ ያለውን የቅብብሎሽ አሠራር በተሻለ መልኩ ለማደራጀት እና ለማጠናከር በዳሰሳ ጥናቱ ግኝቶች ላይ እንዲሁም ኢሰመኮ ወደፊት ለሚተገብረው መደበኛ የቅብብሎሽ ሥርዓት ከባለድርሻ አካላት ግብአት ማሰባሰብ ነው።
በውይይቱ ለተጎጂዎች ድጋፍ የሚሰጡ ከ35 በላይ የሚሆኑ መንግሥታዊና መንግሥታዊ ያልሆኑ አካላትን ጨምሮ በሴቶች፣ በሕፃናት፣ በአካል ጉዳተኞች እና በሌሎች ዘርፎች ላይ የሚንቀሳቀሱ ተቋማት ተሳትፈዋል።
በውይይት መድረኩም በዳሰሳ ጥናቱ የተለዩ ቁልፍ ግኝቶች የቀረቡ ሲሆን ኢሰመኮ ተጎጂዎችን ከሕግ፣ ከሥነ ልቦና፣ ከመጠለያ፣ ከማኅበራዊ ወዘተ. ድጋፍ ሰጪ ድርጅቶች ጋር ማገናኘት መቻሉ፤ ተጎጂዎች በተቻለ መጠን ለዳግም ጥቃት ተጋላጭ እንዳይሆኑ፤ ሰብአዊ መብቶች እንዲጠበቁ ከማድረግ አንጻር መልካም ሥራ ማከናወን መቻሉ ተጠቃሽ ናቸው። እንዲሁም የሰብአዊ መብቶች ጥሰቶችን በተቀናጀ እና በፍጥነት ምላሽ ለመስጠት ኢሰመኮ ከመቼውም ጊዜ በላይ የተጠናከረ መደበኛ የቅብብሎሽ ሥርዓት (Referral System) መዘርጋቱ በይበልጥ አስፈላጊ መሆኑ ተመላክቷል።
🔗 https://ehrc.org/?p=31843
#Ethiopia🇪🇹 #HumanRightsForAll
በነጻ የስልክ መስመራችን 7307 ላይ በመደወል የሰብአዊ መብቶች ጥሰት አቤቱታ ማቅረብ ወይም ጥቆማ መስጠት ይችላሉ።
👍3
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
የሳምንቱ #HumanRights Concept: ከአድሎአዊ የዘር ልዩነቶች የመጠበቅ መብት
...
ሁሉ አቀፍ የሰብአዊ መብቶች መግለጫ፣ አንቀጽ 1
ሁሉም የሰው ልጆች እኩል ክብርና መብቶች ይዘው ነጻ ሆነው ተፈጥረዋል።
ሁሉንም ዐይነት አድሎአዊ የዘር ልዩነቶች ለማስወገድ የተደረገ ዓለም አቀፍ ስምምነት፣ አንቀጽ 1 (1) እና 5
“አድሎአዊ የዘር ልዩነት” ማለት በፖለቲካ፣ በኢኮኖሚ፣ በማኅበራዊ፣ በባህላዊ ወይም በሌላ በማንኛውም ሕዝባዊ የሕይወት መስክ የሰብአዊ መብቶችን እና የመሠረታዊ ነጻነቶችን እኩል ዕውቅና፣ ተጠቃሚነት ወይም ትግበራ ዋጋ የማሳጣት ወይም የመጉዳት ዐላማ ወይም ውጤት ያለው በዘር፣ በቀለም፣ በትውልድ ወይም በብሔር ወይም በዘር ሐረግ ላይ የተመሠረተ ልዩነት ማድረግ፣ ማግለል፣ መገደብ ወይም ማበላለጥ ነው።
አባል ሀገራት ሁሉንም ዐይነት የዘር አድልዎ የመከልከል እና የማስወገድ እንዲሁም ማንኛውም ሰው በዘር፣ በቀለም፣ በብሔር ወይም በዘር ሐረግ ልዩነት ሳይደረግበት በሕግ ፊት እኩል የመሆን መብቱን የማረጋገጥ ግዴታ አለባቸው።
🔗 https://ehrc.org/?p=31825
#Ethiopia🇪🇹 #KeepWordSafe #ጤናማቃላት
በነጻ የስልክ መስመራችን 7307 ላይ በመደወል የሰብአዊ መብቶች ጥሰት አቤቱታ ማቅረብ ወይም ጥቆማ መስጠት ይችላሉ።
...
ሁሉ አቀፍ የሰብአዊ መብቶች መግለጫ፣ አንቀጽ 1
ሁሉም የሰው ልጆች እኩል ክብርና መብቶች ይዘው ነጻ ሆነው ተፈጥረዋል።
ሁሉንም ዐይነት አድሎአዊ የዘር ልዩነቶች ለማስወገድ የተደረገ ዓለም አቀፍ ስምምነት፣ አንቀጽ 1 (1) እና 5
“አድሎአዊ የዘር ልዩነት” ማለት በፖለቲካ፣ በኢኮኖሚ፣ በማኅበራዊ፣ በባህላዊ ወይም በሌላ በማንኛውም ሕዝባዊ የሕይወት መስክ የሰብአዊ መብቶችን እና የመሠረታዊ ነጻነቶችን እኩል ዕውቅና፣ ተጠቃሚነት ወይም ትግበራ ዋጋ የማሳጣት ወይም የመጉዳት ዐላማ ወይም ውጤት ያለው በዘር፣ በቀለም፣ በትውልድ ወይም በብሔር ወይም በዘር ሐረግ ላይ የተመሠረተ ልዩነት ማድረግ፣ ማግለል፣ መገደብ ወይም ማበላለጥ ነው።
አባል ሀገራት ሁሉንም ዐይነት የዘር አድልዎ የመከልከል እና የማስወገድ እንዲሁም ማንኛውም ሰው በዘር፣ በቀለም፣ በብሔር ወይም በዘር ሐረግ ልዩነት ሳይደረግበት በሕግ ፊት እኩል የመሆን መብቱን የማረጋገጥ ግዴታ አለባቸው።
🔗 https://ehrc.org/?p=31825
#Ethiopia🇪🇹 #KeepWordSafe #ጤናማቃላት
በነጻ የስልክ መስመራችን 7307 ላይ በመደወል የሰብአዊ መብቶች ጥሰት አቤቱታ ማቅረብ ወይም ጥቆማ መስጠት ይችላሉ።
60 Years of the International Convention on the Elimination of All Forms of Racial Discrimination (ICERD)
...
What is ICERD? What are the key features of ICERD? What is CERD/the Committee? Mechanisms used by CERD/the Committee to monitor state actions and advise. Is Ethiopia party to ICERD? How can human rights actors engage with ICERD?
The International Convention on the Elimination of All Forms of Racial Discrimination (ICERD) is one of the earliest United Nations (UN) treaties aimed at eradicating racial discrimination globally. ICERD emerged in the 1960s amid global struggles against colonialism, apartheid, and systemic racism, and was adopted on 21 December 1965 by the UN General Assembly, entering into force on 4 January 1969. As of today, 182 States are parties to the Convention, reflecting its wide acceptance as a cornerstone of international human rights law.
🔗 https://ehrc.org/?p=31884
#Ethiopia #HumanRightsForAll
በነጻ የስልክ መስመራችን 7307 ላይ በመደወል የሰብአዊ መብቶች ጥሰት አቤቱታ ማቅረብ ወይም ጥቆማ መስጠት ይችላሉ።
...
What is ICERD? What are the key features of ICERD? What is CERD/the Committee? Mechanisms used by CERD/the Committee to monitor state actions and advise. Is Ethiopia party to ICERD? How can human rights actors engage with ICERD?
The International Convention on the Elimination of All Forms of Racial Discrimination (ICERD) is one of the earliest United Nations (UN) treaties aimed at eradicating racial discrimination globally. ICERD emerged in the 1960s amid global struggles against colonialism, apartheid, and systemic racism, and was adopted on 21 December 1965 by the UN General Assembly, entering into force on 4 January 1969. As of today, 182 States are parties to the Convention, reflecting its wide acceptance as a cornerstone of international human rights law.
🔗 https://ehrc.org/?p=31884
#Ethiopia #HumanRightsForAll
በነጻ የስልክ መስመራችን 7307 ላይ በመደወል የሰብአዊ መብቶች ጥሰት አቤቱታ ማቅረብ ወይም ጥቆማ መስጠት ይችላሉ።
የውሃ መብት
...
ውሃ ለሕይወት እና ጤና መሠረታዊ የሆነ ውስን የተፈጥሮ ሀብት ከመሆኑም በተጨማሪ የሰው ልጅ ሰብአዊ ክብሩ ተጠብቆ እንዲኖር እንዲሁም ሌሎች ሰብአዊ መብቶቹን እንዲጠቀም ለማስቻል መሠረታዊ ቅድመ ሁኔታ ሲሆን በተለያዩ የሰብአዊ መብቶች ሰነዶችም ጥበቃ የሚደረግለት መብት ነው። የውሃ ሀብት ጥበቃና ልማት ግንዛቤን ለማስጨበጥ እና ተጨባጭ ተግባራትን ለማበረታታት በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት (ተ.መ.ድ.) ጠቅላላ ጉባኤ ውሳኔ መሠረት እ.ኤ.አ. ከ1993 ጀምሮ በየዓመቱ መጋቢት 13 የዓለም የውሃ ቀን ሆኖ ይከበራል። ይህም ማብራሪያ ቀኑን በማስመልከት የውሃ መብት ምንነት፣ ጥበቃ፣ ይዘት እና የመንግሥታት ግዴታዎችን አስመልክቶ የማኅበረሰቡን ግንዛቤ ለማሳደግ የተዘጋጀ ነው።
የውሃ መብት ምንድን ነው?
የውሃ መብት ሁሉም ሰው ለግሉ እና ለቤት ውስጥ አገልግሎት በቂ የሆነ፣ ደኅንነቱ የተጠበቀ፣ ተቀባይነት ያለው፣ በአካል ተደራሽ እና በዋጋ ተመጣጣኝ/affordable የሆነ ውሃ የማግኘት መብት ሲሆን በውስጡ ሌሎች ነጻነቶችን/freedoms እና መብቶችን/entitlments እንደሚይዝ የኢኮኖሚያዊ፣ ማኅበራዊ እና የባህል መብቶች ኮሚቴ የውሃ መብትን አስመልክቶ የሰጠው አጠቃላይ ትንታኔ ቁጥር 15 ያስረዳል።
🔗 https://ehrc.org/?p=31898
#Ethiopia🇪🇹 #WorldWaterDay #HumanRightsForAll
በነጻ የስልክ መስመራችን 7307 ላይ በመደወል የሰብአዊ መብቶች ጥሰት አቤቱታ ማቅረብ ወይም ጥቆማ መስጠት ይችላሉ።
...
ውሃ ለሕይወት እና ጤና መሠረታዊ የሆነ ውስን የተፈጥሮ ሀብት ከመሆኑም በተጨማሪ የሰው ልጅ ሰብአዊ ክብሩ ተጠብቆ እንዲኖር እንዲሁም ሌሎች ሰብአዊ መብቶቹን እንዲጠቀም ለማስቻል መሠረታዊ ቅድመ ሁኔታ ሲሆን በተለያዩ የሰብአዊ መብቶች ሰነዶችም ጥበቃ የሚደረግለት መብት ነው። የውሃ ሀብት ጥበቃና ልማት ግንዛቤን ለማስጨበጥ እና ተጨባጭ ተግባራትን ለማበረታታት በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት (ተ.መ.ድ.) ጠቅላላ ጉባኤ ውሳኔ መሠረት እ.ኤ.አ. ከ1993 ጀምሮ በየዓመቱ መጋቢት 13 የዓለም የውሃ ቀን ሆኖ ይከበራል። ይህም ማብራሪያ ቀኑን በማስመልከት የውሃ መብት ምንነት፣ ጥበቃ፣ ይዘት እና የመንግሥታት ግዴታዎችን አስመልክቶ የማኅበረሰቡን ግንዛቤ ለማሳደግ የተዘጋጀ ነው።
የውሃ መብት ምንድን ነው?
የውሃ መብት ሁሉም ሰው ለግሉ እና ለቤት ውስጥ አገልግሎት በቂ የሆነ፣ ደኅንነቱ የተጠበቀ፣ ተቀባይነት ያለው፣ በአካል ተደራሽ እና በዋጋ ተመጣጣኝ/affordable የሆነ ውሃ የማግኘት መብት ሲሆን በውስጡ ሌሎች ነጻነቶችን/freedoms እና መብቶችን/entitlments እንደሚይዝ የኢኮኖሚያዊ፣ ማኅበራዊ እና የባህል መብቶች ኮሚቴ የውሃ መብትን አስመልክቶ የሰጠው አጠቃላይ ትንታኔ ቁጥር 15 ያስረዳል።
🔗 https://ehrc.org/?p=31898
#Ethiopia🇪🇹 #WorldWaterDay #HumanRightsForAll
በነጻ የስልክ መስመራችን 7307 ላይ በመደወል የሰብአዊ መብቶች ጥሰት አቤቱታ ማቅረብ ወይም ጥቆማ መስጠት ይችላሉ።
👍3
International Day for the Right to Truth concerning Gross Human Rights Violations and for the Dignity of Victims
...
On this International Day, EHRC emphasizes the importance of victims’ right to truth
On this International Day for the Right to Truth Concerning Gross Human Rights Violations and for the Dignity of Victims (24 March), the Ethiopian Human Rights Commission (EHRC) reiterates the importance of victims’ right to the truth. Victims include persons who individually or collectively suffered physical or mental harm, substantial impairment of their fundamental rights, through acts or omissions that constitute gross violations of international human rights law, or serious violations of international humanitarian law.
🔗 https://ehrc.org/?p=31939
#Ethiopia🇪🇹 #StandUp4HumanRights #TruthAndDignity #JusticeForAll #RightToTheTruth #HumanRightsForAll
በነጻ የስልክ መስመራችን 7307 ላይ በመደወል የሰብአዊ መብቶች ጥሰት አቤቱታ ማቅረብ ወይም ጥቆማ መስጠት ይችላሉ።
...
On this International Day, EHRC emphasizes the importance of victims’ right to truth
On this International Day for the Right to Truth Concerning Gross Human Rights Violations and for the Dignity of Victims (24 March), the Ethiopian Human Rights Commission (EHRC) reiterates the importance of victims’ right to the truth. Victims include persons who individually or collectively suffered physical or mental harm, substantial impairment of their fundamental rights, through acts or omissions that constitute gross violations of international human rights law, or serious violations of international humanitarian law.
🔗 https://ehrc.org/?p=31939
#Ethiopia🇪🇹 #StandUp4HumanRights #TruthAndDignity #JusticeForAll #RightToTheTruth #HumanRightsForAll
በነጻ የስልክ መስመራችን 7307 ላይ በመደወል የሰብአዊ መብቶች ጥሰት አቤቱታ ማቅረብ ወይም ጥቆማ መስጠት ይችላሉ።
❤1
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
የሳምንቱ #HumanRights Concept: የመደራጀት መብት
...
የሲቪል እና ፖለቲካ መብቶች ዓለም አቀፍ ቃልኪዳን፣ አንቀጽ 22 (1) (2)
ማንኛውም ሰው ከሌሎች ጋር በማኅበር የመደራጀት ነጻነት አለው፡፡ ይህም ጥቅሞቹን ለማስጠበቅ የሠራተኛ ማኅበራትን የማቋቋም እና አባል የመሆን መብትን ይጨምራል።
በሕግ ከተደነገገው እና በዴሞክራሲያዊ ማኅብረሰብ ውስጥ ለብሔራዊ ደኅንነት፣ ለሕዝብ ሰላምና ጸጥታ ጥቅም ወይም የሕዝብን ጤናና ሥነ ምግባር ወይም የሌሎችን መብቶችና ነጻነቶች ለመጠበቅ አስፈላጊ ከሆነው በቀር በዚህ መብት አጠቃቀም ላይ ምንም ዐይነት ገደብ አይደረግበትም፡፡
🔗 https://ehrc.org/?p=31952
#Ethiopia🇪🇹 #KeepWordSafe #ጤናማቃላት
በነጻ የስልክ መስመራችን 7307 ላይ በመደወል የሰብአዊ መብቶች ጥሰት አቤቱታ ማቅረብ ወይም ጥቆማ መስጠት ይችላሉ።
...
የሲቪል እና ፖለቲካ መብቶች ዓለም አቀፍ ቃልኪዳን፣ አንቀጽ 22 (1) (2)
ማንኛውም ሰው ከሌሎች ጋር በማኅበር የመደራጀት ነጻነት አለው፡፡ ይህም ጥቅሞቹን ለማስጠበቅ የሠራተኛ ማኅበራትን የማቋቋም እና አባል የመሆን መብትን ይጨምራል።
በሕግ ከተደነገገው እና በዴሞክራሲያዊ ማኅብረሰብ ውስጥ ለብሔራዊ ደኅንነት፣ ለሕዝብ ሰላምና ጸጥታ ጥቅም ወይም የሕዝብን ጤናና ሥነ ምግባር ወይም የሌሎችን መብቶችና ነጻነቶች ለመጠበቅ አስፈላጊ ከሆነው በቀር በዚህ መብት አጠቃቀም ላይ ምንም ዐይነት ገደብ አይደረግበትም፡፡
🔗 https://ehrc.org/?p=31952
#Ethiopia🇪🇹 #KeepWordSafe #ጤናማቃላት
በነጻ የስልክ መስመራችን 7307 ላይ በመደወል የሰብአዊ መብቶች ጥሰት አቤቱታ ማቅረብ ወይም ጥቆማ መስጠት ይችላሉ።
❤4
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
የሳምንቱ #HumanRights Concept: የአካል ጉዳተኛ ሴቶች ጥበቃ
...
ዓለም አቀፍ የአካል ጉዳተኞች መብቶች ስምምነት፣ አንቀጽ 6 (1) እና (2)
አባል ሀገራት አካል ጉዳተኛ ሴቶችና ሴት ልጆች ለተደራራቢ አድልዎ የተዳረጉ መሆናቸውን ዕውቅና ይሰጣሉ፤ ይህንንም ከግንዛቤ በማስገባት በሁሉም ሰብአዊ መብቶችና መሠረታዊ ነጻነቶች ሙሉ እና እኩል ተጠቃሚ መሆናቸውን ለማረጋገጥ እርምጃዎችን ይወስዳሉ።
አካል ጉዳተኛ ሴቶች በዚህ ስምምነት በተደነገጉት ሰብአዊ መብቶችና መሠረታዊ ነጻነቶች ተጠቃሚ መሆናቸውን ለማረጋገጥ፣ አባል ሀገራት የሴቶችን የተሟላ ልማትና ዕድገት ዕውን ለማድረግ እና ለማብቃት የሚያስችሉ ተገቢ እርምጃዎችን ሁሉ ይወስዳሉ።
🔗 https://ehrc.org/?p=32014
#Ethiopia🇪🇹 #DisabilityInclusion #DisabilityRights #CommitToChange #GDS2025 #KeepWordSafe #ጤናማቃላት
በነጻ የስልክ መስመራችን 7307 ላይ በመደወል የሰብአዊ መብቶች ጥሰት አቤቱታ ማቅረብ ወይም ጥቆማ መስጠት ይችላሉ።
...
ዓለም አቀፍ የአካል ጉዳተኞች መብቶች ስምምነት፣ አንቀጽ 6 (1) እና (2)
አባል ሀገራት አካል ጉዳተኛ ሴቶችና ሴት ልጆች ለተደራራቢ አድልዎ የተዳረጉ መሆናቸውን ዕውቅና ይሰጣሉ፤ ይህንንም ከግንዛቤ በማስገባት በሁሉም ሰብአዊ መብቶችና መሠረታዊ ነጻነቶች ሙሉ እና እኩል ተጠቃሚ መሆናቸውን ለማረጋገጥ እርምጃዎችን ይወስዳሉ።
አካል ጉዳተኛ ሴቶች በዚህ ስምምነት በተደነገጉት ሰብአዊ መብቶችና መሠረታዊ ነጻነቶች ተጠቃሚ መሆናቸውን ለማረጋገጥ፣ አባል ሀገራት የሴቶችን የተሟላ ልማትና ዕድገት ዕውን ለማድረግ እና ለማብቃት የሚያስችሉ ተገቢ እርምጃዎችን ሁሉ ይወስዳሉ።
🔗 https://ehrc.org/?p=32014
#Ethiopia🇪🇹 #DisabilityInclusion #DisabilityRights #CommitToChange #GDS2025 #KeepWordSafe #ጤናማቃላት
በነጻ የስልክ መስመራችን 7307 ላይ በመደወል የሰብአዊ መብቶች ጥሰት አቤቱታ ማቅረብ ወይም ጥቆማ መስጠት ይችላሉ።
👍2
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
የሳምንቱ #HumanRights Concept: የጤና አገልግሎት ተደራሽነት
...
የኢኮኖሚ፣ የማኅበራዊ እና የባህላዊ መብቶች ዓለም አቀፍ ቃልኪዳን፣ አንቀጽ 12 (1) እና (2)(መ)
አባል ሀገራት የማንኛውንም ሰው ሊደረስበት የሚችለውን ከፍተኛውን የአካል እና የአእምሮ ጤና ደረጃ የማግኘት መብት ዕውቅና ይሰጣሉ።
የዚህን መብት ሙሉ ተፈጻሚነት ለማረጋገጥ አባል ሀገራት የሚወስዷቸው እርምጃዎች በሕመም ጊዜ ሁሉንም የሕክምና አገልግሎት እና ክትትል አቅርቦት መኖሩን የሚያረጋግጡ ሁኔታዎችን መፍጠርን ይጨምራል።
የኢትዮጵያ ሕገ መንግሥት፣ አንቀጽ 41(4)
መንግሥት የጤና፣ የትምህርትና ሌሎች የማኅበራዊ አገልግሎቶችን ለሕዝብ ለማቅረብ በየጊዜው እየጨመረ የሚሄድ ሀብት ይመድባል።
🔗 https://ehrc.org/?p=32142
#Ethiopia🇪🇹 #AccessToHealth #KeepWordSafe #ጤናማቃላት
በነጻ የስልክ መስመራችን 7307 ላይ በመደወል የሰብአዊ መብቶች ጥሰት አቤቱታ ማቅረብ ወይም ጥቆማ መስጠት ይችላሉ።
...
የኢኮኖሚ፣ የማኅበራዊ እና የባህላዊ መብቶች ዓለም አቀፍ ቃልኪዳን፣ አንቀጽ 12 (1) እና (2)(መ)
አባል ሀገራት የማንኛውንም ሰው ሊደረስበት የሚችለውን ከፍተኛውን የአካል እና የአእምሮ ጤና ደረጃ የማግኘት መብት ዕውቅና ይሰጣሉ።
የዚህን መብት ሙሉ ተፈጻሚነት ለማረጋገጥ አባል ሀገራት የሚወስዷቸው እርምጃዎች በሕመም ጊዜ ሁሉንም የሕክምና አገልግሎት እና ክትትል አቅርቦት መኖሩን የሚያረጋግጡ ሁኔታዎችን መፍጠርን ይጨምራል።
የኢትዮጵያ ሕገ መንግሥት፣ አንቀጽ 41(4)
መንግሥት የጤና፣ የትምህርትና ሌሎች የማኅበራዊ አገልግሎቶችን ለሕዝብ ለማቅረብ በየጊዜው እየጨመረ የሚሄድ ሀብት ይመድባል።
🔗 https://ehrc.org/?p=32142
#Ethiopia🇪🇹 #AccessToHealth #KeepWordSafe #ጤናማቃላት
በነጻ የስልክ መስመራችን 7307 ላይ በመደወል የሰብአዊ መብቶች ጥሰት አቤቱታ ማቅረብ ወይም ጥቆማ መስጠት ይችላሉ።
#ትግራይ፦ ወደ ቀድሞ የመኖሪያ አካባቢያቸው እንዲመለሱ የተደረጉ የሀገር ውስጥ ተፈናቃዮች የሰብአዊ መብቶች ሁኔታ ላይ የተከናወነ ክትትል
...
የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) በሰሜን ኢትዮጵያ በነበረው ጦርነት ምክንያት ተፈናቅለው በትግራይ ክልል የተለያዩ አካባቢዎች ተጠልለው ከቆዩ በኋላ በደቡባዊ እና ሰሜን ምዕራብ ዞኖች ወደሚገኙ የቀድሞ መኖሪያ አካባቢዎቻቸው እንዲመለሱ የተደረጉ የሀገር ውስጥ ተፈናቃዮችን የሰብአዊ መብቶች ሁኔታ በተመለከተ ከነሐሴ 19 እስከ ጷጉሜን 1 ቀን 2016 ዓ.ም. ክትትል በማከናወን ያዘጋጀውን ባለ 11 ገጽ ሪፖርት ዛሬ ይፋ አድርጓል። ክትትሉ የተደረገው ኢሰመኮ ከዚህ ቀደም በክልሉ የሚገኙ የሀገር ውስጥ ተፈናቃዮችን የሰብአዊ መብቶች ሁኔታ በተመለከተ ክትትሎችን በማከናወን በተለያዩ ጊዜያት መግለጫዎችን እና ሪፖርቶችን ይፋ ሲያደርግ እንዲሁም ተፈናቃዮች ዘላቂ መፍትሔ በሚያገኙበት ሁኔታ ላይ የሚያደርገውን ክትትልና ውትወታ አጠናክሮ እንደሚቀጥል ሲገልጽ በቆየው መሠረት ነው።
ጋዜጣዊ መግለጫ፦ https://ehrc.org/?p=32253
ሙሉ ሪፖርቱን ያንብቡ፦ https://ehrc.org/download/?p=32255
#Ethiopia🇪🇹 #HumanRightsForAll
በነጻ የስልክ መስመራችን 7307 ላይ በመደወል የሰብአዊ መብቶች ጥሰት አቤቱታ ማቅረብ ወይም ጥቆማ መስጠት ይችላሉ።
...
የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) በሰሜን ኢትዮጵያ በነበረው ጦርነት ምክንያት ተፈናቅለው በትግራይ ክልል የተለያዩ አካባቢዎች ተጠልለው ከቆዩ በኋላ በደቡባዊ እና ሰሜን ምዕራብ ዞኖች ወደሚገኙ የቀድሞ መኖሪያ አካባቢዎቻቸው እንዲመለሱ የተደረጉ የሀገር ውስጥ ተፈናቃዮችን የሰብአዊ መብቶች ሁኔታ በተመለከተ ከነሐሴ 19 እስከ ጷጉሜን 1 ቀን 2016 ዓ.ም. ክትትል በማከናወን ያዘጋጀውን ባለ 11 ገጽ ሪፖርት ዛሬ ይፋ አድርጓል። ክትትሉ የተደረገው ኢሰመኮ ከዚህ ቀደም በክልሉ የሚገኙ የሀገር ውስጥ ተፈናቃዮችን የሰብአዊ መብቶች ሁኔታ በተመለከተ ክትትሎችን በማከናወን በተለያዩ ጊዜያት መግለጫዎችን እና ሪፖርቶችን ይፋ ሲያደርግ እንዲሁም ተፈናቃዮች ዘላቂ መፍትሔ በሚያገኙበት ሁኔታ ላይ የሚያደርገውን ክትትልና ውትወታ አጠናክሮ እንደሚቀጥል ሲገልጽ በቆየው መሠረት ነው።
ጋዜጣዊ መግለጫ፦ https://ehrc.org/?p=32253
ሙሉ ሪፖርቱን ያንብቡ፦ https://ehrc.org/download/?p=32255
#Ethiopia🇪🇹 #HumanRightsForAll
በነጻ የስልክ መስመራችን 7307 ላይ በመደወል የሰብአዊ መብቶች ጥሰት አቤቱታ ማቅረብ ወይም ጥቆማ መስጠት ይችላሉ።
👍3
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
የሳምንቱ #HumanRights Concept: በሥነ-ጥበብ ሐሳብን የመግለጽ እና የፈጠራ ነጻነት
...
የሲቪል እና ፖለቲካ መብቶች ዓለም አቀፍ ቃልኪዳን፣ አንቀጽ 19 (2) እና የኢኮኖሚ፣ የማኅበራዊ እና የባህል መብቶች ዓለም አቀፍ ቃልኪዳን፣ አንቀጽ 15 (1) (ሐ)
ማንኛውም ሰው በሥነ-ጥበብ መልክ ሐሳቡን በነጻነት የመግለጽ መብት አለው።
አባል ሀገራት የማንኛውንም ሰው ከሥነ-ጽሑፋዊ ወይም ከሥነ-ጥበባዊ የሥራ ውጤቱ የሚመነጨውን የሞራል እና ቁሳዊ ጥቅም የማግኘት መብት ዕውቅና ይሰጣሉ።
የኢትዮጵያ ሕገ መንግሥት፣ አንቀጽ 41 (9)
መንግሥት የባህልና የታሪክ ቅርሶችን የመጠበቅ እና የመንከባከብ እንዲሁም ለሥነ-ጥበብ መስፋፋት አስተዋጽዖ የማድረግ ኃላፊነት አለበት።
🔗 https://ehrc.org/?p=32361
#Ethiopia🇪🇹 #KeepWordSafe #ጤናማቃላት
በነጻ የስልክ መስመራችን 7307 ላይ በመደወል የሰብአዊ መብቶች ጥሰት አቤቱታ ማቅረብ ወይም ጥቆማ መስጠት ይችላሉ።
...
የሲቪል እና ፖለቲካ መብቶች ዓለም አቀፍ ቃልኪዳን፣ አንቀጽ 19 (2) እና የኢኮኖሚ፣ የማኅበራዊ እና የባህል መብቶች ዓለም አቀፍ ቃልኪዳን፣ አንቀጽ 15 (1) (ሐ)
ማንኛውም ሰው በሥነ-ጥበብ መልክ ሐሳቡን በነጻነት የመግለጽ መብት አለው።
አባል ሀገራት የማንኛውንም ሰው ከሥነ-ጽሑፋዊ ወይም ከሥነ-ጥበባዊ የሥራ ውጤቱ የሚመነጨውን የሞራል እና ቁሳዊ ጥቅም የማግኘት መብት ዕውቅና ይሰጣሉ።
የኢትዮጵያ ሕገ መንግሥት፣ አንቀጽ 41 (9)
መንግሥት የባህልና የታሪክ ቅርሶችን የመጠበቅ እና የመንከባከብ እንዲሁም ለሥነ-ጥበብ መስፋፋት አስተዋጽዖ የማድረግ ኃላፊነት አለበት።
🔗 https://ehrc.org/?p=32361
#Ethiopia🇪🇹 #KeepWordSafe #ጤናማቃላት
በነጻ የስልክ መስመራችን 7307 ላይ በመደወል የሰብአዊ መብቶች ጥሰት አቤቱታ ማቅረብ ወይም ጥቆማ መስጠት ይችላሉ።
👍3❤1