ግዴ-የለሽ!
.
(#ፈይሠል_አሚን)
.
ወደ ቀኝ ብጋረድ፣
ወደ ግራ ብጠመድ፣
(ግዴየለኝም!)
ብቀር ተጋርጄ፣በሐገሬው ልጓም፣
ወደ ተሸፈነው ለመሔድ አልጓጓም !
.
ለማይተወኝ ሕመም፣
ለማይዘልቀኝ ዓለም፣
(ግድ የለኝም!)
የሚያቃጥል እንባ አፍስሼ ዐውቃለሁ፣
አሁን. . .
በእንባዬ ደንድኜ በደሜ እሥቃለሁ።
.
አምላክ ለመመ'ለክ. . .
ፈጠረ ኝ በባሪያ መልክ።
(መልስ የለኝም!)
መልኬን እንደ ሰው፣ልኬን እንደጠጠር፣
እንደ የት? እንደ ማን?
በምን ሥም ልቆጠር?
በሰው እሾህ ስታጠር?
ከእንባና ከበድኔ. . .
ምን አምልኮ ልፍጠር?
.
እንቅልፍ ያጣሁ ጊዜ፣
እንደገና ተኛሁ፣ወዲያ ጥዬ ትራስ፣
ሕልሜን ሳጣስ?
የማንን ሕግ ልጣስ?
.
እርግጥ ነው ባምንም፣
"ሞት አይቀር ለማንም!"
ሲሉኝ. . . በፍርስራሽ ቃል፣
አንጀቴ ይሥቃል!
ነፍስ ተሸክመን ስለ ሞት ስናስል፣
አኗኗሩ ጠፋን የመሰንበት ምስል፣
"መኖር ለማንም" የሚቀር ይመስል!
(ብኖር ግድየለኝም!)
@huluezih
@huluezih
.
(#ፈይሠል_አሚን)
.
ወደ ቀኝ ብጋረድ፣
ወደ ግራ ብጠመድ፣
(ግዴየለኝም!)
ብቀር ተጋርጄ፣በሐገሬው ልጓም፣
ወደ ተሸፈነው ለመሔድ አልጓጓም !
.
ለማይተወኝ ሕመም፣
ለማይዘልቀኝ ዓለም፣
(ግድ የለኝም!)
የሚያቃጥል እንባ አፍስሼ ዐውቃለሁ፣
አሁን. . .
በእንባዬ ደንድኜ በደሜ እሥቃለሁ።
.
አምላክ ለመመ'ለክ. . .
ፈጠረ ኝ በባሪያ መልክ።
(መልስ የለኝም!)
መልኬን እንደ ሰው፣ልኬን እንደጠጠር፣
እንደ የት? እንደ ማን?
በምን ሥም ልቆጠር?
በሰው እሾህ ስታጠር?
ከእንባና ከበድኔ. . .
ምን አምልኮ ልፍጠር?
.
እንቅልፍ ያጣሁ ጊዜ፣
እንደገና ተኛሁ፣ወዲያ ጥዬ ትራስ፣
ሕልሜን ሳጣስ?
የማንን ሕግ ልጣስ?
.
እርግጥ ነው ባምንም፣
"ሞት አይቀር ለማንም!"
ሲሉኝ. . . በፍርስራሽ ቃል፣
አንጀቴ ይሥቃል!
ነፍስ ተሸክመን ስለ ሞት ስናስል፣
አኗኗሩ ጠፋን የመሰንበት ምስል፣
"መኖር ለማንም" የሚቀር ይመስል!
(ብኖር ግድየለኝም!)
@huluezih
@huluezih
ድንገተኛ ማስታወሻ!
.
ትናንት አንድ ትልቅ ትምህርት አገኘሁ። "ምትክ" የሚባል ትምህርት።
.
ትናንት የተወለድኩበት ቀን ነበር። " እና ስለተወለድኩ ምን ይጠበስ?" የምል ዓይነት ሰው ነኝ። በቃ ተወለድኩ፣ በቃ አለቀ። የተለየ ነገር አላደረግኩም፣ ለማድረግም ጥረት አላደረግኩም። የሥራ ገበታዬ ላይ ተገኘሁ። የአዘቦት እንቅስቃሴዬን ማድረግ ጀመርኩ። በሶሻል ሚድያ ልደቴ መኾኑን ያወቁ ጥቂት ሰዎች መልካም ምኞታቸውን ገለፁልኝ።
.
በልባቸው ውስጥ ለእኔ የተለየ ቦታ ያላቸው ሰዎች ግን በዚህ ምኞት ማለፍን አልመረጡም ። ከሥራ ገበታዬ አፈናቅለው ጥሩ ጊዜ እንዳሳልፍ፣ የተወለድኩበት ቀን በመኾኑ እንድቀብጥባቸው ዕድሉን ሠጡኝ። ጥሩ ጊዜ አሳለፍኩ። እንዲህ ዓይነት ሰዎች ጥቂትም ቢኾኑ ዙሪያዬ ስላሉ አምላኬን አመሠገንኩ።
.
ትምህርቱ የመጣው ውሎዬን ስገመግም ነው ። እነዚህ ለእኔ የተለየ ሥፍራ ያላቸው ሰዎች የዛሬ ዓመት ልክ በዚህ ቀን ሕይወቴ ውስጥ አልነበሩም። የዛሬ ዓመት ሕይወቴ ውስጥ የነበሩ ሰዎች አሁን የት እንዳሉ እንኳ አላውቅም። በዚህ ዓመት ሕይወቴ ውስጥ ባይኖሩም እንኳ አንዳችም የጎደለኝ ነገር የለም ። አንዳንዴ ጤነኝነቴን እጠራጠራለሁ...እንዴት ያን ግዙፍ ቦታ የሠጣኋቸው ሰዎች ከሕይወቴ ወጥተው ደስተኛ ልኾን ቻልኩ? ከልሳናቸው ሲዘንብልኝ የነበሩት ብዙ ዘመን የሚንደረደር የሚመስሉ ቃላቸውስ ዛሬ የት ሔደ ? እንዴት የጎደለ ነገር እንዳለ አልተ ሰማኝም?
.
ለመማር ዝግጁ ከኾንን ሕይወታችን በትምህርት የተሞላ ነው። ወደ እኛ የሚመጡ ነገሮች ሁሉ ሁለት ዓይነት ናቸው ። አንደኛው አስተምሮ ለማለፍ የሚመጣ ሲኾን ሌላኛው እያስተማረ ለመቅረት ይመጣል ። በዚህ ዕድለኛ ነኝ ። ከእያንዳንዱ ሁኔታ ለመማር ጉጉ ስለኾንኩ ያልተማርኩበት ህመም የለም ። ለዘመናት አብረውኝ ያሉ እና የሚኖሩ ባለ ቀና ልቦችም ዙሪያዬ እንደ ሐረግ ተጠምጥመዋል ። ለእነሱ ደግሞ አመሥጋኝ ነኝ ። ትናንት ያገኘሁት ትልቁ ትምህርት ግን ማንም ቢሔድ የሕይወት ደንብ ነውና የሔደውን የሚተካ በትክክል ይመጣል ። ካስተዋልን ሔዶ ያልተካነው አንድም የለም። እናትህን ወይ አባትህን ብቻ ላትተካ ትችል ይኾናል እንጂ ሌላው ምንም ህመም ቢኖረውም ምትክ አለው። ይኼን በፍፁም አትርሱ!
.
(#ፈይሠል_አሚን)
.
@huluezih
@huluezih
.
ትናንት አንድ ትልቅ ትምህርት አገኘሁ። "ምትክ" የሚባል ትምህርት።
.
ትናንት የተወለድኩበት ቀን ነበር። " እና ስለተወለድኩ ምን ይጠበስ?" የምል ዓይነት ሰው ነኝ። በቃ ተወለድኩ፣ በቃ አለቀ። የተለየ ነገር አላደረግኩም፣ ለማድረግም ጥረት አላደረግኩም። የሥራ ገበታዬ ላይ ተገኘሁ። የአዘቦት እንቅስቃሴዬን ማድረግ ጀመርኩ። በሶሻል ሚድያ ልደቴ መኾኑን ያወቁ ጥቂት ሰዎች መልካም ምኞታቸውን ገለፁልኝ።
.
በልባቸው ውስጥ ለእኔ የተለየ ቦታ ያላቸው ሰዎች ግን በዚህ ምኞት ማለፍን አልመረጡም ። ከሥራ ገበታዬ አፈናቅለው ጥሩ ጊዜ እንዳሳልፍ፣ የተወለድኩበት ቀን በመኾኑ እንድቀብጥባቸው ዕድሉን ሠጡኝ። ጥሩ ጊዜ አሳለፍኩ። እንዲህ ዓይነት ሰዎች ጥቂትም ቢኾኑ ዙሪያዬ ስላሉ አምላኬን አመሠገንኩ።
.
ትምህርቱ የመጣው ውሎዬን ስገመግም ነው ። እነዚህ ለእኔ የተለየ ሥፍራ ያላቸው ሰዎች የዛሬ ዓመት ልክ በዚህ ቀን ሕይወቴ ውስጥ አልነበሩም። የዛሬ ዓመት ሕይወቴ ውስጥ የነበሩ ሰዎች አሁን የት እንዳሉ እንኳ አላውቅም። በዚህ ዓመት ሕይወቴ ውስጥ ባይኖሩም እንኳ አንዳችም የጎደለኝ ነገር የለም ። አንዳንዴ ጤነኝነቴን እጠራጠራለሁ...እንዴት ያን ግዙፍ ቦታ የሠጣኋቸው ሰዎች ከሕይወቴ ወጥተው ደስተኛ ልኾን ቻልኩ? ከልሳናቸው ሲዘንብልኝ የነበሩት ብዙ ዘመን የሚንደረደር የሚመስሉ ቃላቸውስ ዛሬ የት ሔደ ? እንዴት የጎደለ ነገር እንዳለ አልተ ሰማኝም?
.
ለመማር ዝግጁ ከኾንን ሕይወታችን በትምህርት የተሞላ ነው። ወደ እኛ የሚመጡ ነገሮች ሁሉ ሁለት ዓይነት ናቸው ። አንደኛው አስተምሮ ለማለፍ የሚመጣ ሲኾን ሌላኛው እያስተማረ ለመቅረት ይመጣል ። በዚህ ዕድለኛ ነኝ ። ከእያንዳንዱ ሁኔታ ለመማር ጉጉ ስለኾንኩ ያልተማርኩበት ህመም የለም ። ለዘመናት አብረውኝ ያሉ እና የሚኖሩ ባለ ቀና ልቦችም ዙሪያዬ እንደ ሐረግ ተጠምጥመዋል ። ለእነሱ ደግሞ አመሥጋኝ ነኝ ። ትናንት ያገኘሁት ትልቁ ትምህርት ግን ማንም ቢሔድ የሕይወት ደንብ ነውና የሔደውን የሚተካ በትክክል ይመጣል ። ካስተዋልን ሔዶ ያልተካነው አንድም የለም። እናትህን ወይ አባትህን ብቻ ላትተካ ትችል ይኾናል እንጂ ሌላው ምንም ህመም ቢኖረውም ምትክ አለው። ይኼን በፍፁም አትርሱ!
.
(#ፈይሠል_አሚን)
.
@huluezih
@huluezih
❤1
የማለዳ ማስታወሻ #145
.
ሕልም የሌላትን ሴት እፈራለሁ። ሕልሟ አግብቶ መውለድ ብቻ የኾነች ሴት ሳይ ደግሞ እሸማቀቃለሁ። አግብቶ መውለድ በተፈጥሮ የተሠጠ መንገድ እንጂ ሕልም መኾን አይችልም። ድመትም ፍየልም ሳያልሙ በተሠጣቸው አጭር ዕድሜ ውስጥ ወልደው ያልፋሉ። መጠለያ የሌላቸው የጎዳና ተዳዳሪ ሴቶችም ይወልዳሉ። ምክንያቱም መውለድ የተፈጥሮ ሕግ እንጂ ሕልም ስላለኾነ።
.
የማሕበረሰብ ቀውስ መድኃኒትም መርዝም ሴት ልጅ ናት። ሴት ቁሳዊ ስትኾን፣ እናት ለልጇ ዋጋ ስትተምን ቀሪው ማሕበረሰብ ቁስ አዳኝ ይኾናል። ተምራ፣ሠርታ እና ለፍታ መኪናም ኾነ ቤት መግዛት እንደምትችል ያልተነገራት ሴት ደስተኛ ቤተሰብ መመሥረት አይቻላትም። ደስተኛ ካልኾነ ቤተሰብ የወጣ ልጅስ ለማሕበረሰቡ ብሎም ለሐገሩ ምን መሥጠት ይችላል?(ከጨለምተኝነት ውጪ?)
.
አንጋፋው የራሺያ ደራሲ ማክሲም ጎርኪ "ሴት ልጅ ሁለተኛ ነፍስህ ናት!" በሚለው አምናለሁ። ከማመንም አልፎ ሴት ልጅ ከወንድ አንድ ደረጃ ከፍ ብላ የተቀመጠች ባለማዕረግ መኾኗን እቀበላለሁ።
.
ዘመናችን የሴቶችን ማዕረግና ክብር ከራሳቸው ከሴቶቹም የሸሸገ ይመስላል። አግብቶ ለመውለድ የተፈጠሩ እስኪመስል ድረስ ሕልም አልባ አድርጓቸዋል። ሴትነታቸው ፈተና እንጂ ፀጋ እንዳልኾነ ሁሉ በትዳር ውስጥ ከትግል ለመራቅ ሲጥሩ ይታያል።ይመስላቸው ይኾናል እንጂ ትዳር ውስጥ ያለው ፈተና ቢከፋ እንጂ አያንስም። ትዳር ውስጥ ያለውን ፈተና የሚቋቋም ትከሻቸው ሕልማቸውን ለመኖር ለሚጎሽማቸው የውጪው ዓለም ፈተናም ብቁ ስለመኾኑ ይጠራጠራሉ።
.
ትዳር በትክክለኛው ጊዜ፣ ከትክክለኛው የነፍስ አጋር ጋር ሲኾን ቅዱስ እና ብሩክ ነው። ሕልምን የሚሰዉበት ሳይኾን ሕልምን ለማሳካት የኃይል ስንቅ የሚቋጥሩበት ዓለም ነው።
.
ከአጠገባችን ብዙ ሴቶች እንደፈረስ የፊቱን ብቻ እያዩ ከነ ልጓማቸው ተድረዋል። ቤት ንብረት እና ገንዘብ ስላለው ብቻ አግብተው፣ሕልማቸውንና ዕውቀታቸውን ሰውተው በአንድ ጎጆ ውስጥ ይኖራሉ። ቤት እንደሚፈርስ፣ ንብረት እንደሚወድም፣ ገንዘብ እንደሚጠፋ አለማሰባቸው ውስጥ የማሕበረሰቤን ውደቀት አስተውለላሁ። ሐገር ለማቆም፣ መንገድ ለማቅናት መፍትሔ መኾን የሚችሉ እንስቶች "አልችልም" በሚል መረብ ራሳቸውን አጥምደው ሳይ አዝናለሁ። የሴት ልጅ የመጀመሪያው መስፈርት "ምን ታበላኛለህ?" የኾነ ጊዜ ነበር እንደማሕበረሰብ የከሸፍነው። ወንድ ልጅም የትዳር ጥያቄውን ተንበርክኮ በክብር ጥያቄ ሊያቀርብላት ለሚገባው ሴት " ከገንዘብ፣ ከመኪና፣ ከቤት ውጪ ምን ትፈልጊያለሽ?" ሲላት መውደቂያችን ላይ ተደላድለናል ማለት ነው።
.
ሴት ልጅ ሕልም ይኑራት፣ ለዓለም የሚተርፍ ሕልም። ሴት ልጅ ልብ ይኑራት፣ ለሐገር የሚበቃ። ሴት ልጅ ምንም ማድረግ እንደምትችል ስታምን የሚያገባት ወንድ ሳይኾን የምታገባውን ወንድ በልቧ ፈልጋ ታገኛለች።
.
(#ፈይሠል_አሚን)
.
@huluezih
@huluezih
.
ሕልም የሌላትን ሴት እፈራለሁ። ሕልሟ አግብቶ መውለድ ብቻ የኾነች ሴት ሳይ ደግሞ እሸማቀቃለሁ። አግብቶ መውለድ በተፈጥሮ የተሠጠ መንገድ እንጂ ሕልም መኾን አይችልም። ድመትም ፍየልም ሳያልሙ በተሠጣቸው አጭር ዕድሜ ውስጥ ወልደው ያልፋሉ። መጠለያ የሌላቸው የጎዳና ተዳዳሪ ሴቶችም ይወልዳሉ። ምክንያቱም መውለድ የተፈጥሮ ሕግ እንጂ ሕልም ስላለኾነ።
.
የማሕበረሰብ ቀውስ መድኃኒትም መርዝም ሴት ልጅ ናት። ሴት ቁሳዊ ስትኾን፣ እናት ለልጇ ዋጋ ስትተምን ቀሪው ማሕበረሰብ ቁስ አዳኝ ይኾናል። ተምራ፣ሠርታ እና ለፍታ መኪናም ኾነ ቤት መግዛት እንደምትችል ያልተነገራት ሴት ደስተኛ ቤተሰብ መመሥረት አይቻላትም። ደስተኛ ካልኾነ ቤተሰብ የወጣ ልጅስ ለማሕበረሰቡ ብሎም ለሐገሩ ምን መሥጠት ይችላል?(ከጨለምተኝነት ውጪ?)
.
አንጋፋው የራሺያ ደራሲ ማክሲም ጎርኪ "ሴት ልጅ ሁለተኛ ነፍስህ ናት!" በሚለው አምናለሁ። ከማመንም አልፎ ሴት ልጅ ከወንድ አንድ ደረጃ ከፍ ብላ የተቀመጠች ባለማዕረግ መኾኗን እቀበላለሁ።
.
ዘመናችን የሴቶችን ማዕረግና ክብር ከራሳቸው ከሴቶቹም የሸሸገ ይመስላል። አግብቶ ለመውለድ የተፈጠሩ እስኪመስል ድረስ ሕልም አልባ አድርጓቸዋል። ሴትነታቸው ፈተና እንጂ ፀጋ እንዳልኾነ ሁሉ በትዳር ውስጥ ከትግል ለመራቅ ሲጥሩ ይታያል።ይመስላቸው ይኾናል እንጂ ትዳር ውስጥ ያለው ፈተና ቢከፋ እንጂ አያንስም። ትዳር ውስጥ ያለውን ፈተና የሚቋቋም ትከሻቸው ሕልማቸውን ለመኖር ለሚጎሽማቸው የውጪው ዓለም ፈተናም ብቁ ስለመኾኑ ይጠራጠራሉ።
.
ትዳር በትክክለኛው ጊዜ፣ ከትክክለኛው የነፍስ አጋር ጋር ሲኾን ቅዱስ እና ብሩክ ነው። ሕልምን የሚሰዉበት ሳይኾን ሕልምን ለማሳካት የኃይል ስንቅ የሚቋጥሩበት ዓለም ነው።
.
ከአጠገባችን ብዙ ሴቶች እንደፈረስ የፊቱን ብቻ እያዩ ከነ ልጓማቸው ተድረዋል። ቤት ንብረት እና ገንዘብ ስላለው ብቻ አግብተው፣ሕልማቸውንና ዕውቀታቸውን ሰውተው በአንድ ጎጆ ውስጥ ይኖራሉ። ቤት እንደሚፈርስ፣ ንብረት እንደሚወድም፣ ገንዘብ እንደሚጠፋ አለማሰባቸው ውስጥ የማሕበረሰቤን ውደቀት አስተውለላሁ። ሐገር ለማቆም፣ መንገድ ለማቅናት መፍትሔ መኾን የሚችሉ እንስቶች "አልችልም" በሚል መረብ ራሳቸውን አጥምደው ሳይ አዝናለሁ። የሴት ልጅ የመጀመሪያው መስፈርት "ምን ታበላኛለህ?" የኾነ ጊዜ ነበር እንደማሕበረሰብ የከሸፍነው። ወንድ ልጅም የትዳር ጥያቄውን ተንበርክኮ በክብር ጥያቄ ሊያቀርብላት ለሚገባው ሴት " ከገንዘብ፣ ከመኪና፣ ከቤት ውጪ ምን ትፈልጊያለሽ?" ሲላት መውደቂያችን ላይ ተደላድለናል ማለት ነው።
.
ሴት ልጅ ሕልም ይኑራት፣ ለዓለም የሚተርፍ ሕልም። ሴት ልጅ ልብ ይኑራት፣ ለሐገር የሚበቃ። ሴት ልጅ ምንም ማድረግ እንደምትችል ስታምን የሚያገባት ወንድ ሳይኾን የምታገባውን ወንድ በልቧ ፈልጋ ታገኛለች።
.
(#ፈይሠል_አሚን)
.
@huluezih
@huluezih
የማለዳ ማስታወሻ #146
.
"ዝናብ እንወዳለን" ያሉት ሲዘንብ ዣንጥላ ዘርግተው ዐይቻለሁ። ፀሐይ የሚወዱት ከፀሐይ ሸሽተው መጠለያ ሥር ሲውሉ አስተውያለሁ። "የተፈጥሮ አድናቂ ነኝ!" ያሉኝ የተፈጥሮ ጸጋቸውን በዘመን አመጣሽ ብልሃት ሲጋርዱ ታዝቤያለሁ።
.
"እውነት ለሰው ልጅ መሠረታዊ ነገር ነው!" ብለው ሰይጣን ሚያስቀና ውሸት ይዋሻሉ። ግልፅነትን ከልሳናቸው ዘርተው ሁለመናቸውን ይደብቃሉ። ብዙ የኖረ ትልቅ ሰውነት ይዘው የጨቅላ ጣት በምታክል አዕምሮ የሚኖሩ ሰዎች ገጥመውኛል። ሰይጣንን አጥላልተው የሚኮንኑ ግን ከሰይጣን የከፉ ሰዎች በሕይወት መንገዴ ላይ ቆመው ያወቃሉ።
.
ምላስ ያለው፣ልሳን የታደለ ሁሉ ቃላትን እንደዋዛ ይተፋል። ቃል የማንነት ማሣያ ሽንቁር መኾኑን ዘንግቶ። በብዙ ስብራት፣ በእልፍ ትዝብት፣ በአይቆጠሬ ክህደት ውስጥ አልፌ ከሰው የሚወጣ ቃል ባላምን ትፈርጂብኛለሽ?
.
"እወድሃለሁ!" ስትይኝ ጠባሳዬን አልፎ ልቤ ጋር ባይደርስ ጥፋቴ ምንድነው? ይኼን እያወቅሽ ንፁሕ የፍቅር ቃላት የወረወርሺው አንቺስ ምን አጠፋሽ? አንዳንዴ. . .አልፈን የመጣነው ገሃነም የገነትን መግቢያ ይጋርድብናል!
.
(#ፈይሠል_አሚን)
.
@huluezih
@huluezih
.
"ዝናብ እንወዳለን" ያሉት ሲዘንብ ዣንጥላ ዘርግተው ዐይቻለሁ። ፀሐይ የሚወዱት ከፀሐይ ሸሽተው መጠለያ ሥር ሲውሉ አስተውያለሁ። "የተፈጥሮ አድናቂ ነኝ!" ያሉኝ የተፈጥሮ ጸጋቸውን በዘመን አመጣሽ ብልሃት ሲጋርዱ ታዝቤያለሁ።
.
"እውነት ለሰው ልጅ መሠረታዊ ነገር ነው!" ብለው ሰይጣን ሚያስቀና ውሸት ይዋሻሉ። ግልፅነትን ከልሳናቸው ዘርተው ሁለመናቸውን ይደብቃሉ። ብዙ የኖረ ትልቅ ሰውነት ይዘው የጨቅላ ጣት በምታክል አዕምሮ የሚኖሩ ሰዎች ገጥመውኛል። ሰይጣንን አጥላልተው የሚኮንኑ ግን ከሰይጣን የከፉ ሰዎች በሕይወት መንገዴ ላይ ቆመው ያወቃሉ።
.
ምላስ ያለው፣ልሳን የታደለ ሁሉ ቃላትን እንደዋዛ ይተፋል። ቃል የማንነት ማሣያ ሽንቁር መኾኑን ዘንግቶ። በብዙ ስብራት፣ በእልፍ ትዝብት፣ በአይቆጠሬ ክህደት ውስጥ አልፌ ከሰው የሚወጣ ቃል ባላምን ትፈርጂብኛለሽ?
.
"እወድሃለሁ!" ስትይኝ ጠባሳዬን አልፎ ልቤ ጋር ባይደርስ ጥፋቴ ምንድነው? ይኼን እያወቅሽ ንፁሕ የፍቅር ቃላት የወረወርሺው አንቺስ ምን አጠፋሽ? አንዳንዴ. . .አልፈን የመጣነው ገሃነም የገነትን መግቢያ ይጋርድብናል!
.
(#ፈይሠል_አሚን)
.
@huluezih
@huluezih
የማለዳ ማስታወሻ #147
.
ገና ነን. . .ሕይወትን ለመፈረጅ፣ መንገዳችንን ለመተርጎም፣ ኖርን ለማለት።ገና ገና ነን!
.
ምድርን ዐይተን መቼ ጨረስን? የምሥራቋን ፀሐይ፣ የምዕራቧን ጀምበር ውቅያኖስ ጠርዝ ላይ መቼ ተመለከትን? ተራራዎችን መቼ ወጣን? ሸለቆዎችን መቼ አቋረጥን?
.
ነገሩ ስላለማቆም ነው። ባሰብነው ልክ ባይኾን እንኳ በቻልነው መጠን ስለ መንቀራፈፍ! የሚያሰጥም በሚመስል ግዙፍ ውኃ ላይ በትዕግሥት ስለ መንሳፈፍ! የምንመኘውን ያክል ብርቱ ባንኾንም ወደ ነገ እጅን ለመስደድ ስላለመስነፍ። ይኼው ነው የሕይወት ውል። ዘወትር በሙከራ ውስጥ ራስን መዝፈቅ።
.
ብዙ ሞክሮ ያልተሳካለት የለም። ያልተሳካለትም አልከሰረም። በብዙ ሙከራ ውስጥ ተዓምር አለና ከሞከረው የበለጠ ጣዕም ያለው በለስ ይገጥመው ይኾናል።
.
ገና ነው። ፈርጀ ብዙ መንገድ ይጠብቀናል። የደከምንለት ገና መቼ ካሠን? የወደቅንለት መቼ አስከበረን? ከራሳችን አልፈን ለምንወዳቸው መቼ ተረፍን? ሕይወትን መቼ ዐየን? "ዓለም ዘጠኝ ናት" ሲባል አልሰማህም? ዘጠኙም ዓለም በሕይወትህ እስካልመጣ ኖርኩኝ አትበል። ገና መጀመራችን ነው. . .ያንተን ታሪክ ለመስማት ጆሮዎች እስኪጓጉ ድረስ አትቦዝን. . .ብዙዎች አንቺን ለመኾን እስኪመኙ ድረስ መሞከር አታቁሚ። ሌላው ካሰበበት ከደረሰ እኛን ማን ይከለክለናል? ገና ነው!!!
.
(#ፈይሠል_አሚን)
.
@huluezih
@huluezih
.
ገና ነን. . .ሕይወትን ለመፈረጅ፣ መንገዳችንን ለመተርጎም፣ ኖርን ለማለት።ገና ገና ነን!
.
ምድርን ዐይተን መቼ ጨረስን? የምሥራቋን ፀሐይ፣ የምዕራቧን ጀምበር ውቅያኖስ ጠርዝ ላይ መቼ ተመለከትን? ተራራዎችን መቼ ወጣን? ሸለቆዎችን መቼ አቋረጥን?
.
ነገሩ ስላለማቆም ነው። ባሰብነው ልክ ባይኾን እንኳ በቻልነው መጠን ስለ መንቀራፈፍ! የሚያሰጥም በሚመስል ግዙፍ ውኃ ላይ በትዕግሥት ስለ መንሳፈፍ! የምንመኘውን ያክል ብርቱ ባንኾንም ወደ ነገ እጅን ለመስደድ ስላለመስነፍ። ይኼው ነው የሕይወት ውል። ዘወትር በሙከራ ውስጥ ራስን መዝፈቅ።
.
ብዙ ሞክሮ ያልተሳካለት የለም። ያልተሳካለትም አልከሰረም። በብዙ ሙከራ ውስጥ ተዓምር አለና ከሞከረው የበለጠ ጣዕም ያለው በለስ ይገጥመው ይኾናል።
.
ገና ነው። ፈርጀ ብዙ መንገድ ይጠብቀናል። የደከምንለት ገና መቼ ካሠን? የወደቅንለት መቼ አስከበረን? ከራሳችን አልፈን ለምንወዳቸው መቼ ተረፍን? ሕይወትን መቼ ዐየን? "ዓለም ዘጠኝ ናት" ሲባል አልሰማህም? ዘጠኙም ዓለም በሕይወትህ እስካልመጣ ኖርኩኝ አትበል። ገና መጀመራችን ነው. . .ያንተን ታሪክ ለመስማት ጆሮዎች እስኪጓጉ ድረስ አትቦዝን. . .ብዙዎች አንቺን ለመኾን እስኪመኙ ድረስ መሞከር አታቁሚ። ሌላው ካሰበበት ከደረሰ እኛን ማን ይከለክለናል? ገና ነው!!!
.
(#ፈይሠል_አሚን)
.
@huluezih
@huluezih