Telegram Web Link
እንኳን ከዘጠኙ ዐበይት የጌታ በዓላት (ብሥራት ልደት ጥምቀት ደብረ ታቦር ሆሳዕና ስቅለት ትንሣኤ ዕርገትና ጰራቅሊጦስ) አንዱ ለሆነው ለሆሳዕና በዓል በሰላም አደረሳችሁ::
መርገመ በለስ
በዚህ ዕለት ጌታችን ከቢታኒያ ሲወጣ ተራበ ቅጠል ያለባትን በለስ ተመልክቶ ወደ በለሲቱ ቢቀርብ ከቅጠል በቀር ምንም ነገር ባለማግኘቱ “ከአሁን ጀምሮ ለዘላለም ምንም ካንቺ ፍሬ አይበላ” ማር ፲፩፥፲፬ በማለት ስለረገማት መርገመ በለስ የተፈጸመበት ሰኞ ይባላል።
የትምህርት ቀን
በዚህ ዕለት በቤተመቅደስ ረጅም ትምህርት ስላስተማረም የትምህርት ቀን ይባላል። ሉቃ ፳፩ ፥፳፰ ፣ ማር ፲፪፥፪።
ምክረ አይሁድ
ረቡዕ ዕለት የአይሁድ ሊቃነ ካህናትና ጸሐፍት ጌታን እንዴት መያዝ እንዳለባቸው የመከሩበትና ውሳኔ ያሳለፉበት ቀን በመሆኑ ምክረ አይሁድ ይባላል። ሉቃ ፳፪፥፩-፮

የመልካም መዓዛ ቀን
ጌታችን በዚህ ዕለት በለምጻሙ በስምዖን ቤት ተቀምጦ ሳለ ማርያም እንተ ዕፍረት/ባለሽቶዋ ማርያም/ ዋጋው እጅግ ውድ የሆነ የአልባጥሮስ ሽቱ አምጥታ በራሱ ላይ በማርከፍከፍ ስለቀባቸው ማቴ ፳፮፥፮-፯ የመዓዛ ቀን ይባላል።

የዕንባ ቀን
ባለሽቱዋ ሴት (ማርያም እንተ ዕፍረት) ኃጢአቷን ይቅር እንዲላት እየለመነች በእግሩ ስር ተደፍታ በእንባዋ እግሩን አጥባለችና ማር ፲፬፥፱ የዕንባ ቀን ይባላል።
ሕጽበተ ኅሙስ
ጌታችን የደቀመዛሙርቱን እግር በፍጹም ትሕትና ዝቅ ብሎ ያጠበበት ዕለት በመሆኑም ዮሐ ፲፫፥፫-፲፩ ሕጽበተ ሐሙስ ይባላል።

የምሥጢር ቀን
ከሰባቱ ምሥጢራት አንዱ የቅዱስ ቁርባን ምሥጢር ማቴ፳፮፥፳፮-፳፱ በዚህ ዕለት ተፈጽሟልና የምሥጢር ቀን ይባላል።
የስቅለት ዓርብ
ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለአዳምና ለልጆቹ ሁሉ ቤዛ ሆኖ በመልዕልተ መስቀል ላይ ተሰቅሎ የዋለበት ዕለት ነውና ማቴ ፳፯፥፴፭ የስቅለት ዓርብ ይባላል።
2025/06/30 19:29:17
Back to Top
HTML Embed Code: