እንኳን ከዘጠኙ ዐበይት የጌታ በዓላት (ብሥራት ልደት ጥምቀት ደብረ ታቦር ሆሳዕና ስቅለት ትንሣኤ ዕርገትና ጰራቅሊጦስ) አንዱ ለሆነው ለሆሳዕና በዓል በሰላም አደረሳችሁ::
ምክረ አይሁድ
ረቡዕ ዕለት የአይሁድ ሊቃነ ካህናትና ጸሐፍት ጌታን እንዴት መያዝ እንዳለባቸው የመከሩበትና ውሳኔ ያሳለፉበት ቀን በመሆኑ ምክረ አይሁድ ይባላል። ሉቃ ፳፪፥፩-፮
የመልካም መዓዛ ቀን
ጌታችን በዚህ ዕለት በለምጻሙ በስምዖን ቤት ተቀምጦ ሳለ ማርያም እንተ ዕፍረት/ባለሽቶዋ ማርያም/ ዋጋው እጅግ ውድ የሆነ የአልባጥሮስ ሽቱ አምጥታ በራሱ ላይ በማርከፍከፍ ስለቀባቸው ማቴ ፳፮፥፮-፯ የመዓዛ ቀን ይባላል።
የዕንባ ቀን
ባለሽቱዋ ሴት (ማርያም እንተ ዕፍረት) ኃጢአቷን ይቅር እንዲላት እየለመነች በእግሩ ስር ተደፍታ በእንባዋ እግሩን አጥባለችና ማር ፲፬፥፱ የዕንባ ቀን ይባላል።
ረቡዕ ዕለት የአይሁድ ሊቃነ ካህናትና ጸሐፍት ጌታን እንዴት መያዝ እንዳለባቸው የመከሩበትና ውሳኔ ያሳለፉበት ቀን በመሆኑ ምክረ አይሁድ ይባላል። ሉቃ ፳፪፥፩-፮
የመልካም መዓዛ ቀን
ጌታችን በዚህ ዕለት በለምጻሙ በስምዖን ቤት ተቀምጦ ሳለ ማርያም እንተ ዕፍረት/ባለሽቶዋ ማርያም/ ዋጋው እጅግ ውድ የሆነ የአልባጥሮስ ሽቱ አምጥታ በራሱ ላይ በማርከፍከፍ ስለቀባቸው ማቴ ፳፮፥፮-፯ የመዓዛ ቀን ይባላል።
የዕንባ ቀን
ባለሽቱዋ ሴት (ማርያም እንተ ዕፍረት) ኃጢአቷን ይቅር እንዲላት እየለመነች በእግሩ ስር ተደፍታ በእንባዋ እግሩን አጥባለችና ማር ፲፬፥፱ የዕንባ ቀን ይባላል።
ሕጽበተ ኅሙስ
ጌታችን የደቀመዛሙርቱን እግር በፍጹም ትሕትና ዝቅ ብሎ ያጠበበት ዕለት በመሆኑም ዮሐ ፲፫፥፫-፲፩ ሕጽበተ ሐሙስ ይባላል።
የምሥጢር ቀን
ከሰባቱ ምሥጢራት አንዱ የቅዱስ ቁርባን ምሥጢር ማቴ፳፮፥፳፮-፳፱ በዚህ ዕለት ተፈጽሟልና የምሥጢር ቀን ይባላል።
ጌታችን የደቀመዛሙርቱን እግር በፍጹም ትሕትና ዝቅ ብሎ ያጠበበት ዕለት በመሆኑም ዮሐ ፲፫፥፫-፲፩ ሕጽበተ ሐሙስ ይባላል።
የምሥጢር ቀን
ከሰባቱ ምሥጢራት አንዱ የቅዱስ ቁርባን ምሥጢር ማቴ፳፮፥፳፮-፳፱ በዚህ ዕለት ተፈጽሟልና የምሥጢር ቀን ይባላል።