Telegram Web Link
#YonatanBTFurniture

የቢሮዎን እቃዎች ለመቀየር አስበዋል?

ዮናታን ቢቲ ፈርኒቸር ለቢሮዎ ግርማሞገስ፣ ምቾት፣ ጥንካሬ እና ዘመናዊነትን የሚያላብሱ የቢሮ ወንበሮች፣ ጠረጴዛዎች እንዲሁም ለቢሮዎ ያስፈልገኛል ብለው የሚያስቧቸውን ምርቶች በፈለጉት አማራጭ እና ዲዛይን አቅርበንሎታል።

ይምጡ እና ይጎብኙን!

📍አድራሻችን

1. ፒያሳ እሪ በከንቱ ቢቲ ታወር
2. ከዊንጌት አደባባይ አለፍ ብሎ ከአቢሲኒያ ባንክ ፊትለፊት
3. ከሲኤምሲ አደባባይ ወደ አያት መንገድ መሪ ሳይደርስ (ዘመን ባንክ አጠገብ)

☎️ ይደውሉልን
+251957868686/ +251995272727/ +251993828282

Telegram/Facebook/Instagram/TikTok

#OfficeFurniture #ConferenceTables #OfficeTable
144🙏4👏2🕊1
#SafaricomEthiopia

ቀጣይ የ1 ሚሊየን ዕደለኛ ማን ይሆን! 2ቀን ብቻ ቀረው! 🏆💚 ዛሬዉኑ የበሽ ጥቅልን ይግዙ፤ ሚሊየነር የመሆን እድሎን ያስፉ!

📲 የM-PESA መተግበሪያን አሁኑኑ ያውርዱ፡
https://onelink.to/ewsb22

የቴሌግራም ቦታችን: https://www.tg-me.com/official_safaricomet_bot

ወደ *777*0# ይደውሉ ወይም በM-PESA የበሽ ጥቅል ይግዙ!

#MPESASafaricom
#furtheraheadtogether
#Besh
73🙏10😡7🕊2👏1
የሰዎችን_ከቦታ_ቦታ_የመዘዋወር_ነጻነት_በተሟላ_ሁኔታ_መፈጸም_የሚያስችሉ_እርምጃዎች_በአፋጣኝ_ሊወሰዱ.pdf
271.1 KB
የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን ን የሰዎችን ከቦታ ቦታ የመዘዋወር ነጻነት በተሟላ ሁኔታ መፈጸም የሚያስችሉ እርምጃዎች በአፋጣኝ እንዲወሰዱ አሳሰበ።

በተለያዩ ክልሎች በመንገድ ላይ ለሚደርሱ ጥቃቶች ፣ እገታዎች፣ የንብረት ዘረፋዎች እና ውድመቶች የሰዎች ከቦታ ቦታ የመዘዋወር ነጻነት አደጋ ላይ እንደወደቀ ገልጿል።

መንግሥት በተለያዩ ቦታዎች የተፈጸሙ የሰብአዊ መብቶች ጥሰቶች ላይ የተሟላ ማጣራት በማድረግ ተጠያቂነትን ሊያረጋግጥ እንዲሁም በድርጊቶቹ ተጎጂ ለሆኑ ሰዎች ፍትሕ ሊያሰፍን እንደሚገባ አሳስቧል።

(ኮሚሽኑ የላከው መግለጫ ከላይ ተያይዟል)

@tikvahethiopia
311👏52😢13🕊13🥰10😭6🙏2
“ጠዋት በተኙበት ነው እናትና አባቴን የገደሉብኝ፤ ታናሽ እህታችንም ታግታለች” - የሟቾች ልጅ

➡️ “ አራት ሰዎች ተገድለዋል፤ ስድስት ደግሞ ታግተዋል፣ 81 የግለሰብ ከብቶች ተወስደዋል ” ባለስልጣን

በኦሮሚያ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን ወረጃርሶ ወረዳ ጊርሚጎባ ቀበሌ ታጣቂዎች በንጹሐን ላይ የሞትና እገታ፣ በንብረት ላይ የውድመት ጥቃት ማድረሳቸውን ነዋሪዎችና ባለስልጣን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገለጹ፡፡

ነዋሪዎቹ፣ መስከረም 29 ቀን 2018 ዓ/ም፣ “ህዝቡ በተኛበት ንጋት 11 ሰዓት አካባቢ ተኩስ ከፍተው አራት ሰዎች ገድለዋል፤ ስድስት ሰዎች አግተዋል፤ ቤትም አቃጥለዋል” ብለዋል፡፡

“ወደ 100 ከብቶች” እንደተነዱና “ወደ 100 ቤቶች” እንደተቃጠሉ፣ ጥቃቱን ያደረሰው "ሸኔ" እንደሆነ ገልጸው፣ “ከሦስት ወራት በፊትም ተራራ ላይ መሳሪያ አጥምደው አጋምሳ መንደርን አቃጥለው ዘጠኝ ሰዎች ገድለዋል” ሲሉም አስታውሰዋል።

ቃላቸውን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ የሰጡ የሁለት ሟቾች ልጅ፣  "ጠዋት 12 ሰዓት አካባቢ በተኙበት ነው እናትና አባቴን የገደሉብኝ፤ ታናሽ እህታችንም ታግታለች፡፡ ከብቶችንም ወስደዋል " ብለዋል።

“አባቴ ከአመት በላይ ታሞ ተኝቶ ነበር፤ እግሩ ተዘርግቶ መሄድ አይችልም በበሽታ ምክንያት፤ እናቴ ደግሞ ሌላው ሰው ሲሸሽ 'ባለቤቴን ትቼ አልሄድም' ብላ እዚያው ሲያገኟቸው ገደሏቸው " ሲሉ ገልጸዋል።

" ሸሽቶ ስለነበር በሰዓቱ ብዙ ሰው የለም ነበር፤ ባለው ትንሽ ሰው በአንድ ጉድጓድ ነው የተቀሩት፡፡ እኔ የሟቾች ልጅ ነኝ። መንግስት እንዲህ ያለጥቃት እንዲቆም መስራትና ለተጎጂዎች መድረስ አለበት ” ሲሉ አስገንዝሸዋል።

ስለጥቃቱ ማረጋገጫ የተጠየቅናቸው አንድ የቀበሌው ከፍተኛ አመራር በበኩላቸው፣ “አራት ሰዎች ገድለዋል፤ ስድስት ታግተዋል፣ 81 የግለሰብ ከብቶች ተወስደዋል። በአካባቢው ነበርኩ በርካታ ጥይቶች ተተኩሰውብናል፡፡ 50 የሚጠጉ ቤቶች ተቃጥለዋል፡፡ አንድ የህዝብ ወፍጮ ተቃጥሏል” ሲሉ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል።

ቀበሌውን ከወረዳው በስተደቡብ “አብዛኛዎቹ በሸኔ ታጣቂዎች የተያዙ” ቀበሌዎች እንደሚያዋስኑት ገልጸው፣ “ከዚህም በፊትም ከአንዴም ሁለት ጊዜ ነዋሪውን ለማጥቃት ተሞክሯል፡፡ መስከረም 29/2018 ዓ/ም የደረሰው ጥቃት ግን ከምንም በላይ የከፋ ነበር” ነው ያሉት፡፡

እኝሁ አካል፣ ጥቃቱ ከተፈጸመት “ከንጋት ከ11 ሰዓት ጀምሮ ለሚመለከተው አካል ደውለናል፤ ግን ጎሃጽዮን ታጣቂዎች መኪና ራሱ እንዳይወጣ የሚያደርጉበት በመሆኑ መከላከያ አልደረሰልንም” ነው ያሉት፡፡

“ከዚህ በፊት ጥቃት ተፈጽሞ በአንድ ቀን ስምንት ሰዎች ተገድለዋል፡፡ 47 ቤቶች ተቃጥለዋል፤ በርካታ ሰዎችም ታግተው ገንዘብ ከፍለው የተመለሱ አሉ” ሲሉ ያስታወሱት አመራሩ፣ ጥቃቱ እየተደጋገመ መሆኑን አልደበቁም፡፡

ቀሪ ነዋሪዎች ዳግም እንዳይጠቁ ምን እየተሰራ እንደሆነ ሲያስረዱ ደግሞ፣ መከላከያ በቋሚነት በአካባቢው እንዲመደብ እንዳሳሰቡና ህዝቡ ራሱን እንዲከላከል አቅጣጫ እንደተቀመጠ ገልጸዋል፡፡

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
😭901651😡69💔31😢28🕊26🙏20🤔7😱4🥰3
#SocialMedia

የአሜሪካዋ ኒውዮርክ ከተማ ታላላቅ የሚባሉ የማህበራዊ ሚዲያዎችን ህፃናትን ሱስ በማስያዝ ከሳለች።

ከተማዋ ፌስቡክ፣ ጎግል፣ ስናፕቻትና እንደ ቲክቶክ ያሉ የማህበራዊ ሚዲያዎች ህፃናትን ሱስ በማስያዝ አዕምሯዊ ጤናቸውን እየጎዱ ነው በማለት 327 ገፅ ያለው ክስ በፍርድ ቤት አቅርባለች።

በኒውዮርክ ከተማ ከሚኖሩ 8 ሚሊየን ሰዎች ውስጥ 1.8 ሚሊየኑ ህፃናት ናቸው።

የጎግል ቃለ አቀባይ በዩቲዩብ ላይ የተከፈተው ክስ ትክክል አይደለም ሲሉ ዩቲዩብ ሰዎች ቪዲዮ የሚያዩበት እንጂ ከጓደኞቻቸው ጋር የሚገናኙበት የማህበራዊ ሚዲያ አይደለም ብለዋል።

በክሱ 77.3% የሚሆኑት በኒውዮርክ የሚኖሩ የሁለተኛ ደረጃ ተማሪዎች በቀን ከሶስት ሰዓት በላይ በስክሪን ላይ እንደሚያጠፉ ተገልፆ ይህም የተማሪዎቹን ጤና እየጎዳ ነው ተብሏል።

ከዚሁ ከማህበራዊ ሚዲያ ጋር በተያያዘ ዜና ዴንማርክ ከ15 ዓመት በታች ያሉ ህፃናት ማህበራዊ ሚዲያዎችን እንዳይጠቀሙ እገዳ ለማስቀመጥ እየሰራች ነው።

የዴንማርክ ጠቅላይ ሚኒስትር ሜት ፍሬድሪክሰን ማህበራዊ ሚዲያዎች" የልጆቻችንን ህፃንነት እየሰረቁ" ነው ብለዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትሯ የሃገሪቱ ህግ አውጪዎች ከ15 አመት በታች ያሉ ህፃናት ማህበራዊ ሚዲያን እንዳይጠቀሙ እንዲከለክሉ ጠይቀዋል።

በአውሮፓ ህብረት ሃገራት ህፃናት 13 አመት ሳይሞላቸው የማህበራዊ ሚዲያ አካውንት መክፈት እንደማይችሉ ቢቀመጥም ጠቅላይ ሚኒስትሯ 94 በመቶ የዴንማርክ ህፃናት እዚህ ዕድሜ ላይ ሳይደርሱ ይከፍታሉ ብለዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትሯ " ህፃናት ማህበራዊ ሚዲያ ላይ ማየት የሌለባቸውን ነገሮች ያያሉ" ያሉ ሲሆን ይህም ጭንቀትና ድብርትን ጨምሮ ሌሎቸ መዘዞችን እያዋለደ ነው ብለዋል።

ዘገባዎቹ የተገኙት ከዩሮ ኒውስና ከአሌጄዘራ ነው።

Via @TikvahethMagazine
1.18K👏173🙏48😭21😡19🤔17🕊15😢8😱5💔2
#Afar #Tigray

ዛሬ በትግራይ እና አፋር ክልል የተለያዩ አካባቢዎች ተደጋግሞ የተሰማ የመሬት መንቀጥቀጥ ንዝረት ተከስቷል።

የአሜሪካ ጂኦሎጂካል ሰርቬይ ይፋ ባደረገው መረጃ በተደጋጋሚ የመሬት መንቀጥቀጥ ንዝረት ተሰምቷል።

የመጀመሪያው ከመቐለ ሰሜን ምስራቅ 47 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ 4.2 በሬክተር ስኬል የተለካ የመሬት መንቀጥቀጥ ተከስቶ ነበር ፤ ንዝረቱ በተለያዩ የትግራይ እና አፋር አካባቢዎች ተሰምቷል።

ከዚህ ቀጥሎ ከመቐለ ሰሜን ምስራቅ 58 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ 5.3 በሬክተር ስኬል የተለካ የመሬት መንቀጥቀጥ ተከስቶ ንዝረቱ መቐለን ጨምሮ በርካታ ከተሞች ተሰምቷል።

ቅርብ ሰዓት ደግሞ በሬክተር ስኬል 5.6 የተለካ የመሬት መንቀጥቀጥ ከመቐለ ሰሜን ምስራቅ 53 ኪሎ ሜትር ላይ ተከስቶ ነበር።

@tikvahethiopia
2😢600516🙏128🕊63😭57💔28😱26🥰12🤔10😡6👏2
" የውሃ አገልግሎት በከፊል እና ሙሉ ለሙሉ ስለሚቋረጥ አስፈላጊውን ቅድመ ዝግጅት አድርጉ " - ውሃ እና ፍሳሽ ባለሥልጣን

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ውሃ እና ፍሳሽ ባለሥልጣን የለገዳዲ ግድብ የጥሬ ውሃ ማስተላለፊያ ቫልቭ ቅየራ ስራ ከጥቅምት 2/2018 ዓም እስከ ጥቅምት 16/2018 ዓም ድረስ የሚከናወን መሆኑን ገልጿል።

የጥገና ስራው እስከሚጠናቀቅም በአንዳንድ የከተማዋ አካባቢዎች የውሃ አገልግሎት በከፊል እና ሙሉ በሙሉ የሚቋረጥ ይሆናል ብሏል።

የውሃ አገልግሎት በከፊል የሚቋረጥባቸው አካባቢዎች :-

- በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ወረዳ 2፣ 3፣ 5፣ 8፣ 9፣ 10 እና 13

- በቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 1፣ 2፣ 3፣ 4፣ 5፣ 6፣ 7፣ 11፣ 13 እና14

- በቂርቆስ ክፍለ ከተማ ወረዳ 1፣ 2፣ 3፣ 7፣ 8፣ 10 እና 11

ስራው እስከሚጠናቀቅ የውሃ አገልግሎት በከፊል እና ሙሉ ለሙሉ ስለሚቋረጥ አስፈላጊውን ቅድመ ዝግጅት እንድታደርጉ ሲል ባለሥልጣኑ አሳስቧል።

Credit - AAWSA

@tikvahethiopia
1.11K😡395😭119😢65👏42🤔41🙏30🕊24💔20😱14🥰3
TIKVAH-ETHIOPIA
" በተለያዩ ማስታወቂያዎች የሚጭበረበረውን ማኅበረሰብ መጠበቅ ኃላፊነታችን ነው " - ወ/ሮ ትዕግስት ሃሚድ የሳይበር ደኅንነት ወር " የሳይበር ደኅንነት - የዲጂታል ኢትዮጵያ መሰረት " በሚል መሪ ቃል ለ6ኛ ጊዜ በሀገር አቀፍ ደረጃ ከጥቅምት 1 - 30 እንደሚከበር የኢንፎርሜሽን መረብ ደኅንነት አስተዳደር አስታውቋል። የአስተዳደሩ ዋና ዳይሬክተር ወ/ሮ ትዕግስት ሃሚድ በዚህ ዓመት በሁለት ዋና ዋና…
ፎቶ ፦ 6ተኛው ሀገር አቀፍ የሳይበር ደህንነት ወር ትላንት ተጀምሯል።

ወሩ “የሳይበር ደህንነት - የዲጂታል ኢትዮጵያ መሰረት” በሚል መሪ ቃል ነው የሚከበረው።

የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር በኢትዮጵያ የቴክኖሎጂ ተጠቃሚነት ከማደጉ ጋር ተያይዞ በዜጎች፣ በተቋማት እና ቁልፍ መሰረተ ልማቶች ላይ የሚደርሰው የሳይበር ጥቃት በከፍተኛ ሁኔታ ጨምሯል ብሏል።

የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር (ኢመደአ) ዋና ዳይሬክተር ወ/ሮ ትዕግስት ሃሚድ ምን አሉ ?

" ከጥቅምት 1-30/2018 ዓ.ም 6ኛውን ሀገር አቀፍ የሳይበር ደህንነት ወር ይከበራል።

የሳይበር ደህንነት ወሩ የሚከበረው የተቋማትን እና የኅብረተሰቡን የሳይበር ደህንነት ንቃተ-ህሊና በማጎልበት ለሳይበር ደህንነት ተገቢ ትኩረት እንዲሰጡ ለማስቻል ነው።

ወሩ ሲከበር  የሃሰተኛ መረጃ ዝግጅትና ስርጭት መከላከል ላይ እና ዲጂታላይዜሽን እንዲሁም የሳይበር ደህንነት ላይ የሚያተኩር ይሆናል " ብለዋል።

የጥቅምት ወርን ሙሉ ቀናት የሕብረተሰቡንና የተቋማትን የሳይበር ደህንነት ንቃተ ሕሊና የሚያጎለብቱ ስራዎች እንደሚሰሩ ተገልጿል።

የሳይበር ደህንነት ወር በዓለም አቀፍ ደረጃ ዘንድሮ ለ22ኛ ጊዜ የሚከበር ሲሆን በኢትዮጵያ ለ6ኛ ጊዜ ነው መከበር የጀመረው።

ፎቶ ፦ INSA

@tikvahethiopia
387😡24🙏12😱7🤔6🕊6😭6🥰4😢1
2025/10/23 08:17:05
Back to Top
HTML Embed Code: