🌟 የአሜሪካ ደርሶ መልስ ትኬት መግዣን ጨምሮ የተለያዩ አጓጊ ሸልማቶችን ከ11% የገንዘብ ስጦታ ጋር ይሸለሙ!!
የግራንድ አፍሪካ ሩጫን አስመልክቶ እስከ ጥቅምት 21 ቀን 2018 ዓ.ም ከአሜሪካ በቴሌብር ሬሚት እና በአጋሮቻችን በኩል የተላከልዎን ዓለም አቀፍ ሐዋላ በቴሌብር ሲቀበሉ 11% የገንዘብ ስጦታ ያገኛሉ።
በተጨማሪ 300 ዶላር እና ከዚያ በላይ ሲቀበሉ
✈️ 💰 300ሺህ ብር አሜሪካ ደርሶ መልስ ነጻ የበረራ ትኬት
💻 ላፕቶፕ ኮምፒተሮች
📲 የስልክ ቀፎዎች
🌐 የብሮድባንድ ኢንተርኔት የ6 ወር ክፍያዎች
📶 ከ10,000 በላይ 1GB የሞባይል ዳታ ስጦታዎችን ለሚያሸልመው የዕድል ጨዋታ ብቁ ይሆናሉ!
ዕጣዎቹ ቴሌብር ሱፐርአፕ https://bit.ly/telebirr_SuperApp ላይ ከጥቅምት 22 እስከ ጥቅምት 28/2018 ዓ.ም ክፍት ይሆናሉ!
#Ethiotelecom #telebirr #telebirrSuperApp #DigitalEthiopia #DigitalAfrica #RealizingDigitalEthiopia
የግራንድ አፍሪካ ሩጫን አስመልክቶ እስከ ጥቅምት 21 ቀን 2018 ዓ.ም ከአሜሪካ በቴሌብር ሬሚት እና በአጋሮቻችን በኩል የተላከልዎን ዓለም አቀፍ ሐዋላ በቴሌብር ሲቀበሉ 11% የገንዘብ ስጦታ ያገኛሉ።
በተጨማሪ 300 ዶላር እና ከዚያ በላይ ሲቀበሉ
✈️ 💰 300ሺህ ብር አሜሪካ ደርሶ መልስ ነጻ የበረራ ትኬት
💻 ላፕቶፕ ኮምፒተሮች
📲 የስልክ ቀፎዎች
🌐 የብሮድባንድ ኢንተርኔት የ6 ወር ክፍያዎች
📶 ከ10,000 በላይ 1GB የሞባይል ዳታ ስጦታዎችን ለሚያሸልመው የዕድል ጨዋታ ብቁ ይሆናሉ!
ዕጣዎቹ ቴሌብር ሱፐርአፕ https://bit.ly/telebirr_SuperApp ላይ ከጥቅምት 22 እስከ ጥቅምት 28/2018 ዓ.ም ክፍት ይሆናሉ!
#Ethiotelecom #telebirr #telebirrSuperApp #DigitalEthiopia #DigitalAfrica #RealizingDigitalEthiopia
❤238😱6🥰5🕊4😡3😢2👏1
" በሚቀጥሉት ዓመታት የተማሪዎች ምደባ ይቆማል " - ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ
ትምህርት ሚኒስቴር በሚቀጥሉት ዓመታት የተማሪዎች ምደባ እንደሚያቆም ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሀኑ ነጋ አስታወቁ።
ይህ ያሳወቁት የትምህርት ሚኒስቴር ከመንግስት ዩኒቨርስቲዎች ጋር የ2018 ዓ.ም የትምህርት ዘመን የቁልፍ ተግባራት የፊርማ ስነስርዓት ባከናወነበት ወቅት ነው።
በዚሁ ወቅት ፕሮፌሰር ብርሀኑ ነጋ ጠንካራ የስራ አቅጣጫ አስቀምጠዋል፡፡
ፕሮፌሰር ብርሀኑ ነጋ እንደገለፁት፤ በሚቀጥሉት ዓመታት የትምህርት ሚኒስቴር የተማሪዎችን ምደባ እንደሚያቆምና የማለፊያ ነጥብ የሚያስመዘግቡ ተማሪዎች በሚፈልጓቸው ዩኒቨርሲቲዎችና የትምህርት መስኮች እንዲያመለክቱ ይደረጋል፡፡
" የዩኒቨርሲቲ ትምህርት እንደከዚህ ቀደሙ በትምህርት ሚኒስቴር ምደባ ሳይሆን በተማሪዎቹ ምርጫ ይሆናል " ብለዋል።
" ተማሪዎች የሚማሩበትን ዩኒቨርሲቲ ሲመርጡም ምክንያታዊ በመሆን በዬትኛው ዩኒቨርሲቲ የተሻለ የትምህርት መስክ፣ እውቀትና የስራ እድል ላገኝ እችላለሁ በማለት ይመርጣሉ " ሲሉ ገልጸዋል። #ኢፕድ
@tikvahethiopia
ትምህርት ሚኒስቴር በሚቀጥሉት ዓመታት የተማሪዎች ምደባ እንደሚያቆም ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሀኑ ነጋ አስታወቁ።
ይህ ያሳወቁት የትምህርት ሚኒስቴር ከመንግስት ዩኒቨርስቲዎች ጋር የ2018 ዓ.ም የትምህርት ዘመን የቁልፍ ተግባራት የፊርማ ስነስርዓት ባከናወነበት ወቅት ነው።
በዚሁ ወቅት ፕሮፌሰር ብርሀኑ ነጋ ጠንካራ የስራ አቅጣጫ አስቀምጠዋል፡፡
ፕሮፌሰር ብርሀኑ ነጋ እንደገለፁት፤ በሚቀጥሉት ዓመታት የትምህርት ሚኒስቴር የተማሪዎችን ምደባ እንደሚያቆምና የማለፊያ ነጥብ የሚያስመዘግቡ ተማሪዎች በሚፈልጓቸው ዩኒቨርሲቲዎችና የትምህርት መስኮች እንዲያመለክቱ ይደረጋል፡፡
" የዩኒቨርሲቲ ትምህርት እንደከዚህ ቀደሙ በትምህርት ሚኒስቴር ምደባ ሳይሆን በተማሪዎቹ ምርጫ ይሆናል " ብለዋል።
" ተማሪዎች የሚማሩበትን ዩኒቨርሲቲ ሲመርጡም ምክንያታዊ በመሆን በዬትኛው ዩኒቨርሲቲ የተሻለ የትምህርት መስክ፣ እውቀትና የስራ እድል ላገኝ እችላለሁ በማለት ይመርጣሉ " ሲሉ ገልጸዋል። #ኢፕድ
@tikvahethiopia
1❤3.84K👏1.01K😡192🤔114😱96😭81🙏58🕊37😢34💔26🥰24
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#Ethiopia
በተፈጥሮ ጋዝ የሚሰሩ ማናቸውም አይነት የደረቅና የፈሳሽ ጭነት እንዲሁም የህዝብ ማመላለሻ ተሽከርካሪዎች ከጉምሩክ ቀረጥ ነጻ ወደ ሀገር እንዲገቡ መፈቀዱን የገንዘብ ሚኒስቴር አሳውቋል።
" ኢትዮጵያ ከፍተኛ መጠን ያለው የተፈጥሮ ጋዝ ክምችት ያላት መሆኑ ቢታወቅም ለዘመናት የዚህ የተፈጥሮ ሃብት ተጠቃሚ ሳትሆን ቆይታለች " ያለው ሚኒስቴሩ " ይህንን ሁኔታ ለመለወጥ መንግስት ሲያደርግ የቆየው እልህ አስጨራሽ ጥረት ተሳክቶ በቅርቡ በካሉብ አካባቢ የሚገኘውን የተፈጥሮ ጋዝ ጥቅም ላይ ማዋል የሚያስችል ኢንዱስትሪ ተመርቆ የተፈጥሮ ጋዝ የማምረት ስራ በይፋ ተጀምሯል " ብሏል።
" ይህን ምርት ለሀገር ውስጥ ገበያ በማቅረብ ቤንዚንና ናፍታ የሚጠቀሙ ተሽከርካሪዎችን የተፈጥሮ ጋዝ በሚጠቀሙ ተሽከርካሪዎች መተካት አስፈላጊ ሆኖ ተገኝቷል " ሲል ገልጿል።
" የተፈጥሮ ጋዝ የሚያመነጨው በካይ አየር እጅግ በጣም ዝቅተኛ የሆነ፤ ለተለያየ የኃይል ምንጭ አገልግሎት ሊውል የሚችል፤ በኃይል አጠቃቀም ረገድ ውጤታማነት ያለው ነው " ብሏል።
" የተፈጥሮ ጋዝ በኢትዮጵያ የሚመረት በመሆኑ ለነዳጅ ግዥ ታወጣ የነበረውን የውጭ ምንዛሬ የሚያስቀር በመሆኑ መንግስት የተፈጥሮ ጋዝ አጠቃቀምን ለማበረታታት ወስኗል፤ በዚህም መሰረት ይህ መመሪያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ሙሉ በሙሉ በተፈጥሮ ጋዝ የሚሰሩ ማናቸውም አይነት የደረቅ እና የፈሳሽ ጭነት እና የህዝብ ማመላለሻ ተሽከርካሪዎች ከጉምሩክ ቀረጥ ነጻ ወደ ሀገር እንዲገቡ ተፈቅዷል " ሲል አሳውቋል።
ይህ መመሪያ ከወጣበት ቀን በፊት በትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር እና በሌሎች ተቋማት ወደ ሀገር እንዲገቡ ከተፈቀደላቸውና በስድስት ወር ጊዜ ውስጥ ወደ ሀገር ከሚገቡት በስተቀር በቤንዚን እና በናፍጣ የሚሰሩ የጭነት እና የህዝብ ማመላለሻ ተሽከርካሪዎች ወደ ሀገር እንዳይገቡ ጥብቅ ቁጥጥር እንዲደረግ ሚኒስቴሩ አዟል።
@tikvahethiopia
በተፈጥሮ ጋዝ የሚሰሩ ማናቸውም አይነት የደረቅና የፈሳሽ ጭነት እንዲሁም የህዝብ ማመላለሻ ተሽከርካሪዎች ከጉምሩክ ቀረጥ ነጻ ወደ ሀገር እንዲገቡ መፈቀዱን የገንዘብ ሚኒስቴር አሳውቋል።
" ኢትዮጵያ ከፍተኛ መጠን ያለው የተፈጥሮ ጋዝ ክምችት ያላት መሆኑ ቢታወቅም ለዘመናት የዚህ የተፈጥሮ ሃብት ተጠቃሚ ሳትሆን ቆይታለች " ያለው ሚኒስቴሩ " ይህንን ሁኔታ ለመለወጥ መንግስት ሲያደርግ የቆየው እልህ አስጨራሽ ጥረት ተሳክቶ በቅርቡ በካሉብ አካባቢ የሚገኘውን የተፈጥሮ ጋዝ ጥቅም ላይ ማዋል የሚያስችል ኢንዱስትሪ ተመርቆ የተፈጥሮ ጋዝ የማምረት ስራ በይፋ ተጀምሯል " ብሏል።
" ይህን ምርት ለሀገር ውስጥ ገበያ በማቅረብ ቤንዚንና ናፍታ የሚጠቀሙ ተሽከርካሪዎችን የተፈጥሮ ጋዝ በሚጠቀሙ ተሽከርካሪዎች መተካት አስፈላጊ ሆኖ ተገኝቷል " ሲል ገልጿል።
" የተፈጥሮ ጋዝ የሚያመነጨው በካይ አየር እጅግ በጣም ዝቅተኛ የሆነ፤ ለተለያየ የኃይል ምንጭ አገልግሎት ሊውል የሚችል፤ በኃይል አጠቃቀም ረገድ ውጤታማነት ያለው ነው " ብሏል።
" የተፈጥሮ ጋዝ በኢትዮጵያ የሚመረት በመሆኑ ለነዳጅ ግዥ ታወጣ የነበረውን የውጭ ምንዛሬ የሚያስቀር በመሆኑ መንግስት የተፈጥሮ ጋዝ አጠቃቀምን ለማበረታታት ወስኗል፤ በዚህም መሰረት ይህ መመሪያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ሙሉ በሙሉ በተፈጥሮ ጋዝ የሚሰሩ ማናቸውም አይነት የደረቅ እና የፈሳሽ ጭነት እና የህዝብ ማመላለሻ ተሽከርካሪዎች ከጉምሩክ ቀረጥ ነጻ ወደ ሀገር እንዲገቡ ተፈቅዷል " ሲል አሳውቋል።
ይህ መመሪያ ከወጣበት ቀን በፊት በትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር እና በሌሎች ተቋማት ወደ ሀገር እንዲገቡ ከተፈቀደላቸውና በስድስት ወር ጊዜ ውስጥ ወደ ሀገር ከሚገቡት በስተቀር በቤንዚን እና በናፍጣ የሚሰሩ የጭነት እና የህዝብ ማመላለሻ ተሽከርካሪዎች ወደ ሀገር እንዳይገቡ ጥብቅ ቁጥጥር እንዲደረግ ሚኒስቴሩ አዟል።
@tikvahethiopia
❤1.3K👏121🙏46😭35😡34🤔30🕊18💔16🥰11😢1
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#Ethiopia
በቤንዚን እና በናፍጣ የሚሰሩ ከባድ ተሽከርካሪዎች ወደ ሀገር እንዳይገቡ ተከልክሏል።
በተፈጥሮ ጋዝ የሚሰሩ የጭነትና የህዝብ ማመላለሻ ተሽከርካሪዎች ከጉምሩክ ቀረጥ ነፃ እንዲገቡ መመሪያ ወጥቷል።
ይህ መመሪያ ከወጣበት ቀን በፊት በትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር እና በሌሎች ተቋማት ወደ ሀገር እንዲገቡ ከተፈቀደላቸውና በስድስት ወር ጊዜ ውስጥ ወደ ሀገር ከሚገቡት በስተቀር በቤንዚን እና በናፍጣ የሚሰሩ የጭነት እና የህዝብ ማመላለሻ ተሽከርካሪዎች ወደ ሀገር እንዳይገቡ ክልከላ ተላልፏል።
@tikvahethiopia
በቤንዚን እና በናፍጣ የሚሰሩ ከባድ ተሽከርካሪዎች ወደ ሀገር እንዳይገቡ ተከልክሏል።
በተፈጥሮ ጋዝ የሚሰሩ የጭነትና የህዝብ ማመላለሻ ተሽከርካሪዎች ከጉምሩክ ቀረጥ ነፃ እንዲገቡ መመሪያ ወጥቷል።
ይህ መመሪያ ከወጣበት ቀን በፊት በትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር እና በሌሎች ተቋማት ወደ ሀገር እንዲገቡ ከተፈቀደላቸውና በስድስት ወር ጊዜ ውስጥ ወደ ሀገር ከሚገቡት በስተቀር በቤንዚን እና በናፍጣ የሚሰሩ የጭነት እና የህዝብ ማመላለሻ ተሽከርካሪዎች ወደ ሀገር እንዳይገቡ ክልከላ ተላልፏል።
@tikvahethiopia
2❤701😡170👏78😢30🕊23🙏22😭21🤔16😱16💔6🥰5
TIKVAH-ETHIOPIA
" በሚቀጥሉት ዓመታት የተማሪዎች ምደባ ይቆማል " - ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ትምህርት ሚኒስቴር በሚቀጥሉት ዓመታት የተማሪዎች ምደባ እንደሚያቆም ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሀኑ ነጋ አስታወቁ። ይህ ያሳወቁት የትምህርት ሚኒስቴር ከመንግስት ዩኒቨርስቲዎች ጋር የ2018 ዓ.ም የትምህርት ዘመን የቁልፍ ተግባራት የፊርማ ስነስርዓት ባከናወነበት ወቅት ነው። በዚሁ ወቅት ፕሮፌሰር ብርሀኑ ነጋ ጠንካራ የስራ አቅጣጫ…
#MoE
ዩኒቨርሲቲዎች ስለተማሪዎቻቸው ትክክለኛ መረጃ ካላቀረቡ ፕሬዝዳንቱን ጨምሮ ሀላፊዎቻቸው ከስራ ይባረራሉ ተባለ።
የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በቀጣይ 6 ወራት ዩኒቨርሲቲዎች ስለተማሪዎቻቸውና ሌሎችም ጉዳዮች መረጃ በትክክል ለትምህርት ሚኒስቴር ማቅረብ አለባቸው ብለዋል።
ይህንን ያላደረገ የዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት በስራው አይቀጥልም ሲሉ አስጠንቅቀዋል።
" ይህንን ስራ እኔ በቀጥታ እከታተለዋለሁ " ማለታቸውን ሸገር ኤፍ ኤም ዘግቧል።
ከወራት በፊት ሚኒስትሩ " ዩኒቨርሲቲዎች ተማሪዎቻቸውን ከነፎቶ እንዲሁም ስለሚሠሩት ሥራ ትክክለኛ መረጃ ስጡን ብለን ከጠየቅን ሦስት ዓመት አልፎናል፡፡ ሆኖም እስካሁን የተሟላ መረጃ ለማግኘት ችግር ሆኖብናል፡፡ በዩኒቨርሲቲዎች ዘንድ እውነተኛ መረጃ መስጠት አልተለመደም " ማለታቸው ይታወሳል።
ዩኒቨርስቲዎች ከተማሪዎች ምገባ ጋር ተያይዞ የውሸት ሪፖርት ያቀርቡ እንደነበር ዩኒቨርሲቲዎች የተማሪ ቁጥር በውሸት በመጨመር በጀት እንዲጨመርላቸው ያደርጉም እንደበር ተናግረው ነበር።
#TikvahEthiopiaFamily
@tikvahethiopia
ዩኒቨርሲቲዎች ስለተማሪዎቻቸው ትክክለኛ መረጃ ካላቀረቡ ፕሬዝዳንቱን ጨምሮ ሀላፊዎቻቸው ከስራ ይባረራሉ ተባለ።
የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በቀጣይ 6 ወራት ዩኒቨርሲቲዎች ስለተማሪዎቻቸውና ሌሎችም ጉዳዮች መረጃ በትክክል ለትምህርት ሚኒስቴር ማቅረብ አለባቸው ብለዋል።
ይህንን ያላደረገ የዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት በስራው አይቀጥልም ሲሉ አስጠንቅቀዋል።
" ይህንን ስራ እኔ በቀጥታ እከታተለዋለሁ " ማለታቸውን ሸገር ኤፍ ኤም ዘግቧል።
ከወራት በፊት ሚኒስትሩ " ዩኒቨርሲቲዎች ተማሪዎቻቸውን ከነፎቶ እንዲሁም ስለሚሠሩት ሥራ ትክክለኛ መረጃ ስጡን ብለን ከጠየቅን ሦስት ዓመት አልፎናል፡፡ ሆኖም እስካሁን የተሟላ መረጃ ለማግኘት ችግር ሆኖብናል፡፡ በዩኒቨርሲቲዎች ዘንድ እውነተኛ መረጃ መስጠት አልተለመደም " ማለታቸው ይታወሳል።
ዩኒቨርስቲዎች ከተማሪዎች ምገባ ጋር ተያይዞ የውሸት ሪፖርት ያቀርቡ እንደነበር ዩኒቨርሲቲዎች የተማሪ ቁጥር በውሸት በመጨመር በጀት እንዲጨመርላቸው ያደርጉም እንደበር ተናግረው ነበር።
#TikvahEthiopiaFamily
@tikvahethiopia
❤1.66K👏371😡69😱38🤔33🥰27🙏27😭24🕊13😢11💔8
" አራት አርሶ አደሮችን ከቤት በማውጣት በጥይት ደብድበው ገድለዋል፤ 10 ሰዎች አግተው ወስደዋል" - ነዋሪዎች
➡️ " የስንት ሰው ሕይወት አለፈ የሚለውን ዝርዝር መረጃ ገና እያጣራን ነው ያለነው " - የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሰላምና ጸጥታ ቢሮ
በምሥራቅ ጉራጌ ዞን ሶዶ ወረዳ ታጣቂዎች አደረሱት በተባለ ጥቃት በንጹሐንና በቤት ላይ ጉዳት መድረሱን የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሰላምና ጸጥታ ቢሮ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጿል፡፡
የአካባቢው ነዋሪዎች ታጣቂዎች ትላንት በፈጸሙት ጥቃት ንጹሐን መገዳቸውን የገለጹ ሲሆን፣ ስለጉዳዩ ማብራሪያ የጠየቅናቸው የቢሮው ኃላፊ አቶ ተመስገን ካሳ በበኩላቸው፣ ጥቃት ተፈጽሟል መባሉ እውነት መሆኑን አረጋግጠዋል፡፡
" የሸኔ ጽንፈኞች ትላንትና ማምሻውን በሰዶ ወረዳ ሰመሮ አካባቢ ገብተው እየተታኮሱ እንደነበርና ቤቶች ላይም ጉዳት እንዳደረሱ መረጃው አለን " ብለዋል፡፡
" የስንት ሰው ሕይወት አለፈ የሚለውን ዝርዝር መረጃ ገና እያጣራን ነው ያለነው " ሲሉም አክለዋል፡፡
ታጣቂዎች በተለያዩ ጊዜያቶች እንደዚህ አይነት ጥቃቶችን ሰነዘሩ ሲባል ይደመጣል፤ ጉዳዩ መፍትሄ እንዲያገኝ ምን እየተሰራ እንደሆነ ስንጠይቃቸውም፣ " ይሄኮ ታጣቂ አይደለም፤ ጽንፈኛ ሸኔ ነው ሌላ የመንግስት ታጣቂ አይደለም ጉዳት እያደረሰ ያለው " ብለዋል፡፡
" አሳቻ ሰዓት ተጠቅሞ ነው ይህ ድርጊት ፈጸመ የሚል መረጃ ደረሰን " ያሉት ኃላፊው፣ ስለዝርዝር ጉዳቱን ገና መረጃዎች እያጣሩ እንደሆነና በአካባቢው ተመሳሳይ ችግር እንዳይፈጠር ጥበቃ የማጠናከር ሥራ እየተሰራ መሆኑን አስረድተዋል፡፡
የአካባቢው ነዋሪዎች በበኩላቸው፣ ታጣቂዎች ትላንት 12 ሰዓት ገደማ ባደረሱት ጥቃት አራት ሰዎች ተገድለው አሥር ደግሞ ታግተዋል ማለታቸውን ዶቼቨሌ ዘግቧል፡፡
ሦስት ነዋሪዎች፣ ከአጎራባች የኦሮሚያ ክልል ደቡብ ምዕራብ ሸዋ ዞን የተሻገሩ ናቸው ያሏቸው ታጣቂዎች እየተኮሱ መንደሩን መክበባቸውን ተናግረው፣ " አራት አርሶ አደሮችን ከቤት በማውጣት በጥይት ደብድበው ገድለዋል " ነው ያሉት፡፡
ሌሎች ነዋሪዎች ተደናግጠው ከመንደሩ ሲሸሹም " 15 የመኖሪያ ጎጆዎችን በእሳት አቃጥለዋል፡፡ ማምለጥ ያልቻሉ ሴቶችና ህጻናትን ጨምሮ 10 ሰዎችን አግተው ወስደዋል " ሲሉም ነዋሪዎቹ ተናግረዋል፡፡
የአራቱን አስከሬን ዛሬ እንደቀበሩና የታገቱት ደግሞ ይኑሩ ይሙቱ እንደማይታወቅ ገልጸዋል፡፡
(ጉዳዩን የምንከታተለው ይሆናል)
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
➡️ " የስንት ሰው ሕይወት አለፈ የሚለውን ዝርዝር መረጃ ገና እያጣራን ነው ያለነው " - የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሰላምና ጸጥታ ቢሮ
በምሥራቅ ጉራጌ ዞን ሶዶ ወረዳ ታጣቂዎች አደረሱት በተባለ ጥቃት በንጹሐንና በቤት ላይ ጉዳት መድረሱን የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሰላምና ጸጥታ ቢሮ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጿል፡፡
የአካባቢው ነዋሪዎች ታጣቂዎች ትላንት በፈጸሙት ጥቃት ንጹሐን መገዳቸውን የገለጹ ሲሆን፣ ስለጉዳዩ ማብራሪያ የጠየቅናቸው የቢሮው ኃላፊ አቶ ተመስገን ካሳ በበኩላቸው፣ ጥቃት ተፈጽሟል መባሉ እውነት መሆኑን አረጋግጠዋል፡፡
" የሸኔ ጽንፈኞች ትላንትና ማምሻውን በሰዶ ወረዳ ሰመሮ አካባቢ ገብተው እየተታኮሱ እንደነበርና ቤቶች ላይም ጉዳት እንዳደረሱ መረጃው አለን " ብለዋል፡፡
" የስንት ሰው ሕይወት አለፈ የሚለውን ዝርዝር መረጃ ገና እያጣራን ነው ያለነው " ሲሉም አክለዋል፡፡
ታጣቂዎች በተለያዩ ጊዜያቶች እንደዚህ አይነት ጥቃቶችን ሰነዘሩ ሲባል ይደመጣል፤ ጉዳዩ መፍትሄ እንዲያገኝ ምን እየተሰራ እንደሆነ ስንጠይቃቸውም፣ " ይሄኮ ታጣቂ አይደለም፤ ጽንፈኛ ሸኔ ነው ሌላ የመንግስት ታጣቂ አይደለም ጉዳት እያደረሰ ያለው " ብለዋል፡፡
" አሳቻ ሰዓት ተጠቅሞ ነው ይህ ድርጊት ፈጸመ የሚል መረጃ ደረሰን " ያሉት ኃላፊው፣ ስለዝርዝር ጉዳቱን ገና መረጃዎች እያጣሩ እንደሆነና በአካባቢው ተመሳሳይ ችግር እንዳይፈጠር ጥበቃ የማጠናከር ሥራ እየተሰራ መሆኑን አስረድተዋል፡፡
የአካባቢው ነዋሪዎች በበኩላቸው፣ ታጣቂዎች ትላንት 12 ሰዓት ገደማ ባደረሱት ጥቃት አራት ሰዎች ተገድለው አሥር ደግሞ ታግተዋል ማለታቸውን ዶቼቨሌ ዘግቧል፡፡
ሦስት ነዋሪዎች፣ ከአጎራባች የኦሮሚያ ክልል ደቡብ ምዕራብ ሸዋ ዞን የተሻገሩ ናቸው ያሏቸው ታጣቂዎች እየተኮሱ መንደሩን መክበባቸውን ተናግረው፣ " አራት አርሶ አደሮችን ከቤት በማውጣት በጥይት ደብድበው ገድለዋል " ነው ያሉት፡፡
ሌሎች ነዋሪዎች ተደናግጠው ከመንደሩ ሲሸሹም " 15 የመኖሪያ ጎጆዎችን በእሳት አቃጥለዋል፡፡ ማምለጥ ያልቻሉ ሴቶችና ህጻናትን ጨምሮ 10 ሰዎችን አግተው ወስደዋል " ሲሉም ነዋሪዎቹ ተናግረዋል፡፡
የአራቱን አስከሬን ዛሬ እንደቀበሩና የታገቱት ደግሞ ይኑሩ ይሙቱ እንደማይታወቅ ገልጸዋል፡፡
(ጉዳዩን የምንከታተለው ይሆናል)
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
😭803❤585😡55💔36🕊24🙏21🤔13😢8😱6🥰5👏5
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
" አሽከርካሪው ' ቁም ' የሚል የፖሊስ ትእዛዝ ጥሶ ቢያመልጥም መኪናው በጥይት ተመቶ ቆሟል " - ፖሊስ
የትግራይ ደቡባዊ ምስራቅ ዞን ፓሊስ እንዳስታወቀው ሀሙስ መስከረም 29/2018 ዓ.ም ሌሊት በአንድ አይስዙ የተጨኑና ለህገወጥ ስደት ከቤታቸው የወጡ 67 ወጣቶችን በቁጥጥር ስር እንዳዋለ ገልጿል።
አዘዋዋሪዎቹ አልተያዙም።
ወዴት ቦታና አቅጣጫ በመጓዝ እያሉ እንደተያዙ ያልገለፀው ፓሊስ ሰው አዘዋዋሪዎቹ አይስዙው ላይ ጥለዋቸው መጥፋታቸውን አስታውቋል።
የመኪናው አሽከርካሪ ጨለማ ተገን አድርጎ እያሽከረከረ እያለ " ቁም " የሚል የፓሊስ ትእዛዝ ጥሶ ቢያመልጥም መኪናዋ በጥይት ተመትታ ለመቆም ችላለች።
ወጣቶቹ " አዛዋዋሪዎቹ ' መስከረም 29/2018 ዓ.ም ከሌሊቱ 7:00 ሰዓት ኬላ ሳትፈተሹ ታልፋላችሁ ' በማለት አጓጉዘውናል " በማለት ለፓሊስ ቃላቸውን ሰጥተዋል።
ወጣቶች በህገ-ወጥ ደላሎች የሚካሄድ ህገ-ወጥ ስደት እንዲፀየፉ ያሳሰበው ፓሊስ ፤ ሰው አዘዋዋሪዎቹ እንዲያዙ የህዝብ ትብብር ጠይቋል።
#TikvahEthiopiaFamilyMekelle
@tikvahethiopia
የትግራይ ደቡባዊ ምስራቅ ዞን ፓሊስ እንዳስታወቀው ሀሙስ መስከረም 29/2018 ዓ.ም ሌሊት በአንድ አይስዙ የተጨኑና ለህገወጥ ስደት ከቤታቸው የወጡ 67 ወጣቶችን በቁጥጥር ስር እንዳዋለ ገልጿል።
አዘዋዋሪዎቹ አልተያዙም።
ወዴት ቦታና አቅጣጫ በመጓዝ እያሉ እንደተያዙ ያልገለፀው ፓሊስ ሰው አዘዋዋሪዎቹ አይስዙው ላይ ጥለዋቸው መጥፋታቸውን አስታውቋል።
የመኪናው አሽከርካሪ ጨለማ ተገን አድርጎ እያሽከረከረ እያለ " ቁም " የሚል የፓሊስ ትእዛዝ ጥሶ ቢያመልጥም መኪናዋ በጥይት ተመትታ ለመቆም ችላለች።
ወጣቶቹ " አዛዋዋሪዎቹ ' መስከረም 29/2018 ዓ.ም ከሌሊቱ 7:00 ሰዓት ኬላ ሳትፈተሹ ታልፋላችሁ ' በማለት አጓጉዘውናል " በማለት ለፓሊስ ቃላቸውን ሰጥተዋል።
ወጣቶች በህገ-ወጥ ደላሎች የሚካሄድ ህገ-ወጥ ስደት እንዲፀየፉ ያሳሰበው ፓሊስ ፤ ሰው አዘዋዋሪዎቹ እንዲያዙ የህዝብ ትብብር ጠይቋል።
#TikvahEthiopiaFamilyMekelle
@tikvahethiopia
❤659😭223😡33🙏24😢20👏18🕊17🤔10😱9🥰6
TIKVAH-ETHIOPIA
አዲሱ የተሽከርካሪ ሰሌዳ የኢትዮጵያ ሰንደቅ አላማ ለምን አልተካተተበትም ? (ቲክቫህ ኢትዮጵያ - Tikvah Ethiopia) አዲሱ የተሽከርካሪ መለያ ሰሌዳ ቁጥር (ታርጋ) የኢትዮጵያ አለም አቀፍ መለያ ኮድ "ETH" ፣ የኢትዮጵያ ካርታ ፣ ጦር እና ጋሻ ወይም የአድዋ ምልክት በግልጽ እና በአንጸባራቂ መብራት በመታገዝ በሚታይ መልኩ ቢኖረውም የኢትዮጵያ ሰንደቅ አላማ ግን አልተካተተበትም። የኢትዮጵያን…
አዲሱን የተሽከርካሪ መለያ ሰሌዳ (ታርጋ) ለመቀየር ስንት ነው የሚከፈለው ?
አዲሱ የተሽከርካሪ መለያ ሰሌዳ (ታርጋ) በሚቀየርበት ጊዜ ወጪውን እራሳቸው የተሽከርካሪ ባለንብረቶች እንደሚሸፍኑት የትራንስፖርት እና ሎጅስቲክስ ሚኒስቴር ማሳወቁ ይታወሳል።
ክፍያውን በተመለከተ ግን እስካሁን ምን ያህል ይሁን የሚለው ተቆርጦ አልተቀመጠም ሲል ሚኒስቴሩ ገልጿል።
በሚኒስቴሩ አማካሪ የሆኑት የድልማግስት ኢብራሂም ለፋና ቴሌቪዥን በሰጡት ቃል " እስካሁን ክፍያው ተቆርጦ አልተቀመጠም። አሁን እየተሰራ ያለው ሲስተም የመዘርጋት ነው። ይህ ነው መጀመሪያ የሚጠናቀቀው " ብለዋል።
የተሽከርካሪ ባለንብረቶች እስከዛው የተሽከርካሪውን ሙሉ መረጃ አደራጅተው መጠበቅ እንዳለባቸው ጠቁመዋል።
ታርጋ በመቀየሩ ሂደት የምርመራ ማዕከላት እንደሚኖሩና ተሽከርካሪዎቹ ሄደው መመርመር እንዳለባቸው ፤ ተመርምረውም ህጋዊ ሰነዳቸውን ይዘው በሚወጣላቸው የጊዜ ሰሌዳ መሰረት ቀጥታ ሰሌዳቸውን እንደሚቀይሩ አስረድተዋል።
#ታርጋ #ኢትዮጵያ
@tikvahethiopia
አዲሱ የተሽከርካሪ መለያ ሰሌዳ (ታርጋ) በሚቀየርበት ጊዜ ወጪውን እራሳቸው የተሽከርካሪ ባለንብረቶች እንደሚሸፍኑት የትራንስፖርት እና ሎጅስቲክስ ሚኒስቴር ማሳወቁ ይታወሳል።
ክፍያውን በተመለከተ ግን እስካሁን ምን ያህል ይሁን የሚለው ተቆርጦ አልተቀመጠም ሲል ሚኒስቴሩ ገልጿል።
በሚኒስቴሩ አማካሪ የሆኑት የድልማግስት ኢብራሂም ለፋና ቴሌቪዥን በሰጡት ቃል " እስካሁን ክፍያው ተቆርጦ አልተቀመጠም። አሁን እየተሰራ ያለው ሲስተም የመዘርጋት ነው። ይህ ነው መጀመሪያ የሚጠናቀቀው " ብለዋል።
የተሽከርካሪ ባለንብረቶች እስከዛው የተሽከርካሪውን ሙሉ መረጃ አደራጅተው መጠበቅ እንዳለባቸው ጠቁመዋል።
ታርጋ በመቀየሩ ሂደት የምርመራ ማዕከላት እንደሚኖሩና ተሽከርካሪዎቹ ሄደው መመርመር እንዳለባቸው ፤ ተመርምረውም ህጋዊ ሰነዳቸውን ይዘው በሚወጣላቸው የጊዜ ሰሌዳ መሰረት ቀጥታ ሰሌዳቸውን እንደሚቀይሩ አስረድተዋል።
#ታርጋ #ኢትዮጵያ
@tikvahethiopia
❤640😡177🤔37😭32🕊24👏22😱9💔7😢4
TIKVAH-ETHIOPIA
አዲሱን የተሽከርካሪ መለያ ሰሌዳ (ታርጋ) ለመቀየር ስንት ነው የሚከፈለው ? አዲሱ የተሽከርካሪ መለያ ሰሌዳ (ታርጋ) በሚቀየርበት ጊዜ ወጪውን እራሳቸው የተሽከርካሪ ባለንብረቶች እንደሚሸፍኑት የትራንስፖርት እና ሎጅስቲክስ ሚኒስቴር ማሳወቁ ይታወሳል። ክፍያውን በተመለከተ ግን እስካሁን ምን ያህል ይሁን የሚለው ተቆርጦ አልተቀመጠም ሲል ሚኒስቴሩ ገልጿል። በሚኒስቴሩ አማካሪ የሆኑት የድልማግስት ኢብራሂም…
በአዲሱ ታርጋ ላይ የሚቀመጡት 3ቱ ፊደላት ምንድናቸው ? የታርጋ ቁጥሩስ እንዴት ነው የሚቀጥለው ?
በትራንስፖርት እና ሎጅስቲክስ ሚኒስቴር አማካሪ አቶ የድልማግስት ኢብራሂም (ለኤፍኤምሲ) ፦
" ሶስቱ ፊደላት የተቀመጡት ከዚህ ቀደም ከነበሩት ከቁጥሮች አያያዝ አንጻር ችግሮች አጋጥመውን ብዙ የተሽከርካሪ ቁጥርን ሰሌዳችን ሊመዘግብ ባለመቻሉ ምክንያት ነው።
ከዚህ ቀደም የነበረው ሰሌዳ 5 ነበር ቁጥሩ ከፊት ለፊት አልፋ ቤት አለው ያ አጠቃላይ ሆኖ 9 ሚሊዮን ሰሌዳዎችን ነው ሊይዝልን የሚችለው። አሁን 1.6 ሚሊዮን ሰሌዳዎችን መዝግበናል ግን እንለጥጠው ብንል 9 ሚሊዮን ሰሌዳ ብቻ ነው የሚችለው።
አሁን በመጣው ታርጋ አልፋቤቱና አራቱ ዲጅት እስከ 121 ሚሊዮን ተሽከርካሪ ድረስ መመዝገብ ይቻላል።
ለምሳሌ ፦ AAA0000 የሚለውን ታርጋ እንውሰድ። በቀኝ በኩል ያለችው ሶስተኛዋ A የምትቀየረው ቁጥሩ 9999 (AAA9999) በሚሆንበት ጊዜ ነው። ልክ AAA9999 ሲሆን AAA የነበረው ሰሌዳ ወደ AAB ይሄዳል። ልክ AAB ሲሆን 0001 ብሎ (AAB0001) ይቀጥላል። አሁንም AAB9999 ሲደርስ B ወደ C ትሄዳለች ማለትም AAC0001 ይሆናል። "
#ማሳያ ፦
የአዲሱ ታርጋ ቁጥር የሚሄደው በዚህ መልኩ ነው።
AAA0000
⬇️
AAA9999
⬇️
AAB0001
⬇️
AAB9999
⬇️
AAC0001
... እያለ ይቀጥላል።
#TikvahEthiopiaFamilyAA
#ቲክቫህ_ኢትዮጵያ
@tikvahethiopia
በትራንስፖርት እና ሎጅስቲክስ ሚኒስቴር አማካሪ አቶ የድልማግስት ኢብራሂም (ለኤፍኤምሲ) ፦
" ሶስቱ ፊደላት የተቀመጡት ከዚህ ቀደም ከነበሩት ከቁጥሮች አያያዝ አንጻር ችግሮች አጋጥመውን ብዙ የተሽከርካሪ ቁጥርን ሰሌዳችን ሊመዘግብ ባለመቻሉ ምክንያት ነው።
ከዚህ ቀደም የነበረው ሰሌዳ 5 ነበር ቁጥሩ ከፊት ለፊት አልፋ ቤት አለው ያ አጠቃላይ ሆኖ 9 ሚሊዮን ሰሌዳዎችን ነው ሊይዝልን የሚችለው። አሁን 1.6 ሚሊዮን ሰሌዳዎችን መዝግበናል ግን እንለጥጠው ብንል 9 ሚሊዮን ሰሌዳ ብቻ ነው የሚችለው።
አሁን በመጣው ታርጋ አልፋቤቱና አራቱ ዲጅት እስከ 121 ሚሊዮን ተሽከርካሪ ድረስ መመዝገብ ይቻላል።
ለምሳሌ ፦ AAA0000 የሚለውን ታርጋ እንውሰድ። በቀኝ በኩል ያለችው ሶስተኛዋ A የምትቀየረው ቁጥሩ 9999 (AAA9999) በሚሆንበት ጊዜ ነው። ልክ AAA9999 ሲሆን AAA የነበረው ሰሌዳ ወደ AAB ይሄዳል። ልክ AAB ሲሆን 0001 ብሎ (AAB0001) ይቀጥላል። አሁንም AAB9999 ሲደርስ B ወደ C ትሄዳለች ማለትም AAC0001 ይሆናል። "
#ማሳያ ፦
የአዲሱ ታርጋ ቁጥር የሚሄደው በዚህ መልኩ ነው።
AAA0000
⬇️
AAA9999
⬇️
AAB0001
⬇️
AAB9999
⬇️
AAC0001
... እያለ ይቀጥላል።
#TikvahEthiopiaFamilyAA
#ቲክቫህ_ኢትዮጵያ
@tikvahethiopia
❤2.69K👏318😡162🤔96🙏65🕊41💔40😭29🥰17😢16😱15
#AbayBank
ዓባይ ባንክ የ15ኛ ዓመት የምስረታ በዓሉን ምክንያት በማድረግ ከኢትዮጵያ ደም ባንክና የሕብረ ሕዋስ አገልግሎት ጋር በመተባበር በሀገር አቀፍ ደረጃ የደም ልገሳ መርሀ ግብር ማካሄድ ጀምሯል።
በደም ልገሳ ማስጀመሪያ መርሀ ግብሩ ላይ ንግግር ያደረጉት የዓባይ ባንክ የስትራቴጂ ዋና መኮንን አቶ ወንድይፍራው ታደስ በዛሬው እለት በአዲስ አበባ ከተማ ውስጥ በ6 ቅርንጫፎች ደም እየተለገሰ መሆኑን ገልጸዋል።
"በቀጣይ ሰኞም ደም ልገሳው ይቀጥላል፣ ወደ 90 የሚሆኑ ሰዎችም ደም ይለግሳሉ የሚል እቅድ አለን። በሀገር አቀፍ ደረጃ ከ600 በላይ ለጋሾች ደም ይለግሳሉ ብለን እናስባለን" ሲሉ ተናግረዋል።
አክለው በሁሉም ቅርንጫፍቻችን ከሚገኙ ሠራተኞቻችን፣ ደንበኞቻችንና ከመላው የባንካችን ቤተሰቦች ከተውጣጡ ከ1ሺህ በላይ በጎ ፈቃደኛ ደም ለጋሾችን በማንቀሳቀስ ለሕይወት አድን ዓላማ ቀጥተኛ አስተዋጽዖ በማድረጋችን ደስተኞች ነን ብለዋል፡፡
"ይህ የበጎ አድራጎት ሥራ የ15 ዓመት ጉዟችንን በድምቀት ለማክበርና ለማኅበራዊ ኃላፊነት ያለንን ዘላቂ ቁርጠኝነት ያጠናክራል" ሲሉ ነው የተናገሩት።
በዚህ መርሐግብር ላይ የተገኙት በኢትዮጵያ ደም ባንክና የሕብረ ሕዋስ አገልግሎት ውስጥ የደም ለጋሾች ተወካይ ደስክ ሃላፊ ሙላት በቀለ በበኩላቸው አባይ ባንክ በመላዊ ሀገሪቱ በሚገኙ ቅርንጫፎቹ የደም ልገሳ ፕሮግራም በማካሄድ የወገንን ህይወት እየታደገ ነው ሲሉ ተናግረዋል።
በባለፉት በዓላት ወቅት ከፍተኛ የሆነ የደም እጥረት ተከስቶ እንደነበር ያስታወሱት ሃላፊው "አባይ ባንክ እጥረቱን በመገንዘብ በዛሬው እለት ሰራተኞቹ ደም እንድለግሱ እያደረገ ነው። በሚተካ ደም የማይተካውን የሰው ልጅ ህይወት ለማዳን ፕሮግራሙን በማዘጋጀቱም ደስ ብሎናል" ሲሉ ነው የገለጹት።
አባይ ባንክ ከ71 ቢሊዮን በላይ ተቀማጭ ገንዘብ፣ 7 ቢሊዮን ብር የተከፈለ ካፒታል እንዲሁም ጠቅላላ ሀብቱ 91 ቢሊዮን ብር መድረሱም ተነስቷል።
#ዓባይባንክ
Proud to D🩸nate
ዓባይ ባንክ የ15ኛ ዓመት የምስረታ በዓሉን ምክንያት በማድረግ ከኢትዮጵያ ደም ባንክና የሕብረ ሕዋስ አገልግሎት ጋር በመተባበር በሀገር አቀፍ ደረጃ የደም ልገሳ መርሀ ግብር ማካሄድ ጀምሯል።
በደም ልገሳ ማስጀመሪያ መርሀ ግብሩ ላይ ንግግር ያደረጉት የዓባይ ባንክ የስትራቴጂ ዋና መኮንን አቶ ወንድይፍራው ታደስ በዛሬው እለት በአዲስ አበባ ከተማ ውስጥ በ6 ቅርንጫፎች ደም እየተለገሰ መሆኑን ገልጸዋል።
"በቀጣይ ሰኞም ደም ልገሳው ይቀጥላል፣ ወደ 90 የሚሆኑ ሰዎችም ደም ይለግሳሉ የሚል እቅድ አለን። በሀገር አቀፍ ደረጃ ከ600 በላይ ለጋሾች ደም ይለግሳሉ ብለን እናስባለን" ሲሉ ተናግረዋል።
አክለው በሁሉም ቅርንጫፍቻችን ከሚገኙ ሠራተኞቻችን፣ ደንበኞቻችንና ከመላው የባንካችን ቤተሰቦች ከተውጣጡ ከ1ሺህ በላይ በጎ ፈቃደኛ ደም ለጋሾችን በማንቀሳቀስ ለሕይወት አድን ዓላማ ቀጥተኛ አስተዋጽዖ በማድረጋችን ደስተኞች ነን ብለዋል፡፡
"ይህ የበጎ አድራጎት ሥራ የ15 ዓመት ጉዟችንን በድምቀት ለማክበርና ለማኅበራዊ ኃላፊነት ያለንን ዘላቂ ቁርጠኝነት ያጠናክራል" ሲሉ ነው የተናገሩት።
በዚህ መርሐግብር ላይ የተገኙት በኢትዮጵያ ደም ባንክና የሕብረ ሕዋስ አገልግሎት ውስጥ የደም ለጋሾች ተወካይ ደስክ ሃላፊ ሙላት በቀለ በበኩላቸው አባይ ባንክ በመላዊ ሀገሪቱ በሚገኙ ቅርንጫፎቹ የደም ልገሳ ፕሮግራም በማካሄድ የወገንን ህይወት እየታደገ ነው ሲሉ ተናግረዋል።
በባለፉት በዓላት ወቅት ከፍተኛ የሆነ የደም እጥረት ተከስቶ እንደነበር ያስታወሱት ሃላፊው "አባይ ባንክ እጥረቱን በመገንዘብ በዛሬው እለት ሰራተኞቹ ደም እንድለግሱ እያደረገ ነው። በሚተካ ደም የማይተካውን የሰው ልጅ ህይወት ለማዳን ፕሮግራሙን በማዘጋጀቱም ደስ ብሎናል" ሲሉ ነው የገለጹት።
አባይ ባንክ ከ71 ቢሊዮን በላይ ተቀማጭ ገንዘብ፣ 7 ቢሊዮን ብር የተከፈለ ካፒታል እንዲሁም ጠቅላላ ሀብቱ 91 ቢሊዮን ብር መድረሱም ተነስቷል።
#ዓባይባንክ
Proud to D🩸nate
❤500🙏32😡8👏6🥰2