" የውሃ አገልግሎት በከፊል እና ሙሉ ለሙሉ ስለሚቋረጥ አስፈላጊውን ቅድመ ዝግጅት አድርጉ " - ውሃ እና ፍሳሽ ባለሥልጣን
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ውሃ እና ፍሳሽ ባለሥልጣን የለገዳዲ ግድብ የጥሬ ውሃ ማስተላለፊያ ቫልቭ ቅየራ ስራ ከጥቅምት 2/2018 ዓም እስከ ጥቅምት 16/2018 ዓም ድረስ የሚከናወን መሆኑን ገልጿል።
የጥገና ስራው እስከሚጠናቀቅም በአንዳንድ የከተማዋ አካባቢዎች የውሃ አገልግሎት በከፊል እና ሙሉ በሙሉ የሚቋረጥ ይሆናል ብሏል።
የውሃ አገልግሎት በከፊል የሚቋረጥባቸው አካባቢዎች :-
- በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ወረዳ 2፣ 3፣ 5፣ 8፣ 9፣ 10 እና 13
- በቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 1፣ 2፣ 3፣ 4፣ 5፣ 6፣ 7፣ 11፣ 13 እና14
- በቂርቆስ ክፍለ ከተማ ወረዳ 1፣ 2፣ 3፣ 7፣ 8፣ 10 እና 11
ስራው እስከሚጠናቀቅ የውሃ አገልግሎት በከፊል እና ሙሉ ለሙሉ ስለሚቋረጥ አስፈላጊውን ቅድመ ዝግጅት እንድታደርጉ ሲል ባለሥልጣኑ አሳስቧል።
Credit - AAWSA
@tikvahethiopia
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ውሃ እና ፍሳሽ ባለሥልጣን የለገዳዲ ግድብ የጥሬ ውሃ ማስተላለፊያ ቫልቭ ቅየራ ስራ ከጥቅምት 2/2018 ዓም እስከ ጥቅምት 16/2018 ዓም ድረስ የሚከናወን መሆኑን ገልጿል።
የጥገና ስራው እስከሚጠናቀቅም በአንዳንድ የከተማዋ አካባቢዎች የውሃ አገልግሎት በከፊል እና ሙሉ በሙሉ የሚቋረጥ ይሆናል ብሏል።
የውሃ አገልግሎት በከፊል የሚቋረጥባቸው አካባቢዎች :-
- በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ወረዳ 2፣ 3፣ 5፣ 8፣ 9፣ 10 እና 13
- በቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 1፣ 2፣ 3፣ 4፣ 5፣ 6፣ 7፣ 11፣ 13 እና14
- በቂርቆስ ክፍለ ከተማ ወረዳ 1፣ 2፣ 3፣ 7፣ 8፣ 10 እና 11
ስራው እስከሚጠናቀቅ የውሃ አገልግሎት በከፊል እና ሙሉ ለሙሉ ስለሚቋረጥ አስፈላጊውን ቅድመ ዝግጅት እንድታደርጉ ሲል ባለሥልጣኑ አሳስቧል።
Credit - AAWSA
@tikvahethiopia
❤1.11K😡395😭119😢65👏42🤔41🙏30🕊24💔20😱14🥰3
TIKVAH-ETHIOPIA
" በተለያዩ ማስታወቂያዎች የሚጭበረበረውን ማኅበረሰብ መጠበቅ ኃላፊነታችን ነው " - ወ/ሮ ትዕግስት ሃሚድ የሳይበር ደኅንነት ወር " የሳይበር ደኅንነት - የዲጂታል ኢትዮጵያ መሰረት " በሚል መሪ ቃል ለ6ኛ ጊዜ በሀገር አቀፍ ደረጃ ከጥቅምት 1 - 30 እንደሚከበር የኢንፎርሜሽን መረብ ደኅንነት አስተዳደር አስታውቋል። የአስተዳደሩ ዋና ዳይሬክተር ወ/ሮ ትዕግስት ሃሚድ በዚህ ዓመት በሁለት ዋና ዋና…
ፎቶ ፦ 6ተኛው ሀገር አቀፍ የሳይበር ደህንነት ወር ትላንት ተጀምሯል።
ወሩ “የሳይበር ደህንነት - የዲጂታል ኢትዮጵያ መሰረት” በሚል መሪ ቃል ነው የሚከበረው።
የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር በኢትዮጵያ የቴክኖሎጂ ተጠቃሚነት ከማደጉ ጋር ተያይዞ በዜጎች፣ በተቋማት እና ቁልፍ መሰረተ ልማቶች ላይ የሚደርሰው የሳይበር ጥቃት በከፍተኛ ሁኔታ ጨምሯል ብሏል።
የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር (ኢመደአ) ዋና ዳይሬክተር ወ/ሮ ትዕግስት ሃሚድ ምን አሉ ?
" ከጥቅምት 1-30/2018 ዓ.ም 6ኛውን ሀገር አቀፍ የሳይበር ደህንነት ወር ይከበራል።
የሳይበር ደህንነት ወሩ የሚከበረው የተቋማትን እና የኅብረተሰቡን የሳይበር ደህንነት ንቃተ-ህሊና በማጎልበት ለሳይበር ደህንነት ተገቢ ትኩረት እንዲሰጡ ለማስቻል ነው።
ወሩ ሲከበር የሃሰተኛ መረጃ ዝግጅትና ስርጭት መከላከል ላይ እና ዲጂታላይዜሽን እንዲሁም የሳይበር ደህንነት ላይ የሚያተኩር ይሆናል " ብለዋል።
የጥቅምት ወርን ሙሉ ቀናት የሕብረተሰቡንና የተቋማትን የሳይበር ደህንነት ንቃተ ሕሊና የሚያጎለብቱ ስራዎች እንደሚሰሩ ተገልጿል።
የሳይበር ደህንነት ወር በዓለም አቀፍ ደረጃ ዘንድሮ ለ22ኛ ጊዜ የሚከበር ሲሆን በኢትዮጵያ ለ6ኛ ጊዜ ነው መከበር የጀመረው።
ፎቶ ፦ INSA
@tikvahethiopia
ወሩ “የሳይበር ደህንነት - የዲጂታል ኢትዮጵያ መሰረት” በሚል መሪ ቃል ነው የሚከበረው።
የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር በኢትዮጵያ የቴክኖሎጂ ተጠቃሚነት ከማደጉ ጋር ተያይዞ በዜጎች፣ በተቋማት እና ቁልፍ መሰረተ ልማቶች ላይ የሚደርሰው የሳይበር ጥቃት በከፍተኛ ሁኔታ ጨምሯል ብሏል።
የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር (ኢመደአ) ዋና ዳይሬክተር ወ/ሮ ትዕግስት ሃሚድ ምን አሉ ?
" ከጥቅምት 1-30/2018 ዓ.ም 6ኛውን ሀገር አቀፍ የሳይበር ደህንነት ወር ይከበራል።
የሳይበር ደህንነት ወሩ የሚከበረው የተቋማትን እና የኅብረተሰቡን የሳይበር ደህንነት ንቃተ-ህሊና በማጎልበት ለሳይበር ደህንነት ተገቢ ትኩረት እንዲሰጡ ለማስቻል ነው።
ወሩ ሲከበር የሃሰተኛ መረጃ ዝግጅትና ስርጭት መከላከል ላይ እና ዲጂታላይዜሽን እንዲሁም የሳይበር ደህንነት ላይ የሚያተኩር ይሆናል " ብለዋል።
የጥቅምት ወርን ሙሉ ቀናት የሕብረተሰቡንና የተቋማትን የሳይበር ደህንነት ንቃተ ሕሊና የሚያጎለብቱ ስራዎች እንደሚሰሩ ተገልጿል።
የሳይበር ደህንነት ወር በዓለም አቀፍ ደረጃ ዘንድሮ ለ22ኛ ጊዜ የሚከበር ሲሆን በኢትዮጵያ ለ6ኛ ጊዜ ነው መከበር የጀመረው።
ፎቶ ፦ INSA
@tikvahethiopia
❤383😡24🙏12😱7🤔6🕊6😭6🥰4😢1
TIKVAH-ETHIOPIA
“ በዚህ አመት 11 አዳዲስ የስልጠና ፕሮግራሞች ይከፈታሉ ” - ብሩክ ከድር (ዶ/ር) በዚህ አመት 11 የሥልጠና ፕሮግራሞችን እንደሚከፈቱ የኢፌዴሪ ቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኢንስቲትዩት አስታወቀ። የኢንስቲትዩቱ ዋና ዳይሬክተር ብሩክ ከድር (ዶ/ር) “በደረጃ 8 (በ3ኛ ዲግሪ) በቴክኒክና ሙያ ስልጠና ስርዓት ውስጥ ለመጀመሪያ ጊዜ በሁለት ፕሮግራሞች ስልጠና ይሰጠል” ብለዋል። አዳዲስ በሚከፈቱት ፕሮግራሞች…
“ በተያዘው ዓመት ለመጀመሪያ ጊዜ የሪሜዲያል ተፈታኞችን እቀበላላሁ ” - ኢንስቲትዩቱ
የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኢንስቲትዩት በ2018 ዓ/ም ለመጀመሪያ ጊዜ የሪሜዳል ተፈታኞችን እንደሚቀበልና አዲስ የተቀረጹ የስልጠና መርሃግብሮችንም ይፋ እንዳደረገ ገልጿል።
የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ማለፊያ ውጤት ያመጡ ተማሪዎችን ተቀብሎ እስከ 3 ዲግሪ ባሉት ደረጃዎች እንደሚያሰለጥን ያስታወቀው ተቋሙ፣ በዚሁ ዓመት ለመጀመሪያ ጊዜ የሪሚዳል ተፈታኞችን እንደሚቀበልም ጠቁሟል፡፡
በመደበኛው በቅዳሜ እና እሁድ እንዲሁም በክረምት የስልጠና መርሃግብሮች ከደረጃ ስድስት እስከ 8 (ከመጀመሪያ እስከ 3ኛ ዲግሪ) የቴክኒክና ሙያ ስልጠና አንደሚሰጥ የኢንስቲትዩቱ ዋና ዳይሬክተር ብሩክ ከድር (ዶ/ር) ገልጸዋል፡፡
ኢንስቲትዩቱ ሰልጣኞችን የሚቀበልባቸው አራት መንገዶች ምን ምን ናቸው?
- ደረጃቸውን ለማሻሻል የቴክኒክና ሙያ አመራሮችና ሰልጣኞችን፣
- የኢንዱስትሪ ቴክኒሻኖችን በማታው፣ በቅዳሜና እሁድ ፕሮግራሞች፣
- የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ወስደው የከፍተኛ ትምህርት መግቢያ ውጤት ያመጡትን፣ እንዲሁም የሪሜዳል ተፈታኞችን (ዘንድሮ ለመጀመሪያ ጊዜ) እንደሚቀበል ነው የገለጸው፡፡
ተደራሽነቱ ምን ይመለስላል?
ኢንስቲትዩቱ በአዲስ አበባ ከሚገኘው ዋና ካምፓሱ በተጨማሪ የሀዋሳ ካምፓስና የብየዳ ስልጠና ልህቀት ማዕከል ካምፓሶች፣ በተለያዩ የኢትዮጵያ ክፍሎች በሚገኙ 16 የሳተላይት ተቋማት በደረጃ 6 ወይም በመጀመሪያ ዲግሪ ስልጠና እየሰጠ መሆኑን አስረድቷል፡፡
አዲስ የተቀረጹት አጫጭር የስልጠና መርሃግብሮች ምንድን ናቸው?
በዘንደሮው አመት 11 አዳዲስ የስልጠና ፕርግራሞች ከመታከላቸው በተጨማሪ አዳዲስ የተቀረጹ የአጭር ጊዜ የስልጠና መርሃ ግብሮችም ይፋ ተደርገዋል፡፡ በዚህም፦
- በሲቪል ቴክኖሎጂ፣
- በኤሌክትሪክ እና አይሲቲ፣
- በመካኒካል ቴክኖሎጂ፣
- በቴክስታይል እና አፓረል፣
- በአግሪካልቸራል እና አግሮፕሮሰሲንግ፣
- በሉባን ወርኪንግ የሚሰጡ ሲሆኑ፣ በእነዚህ ስር ያሉ ዝርዝሮችና ሌሎች የስልጠና ዝርዝሮች ከላይ ተያይዘዋል፡፡
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኢንስቲትዩት በ2018 ዓ/ም ለመጀመሪያ ጊዜ የሪሜዳል ተፈታኞችን እንደሚቀበልና አዲስ የተቀረጹ የስልጠና መርሃግብሮችንም ይፋ እንዳደረገ ገልጿል።
የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ማለፊያ ውጤት ያመጡ ተማሪዎችን ተቀብሎ እስከ 3 ዲግሪ ባሉት ደረጃዎች እንደሚያሰለጥን ያስታወቀው ተቋሙ፣ በዚሁ ዓመት ለመጀመሪያ ጊዜ የሪሚዳል ተፈታኞችን እንደሚቀበልም ጠቁሟል፡፡
በመደበኛው በቅዳሜ እና እሁድ እንዲሁም በክረምት የስልጠና መርሃግብሮች ከደረጃ ስድስት እስከ 8 (ከመጀመሪያ እስከ 3ኛ ዲግሪ) የቴክኒክና ሙያ ስልጠና አንደሚሰጥ የኢንስቲትዩቱ ዋና ዳይሬክተር ብሩክ ከድር (ዶ/ር) ገልጸዋል፡፡
ኢንስቲትዩቱ ሰልጣኞችን የሚቀበልባቸው አራት መንገዶች ምን ምን ናቸው?
- ደረጃቸውን ለማሻሻል የቴክኒክና ሙያ አመራሮችና ሰልጣኞችን፣
- የኢንዱስትሪ ቴክኒሻኖችን በማታው፣ በቅዳሜና እሁድ ፕሮግራሞች፣
- የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ወስደው የከፍተኛ ትምህርት መግቢያ ውጤት ያመጡትን፣ እንዲሁም የሪሜዳል ተፈታኞችን (ዘንድሮ ለመጀመሪያ ጊዜ) እንደሚቀበል ነው የገለጸው፡፡
ተደራሽነቱ ምን ይመለስላል?
ኢንስቲትዩቱ በአዲስ አበባ ከሚገኘው ዋና ካምፓሱ በተጨማሪ የሀዋሳ ካምፓስና የብየዳ ስልጠና ልህቀት ማዕከል ካምፓሶች፣ በተለያዩ የኢትዮጵያ ክፍሎች በሚገኙ 16 የሳተላይት ተቋማት በደረጃ 6 ወይም በመጀመሪያ ዲግሪ ስልጠና እየሰጠ መሆኑን አስረድቷል፡፡
አዲስ የተቀረጹት አጫጭር የስልጠና መርሃግብሮች ምንድን ናቸው?
በዘንደሮው አመት 11 አዳዲስ የስልጠና ፕርግራሞች ከመታከላቸው በተጨማሪ አዳዲስ የተቀረጹ የአጭር ጊዜ የስልጠና መርሃ ግብሮችም ይፋ ተደርገዋል፡፡ በዚህም፦
- በሲቪል ቴክኖሎጂ፣
- በኤሌክትሪክ እና አይሲቲ፣
- በመካኒካል ቴክኖሎጂ፣
- በቴክስታይል እና አፓረል፣
- በአግሪካልቸራል እና አግሮፕሮሰሲንግ፣
- በሉባን ወርኪንግ የሚሰጡ ሲሆኑ፣ በእነዚህ ስር ያሉ ዝርዝሮችና ሌሎች የስልጠና ዝርዝሮች ከላይ ተያይዘዋል፡፡
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
❤827🙏45😡26😢18😭13🥰9👏7😱6🕊5
ነፃ የትምህርት ዕድል !
የኢትዮጵያ ወጣት ወንዶች ክርስቲያናዊ ማህበር (ወወክማ)፦
➡️ ስልጠናውን ላጠናቀቁ ሰልጣኞች የራሳቸውን ስራ/ቢዝነስ ለመጀመር የገንዘብ ድጋፍ ይሰጣቸዋል!
➡️ ሴት አመልካቾች ይበረታታሉ
➡️ በፋሽን ዲዛይን የትምህርት ዘርፍ ለመሰልጠን ፍላጎት ያለው/ያላት
ለመመዝገብ የሚያስፈልጉ ሰነዶች፦
ዕድሜ ፡ ከ 18 እስከ 29 ዓመት
ፎቶ ፡ አምስት (5) ጉርድ ፎቶ
የቀበሌ መታወቂያ
የድጋፍ ደብዳቤ፦ በክፍያ መማር አለመቻልን የሚያሳይ የድጋፍ ደብዳቤ ከወረዳ
የትምህርት ደረጃ፡ 8ኛ ክፍል እና ከዚያ በላይ
አድራሻ፦ መስቀል ፍላወር፣ ቅዱስ ያሬድ ቤተክርስቲያን ፊት፣ ዶንቦስኮ ገዳም አጠገብ (ወደ ግራ 100 ሜትር ገባ ብሎ) ለበለጠ መረጃ፡ 0114160640
@tikvahethiopia
የኢትዮጵያ ወጣት ወንዶች ክርስቲያናዊ ማህበር (ወወክማ)፦
➡️ ስልጠናውን ላጠናቀቁ ሰልጣኞች የራሳቸውን ስራ/ቢዝነስ ለመጀመር የገንዘብ ድጋፍ ይሰጣቸዋል!
➡️ ሴት አመልካቾች ይበረታታሉ
➡️ በፋሽን ዲዛይን የትምህርት ዘርፍ ለመሰልጠን ፍላጎት ያለው/ያላት
ለመመዝገብ የሚያስፈልጉ ሰነዶች፦
ዕድሜ ፡ ከ 18 እስከ 29 ዓመት
ፎቶ ፡ አምስት (5) ጉርድ ፎቶ
የቀበሌ መታወቂያ
የድጋፍ ደብዳቤ፦ በክፍያ መማር አለመቻልን የሚያሳይ የድጋፍ ደብዳቤ ከወረዳ
የትምህርት ደረጃ፡ 8ኛ ክፍል እና ከዚያ በላይ
አድራሻ፦ መስቀል ፍላወር፣ ቅዱስ ያሬድ ቤተክርስቲያን ፊት፣ ዶንቦስኮ ገዳም አጠገብ (ወደ ግራ 100 ሜትር ገባ ብሎ) ለበለጠ መረጃ፡ 0114160640
@tikvahethiopia
❤408😡38😭27🙏25🕊2
TIKVAH-ETHIOPIA
#Earthquake ሌላ የመሬት መንቀጥቀጥ ከዓዲግራት ደቡባዊ ምስራቅ 44 ኪ/ሜ ላይ ከደቂቃዎች በፊት ተከስቷል። የመሬት መንቀጥቀጡ በሬክተር ስኬል 4.8 የተለካ ሲሆን ንዝረቱ በተለያዩ ከተሞችም ተሰምቷል። @tikvahethiopia
“ በርህሌ አካባቢ ሰዎች በቤት ውስጥ እያሉ ቤቶች ፈርሰው ሰዎች ላይ አደጋ ደርሷል፣ ለህክምና ወደ ሆስፒታሎች ሂደዋል ” - ፕሮፌሰር አታላይ አየለ
መቐለ ከተማና አካባቢው ከትላንት ጀምሮ ተደጋጋሚ የመሬት መንቀጥቀጥ እንደተከሰተ፣ ይህም በተለያዩ የክልሉና አጎራባች ቦታዎች እንደተሰማ ተነግሯል፡፡
ለአደጋው መከሰት ምን የተለየ ምክንያት አለ? ስንል የጠየቅናቸው በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የጂኦ ፊዚክስ ስፔስ ሳይንስና አስትሮኖሚ ኢንስቲትዩት ተማራማሪ ፕ/ር አታላይ አየለ፣ “በቆላማው የአፋር ክፍልና በደጋማው ክፍል በግልጽ የሚታይ ዝንፈት አለ፣ በተደጋጋሚ የመሬት መንቀጥቀጥ የሚያዘወትረው ቦታ ነው” ብለዋል፡፡
“አሁን በተፈጠበት አካባቢ በተደጋጋሚ ተፈጥሮ ያውቃል፡፡ ትላንት ከእኩለ ቀን ጅምሮ ከ4.2 በሬክተር ስኬል ጀምሮ እስከ 5.6 ከፍተኛው የሆነ መሬት መንቀጥቀጥ ከሰሜን ምሥራቅ መቐሌ ጀምሮ እስከ ምሥራቅ መቐለ ድረስ ተሰምቷል” ሲሉም ገልጸዋል፡፡
“በርህሌ አካባቤ ጉዳት እንዳዳረሰ እየተዘገበ ነው፡፡ ሰዎች በቤት ውስጥ እያሉ ቤቶች ፈርሰው ሰዎች ላይ አደጋ ደርሷል፣ ለህክምና ወደ ሆስፒታሎች ሂደዋል”፣ ያሉት ፕሮፌሰር አታላይ፣ ይህ ክስተት በዚህ ጊዜ ይመጣል ተብሎ “የሚተነበይ" እንዳለሆነም ተናግረዋል፡፡
ጉዳት ያስተናገዱት ቤቶች ደረጃቸውን ያልጠበቁ ሊሆኑ እንደሚችሉ ጠቅሰው፣ “ደረጃውን የጠበቀ ህንጻ ቢሆን ኑሮ እንደዚህ አይፈጥርም ነበር” ሲሉም ተናግረዋል።
ኢትዮጵያ የመሬት መንቀጥቀጥ ተጋላጭ አገር መሆኗን፣ በዚህም በሂደት ያለ የስምጥ ሸለቆ ተፈጥሮ እያስተናግደን ስለሆነ ከቀይ ባህርና ከአፋር አካባቢ ጀምሮ በድሬዳዋን፣ ናዝሬት፣ ሀዋሳ፣ አርባምንጭ እያካለለ እንደሚሄድ ገልጸዋል፡፡
አሁን በትግራይ የተፈጠረው የመሬት መንቀጥቀጥ ከፍተኛው 5.6 ስኬል እንደሆነና የተጋነነ እንዳልሆነ አብራርተው፣ “በዚያው ይቀራል ብለን ተስፋ እናደርጋለን” ሲሉ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል፡፡
“5.6 የተለካ የመሬት መንቀጥቀጥ ጉዳት ሊያደርስ ይችላል፤ እንኳ 5.6 ሦስትና ሁለት” ያሉት ተመራማሪው፣ የት ነው አደጋው የተፈጠረው? የሚለው እንደሚወስነው፣ የሬክተር ስኬሉ ሁለት የሆነ የመሬት መንቀጥቀጥም ቢከሰት ቤት እንደሚያፈርስ አስረድተዋል፡፡
ምን ጥንቃቄ መደረግ እንዳለበት ሲያስረዱ ደግሞ፣ “የግንባታ ደረጃን ማሻሻል” እንደሚገባ ገልጸው፣ በስምጥ ሸለቆ ዙሪያ የሚሰሩ ቤቶች ትንሽም ቢሆኑ ተደርምሰው አደጋ ሊያደርሱ እንደሚችሉ ገልጸዋል፡፡
እንዲሁም በፈንታሌው ጊዜ እንደተማርነው ባለመረበሽ ግንዛቤ መውሰድ እንደሚያስፈልግ መክረዋል፡፡
“መሬት መንቀጥቀጡ ብቻውን ምንም ጉዳት ሊያደርስ አይችልም” ብለው፣ ግን ከህንጻና ከመሰረተ ልማት አጠገብ፣ ከቮልቴጅ አካባቢ ከሆነ አደጋ እንደሚያደርስ አስረድተዋል፡፡
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
መቐለ ከተማና አካባቢው ከትላንት ጀምሮ ተደጋጋሚ የመሬት መንቀጥቀጥ እንደተከሰተ፣ ይህም በተለያዩ የክልሉና አጎራባች ቦታዎች እንደተሰማ ተነግሯል፡፡
ለአደጋው መከሰት ምን የተለየ ምክንያት አለ? ስንል የጠየቅናቸው በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የጂኦ ፊዚክስ ስፔስ ሳይንስና አስትሮኖሚ ኢንስቲትዩት ተማራማሪ ፕ/ር አታላይ አየለ፣ “በቆላማው የአፋር ክፍልና በደጋማው ክፍል በግልጽ የሚታይ ዝንፈት አለ፣ በተደጋጋሚ የመሬት መንቀጥቀጥ የሚያዘወትረው ቦታ ነው” ብለዋል፡፡
“አሁን በተፈጠበት አካባቢ በተደጋጋሚ ተፈጥሮ ያውቃል፡፡ ትላንት ከእኩለ ቀን ጅምሮ ከ4.2 በሬክተር ስኬል ጀምሮ እስከ 5.6 ከፍተኛው የሆነ መሬት መንቀጥቀጥ ከሰሜን ምሥራቅ መቐሌ ጀምሮ እስከ ምሥራቅ መቐለ ድረስ ተሰምቷል” ሲሉም ገልጸዋል፡፡
“በርህሌ አካባቤ ጉዳት እንዳዳረሰ እየተዘገበ ነው፡፡ ሰዎች በቤት ውስጥ እያሉ ቤቶች ፈርሰው ሰዎች ላይ አደጋ ደርሷል፣ ለህክምና ወደ ሆስፒታሎች ሂደዋል”፣ ያሉት ፕሮፌሰር አታላይ፣ ይህ ክስተት በዚህ ጊዜ ይመጣል ተብሎ “የሚተነበይ" እንዳለሆነም ተናግረዋል፡፡
ጉዳት ያስተናገዱት ቤቶች ደረጃቸውን ያልጠበቁ ሊሆኑ እንደሚችሉ ጠቅሰው፣ “ደረጃውን የጠበቀ ህንጻ ቢሆን ኑሮ እንደዚህ አይፈጥርም ነበር” ሲሉም ተናግረዋል።
ኢትዮጵያ የመሬት መንቀጥቀጥ ተጋላጭ አገር መሆኗን፣ በዚህም በሂደት ያለ የስምጥ ሸለቆ ተፈጥሮ እያስተናግደን ስለሆነ ከቀይ ባህርና ከአፋር አካባቢ ጀምሮ በድሬዳዋን፣ ናዝሬት፣ ሀዋሳ፣ አርባምንጭ እያካለለ እንደሚሄድ ገልጸዋል፡፡
አሁን በትግራይ የተፈጠረው የመሬት መንቀጥቀጥ ከፍተኛው 5.6 ስኬል እንደሆነና የተጋነነ እንዳልሆነ አብራርተው፣ “በዚያው ይቀራል ብለን ተስፋ እናደርጋለን” ሲሉ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል፡፡
“5.6 የተለካ የመሬት መንቀጥቀጥ ጉዳት ሊያደርስ ይችላል፤ እንኳ 5.6 ሦስትና ሁለት” ያሉት ተመራማሪው፣ የት ነው አደጋው የተፈጠረው? የሚለው እንደሚወስነው፣ የሬክተር ስኬሉ ሁለት የሆነ የመሬት መንቀጥቀጥም ቢከሰት ቤት እንደሚያፈርስ አስረድተዋል፡፡
ምን ጥንቃቄ መደረግ እንዳለበት ሲያስረዱ ደግሞ፣ “የግንባታ ደረጃን ማሻሻል” እንደሚገባ ገልጸው፣ በስምጥ ሸለቆ ዙሪያ የሚሰሩ ቤቶች ትንሽም ቢሆኑ ተደርምሰው አደጋ ሊያደርሱ እንደሚችሉ ገልጸዋል፡፡
እንዲሁም በፈንታሌው ጊዜ እንደተማርነው ባለመረበሽ ግንዛቤ መውሰድ እንደሚያስፈልግ መክረዋል፡፡
“መሬት መንቀጥቀጡ ብቻውን ምንም ጉዳት ሊያደርስ አይችልም” ብለው፣ ግን ከህንጻና ከመሰረተ ልማት አጠገብ፣ ከቮልቴጅ አካባቢ ከሆነ አደጋ እንደሚያደርስ አስረድተዋል፡፡
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
❤968😭245🕊52😢45💔35🙏31🥰7😡7🤔6👏3
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#Afar
በአፋር ክልል ሰሜናዊ ዞን በባራሕሌ ወረዳ ትናንት ምሽት በተከሰተው የመሬት መንቀጥቀጥ አደጋ እድሜው 12 ዓመት የሆነ ልጅ ህይወት ሲያልፍ 6 ሰዎች ላይ ጉዳት ደርሷል።
የሰሜናዊ ዞን አስተዳደር የመሬት መንቀጥቀጡ በዞኑ ባራሕሌ፣ ኮናባ እና ዳሎል ወረዳዎች መከሰቱን አሳውቋል።
በዚህም የ12 ዓመት ልጅ ህይወቱ ሲያልፍ 6 ሰዎች ተጎድተዋል።
በቡሬ እና ዓስጉቢ ቀበሌዎች በርካታ ቤቶች ፈርሰዋል።
በመሬት መንቀጥቀጡ 43 ሺህ 456 የሚሆኑ ሰዎች ቤታቸው ሙሉ በሙሉ መውደሙንና ያለመጠለያ ቀርተዋል።
ለተጎጂዎች ድጋፍ ለማድረግ ጥረት እየተደረገ መሆኑን ዞኑ ለኤፍ ኤም ሲ ገልጿል። #ኤፍኤምሲ
@tikvahethiopia
በአፋር ክልል ሰሜናዊ ዞን በባራሕሌ ወረዳ ትናንት ምሽት በተከሰተው የመሬት መንቀጥቀጥ አደጋ እድሜው 12 ዓመት የሆነ ልጅ ህይወት ሲያልፍ 6 ሰዎች ላይ ጉዳት ደርሷል።
የሰሜናዊ ዞን አስተዳደር የመሬት መንቀጥቀጡ በዞኑ ባራሕሌ፣ ኮናባ እና ዳሎል ወረዳዎች መከሰቱን አሳውቋል።
በዚህም የ12 ዓመት ልጅ ህይወቱ ሲያልፍ 6 ሰዎች ተጎድተዋል።
በቡሬ እና ዓስጉቢ ቀበሌዎች በርካታ ቤቶች ፈርሰዋል።
በመሬት መንቀጥቀጡ 43 ሺህ 456 የሚሆኑ ሰዎች ቤታቸው ሙሉ በሙሉ መውደሙንና ያለመጠለያ ቀርተዋል።
ለተጎጂዎች ድጋፍ ለማድረግ ጥረት እየተደረገ መሆኑን ዞኑ ለኤፍ ኤም ሲ ገልጿል። #ኤፍኤምሲ
@tikvahethiopia
😢505❤332😭125🙏29💔21🕊18🤔9🥰8
TIKVAH-ETHIOPIA
#Afar በአፋር ክልል ሰሜናዊ ዞን በባራሕሌ ወረዳ ትናንት ምሽት በተከሰተው የመሬት መንቀጥቀጥ አደጋ እድሜው 12 ዓመት የሆነ ልጅ ህይወት ሲያልፍ 6 ሰዎች ላይ ጉዳት ደርሷል። የሰሜናዊ ዞን አስተዳደር የመሬት መንቀጥቀጡ በዞኑ ባራሕሌ፣ ኮናባ እና ዳሎል ወረዳዎች መከሰቱን አሳውቋል። በዚህም የ12 ዓመት ልጅ ህይወቱ ሲያልፍ 6 ሰዎች ተጎድተዋል። በቡሬ እና ዓስጉቢ ቀበሌዎች በርካታ ቤቶች ፈርሰዋል።…
#Tigray
ጥቅምት 1/2018 ዓ.ም የተከሰተው የመሬት መንቀጥቀጥ ንዝረት በትግራክ 6 የመኖሪያ ቤቶች አፈረሰ።
የመሬት ንዝረቱ ዛሬም ተከስቷል።
በትግራይ ክልል ከምስራቃዊ ኣፅቢ ወምበርታ ወረዳ 26 ኪ/ሜ ርቀት ላይ የተከሰተው በሬክተር ስኬል 5.6 የተለካ የመሬት መንቀጥቀጥ ተከትሎ በቃል ኣሚን ቀበሌ ገበሬ ማህበር ቡሐለ መንደር 6 ቤቶች በከፊል እንደፈረሱ ወረዳው አሳውቋል።
እንደ ትናንትናው ከበድ ባይሆንም ዛሬ ጥቅምት 2/2018 ዓ.ም የመሬት ንዝረቱ በተወሰነ መልኩ መቀጠሉ የገለፀው የወረዳው አስተዳደር በሰው ፣ በእንስሳትና በንብረት ያስከተለው አደጋ እንደሌለ ገልጿል።
#TikvahEthiopiaFamilyMekelle
@tikvahethiopia
ጥቅምት 1/2018 ዓ.ም የተከሰተው የመሬት መንቀጥቀጥ ንዝረት በትግራክ 6 የመኖሪያ ቤቶች አፈረሰ።
የመሬት ንዝረቱ ዛሬም ተከስቷል።
በትግራይ ክልል ከምስራቃዊ ኣፅቢ ወምበርታ ወረዳ 26 ኪ/ሜ ርቀት ላይ የተከሰተው በሬክተር ስኬል 5.6 የተለካ የመሬት መንቀጥቀጥ ተከትሎ በቃል ኣሚን ቀበሌ ገበሬ ማህበር ቡሐለ መንደር 6 ቤቶች በከፊል እንደፈረሱ ወረዳው አሳውቋል።
እንደ ትናንትናው ከበድ ባይሆንም ዛሬ ጥቅምት 2/2018 ዓ.ም የመሬት ንዝረቱ በተወሰነ መልኩ መቀጠሉ የገለፀው የወረዳው አስተዳደር በሰው ፣ በእንስሳትና በንብረት ያስከተለው አደጋ እንደሌለ ገልጿል።
#TikvahEthiopiaFamilyMekelle
@tikvahethiopia
😭369❤314🙏53😢28💔22🕊14🤔9🥰8👏1