Telegram Web Link
የደሞዝ እና ጥቅማ ጥቅም ጥያቄ በማንሳት ለመንግሥት የሰላሳ ቀናት የቅድሚያ ማስጠንቀቂያ ጊዜ ሰጥተው የነበሩት የጤና ባለሙያዎች ምላሽ ባለማግኘታቸው ከፊል የሥራ ማቆም አድማ መምታታቸውን ለቢቢሲ ተናገሩ።

ባለሙያዎች ከጥቂት "የተመረጡ የሕክምና ክፍሎች" ውጪ ያሉ ክፍሎች የሚሰሩ የጤና ባለሙያዎች ከዛሬ ግንቦት 5/2017 ዓ.ም. ጀምሮ ሥራ ማቆማቸውን ገልፀዋል።

የቢቢሲን ዘገባ ያንብቡ
https://www.bbc.com/amharic/articles/c9893ed807po
👍643👎2👀2
የጤና ባለሙያዎች በሀገር አቀፍ ደረጃ ከፊል የስራ ማቆም አድማ መጀመራቸውን ተከትሎ ዛቻና ማስፈራሪያ እየደረሰባቸው መሆኑን ገለፁ

በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች የሚገኙ የጤና ባለሙያዎች ዛሬ ማክሰኞ ግንቦት 5 ቀን 2017 ዓ.ም. በመላ ሀገሪቱ የተጀመረውን የከፊል የስራ ማቆም አድማ ለማካሄድ ሲሞክሩ ከመንግሥት አካላት ማስፈራሪያና ጫና እንደደረሰባቸው አስታወቁ።

#በኦሮሚያ ክልል ባሌ ዞን ሮቤ ከተማ በሚገኘው የማዳ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ ጎባ ሪፈራል ሆስፒታል የህክምና የሰራተኛ የሆኑ አንድ ግለሰብ ለአዲስ ስታንዳርድ እንደገለጹት የጤና ባለሙያዎች አድማውን ለማድረግ ሲሞክሩ ከአካባቢው ባለስልጣናት ጫና እንደገጠማቸው አስረድተዋል።

ባለሙያው "ማስፈራሪያ እየደረሰብን ነው" ያሉ ሲሆን፤ ሆስፒታሉ ከማለዳ ጀምሮ "በመንግስት የስራ ሀላፊዎች የተሞላ" እንደነበር ጨምረው ተናግረዋል።

ሌላኛው በአማራ ክልል ደቡብ #ወሎ ዞን በአቀስታ ከተማ የአቀስታ አጠቃላይ ሆስፒታል የሚሰሩ አንድ የጤና ባለሙያ በበኩላቸው በድንገተኛ ክፍል የተመደበ አንድ ሀኪም "በፀጥታ ሀይሎች" ተይዞ የተለመደውን የህሙማን ህክምና አገልግሎት እንዲሰጥ አልያም "ወደ እስር ቤት እንዲሄድ" እንደተነገረው ለአዲስ ስታንዳርድ ገልጸዋል።

በአዲስ አበባ ከተማ በዛሬው ዕለት ተጠርቷል የተባለውን የህክምና ባለሙያዎች አድማ ለመታዘብ በሶስት ዋና ዋና የመንግስት ሆስፒታሎች ማለትም በዳግማዊ #ምኒልክ ሪፈራል ሆስፒታል፣ #በዘውዲቱ መታሰቢያ ሆስፒታል እና #በየካቲት12 ሜዲካል ኮሌጅ ሆስፒታል ቅኝት ያደረግን ሲሆን በእነዚሁ ተቋማት ከሰዓት በኋላ ስራ የተጀመረ ይሁን እንጂ ጠዋት ላይ የከፊል የስራ ማቆም መካሄዱን ታዝበናል።

የአዲስ ስታንዳርድ ዘገባ ይመልከቱ

https://addisstandard.com/Amharic/?p=7748
👍40🔥5👀32😭2
ከቆሙ ተሽከርካሪዎች ላይ ሠሌዳ በመፍታት የሚሸጡ ተጠርጣሪዎችን በቁጥጥር ስር አውሎ ምርመራ እያጣራ መሆኑን የአዲስ አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አስታወቀ።

በረከት ማዕረጉ እና ሚኪያስ ባየልኝ የተባሉ ተጠርጣሪዎች ሚያዝያ 26 ቀን 2017 ዓ/ም ከሌሊቱ 7:00 ሠዓት በቂርቆስ ክ/ከተማ ወረዳ 11 ልዩ ቦታው ለገሀር ግቢ ውስጥ በአጥር ዘለው በመግባት ከሁለት ተሽከርካሪዎች ላይ የፊትና የኋላ ሠሌዳ ፈትተው ሲወጡ በወቅቱ የነበሩት የጥበቃ ሠራተኞችም ሊይዟቸው ባለመቻላቸው አምልጠዋል።

ነገር ግን በሠዓቱ በአካባቢው በስራ ላይ የነበሩ የወንጀል መከላከል አባላት በዚያ ሌሊት ሚኪያስ ባየልኝ ሲሮጥ በማግኘታቸው በቁጥጥር ስር አውለው ሲፈትሹት የተሽከርካሪ ሠሌዳ በማግኘታቸው በቁጥጥር ስር መዋሉን በቂርቆስ ክ/ከተማ ፖሊስ መምሪያ የፖፑላሬ አካባቢ ፖሊስ ጣቢያ አስታውቋል።

ፖሊስም ከሚኪያስ ባየልኝ ጋር አብሮት በወንጀሉ ተሳታፊ የነበረውን በረከት ማዕረጉን በቀጣዩ ቀን በመያዝ ባደረገው ምሪት የሠረቀውን ሠሌዳ ከደበቀበት የመኖሪያ ቤቱ ኮርኒስ ውስጥ መርቶ ሊያመጣም ችሏል።የምርመራ ክፍሉም በተጠርጣሪዎቹ ላይ ተገቢውን ምርመራ የማስፋት ተግባር እያከናወነ የሚገኝ ሲሆን ግለሠቦቹ አንዱን ሠሌዳ በ4ሺህ ብር እንደሚሸጡም የወንጀል ምርመራ መዝገቡ ያስረዳል።

በየጊዜው የወንጀል ድርጊቶች መልካቸውንና ጸባያቸውን እየቀያየሩ እየተፈጸሙ ሲሆን በተለይም አንዳንድ ጊዜ በከተማችን የሚከሰቱ የሿሿና ሌሎች ወንጀሎች፤ በመሠል ሁኔታ የሚሠረቁ ሠሌዳዎችን በመጠቀም ስለሚሆን ህብረተሠቡ ተገቢውን ጥንቃቄ ከማድረግ ጀምሮ መረጃ የመስጠት ተግባሩን ማጠናከር እንዳለበት የአዲስ አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አሳስቧል።

@YeneTube @FikerAssefa
👍333😁1
“ የዲኤችኤል/DHL ሰራተኞች ነገ ወደ ስራ ይመለሳሉ፡፡ ለሰራተኞቹ የ 35 በመቶ የደመወዝ ጭማሪ ይደረጋል”


ባለፈው ሐሙስ ከአሰሪው ድርጅት ጋር ባለመግባባታቸው ስራ ያቆሙት የዲኤችኤል/DHL ሰራተኞች ስራ ማቆማቸውን ተከትሎ ከዛ በኋላ በተደረገ ድርድር የሰራተኛ ማህበሩና ድርጅቱ የ35% የደመወዝ ጭማሪ እንዲደረግላቸው ከስምምነት ላይ በመድረሳቸው በነገው ዕለት ወደ ስራ ይመለሳሉ።

@Yenetube @Fikerassefa
👍26
የጤና ባለሞያዎችን በማስታወቂያ ወደ ስራ መደባቸው እንዲገብ የተለያዩ ሆስፒታሎች ቢያስጠነቅቁም የጤና ባለሙያዎች አድማውን እንደሚቀጥሉ አንድ አንድ ያናገርናቸው ባለሙያዎች ተናግረዋል።

@Yenetube @Fikerassefa
👍44👎31
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
900,000 ብር ምን መግዛት ይችላል?

መኪና? ቤት?

በዚህ ጊዜ 900,000 ብር ምንም መግዛት አይችልም ።

እኛ ጋር ግን በ900,000 ብር ሱቅ መግዛት ትችላላችሁ ።

ያውም እስከ 200,000 ብር መከራየት የሚችል ሱቅ።

ፒያሳ አድዋ ዜሮ ዜሮ አጠገብ 20 ካሬ ሱቅ አየሸጥን ነው።

ከግራውንድ እስከ 5ኛ ፎቅ።

ለሁለት ሳምንት ብቻ የሚቆይ ዋጋ ነው።

ፈጥነው ይደውሉ!

ለበለጠ መረጃ  (Direct/ Whatsapp) ፦ በ
0909253426 / 0940407294 ይደውሉ
1👍1
🛒 BUYING OLD GROUPS 🛒

ድሮ የከፈታችሁት Group Chat ነበር? Owner ከሆናችሁ ፣ History Visible ከሆነ እና Chat Clear ካልተደረገ እንገዛችኋለን!

👥2023 - 🇪🇹 200 ETB

👥2022 - 🇪🇹400 ETB

👥2021 - 🇪🇹450 ETB

👥2020 & 2019 - 🇪🇹500 ETB

👥2018 & 2017 - 🇪🇹600 ETB

Payment Methods:
🇪🇹Telebirr, Bank
Proofs - https://www.tg-me.com/OLDGPPROOF

ሜምበር ለውጥ አያመጣም 1ሺ ሜምበርም ሆነ 10 ዋጋው አንድ ነው.. የተከፈተበት አመት ላይ ብቻ Chat ይኑረው።

ለመሸጥ: @OldGroupBuyer_APX
👍5
በ490,000 ቅድመ ክፍያ  በመሀል ካዛንቺስ  የቤት ባለቤት ይሁኑ ‼️

በጉጉት ሲጠበቅ የነበረው አያት ካዛንቺስ መንደር

እጅግ ውብ ዕይታ ያላቸው ቤቶች

ከ 1 መኝታ እስከ ባለ 4 መኝታ
👉ባለ አንድ መኝታ 45, 55 ,60 ካ.ሜ
👉ባለ ሁለት መኝታ  80,ካ.ሜ
👉ባለ ሶስት መኝታ  95,105,115 ካ.ሜ
👉ባለ አራት መኝታ  140  ,160 ካ.ሜ

✍️ ቅድመ ክፍያ 10%
📹 (ከ490,000ብር ቅድመ ክፍያ  ጀምሮ)

❇️  በ 18 ወራት የሚረከቡት ቤት💁

      

       📍በግቢው ዙሪያ

   ➾ፓርኮች ና የወንዝ ዳር ልማት
    ➾አለማቀፍ ት/ቤትና ሆስፒታል
    ➾የእምነት ተቋማ

       📍የቤቶቹ እይታ

    ➤ ወደ ቤተ መንግስት ( ጊቢ ገብርኤል )
    ➤ ወደ ያካ ተራራ ጫካ
    ➤ ወደ ወንዝ ዳር ልማት
    ➤ ወደ ወዳጅነት ፓርክ

👉 ቀድሞ ለመጣ ቅድሚያ ይስተናገዳል

❇️  ከሀገር ውጭ ያላችሁ ደንበኞች በወኪል መግዛት እንደምትችሉ እናሳውቃለን ።

ለምዝገባ 📲 0950123353 ወይም
በ whatsapp :-https://wa.me/251950123353
አሁኑ ይደውሉ
👍6
🟢 SAMSUNG M16 5G 🟢 (NEW)

✔️storage 128gb
✔️Ram 6gb
✔️Dual

💵Price 25,000 Birr

🔺🔺🔺🔺🔺🔺🔺🔺🔺🔺

😀 0942405669
✈️@Endalk4240

Join channel https://www.tg-me.com/phonestore_22
👍5
ከሴት መስተንግዶ ሠራተኞች አለባበስ ጋር በተያያዘ በአንድ ወር ውስጥ ከ35 በላይ ሆቴሎች የማስጠንቀቂያ ደብዳቤ ተሰጥቷቸዋል ተባለ!

በአዲስ አበባ ከተማ በአንድ ወር ጊዜ ውስጥ ብቻ ሴት የመስተንግዶ ሠራተኞች ሰውነታቸውን የሚያጋልጥ አለባበስ እንዲለብሱ የሚያስገድዱ ከ35 በላይ ሆቴሎች የማስጠንቀቂያ ደብዳቤ እንደተሰጣቸው የከተማ አስተዳደሩ ባህል፣ ኪነ-ጥበብ እና ቱሪዝም ቢሮ አስታውቋል።

በሆቴል አገልግሎት ሰጪ ተቋማት ውስጥ ተቀጥረው የሚያገለግሉ ሴት የመስተንግዶ ሠራተኞች አለባበስን የተመለከተ መመሪያ ጸድቆ ሥራ ላይ መዋሉ ይታወሳል።በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ባህል፣ ኪነ-ጥበብ እና ቱሪዝም ቢሮ የወጣው መመሪያ፤ ሴት የመስተንግዶ ሠራተኞች ሰውነታቸውን የሚያጋልጥ አለባበስ እንዲለብሱ የሚያስገድዱ አሰሪዎች ላይ ቅጣት የሚጥል ነው። 

ይህም የጸደቀው መመሪያ ተግባር ላይ ከመዋል የዘገየው የትርጉም ሥራዎች ባለመጠናቀቃቸው እንደሆነ፤ በቢሮው የቱሪስት አገልግሎት ብቃት ማረጋገጥ እና ደረጃ ምደባ ዳይሬክተር ገነት ይመር ለአሐዱ ተናግረዋል።በአሁን ሰዓት የትርጉም ሥራዎች መጠናቀቃቸውን የገለጹት ወ/ሮ ገነት፤ ለሆቴል አገልግሎት ሰጪዎቹ ከቅጣት በፊት ማስጠንቀቂያ እየተሰጠ እንደሚገኝ አስረድተዋል።

በዚህም ባለፈው አንድ ወር ውስጥ ብቻ 35 ሆቴሎች እና ሬስቶራንቶች የማስጠንቀቂያ ደብዳቤ እንደደረሳቸው ገልጸዋል።"ከቀጣዩ ሰኔ ወር ጀምሮ መመሪያው በሚያዘው መሠረት የቅጣት እርምጃ መውሰድ እንጀምራለን" ያሉት ኃላፊዋ፤ መረጃዎች ተጠናቅረው ሲቀርቡ ቁጥሩ ከዚህም ከፍ ሊል እንደሚችል ጠቁመዋል፡፡አክለውም፤ "ከማስጠንቀቂያው ጎን ለጎን የግንዛቤ ፈጠራ ሥራ ከወረዳ እስከ ክፍለ ከተማ እና ላይኛው መዋቅር ድረስ እየተሰጠ ይገኛል" ብለዋል።

Via Ahadu
@YeneTube  @FikerAssefa
👍464👎1
አትሌት ትግስት ግርማ ታሰረች!

አትሌት ትግስት ግርማ ከትናንት በስትያ በተጠናቀቀው የኢትዮጵያ አትሌትክስ ሻምፒዮና በ1500ሜ ክለቧን መቻልን በመወከል 2ኛ በመውጣት ውድድራን ያጠናቀቀችው የመቻል ስፖርት ከለብ አትሌት ትዕግስት ግርማ መታሰሯ ተሰምቷል።

አትሌቷ ለቶኪዮ የዓለም አትሌትክስ ሻፒዮና ሚኒማ ለማምጣት ወደ ኳታር ዶሃ ዳይመንድ ሊግ በማቅናት ላይ እያለች ነው በቦሌ አለማቀፍ አየር ማረፊያ ከክለቧ በተላለፈ ደብደቤ መሰረት እንደታሰረች ኢትዮ ራነርስ ገፅ አስነብቧል።

የአትሌቷ እስር ምክንያት ከዚህ በፊት ክለቧን ሳታስፈቅድ ወደ አውሮፓ ለውድድር በመሄዷ እንደሆነ ምንጮች ገልፀውልኛል ያለው ገፁ ሳታስፈቅድ ስለሄደችበት ምክንያት መጠየቁን አንስቷል።

ምንጩ ጥያቄ ሲመልሱም አትሌቷ አሰልጣኟን ጠይቃ በቃል እንደፈቀደላት ከውድድር ከተመለሰችም በኋላ ጉዳዩ እንደታየና እንደተፈታላት የገለፁ ሲሆን ከመፈታቱ በፊት በተላለፈ ደብዳቤ ምክንያት ሊሆን እንደሚችል ለኢትዮራነርስ ገልፀዋል።

ጉዳዩ የሚመለከታችሁ በሙሉ ከክለቧ ጋር በመነጋገርና ችግረሩን በመፍታት ለአትሌቷ መፍትሔ እንዲመጣና ወደ ውድድሯ እንድታቀና አስፈላጊውን ሁሉ ትብብር እንዲደረግላት በታላቅ አክብሮት እንጠይቃለን ብለዋል የአትሌቷ የቅርብ የሆኑ የመረጃ ምንጮች መግለፃቸውን ጠቁሟል።

via ኢትዮ ራነርስ
👍33😁144👀1
2025/07/10 17:16:23
Back to Top
HTML Embed Code: