በሱሉልታ ፍተሻ ጣቢያ አካባቢ በደረሰው የትራፊክ አደጋ የአራት ሰዎች ህይወት አለፈ
ዛሬ ሰኔ 19 ቀን 2017 ዓ.ም ከረፋዱ 4:50 ገደማ በጉለሌ ክፍለ-ከተማ ወረዳ 7
ሱሉልታ ፍተሻ ጣቢያ ከመድረሱ በፊት ባለዉ ቁልቁለት መንገድ ላይ በደረሰ የተሽከርካሪ አደጋ የአራት ሰዎች ህይወት ማለፉን የእሳትና አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን አስታውቋል።
አደጋው የደረሰው ከባድ ጭነት ጭኖ ይጓዝ የነበረ ከባድ ተሽከርካሪ የጫነዉ ጭነት ተሳፋሪ ጭኖ ወደ ሱሉልታ ይጓዝ በነበረዉ ሚኒባስ ተሽከርካሪ ላይ በመወደቁ መሆኑን የኮሚሽኑ የህዝብ ግንኙነት ባለሙያ አቶ ንጋቱ ማሞ ለብስራት ሬድዮ ተናግረዋል። በአደጋዉ በሚኒባስ ታክሲ ዉስጥ የነበሩ አራት ተሳፋሪዎች ህይወታቸዉ አልፏል።
የኮሚሽኑ የአደጋ ጊዜ ሰራተኞች ህይወታቸዉ ያለፈዉን ሰዎች ከአራት ሰዓታት ጥረት በኋላ አስከሬናቸውን ከተጫናቸዉ ጭነትና ከተሽከርካሪ ዉስጥ አዉጥተዉ ለፖሊስ አስረክበዋል።
የሟቾችን አስከሬን ለማዉጣት የኮሚሽኑ እና የአዲስ አበባ መንገዶች ባለስልጣን ክሬኖች ጥቅም ላይ የዋሉ ሲሆን በሂደቱም የአዲስ አበባ ፖሊስና ሌሎች የጸጥታ አመራርና አባላት ድጋፍ አድርገዋል።
በትግስት ላቀው
#ዳጉ_ጆርናል
ዛሬ ሰኔ 19 ቀን 2017 ዓ.ም ከረፋዱ 4:50 ገደማ በጉለሌ ክፍለ-ከተማ ወረዳ 7
ሱሉልታ ፍተሻ ጣቢያ ከመድረሱ በፊት ባለዉ ቁልቁለት መንገድ ላይ በደረሰ የተሽከርካሪ አደጋ የአራት ሰዎች ህይወት ማለፉን የእሳትና አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን አስታውቋል።
አደጋው የደረሰው ከባድ ጭነት ጭኖ ይጓዝ የነበረ ከባድ ተሽከርካሪ የጫነዉ ጭነት ተሳፋሪ ጭኖ ወደ ሱሉልታ ይጓዝ በነበረዉ ሚኒባስ ተሽከርካሪ ላይ በመወደቁ መሆኑን የኮሚሽኑ የህዝብ ግንኙነት ባለሙያ አቶ ንጋቱ ማሞ ለብስራት ሬድዮ ተናግረዋል። በአደጋዉ በሚኒባስ ታክሲ ዉስጥ የነበሩ አራት ተሳፋሪዎች ህይወታቸዉ አልፏል።
የኮሚሽኑ የአደጋ ጊዜ ሰራተኞች ህይወታቸዉ ያለፈዉን ሰዎች ከአራት ሰዓታት ጥረት በኋላ አስከሬናቸውን ከተጫናቸዉ ጭነትና ከተሽከርካሪ ዉስጥ አዉጥተዉ ለፖሊስ አስረክበዋል።
የሟቾችን አስከሬን ለማዉጣት የኮሚሽኑ እና የአዲስ አበባ መንገዶች ባለስልጣን ክሬኖች ጥቅም ላይ የዋሉ ሲሆን በሂደቱም የአዲስ አበባ ፖሊስና ሌሎች የጸጥታ አመራርና አባላት ድጋፍ አድርገዋል።
በትግስት ላቀው
#ዳጉ_ጆርናል
Forwarded from ዳጉ ጆርናል-ስፖርት (Beⓒk)
Breaking : አርሰናሎች ኤብሪቼ ኤዜን የዝዉዉር እቅዳቸዉ ዉስጥ እንዳስገቡት ቤን ጄኮብስ ዘግቧል። የ 68 ሚሊዮን ፓዉንድ ዉል ማፍረሻ ያለዉ ሲሆን ቶትንሃምም የተጨዋቹ ፈላጊዎች ናቸዉ።
ስካይ ስፖርት በአንጻሩ አርሰናል እና ኤዜ በግል ጉዳዮች መስማማታቸዉን ዘግቧል። ፓላስም በሶስት ጊዜ ተቆራርጦ የሚከፈል በየአመቱ 20 ሚሊዮን ፓዉንድ እና 8 ሚሊዮን ተጨማሪ ክፍያ ይፈልጋል። ተጨዋቹም ወደ አርሰናል ለመዘዋወር ግፊት እያደረገ ነዉ ብሏል።
አርሰናል የሮድሪጎንም ሁኔታ እየተከታተለ ሲሆን ተጨዋቹ ስለ ዝዉዉር ከማሰቡ በፊት በቅድሚያ ከዣቪ አሎንሶ ጋር ስለሚኖረዉ ቆይታ ማየት ይፈልጋል።
#ዳጉ_ጆርናል_ስፖርት
@Dagujournalsport
ስካይ ስፖርት በአንጻሩ አርሰናል እና ኤዜ በግል ጉዳዮች መስማማታቸዉን ዘግቧል። ፓላስም በሶስት ጊዜ ተቆራርጦ የሚከፈል በየአመቱ 20 ሚሊዮን ፓዉንድ እና 8 ሚሊዮን ተጨማሪ ክፍያ ይፈልጋል። ተጨዋቹም ወደ አርሰናል ለመዘዋወር ግፊት እያደረገ ነዉ ብሏል።
አርሰናል የሮድሪጎንም ሁኔታ እየተከታተለ ሲሆን ተጨዋቹ ስለ ዝዉዉር ከማሰቡ በፊት በቅድሚያ ከዣቪ አሎንሶ ጋር ስለሚኖረዉ ቆይታ ማየት ይፈልጋል።
#ዳጉ_ጆርናል_ስፖርት
@Dagujournalsport
በደቡብ ጎንደር ዞን የትራንስፖርት አገልሎት ለሶስት ቀናት በመቋረጡ ማህበረሰቡ ለእንግልት መዳረጉ ተገለፀ
በደቡብ ጎንደር ዞን እስቴ መካነ ኢየሱስ የትራንስፖርት አገልግሎት ሙሉ በሙሉ በመቋረጡ ህብረተሰቡ ለከፍተኛ እንግልት እየተጋለጠ መሆኑን የመካነ-ኢየሱስ ከተማ አስተዳደር ትራንስፖርት ተጠሪ ጽ/ቤት አስታውቋል።በዞኑ የኮሚኒኬሽን መምሪያ ሀላፊ አቶ እሱባለው መስፍን ለብስራት ሬድዮ እንደተናገሩት በአካባቢው የትራንስፓርት አገልግሎቱ ከተቋረጠ ዛሬ ሶስተኛ ቀኑን ይዟል።
በሁሉም አቅጣጫ ሙሉ በሙሉ የትራንስፖርት ሊቋረጥ የቻለው በፀጥታ ችግር እንደሆነ አቶ እሱባለው ጠቅሰው ይህም አሽከርካሪዎች ለከፍተኛ ድብደባ እንዲሁም ግድያ እና እንግልት መጋለጣቸውን ተናግረዋል።ባለሀብቶች በንብረታቸው ማዘዝና በገንዘባቸው መጠቀም፤ ነጋዴዎች ከቦታ ቦታ በመንቀሳቀስ ሸቀጣ ሸቀጥ ማቅረብ አለመቻላቸውም ተጠቅሷል።
በተጨማሪም የትራንስፖርት አገልግሎቱ በመቋረጡ የተነሳ ሰኔ 23/2017 ዓ.ም በሀገር አቀፍ ደረጃ የሚሰጠውን የ12ኛ ክፍል ፈተና ለማደናቀፍ ተማሪዎች ፈተናው ወደ ሚሰጥበት ማዕከል እንዳይሄዱ አሉታዊ ጫናን ፈጥሯል ተብሏል።አሁን ላይ ችግሩን ለመፍታት የከተማው አስተዳደርና የወረዳው አመራሮች ከባለሀብቶችና አሽከርካሪዎች ጋር ውይይት እያደረጉ እንደሚገኙ ተገልጿል።
ቅድስት ደጀኔ
#ዳጉ_ጆርናል
በደቡብ ጎንደር ዞን እስቴ መካነ ኢየሱስ የትራንስፖርት አገልግሎት ሙሉ በሙሉ በመቋረጡ ህብረተሰቡ ለከፍተኛ እንግልት እየተጋለጠ መሆኑን የመካነ-ኢየሱስ ከተማ አስተዳደር ትራንስፖርት ተጠሪ ጽ/ቤት አስታውቋል።በዞኑ የኮሚኒኬሽን መምሪያ ሀላፊ አቶ እሱባለው መስፍን ለብስራት ሬድዮ እንደተናገሩት በአካባቢው የትራንስፓርት አገልግሎቱ ከተቋረጠ ዛሬ ሶስተኛ ቀኑን ይዟል።
በሁሉም አቅጣጫ ሙሉ በሙሉ የትራንስፖርት ሊቋረጥ የቻለው በፀጥታ ችግር እንደሆነ አቶ እሱባለው ጠቅሰው ይህም አሽከርካሪዎች ለከፍተኛ ድብደባ እንዲሁም ግድያ እና እንግልት መጋለጣቸውን ተናግረዋል።ባለሀብቶች በንብረታቸው ማዘዝና በገንዘባቸው መጠቀም፤ ነጋዴዎች ከቦታ ቦታ በመንቀሳቀስ ሸቀጣ ሸቀጥ ማቅረብ አለመቻላቸውም ተጠቅሷል።
በተጨማሪም የትራንስፖርት አገልግሎቱ በመቋረጡ የተነሳ ሰኔ 23/2017 ዓ.ም በሀገር አቀፍ ደረጃ የሚሰጠውን የ12ኛ ክፍል ፈተና ለማደናቀፍ ተማሪዎች ፈተናው ወደ ሚሰጥበት ማዕከል እንዳይሄዱ አሉታዊ ጫናን ፈጥሯል ተብሏል።አሁን ላይ ችግሩን ለመፍታት የከተማው አስተዳደርና የወረዳው አመራሮች ከባለሀብቶችና አሽከርካሪዎች ጋር ውይይት እያደረጉ እንደሚገኙ ተገልጿል።
ቅድስት ደጀኔ
#ዳጉ_ጆርናል
የእስራኤል የደህንነት ሚኒስተር ለጋዛ የሚሰጠውን እርዳታ በሙሉ እንዲቋረጥ በድጋሚ ጥሪ አቀረቡ
የእስራኤል ብሄራዊ ደህንነት ሚኒስትር ኢታማር ቤን-ጊቪር "በአሁኑ ጊዜ ወደ ጋዛ እየገባ ያለው የሰብአዊ እርዳታ ፍጹም አሳፋሪ ነው" ብለዋል። “በተደጋጋሚ ባስጠነቀቅኩ ጊዜ እና በሚያሳዝን ሁኔታ ከአንድ ወር ተኩል በፊት እርዳታ እንዳይገባ ድምጽ የሰጠ ብቸኛው ሰው ሆኜ ለሃማስ የህይወት መስመር እንደሚሰጥ እርግጠኛ ነበርኩ” ሲሉ የቀኝ አክራሪውና እና ብዙ ጊዜ አነጋጋሪ አስተያየት በመስጠት የሚታወቁተወ ሚኒስትር በኤክስ ላይ ባሰፈሩት ጽሁፍ ተናግረዋል።
ቀጥሎም “በዚያን ጊዜ አንዳንዶች ‘እርዳታው ወደ ሰሜናዊው ሴክተር እና ለ10 ቀናት ብቻ ነው የሚሄደው’ ብለው ያፌዙብኝ ነበር፣ እናም ዛሬ ምን እየተፈጠረ እንደሆነ ግልፅ ነው። ሃማስ የምግብ እና የሸቀጦችን መጠን ይቆጣጠራል፣ ይህም ለህልውናው አስተዋጽኦ ያደርጋል ብለዋል።
"ዕርዳታውን ማቆም ድል ያፋጥናል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በሚቀጥለው የካቢኔ ስብሰባ ላይ ወደ ጋዛ በሚገባው ዕርዳታ ዙርያ እንደገና ድምፅ እንዲሰጥ እጠይቃለሁ " ሲሉ የእስራኤል የደህንነት ሚንስቴሩ ኢታማር ቤን ጊቨር ተናግረዋል።
በሚሊዮን ሙሴ
#ዳጉ_ጆርናል
የእስራኤል ብሄራዊ ደህንነት ሚኒስትር ኢታማር ቤን-ጊቪር "በአሁኑ ጊዜ ወደ ጋዛ እየገባ ያለው የሰብአዊ እርዳታ ፍጹም አሳፋሪ ነው" ብለዋል። “በተደጋጋሚ ባስጠነቀቅኩ ጊዜ እና በሚያሳዝን ሁኔታ ከአንድ ወር ተኩል በፊት እርዳታ እንዳይገባ ድምጽ የሰጠ ብቸኛው ሰው ሆኜ ለሃማስ የህይወት መስመር እንደሚሰጥ እርግጠኛ ነበርኩ” ሲሉ የቀኝ አክራሪውና እና ብዙ ጊዜ አነጋጋሪ አስተያየት በመስጠት የሚታወቁተወ ሚኒስትር በኤክስ ላይ ባሰፈሩት ጽሁፍ ተናግረዋል።
ቀጥሎም “በዚያን ጊዜ አንዳንዶች ‘እርዳታው ወደ ሰሜናዊው ሴክተር እና ለ10 ቀናት ብቻ ነው የሚሄደው’ ብለው ያፌዙብኝ ነበር፣ እናም ዛሬ ምን እየተፈጠረ እንደሆነ ግልፅ ነው። ሃማስ የምግብ እና የሸቀጦችን መጠን ይቆጣጠራል፣ ይህም ለህልውናው አስተዋጽኦ ያደርጋል ብለዋል።
"ዕርዳታውን ማቆም ድል ያፋጥናል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በሚቀጥለው የካቢኔ ስብሰባ ላይ ወደ ጋዛ በሚገባው ዕርዳታ ዙርያ እንደገና ድምፅ እንዲሰጥ እጠይቃለሁ " ሲሉ የእስራኤል የደህንነት ሚንስቴሩ ኢታማር ቤን ጊቨር ተናግረዋል።
በሚሊዮን ሙሴ
#ዳጉ_ጆርናል
ደሞዝ አልከፈልከኝም በሚል ምክንያት አሰሪውን የገደለው በእስራት ተቀጣ
ተከሳሹ ጌቱ መስፍን ይባላል፤ የወንጀል ድርጊቱን የፈፀመው ነሀሴ 27 ቀን 2014 ዓ/ም ከረፋዱ 4 ሰዓት ከ30 ሲሆን በቂርቆስ ክፍለ ከተማ ወረዳ 10 ለገሃር ተብሎ ከሚጠራው አካባቢ ኖህ ሪል ስቴት ከሚያሰራው ህንፃ 16ኛ ጅምር ፎቅ ላይ ነው።
ሟች ሀጂብ ያሲን የተባለው ግለሰብ ከኖህ ሪል እስቴት ኮንትራት በመውሰድ ከስሩ በርካታ ሰራተኞችን ቀጥሮ የሚያሰራ ግለሰብ ነው።
ሟች የዘወትር ስራውን ለማሰራት ሰራተኞችን ወደ የስራቸው ያሰማራል። ተከሳሽም ሟች የነበረበት ቦታ ጭር ማለቱን እና ማንም አለመኖሩን እንደ ጥሩ አጋጣሚ በመውሰድ ደሞዜን ከለከልከኝ በሚል ምክንያት በተፈጠረ አለመግባባት ሟች ሀጂብ ያሲንን ስራ እየሰራ ባለበት 16ኛ ፎቅ ላይ በፌሮ ብረት ግንባሩን በመምታት እና አንገቱን በሽቦ ገመድ በማነቅና በማሰር ህይወቱ እንዲያልፍ በማድረግ ሟችን ከህንፃው ተሸክሞ በማውረድ የህንፃው መሰረት ስር የሚገኝ የተጠራቀመ ውሃ ውስጥ አስከሬኑን በመጣል ከአካባቢው ይሰወራል።
የወንጀሉ መፈፀም ሪፖርት የደረሰው ፖሊስ የምርመራ ክፍሉና የክትትልና ኦፕሬሽን ቡድኑ በመዋቀርና በመቀናጀት ወንጀል ፈፃሚውን ለመያዝ በተደረገ ጥረት ተከሳሽ ጌቱ መስፍን ወንጀሉን ከፈፀመ በኋላ ምንም እንዳልተፈፀመ በኔጌሌ ቦረና ከተማ በአንድ ተቋም ውስጥ ተቀጥሮ በመስራት ላይ እንዳለ በቁጥጥር ስር ሊውል መቻሉን የአዲስ አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ ገልጿል።
በተከሳሽ ጌቱ መስፍን ላይ የምርመራ መዝገቡን በሰውና በሰነድ ማስረጃ በማጠናከር ለሚመለከተው የፍትህ አካል በመላክ ክስ እንደተመሰረተበት የገለፀው የአዲስ አበባ ፖሊስ ተከሳሽ ጌቱ ጥፋተኛ ሆኖ በማግኘቱ የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ ወንጀል ችሎት በ21 አመት ፅኑ እስራት እንዲቀጣ እንደተወሰነበት ገልጿል።
ማንም ሰው ወንጀል ፈፅሞ ከህግ እና ከማህበረሰቡ ማምለጥ እንደማይቻል የአዲስ አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ ጠቅሶ ያለመግባባት በሚፈጠርበት ወቅት በመነጋገር መፍታት ይገባል ሲል መልዕክቱን አስተላልፏል።
#ዳጉ_ጆርናል
ተከሳሹ ጌቱ መስፍን ይባላል፤ የወንጀል ድርጊቱን የፈፀመው ነሀሴ 27 ቀን 2014 ዓ/ም ከረፋዱ 4 ሰዓት ከ30 ሲሆን በቂርቆስ ክፍለ ከተማ ወረዳ 10 ለገሃር ተብሎ ከሚጠራው አካባቢ ኖህ ሪል ስቴት ከሚያሰራው ህንፃ 16ኛ ጅምር ፎቅ ላይ ነው።
ሟች ሀጂብ ያሲን የተባለው ግለሰብ ከኖህ ሪል እስቴት ኮንትራት በመውሰድ ከስሩ በርካታ ሰራተኞችን ቀጥሮ የሚያሰራ ግለሰብ ነው።
ሟች የዘወትር ስራውን ለማሰራት ሰራተኞችን ወደ የስራቸው ያሰማራል። ተከሳሽም ሟች የነበረበት ቦታ ጭር ማለቱን እና ማንም አለመኖሩን እንደ ጥሩ አጋጣሚ በመውሰድ ደሞዜን ከለከልከኝ በሚል ምክንያት በተፈጠረ አለመግባባት ሟች ሀጂብ ያሲንን ስራ እየሰራ ባለበት 16ኛ ፎቅ ላይ በፌሮ ብረት ግንባሩን በመምታት እና አንገቱን በሽቦ ገመድ በማነቅና በማሰር ህይወቱ እንዲያልፍ በማድረግ ሟችን ከህንፃው ተሸክሞ በማውረድ የህንፃው መሰረት ስር የሚገኝ የተጠራቀመ ውሃ ውስጥ አስከሬኑን በመጣል ከአካባቢው ይሰወራል።
የወንጀሉ መፈፀም ሪፖርት የደረሰው ፖሊስ የምርመራ ክፍሉና የክትትልና ኦፕሬሽን ቡድኑ በመዋቀርና በመቀናጀት ወንጀል ፈፃሚውን ለመያዝ በተደረገ ጥረት ተከሳሽ ጌቱ መስፍን ወንጀሉን ከፈፀመ በኋላ ምንም እንዳልተፈፀመ በኔጌሌ ቦረና ከተማ በአንድ ተቋም ውስጥ ተቀጥሮ በመስራት ላይ እንዳለ በቁጥጥር ስር ሊውል መቻሉን የአዲስ አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ ገልጿል።
በተከሳሽ ጌቱ መስፍን ላይ የምርመራ መዝገቡን በሰውና በሰነድ ማስረጃ በማጠናከር ለሚመለከተው የፍትህ አካል በመላክ ክስ እንደተመሰረተበት የገለፀው የአዲስ አበባ ፖሊስ ተከሳሽ ጌቱ ጥፋተኛ ሆኖ በማግኘቱ የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ ወንጀል ችሎት በ21 አመት ፅኑ እስራት እንዲቀጣ እንደተወሰነበት ገልጿል።
ማንም ሰው ወንጀል ፈፅሞ ከህግ እና ከማህበረሰቡ ማምለጥ እንደማይቻል የአዲስ አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ ጠቅሶ ያለመግባባት በሚፈጠርበት ወቅት በመነጋገር መፍታት ይገባል ሲል መልዕክቱን አስተላልፏል።
#ዳጉ_ጆርናል
Forwarded from ዳጉ ጆርናል-ስፖርት (Beⓒk)
የአሜሪካ ፖሊስ በክለቦች የአለም ዋንጫ ዉድድር ጥበቃ ለሚጠቀማቸዉ ዉሾች ጫማ መጠቀም ጀመረ
የአሜሪካ ፖሊስ በስራዎቹ ለሚያግዙትን የሰለጠኑ ዉሾች ጫማ መጠቀም ጀመሯል። የአሜሪካ ፖሊስ በክለቦች የለም ዋንጫ የጸጥታ ስራዉ ነዉ ዉሾቹን የሚጠቀመዉ።
ፖሊስ ለዉሾቹ ጫማ መጠቀም የጀመረዉ በሀገሪቱ በአሁኑ ሰዓት ካለዉ ከፍተኛ ሙቀት የተነሳ መሆኑ ተዘግቧል። በክለቦች የአለም ዋንጫ ተጨዋቾች ያለዉን ሙቀት መቋቋም ሲያቅታቸዉ ተመልክተናል።
ለአብነት ከትናንትና በስቲያ ቦሩሲያ ዶርትሙንድ ከኡልሳን ጋር ባደረገዉ ጨዋታ የአየር ንብረቱ ወይም ሙቀቱ ከ 42 ሴንቲግሬድ በላይ ነበር።
በተቀያሪ ወንበር ላይ የሚቀመጡ ተጨዋቾችም ሙቀቱን መቋቋም አቅቷቸዉ በመልበሻ ክፍል ጨዋታዉን በቴሌቪዥን ሲከታተሉ በተደጋጋሚ ተመልክተናል።
የአሜሪካ የአሁኑ የአየር ንብረት ሁኔታ በቀጣይ አመት ሀገሪቱ ከካናዳ እና ሜክሲኮ ጋር በጋራ በምታዘጋጀው የሀገራት የአለም ዋንጫ ዉድድር ላይ ጥላ እንዳያጠላ ተሰግቷል።
በበረከት ሞገስ
#ዳጉ_ጆርናል_ስፖርት
@Dagujournalsport
የአሜሪካ ፖሊስ በስራዎቹ ለሚያግዙትን የሰለጠኑ ዉሾች ጫማ መጠቀም ጀመሯል። የአሜሪካ ፖሊስ በክለቦች የለም ዋንጫ የጸጥታ ስራዉ ነዉ ዉሾቹን የሚጠቀመዉ።
ፖሊስ ለዉሾቹ ጫማ መጠቀም የጀመረዉ በሀገሪቱ በአሁኑ ሰዓት ካለዉ ከፍተኛ ሙቀት የተነሳ መሆኑ ተዘግቧል። በክለቦች የአለም ዋንጫ ተጨዋቾች ያለዉን ሙቀት መቋቋም ሲያቅታቸዉ ተመልክተናል።
ለአብነት ከትናንትና በስቲያ ቦሩሲያ ዶርትሙንድ ከኡልሳን ጋር ባደረገዉ ጨዋታ የአየር ንብረቱ ወይም ሙቀቱ ከ 42 ሴንቲግሬድ በላይ ነበር።
በተቀያሪ ወንበር ላይ የሚቀመጡ ተጨዋቾችም ሙቀቱን መቋቋም አቅቷቸዉ በመልበሻ ክፍል ጨዋታዉን በቴሌቪዥን ሲከታተሉ በተደጋጋሚ ተመልክተናል።
የአሜሪካ የአሁኑ የአየር ንብረት ሁኔታ በቀጣይ አመት ሀገሪቱ ከካናዳ እና ሜክሲኮ ጋር በጋራ በምታዘጋጀው የሀገራት የአለም ዋንጫ ዉድድር ላይ ጥላ እንዳያጠላ ተሰግቷል።
በበረከት ሞገስ
#ዳጉ_ጆርናል_ስፖርት
@Dagujournalsport
በአረብ ሀገራት የሚገኙት አብዛኛዎቹ አቦሸማኔዎች በህገወጥ መልኩ ከኢትዮጵያ የተወሰዱ ናቸው ተባለ
በኢትዮጵያ የዱር እንስሳት ሀብት ላይ ከተደቀኑ በርካታ ችግሮች መካከል ህገወጥ የእንስሳት ዝውውር አንዱ መሆኑን የኢትዮጵያ የዱር እንስሳት ጥበቃ ባለስልጣን አስታውቋል።በባለስልጣኑ የዱር እንስሳት ህገወጥ ዝውውር ቁጥጥር ከፍተኛ ባለሙያ የሆኑት አቶ ዳንኤል ጳውሎስ ለብስራት ሬድዮ እንደተናገሩት ለተለያዩ አላማዎች ሲባል በኢትዮጵያ የሚገኙ የዱር እንስሳት ከነህይወታቸው በህገወጥ መንገድ ይዘዋወራሉ።
በዚህ መልኩ ከሀገር የሚወጡ እንስሳቶች በርካታ ቢሆኑም በቀዳሚነት አቦሸማኔ ይጠቀሳል ። አቦሸማኔ በተለይም በምስራቁ የኢትዮጵያ ክፍል በሱማሌ ክልል መኖሪያውን በማድረጉ የአካባቢው ማህበረሰቦች ባካበቱት ተፈጥሮአዊ ዘዴ የአቦሸማኔ ቡችላዎችን በመያዝ ሶማሌላንድ አካባቢ ለሽያጭ እንደሚያቀርቡ ተጠቁሟል።
በዚህ መልኩ ይህ እንስሳ ወደ መካከለኛው የአረብ ሀገራት ጭምር ላሉ ባለሀብቶች የሚሸጥበት ሁኔታ መኖሩን የገለፁት አቶ ዳንኤል ግለሰቦቹ የራሳቸው የሆነ መካነ አራዊት ስላላቸው እንስሳቱን የመግዛት ፍላጎታቸው ከፍተኛ መሆኑን አብራርተዋል።ወደ መካከለኛው ምስራቅ የአረብ ሀገራት የሚገኙት አቦ ሸማኔዎችም ከአፍሪካ ቀንድ በተለይም ከኢትዮጵያ የተወሰዱ ስለመሆናቸው መረጃዎች ይጠቁማሉ ሲሉ ባለሙያው ጨምረው ለጣቢያችን ተናግረዋል።
አቦሸማኔን ጨምሮ ሌሎች እንስሳትን ከህገወጥ ዝውውር ለመታደግና ኢትዮጵያ ከእንስሳት ሀብቷ ተጠቃሚ እንድትሆን አሁን ላይ በአነፍናፊ ውሾች የታገዘ የቁጥጥር ስራ እየተከናወነ ይገኛል ተብሏል።
ቅድስት ደጀኔ
#ዳጉ_ጆርናል
በኢትዮጵያ የዱር እንስሳት ሀብት ላይ ከተደቀኑ በርካታ ችግሮች መካከል ህገወጥ የእንስሳት ዝውውር አንዱ መሆኑን የኢትዮጵያ የዱር እንስሳት ጥበቃ ባለስልጣን አስታውቋል።በባለስልጣኑ የዱር እንስሳት ህገወጥ ዝውውር ቁጥጥር ከፍተኛ ባለሙያ የሆኑት አቶ ዳንኤል ጳውሎስ ለብስራት ሬድዮ እንደተናገሩት ለተለያዩ አላማዎች ሲባል በኢትዮጵያ የሚገኙ የዱር እንስሳት ከነህይወታቸው በህገወጥ መንገድ ይዘዋወራሉ።
በዚህ መልኩ ከሀገር የሚወጡ እንስሳቶች በርካታ ቢሆኑም በቀዳሚነት አቦሸማኔ ይጠቀሳል ። አቦሸማኔ በተለይም በምስራቁ የኢትዮጵያ ክፍል በሱማሌ ክልል መኖሪያውን በማድረጉ የአካባቢው ማህበረሰቦች ባካበቱት ተፈጥሮአዊ ዘዴ የአቦሸማኔ ቡችላዎችን በመያዝ ሶማሌላንድ አካባቢ ለሽያጭ እንደሚያቀርቡ ተጠቁሟል።
በዚህ መልኩ ይህ እንስሳ ወደ መካከለኛው የአረብ ሀገራት ጭምር ላሉ ባለሀብቶች የሚሸጥበት ሁኔታ መኖሩን የገለፁት አቶ ዳንኤል ግለሰቦቹ የራሳቸው የሆነ መካነ አራዊት ስላላቸው እንስሳቱን የመግዛት ፍላጎታቸው ከፍተኛ መሆኑን አብራርተዋል።ወደ መካከለኛው ምስራቅ የአረብ ሀገራት የሚገኙት አቦ ሸማኔዎችም ከአፍሪካ ቀንድ በተለይም ከኢትዮጵያ የተወሰዱ ስለመሆናቸው መረጃዎች ይጠቁማሉ ሲሉ ባለሙያው ጨምረው ለጣቢያችን ተናግረዋል።
አቦሸማኔን ጨምሮ ሌሎች እንስሳትን ከህገወጥ ዝውውር ለመታደግና ኢትዮጵያ ከእንስሳት ሀብቷ ተጠቃሚ እንድትሆን አሁን ላይ በአነፍናፊ ውሾች የታገዘ የቁጥጥር ስራ እየተከናወነ ይገኛል ተብሏል።
ቅድስት ደጀኔ
#ዳጉ_ጆርናል
በኢራን የስለላ ድርጅት ውስጥ ይሰራል ተብሎ የተጠረጠረ ወጣት በእስራኤል በቁጥጥር ስር ዋለ
በሰሜን እስራኤል ከሚገኘው ከዴር አል አሳድ የመጣው የ22 ዓመት ተማሪ ኢራንን ወክሎ ተልእኮዎችን በማከናወን ክስ ሊመሰረትበት እንደሚችል ፖሊስ እና የሀገሪቱን የሺን ቤት የደህንነት አገልግሎትን ጠቅሶ ሃሬትዝ ዘግቧል።
ባሻር ሀሰን ቃሲም ሙሳ በደቡብ እስራኤል በቤር ሼቫ በማዕከላዊ ግዛት ላይ የመንገድ የተለያዩ ተቀጣጣይ ነገሮችን ካስቀመጠ እና ሰው ለመጉዳት ከሞከረ በኋላ ለኢራን የስለላ ስራ በመስራት ተጠርጥሮ በዚህ ወር መጀመሪያ ላይ በቁጥጥር ስር መዋሉን የእስራኤሉ ጋዜጣ ዘግቧል። ነግር ግን ሺን ቤት የሙሳን ኢላማ ማንነት ግልፅ አለመሆኑን ሃሬትዝ አክሏል።
በሌላ መረጃ
በሚሊዮን ሙሴ
#ዳጉ_ጆርናል
በሰሜን እስራኤል ከሚገኘው ከዴር አል አሳድ የመጣው የ22 ዓመት ተማሪ ኢራንን ወክሎ ተልእኮዎችን በማከናወን ክስ ሊመሰረትበት እንደሚችል ፖሊስ እና የሀገሪቱን የሺን ቤት የደህንነት አገልግሎትን ጠቅሶ ሃሬትዝ ዘግቧል።
ባሻር ሀሰን ቃሲም ሙሳ በደቡብ እስራኤል በቤር ሼቫ በማዕከላዊ ግዛት ላይ የመንገድ የተለያዩ ተቀጣጣይ ነገሮችን ካስቀመጠ እና ሰው ለመጉዳት ከሞከረ በኋላ ለኢራን የስለላ ስራ በመስራት ተጠርጥሮ በዚህ ወር መጀመሪያ ላይ በቁጥጥር ስር መዋሉን የእስራኤሉ ጋዜጣ ዘግቧል። ነግር ግን ሺን ቤት የሙሳን ኢላማ ማንነት ግልፅ አለመሆኑን ሃሬትዝ አክሏል።
በሌላ መረጃ
የእስራኤልጦር በዮርዳኖስ ሸለቆ አካባቢ የጦር ልምምዱን ከሀሙስ ከጠዋት ጀምሮ እስከ ከሰአት በኋላ እንደሚደረግ ገልጿል። በልምምድ ወቅት በአካባቢው ከፍተኛ የወታደራዊ ተሽከርካሪዎች እንቅስቃሴ እንደሚኖርም አክሏል። ልምምዱ እስራኤል በአሜሪካ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ አደራዳሪነት ከኢራን ጋር የተኩስ አቁም ስምምነት ከጀመረች ከቀናት በኋላ ነው።
በሚሊዮን ሙሴ
#ዳጉ_ጆርናል