Telegram Web Link
🕊መንግሥተ ሰማያት ቀርባለችና ንስኅ ግቡ🕊
(ማቴ ፫:፫)

በአማን ተንሥአ መድኃኒነ!
🌿ብፁዕ አባ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ዘኤለ ገዳማተ እምኀበ እግዚኡ ይነሣእ እሴተ ቦአ ሀገረ ደብረ ሊባኖስ በፍሥሐ ወበሰላም።

ሰአል ለነ ጊዮርጊስ ኀበ እግዚአብሔር ወጸሊ በእንቲአነ ሐረድዎ ወገመድዎ ወዘረዉ ሥጋሁ ከመ ሐመድ ወወሰድዎ ኀበ ሰብአ ነገሥት ረገጸ ምድረ አንሥአ ሙታነ አባ ጊዮርጊስ በሰላም ዐደወ መንግሥተ ክብር ወረሰ።

🌿ወልደ እግዚአብሔር አምላክነ ወመድኃኒነ ዕቀብ  ሕይወተነ እም ገሀነመ እሳት ወእምኵሉ መንሱት በእንተ ቅዱስ ስምከ ወበእንተ ማርያም እምከ ወበእንተ ቅዱስ መስቀል ወበእንተ ዮሐንስ ወንጌላዊ ወበእንተ ዮሐንስ መጥምቅከ ወበእንተ ኵሎሙ ቅዱሳን ወሀባ ሰላመ ለሀገሪትነ ኢትዮጵያ ወለቅድስት ቤተክርስቲያን።

ሰላም ለክሙ ጻድቃን ወሰማዕት እለ አዕረፍክሙ በዛቲ ዕለት መዋዕያነ ዓለም አንትሙ በብዙኅ ትዕግሥት። ሰአሉ ቅድመ ፈጣሪ በኩሉ ሰዓት እንበለ ንስሐ ኪያነ ኢይንሣእ ሞት።

🌿አንቅሐኒ በጽባሕ ክሥተኒ ዕዝንየ በዘአጸምእ አምላኪየ አምላኪየ እገይሥ ኀቤከ ዘይሰማዕ ግበር ሊተ ምሕረተከ በጽባሕ"

ነቢያት ወሐዋርያት፥ ጻድቃን ወሰማዕት፤ ደናግል ወመነኮሳት፥ አዕሩግ ወሕጻናት፤ ገዳማውያን ወሊቃውንት፤ ሰአሉ ለነ ኲልክሙ፥ ቅድመ መንበሩ ለጸባኦት።

🌿እግዝእትየ ፍትሕኒ እማዕሠሩ ለሰይጣን፤
እሙ ለመድኅን ወለተ ብርሃን።

ዝክረ ቅዱሳን ማኅበረ ቅዱስ ዳዊት ጉባኤ ዘጎንደር

🌿ፍቅር ያጌብረኒ ከመ እንግር ዜናሆሙ ለቅዱሳን! (የቅዱሳንን ታሪክ እንድመሰክር ፍቅር ያስገድደኛል)
🌿አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ (መጽሐፈ ምሥጢር)

🔗https://www.tg-me.com/zikirekdusn
▶️https://www.youtube.com/@ZikereKedusan
ታላቁ ነቢይ ቅዱስ እንባቆም

"እግዚኦ ሰማዕኩ ድምጸከ ወፈራህኩ::
ርኢኩ ግብረከ ወአንከርኩ . . . " (ዕን. 3:1)

☞ግንቦት24 ዕረፍቱ፡ ቅዳሴ ቤቱም ነው፡፡

ከአረጋዊው ነቢይ በረከት አምላኩ አይለየን::


ዝክረ ቅዱሳን ማኅበረ ቅዱስ ዳዊት

🌿ፍቅር ያጌብረኒ ከመ እንግር ዜናሆሙ ለቅዱሳን! (የቅዱሳንን ታሪክ እንድመሰክር ፍቅር ያስገድደኛል)
🌿አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ (መጽሐፈ ምሥጢር)
🔗https://www.tg-me.com/zikirekdusn
▶️https://www.youtube.com/@ZikereKedusan
እናታችን ቅድስት ዮሐና

☞ጌታን ለ3 ዓመታት ያገለገለች:: (ሉቃ. ፰:፪)
☞ከሕማሙ ያልተለየች::
☞ከመስቀሉ እግር የተገኘች::
☞ትንሳኤውን ተመልክታ የሰበከች::
☞በዘመነ ሐዋርያትም ስመ ጥር የነበረች ቡርክት እናት ናት:: (ሉቃ. 24:10)
☞ግንቦት24 ዓመታዊ በዓሏ ነው::

☞እናታችን ቅድስት ዮሐና ከ36ቱ ቅዱሳት አንስት አንዷ ናት፡፡

✿በረከቷ በዝቶ ይደርብን፡፡✿


ዝክረ ቅዱሳን ማኅበረ ቅዱስ ዳዊት

🌿ፍቅር ያጌብረኒ ከመ እንግር ዜናሆሙ ለቅዱሳን! (የቅዱሳንን ታሪክ እንድመሰክር ፍቅር ያስገድደኛል)
🌿አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ (መጽሐፈ ምሥጢር)

🔗https://www.tg-me.com/zikirekdusn
▶️https://www.youtube.com/@ZikereKedusan
እንኳን አደረሰነ!

☞ወርኀ ግንቦት ቡሩክ፤ አመ ፳ወ፬፦

ርደቱ ለእግዚእነ ኢየሱስ ክርስቶስ፥ ውስተ ምድረ ግብጽ
ተዝካረ ጻማ ንግደታ፥ ለእግዝእትነ ማርያም (እሙ ለመድኅን)
በዓለ አስተርእዮታ ለእግዝእትነ ማርያም ድንግል፥ ወላዲተ አምላክ
ቅድስት ደብረ ምጥማቅ (ሐመረ ብርሃን)

✞ወበዓለ ቅዱሳን፦

✿ዮሐና ቅድስት ወቡርክት፥ ብእሲተ ኩዛ (ዘተልእከቶ ለመድኀኒነ በንዋያ)
✿አልዓዛር ካህን (ወልደ አሮን ካህን)
✿ዐቢይ ነቢይ ዕንባቆም (አረጋዊ ጠቢብ)
✿ዮሴፍ አረጋዊ፥ ወሰሎሜ ብጽዕት
✿አብቁልታ ቀሲስ ወሰማዕት (ዐቃቤ ሥራይ)
✿አክሌድስ፥ ወቴፍላስ፥ ወማርዮ

❖ወስብሐት ለእግዚአብሔር፤
ኪያነኒ ይምሐረነ በጸሎቶሙ።
ወበረከቶሙ ይብጽሐነ፤ ለዓለመ ዓለም አሜን፡፡

https://www.tg-me.com/zikirekdusn
እንኳን ለእናታችን ቅድስት ሰሎሜ ዓመታዊ የዕረፍት በዓል እና ለበዓለ ቅዱስ ሜሮን በሰላም አደረሳችሁ

+"+ ቅድስት ሰሎሜ +"+

=>የክብር ባለቤት መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በመዋዕለ ስብከቱ ከመረጣቸው 36ቱ ቅዱሳት አንስት የቅድስት ሰሎሜን ያሕል ያገለገለ: ክብርም የተቀበለ የለም:: ከእመቤታችን ቀጥሎ ከጽንሰቱ እስከ ዕርገቱ ያልተለየች ብቸኛዋ ሰው ናትና::

+ይሕስ እንደ ምን ነው ቢሉ:- ቅድስት ሰሎሜ ከነገደ አሮን በሚመዘዝ የዘር ሐረግ እናቷ ማርያም ትባል ነበር:: አባቷ ደግሞ ክቡር አረጋዊ ቅዱስ ዮሴፍ ነው:: ቅድስት ሰሎሜና እመቤታችን የእህትማማች ልጆች ናቸው::

+ቅድስት ኤልሳቤጥም ዝምድናዋ ተመሳሳይ ነው:: የ3ቱ እናቶች (ሐና: ማርያምና ሶፍያ) የማጣትና የሔርሜላ ልጆች በመሆናቸው እህታማቾች ናቸው::

+<< ጥቂት ነገሮች ስለ እናታችን ቅድስት ሰሎሜ >>+
1.የአረጋዊ ዮሴፍ ልጆችን (ወንድሞቿን) እንደሚገባ አሳድጋለች::

2.ጌታችን በተወለደ ጊዜ በቤተ ልሔም ነበረች:: የእመቤታችን መውለድ እንደ ሌሎች ሴቶች መስሏት ድንግልን ስለ ነካች እጆቿ ተቃጥለዋል:: ምሕረት ጠይቃ ጌታን ስትዳስሰው ግን ተፈወሰች::

3.እመ ብርሃን ስደት ስትወጣ ቅድስት ሰሎሜ "ባንቺ የደረሰ በኔም ይድረስ" ብላት አብራ ተሰዳለች:: ረሐቧን ተርባለች:: ጥሟን ተጠምታለች:: በሐዘኗ አዝናለች:: አብራት አልቅሳለች:: ለ3 ዓመታት ከ6 ወራት ያን ሁሉ ጭንቅ አብራ ተካፍላለች::
+ድንግል እመቤታችን እሾህ ሲወጋት ታወጣላት: እንቅፋት ሲመታት ደሟን ትጠርግላት ነበር:: ባለቤቱ አድሏታልና ጌታችንን አንዴ በጎኗ ታቅፈው: አንዴም በጀርባዋ ታዝለው: አንዳንዴም ትስመው ነበር::

<< መለኮትን ማቀፍ: ማዘልና መሳም ምን ይደንቅ! ለቅድስት እናታችን አንክሮና ምስጋና በጸጋ ይገባል! >>

+ከስደት ከተመለሱ በሁዋላም ለ25 ዓመታት ከጌታና ከድንግል ማርያም ጋር ኑራለች: አገልግላቸዋለችም::
+ጌታችን ተጠምቆ ማስተማር ሲጀምርም ተከተለችው:: እርሱም ከ36ቱ ቅዱሳት አንስት ደምሯታል:: ለ3 ዓመታት ከ6 ወራት ከዋለበት ውላ: ካደረበት አድራ ተምራለች:: እንደሚገባም አገልግላለች::

+አምላክ ሲሰቃይ ከጐኑ: ሲሰቀልም ከእግረ መስቀሉ ነበረች:: ብርሃነ ትንሳኤውም ከተገለጠላቸው ቅዱሳት አንስት አንዷ ናት:: ከመድኃኔ ዓለም ዕርገት በሁዋላ መንፈስ ቅዱስን ተቀብላ በሐዋርያት ዘመን የነበረችውን ቤተ ክርስቲያን አገልግላለች::

+እድሜዋ ምን ቢገፋ ለወንጌልና ለማዕድ ተግባር ተግታለች:: ወገኖቿ አይሁድ ብዙ አሰቃይተዋት በዚህች ዕለት በመልካም ዕረፍት ወደ ፈጣሪዋ ሔዳለች::

+"+ ቅብዐ ሜሮን +"+

=>ዳግመኛ በዚሕ ቀን ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እኛ የምንከብርበትን ቅብዐ ሜሮን አፍልቆልናል::

+በስደቱ ጊዜ ጌታችን በምድረ ግብፅ ደክሟቸው ካረፉበት ቦታ ላይ የዮሴፍ በትርን ቆራርጦ: በኪነ ጥበቡ ውሃ አፍልቆ: አጠጥቶ: ትልልቅ ዛፎች አደረጋቸው:: እዛውም ላይ ቅብዐ ሜሮንን አፈለቀ:: ቅብዐ በለሶንም ይሏቸዋል::
+በሁዋላም የጌታችን ወዙ በታጠበ ጊዜ ተቀላቅሎበታል:: ዛሬ እኛም: ንዋየ ቅድሳትም የምንከብረው በዚሁ ቅዱስ ቅብዐት ነው::

=>አምላካችን እግዚአብሔር በቅድስት ሰሎሜ ላይ ያሳደረውን ጸጋ በእኛም ላይ ያሳድርልን::

=>ግንቦት 25 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት=
1.እናታችን ቅድስት ሰሎሜ (ከ36ቱ ቅዱሳት አንስት)
2.ታላቁ አባ ሔሮዳ ሰማዕት
3."30,000" ሰማዕታት (የአባ ሔሮዳ ማሕበር)
4.ቅዱስ አብቁልታ ሰማዕት
5.ቅዱስ ቅብዐ ሜሮን

=>ወርሐዊ በዓላት
1.ቅዱስ መርቆሬዎስ ሰማዕት
2.ቅድስት ቴክላ ሐዋርያዊት
3.ቅዱስ አበከረዙን ሰማዕት
4.ቅዱስ ዱማድዮስ ሶርያዊ
5.አቡነ አቢብ (አባ ቡላ)
6.ቅዱስ አባ አቡፋና ጻድቅ

=>+"+ ሰንበትም ካለፈ በሁዋላ መግደላዊት ማርያም: የያዕቆብም እናት ማርያም: ሰሎሜም መጥተው ሊቀቡት ሽቱ ገዙ:: ከሳምንቱም በፊተኛው ቀን እጅግ በማለዳ ፀሐይ ከወጣ በሁዋላ ወደ መቃብር መጡ . . . ወደ መቃብርም ገብተው ነጭ ልብስ የተጐናጸፈ ጐልማሳ በቀኝ በኩል አዩና ደነገጡ:: እርሱ ግን አትደንግጡ የተሰቀለውን የናዝሬቱን ኢየሱስን ትፈልጋላችሁ:: ተነስቷል: በዚህ የለም . . . አላቸው:: +"+ (ማር. 16:1-8)

<<< ወስብሐት ለእግዚአብሔር >>>
Memhir Esuendale:
#Feasts of #Ginbot_25

✞✞✞On this day we commemorate the Departure of our Mother Saint Salome and hold the Feast of the Oil of Chrism (The Holy Myron)✞✞✞

✞✞✞In the name of the Father, the Son and the Holy Spirit, one God. Amen!✞✞✞

✞✞✞Saint Salome✞✞✞
=> There is none from the 36 Holy Women whom our Savior Jesus Christ, during His ministry, chose that served or received an honor as St. Salome. After our Lady, she was the only person that did not depart from the Lord starting from His conception to His ascension.

✞ And if asked how that came to be, it was as follows. St. Salome’s mother was called Mary, and she descended from the House of Aaron, while her father was the Honorable St. Joseph the Elder (the Betrothed). St. Salome and our Lady were daughters of sisters (cousins).

✞ And St. Elisabeth also had the same kind of kinship. The mothers of the three (Hannah, Mary, and Sophia) were sisters as they were the daughters of Matthat and Hermela.

✞✞✞Some things about our Mother St. Salome✞✞✞
1. She did raise the sons of Joseph the Elder (her brothers) properly.
2. When our Lord was born, she was in Bethlehem. And because she thought the birth - our Lady gave - was like that of other women, and she touched her, her hands were charred. And because she asked for forgiveness and came in contact with the Lord, she was healed.
3. When the Mother of Light fled, she took flight also with her saying, “Whatever happens unto you, let it also happen unto me.” Hence, she thirsted with our Lady, anguished because of her sorrow, and wept with the Theotokos. Accordingly, she partook in her suffering for three years and six months.

✞ When thorns pierced our Lady, she used to remove them for her. And when stumbling blocks injured her, she used to clean her blood. And because the Lord had allowed her, she also used to hold Him on her side, carry Him sometimes on her back, and kiss Him at other times.

✞How wondrous is it to hold, carry, and kiss the Divine! Honor and praise are worthy to our holy mother!

✞And after they returned from their flight, she lived with and served the Lord and the Virgin Mary for 25 years.

✞ Then she followed our Lord after His baptism when He started preaching. And He added her to the 36 Holy Women. And she spent the days and the nights where He did and learned for three years and six months. And she served accordingly.

✞ And during the Passion of our Lord, she was by His side. And at His crucifixion, she was at the Cross. And she was one of the women to whom the Light of His Resurrection was revealed. And after the ascent of the Holy Savior, and she received the Holy Spirit, she served the Church, which was at the time of the Apostles.
✞And though her age had advanced, she was diligent in the service of the Gospel and the table. And after enduring many trials from her kinsfolk, the Jews, she departed in peace to her Creator on this day.

✞✞✞The Holy Myron✞✞✞
=>Also on this day, our Lord Jesus Christ brought forth for us the Holy Ointment – Myron by which we are anointed.

✞ During the flight of our Lord, in a place where they rested from their exhaustion in Egypt, He took the rod of Joseph, cut it into different pieces, brought about a spring of water through His wisdom, watered [them], and made them into big mature trees. And there, He had the Ointment of the Myron, also called the Ointment of the Balsam, spring forth.

✞Later, when our Lord’s sweat was washed, it was added to it. And today, this Holy Ointment anoints/sanctifies the Holy Vessels and us.

✞✞✞May our God also place in us the grace which He indwelt in St. Salome.

✞✞✞ Annual feasts celebrated on the 25th of Ginbot
1. Our Mother St. Salome (One of the 36 Holy Women)
2. The Great Abba Heroda the Martyr
3. The 30,000 Martyrs (The Followers of Abba Heroda)
4. St. Cotylus/ Colluthus the Martyr of Antinoe
5. The Holy Ointment – Myron (Chrism)
✞✞✞ Monthly Feasts
1. St. Mercurius the Martyr
2. St. Thecla the Apostolic
3. St. Abakragoun the Martyr
4. St. Domadius El-Souriani (The Syrian)
5. Abune Abib (Abba Bula)
6. St. Abba Abu Fana the Righteous

✞✞✞ “And when the sabbath was past, Mary Magdalene, and Mary the mother of James, and Salome, had bought sweet spices, that they might come and anoint him. And very early in the morning the first day of the week, they came unto the sepulchre at the rising of the sun. . .And entering into the sepulchre, they saw a young man sitting on the right side, clothed in a long white garment; and they were affrighted. And he saith unto them, Be not affrighted: Ye seek Jesus of Nazareth, which was crucified: he is risen; he is not here”✞✞✞
Mark 16:1-6

✞✞✞ Salutations to God ✞✞✞

(Translated by Mhr. Esuendale Shemeles with the permission of Dn. Yordanos Abebe)
🕊መንግሥተ ሰማያት ቀርባለችና ንስኅ ግቡ🕊
(ማቴ ፫:፫)

በአማን ተንሥአ መድኃኒነ!
🌿ብፁዕ አባ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ዘኤለ ገዳማተ እምኀበ እግዚኡ ይነሣእ እሴተ ቦአ ሀገረ ደብረ ሊባኖስ በፍሥሐ ወበሰላም።

ሰአል ለነ ጊዮርጊስ ኀበ እግዚአብሔር ወጸሊ በእንቲአነ ሐረድዎ ወገመድዎ ወዘረዉ ሥጋሁ ከመ ሐመድ ወወሰድዎ ኀበ ሰብአ ነገሥት ረገጸ ምድረ አንሥአ ሙታነ አባ ጊዮርጊስ በሰላም ዐደወ መንግሥተ ክብር ወረሰ።

🌿ወልደ እግዚአብሔር አምላክነ ወመድኃኒነ ዕቀብ  ሕይወተነ እም ገሀነመ እሳት ወእምኵሉ መንሱት በእንተ ቅዱስ ስምከ ወበእንተ ማርያም እምከ ወበእንተ ቅዱስ መስቀል ወበእንተ ዮሐንስ ወንጌላዊ ወበእንተ ዮሐንስ መጥምቅከ ወበእንተ ኵሎሙ ቅዱሳን ወሀባ ሰላመ ለሀገሪትነ ኢትዮጵያ ወለቅድስት ቤተክርስቲያን።

ሰላም ለክሙ ጻድቃን ወሰማዕት እለ አዕረፍክሙ በዛቲ ዕለት መዋዕያነ ዓለም አንትሙ በብዙኅ ትዕግሥት። ሰአሉ ቅድመ ፈጣሪ በኩሉ ሰዓት እንበለ ንስሐ ኪያነ ኢይንሣእ ሞት።

🌿አንቅሐኒ በጽባሕ ክሥተኒ ዕዝንየ በዘአጸምእ አምላኪየ አምላኪየ እገይሥ ኀቤከ ዘይሰማዕ ግበር ሊተ ምሕረተከ በጽባሕ"

ነቢያት ወሐዋርያት፥ ጻድቃን ወሰማዕት፤ ደናግል ወመነኮሳት፥ አዕሩግ ወሕጻናት፤ ገዳማውያን ወሊቃውንት፤ ሰአሉ ለነ ኲልክሙ፥ ቅድመ መንበሩ ለጸባኦት።

🌿እግዝእትየ ፍትሕኒ እማዕሠሩ ለሰይጣን፤
እሙ ለመድኅን ወለተ ብርሃን።

ዝክረ ቅዱሳን ማኅበረ ቅዱስ ዳዊት ጉባኤ ዘጎንደር

🌿ፍቅር ያጌብረኒ ከመ እንግር ዜናሆሙ ለቅዱሳን! (የቅዱሳንን ታሪክ እንድመሰክር ፍቅር ያስገድደኛል)
🌿አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ (መጽሐፈ ምሥጢር)

🔗https://www.tg-me.com/zikirekdusn
▶️https://www.youtube.com/@ZikereKedusan
አቡነ ሕፃን ሞዐ


ግንቦት 25 በዓለ ፅንሰታቸው።

በረከታቸው ይደርብን።

ዝክረ ቅዱሳን ማኅበረ ቅዱስ ዳዊት ጉባኤ ዘጎንደር
'
" ፍቅር ያጌብረኒ ከመ እንግር ዜናሆሙ ለቅዱሳን"::/የቅዱሳንን ዜና(ታሪክ) እንድመሰክር ፍቅር ያስገድደኛል::  አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ /መጽሐፈ ምሥጢር/

https://www.tg-me.com/zikirekdusn
ስንት ኦርቶዶክሳዊ ተረፈልን . . .?

☞ማዕተብ ካሠረው 50-60? ሚሊየን፦

➊ከእግዚአብሔር ይልቅ ለራሱ አመለካከት የሚገዛ፤
➋በተለያየ ሱስ የታሠረ፤
➌ሥጋ ወደሙን ከሕጻንነቱ በቀር የማያውቅ፤
➍ስለ ቅድስና (ክርስትና) ተግባራዊ ሕይወትን ያላወቀ፤
➎ቤተ ክርስቲያን በመንገድ መሳለም (ብቻውን) እንደሚያጸድቀው የሚያስብ፤
➏ንስሃ መግባት ይቅርና የነፍስ አባት የሌለው፤
➐እኖራለሁ እንጂ እሞታለሁን (ኩነኔን) ያልፈራ . . .

ብለን ስናስበው፥ እውነቱን ተረድቶ ትክክለኛ ክርስቲያን የሆነ ስንት ኦርቶዶክሳዊ ይቀረናል . . .?

☞ከዚህ ተርፎ ወደ ደጁ የመጣውን ደግሞ፦

•አጥማቂ
•"ባሕታውያን"
•"ሰባኪ"
•"ዘማሪ"
•"Artist"
•ቀላጤ (Activist)
•ካድሬ፥ ጸሐፊ ፥ ለጣፊ፥ . . . ነን የሚሉ ዘርፈው ተከታይ አድርገውታል!

°ከእግዚአብሔር ይልቅ የነርሱን ድምጽ ይማል!
°ከቤተክርስቲያን ይልቅ ለነርሱ ክብር ጥብቅናን ያስቀድማል!

"እስመ በልዕዎ ለያዕቆብ" (መዝ. ፸፰)
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በታሪኳ እንዲህ የተዋረደችበት፥ ቅድስና እንኳን ግብሩ ስሙ የተረሳበት ጊዜ መኖሩን እጠራጠራለሁ፡፡
ጊዜው ደግሞ እንዳያያዛችን ታሪካዊ እጥፋት ላይ አድርሶናል፤
ከታላቁ ውርደት የመጨረሻ አፋፍ ላይም አቁሞናል።
በዚህ መንገድ መጨረሻን "ነበረ" ተብሎ በታሪክ እንደሚነገርላቸው አብያተክርስቲያናት እንዳያደርሰን ያስፈራል፡፡
አውቃለሁ፤ "ሐሳቡ" በራሱ ትልቅ ርዕስ ሆኖ አይሰማን ይሆናል፤
ከግል፥ ከቤተዘመድ፥ ከጓደኛ፥ ከጎሳና ከፖለቲካ ጉዳይ በላይ ገዝፎ ላያስጨንቀንም ይችላል፡፡ ግን እውነቱን መካድ አይቻለንም።
"አኃዊነ ምንተ ንግበር፤ ወንድሞቻችን ሆይ፥ ምን እናድርግ?" (ሐዋ. ፪:፴፯)
@Re DnYordanosAbebe
https://www.tg-me.com/zikirekdusn
ቅብዐ ሜሮን

በዚሕ ቀን ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እኛ የምንከብርበትን ቅብዐ ሜሮን አፍልቆልናል::

+በስደቱ ጊዜ ጌታችን በምድረ ግብፅ ደክሟቸው ካረፉበት ቦታ ላይ የዮሴፍ በትርን ቆራርጦ: በኪነ ጥበቡ ውሃ አፍልቆ: አጠጥቶ: ትልልቅ ዛፎች አደረጋቸው:: እዛውም ላይ ቅብዐ ሜሮንን አፈለቀ:: ቅብዐ በለሶንም ይሏቸዋል::
+በሁዋላም የጌታችን ወዙ በታጠበ ጊዜ ተቀላቅሎበታል:: ዛሬ እኛም: ንዋየ ቅድሳትም የምንከብረው በዚሁ ቅዱስ ቅብዐት ነው::

https://www.tg-me.com/zikirekdusn
እንኳን አደረሰነ!

☞ወርኀ ግንቦት ቡሩክ፤ አመ ፳ወ፭፦

ተዝካረ ተአምር ዘገብረ እግዚእነ ኢየሱስ ክርስቶስ፥ ውስተ ምድረ ግብጽ
ተዝካረ ጻማ ንግደታ፥ ለእግዝእትነ ማርያም (እሙ ለመድኅን)
በዓለ አስተርእዮታ ለእግዝእትነ ማርያም ድንግል፥ ወላዲተ አምላክ
ቅድስት ደብረ ምጥማቅ (ሐመረ ብርሃን)

✞ወበዓለ ቅዱሳን፦

✿ሰሎሜ ቅድስት ወብጽዕት (ሐጻኒቱ ለመድኀኒነ ክርስቶስ)
✿ዮሴፍ አረጋዊ ትሩፍ (ወጻድቅ)
✿አባ ኄሮዳ ሰማዕት (ዘሃገረ ስብስጣ)
✿፫ቱ ፼ ሰማዕታት (ማኅበራኒሁ)
✿ኮጦሎስ ሰማዕት (ዘሃገረ እንዴናው)
✿በላኖስ ወእሎንትራን ወራምኔሳ
✿ሕጻን ሞዐ ጻድቅ (ዘደብረ በግዕ)
✿፻ ወ፶ ሰማዕታት
✿ቆስጠንጢኖስ ወእሙ ሔላ
✿በዓለ ቅብዐ ሜሮን (ቅብዐ በለሳ/ሶን)

❖ወስብሐት ለእግዚአብሔር፤
ኪያነኒ ይምሐረነ በጸሎቶሙ።
ወበረከቶሙ ይብጽሐነ፤ ለዓለመ ዓለም አሜን፡፡

https://www.tg-me.com/zikirekdusn
2025/07/09 15:50:07
Back to Top
HTML Embed Code: